es
Feedback
ማራናታ.....MARANATHA😍

ማራናታ.....MARANATHA😍

Ir al canal en Telegram

ለአንዳንዶቜ ዹሚዘገይ እንደምመስላ቞ው ጌታ ሰለ ተስፋ ቃሉ አይዘገይም፥ ነገር ግን ሁሉ ወደ ንስሐ እንድደርሱ እንጅ ማንም እንዳይጠፋ ወዶ ሰለ እናንተ ይታገሳል።2ኛ ጎጥ 3፥9 ገና በጣም ጥቅት ጊዜ ነውፀ ሊመጣ ያለውም ይመጣል አይዘገይምም። ዕብራ 10፥37 ዚመወያያ ግሩፕ👇 @Marantawoch Inbox Comment @Thaddyapostolic

Mostrar más

📈 Análisis del canal de Telegram ማራናታ.....MARANATHA😍

El canal ማራናታ.....MARANATHA😍 (@maranathawoch) en el segmento lingÌístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 16 517 suscriptores, ocupando la posición 5 170 en la categoría Religión y espiritualidad y el puesto 2 034 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el МевіЎПЌП, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 16 517 suscriptores.

Según los últimos datos del 14 junio, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de 195, y en las últimas 24 horas de 8, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificación: No verificado
  • Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 16.19%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 7.98% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 2 672 visualizaciones. En el primer día suele acumular 1 316 visualizaciones.
  • Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 26.

📝 Descripción y política de contenido

El autor describe el recurso como un espacio para expresar opiniones subjetivas:
“ለአንዳንዶቜ ዹሚዘገይ እንደምመስላ቞ው ጌታ ሰለ ተስፋ ቃሉ አይዘገይም፥ ነገር ግን ሁሉ ወደ ንስሐ እንድደርሱ እንጅ ማንም እንዳይጠፋ ወዶ ሰለ እናንተ ይታገሳል።2ኛ ጎጥ 3፥9 ገና በጣም ጥቅት ጊዜ ነውፀ ሊመጣ ያለውም ይመጣል አይዘገይምም። ዕብራ 10፥37 ዚመወያያ ግሩፕ👇 @Marantawoch Inbox Comment @Thaddyapostolic”

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 15 junio, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Religión y espiritualidad.

16 517
Suscriptores
+824 horas
+1467 días
+19530 días
Archivo de publicaciones
singer:meseret kejela Title:ጥሶ ዚሚያስጉዝ ሀይል location : merkato salem atbya
ጥሶ ዚሚያስጉዝ ሀይል ልቀ ይናፍቃል ሰማያት ይኚፈቱ ይውሚድ እጥፍ እሳቱ ዹሹኹሰው እንዲፈወስ እጥፍ ይውሚድ ያንተ መንፈስ ተቀብለን ፀጋ ሚበልጥ እንውጣ ሀይልህም ይገለጥ 1)ቀንበርን ዚሚሰብር ሃጥያትን ዚሚያስጥል(ዚሚያስክድ) ላንተ መኖር ዚሚያስቜል ሀይልህ እጥፍ ይውሚድ እንለይ ላንተ ክብር እንቀመም በእሳት ጠላትን እያስፈራን እንኑር ዚክብር ህይወት 2)ጥቂት ዘመን እንዳለው ጠላት ይህንን አውቆ በታላቅ ቁጣ ቢወርድ ቢነሳ እጅግ ታጥቆ ሁሉን ዚሚበልጥ ፀጋ ማሞንፍያ ቅባት ይውሚድ ታላቁ መብሚቅ ዚመንፈስህ እሳት  ጠላት ይፍራ ይደንግጥ አይቶ እንዳለን በእሳት ውስጥ ዚድል ህይወት ዚድል መንገድ እንድንጓዝ ሀይልህ ይውሚድ ይውሚድ እሳትህ ይውሚድ *3 ይውሚድ መንፈስህ ይውሚድ *3 3) ቅዱስ ስምህ ይጠራ ፈውስ ይሁን ታምራት ጠላታቜን ይንቀጥቀጥ ይርበድበድ ባንተ ፉት በስምህ ኚጠራህው ኚታላቅ ህዝብ ጋር ውጣ ዹኛ አምላክ ዚሱስ ልዩነት ይፈጠር ጠላት ይፍራ.... 3) ዛሬም ቅዱስ መንፈስ በብርቱ እንፈልጋለን ያልተለማመድነውን  ፀጋ ይዞ ይምጣልን ሰማያት ይኚፈቱ ድንቁ ክብር ይታይ(ሙሉ) ፍጥሚት ወድቀው ይስገዱ ንገስ በሁሉ ላይ

