uz
Feedback
ማራናታ.....MARANATHA

ማራናታ.....MARANATHA

Kanalga Telegram’da o‘tish

ለአንዳንዶች የሚዘገይ እንደምመስላቸው ጌታ ሰለ ተስፋ ቃሉ አይዘገይም፥ ነገር ግን ሁሉ ወደ ንስሐ እንድደርሱ እንጅ ማንም እንዳይጠፋ ወዶ ሰለ እናንተ ይታገሳል።2ኛ ጴጥ 3፥9 ገና በጣም ጥቅት ጊዜ ነው፤ ሊመጣ ያለውም ይመጣል አይዘገይምም። ዕብራ 10፥37 የመወያያ ግሩፕ👇 @Marantawoch Inbox Comment @Thaddyapostolic

Ko'proq ko'rsatish

📈 Telegram kanali ማራናታ.....MARANATHA analitikasi

ማራናታ.....MARANATHA (@maranathawoch) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 17 330 obunachidan iborat bo'lib, Din & Maʼnaviyat toifasida 4 727-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 1 990-o'rinni egallagan.

📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika

невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 17 330 obunachiga ega bo‘ldi.

01 Sentabr, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni 313 ga, so‘nggi 24 soatda esa 20 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.

  • Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
  • Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 19.66% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 7.93% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
  • Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 3 407 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 1 375 ta ko‘rish yig‘iladi.
  • Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 23 ta reaksiya keladi.

📝 Tavsif va kontent siyosati

Muallif resursni shaxsiy fikrni ifoda etish maydoni sifatida ta’riflaydi:
ለአንዳንዶች የሚዘገይ እንደምመስላቸው ጌታ ሰለ ተስፋ ቃሉ አይዘገይም፥ ነገር ግን ሁሉ ወደ ንስሐ እንድደርሱ እንጅ ማንም እንዳይጠፋ ወዶ ሰለ እናንተ ይታገሳል።2ኛ ጴጥ 3፥9 ገና በጣም ጥቅት ጊዜ ነው፤ ሊመጣ ያለውም ይመጣል አይዘገይምም። ዕብራ 10፥37 የመወያያ ግሩፕ👇 @Marantawoch Inbox Comment @Thaddyapostolic

Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 02 Sentabr, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Din & Maʼnaviyat toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.

