ru
Feedback
ማራናታ.....MARANATHA😍

ማራናታ.....MARANATHA😍

Открыть в Telegram

ለአንዳንዶች የሚዘገይ እንደምመስላቸው ጌታ ሰለ ተስፋ ቃሉ አይዘገይም፥ ነገር ግን ሁሉ ወደ ንስሐ እንድደርሱ እንጅ ማንም እንዳይጠፋ ወዶ ሰለ እናንተ ይታገሳል።2ኛ ጴጥ 3፥9 ገና በጣም ጥቅት ጊዜ ነው፤ ሊመጣ ያለውም ይመጣል አይዘገይምም። ዕብራ 10፥37 የመወያያ ግሩፕ👇 @Marantawoch Inbox Comment @Thaddyapostolic

Больше

📈 Аналитический обзор Telegram-канала ማራናታ.....MARANATHA😍

Канал ማራናታ.....MARANATHA😍 (@maranathawoch) языкового сегмента Амхарский является активным участником. Сейчас сообщество объединяет 16 517 подписчиков, занимая 5 170 место в категории Религия и духовность и 2 034 место в регионе Эфиопия.

📊 Показатели аудитории и динамика

С момента создания невідомо проект демонстрирует стремительный рост, собрав аудиторию из 16 517 подписчиков.

Согласно последним данным от 14 июня, 2026, канал показывает стабильную активность. За последние 30 дней изменение числа участников составило 195, а за последние 24 часа — 8, при этом общий охват остаётся высоким.

  • Статус верификации: Не верифицирован
  • Уровень вовлечённости (ER): Средний показатель вовлечённости аудитории составляет 16.19%. В первые 24 часа после публикации контент обычно набирает 7.98% реакций от общего числа подписчиков.
  • Охват публикаций: В среднем каждый пост получает 2 672 просмотров. В течение первых суток публикация набирает 1 316 просмотров.
  • Реакции и взаимодействия: Аудитория активно поддерживает контент: среднее количество реакций на один пост — 26.

📝 Описание и контентная политика

Автор описывает ресурс как площадку для выражения субъективного мнения:
ለአንዳንዶች የሚዘገይ እንደምመስላቸው ጌታ ሰለ ተስፋ ቃሉ አይዘገይም፥ ነገር ግን ሁሉ ወደ ንስሐ እንድደርሱ እንጅ ማንም እንዳይጠፋ ወዶ ሰለ እናንተ ይታገሳል።2ኛ ጴጥ 3፥9 ገና በጣም ጥቅት ጊዜ ነው፤ ሊመጣ ያለውም ይመጣል አይዘገይምም። ዕብራ 10፥37 የመወያያ ግሩፕ👇 @Marantawoch Inbox Comment @Thaddyapostolic

Благодаря высокой частоте обновлений (последние данные получены 15 июня, 2026) канал поддерживает актуальность и высокий уровень охвата публикаций. Аналитика показывает, что аудитория активно взаимодействует с контентом, что делает его важной точкой влияния в категории Религия и духовность.

16 517
Подписчики
+824 часа
+1467 дней
+19530 день
Архив постов
singer:meseret kejela Title:ጥሶ የሚያስጉዝ ሀይል location : merkato salem atbya
ጥሶ የሚያስጉዝ ሀይል ልቤ ይናፍቃል ሰማያት ይከፈቱ ይውረድ እጥፍ እሳቱ የረከሰው እንዲፈወስ እጥፍ ይውረድ ያንተ መንፈስ ተቀብለን ፀጋ ሚበልጥ እንውጣ ሀይልህም ይገለጥ 1)ቀንበርን የሚሰብር ሃጥያትን የሚያስጥል(የሚያስክድ) ላንተ መኖር የሚያስችል ሀይልህ እጥፍ ይውረድ እንለይ ላንተ ክብር እንቀመም በእሳት ጠላትን እያስፈራን እንኑር የክብር ህይወት 2)ጥቂት ዘመን እንዳለው ጠላት ይህንን አውቆ በታላቅ ቁጣ ቢወርድ ቢነሳ እጅግ ታጥቆ ሁሉን የሚበልጥ ፀጋ ማሸንፍያ ቅባት ይውረድ ታላቁ መብረቅ የመንፈስህ እሳት  ጠላት ይፍራ ይደንግጥ አይቶ እንዳለን በእሳት ውስጥ የድል ህይወት የድል መንገድ እንድንጓዝ ሀይልህ ይውረድ ይውረድ እሳትህ ይውረድ *3 ይውረድ መንፈስህ ይውረድ *3 3) ቅዱስ ስምህ ይጠራ ፈውስ ይሁን ታምራት ጠላታችን ይንቀጥቀጥ ይርበድበድ ባንተ ፉት በስምህ ከጠራህው ከታላቅ ህዝብ ጋር ውጣ የኛ አምላክ የሱስ ልዩነት ይፈጠር ጠላት ይፍራ.... 3) ዛሬም ቅዱስ መንፈስ በብርቱ እንፈልጋለን ያልተለማመድነውን  ፀጋ ይዞ ይምጣልን ሰማያት ይከፈቱ ድንቁ ክብር ይታይ(ሙሉ) ፍጥረት ወድቀው ይስገዱ ንገስ በሁሉ ላይ