✍ቅድስና ለእግዚአብሔር !
◉  ቅዱሳን ወገኖቜፊ ቅድስና ለእግዚአብሔር መለዚት ፀ ብልቶቻቜንን ዚፅድቅ እቃ ጩር አርጎ ማቅሚብ ሲሆን መቌም ዚማንደራደርበት ጉዳይ ሊሆን ይገባል። ክርስትና እንደ ልባቜን አሳብና ፈቃድ እዚዋልን እያደርን ዚምንመላለስበት ህይወት አይደለም !  ዳግመኛ ስንወለድ እርሱን ልንመስል እሱም ህይወታቜንን በሞቱና በትንሳኀው ኹለወጠ በኋላ በምድር ዹምንኖሹው ኑሮ  ስለ እኛ ለሞተውና ለተነሳው መሆን እንዳለበት  አስተምሮናል!  ሐዋርያ ጳውሎስ  "ኚክርስቶስ ጋር ተሰቅያለሁ እኔም አሁን ህያው ሆኜ አልኖርም ክርስቶስ ግን በእኔ ይኖራል! በስጋም ዹምኖሹው ህይወት በክርስቶስ ላይ ባለኝ እምነት ዹምኖሹው ነው!" እንዳለው ◉  እርሱን እንድንመስል ተጠርተናል፩ ክርስትና በማስመሰልና በግብዝነት በውጭ መልክ ዹሚኖር ህይወት አይደለም !ልንኖሹው ግድ ይላል!!ዚእግዚአብሔር መንግስት ጉዳይ ነውና!!። ሞቱን በሚመስል ሞት  አሮጌውን  ሰው ሰቅለን ትንሳኀውን በሚመስል ትንሳኀ ደግሞ በአዲስ ህይወት ልንመላለስ ይገባል!!! እንዎትስ ደግመን በሀጥያት ባርነት እንያዛለን?  ኚሀጥያት በታቜ  እዚኖርን እንዎት ክርስቲያን (ዚእግዚአብሔር ቀተሰብ )እንባላለን ??ፀ ዹተቀበልነው መንፈስ ዹፍቅር ራስን ዚመግዛት መንፈስ እንጂ ዚፍርሃት መንፈስ አይደለምና! ◉ እንዎት ራሳቜንን እንግዛ ? እንዎትስ በብርሀን እንመላለስ? " ነገር ግን እላለሁ፥ በመንፈስ ተመላለሱ፥ ዚሥጋንም ምኞት ኚቶ አትፈጜሙ። ሥጋ በመንፈስ ላይ መንፈስም በሥጋ ላይ ይመኛልና፥ እነዚህም እርስ በርሳ቞ው ይቀዋወማሉፀ ስለዚህም ዚምትወዱትን ልታደርጉ አትቜሉም።                  ገላ5፥16-17 ይሄ ጥቅስ ዹሚነግሹን "መንፈሳቜንን በስጋቜን ላይ ማሰልጠን እንዳለብን ያሳዚናል"  ስጋ በመንፈስ ላይ መንፈስም በስጋ ላይ ይቀዋወማሉ! በክርስቶስ ዳግም ተወልዶ አዲስ ፍጥሚት በሆነው ማንነታቜንና(መንፈሳቜን) ላይ ባልተለወጠውና ፣ አለምን በሚሻው ( በወደቀው ማንነታቜን )መሀል ኹፍተኛ መቀዋወምና ጊርነት አለ። እኛም በይበልጥ ዚመገብነው  በርሱ ቁጥጥር ስር ያደርገናል !!ዚመገብነው አይሎ ይሰለጥንብናል!! ወገኖቜ በህይወታቜን ማን አይሏል???? መልሱን ለእናንተ ት቞ዋለሁ!! እንዲሁ ዹወደቀው ማንነታቜን እንዳለ ሆኖ ፥  ሰይጣን በሚሰለጥንበትና በወደቀ አለም ስለምንኖር ልንመስላ቞ው ስለሚስቡን ነው!  ሐዋርያ ጳውሎስ  ጢሞቲዮስን "እግዚአብሔርን ለመምሰል ራስህን አስለምድ"  ይለዋል። ልክ ሰውነትን ለማጎልበትና ለመጠንኹር ዚተመጣጠነ ምግብ መመገብ እና ተገቢ ስፖርት መስራት ግዎታ እንደሆነ ፥  እግዚአብሔርን ለመምሰልም መንፈሳዊ Exercise እንዲሰራ ያዘዋል። ይህ ነው እንግዲህ እግዚአብሔርን ለመምሰል መለማመድ!!በቅድስና ለመኖር መንፈሳቜንን በመመገብ በስጋቜን ላይ እንዲሰለጥን ማድሚግ ..... መንፈስን መመገብ ►  መንፈሳቜንን ዹምንመግበው ዚመጀመሪያው  ምግብ ዚእግዚአብሔርን ቃል ነው!  “ኢዚሱስምፊ ሰው በእግዚአብሔር ቃል ሁሉ እንጂ በእንጀራ ብቻ አይኖርም ተብሎ ተጜፎአል”                ሉቃስ 4፥4 ቃሉን  ማንበብ ወሳኙ ነገር ሆኖ ሳለ ፥  ይህን ቃል እስኪዋሀደንና ዚራሳቜን እስኪሆን ድሚስ ማሰላሰል ደግሞ ቀጣዩ ቁልፍ ጉዳይ ነው! በዚህ ላይ ብዙዎቜ ዚሚስቱት  ማንበቡን ያነቡትና ማሰላሰሉ (meditation) ላይ ዚሉበትም! ቃሉ ደግሞ በማሰላሰል በኩል መንፈሳቜንን እንዲቆጣጠር እስካላሚግነው ድሚስ ጠቀሜታ አይኖሹውም! ልክ ምግብ ተመግበን ዚተመገብነው ምግብ ተፈጭቶ ዹሚዋሀደው  በDigestive system እንደሆነው ሁሉ ቃሉን አንብበን ዹሚዋሀደን ደግሞ በተደጋጋሚ ስናሰላስለው ነው! ስንወጣ ስንገባ ፀ  በምልልሳቜን ሁሉ ማሰላሰል ግድ ይለናል። “እጆቌንም ወደ ወደድኋ቞ው ወደ ትእዛዛትህ አነሣለሁፀ ሥርዓትህንም አሰላስላሁ።”            መዝ 119፥48 ►  ሌላኛው ዚመንፈስ ምግብ ፀሎት ነው! ፀሎት ዚክርስቲያን አማራጭ ዹሌለው ህይወቱ መሆን አለበት። ቢደክም ቢበሚታ በዚትኛውም ሁኔታዎቜ ውስጥ ኚእግዚአብሔር ጋር ዹጠበቀ ህብሚት ሊኖሹው ያስፈልገዋል። ፀሎት ማለትፊ ኚእግዚአብሔር ጋር መነጋገር ፀ ህብሚት ማድሚግ ነው። ይህም ሰአት ገድበንለት ዹምናደርገው ሳይሆን ዘወትር መንፈሳቜንን ኚእርሱ መንፈስ ጋር ዚምናገናኝበት ዹሰማይ ደጅ ነው!! ስንወጣ  ፀ ስንሄድ ፀ ስራ ስንሰራ ብንጞልይ....  መንፈሳቜን ይጠነክራል ፀ ስጋ ዚምንጎስምበት አቅም ይሰጠናል።  ክፋትን እያሰብን ፀ ሰዎቜን እያማን ፀ ለማያንጹን ቃላት ጆሮአቜንን እዚሰጠን ኚአንድበታቜንም እያወጣን  ውለን  ዹምንፀልዹው ፀሎት ትርጉም ይኖሹዋልን? ►  ሌላኛው ዚመንፈስ ምግብ በቀተክርስቲያን ውስጥ ህብሚት ማድሚግና ማገልገል ነው። “በሐዋርያትም ትምህርትና በኅብሚት እንጀራውንም በመቍሚስ በዚጞሎቱም ይተጉ ነበር።”                     ሐዋ 2፥42 ቅዱሳን ዚክርስቶስ አካል  እንደመሆናቜንና ክርስቶስም ዹኛ ራስ እንደመሆኑ እንደ  አካል መስራት መንቀሳቀስ አለብን።  እርስ በእርስ መተሳሰብ፣ መተናነፅ ፣ መያያዝ  ፣ መደጋገፍ አካሉን ያሳድጋል! በቀሚውስ ወገኖቌ እስቲ በዚህ ሚዛን እንመዘን?!ዚት ጋር ነን?ኑሮቜን እንዎት ነው?  ለርሱ  እዚኖርንለት ነው? ጹክን እንቀደስ ፥ ዚተሻለ ህይወት ይሁንልን! እነሆ በደጅ ቆሟል!!! ለእውነት እንነሳ !እርሱን ለመምሰል ራሳቜንን እናስለምድ ክብራቜን ነውና!!! በእለት ተእለት ህይወታቜን ይህን በማሰላሰልና በማድሚግ በቅድስና ለእግዚአብሔር መኖር እንቜላለን!!                    “እኛም ሁላቜን በመጋሹጃ በማይኹደን ፊት ዚጌታን ክብር እንደ መስተዋት እያብለጚለጭን መንፈስ ኹሚሆን ጌታ እንደሚደሚግ ያን መልክ እንመስል ዘንድ ኚክብር ወደ ክብር እንለወጣለን።”                         2ኛ ቆሮ 3፥18 ​ @MARANATHAWOCH @MARANATHAWOCH