17 330
Obunachilar
+2024 soatlar
+877 kun
+31330 kun
Postlar arxiv
የማለዳ ትምህርት የጸሎታችን መልስ ለምን ይዘገያል? ክፍል 10 ጸሎትን የሚሰማ አምላክ ለይቶ አለማወቅ በዚህ ምድር ላይ ሰው ለሰው ደብዳቤ ስጽፍ የደብዳቤ መነሻና መድረሻ እንዳለው ሁላ ለጸሎትም መነሻና መድረሻ አለው። መነሻ ከዚህ ከሰውዬው ብሆን እንኳ መድረሻው ግን የሚሰማ አምላኬ ነው ብሎ የሚያምን አካል መኖር አለበት። ለብዙ ሰዎች ችግራቸው ግን ማን እንደሚሰማቸው ወደ ማን እንደሚጸልዩ አለማወቅ ነው። ስለዚህ ይህ ጸሎት የሚቀርብለት /የሚደርስለት/ አካል በእውነትም ጸሎታችንን ሰምቶ የሚመልስ አምላክ ነው ወይስ አይደለም የሚለውን ማወቅና ማጣራት ወሳኝ ነጥብ ነው። ሰው አምላኬ ነው ብሎ በተዘዋዋሪ መንገድ አማልክትን ማምለክ ወይም መጸለይ ይችላል። ነገር ግን ለጸሎት መልስ የሚመልሰው አንዱ እውነተኛ አምላክ እንጂ አማልክት አይደሉም ። ጸሎትን የሚሰማ አምላክ ለይቶ ሳያውቅ በየቀኑ መጾምና መጸለይ ሞኝነት ነው። ከጸሎት በፊት ሰምቶ እውነተኛ መልስ የሚሰጥ አምላክ ማወቅ ወሳኝ ነው፤ አለበለዚያ በየቀኑ ወደማይሰማ አምላክ እየጸለየ መኖር ነው። መዝ 115፥4-8 እና 135፥15-18 የአሕዛብ ጣዖታቶች የወርቅና የብር፥ የሰው እጅ ሥራ ናቸው። አፍ አላቸው አይናገሩምም፤ ዓይን አላቸው አያዩምም፤ ጆሮ አላቸው አይሰሙምም፤ አፍንጫ አላቸው አያሸትቱምም፤ እጅ አላቸው አይዳሰሱምም፤ እግር አላቸው አይሄዱምም፤ በጕሮሮአቸውም አይናገሩም። የሚሠሩአቸውም የሚያምኑባቸውም ሁሉ እንደ እነርሱ ይሁኑ። ዛሬም ወደ እኛ ዘመን ብንመጣም በተዘዋዋሪ ሰው ሁሉ ወደማይመለስ አምላክ እየጸለዬ ከኮንፈረንስ ወደ ኮንፈረንስ እየዞረ ይገኛል። አጠገባችን ያሉ ሰዎች ብዙዎችን እንታዘባለን፤ በየቀኑ የት እየጎረፈ ነው ብባል ዛሬ ያቺ ሰፈር ነብዩ እገለ መጥቷል፣ ነገም ያኛው ሰፈር የሆነ ነብይ መጣ፣ ቀጣይ ሳምንትም የሆነ ታላቅ ነብይ ሰፈራችን መጣ፣... ለኮንፈረንስም ደግሞ በየቀኑ ስም ተሰይሟል። አንዴ ነጻ የመውጣት ኮንፈረንስ፣ አንዴ የፋይናንስ ድርመሳ፣ አንዴ ከክብር ወደ ክብር የመለወጥ ኮንፈረንስ፣.... ብቻ የማይወጣላት ስም የለም። እንደዚህ እየሆነ እየባዘነ ዘመኑን እየጨረሰ ነው። ይህንን የሚሆነው ግን አንድ እውነታ አላቸው። የተሸከሙት የችግራቸው ቀምበር ሊያደርጋቸው ይችላል። ግን ቆም ብሎ የሚሰማ አምላክ የት አለ የሚለውን ማየት ተስኖአቸዋል። የእገለ አምላክ፣ የእገለ አምላክ እያሉ በየሳምንቱ አማልክትን የሚጠሩ ሆኑ። በነብያቶች ብዛት የማን አምላክ  እንደሚሰማ እራሱ አያወቁም፣ እራሳቸውን ነብያቶች ነን ብለው የሰየሙት ግን የኔው ይበልጣል፤ የኔው ይበልጣል በሚል ፉክክር በየቀኑ ማስታወቂያ እያወጡ promotion እየሰሩ የህዘብ ልብ ያወካሉ። በእግዚአብሔር ትምህርት ጸንቶ ያልቆመ ትውልድ እረኛ እንደሌላቸው መንጋ በየቀኑ በትምህርት ንፋስ እየተወሰደ ይገኛል። ይህ ምንድነው ብባል አንዳንዶቹ "ብቻ የእግዚአብሔር ቃል የሚናገርበት ቦታ ይሁን እንጅ፣ ብቻ የኔ ችግር የሚያውቅ ነብይ ይሁን እንጅ፣ ብቻ ከዚህ ከችግሬ ይዉጣ እንጂ..." እያሉ አንድም ቀን እረፍት አያገኙም። እንደው አንድ ጊዜ ከአንድ ልጅ ጋር ስለ ሐሰተኛ ነብያቶችና ስለ ስራቸው መንፈሳቸውም የጠንቆላ መንፈስ መሆኑን ስናወራ ልጁ ምን አለኝ መሰላችሁ፦ " ነብዩ የትም የትም ጠንቆላ ሰርቶ ይምጣ፣ 666 አባልም ሆኖ ብሰራ፤ ለእኔ ግን በእግዚአብሔር ቃል ተናግሮ ችግረን የሚፈታ ከሆነ ምንም ችግር የለም እቀበላለሁ" አለኝ። ምን ማለት ፈልገ ነው ሰው በዚህ ልክ ነው ከእውነተኛ አምላክ የሸሸው። ለዚህ ሰውዬ በራሱ የሚሰራ ስንት ተአምራት እያለ የኔ ነገር ከነብዩ እጅ ብቻ ነው ብሎ እንዳመነ አስቡ። በእሱ ቤት የሚሰማ አምላክ ያለው ለነብዩ ብቻ ነው እንጅ ለራሱ የሚሰማ አምላክ የለውም ማለት ነው። ብዙ ሰዎች እንደዛ የሚያስቡ አሉ። ይህ ግን ወደሚሰማ አምላክ መጸለይ ሳይሆን አማልክትን መከተል ነው። እንኳን ሄዶ መጸለይና በቤተ/ያን ውስጥ ሆኖም በልቡ እየከጀለ ልቡን ማከፋፈል፣ የኔ ነገር ነብዩ እገለ ጋር ሄጄ ብጸልይ፣ እገለ ብጸልይልኝ ይቀረፋል መሰለኝ እያለ ልቡን በዛው ሰውጋር ማንልጠል እውነተኛ አምላክ ልቡንና ኩላልቱን ስለሚመረምረው ሀሳቡ እንደተሰረቀ ያውቃልና ለጸሎቱ መልሱ አይመለስለትም። ይህ ሰውዬ በልቡ አምላክ ሳይህን አማልክት እየለመነ ነው። እግዚአብሔርም በምድር ላይ የተደነቀው ነገር ብኖር ሰው ሁሉ ወደገዛ መንገድ ሄዶ የራሱን አምላክ ፈጥሮ ወደ እርሱ /ወደ እውነተኛ አምላክ / የሚማለድ ሰው እንደሌለ ተረድቶ ነው። ፤ ሰውም እንደሌለ አየ፥ ወደ እርሱ የሚማልድ እንደሌለ ተረዳ ተደነቀም፤ ስለዚህ የገዛ ክንዱ መድኃኒት አመጣለት፥ ጽድቁም አገዘው። /ት/ኢሳ 59፥16/ ወደ ምድር ሰውን ስመለከት ከአምላክ ይልቅ የአማልክት ክብር በዝቷል፣ ሰው ሁሉ ይሰማኛል ብሎ በየቀኑ ወደ አማልክት ይማለዳል፤ ወደ እውነተኛ አምላክ የሚማለድ አጣ፣ አየ፣ ተደነቀም። እኛስ ዛሬ ወዴት እየማለድን ነን? በእርግጥ የእኛ ወንድሞችና እህቶች ለዚህ ጉዳይ ጠንቃቃዎች መሆናቸውንና አንዱ እውነተኛ አምላክ እንዳላቸው አምናለሁ። ነገር ግን አልፎ አልፎ በማወቅም ባለማወቅም በሰው ግፊት ሾልከው እናያለን ብለው የሚሄዱ ሊኖሩ ይችላሉ። በአህዛብ በኩል ያላው የሚበልጥና እነርሱ እዚህ ተቀምጠው የተጎዱ የሚመስላቸውም አይጠፉም። ነገር ግን እርግጠኛ ነኝ እንደዚህ አይነት ሰዎች( አምላክንና አማልክትን) የሚትቀላቀሉ ሰዎች በእውነት ለጸሎታችሁ መቼም መልስ አትጠብቁ፤ ይልቅ እግዚአብሔር ከቁጣ ይጠብቃችሁ። ለእኛ ግን ሰምቶ በእሳት የሚመልስ አንዱ እውነተኛ የኤልያስ አምላክ ያለን ህዝብ ነን። ነገር ግን በቤተ/ያን ውስጥ ሆናችሁ በሁለት ሀሳብ አታነክሱ፤ እግዚአብሔር አምላክ ብሆን እርሱን ተከተሉና ወደ እርሱ ጸልዩ፤ በአል/ ነብይ/ አምላክ ብሆን እርሱን ተከተሉና አምልኩ። የሚበልጠውና እናያለን!! 1ኛ ነግ 18፥24-28 እናንተ አምብቡ አደራ። የማን አምላክ መልስ እንደሚሰጥ በግልጽ ተቀምጧል። አምላካችሁን ሳትለዩ እየጸለያችሁ ዘመናችሁን አትጨርሱ። እኛ ግን ጸሎትን ሰምቶ የሚመልስ አንዱን የኤልያስ አምላክ የሚናመልክና ወደ እርሱ የሚንጸልይ የአንዱ ሰዎች ነን። @MARANATHAWOCH @MARANATHAWOCH INBOX @Thaddyapostolic GROUP @Marantawoch