✍️ቅድስና ለእግዚአብሔር !
◉  ቅዱሳን ወገኖች፦ ቅድስና ለእግዚአብሔር መለየት ፤ ብልቶቻችንን የፅድቅ እቃ ጦር አርጎ ማቅረብ ሲሆን መቼም የማንደራደርበት ጉዳይ ሊሆን ይገባል። ክርስትና እንደ ልባችን አሳብና ፈቃድ እየዋልን እያደርን የምንመላለስበት ህይወት አይደለም !  ዳግመኛ ስንወለድ እርሱን ልንመስል እሱም ህይወታችንን በሞቱና በትንሳኤው ከለወጠ በኋላ በምድር የምንኖረው ኑሮ  ስለ እኛ ለሞተውና ለተነሳው መሆን እንዳለበት  አስተምሮናል!  ሐዋርያ ጳውሎስ  "ከክርስቶስ ጋር ተሰቅያለሁ እኔም አሁን ህያው ሆኜ አልኖርም ክርስቶስ ግን በእኔ ይኖራል! በስጋም የምኖረው ህይወት በክርስቶስ ላይ ባለኝ እምነት የምኖረው ነው!" እንዳለው ◉  እርሱን እንድንመስል ተጠርተናል፦ ክርስትና በማስመሰልና በግብዝነት በውጭ መልክ የሚኖር ህይወት አይደለም !ልንኖረው ግድ ይላል!!የእግዚአብሔር መንግስት ጉዳይ ነውና!!። ሞቱን በሚመስል ሞት  አሮጌውን  ሰው ሰቅለን ትንሳኤውን በሚመስል ትንሳኤ ደግሞ በአዲስ ህይወት ልንመላለስ ይገባል!!! እንዴትስ ደግመን በሀጥያት ባርነት እንያዛለን?  ከሀጥያት በታች  እየኖርን እንዴት ክርስቲያን (የእግዚአብሔር ቤተሰብ )እንባላለን ??፤ የተቀበልነው መንፈስ የፍቅር ራስን የመግዛት መንፈስ እንጂ የፍርሃት መንፈስ አይደለምና! ◉ እንዴት ራሳችንን እንግዛ ? እንዴትስ በብርሀን እንመላለስ? " ነገር ግን እላለሁ፥ በመንፈስ ተመላለሱ፥ የሥጋንም ምኞት ከቶ አትፈጽሙ። ሥጋ በመንፈስ ላይ መንፈስም በሥጋ ላይ ይመኛልና፥ እነዚህም እርስ በርሳቸው ይቀዋወማሉ፤ ስለዚህም የምትወዱትን ልታደርጉ አትችሉም።                  ገላ5፥16-17 ይሄ ጥቅስ የሚነግረን "መንፈሳችንን በስጋችን ላይ ማሰልጠን እንዳለብን ያሳየናል"  ስጋ በመንፈስ ላይ መንፈስም በስጋ ላይ ይቀዋወማሉ! በክርስቶስ ዳግም ተወልዶ አዲስ ፍጥረት በሆነው ማንነታችንና(መንፈሳችን) ላይ ባልተለወጠውና ፣ አለምን በሚሻው ( በወደቀው ማንነታችን )መሀል ከፍተኛ መቀዋወምና ጦርነት አለ። እኛም በይበልጥ የመገብነው  በርሱ ቁጥጥር ስር ያደርገናል !!የመገብነው አይሎ ይሰለጥንብናል!! ወገኖች በህይወታችን ማን አይሏል???? መልሱን ለእናንተ ትቸዋለሁ!! እንዲሁ የወደቀው ማንነታችን እንዳለ ሆኖ ፥  ሰይጣን በሚሰለጥንበትና በወደቀ አለም ስለምንኖር ልንመስላቸው ስለሚስቡን ነው!  ሐዋርያ ጳውሎስ  ጢሞቲዮስን "እግዚአብሔርን ለመምሰል ራስህን አስለምድ"  ይለዋል። ልክ ሰውነትን ለማጎልበትና ለመጠንከር የተመጣጠነ ምግብ መመገብ እና ተገቢ ስፖርት መስራት ግዴታ እንደሆነ ፥  እግዚአብሔርን ለመምሰልም መንፈሳዊ Exercise እንዲሰራ ያዘዋል። ይህ ነው እንግዲህ እግዚአብሔርን ለመምሰል መለማመድ!!በቅድስና ለመኖር መንፈሳችንን በመመገብ በስጋችን ላይ እንዲሰለጥን ማድረግ ..... መንፈስን መመገብ ►  መንፈሳችንን የምንመግበው የመጀመሪያው  ምግብ የእግዚአብሔርን ቃል ነው!  “ኢየሱስም፦ ሰው በእግዚአብሔር ቃል ሁሉ እንጂ በእንጀራ ብቻ አይኖርም ተብሎ ተጽፎአል”                ሉቃስ 4፥4 ቃሉን  ማንበብ ወሳኙ ነገር ሆኖ ሳለ ፥  ይህን ቃል እስኪዋሀደንና የራሳችን እስኪሆን ድረስ ማሰላሰል ደግሞ ቀጣዩ ቁልፍ ጉዳይ ነው! በዚህ ላይ ብዙዎች የሚስቱት  ማንበቡን ያነቡትና ማሰላሰሉ (meditation) ላይ የሉበትም! ቃሉ ደግሞ በማሰላሰል በኩል መንፈሳችንን እንዲቆጣጠር እስካላረግነው ድረስ ጠቀሜታ አይኖረውም! ልክ ምግብ ተመግበን የተመገብነው ምግብ ተፈጭቶ የሚዋሀደው  በDigestive system እንደሆነው ሁሉ ቃሉን አንብበን የሚዋሀደን ደግሞ በተደጋጋሚ ስናሰላስለው ነው! ስንወጣ ስንገባ ፤  በምልልሳችን ሁሉ ማሰላሰል ግድ ይለናል። “እጆቼንም ወደ ወደድኋቸው ወደ ትእዛዛትህ አነሣለሁ፤ ሥርዓትህንም አሰላስላሁ።”            መዝ 119፥48 ►  ሌላኛው የመንፈስ ምግብ ፀሎት ነው! ፀሎት የክርስቲያን አማራጭ የሌለው ህይወቱ መሆን አለበት። ቢደክም ቢበረታ በየትኛውም ሁኔታዎች ውስጥ ከእግዚአብሔር ጋር የጠበቀ ህብረት ሊኖረው ያስፈልገዋል። ፀሎት ማለት፦ ከእግዚአብሔር ጋር መነጋገር ፤ ህብረት ማድረግ ነው። ይህም ሰአት ገድበንለት የምናደርገው ሳይሆን ዘወትር መንፈሳችንን ከእርሱ መንፈስ ጋር የምናገናኝበት የሰማይ ደጅ ነው!! ስንወጣ  ፤ ስንሄድ ፤ ስራ ስንሰራ ብንጸልይ....  መንፈሳችን ይጠነክራል ፤ ስጋ የምንጎስምበት አቅም ይሰጠናል።  ክፋትን እያሰብን ፤ ሰዎችን እያማን ፤ ለማያንጹን ቃላት ጆሮአችንን እየሰጠን ከአንድበታችንም እያወጣን  ውለን  የምንፀልየው ፀሎት ትርጉም ይኖረዋልን? ►  ሌላኛው የመንፈስ ምግብ በቤተክርስቲያን ውስጥ ህብረት ማድረግና ማገልገል ነው። “በሐዋርያትም ትምህርትና በኅብረት እንጀራውንም በመቍረስ በየጸሎቱም ይተጉ ነበር።”                     ሐዋ 2፥42 ቅዱሳን የክርስቶስ አካል  እንደመሆናችንና ክርስቶስም የኛ ራስ እንደመሆኑ እንደ  አካል መስራት መንቀሳቀስ አለብን።  እርስ በእርስ መተሳሰብ፣ መተናነፅ ፣ መያያዝ  ፣ መደጋገፍ አካሉን ያሳድጋል! በቀረውስ ወገኖቼ እስቲ በዚህ ሚዛን እንመዘን?!የት ጋር ነን?ኑሮችን እንዴት ነው?  ለርሱ  እየኖርንለት ነው? ጨክን እንቀደስ ፥ የተሻለ ህይወት ይሁንልን! እነሆ በደጅ ቆሟል!!! ለእውነት እንነሳ !እርሱን ለመምሰል ራሳችንን እናስለምድ ክብራችን ነውና!!! በእለት ተእለት ህይወታችን ይህን በማሰላሰልና በማድረግ በቅድስና ለእግዚአብሔር መኖር እንችላለን!!                    “እኛም ሁላችን በመጋረጃ በማይከደን ፊት የጌታን ክብር እንደ መስተዋት እያብለጨለጭን መንፈስ ከሚሆን ጌታ እንደሚደረግ ያን መልክ እንመስል ዘንድ ከክብር ወደ ክብር እንለወጣለን።”                         2ኛ ቆሮ 3፥18@MARANATHAWOCH @MARANATHAWOCH