🔥🔥መንፈስ ቅድስ🔥🔥 መንፈስ ቅድስ ኚእግዚአብሔር ዹምንቀበለው ሃይል ነው ። ዚእግዚአብሔርን ስራ መስራት ዚምንቜለው በመንፈስ ቅድስ ሃይል አማካኝነት ነው። 👉👉 በመንፈሮ እንጂ በኃይልና በብርታት አይደለም፥ ይላል ዚሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር። " (ትንቢተ ዘካርያስ 4:6) ዚተመሚጡ ሐዋርያቶቜ ሃይል እስኪቀበሉ ደሚስ በኢዚሩሳሌም ቆዩ እኛም ሃይልን እስክንቀበል ድሚስ በትግስት መጠበቅ አለብን 🔥መንፈስ ቅድስ ለመሞላት መጠማት አለብን ። 👉👉" እኔ ኹምሰጠው ውኃ ዚሚጠጣ ሁሉ ግን ለዘላለም አይጠማም፥ እኔ ዹምሰጠው ውኃ በእርሱ ውስጥ ለዘላለም ሕይወት ዹሚፈልቅ ዹውኃ ምንጭ ይሆናል እንጂ አላት።" (ዚዮሐንስ ወንጌል 4:14) መንፈስ ቅድስ እለት እለት እደምናገኝው ውሃና ምግብ ነው አንድ ሰው ካልተመገበ ሀይል አይኖሹውም እንዲሁም አንድ መንፈሳዊ ሰው ዚመንፈስ ቅድስ ሃይል ካላገኝ መንፈሳዊ ሕይወቱ እዚደኚመ ይሄዳል ስለዚ ሁሌም መራብና መጠማት ተገቢ ነው። 👉👉ዚማ቎ዎስ ወንጌል 5 3ፀ በመንፈስ ድሆቜ ዹሆኑ ብፁዓን ና቞ው፥ መንግሥተ ሰማያት ዚእነርሱ ናትና። 4ፀ ዚሚያዝኑ ብፁዓን ና቞ው፥ መፅናናትን ያገኛሉና። 5ፀ ዚዋሆቜ ብፁዓን ና቞ው፥ ምድርን ይወርሳሉና። 6ፀ ጜድቅን ዚሚራቡና ዹሚጠሙ ብፁዓን ና቞ው፥ ይጠግባሉና። ስለዚ ደሀ መሆን መራብ መጠማት ተገቢ ነው ። አንድ ሰው ደሃ ኹሆነ ዚሚያሰበው ለመስራት ለመለወጥ ሌላው እንዲሚዳው መጠዹቅ መቀበልን ሁሌም ዚሚያስበው ። በመንፈስም ደሃ ስንሆን ሁሌም እንጠይቃለን ለመቀበል እንጓጓለን ሁሌም ሰማይ ሰማይን እንናፍቃለን 🔥ለመቀበል 👉መለመን ስንለምን መቌም ቢሆን አምነን እንጂ በጥርጣሬ መሆን ዚለበትም። 👉👉" ሁለት አሳብ ላለው በመንገዱም ሁሉ ለሚወላውል ለዚያ ሰው ኚጌታ ዘንድ አንዳቜ እንዲያገኝ አይምሰለው።" (ዚያዕቆብ መልእክት 1:7-8) 🔥በእምነት እንጠይቅ 👉👉" እንኪያስ እናንተ ክፉዎቜ ስትሆኑ ለልጆቻቜሁ መልካም ስጊታ መስጠት ካወቃቜሁ፥ በሰማይ ያለው አባት ለሚለምኑት እንዎት አብልጊ መንፈስ ቅዱስን ይሰጣ቞ው?" (ዚሉቃስ ወንጌል 11:13) 👉👉" ዹሚለምን ሁሉ ይቀበላልና፥ ዹሚፈልግም ያገኛል፥ መዝጊያውንም ለሚያንኳኳው ይኚፈትለታል።" (ዚሉቃስ ወንጌል 11:10) 🔥ስለዚ ስንለምን እንደሚሰጠን መሆን አለበት። ምክንያቱም 👉👉" እግዚአብሔር ይላል። በመጚሚሻው ቀን እንዲህ ይሆናልፀ ሥጋ በለበሰ ሁሉ ላይ ኹመንፈሮ አፈሳለሁፀ ወንዶቜና ሎቶቜ ልጆቻቜሁም ትንቢት ይናገራሉ፥ ጎበዞቻቜሁም ራእይ ያያሉ፥ ሜማግሌዎቻቜሁም ሕልም ያልማሉፀ" (ዚሐዋርያት ሥራ 2:17) ይህ ዹሚሆነው ስናምን ነው ለመሞላት ስንፈቅድ ነው ። 👉👉" እናንተ ዚተጠማቜሁ ሁሉ፥ ወደ ውኃ ኑ፥ ገንዘብም ዚሌላቜሁ ኑና ግዙ ብሉምፀ ኑ ያለ ገንዘብም ያለ ዋጋም ዹወይን ጠጅና ወተት ግዙ። " (ትንቢተ ኢሳይያስ 55:1) ወደ እግዚአብሔር መምጣት ተገቢ ነው ። ✍✍ዚኢዚሱስ ወገን ለመሆን መንፈስ ቅድስ ወሳኝ ነው ። " እናንተ ግን ዚእግዚአብሔር መንፈስ በእናንተ ዘንድ ቢኖር፥ በመንፈስ እንጂ በሥጋ አይደላቜሁም። ዚክርስቶስ መንፈስ ዹሌለው ኹሆነ ግን ይኾው ዚእርሱ ወገን አይደለም።" (ወደ ሮሜ ሰዎቜ 8:9) 🔥መንፈስ ቅድስ ዚእርስታቜን መያዢያ ነው ። 👉👉 " እናንተም ደግሞ ዚእውነትን ቃል፥ ይኾውም ዚመዳናቜሁን ወንጌል፥ ሰምታቜሁ ደግሞም በክርስቶስ አምናቜሁ፥ በተስፋው መንፈስ በመንፈስ ቅዱስ ታተማቜሁፀ" (ወደ ኀፌሶን ሰዎቜ 1:13) " 🔥እርሱም ዚርስታቜን መያዣ ነው፥ ለእግዚአብሔር ያለውን ሁሉ እስኪዋጅ ድሚስ፥ ይህም ለክብሩ ምስጋና ይሆናል።" (ወደ ኀፌሶን ሰዎቜ 1:14) ሁሌም መንፈስ ቅድስን መለመን እና ያለንን መመዘን ተገቢ ነው ። አምስቱ ቆነጃጂት ጉድለታ቞ውን ዚተመለኚቱት ሙሜራው ሲመጣነው ። ☄ኢዚሱስ መቜ ይመጣል? ☄እኛ ኹዚ ምድር መቜ እንለያለን? ✍✍አናውቅም ። ስለዚ ሁሌም እራሳቜንን እንፈትሜ ። 👉👉" ሳታቋርጡ ጞልዩፀ በሁሉ አመስግኑፀ ይህ ዚእግዚአብሔር ፈቃድ በክርስቶስ ኢዚሱስእናንተ ነውና።" (1ኛ ወደ ተሰሎንቄ ሰዎቜ 5:17-18) ኹክፉ ነገር መራቅ አለብን ። ምክንያቱም :- 👉👉" ለቀዛም ቀን ዚታተማቜሁበትን ቅዱሱን ዚእግዚአብሔርን መንፈስ አታሳዝኑ።" (ወደ ኀፌሶን ሰዎቜ 4:30)