ያ-ክብር-ይገለጥAddisaba-sebeka-Apostolic-song.m4a8.45 MB

ይቅር የሚል አምላክ!
ዘወትር ይቅርታ መጠየቅ ንሰሃ መግባት ከኢየሱስ ጋር ያለንን የአብሮነት መንገድ ብሩህ ያደርገዋል።
ማቴዎስ 6፡9-13 12፤ እኛም ደግሞ የበደሉንን ይቅር እንደምንል፥    በደላችንን ይቅር በለን፤ ኢየሱስ በየቀኑ ይቅርታ መጠየቅን ጨምሮ ለሚከተሉት የጸሎት ምሳሌ ሰጥቷቸዋል። አዘውትሮ ንስሐ መግባትና ይቅር በለን ማለት ከእግዚአብሔር ጋር ያለንን ህብረት የምናስተካክልበት ነው። በኢየሱስ ስም ስንጠመቅ ኃጢአታችን ለዘላለም ተሰርዮልናል—ያለፈው፣ የአሁን እና የወደፊት በደሎቻችን እድፍ ይደመሰሳል። የኃጢአት ዝንባሌ ግን የሰው ልጅ ልምምድ አካል ሆኖ ይቆያል፣ ምንም እንኳን ክርስቶስን እየመሰልን በሄድን ቁጥር ተፅዕኖው እየቀነሰ ቢሄድም። ከኢየሱስ በስተቀር ማንም ፍጹም አይደለም። ስለዚህ፣ በምድር ላይ ሳለን ሁላችንም ኃጢአትና መዘዙ ያገኘናል። በየእለቱ ይቅርታን እንድንፈልግ የጌታ ኢየሱስ ማሳሰቢያ ኃጢአታችንን እንድንናዘዝ እና ከኃጥያት እንድንርቅ ነው ይቅር ስለተባልን። የእግዚአብሔር ጸጋ የኃጢአት ፈቃድ አይደለም። ይልቁንም ጽድቅን ያለማቋረጥ ለመከታተል ምክንያት ነው። መጥፎ አመለካከቶች፣ ግድየለሽ ድርጊቶች እና ደግነት የጎደለው ንግግር እኛ በክርስቶስ አዲስ ፍጥረት ለመሆናችን አይመጥኑም። 1ኛ ዮሐንስ 1: 9፤ በኃጢአታችን ብንናዘዝ ኃጢአታችንን ይቅር ሊለን ከዓመፃም ሁሉ ሊያነጻን የታመነና ጻድቅ ነው። እርሱ ይቅር ለማለት ከታመነ እኛ ንሰሃ እየገቡ በየእለቱ ለመፀለይ አንታክት። ኃጥያት እንቅፋት እንዳይሆንብን። መልካምና የተባረከ ምሽት ይሁንላችሁ @MARANATHAWOCH

#ማነው #ሚታመነው ? አንድ ልናስተውል የሚገባን ነገር ቢኖር  እግዚአብሔርን  የምታውቅ እና በእግዚአብሔር የምትታወቅ አንዲት እምነት ሃይማኖት እዳለች ነው ። #አንድ ሃይማኖት ኤፌ  4:5 ስንት ሃይማኖት ❓ #አንድ #ሃይማኖት ማመን መታመን መልካም ገድል ነው። #የሚጠበቅ #የምንፀናበት መጨረስ የሚገባን #እሩጫ #ፅናት ነው " ንቁ፥ በሃይማኖት ቁሙ፥ ጎልምሱ ጠንክሩ።" (1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 16:13) " ወዳጆች ሆይ፥ ስለምንካፈለው ስለ መዳናችን ልጽፍላችሁ እጅግ ተግቼ ሳለሁ፥ ለቅዱሳን አንድ ጊዜ ፈጽሞ ስለ ተሰጠ ሃይማኖት እንድትጋደሉ እየመከርኋችሁ እጽፍላችሁ ዘንድ ግድ ሆነብኝ።" (የይሁዳ መልእክት 1:3) "መልካሙን ገድል ተጋድዬአለሁ፥ ሩጫውን ጨርሼአለሁ፥ ሃይማኖትን ጠብቄአለሁ፤" (2ኛ ወደ ጢሞቴዎስ 4:7 ስለዚህ  #ማነው #ሚታመነው❓ የሚታመን አንድ እግዚአብሔር ብቻ! ሁለት እግዚአብሔር ወይም ሶስት እግዚአብሔር (ሮች) የሉም። እምነት የሚጀምረው ተመላኪውን በቁጥር እና በስም በማውቅ ነው። #ስንት እግዚአብሔር አለ? ስንልን #በቁጥር                   #አንድ እግዚአብሔር አለ ። " እስራኤል ሆይ፥ ስማ፤ አምላካችን እግዚአብሔር አንድ እግዚአብሔር ነው፤" (ኦሪት ዘዳግም 6:4) ይህን ሁሉም የሚያውቀው ነው አጋንንትም ጭምር #አንድ እግዚአብሔር  ብቻ ነው ያለው " እግዚአብሔር አንድ እንደ ሆነ አንተ ታምናለህ፤ መልካም ታደርጋለህ፤ አጋንንት ደግሞ ያምናሉ ይንቀጠቀጡማል።" (የያዕቆብ መልእክት 2:19) እግዚአብሔር አንድ እንደሆነ አንተም ታምናለህ @MARANATHAWOCH @MARANATHAWOCH