🔥🔥መንፈስ ቅድስ🔥🔥 መንፈስ ቅድስ ከእግዚአብሔር የምንቀበለው ሃይል ነው ። የእግዚአብሔርን ስራ መስራት የምንችለው በመንፈስ ቅድስ ሃይል አማካኝነት ነው። 👉👉 በመንፈሴ እንጂ በኃይልና በብርታት አይደለም፥ ይላል የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር። " (ትንቢተ ዘካርያስ 4:6) የተመረጡ ሐዋርያቶች ሃይል እስኪቀበሉ ደረስ በኢየሩሳሌም ቆዩ እኛም ሃይልን እስክንቀበል ድረስ በትግስት መጠበቅ አለብን 🔥መንፈስ ቅድስ ለመሞላት መጠማት አለብን ። 👉👉" እኔ ከምሰጠው ውኃ የሚጠጣ ሁሉ ግን ለዘላለም አይጠማም፥ እኔ የምሰጠው ውኃ በእርሱ ውስጥ ለዘላለም ሕይወት የሚፈልቅ የውኃ ምንጭ ይሆናል እንጂ አላት።" (የዮሐንስ ወንጌል 4:14) መንፈስ ቅድስ እለት እለት እደምናገኝው ውሃና ምግብ ነው አንድ ሰው ካልተመገበ ሀይል አይኖረውም እንዲሁም አንድ መንፈሳዊ ሰው የመንፈስ ቅድስ ሃይል ካላገኝ መንፈሳዊ ሕይወቱ እየደከመ ይሄዳል ስለዚ ሁሌም መራብና መጠማት ተገቢ ነው። 👉👉የማቴዎስ ወንጌል 5 3፤ በመንፈስ ድሆች የሆኑ ብፁዓን ናቸው፥ መንግሥተ ሰማያት የእነርሱ ናትና። 4፤ የሚያዝኑ ብፁዓን ናቸው፥ መፅናናትን ያገኛሉና። 5፤ የዋሆች ብፁዓን ናቸው፥ ምድርን ይወርሳሉና። 6፤ ጽድቅን የሚራቡና የሚጠሙ ብፁዓን ናቸው፥ ይጠግባሉና። ስለዚ ደሀ መሆን መራብ መጠማት ተገቢ ነው ። አንድ ሰው ደሃ ከሆነ የሚያሰበው ለመስራት ለመለወጥ ሌላው እንዲረዳው መጠየቅ መቀበልን ሁሌም የሚያስበው ። በመንፈስም ደሃ ስንሆን ሁሌም እንጠይቃለን ለመቀበል እንጓጓለን ሁሌም ሰማይ ሰማይን እንናፍቃለን 🔥ለመቀበል 👉መለመን ስንለምን መቼም ቢሆን አምነን እንጂ በጥርጣሬ መሆን የለበትም። 👉👉" ሁለት አሳብ ላለው በመንገዱም ሁሉ ለሚወላውል ለዚያ ሰው ከጌታ ዘንድ አንዳች እንዲያገኝ አይምሰለው።" (የያዕቆብ መልእክት 1:7-8) 🔥በእምነት እንጠይቅ 👉👉" እንኪያስ እናንተ ክፉዎች ስትሆኑ ለልጆቻችሁ መልካም ስጦታ መስጠት ካወቃችሁ፥ በሰማይ ያለው አባት ለሚለምኑት እንዴት አብልጦ መንፈስ ቅዱስን ይሰጣቸው?" (የሉቃስ ወንጌል 11:13) 👉👉" የሚለምን ሁሉ ይቀበላልና፥ የሚፈልግም ያገኛል፥ መዝጊያውንም ለሚያንኳኳው ይከፈትለታል።" (የሉቃስ ወንጌል 11:10) 🔥ስለዚ ስንለምን እንደሚሰጠን መሆን አለበት። ምክንያቱም 👉👉" እግዚአብሔር ይላል። በመጨረሻው ቀን እንዲህ ይሆናል፤ ሥጋ በለበሰ ሁሉ ላይ ከመንፈሴ አፈሳለሁ፤ ወንዶችና ሴቶች ልጆቻችሁም ትንቢት ይናገራሉ፥ ጎበዞቻችሁም ራእይ ያያሉ፥ ሽማግሌዎቻችሁም ሕልም ያልማሉ፤" (የሐዋርያት ሥራ 2:17) ይህ የሚሆነው ስናምን ነው ለመሞላት ስንፈቅድ ነው ። 👉👉" እናንተ የተጠማችሁ ሁሉ፥ ወደ ውኃ ኑ፥ ገንዘብም የሌላችሁ ኑና ግዙ ብሉም፤ ኑ ያለ ገንዘብም ያለ ዋጋም የወይን ጠጅና ወተት ግዙ። " (ትንቢተ ኢሳይያስ 55:1) ወደ እግዚአብሔር መምጣት ተገቢ ነው ። ✍✍የኢየሱስ ወገን ለመሆን መንፈስ ቅድስ ወሳኝ ነው ። " እናንተ ግን የእግዚአብሔር መንፈስ በእናንተ ዘንድ ቢኖር፥ በመንፈስ እንጂ በሥጋ አይደላችሁም። የክርስቶስ መንፈስ የሌለው ከሆነ ግን ይኸው የእርሱ ወገን አይደለም።" (ወደ ሮሜ ሰዎች 8:9) 🔥መንፈስ ቅድስ የእርስታችን መያዢያ ነው ። 👉👉 " እናንተም ደግሞ የእውነትን ቃል፥ ይኸውም የመዳናችሁን ወንጌል፥ ሰምታችሁ ደግሞም በክርስቶስ አምናችሁ፥ በተስፋው መንፈስ በመንፈስ ቅዱስ ታተማችሁ፤" (ወደ ኤፌሶን ሰዎች 1:13) " 🔥እርሱም የርስታችን መያዣ ነው፥ ለእግዚአብሔር ያለውን ሁሉ እስኪዋጅ ድረስ፥ ይህም ለክብሩ ምስጋና ይሆናል።" (ወደ ኤፌሶን ሰዎች 1:14) ሁሌም መንፈስ ቅድስን መለመን እና ያለንን መመዘን ተገቢ ነው ። አምስቱ ቆነጃጂት ጉድለታቸውን የተመለከቱት ሙሽራው ሲመጣነው ። ☄ኢየሱስ መች ይመጣል? ☄እኛ ከዚ ምድር መች እንለያለን? ✍✍አናውቅም ። ስለዚ ሁሌም እራሳችንን እንፈትሽ ። 👉👉" ሳታቋርጡ ጸልዩ፤ በሁሉ አመስግኑ፤ ይህ የእግዚአብሔር ፈቃድ በክርስቶስ ኢየሱስእናንተ ነውና።" (1ኛ ወደ ተሰሎንቄ ሰዎች 5:17-18) ከክፉ ነገር መራቅ አለብን ። ምክንያቱም :- 👉👉" ለቤዛም ቀን የታተማችሁበትን ቅዱሱን የእግዚአብሔርን መንፈስ አታሳዝኑ።" (ወደ ኤፌሶን ሰዎች 4:30)