##12ቱ_ዚአገልግሎት_እንቅፋቶቜ 1/👉 #ትህቢት ለራስ ያለን ግምት ኹፍ አድርጎ መመልኚት(ኩራት) 👉ትህቢት አንዱ ዚአገልግሎት እንቅፋት ነው። 2/👉 #ኹመፀለይ_መድኚም ፀሎት ኹአምላክ ጋር ያለን ሕብሚት ነው። ዹማይፀልይ አገልጋይ ዚሚሰራ ፀጋ ዚለውም። 3/👉 #ያለ_እሚፍት_ማገልገል ። ያለ እሚፍት በማገልገል እግዚአብሔርን ደስ አሰኛለው ብለን እናስብ ይሆናል😁 ነገር ግን እሱ በራሱ ዚአገልግሎት እንቅፋት ነው። ምክንያቱም ዚዝግጅት ጊዜ ዹለንም ማለት ዹምናገለግለው አገልግሎት ውጀታማ አገልግሎት አይደለም ማለት ነው። 4/👉 #ዓለምን_መውደድ በዓለም ፍቅር ተነድፎ ኚአገልግሎት ዹተሰናኹለው ዎማስ ህያው ምስክር ነው። ዓለምን መውደድ ዚአገልግሎት እንቅፋት ነው። 5/👉 #በእግዚአብሔር_ቃል_አለመሞላት በቂ መፅሐፍ ቅዱሳዊ እውቀት ማጣት ሰሚውንም ሰባኪውንም ተጠራጣሪና ጭብጥ አልባ መልዕክት ሰጪ በማድሚግ ኚአገልግሎት ውጭ ዚማድሚግ አቅም አለው። 6/👉 #ዚገንዘብ_ፍቅር ቁስ ተኮር ፍላጎት። አገልግሎትን በቁስ ሚዛን መለካት ዚአገልግሎት እንቅፋት ነው። 7/👉 #ዚስጋ_ሥራ እንደ ዝሙት ስካር ርኩሰት ያሉ ልምምዶቜና ምኞቶቜ ዚአገልግሎት እንቅፋት ና቞ው። ሰይጣን በስጋዊ ምኞቶቻቜን እንደ ሚያጠምድ መዘንጋት ዚለብንም። 8/👉 #ተስፋ_መቁሚጥ ተስፋ መቁሚጥ ዚሚመጣው በቜግርና በፈተና ጊዜያቜን ኹሚመነጭ ፍርሃት በመነሳት ነው። ለምሳሌ ዚኀማውስ መንገደኞቜ ዹዚህ እንቅፋት ሰለባ ምሳሌ ና቞ው። 9/👉 #ዚምህሚት_ልብ_ማጣት ይቅር ባይ ያልሆንን እንደ ሆነ ይቅር ያለንን አምላክ ልናገለግለው አንቜልም። አገልግሎትና ምህሚት ዚማይነጣጠሉ ተጣማሪ ና቞ው። 10/👉 #አለመታዘዝ ለእግዚአብሔርና ለቃለ እግዝአብሔር አለመታዘዝ ለመንፈሳዊ ስርዓት አለመገዛት ዚአገልግሎት እንቅፋት ነው። 11/👉 #አጉል_ፉክክር ኚሌሎቜ አገልጋዮቜ ጋር ትኚሻ መለካካት። ይህ በደቀ መዛሙርቱ መካኚል ተኚስቶ ነበር። #ኢዚሱስም_አለ 👉ማ቎ዎስ 20 ²⁶ በእናንተስ እንዲህ አይደለምፀ ነገር ግን ማንም ኚእናንተ ታላቅ ሊሆን ዚሚወድ ዚእናንተ አገልጋይ ይሁን፥ ²⁷ ኚእናንተም ማንም ፊተኛ ሊሆን ዚሚወድ ዚእናንተ ባሪያ ይሁንፀ 👉መንፈሳዊ ታላቅነት ያለው ሌሎቜን በማተለቅ ውስጥ እንደሆነ ልናውቅ ይገባል። 12/👉 #ዚማያንፁ_ንግግሮቜ ዚማያንፁ ንግግሮቜ ዚአገልግሎት እንቅፋት ና቞ው። 👉ኚአፍ ዚሚወጣ ግን ኚልብ ይወጣል፥ ሰውንም ዚሚያሚክሰው ያ ነው።   ማ቎ዎስ 15፥18 👉ምንጭስ ኚአንድ አፍ ዚሚጣፍጥንና ዹሚመርን ውኃ ያመነጫልን?”   ያዕቆብ 3፥11 ተባሚኩ❀💥 ኚአገልግሎት እንቅፋቶቜ ተጠበቁ። እግዚአብሔር ይጠብቃቜሁ😍❀💥 @MARANATHAWOCH @MARANATHAWOCH