የማለዳ ትምህርት የጸሎታችን መልስ ለምን ይዘገያል? ክፍል 9 በጊዜ አለመጸለይ በተለምዶ ሰው ጸሎትና ምልጃ የሚያበዛው በችግር ጊዜ ብቻ ነው። ችግር ስያጋጥመው፣ የመውጫ መንገድ ስያጣ ወደ እግዚአብሔር መጮኽ ከብሉይ ክዳን ከእስራኤል ዘመን ጀምሮ የተለመደ ሆኖ እስከ ዛሬ ድረስ ደርሶዋል። ነገር ግን እግዚአብሔር የሚጸልገው ይሄንን ህይወት አይደለም። በጊዜውም አለጊዜውም መጸለይና መጽናትን ነው። ስለዚህ ቅዱስ ሁሉ በምቹ ጊዜ ወደ አንተ ይለምናል፣ ብዙ የጥፋት ውሃም ወደ እርሱ አይቀርብም  [መዝ 32፥6] ተብሎ ስለተጻፈ ጥፋትና ችግር ወደ እርሱ እንዳይቀርብ ጻድቅ መለመን ያለበት ጊዜ ሳለ ነው እንጅ ፈተና ደርሶ፣ ጥፋት ደርሶ፣ ቀን መሽቶ ብቻ ወደ እግዚአብሔር መጮኽ የጸሎት መልስ አያመጣም። ኢየሱስም ስናገር " ቀን ሳለ የላከኝን ሥራ ላደርግ ይገባኛል፤ ማንም ሊሰራ የማይችልበት ሌሊት ትመጣለች" ይላልና። [ዮሐ 9፥4] ወንድሞችና እህተች መጸለይ ካለብን በጊዜ፣ ማምለክ ካለብን በጊዜ፣ ማልቀሳ ካለብን፣ መጮኽ ካለብን፣ እምባ ማፍሰስም ካለብን በጊዜ ነው እንጅ የፈተና ሰአት ደርሶ "ሠርገኛ መጣ፥ በርበሬ ቀንጥሱ" እንደሚባለው ተረት መሆን የለብንም። ኢየሱስ ከዲያብሎስ በተፈተነ ጊዜ በመጀመሪያ አርባ ቀንና አርባ ሌሊት በጾም ጸሎት ቆይቶ ነው እንጅ ፈተና ደርሶት አይደለም። ፈተናና ችግር እንደሚደርሰን ካመንን ሥራውን ለማፍረስና ለማሸነፍ ቀድመን መዘጋጀት አለብን። ይህ ማለቴ በችግራችን ጊዜ አንጸልይ፣ አይሰማንም ማለቴ አይደለም። ይሰማናል፤ ነገር ግን በኋላ ከሚመጣው ጥፋት ለማምለጥ በእግዚአብሔር ፊት በምቹ ጊዜ መምበርከክ አለብን። "ወደ ፈተና እንዳትገቡ ትጉና ጸልዩ" ብሎዋል እንጅ ፈተና መጥቷልና ጸልዩ አላለም። ወደ ተና እንዳንገባ የሚያደስገን ፀሎት ቀድመን ፀለይነው ፀሎት ነው እንጅ ተፈትነን የሚንልየው ፀሎት አይደለም። እርሱ ጊዜ ሰጥቶን፣ ሰአት ሰጥቶን፣ ቀን አመቻችቶልን ጸልዩ እያለ እየመከረንእምብ ካልን በኋላ ሰሚ በሌለበት ሰአት በር ተዘግቶ የሚንጸልየው ጸሎት መልስ አይገኝም። ጸሎታችን ለምን ዘገየ እያልን ከመማረርና እግዚአብሔርን ከመወቀስ ውጭ ትስፍ አይኖርም። ምሳ 1፥24-31 በጠራሁ ጊዜ እምቢ ስላላችሁ፥ እጄን በዘረጋሁ ጊዜ ማንም ስላላስተዋለ፥ 25 ምክሬን ሁሉ ግን ቸል ስላላችሁ፥ ዘለፋዬንም ስላልፈቀዳችሁ፤ 26 እኔም ስለዚህ በጥፋታችሁ እስቃለሁ፤ ጥፋታችሁም በመጣ ጊዜ አላግጥባችኃለሁ። 27 ድንጋጤ እንደ ጐርፍ በደረሰባችሁ ጊዜ፥ ጥፋታችሁም እንደ ዐውሎ ነፋስ በመጣ ጊዜ፥ ጭንቅና መከራ በወረደባችሁ ጊዜ። 28 የዚያን ጊዜ ይጠሩኛል፥ እኔ ግን አልመልስም፤ ተግተው ይሹኛል፥ ነገር ግን አያገኙኝም። 29 እውቀትን ጠልተዋልና፥ እግዚአብሔርንም መፍራት አልመረጡምና፤ 30 ምክሬን አልፈቀዱምና፥ ዘለፋዬንም ሁሉ ንቀዋልና፤ 31 ስለዚህ የመንገዳቸውን ፍሬ ይበላሉ፥ ከራሳቸው ምክር ይጠግባሉ። እግዚአብሔር የሚሰማበት ሰአት እምብ ብለን የማይሰማትና ፊቱን በሰወረበት ሰአት መጮኽ መፍትሄ አይሆንም። እግዚአብሔር ከደጃችን ሳያልፍ በደጃችን እያለ ወደ ቤታችን ማስገባት ነው እንጅ አንኳክቶ አጥቶ ከደጅ ካለ በኋላ ፈልገንም አናገኘውም። መ/መ/ ዘሰለሞን 5፥2-7 "እኔ ተኝቻለሁ፥ ልቤ ግን ነቅቶአል የውዴ ቃል ነው፥ እርሱም ደጁን ይመታል እኅቴ፥ ወዳጄ፥ ርግቤ፥ መደምደሚያዬ ሆይ፥ በራሴ ጠል፥ በቈንዳላዬም የሌሊት ነጠብጣብ ሞልቶበታልና ክፈችልኝ። 3 ቀሚሴን አወለቅሁ እንዴት እለብሰዋለሁ? እግሬን ታጠብሁ እንዴት አሳድፈዋለሁ? 4 ውዴ እጁን በቀዳዳ ሰደደ፥ አንጀቴም ስለ እርሱ ታወከ። 5 ለውዴ እከፍትለት ዘንድ ተነሣሁ እጆቼ በደጅ መወርወሪያ ላይ ከርቤን አፈሰሱ፥ ጣቶቼ ፈሳሹን ከርቤ አንጠበጠቡ። 6 ለውዴ ከፈትሁለት፥ ውዴ ግን ፈቀቅ ብሎ አልፎ ነበር። ነፍሴ ከቃሉ የተነሣ ደነገጠች ፈለግሁት፥ አላገኘሁትም ጠራሁት፥ አልመለሰልኝም። 7 ከተማይቱን የሚዞሩት ጠባቂዎች አገኙኝ መቱኝ፥ አቈሰሉኝም ቅጥር ጠባቂዎችም የዓይነ ርግብ መሸፈኛዬን ወሰዱት። በጊዜ አለመክፈትና አለመዘጋጀት የሚያመጣው ችግር አያችሁ? ጸሎቴ የት ጠፋ፣ መልሴ ለምን ዘገየ ከማለት ውጭ ምላሽ አናገኝም። ስለዚህ መጸለይ ያለብን ሰአት ቀድመን እንጸልይ፣ መፈለግ ያለብን ሰአትም ቀድመን እንፈልግ እንጅ የእኛ ቅድሜ ሁኔታ ሳናስተካክል ኢየሱስን ጥፋተኛ አናደርግ። ዮሐ/ ራዕየ 3፥20 እነሆ በደጅ ቆሜ አንኳኳለሁ፤ ማንም ድምፄን ቢሰማ ደጁንም ቢከፍትልኝ፥ ወደ እርሱ እገባለሁ ከእርሱም ጋር እራት እበላለሁ እርሱም ከእኔ ጋር ይበላል። ይህ ሰአት የኢያንዳንዱ ደጅ እያንኳኳ ያለበት ሰአት ነውና ክቡር እንግዳዬ ነህና ና ግባ ብለን እንቀበለው። ሀሳቤ ልክ ከሆነ ቀጥል በሉኝ፤ ልክ ካልሆንኩኝ አቁም በሉኝ ተባረኩ! ይቀጥላል........ @MARANATHAWOCH @MARANATHAWOCH INBOX @Thaddyapostolic GROUP @MARANTAWOCH