##12ቱ_የአገልግሎት_እንቅፋቶች 1/👉 #ትህቢት ለራስ ያለን ግምት ከፍ አድርጎ መመልከት(ኩራት) 👉ትህቢት አንዱ የአገልግሎት እንቅፋት ነው። 2/👉 #ከመፀለይ_መድከም ፀሎት ከአምላክ ጋር ያለን ሕብረት ነው። የማይፀልይ አገልጋይ የሚሰራ ፀጋ የለውም። 3/👉 #ያለ_እረፍት_ማገልገል ። ያለ እረፍት በማገልገል እግዚአብሔርን ደስ አሰኛለው ብለን እናስብ ይሆናል😁 ነገር ግን እሱ በራሱ የአገልግሎት እንቅፋት ነው። ምክንያቱም የዝግጅት ጊዜ የለንም ማለት የምናገለግለው አገልግሎት ውጤታማ አገልግሎት አይደለም ማለት ነው። 4/👉 #ዓለምን_መውደድ በዓለም ፍቅር ተነድፎ ከአገልግሎት የተሰናከለው ዴማስ ህያው ምስክር ነው። ዓለምን መውደድ የአገልግሎት እንቅፋት ነው። 5/👉 #በእግዚአብሔር_ቃል_አለመሞላት በቂ መፅሐፍ ቅዱሳዊ እውቀት ማጣት ሰሚውንም ሰባኪውንም ተጠራጣሪና ጭብጥ አልባ መልዕክት ሰጪ በማድረግ ከአገልግሎት ውጭ የማድረግ አቅም አለው። 6/👉 #የገንዘብ_ፍቅር ቁስ ተኮር ፍላጎት። አገልግሎትን በቁስ ሚዛን መለካት የአገልግሎት እንቅፋት ነው። 7/👉 #የስጋ_ሥራ እንደ ዝሙት ስካር ርኩሰት ያሉ ልምምዶችና ምኞቶች የአገልግሎት እንቅፋት ናቸው። ሰይጣን በስጋዊ ምኞቶቻችን እንደ ሚያጠምድ መዘንጋት የለብንም። 8/👉 #ተስፋ_መቁረጥ ተስፋ መቁረጥ የሚመጣው በችግርና በፈተና ጊዜያችን ከሚመነጭ ፍርሃት በመነሳት ነው። ለምሳሌ የኤማውስ መንገደኞች የዚህ እንቅፋት ሰለባ ምሳሌ ናቸው። 9/👉 #የምህረት_ልብ_ማጣት ይቅር ባይ ያልሆንን እንደ ሆነ ይቅር ያለንን አምላክ ልናገለግለው አንችልም። አገልግሎትና ምህረት የማይነጣጠሉ ተጣማሪ ናቸው። 10/👉 #አለመታዘዝ ለእግዚአብሔርና ለቃለ እግዝአብሔር አለመታዘዝ ለመንፈሳዊ ስርዓት አለመገዛት የአገልግሎት እንቅፋት ነው። 11/👉 #አጉል_ፉክክር ከሌሎች አገልጋዮች ጋር ትከሻ መለካካት። ይህ በደቀ መዛሙርቱ መካከል ተከስቶ ነበር። #ኢየሱስም_አለ 👉ማቴዎስ 20 ²⁶ በእናንተስ እንዲህ አይደለም፤ ነገር ግን ማንም ከእናንተ ታላቅ ሊሆን የሚወድ የእናንተ አገልጋይ ይሁን፥ ²⁷ ከእናንተም ማንም ፊተኛ ሊሆን የሚወድ የእናንተ ባሪያ ይሁን፤ 👉መንፈሳዊ ታላቅነት ያለው ሌሎችን በማተለቅ ውስጥ እንደሆነ ልናውቅ ይገባል። 12/👉 #የማያንፁ_ንግግሮች የማያንፁ ንግግሮች የአገልግሎት እንቅፋት ናቸው። 👉ከአፍ የሚወጣ ግን ከልብ ይወጣል፥ ሰውንም የሚያረክሰው ያ ነው።   ማቴዎስ 15፥18 👉ምንጭስ ከአንድ አፍ የሚጣፍጥንና የሚመርን ውኃ ያመነጫልን?”   ያዕቆብ 3፥11 ተባረኩ❤💥 ከአገልግሎት እንቅፋቶች ተጠበቁ። እግዚአብሔር ይጠብቃችሁ😍❤💥 @MARANATHAWOCH @MARANATHAWOCH