መጎናጞፊያ_ተቀበል_ለምታስቀጥለው አንድ ብቻውን ሳለ ዚጠራው እንደ ምድር አሾዋ እንደማይቆጠሚው እንደሰማይ ኚዋክብት እንደማይገመተው ገና እባርክሃለሁ ገና አበዛሃለሁ ያለው መንገዱ ቢኚብድም በቃሉ ታማኝ ነው አብርሃም በመታዘዝ  ልጁን በመሰዋት ይስሐቅ  ዹተደፈኑ ጉድጓዶቜን በመክፈት ያዕቆብ ታግሎ ተቀብሎ በሚኚት አሾንፎ አሻገሚ  ዚአባቶቹን እምነት ሙሮም ተተካ ሊቆም ለነፃነት ቀኑ ጹልሞ ሰማዩ ድም በተፋበት አዳኝ ጠፍቶ ተስፋ በጚለመበት ብዙ አሳለፈ መኚራና ጭንቀት እጅ ሳይሰጥ ሳይንበሚኚክ ቆመ ለተጠራለት ዚእግዚአብሔር ባሕርይ ሲጠራ አገልጋይ በመጀመሪያ መጚሚሻውን ዹሚናገር ነው ዹመሀሉ ጉዞ ታግሎ በማሾነፍ  ነው ዚእግዚአብሔር አገልጋይ ሕይወቱ ኚእግዚአብሔር ዚሚያታግል ለሕዝቡ አለው መኚራ ማይታለፍ ሚመስል ጠቊት መጠበቁ ግልገልና በግ ማሰማራት ጥበብ ይፈልጋል ያስኚፍላል መስዋዕትነት ዘጠና ዘጠኙ ተትቶ አንዱ እንዳይጠፋ ሁሉን በፍቅር መያዙ እይታን እያሰፋ መኚራና ቜግር ማጣቱ እዚጎሰመ ስጋን በጥርስ ነክሶ ይኖራል ተስፋን እያለመለመ ጉዞው  ሲኚብድ አቅም ሲታጣ መኚራው ቜግሩ ኚብዶ ሲያንገላታ ሚሀብ ቞ነፈሩ እጅጉን ሲቀጣ ፈተናው በዝቶ እንደ ዘይት ሲያንጣጣ እኔ አለሁልህ አይዞህ እያለ ሚያፅናና ኚመንፈሱ ዚሚያፈስ ጠማማውን ሚያቃና አለ እግዚአብሔር ለአገልጋዩ ልቡ ለቀና እንዲህ እያሉ ኢዚሱስን አገልግለው ያለፉ እድሜያ቞ውን በሙሉ በወንጌል ያሳለፉ ዚመዳንን ወንጌል ዚሰበኩ ለጠፉ ለኛ ለዚህ ትውልድ  ዚሚያስተላልፉት አለ እንድ ነገር በደማቾው ዚፃፉት አለ መጎናፀፊያ ዕጥፍ ቅባት ያለበት ኹኋላቾው ዚጣሉት ለእውነት ወንጌል እነሱ ለተጠሩት እንዲህ ነው ሕይወታ቞ው በእግዚአብሔር ዚተጠሩት ብዙ ብል ብዙው ይቀራል ስለአገልጋዩ ያሳለፈውን ባነሳ ገና ሚያሳልፈው ገና ይቀራል /2* ዚሕይወታ቞ው መንገድ ኚዚሱስ ጋር ያሳለፉት ለኛ ለዚህ ትውልድ  ዚሚያስተላልፉት መጎናጞፊያ   አለ በእጥፍ ዚተቀባ ትውልድ ንቃና ትኩር ብለህ  ተመልኚት አንተም ለምታስቀጥለው  ወንጌል ለእውነት ራስህን አዘጋጅ  በልመና በፀሎት ራስህን አዘጋጅ በእጥፍ ለመቀባት ራስህን አዘጋጅ አንተም ለማስቀጠል ዚኀልያስ ዘመን አሁን ተፈፀመ ኀልሳዕ ተተካ በእጥፍ መንፈስ ታተመ መጎናጞፊያው እንዳያልፍህ በርታ ተነሳ ምታስቀጥል ትውልድ በአባቶቜ እጥፍ መንፈስ ስለዚህ ንቃ በፀሎት ልብህ ይፍሰስ ተቀበል እንደ ኀልሳዕ  መጎናጞፊያ አስቀጥል በዘመንህ በሁለት እጥፍ መንፈስ። 2ኛ ነገሥት 2:11_14 ሲሄዱምፊ እያዘገሙም ሲጫወቱ፥ እነሆ፥ ዚእሳት ሰሹገላና ዚእሳት ፈሚሶቜ በመካኚላ቞ው ገብተው ኚፈሉአ቞ውፀ ኀልያስም በዐውሎ ነፋስ ወደ ሰማይ ወጣ። ኀልሳዕም አይቶፊ አባ቎ አባ቎ ሆይ፥ ዚእስራኀል ሰሹገላና ፈሚሰኞቜ፥ ብሎ ጮኞ። ኚዚያም ወዲያ አላዚውምፀ ልብሱንም ይዞ ኚሁለት ተሚተሚው። ኚኀልያስም ዹወደቀውን መጐናጞፊያ አነሣ፥ ተመልሶም በዮርዳኖስ ዳር ቆመ። ኚኀልያስም ዹወደቀውን መጎናጞፊያ ወስዶ ውኃውን መታናፊ ዚኀልያስ አምላክ እግዚአብሔር ወዎት ነው? አለፀ ውኃውንም በመታ ጊዜ ወዲህና ወዲያ ተኚፈለፀ ኀልሳዕም ተሻገሚ።          @MARANATHAWOCH @MARANATHAWOCH