የመገረም ጥግ.mp311.37 MB

# አድስ ነገር ጌታ እግዚአብሔር እሱን በመጠባበቅ ላይ ላሉት  ታይቶ የማይታወቀውን ልዩና ድንቅ የሆነ ነገር ያደርጋል ፦       1 ቆሮንቶስ 2 ፥ 9፤ ነገር ግን፡— ዓይን ያላየችው ጆሮም ያልሰማው በሰውም ልብ ያልታሰበው እግዚአብሔር ለሚወዱት ያዘጋጀው ተብሎ እንድተጻፈ፥ እንዲህ እንናገራለን።   ጌታ እግዚአብሔር  አንድን ነገር ስሰራ በሰው  ልክ ተገምቶ የተጠበቀውን ብቻ ሳይሆን  ብዙ  የተጠበቁ ነገሮች እያሉ ከዛም  እጥፍ ድርብ  የሆነ   ከፍ ያለ ነገር ያደርጋል ፦             ኢሳይያስ 43 ፥ 19፤ እነሆ፥ አዲስ ነገርን አደርጋለህ፤ እርሱም አሁን ይበቅላል፥ እናንተም አታውቁትምን? በምድረ በዳም መንገድን በበረሀም ወንዞችን አደርጋለሁ።20-21፤ ምስጋናዬን እንዲናገሩ ለእኔ የፈጠርሁት ሕዝብ፥ የመረጥሁትን ሕዝቤን አጠጣ ዘንድ በምድረ በዳ ውኃን በበረሀም ወንዞችን ሰጥቻለሁና የምድረ በዳ አራዊት፥ ቀበሮችና ሰጎኖች፥ ያከብሩኛል።        እኛ ያመንነዉ አምላክ በፊትም ስሰራ የኖረ ያ ታማኝ አምላክ  ዛረም በእኛ በልጆቹ ላይ በሀይሉ ከፍ ያለ ነገር   ድንቅና ታምር ይሰራል፦             ኢዮብ 36  ፥ 22፤ እነሆ፥ እግዚአብሔር በኃይሉ ከፍ ያለውን ነገር ያደርጋል፤ እንደ እርሱስ ያለ አስተማሪ ማን ነው? በማደሪያው ሆኖ ቃል     የገባ  አምላክ       ራእይ 21 ፥ 5፤ በዙፋንም የተቀመጠው፡—   እነሆ፥ ሁሉን አዲስ አደርጋለሁ፡ አለ። በምመጡት ቀናቶች በምመጣዉ    አመት  ሁሉን ቻይ የሆነ አምላክ በአድሱ አመት  " አድስ ነገር    ያድርግልን"   ይደረግልን ይሁንልን!!!!

ግጥም እልፍ አርገኝ የልምምድ ኑሮ እዛው ተቀምጦ ከፍታ የሌለው ወደታች ሠምጦ ሁሌ ባለሁበት አዲስ ነገር ሳላይ አንድ አይነት ነገር ሳሎጣ ወደ ላይ በጣም ሰልችቶኛል የለመድኩት ልማድ ከፍታ ሳሎጣ  ሁልጊዜ መራመድ እጄን ዘርግቻለው አንተ እንድትረዳኝ በራሴ ጥሪያለው መውጣት ግን አቃተኝ እባክህ ተመልከተኝ አንዴ ብቻ እየኝ ድካሜ በርትቶ ሀይልን እኮ አሳጣኝ ፊትህን ጋረደኝ ድምፅህ ራቀብኝ ተስፋዎቼ ሁሉ በቃ ጨለሙብኝ ይቅርብኝ ያ ልማድ ድግግሞሽ ይብቃ አልፌ  ልሻገር አሁን  ቶሎ  ልንቃ ወዳለመድኩት ወደ አዲስ ነገር ተሻግሬ ልየው ሁሌ ያንተን ክብር ድንበሩ ላይ ቆሜ ለምንስ ልመልከት ተሻግሬ ልሂድ  በሀይል  በጉልበት እልፍ እልፍ እልፍ አርገኝ መራመድ ይብቃና ወደ ላይ አሶጣኝ ከፍ ከፍ ከፍም አርገኝ ዝቅታ ይብቃና ክብርህን አሳየኝ የዛለው ጉልበቴ በድጋሜ ይታደስ ወደታች የሳበኝ  አሁኑኑ ይበጠስ ተራራውን መዞር ምን ጥቅም ይሰጣል እዛው ባለሁበት በጣም ይሰለቻል ሀይልህ ይምጣና ያውጣኝ ወደላይ ጉልበትን እሻለው ፊትህን እስከማይ መንሳፈፍ ናፈኩኝ በፀጋህ ዙፋን እጅግ የሚያስፈልግ በአሁኑ ዘመን ይፍሰስ በእኔ ላይ ይሄ ቅዱስ መንፈስ እላይ የሚያወጣ ካሰብኩት የሚያደርስ አንድ እርምጃ ብቻ አሁን ካለሁበት እንዳይደጋገም የትላንት ማንነት አሮጌውም ይሻር በአዲስ ይለወጥ ማያስፈልግ ነገር ከህይወቴ ይቆረጥ አብዝቼ ልፈልግህ ወደ አንተ ልሩጥ ተራራው ቢጋረጥ ከቶ እንዳልደነግጥ      ከሰፈር ልውጣና ልለይ ላንተ ክብር ከትላንት ማንነት ዛሬ እንድሻገር ድግግሞሽ በቅቶ የድሮ ልማዴ ከዛ እልፍ ልበል ካለሁበት አንዴ አዲስ ነገር ማየት ነውና መሻቴ አንተን መርጠንሀል እኔ እና ቤቴ እናም እልፍ አርገኝ አሁን ካለሁበት ያየሁትን ነገር ወደ ማልደግምበት አንዴ  ብቻ እልፍ አርገኝ አንድ እርምጃ ፈቀቅ አርገኝ S/r eyael

እልፍ አርገኝ
የልማድ ጉዞ ሁሌ ሲደጋገም ለሊቱ ሲነጋ መልሶ ሲጨልም ወይ ላላልፍ ላልሻገር ቀን ፈጀው ቆሜ ከድንበር ትላንትና ዛሬን ተክቶት ሲያልፍ ዛሬ ነገን ሊደርስ በፍጥነት ሲቀዝፍ ወይ ላላልፍ ላልሻገር ቀን ፈጀው ቆሜ ከድንበር የተጋረጠውን ተራራ እየዞርኩ ያኔ በማልኩበት ስፍራ ዛሬም ስገኝ ወይ ላላልፍ ላልሻገር ቀን ፈጀው ቆሜ ከድንበር ሁሌ አንድ አይነት ህይወት መኖር ሰልችቶኛል ቆርጦ ለመውጣት ጥሮ መውደቅ ስልችቶኛል ባለሁበት መራመድ የትም ላልሄድ ኧረ ምንድነው አንተን ይዞ መንገዳገድ እልፍ አርገኝ እልፍ አርገኝ ካለሁበት እልፍ አርገኝ እልፍ አርገኝ ከቆምኩበት እልፍ አርገኝ እልፍ አርገኝ ጥሼ ልሻገር እልፍ አርገኝ እልፍ አርገኝ ከስጋ ነገር እልፍ አርገኝ የከበደኝን ሚያውከኝን ባንተ ላይ ጥዬ ልሂድ ልሻገር ልለፍ እንጂ ተደላድዬ የስምህን በትር በእጄ ይዤ ለምን ቆማለሁ ዮርዳኖስንም ከፍዬበት እሻገራለሁ እልፍ አርገኝ*2 ካለሁበት እኔን አውጣኝ ዘይቴ ፈሶ ተመርጬ ተቀብቻለሁ ታድያ መንደር ውስጥ ከአለም ጋር ምን እስራለሁ ካልተለየሁኝ ስትለየኝ ስትጠራኝ ስጋ መሻቱን ጥፍር አርጎ እንዳይገዛኝ እልፍ አርገኝ አንድ እርምጃ ካለሁበት አንድ እርምጃ ከቆምኩበት አንጅ እርምጃ እልፍ አርገኝ አንዴ ብቻ ፈቀቅ