መጎናጸፊያ_ተቀበል_ለምታስቀጥለው አንድ ብቻውን ሳለ የጠራው እንደ ምድር አሸዋ እንደማይቆጠረው እንደሰማይ ከዋክብት እንደማይገመተው ገና እባርክሃለሁ ገና አበዛሃለሁ ያለው መንገዱ ቢከብድም በቃሉ ታማኝ ነው አብርሃም በመታዘዝ  ልጁን በመሰዋት ይስሐቅ  የተደፈኑ ጉድጓዶችን በመክፈት ያዕቆብ ታግሎ ተቀብሎ በረከት አሸንፎ አሻገረ  የአባቶቹን እምነት ሙሴም ተተካ ሊቆም ለነፃነት ቀኑ ጨልሞ ሰማዩ ድም በተፋበት አዳኝ ጠፍቶ ተስፋ በጨለመበት ብዙ አሳለፈ መከራና ጭንቀት እጅ ሳይሰጥ ሳይንበረከክ ቆመ ለተጠራለት የእግዚአብሔር ባሕርይ ሲጠራ አገልጋይ በመጀመሪያ መጨረሻውን የሚናገር ነው የመሀሉ ጉዞ ታግሎ በማሸነፍ  ነው የእግዚአብሔር አገልጋይ ሕይወቱ ከእግዚአብሔር የሚያታግል ለሕዝቡ አለው መከራ ማይታለፍ ሚመስል ጠቦት መጠበቁ ግልገልና በግ ማሰማራት ጥበብ ይፈልጋል ያስከፍላል መስዋዕትነት ዘጠና ዘጠኙ ተትቶ አንዱ እንዳይጠፋ ሁሉን በፍቅር መያዙ እይታን እያሰፋ መከራና ችግር ማጣቱ እየጎሰመ ስጋን በጥርስ ነክሶ ይኖራል ተስፋን እያለመለመ ጉዞው  ሲከብድ አቅም ሲታጣ መከራው ችግሩ ከብዶ ሲያንገላታ ረሀብ ቸነፈሩ እጅጉን ሲቀጣ ፈተናው በዝቶ እንደ ዘይት ሲያንጣጣ እኔ አለሁልህ አይዞህ እያለ ሚያፅናና ከመንፈሱ የሚያፈስ ጠማማውን ሚያቃና አለ እግዚአብሔር ለአገልጋዩ ልቡ ለቀና እንዲህ እያሉ ኢየሱስን አገልግለው ያለፉ እድሜያቸውን በሙሉ በወንጌል ያሳለፉ የመዳንን ወንጌል የሰበኩ ለጠፉ ለኛ ለዚህ ትውልድ  የሚያስተላልፉት አለ እንድ ነገር በደማቸው የፃፉት አለ መጎናፀፊያ ዕጥፍ ቅባት ያለበት ከኋላቸው የጣሉት ለእውነት ወንጌል እነሱ ለተጠሩት እንዲህ ነው ሕይወታቸው በእግዚአብሔር የተጠሩት ብዙ ብል ብዙው ይቀራል ስለአገልጋዩ ያሳለፈውን ባነሳ ገና ሚያሳልፈው ገና ይቀራል /2* የሕይወታቸው መንገድ ከየሱስ ጋር ያሳለፉት ለኛ ለዚህ ትውልድ  የሚያስተላልፉት መጎናጸፊያ   አለ በእጥፍ የተቀባ ትውልድ ንቃና ትኩር ብለህ  ተመልከት አንተም ለምታስቀጥለው  ወንጌል ለእውነት ራስህን አዘጋጅ  በልመና በፀሎት ራስህን አዘጋጅ በእጥፍ ለመቀባት ራስህን አዘጋጅ አንተም ለማስቀጠል የኤልያስ ዘመን አሁን ተፈፀመ ኤልሳዕ ተተካ በእጥፍ መንፈስ ታተመ መጎናጸፊያው እንዳያልፍህ በርታ ተነሳ ምታስቀጥል ትውልድ በአባቶች እጥፍ መንፈስ ስለዚህ ንቃ በፀሎት ልብህ ይፍሰስ ተቀበል እንደ ኤልሳዕ  መጎናጸፊያ አስቀጥል በዘመንህ በሁለት እጥፍ መንፈስ። 2ኛ ነገሥት 2:11_14 ሲሄዱም፦ እያዘገሙም ሲጫወቱ፥ እነሆ፥ የእሳት ሰረገላና የእሳት ፈረሶች በመካከላቸው ገብተው ከፈሉአቸው፤ ኤልያስም በዐውሎ ነፋስ ወደ ሰማይ ወጣ። ኤልሳዕም አይቶ፦ አባቴ አባቴ ሆይ፥ የእስራኤል ሰረገላና ፈረሰኞች፥ ብሎ ጮኸ። ከዚያም ወዲያ አላየውም፤ ልብሱንም ይዞ ከሁለት ተረተረው። ከኤልያስም የወደቀውን መጐናጸፊያ አነሣ፥ ተመልሶም በዮርዳኖስ ዳር ቆመ። ከኤልያስም የወደቀውን መጎናጸፊያ ወስዶ ውኃውን መታና፦ የኤልያስ አምላክ እግዚአብሔር ወዴት ነው? አለ፤ ውኃውንም በመታ ጊዜ ወዲህና ወዲያ ተከፈለ፤ ኤልሳዕም ተሻገረ።          @MARANATHAWOCH @MARANATHAWOCH