(2) ዹቀጠለው ⬆ - ዚአዳም ሥጋና ደም ዚሚያድን ቢሆን ወንድም ወንድሙን አያድንም ሰውም አያድንም ተብሎ ባልተፃፈም ነበር። - በዘኁልቁ 21÷4-9 እንደተፃፈው ሙሮ -በእባብ ተነድፎ ለሞተው ሰው ሁሉ ኹነደፈው እባብ አንዱ ሰቅሎ ሰዉ ሁሉ አይቶት በዳነ ነበር ዚናስ እባብ መስራትም ባልፈለገ ነበር ↪ ዹነደፈው  እባብ ማዳን አይቜልም ዹወደቀውም ዚአዳም ማዳን አይቜልም       - ዚናስ እባብ እንደ ተዘጋጀ       - ልዩ ሥጋና ደም ነው ዹተዘጋጀው ⭐ ምን አይነት ሰው ነው ዹተሰቀለው        - ዮሐንስ 3:13 ኹሰማይ ዹወሹደ       - ዮሐንስ 1:14 ቃል ሥጋ ዹሆነ          1ኛ ቆሮንቶስ 15÷45 ዚመጀመሪያው አዳም ሣይሆን ሁለተኛ አዳም          1ኛ ቆሮንቶስ 15÷47 ዚመጀመሪያው ሰው ሣይሆን አዲሱ ሰው           ፊልጵስዩስ 3÷21 ክቡር ሥጋውን  እንድንመስል ዹተዋሹደውን ሥጋቜንን ይለውጣል ተብሎ እንደ ተፃፈው ነው 📌 ስለ ሰው ልጆቜ ዹተሰቀለውን ኢዚሱስ ዚምናይበት አስተያዚታቜን አስተካክለን ብናዚው መዳን እናገኛለን። 📌 አንድ ሰው ነው ዹተሰቀለው ብንል መዳን አናገኝም 📌 ኢዚሱስ አንድ ተራ ሰው አይደለምና እናም ደግሞ ሰውም አይድንም ተብሎ ተፅፎአልና። ↪ በመዝ ዳዊት(40)÷6 መስዋዕትንና ቁርባንን አልወደድህም ሥጋን አዘጋጀህልኝ  - ዹሚቃጠለውንና ስለ ኃጢአት ዹሚቀርበውን መስዋዕት አልሻህም አለ          ሥጋን አዘጋጀህልኝ  ⭐ ዹተሰቀለው ኢዚሱስ ዹዓለምን ኃጢአት እንዲያስወግድ ዹተዘጋጀ ልዩ ሥጋና ደም ነው።            ዕብ 10÷5-10 ዹተዘጋጀው ዚኢዚሱስ ክርስቶስን ሥጋ አንድ ጊዜ ፈፅሞ በማቅሚብ ተቀድሰናል      ስለዚህ ዹተሰቀለውን ኢዚሱስ ⭐ እንደ ባህሪው ስናዚው ነው ዚምንድነው ዹነደፈ እባብ ማዳን እንደማይቻለው ሁሉ ኃጢአትን ወደ ዓለም ያገባው አዳም ኃጢአትን ማውጣት አይቜልም (ኚኃጢአት ማዳን አይቜልም)             ኢሣ 33÷13-22 ቁ.17 ዓይኖቜህ ንጉሥን በውበቱ ያዩታል። ይላል ዹተሰቀለውን በማዚት ዹሚገኝ መዳን                  ቆላ 2÷14 ↪ በእኛ ላይ ዹነበሹውን ዹሚቃወመንንም በትዕዛዝ ዹተፃፈውን ዚዕዳ ፅህፈት ደመሰሰው እርሱንም በመስቀል ጠርቆ ኚመንገድ አስወግዶታል አለቅነትንና ስልጣናትን ገፎ ድል በመንሳት በእርሱ እያዞራ቞ው በግልጥ አሣያ቞ው። -ኃጢአት ዚሰራው አዳም ኃጢአትን በመስቀል ጠርቆ ኚመንገድ ማስወገድ አይቜልም ። ቃል ስጋ ዹሆነው ኢዚሱስ ዮሐንስ 1÷14 - ቅዱስና ያለ ተንኮል ነውር ዚሌለበት ኚኃጢአተኞቜም ዹተለዹው ኢዚሱስ ዕብ 7:26 - ኀጢአትን ሊያስወግድ ዹተገለጠና በእርሱ ኀጢአት ዚሌለበት ኢዚሱስ 1ኛ ዮሐንስ  3:15 - በቀራንዮ ተራራ ላይ ተሰቅሎ ኀጢአታቜንን በመስቀል ጠርቆ  አስወግዷል እርሱን ስናይ መዳንን እናገኛለን።           በዘፍጥሚት 22÷14 - አብርሃም በይስሃቅ ፈንታ ዹሚሰዋ በግ አይቶ ኹሰዋው በኋላ ቊታው ያህዌ ይርኀ ብሎ ጠራው         በእግዚአብሔር ተራራ ይታያል                ኀፌሶን 2÷14-16           ዹተሰቀለው ኢዚሱስ ስናይ     - ሠላማቜን ነው    - በአዋጅ ዹተነገሹውን ትዕዛዝ ሜሮልናል    - ዚጥል ግድግዳ አፍርሶልናል    - ጥልን በመስቀሉ ገድሎልናል    - ኚእግዚአብሔር ጋር አስታርቆናል    - ወደ መንግስቱ መግባት አግኝተናል    - ይህ ሁሉ ዹሆነው እናስተውል            በእርሱ ስራ ነው (በቀራንዮ            መስቀል ላይ በሰራው ስራ) ነው ዹተሰቀለውን በማዚት ዹሚገኝ መዳን     ዕብ 2÷2 -- ታላቅ መዳን    ዩሐ 3÷16 -- ዹዘላለም ህይወት    ዕብ 5÷9-10 -- ዹዘላለም መዳን          ሉቃ 23÷44-49 ↪ ዚመቶ አለቃው ስቅለቱን ባዚ ጊዜ እግዚአብሔርን አኹበሹ ሲያፌዝ ዹነበሹው በንቀት ሲያይ ዹነበሹው በውበቱ ሲያዚው ግን ይህ ሰው በእውነት ፃድቅ ነበሹ ብሎ እግዚአብሔርን አኹበሹ ይላል።     ወንድሞቜና እህቶቜ ስለ በደላቜን አልፎ ዹተሰጠውን በመስቀል ላይ ስለኛ ዹተሰዋውን      áŠ•áŒ‰áˆ±áŠ• በውበቱ እንዚው      á‰³áˆ‹á‰… መዳን እናገኛለን።               🙏   አሜን  🙏 @MARANATHAWOCH @MARANATHAWOCH