Tem(2).mp312.46 MB

"ታሪክህ እንዲቀየር ኢየሱስን ወደ ህይወትህ ጋብዝ" ነገር ግን አስቀድማችሁ የእግዚአብሔርን መንግሥት ጽድቁንም ፈልጉ፥ ይህም ሁሉ ይጨመርላችኋል።                           -ማቴዎስ 6:33 በአንድ ሀገር አንድ ንጉሥ በየአመቱ እጣ የማውጣት ባህል ነበረው። እንግዲህ ዕጣው ለወጣለት ሰው ንጉሡ ዜጋው የፈለገውን/የጠየቀውን ነገር ያደርጋል። አንዴም ቃል ስለገባ፤  ከዚህ በፊትም እንዲህ አይነት ልምምድ ስላለ ዕጣው ለወጣለት ሰው ያሻውን ያደርግለታል። የሆነ አመት ላይ ዕጣው ለሆኑ በዕድሜ ለገፉ እናት ይወጣላቸዋል። ከዛ በኃላ ንጉሡ የደህንነት አባላቶቹን ዕጣው መድረሱን እንዲያሳውቋትና ጥያቄዋን ለመቀበል ወደ ሴትዮዋ መንደር ይልኳቸዋል። እነዚህ የደህንነት አባላቶቹ ልክ ሰፈሯ ሲደርሱ መንገዱ አስቸጋሪ የሆነ፣ አከባቢው ላይ ያሉ ቤቶች የደካከሙ እና ሊወድቁ ቀናቶች ብቻ የቀሩት፣ ሴትዮዋም ቤት ሲገቡ ቤቷ እርጅት ያለና ቤቷ ውስጥም ምንም የሚበላ እንኳን የሌለ እንደሆነ ተረዱ። የንጉሡ የደህንነት አባላቶቹ ልክ እንደደረሱ "እንኳን ደስ ያሎዎት እማማ፡ የዘንድሮ ዕጣ ለእርሶዎ ነው የወጣሎት፡ ስለዚህ ከዚህ ደቂቃ ጀምሮ የፈለጉትን ነገር ንጉሡን የመጠየቅ መብት አለዎት።" እሳቸውም ቀጥለው " እንግዲህ እግዚአብሔር ፈቅዶ ዕጣው ለኔ ከወደቀ፡ አንድ ጥያቄ ነው ያለኝ። እሱም ንጉሥ ቤቴ መጥቶ እራት እንዲበላ ነው ምፈልገው።" አሉ! የደህንነት አባላቶቹ ያልጠበቁት አይነት ጥያቄ ስለነበር እጅግ ደነገጡ። "እንደዛማ ሊሆን አይችልም እማማ። እስቲ ከሰፈሮት ብንጀምር እንኳን ንጉሡ ልምጣ ቢል መንገዱ አመቺ አይደለም፡ እጅግ አስቸጋሪ ነው። ቤቶቹ ደግሞ የወዳደቁ እና የደካከሙ ናቸው። እስቲ ዞር ብለው ቤቶትን ይዩ ሊወድቅ ቀናቶች የቀረው ነው በዛ ላይ በስነስርዓት የሚበሉት ምግብ የሚጠጡት ነገር የሎትም። በዚህ ሁኔታ እንዴት ነው የአንድ ሀገር ንጉሥ መጥቶ እራት የሚበላው? ይኼ የማይሆን ነገር ነው እማማ!" ሲሏቸው፡ ወይ ፍንክች " እንግዲህ ሀሳቤን አልቀይርም። የኔ ፍላጎት ንጉሥ መጥቶ አብሮኝ እራት እንዲበላ ነው። ሌላ ጥያቄ የለኝም።" አሏቸው። የደህንት አባላቶቹ ግራ ቢገባቸው ጥያቄውን ወደ ንጉሥ ዘንድ ወሰዱ። ንጉሡም ዕጣ የደረሰው ዜጋው የሚጠይቀውን ለማድረግ ከዚህ በፊት ቃል ስለገባ እንዲሁም የማድረግ ልምምዱም ስላለው እምቢ ማለት ቢቸግረው ጃንደረቦቹን ሰበሰበ። ንጉሡ ከ3 ሳምንታት አስቀድሞ ጃንደረቦቹ ወደ ሴትዮዋ መንደር ሄደው ያለውን ነገር እንዲያዩ ላካቸው። ልክ ሰፈሯ ሲደርሱ መንገዱ የተበላሸ፡ መኪና የማያስገባ ስለነበር አስፓልት ይሰራ ተባለ፡ ተሰራ። አከባቢው ላይ የነበሩ ቤቶች የደካከሙ እና ሊወድቁ አንድ ሐሙስ የቀራቸው ስለነበሩ ሁሉም ፈርሶ እንደገና የሚያምር ቤት ይሰራ ተባለ፡ ተሰራ። ቤቷ ሲደርሱ ቤቷም ያረጀ እና ሊወድቅ  ቀናቶች የቀሩት ስለነበረ ፈርሶ ንጉሡን በሚመጥን ልክ ይሰራ ተባለ፡ ተሰራ። እንዲሁም ቤቷ ምንም የሚበላ ነገር ስላልነበረ ንጉሥን በሚመጥን መልኩ ምግብ በየአይነቱ ይሰራ ተባለ፡ ተሰራ። እንግዲህ በዚህ ሁሉ ታሪክ እንድታዩ የፈለኩት በእውነቱ የተሰራውን ነገር አይደለም። ሰው ከምንም ነገር አስቀድሞ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስን ወደህይወቱ ከጋበዘ በረከት የሚከተል ነገር እንደሆነ እንድትረዱልኝ ነው። እንግዲህ አንድ የሀገር ንገሥ የፈለጉትን ነገር ሊያደርግላቸው ፈቃዱ ሆኖ ሳለ የሳቸው ምላሽ ንጉሡ ወደቤቷ መጥቶ ከእሷ ጋር እራት እንዲበላ መጋበዝ ነበር። ጌታን ወደህይወታችን ስንጋብዝ እኛ ከምናስበው እና ከምንረዳው በላይ ሊያደርግልን ይፈልጋል። የጥያቄ ሁሉ መልስ ኢየሱስ ነው። ታሪክህ/ሽ እንዲቀየር ወደ ህይወትህ/ሽ ኢየሱስን ጋብዝ/ዢው። ልክ ሴትዮዋ ንጉሡን ቤቷ እንዲመጣ ስትጋብዝ ከራሷ አልፋ ለሰፈሯ በረከት እንደሆነችው እኛ ኢየሱስን ወደህይወታችን ስንጋብዝ የኛ ታሪክ ብቻ አይደለም የሚገለበጠው። ለሰዎች የምንተርፍ እንሆናለን። ብቻ ኢየሱስን ወደ እያንዳንዱ ነገራችን እንጋብዘው። አለም ልክ እንደ የደህንነት አባላቶቹ ያልተሳኩ ነገሮቻችንን፡ የወደቅንባቸውን ጊዜያቶች እያመጣ በህሊና ወቀሳ እያሰቃየን፡ አዕምሮአችንን በከንቱ ሀሳብ እየሞላ፡ ማጣታችንን ተጠቅሞ፡ መድከማችንን አይቶ ተስፋ ሊያስቆርጠን ቢሞክርም ንጉሣችንን ኢየሱስን ብቻ ነው ምፈልገው ሌላ ጥያቄ የለኝም ብለን ፀንተን ከቆምን በረከት ይከተለናል።​