(2) የቀጠለው ⬆️ - የአዳም ሥጋና ደም የሚያድን ቢሆን ወንድም ወንድሙን አያድንም ሰውም አያድንም ተብሎ ባልተፃፈም ነበር። - በዘኁልቁ 21÷4-9 እንደተፃፈው ሙሴ -በእባብ ተነድፎ ለሞተው ሰው ሁሉ ከነደፈው እባብ አንዱ ሰቅሎ ሰዉ ሁሉ አይቶት በዳነ ነበር የናስ እባብ መስራትም ባልፈለገ ነበር ↪️ የነደፈው  እባብ ማዳን አይችልም የወደቀውም የአዳም ማዳን አይችልም       - የናስ እባብ እንደ ተዘጋጀ       - ልዩ ሥጋና ደም ነው የተዘጋጀው ⭐️ ምን አይነት ሰው ነው የተሰቀለው        - ዮሐንስ 3:13 ከሰማይ የወረደ       - ዮሐንስ 1:14 ቃል ሥጋ የሆነ          1ኛ ቆሮንቶስ 15÷45 የመጀመሪያው አዳም ሣይሆን ሁለተኛ አዳም          1ኛ ቆሮንቶስ 15÷47 የመጀመሪያው ሰው ሣይሆን አዲሱ ሰው           ፊልጵስዩስ 3÷21 ክቡር ሥጋውን  እንድንመስል የተዋረደውን ሥጋችንን ይለውጣል ተብሎ እንደ ተፃፈው ነው 📌 ስለ ሰው ልጆች የተሰቀለውን ኢየሱስ የምናይበት አስተያየታችን አስተካክለን ብናየው መዳን እናገኛለን። 📌 አንድ ሰው ነው የተሰቀለው ብንል መዳን አናገኝም 📌 ኢየሱስ አንድ ተራ ሰው አይደለምና እናም ደግሞ ሰውም አይድንም ተብሎ ተፅፎአልና። ↪️ በመዝ ዳዊት(40)÷6 መስዋዕትንና ቁርባንን አልወደድህም ሥጋን አዘጋጀህልኝ  - የሚቃጠለውንና ስለ ኃጢአት የሚቀርበውን መስዋዕት አልሻህም አለ          ሥጋን አዘጋጀህልኝ  ⭐️ የተሰቀለው ኢየሱስ የዓለምን ኃጢአት እንዲያስወግድ የተዘጋጀ ልዩ ሥጋና ደም ነው።            ዕብ 10÷5-10 የተዘጋጀው የኢየሱስ ክርስቶስን ሥጋ አንድ ጊዜ ፈፅሞ በማቅረብ ተቀድሰናል      ስለዚህ የተሰቀለውን ኢየሱስ ⭐️ እንደ ባህሪው ስናየው ነው የምንድነው የነደፈ እባብ ማዳን እንደማይቻለው ሁሉ ኃጢአትን ወደ ዓለም ያገባው አዳም ኃጢአትን ማውጣት አይችልም (ከኃጢአት ማዳን አይችልም)             ኢሣ 33÷13-22 ቁ.17 ዓይኖችህ ንጉሥን በውበቱ ያዩታል። ይላል የተሰቀለውን በማየት የሚገኝ መዳን                  ቆላ 2÷14 ↪️ በእኛ ላይ የነበረውን የሚቃወመንንም በትዕዛዝ የተፃፈውን የዕዳ ፅህፈት ደመሰሰው እርሱንም በመስቀል ጠርቆ ከመንገድ አስወግዶታል አለቅነትንና ስልጣናትን ገፎ ድል በመንሳት በእርሱ እያዞራቸው በግልጥ አሣያቸው። -ኃጢአት የሰራው አዳም ኃጢአትን በመስቀል ጠርቆ ከመንገድ ማስወገድ አይችልም ። ቃል ስጋ የሆነው ኢየሱስ ዮሐንስ 1÷14 - ቅዱስና ያለ ተንኮል ነውር የሌለበት ከኃጢአተኞችም የተለየው ኢየሱስ ዕብ 7:26 - ኀጢአትን ሊያስወግድ የተገለጠና በእርሱ ኀጢአት የሌለበት ኢየሱስ 1ኛ ዮሐንስ  3:15 - በቀራንዮ ተራራ ላይ ተሰቅሎ ኀጢአታችንን በመስቀል ጠርቆ  አስወግዷል እርሱን ስናይ መዳንን እናገኛለን።           በዘፍጥረት 22÷14 - አብርሃም በይስሃቅ ፈንታ የሚሰዋ በግ አይቶ ከሰዋው በኋላ ቦታው ያህዌ ይርኤ ብሎ ጠራው         በእግዚአብሔር ተራራ ይታያል                ኤፌሶን 2÷14-16           የተሰቀለው ኢየሱስ ስናይ     - ሠላማችን ነው    - በአዋጅ የተነገረውን ትዕዛዝ ሽሮልናል    - የጥል ግድግዳ አፍርሶልናል    - ጥልን በመስቀሉ ገድሎልናል    - ከእግዚአብሔር ጋር አስታርቆናል    - ወደ መንግስቱ መግባት አግኝተናል    - ይህ ሁሉ የሆነው እናስተውል            በእርሱ ስራ ነው (በቀራንዮ            መስቀል ላይ በሰራው ስራ) ነው የተሰቀለውን በማየት የሚገኝ መዳን     ዕብ 2÷2 -- ታላቅ መዳን    ዩሐ 3÷16 -- የዘላለም ህይወት    ዕብ 5÷9-10 -- የዘላለም መዳን          ሉቃ 23÷44-49 ↪️ የመቶ አለቃው ስቅለቱን ባየ ጊዜ እግዚአብሔርን አከበረ ሲያፌዝ የነበረው በንቀት ሲያይ የነበረው በውበቱ ሲያየው ግን ይህ ሰው በእውነት ፃድቅ ነበረ ብሎ እግዚአብሔርን አከበረ ይላል።     ወንድሞችና እህቶች ስለ በደላችን አልፎ የተሰጠውን በመስቀል ላይ ስለኛ የተሰዋውን      ንጉሱን በውበቱ እንየው      ታላቅ መዳን እናገኛለን።               🙏   አሜን  🙏 @MARANATHAWOCH @MARANATHAWOCH