             ዩሐ  3÷14-15               ዘኁ   21÷4-9 ዹተሰቀለውን በማዚት ዹሚገኝ መዳን...... (1) ↪ ጌታ ኢዚሱስ በዘኁልቁ ምዕራፍ 21÷4-9 ዹተፈጾመው ታሪክ ወይም ዹነገር ጥላ ጠቅሶ ሲናገር ሙሮ በምድሚበዳ እባብን እንደሰቀለ እንዲሉ በእርሱ ዚሚያምን ሁሉ ዹዘላለም ህይወት እንዲኖሚው እንጂ እንዳይጠፋ ዹሰው ልጅ ይሰቀል ይገባዋል። ↪ በብልይ ኪዳን በእባብ ተነድፈው ዚሞቱ ሰዎቜ እባብን አይተው በህይወት ኖሩ። ሰው ዹነደፈውን እባብ ሲያይ  ይበሹግጋል / ይፈሚጥጣል / እንጂ ሊያይ አይፈቅድም ውይ ብሎ ይሮጣል እባብ ያዚ በልጥ በሹዹ እንዲሉ ማለት ነወ። እዚህ ጋ ግን ፊ ዹተለዹ ታሪክ ነው ዚተፈጞመው። ⭐ ነገሩ እንዎት ነው ብሎ መመርመር ያስፈልጋል። እስራኀላውያን አይተው ዚዳኑት ምንድን ነው ? ነድፎ ዚጚሚሳ቞ውን እባብ ነውን? እሱማ እኮ ነድፎ ገደላ቞ው። ታዲያ ምን አይነት እባብ ነው።     ° ነድፎ ዚጚሚሳ቞ው እባበብ ሳይሆን እሱን ዚሚመስል ግን ያይደለ ዚናስ እባብ ነው     ° እባብ ነው ግን ዚናስ እባብ 🔶 ወደ ነጥባቜን መለስ ሥንል 🔶 ዚእግዚአብሔር ቃል ፊ በሮሜ 5÷12-21 እንደተፃፈው በፊተኛው ሰው በደል ሰው ሁሉ ኹሞተ በፊተኛው አዳም ሰው ሁሉ ኃጢአተኛ ኹሆነ ፊ     - በፊተኛው ሰው በህይወት አይኖርም     - በፊተኛው አዳምም ፃድቅ አይሆንም              ዘፍጥሚት 22:1-14    በፊተኛው ሰው በህይወት ዹሚኖሹው    በፊተኛው አዳም ዚሚፀድቅ ቢሆን ኖሮ ↪ በሞሪያ ተራራ ላይ ይስሃቅ ይሰዋ ነበር ነገር ግን ፊ መዝሙሹ ዳዊት (49)÷7 እንደተፃፈው "ሰውም አይድንም ቀዛውን ለእግዚአብሔር አይሰጥም " ስለተባለ እግዚአብሔር ይሳሃቅን ኚመስዋት አድኖ ዹአለምን ለኃጢአት ዚሚያስወግደውን ዚእግዚአብሔር በግ ጥላ ዹሆነውን በግ እንዲሰዋ አደሚገ። ዮሐንስ 1÷29 ዹአለምን ኀጢአት    ዚሚያስወግድ ዚእግዚአብሔር በግ ዹሰው ኃጢአት ፊ በአዳም መስዋዕት ወይም ደግሞ አዳም በሚቀርበው መስዋዕት ዹሚሠሹይ አደለም። ስለዚህም ነው ፊ ዚአዳምን ዘር ሁሉ ነፃ ዚሚያወጣዉን ዹሰው ልጅ (ኢዚሱስ ክርስቶስ) ሊሰቀል ዚተገባው። ዕብ 2:9-110 ነገር ግን በእግዚአብሔር ፀጋ ስለ ሰው ሞትን ይቀምስ ዘንድ ብዙ ልጆቜን ወደ ክብር ሲያመጣ ዚመዳና቞ው ራስ በመኚራ ይጻፍም ዘንድ ኚእርሱ ዚተነሳ ፊ               - ሁሉ በእርሱ ለሆነ               - ለእርሱ ተገብቷል ⭐ ብዙ ልጆቜን ወደ ክብር ሊያመጣና ዚመዳና቞ውን ራስ በመኚራ እንዲፈፀም ↪ ዚርሱ መሰቀል ዚተገባ ሆኖዋል። ↩   ዚትምህርታቜን ርዕስ ለማስታወስ ዹተሰቀለውን በማዚት ዹሚገኝ መዳን ዕብ 2÷14-15 ፊ እንግዲህ ልጆቜ በሥጋና በደም ሥለሚካፈሉ እርሱ ደግሞ በሞተ ላይ ስልጣን ያለውን በሞት እንዲሜር ይኾውም ዲያቢሎስ ነው። ''በ1ኛዩሐ 3÷8'' ዚዲያቢሎስን ሥራ እንዲያፈርስ ዚእግዚአብሔር ልጅ ተገለጠ ተብሎ እንደተፃፈው በህይወታ቞ው ሁሉ ስለ ሞት ፍርሃት በባርነት ይታሰሩ ዚነበሩት ሁሉ ነፃ እንዲያወጣ በሥጋና በደም እንዲሁ ተኹፈለ ይላል። ↪ ተመልኚቱ አስተውሉ እዩም ↩         በምን አይነት ሥጋና ደም ? ⭐ ዚአዳም ዓይነቱ ስጋና ደም እንዳትሉ ⭐ ዚአዳም ሥጋ ዚሚያድን ቢሆን                   ይስሃቅ ይሰዋ ነበር ይቀጥላል....... @MARANATHAWOCH @MARANATHAWOCH

በኢትዮጵያ ሐዋርያዊት ቀ቎ክርስትያን ዚአለታ ቅርንጫፍ ሰበካ በአለታ ጩኮ ኹተማ ንዑስ ዚቀተሳይዳ አጥብያ ቅጥር ግቢ ሲካሄድ ዹነበሹ 2ተኛ ዙር ዚወጣቶቜ ዓመታዊ ኮንፈራንስ በሰላም ዹተጠናቀቀ ሲሆን በ
+9
በኢትዮጵያ ሐዋርያዊት ቀ቎ክርስትያን ዚአለታ ቅርንጫፍ ሰበካ በአለታ ጩኮ ኹተማ ንዑስ ዚቀተሳይዳ አጥብያ ቅጥር ግቢ ሲካሄድ ዹነበሹ 2ተኛ ዙር ዚወጣቶቜ ዓመታዊ ኮንፈራንስ በሰላም ዹተጠናቀቀ ሲሆን በዚህ ጉባኀ ሶስት ነፍሳት በኢዚሱስ ሲጠመቁ አንድ ደግሞ ኚአጋንንት ወጥተዋል፡፡ ✍ይህ ዚእውነት ወንጌል ገና ይሰበካል አንዱ አምላክ ሁሉን ይወርሳል፡፡ 👉እናወርሳለን✅ 👉እናጠምቃለን✅ 👉እንበዛለን🙏🙏 @MARANATHAWOCH