የማለዳ ትምህርት የጸሎታችን መልስ ለምን ይዘገያል ? ክፍል 8 ራሱን ከፍ አድርጎ በማየት ጸሎት ማለት ሰውና እግዚአብሔር የሚገናኝበት የስልክ መስመር በመሆኑ መጠን የሚጸልየው ጸሎት በጥንቃቄ መሆን አለበት። ምክንያቱም በስልክ መስመራችን የሚናወራው ወሬአችን ሁሉ በቴሌ እንደሚመዘገብ የጸለይነው ጸሎታችንም እያንዳንዱ ቃላቶች በእግዚአብሔር ፊት የሚመዘገብ ነው። እየቀለድን የሚናወራቸው ቃላቶች እንኳን በአየር ላይ ተቀምጦ በፍርድ ቀን ተሰብስቦ እንደሚመጡብን በእግዚአብሔር ቃል ውስጥ ስለተጻፈ ሁሉንም ቃላቶቻችን ጥንቃቄ እያደረግን ብናወራ ይሻለናል። ወደ ዋና አላማዬ ስመለስ ስንጸልይ እራሳችንን ማመጻደቅ ሌላውን ግን መኮነን አያስፈልገንም። የሀጥአት ምዛንና የጽድቅ ምዛን ያለው እግዚአብሔር ጋር ነው። ስንጸልይ እራሳችንን አዋርደን በእምባ፣ በለቅሶ እንጅ እኔ ጻድቅ ስለሆንኩኝ ማለት አያስፈልግም። የበታችነት ስሜት ይሰማን፤ ከሐጥአተኞች ዋና ሐጥአተኛ እኔ ነኝ እያልን መጸለይ አለብን። መቼስ የሚለምን እጅ የበታች ነው ይባላልና በታችነት ተሰምቶን መጸለይ አለብን። እኛ ወደ እግዚአብሔር ስንጸልይ እግዚአብሔር ግን ከላያችን ያለው ማንነት ሳይሆን ልባችንን ይመረምራል። መርምሮ ካዬ በኋላ  የተዋረደውን ከፍ ያደርጋል፤ ከፍ ያለውን ዝቅ ያደርጋል። ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል። መጠምጠሚያውን አውልቅ፥ ዘውዱንም አርቅ፤ ይህ እንዲህ አይሆንም፤ የተዋረደውን ከፍ አድርግ፥ ከፍ ያለውንም አዋርድ። [ት/ሕዝ 21፥26] ፤ ለዘላለም የሚኖር ስሙም ቅዱስ የሆነ፥ ከፍ ያለው ልዑል እንዲህ ይላል። የተዋረዱትን ሰዎች መንፈስ ሕያው አደርግ ዘንድ፥ የተቀጠቀጠውንም ልብ ሕያው አደርግ ዘንድ፥ የተቀጠቀጠና የተዋረደ መንፈስ ካለው ጋር በከፍታና በተቀደሰ ስፍራ እቀመጣለሁ። [ ት/ ኢሳ 57፥15] የእግዚአብሔር መሥዋዕት የተሰበረ መንፈስ ነው፥ የተሰበርውንና የተዋረደውን ልብ እግዚአብሔር አይንቅም። [መዝ 51፥17] እንግዲህ በጊዜው ከፍ እንዲያደርጋችሁ ከኃይለኛው ከእግዚአብሔር እጅ በታች ራሳችሁን አዋርዱ፤ እርሱ ስለ እናንተ ያስባልና የሚያስጨንቃችሁን ሁሉ በእርሱ ላይ ጣሉት። [1ጴጥ 5፥6-7] ችግራችን።፣ ቀምበራችንን፣ ሸክማችንን ሁሉ የሚንጥለው በትዕብት ተሞልተን፣ ከፍ ከፍ ብለን ሳይሆን በፊቱ ተዋርደን ብቻ ነው። እኛ ከእርሱ በታች ሆነን መዋረድ ስንጀምር እርሱ ከፍ ከፍ ማድረግን ይጀምራል። እርሱ ጸሎታችን ሰምቶ ከፍ ባደረገን ቁጥር እኛ ጨምረን ዝቅ ዝቅ ማለትን መለማመድ አለብን። ኢየሱሰ ለምሳሌ የተጠቀመውን የሁለት ሰዎች ጸሎት እንመልከት፦ የፈረሳዊው ጸሎት፦ ፈሪሳዊም ቆሞ በልቡ ይህን ሲጸልይ። እግዚአብሔር ሆይ፥ እንደ ሌላ ሰው ሁሉ፥ ቀማኞችና ዓመፀኞች አመንዝሮችም፥ ወይም እንደዚህ ቀራጭ ስላልሆንሁ አመሰግንሃለሁ፤ በየሳምንቱ ሁለት ጊዜ እጦማለሁ፥ ከማገኘውም ሁሉ አሥራት አወጣለሁ አለ። የቀራጩ ጸሎት፦ ቀራጩ ግን በሩቅ ቆሞ ዓይኖቹን ወደ ሰማይ ሊያነሣ እንኳ አልወደደም፥ ነገር ግን። አምላክ ሆይ፥ እኔን ኃጢአተኛውን ማረኝ እያለ ደረቱን ይደቃ ነበር። የኢየሱስ ፍርድ፦ እላችኋለሁ፥ ከዚያ ይልቅ ይህ ጻድቅ ሆኖ ወደ ቤቱ ተመለሰ፤ ራሱን ከፍ የሚያደርግ ሁሉ ይዋረዳልና፥ ራሱን ግን የሚያዋርድ ከፍ ይላል። አንዱ የራሱን ማንነት እያሳየ ከፍ ከፍ ስል ሌላኛው ግን ከሐጥአቴ ውጭ የሚነግርህ ጽድቅ የለኝም ብሎ ገና ከሩቅ ቆሞ ደረቱን እየደቃ ለመነ። በመጨረሻም ሐጥአተኛ ነው ተብሎ የተፈረጀ ቀራጭ ሐጥአቱን አራግፎ በሠላም ወደ ቤቱ ስመለስ ራሱን ከፍ አድርጎ ጽድቁን ያሳየ ሰውዬ ሐጥአቱን ተሸክሞ ወደ ቤቱ ተመልሰዋል። ዛሬም በእግዚአብሔር ፊት ብልጥ ብልጥ መሆን የሚሰማን ሰዎች አንድ ጊዜ እናስተውልና በፊቱ እንዋረድ፣ ዋና ሐጥአተኛ እኔ ነኝ እንበል። ተዋርደን ጸልየን ከፍ ብለን እንመለስ። አለበለዚያ  በልባችን ትዕቢት እግዚአብሔርን እየወቀስን እንኖራለን። ይቀጥላል....... @MARANATHAWOCH @MARANATHAWOCH Comment INBOX  @Thaddyapostolic GROUP @Marantawoch