             ዩሐ  3÷14-15               ዘኁ   21÷4-9 የተሰቀለውን በማየት የሚገኝ መዳን...... (1) ↪️ ጌታ ኢየሱስ በዘኁልቁ ምዕራፍ 21÷4-9 የተፈጸመው ታሪክ ወይም የነገር ጥላ ጠቅሶ ሲናገር ሙሴ በምድረበዳ እባብን እንደሰቀለ እንዲሉ በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘላለም ህይወት እንዲኖረው እንጂ እንዳይጠፋ የሰው ልጅ ይሰቀል ይገባዋል። ↪️ በብልይ ኪዳን በእባብ ተነድፈው የሞቱ ሰዎች እባብን አይተው በህይወት ኖሩ። ሰው የነደፈውን እባብ ሲያይ  ይበረግጋል / ይፈረጥጣል / እንጂ ሊያይ አይፈቅድም ውይ ብሎ ይሮጣል እባብ ያየ በልጥ በረየ እንዲሉ ማለት ነወ። እዚህ ጋ ግን ፦ የተለየ ታሪክ ነው የተፈጸመው። ⭐️ ነገሩ እንዴት ነው ብሎ መመርመር ያስፈልጋል። እስራኤላውያን አይተው የዳኑት ምንድን ነው ? ነድፎ የጨረሳቸውን እባብ ነውን? እሱማ እኮ ነድፎ ገደላቸው። ታዲያ ምን አይነት እባብ ነው።     ° ነድፎ የጨረሳቸው እባበብ ሳይሆን እሱን የሚመስል ግን ያይደለ የናስ እባብ ነው     ° እባብ ነው ግን የናስ እባብ 🔶 ወደ ነጥባችን መለስ ሥንል 🔶 የእግዚአብሔር ቃል ፦ በሮሜ 5÷12-21 እንደተፃፈው በፊተኛው ሰው በደል ሰው ሁሉ ከሞተ በፊተኛው አዳም ሰው ሁሉ ኃጢአተኛ ከሆነ ፦     - በፊተኛው ሰው በህይወት አይኖርም     - በፊተኛው አዳምም ፃድቅ አይሆንም              ዘፍጥረት 22:1-14    በፊተኛው ሰው በህይወት የሚኖረው    በፊተኛው አዳም የሚፀድቅ ቢሆን ኖሮ ↪️ በሞሪያ ተራራ ላይ ይስሃቅ ይሰዋ ነበር ነገር ግን ፦ መዝሙረ ዳዊት (49)÷7 እንደተፃፈው "ሰውም አይድንም ቤዛውን ለእግዚአብሔር አይሰጥም " ስለተባለ እግዚአብሔር ይሳሃቅን ከመስዋት አድኖ የአለምን ለኃጢአት የሚያስወግደውን የእግዚአብሔር በግ ጥላ የሆነውን በግ እንዲሰዋ አደረገ። ዮሐንስ 1÷29 የአለምን ኀጢአት    የሚያስወግድ የእግዚአብሔር በግ የሰው ኃጢአት ፦ በአዳም መስዋዕት ወይም ደግሞ አዳም በሚቀርበው መስዋዕት የሚሠረይ አደለም። ስለዚህም ነው ፦ የአዳምን ዘር ሁሉ ነፃ የሚያወጣዉን የሰው ልጅ (ኢየሱስ ክርስቶስ) ሊሰቀል የተገባው። ዕብ 2:9-110 ነገር ግን በእግዚአብሔር ፀጋ ስለ ሰው ሞትን ይቀምስ ዘንድ ብዙ ልጆችን ወደ ክብር ሲያመጣ የመዳናቸው ራስ በመከራ ይጻፍም ዘንድ ከእርሱ የተነሳ ፦               - ሁሉ በእርሱ ለሆነ               - ለእርሱ ተገብቷል ⭐️ ብዙ ልጆችን ወደ ክብር ሊያመጣና የመዳናቸውን ራስ በመከራ እንዲፈፀም ↪️ የርሱ መሰቀል የተገባ ሆኖዋል። ↩️   የትምህርታችን ርዕስ ለማስታወስ የተሰቀለውን በማየት የሚገኝ መዳን ዕብ 2÷14-15 ፦ እንግዲህ ልጆች በሥጋና በደም ሥለሚካፈሉ እርሱ ደግሞ በሞተ ላይ ስልጣን ያለውን በሞት እንዲሽር ይኸውም ዲያቢሎስ ነው። ''በ1ኛዩሐ 3÷8'' የዲያቢሎስን ሥራ እንዲያፈርስ የእግዚአብሔር ልጅ ተገለጠ ተብሎ እንደተፃፈው በህይወታቸው ሁሉ ስለ ሞት ፍርሃት በባርነት ይታሰሩ የነበሩት ሁሉ ነፃ እንዲያወጣ በሥጋና በደም እንዲሁ ተከፈለ ይላል። ↪️ ተመልከቱ አስተውሉ እዩም ↩️         በምን አይነት ሥጋና ደም ? ⭐️ የአዳም ዓይነቱ ስጋና ደም እንዳትሉ ⭐️ የአዳም ሥጋ የሚያድን ቢሆን                   ይስሃቅ ይሰዋ ነበር ይቀጥላል....... @MARANATHAWOCH @MARANATHAWOCH

በኢትዮጵያ ሐዋርያዊት ቤቴክርስትያን የአለታ ቅርንጫፍ ሰበካ በአለታ ጩኮ ከተማ ንዑስ የቤተሳይዳ አጥብያ ቅጥር ግቢ ሲካሄድ የነበረ 2ተኛ ዙር የወጣቶች ዓመታዊ ኮንፈራንስ በሰላም የተጠናቀቀ ሲሆን በ
+9
በኢትዮጵያ ሐዋርያዊት ቤቴክርስትያን የአለታ ቅርንጫፍ ሰበካ በአለታ ጩኮ ከተማ ንዑስ የቤተሳይዳ አጥብያ ቅጥር ግቢ ሲካሄድ የነበረ 2ተኛ ዙር የወጣቶች ዓመታዊ ኮንፈራንስ በሰላም የተጠናቀቀ ሲሆን በዚህ ጉባኤ ሶስት ነፍሳት በኢየሱስ ሲጠመቁ አንድ ደግሞ ከአጋንንት ወጥተዋል፡፡ ✍ይህ የእውነት ወንጌል ገና ይሰበካል አንዱ አምላክ ሁሉን ይወርሳል፡፡ 👉እናወርሳለን✅ 👉እናጠምቃለን✅ 👉እንበዛለን🙏🙏 @MARANATHAWOCH