⬆ - ዚአዳም ሥጋና ደም ዚሚያድን ቢሆን ወንድም ወንድሙን አያድንም ሰውም አያድንም ተብሎ ባልተፃፈም ነበር። - በዘኁልቁ 21÷4-9 እንደተፃፈው ሙሮ -በእባብ ተነድፎ ለሞተው ሰው ሁሉ ኹነደፈው እባብ አንዱ ሰቅሎ ሰዉ ሁሉ አይቶት በዳነ ነበር ዚናስ እባብ መስራትም ባልፈለገ ነበር ↪ ዹነደፈው  እባብ ማዳን አይቜልም ዹወደቀውም ዚአዳም ማዳን አይቜልም       - ዚናስ እባብ እንደ ተዘጋጀ       - ልዩ ሥጋና ደም ነው ዹተዘጋጀው ⭐ ምን አይነት ሰው ነው ዹተሰቀለው        - ዮሐንስ 3:13 ኹሰማይ ዹወሹደ       - ዮሐንስ 1:14 ቃል ሥጋ ዹሆነ          1ኛ ቆሮንቶስ 15÷45 ዚመጀመሪያው አዳም ሣይሆን ሁለተኛ አዳም          1ኛ ቆሮንቶስ 15÷47 ዚመጀመሪያው ሰው ሣይሆን አዲሱ ሰው           ፊልጵስዩስ 3÷21 ክቡር ሥጋውን  እንድንመስል ዹተዋሹደውን ሥጋቜንን ይለውጣል ተብሎ እንደ ተፃፈው ነው 📌 ስለ ሰው ልጆቜ ዹተሰቀለውን ኢዚሱስ ዚምናይበት አስተያዚታቜን አስተካክለን ብናዚው መዳን እናገኛለን። 📌 አንድ ሰው ነው ዹተሰቀለው ብንል መዳን አናገኝም 📌 ኢዚሱስ አንድ ተራ ሰው አይደለምና እናም ደግሞ ሰውም አይድንም ተብሎ ተፅፎአልና። ↪ በመዝ ዳዊት(40)÷6 መስዋዕትንና ቁርባንን አልወደድህም ሥጋን አዘጋጀህልኝ  - ዹሚቃጠለውንና ስለ ኃጢአት ዹሚቀርበውን መስዋዕት አልሻህም አለ          ሥጋን አዘጋጀህልኝ  ⭐ ዹተሰቀለው ኢዚሱስ ዹዓለምን ኃጢአት እንዲያስወግድ ዹተዘጋጀ ልዩ ሥጋና ደም ነው።            ዕብ 10÷5-10 ዹተዘጋጀው ዚኢዚሱስ ክርስቶስን ሥጋ አንድ ጊዜ ፈፅሞ በማቅሚብ ተቀድሰናል      ስለዚህ ዹተሰቀለውን ኢዚሱስ ⭐ እንደ ባህሪው ስናዚው ነው ዚምንድነው ዹነደፈ እባብ ማዳን እንደማይቻለው ሁሉ ኃጢአትን ወደ ዓለም ያገባው አዳም ኃጢአትን ማውጣት አይቜልም (ኚኃጢአት ማዳን አይቜልም)             ኢሣ 33÷13-22 ቁ.17 ዓይኖቜህ ንጉሥን በውበቱ ያዩታል። ይላል ዹተሰቀለውን በማዚት ዹሚገኝ መዳን                  ቆላ 2÷14 ↪ በእኛ ላይ ዹነበሹውን ዹሚቃወመንንም በትዕዛዝ ዹተፃፈውን ዚዕዳ ፅህፈት ደመሰሰው እርሱንም በመስቀል ጠርቆ ኚመንገድ አስወግዶታል አለቅነትንና ስልጣናትን ገፎ ድል በመንሳት በእርሱ እያዞራ቞ው በግልጥ አሣያ቞ው። -ኃጢአት ዚሰራው አዳም ኃጢአትን በመስቀል ጠርቆ ኚመንገድ ማስወገድ አይቜልም ። ቃል ስጋ ዹሆነው ኢዚሱስ ዮሐንስ 1÷14 - ቅዱስና ያለ ተንኮል ነውር ዚሌለበት ኚኃጢአተኞቜም ዹተለዹው ኢዚሱስ ዕብ 7:26 - ኀጢአትን ሊያስወግድ ዹተገለጠና በእርሱ ኀጢአት ዚሌለበት ኢዚሱስ 1ኛ ዮሐንስ  3:15 - በቀራንዮ ተራራ ላይ ተሰቅሎ ኀጢአታቜንን በመስቀል ጠርቆ  አስወግዷል እርሱን ስናይ መዳንን እናገኛለን።           በዘፍጥሚት 22÷14 - አብርሃም በይስሃቅ ፈንታ ዹሚሰዋ በግ አይቶ ኹሰዋው በኋላ ቊታው ያህዌ ይርኀ ብሎ ጠራው         በእግዚአብሔር ተራራ ይታያል                ኀፌሶን 2÷14-16           ዹተሰቀለው ኢዚሱስ ስናይ     - ሠላማቜን ነው    - በአዋጅ ዹተነገሹውን ትዕዛዝ ሜሮልናል    - ዚጥል ግድግዳ አፍርሶልናል    - ጥልን በመስቀሉ ገድሎልናል    - ኚእግዚአብሔር ጋር አስታርቆናል    - ወደ መንግስቱ መግባት አግኝተናል    - ይህ ሁሉ ዹሆነው እናስተውል            በእርሱ ስራ ነው (በቀራንዮ            መስቀል ላይ በሰራው ስራ) ነው ዹተሰቀለውን በማዚት ዹሚገኝ መዳን     ዕብ 2÷2 -- ታላቅ መዳን    ዩሐ 3÷16 -- ዹዘላለም ህይወት    ዕብ 5÷9-10 -- ዹዘላለም መዳን          ሉቃ 23÷44-49 ↪ ዚመቶ አለቃው ስቅለቱን ባዚ ጊዜ እግዚአብሔርን አኹበሹ ሲያፌዝ ዹነበሹው በንቀት ሲያይ ዹነበሹው በውበቱ ሲያዚው ግን ይህ ሰው በእውነት ፃድቅ ነበሹ ብሎ እግዚአብሔርን አኹበሹ ይላል።     ወንድሞቜና እህቶቜ ስለ በደላቜን አልፎ ዹተሰጠውን በመስቀል ላይ ስለኛ ዹተሰዋውን      áŠ•áŒ‰áˆ±áŠ• በውበቱ እንዚው      á‰³áˆ‹á‰… መዳን እናገኛለን።               🙏   አሜን  🙏 @MARANATHAWOCH @MARANATHAWOCH

ክብር አለኝ ለአንተ
ክብር አለኝ ላንተ *2 ዚማያመጠን*4 ምስክርህ ነኝ ለማዳንህ ዚሱሎ እኔ አንተን ብዬ አፍሬ አላውቅም በህይወቮ ዹፍቅርህ ሚዛን እያደላልኝ ወደእኔ አለው በቀትህ ምህሚትህ ኚቊት ዘመኔን ባመልክህ ያንስብሃል ብዘምር ያንስብሃል በእውነት ግነን ኹፍ በል ይታይ ማንነትህ 1) በእውነት ቃል አስበህ ፈጥሚህ ይህው አኖርኹኝ ዘመኔን በሙሉ ይዘህ እዚመራህኝ ምን አለ ያላንተ ያላለፍኩት ነገር ጌታዬ አምላኬ ምስጋናዬ እኮ ነህ ያማሚ ዜማ ዚሚገባህ እዚሱስ አለ አለ በፂዮን አለ አለ*2 ዚማይቋሚጥ ምስጋና አምልኮ ለአንተ አለ አለ በፂዮን አለ አለ *2 ይሰማ ያስተጋባ ዚእልልታው ድምፅ ይውጣ ሰማይ ልዩ ነህ ዚእኔ ጌታ ኚአማልክት ሁሉ ልቀህ ታይ አይነስብህ ኹኔ ምስጋና ትልቅ ነህ ትልቅ ልበል ገናና አይነስብህ ኹኔ ዝማሬ ለአምላክነትህ ትዋሚድ ክብሬ 2) ማሹጌ ልበልህ ብርቱ ነህ መጠጊያዬ ማዳንህን ስራህን አይቌዋለው ባይኔ ባመታት መሀል ቃልህ ተፈፀመልኝ ትኑርልኝ ነፍሮ ታመልክሃለቜ ዘወትር ዚልቀ ጉልበት (ይንበርኹክልህ)*2 ውለታህ አለብኝ ክበር ልበልህ ያበቃልኝን ዘመን አሻግሚህ ዛሬን አቆምኹኝ ምስጋናን ሞልተህ መዝሙሬ ሀሌሉያ ነው ስጊታዬም ምስጋና ነው ሳመልክህ *3 ብቻ ኖራለው

Z Dawit Dabaro reggea tunse 33.mp35.23 MB

Z Dawit Dabaro buuxe afi 11.mp35.10 MB

Z Dawit Dabaro disk tayinse 22.mp34.19 MB

22 Fikire Girma (9) Track 22.mp34.54 MB

22 Fikire Girma (12) Track 22.mp34.99 MB

22 Fikire Girma (11) Track 22.mp35.88 MB

22 Fikire Girma (6) Track 22 (1).mp35.73 MB

22 Fikire Girma (10) Track 22.mp36.30 MB

22 Fikire Girma (7) Track 22.mp35.93 MB