⬆️ - የአዳም ሥጋና ደም የሚያድን ቢሆን ወንድም ወንድሙን አያድንም ሰውም አያድንም ተብሎ ባልተፃፈም ነበር። - በዘኁልቁ 21÷4-9 እንደተፃፈው ሙሴ -በእባብ ተነድፎ ለሞተው ሰው ሁሉ ከነደፈው እባብ አንዱ ሰቅሎ ሰዉ ሁሉ አይቶት በዳነ ነበር የናስ እባብ መስራትም ባልፈለገ ነበር ↪️ የነደፈው  እባብ ማዳን አይችልም የወደቀውም የአዳም ማዳን አይችልም       - የናስ እባብ እንደ ተዘጋጀ       - ልዩ ሥጋና ደም ነው የተዘጋጀው ⭐️ ምን አይነት ሰው ነው የተሰቀለው        - ዮሐንስ 3:13 ከሰማይ የወረደ       - ዮሐንስ 1:14 ቃል ሥጋ የሆነ          1ኛ ቆሮንቶስ 15÷45 የመጀመሪያው አዳም ሣይሆን ሁለተኛ አዳም          1ኛ ቆሮንቶስ 15÷47 የመጀመሪያው ሰው ሣይሆን አዲሱ ሰው           ፊልጵስዩስ 3÷21 ክቡር ሥጋውን  እንድንመስል የተዋረደውን ሥጋችንን ይለውጣል ተብሎ እንደ ተፃፈው ነው 📌 ስለ ሰው ልጆች የተሰቀለውን ኢየሱስ የምናይበት አስተያየታችን አስተካክለን ብናየው መዳን እናገኛለን። 📌 አንድ ሰው ነው የተሰቀለው ብንል መዳን አናገኝም 📌 ኢየሱስ አንድ ተራ ሰው አይደለምና እናም ደግሞ ሰውም አይድንም ተብሎ ተፅፎአልና። ↪️ በመዝ ዳዊት(40)÷6 መስዋዕትንና ቁርባንን አልወደድህም ሥጋን አዘጋጀህልኝ  - የሚቃጠለውንና ስለ ኃጢአት የሚቀርበውን መስዋዕት አልሻህም አለ          ሥጋን አዘጋጀህልኝ  ⭐️ የተሰቀለው ኢየሱስ የዓለምን ኃጢአት እንዲያስወግድ የተዘጋጀ ልዩ ሥጋና ደም ነው።            ዕብ 10÷5-10 የተዘጋጀው የኢየሱስ ክርስቶስን ሥጋ አንድ ጊዜ ፈፅሞ በማቅረብ ተቀድሰናል      ስለዚህ የተሰቀለውን ኢየሱስ ⭐️ እንደ ባህሪው ስናየው ነው የምንድነው የነደፈ እባብ ማዳን እንደማይቻለው ሁሉ ኃጢአትን ወደ ዓለም ያገባው አዳም ኃጢአትን ማውጣት አይችልም (ከኃጢአት ማዳን አይችልም)             ኢሣ 33÷13-22 ቁ.17 ዓይኖችህ ንጉሥን በውበቱ ያዩታል። ይላል የተሰቀለውን በማየት የሚገኝ መዳን                  ቆላ 2÷14 ↪️ በእኛ ላይ የነበረውን የሚቃወመንንም በትዕዛዝ የተፃፈውን የዕዳ ፅህፈት ደመሰሰው እርሱንም በመስቀል ጠርቆ ከመንገድ አስወግዶታል አለቅነትንና ስልጣናትን ገፎ ድል በመንሳት በእርሱ እያዞራቸው በግልጥ አሣያቸው። -ኃጢአት የሰራው አዳም ኃጢአትን በመስቀል ጠርቆ ከመንገድ ማስወገድ አይችልም ። ቃል ስጋ የሆነው ኢየሱስ ዮሐንስ 1÷14 - ቅዱስና ያለ ተንኮል ነውር የሌለበት ከኃጢአተኞችም የተለየው ኢየሱስ ዕብ 7:26 - ኀጢአትን ሊያስወግድ የተገለጠና በእርሱ ኀጢአት የሌለበት ኢየሱስ 1ኛ ዮሐንስ  3:15 - በቀራንዮ ተራራ ላይ ተሰቅሎ ኀጢአታችንን በመስቀል ጠርቆ  አስወግዷል እርሱን ስናይ መዳንን እናገኛለን።           በዘፍጥረት 22÷14 - አብርሃም በይስሃቅ ፈንታ የሚሰዋ በግ አይቶ ከሰዋው በኋላ ቦታው ያህዌ ይርኤ ብሎ ጠራው         በእግዚአብሔር ተራራ ይታያል                ኤፌሶን 2÷14-16           የተሰቀለው ኢየሱስ ስናይ     - ሠላማችን ነው    - በአዋጅ የተነገረውን ትዕዛዝ ሽሮልናል    - የጥል ግድግዳ አፍርሶልናል    - ጥልን በመስቀሉ ገድሎልናል    - ከእግዚአብሔር ጋር አስታርቆናል    - ወደ መንግስቱ መግባት አግኝተናል    - ይህ ሁሉ የሆነው እናስተውል            በእርሱ ስራ ነው (በቀራንዮ            መስቀል ላይ በሰራው ስራ) ነው የተሰቀለውን በማየት የሚገኝ መዳን     ዕብ 2÷2 -- ታላቅ መዳን    ዩሐ 3÷16 -- የዘላለም ህይወት    ዕብ 5÷9-10 -- የዘላለም መዳን          ሉቃ 23÷44-49 ↪️ የመቶ አለቃው ስቅለቱን ባየ ጊዜ እግዚአብሔርን አከበረ ሲያፌዝ የነበረው በንቀት ሲያይ የነበረው በውበቱ ሲያየው ግን ይህ ሰው በእውነት ፃድቅ ነበረ ብሎ እግዚአብሔርን አከበረ ይላል።     ወንድሞችና እህቶች ስለ በደላችን አልፎ የተሰጠውን በመስቀል ላይ ስለኛ የተሰዋውን      ንጉሱን በውበቱ እንየው      ታላቅ መዳን እናገኛለን።               🙏   አሜን  🙏 @MARANATHAWOCH @MARANATHAWOCH

ክብር አለኝ ለአንተ
ክብር አለኝ ላንተ *2 የማያመጠን*4 ምስክርህ ነኝ ለማዳንህ የሱሴ እኔ አንተን ብዬ አፍሬ አላውቅም በህይወቴ የፍቅርህ ሚዛን እያደላልኝ ወደእኔ አለው በቤትህ ምህረትህ ከቦት ዘመኔን ባመልክህ ያንስብሃል ብዘምር ያንስብሃል በእውነት ግነን ከፍ በል ይታይ ማንነትህ 1) በእውነት ቃል አስበህ ፈጥረህ ይህው አኖርከኝ ዘመኔን በሙሉ ይዘህ እየመራህኝ ምን አለ ያላንተ ያላለፍኩት ነገር ጌታዬ አምላኬ ምስጋናዬ እኮ ነህ ያማረ ዜማ የሚገባህ እየሱስ አለ አለ በፂዮን አለ አለ*2 የማይቋረጥ ምስጋና አምልኮ ለአንተ አለ አለ በፂዮን አለ አለ *2 ይሰማ ያስተጋባ የእልልታው ድምፅ ይውጣ ሰማይ ልዩ ነህ የእኔ ጌታ ከአማልክት ሁሉ ልቀህ ታይ አይነስብህ ከኔ ምስጋና ትልቅ ነህ ትልቅ ልበል ገናና አይነስብህ ከኔ ዝማሬ ለአምላክነትህ ትዋረድ ክብሬ 2) ማረጌ ልበልህ ብርቱ ነህ መጠጊያዬ ማዳንህን ስራህን አይቼዋለው ባይኔ ባመታት መሀል ቃልህ ተፈፀመልኝ ትኑርልኝ ነፍሴ ታመልክሃለች ዘወትር የልቤ ጉልበት (ይንበርከክልህ)*2 ውለታህ አለብኝ ክበር ልበልህ ያበቃልኝን ዘመን አሻግረህ ዛሬን አቆምከኝ ምስጋናን ሞልተህ መዝሙሬ ሀሌሉያ ነው ስጦታዬም ምስጋና ነው ሳመልክህ *3 ብቻ ኖራለው

photo content

Z Dawit Dabaro reggea tunse 33.mp35.23 MB

Z Dawit Dabaro buuxe afi 11.mp35.10 MB

Z Dawit Dabaro disk tayinse 22.mp34.19 MB

22 Fikire Girma (9) Track 22.mp34.54 MB

22 Fikire Girma (12) Track 22.mp34.99 MB

22 Fikire Girma (11) Track 22.mp35.88 MB

22 Fikire Girma (6) Track 22 (1).mp35.73 MB

22 Fikire Girma (10) Track 22.mp36.30 MB

22 Fikire Girma (7) Track 22.mp35.93 MB