በ2019 ዓ.ም የእኛ እቅድ ታጥፎ የእግዚአብሔር ፈቃድ የሚገለጥበት፣ በሕይወታችንም የእርሱ እጅ የሚታይበት ዓመት ይሁንልን

ዘማሪ ሙሴ ሲሳይ ርዕስ:ፍቃድህን የሚያደርግ
አለምም ምኞቱም በከንቱ ያልፋሉ እንደጠዋት ጤዛ ሆነው ይደርቃሉ ዘላለም ይኖራል ፍቃድህን የሚያደርግ አስተውሎ ሚኖር የሚሄድ በአንተ ህግ ፍቃድህ ተገልጦ አንተን የሚያስደስት በመውጣት መግባቴ የአንተ ፍቃድ ይሁን ሁል ጊዜ በህይውቴ በመንገድህ ምራኝ እየሱስ አባቴ መልካም መልካሙን የምታስብል ህይወት አቅጣጫዬን አንተ አሳምርልኝ መልካም ነህ *2 መልካም እየሱስ አላማህ በኔ ላይ ፍቅር ነው እና ያቅዱስ መንፈስህ በእኔ ይፈሰስ እና ይምራኝ ያሳየኝ ክቡር ፍቃድህን በሀሳብህ ኖሬ ከጥፋት እንድድን ተገልጦ ይታይ እያበራ ፍቃድህ በልቤ ተራራ አላማህ በህይወቴ እንዲታየኝ ፍቃድህን ጌታ አስታውቀኝ እኔ ያንተ ብቻ ያንተ ብቻ ነኝ ማንም ምንም አይሰልጥንብኝ እኔ ያንተ ብቻ ያንተ ብቻ ሆኛለው ፍቅርህ ይግዛኝ ያበርታኝ

#ተስፋ ተስፋ ያለዉ ሰው ነገሩን ሁሉ በእርሱ ላይ የጣለ ሰው ሁሉ እስካለመበት ይደርሳል ያ ማለት ተስፋ ሰጪ አምላክ አድራግ አምላክ ነዉ ። ዘፍጥረት 15 ፥ 1፤ ከዚህ ነገር በኋላም የእግዚአብሔር ቃል በራእይ ወደ አብራም መጣ፥ እንዲህ ሲል፡— አብራም ሆይ፥ አትፍራ፤ እኔ ለአንተ ጋሻህ ነኝ፤ ዋጋህም እጅግ ታላቅ ነው። 3፤ አብራምም፡— ለእኔ ዘር አልሰጠኸኝም፤ እነሆም፥ በቤቴ የተወለደ ሰው ይወርሰኛል፡ አለ። 4፤ እነሆም፥ የእግዚአብሔር ቃል እንዲህ ሲል መጣለት፡— ይህ አይወርስህም፤ ነገር ግን ከጉልበትህ የሚወጣው ይወርስሃል። 6፤ አብራምም በእግዚአብሔር አመነ፥ ጽድቅም ሆኖ ተቈጠረለት። ጌታ እግዝአብሔር ስለልጆቹ የምአስብ ያለውን የምፈጽምና ተናግሮ የማይዋሽ ቅዱስ አምላክ ነው ለአብርሃም የገባለትን የተስፋ ቃል ፈጸመ ዘፍጥረት 21 ፥ 1፤ እግዚአብሔርም እንደ ተናገረው ሣራን አሰበ፤ እግዚአብሔርም እንደ ተናገረው ለሣራ አደረገላት።2፤ ሣራም ፀነሰች፥ እግዚአብሔርም በተናገረው ወራት ለአብርሃም በእርጅናው ወንድ ልጅን ወለደችለት።3፤ አብርሃምም የተወለደለትን ሣራ የወለደችለትን የልጁን ስም ይስሐቅ ብሎ ጠራው። ሀናም ለዘመናት ልጅ ባለማግኘቷ ተጨንቃ በጌታ ተስፋ አድርጋ ጸለየች 1 ሳሙኤል 1 ፥ 11፤ እርስዋም፡— አቤቱ፥ የሠራዊት ጌታ ሆይ፥ የባሪያህን መዋረድ ተመልክተህ ብታስበኝ፥ እኔንም ባትረሳ፥ ለባሪያህም ወንድ ልጅ ብትሰጥ፥ ዕድሜውን ሁሉ ለእግዚአብሔር እሰጠዋለሁ፥ ምላጭም በራሱ ላይ አይደርስም ብላ ስእለት ተሳለች። በእሱ ተስፋ ስላደረገች ሆነላት 1 ሳሙኤል 1 ፥ 19፤ ማልደው ተነሥተው በእግዚአብሔር ፊት ሰገዱ፥ ተመልሰውም ወደ አርማቴም ወደ ቤታቸው መጡ። ሕልቃናም ሚስቱን ሐናን አወቃት፤ እግዚአብሔርም አሰባት፤20፤ የመፅነስዋም ወራት ካለፈ በኋላ ሐና ወንድ ልጅ ወለደች፤ እርስዋም፡— ከእግዚአብሔር ለምኜዋለሁ ስትል ስሙን ሳሙኤል ብላ ጠራችው። አሁንም ተስፋችን እየሱስ ነው እህት ውንድሞቸ ተስፋ አንቁረጥ ምንም እንኳ ቀን ብቆይም ሁለም እግዚአብሔር እሱን ተስፋ ከምአደርጉት ጋር ነው ያለውን ይፈጽማል የዘገየ ብመስልም በእርሱ ተስፋ አድርገን የጠበቅነዉ ነገር ሁሉ አንድ ቀን በሀይል ይሆናል ይደረግልናል።

የማለዳ ትምህርት የጸሎታችን መልስ ለምን ይዘገያል? ክፍል 6 ከሐጥያት ጋር የሆነ ጸሎት በዚህ ምድር ላይ እንኳን ሰው ከሰው ጋር መንገድ የሚሄደው ሁለቱም ስሰማሙ ብቻ ነው እንጂ እየተጣሉ ወይንም ተኮራርፈው አብረው መሄድ አይችሉም። "በውኑ ሁለት ሰዎች ሳይስማሙ በአንድነት ይሄዳሉን?" ት /አሞጽ 3፥3 ሌላው ደግሞ አንድ ሰው ገንዘብ ብያስቸግረው አበድረኝ ወይንም ስጠኝ ብሎ የሚጠይቀው በጣም የሚገናኝና በደምብ የሚስማማ ወይንም የቅርብ ዘመድ  የሆነ ወይንም የቅርብ ጓደኛየሆነ ሰው እንጅ ያላወቀ ሰው በመንገድ ላይ ቆሞ አይጠየቅም። ደግሞም ምንም እንኳ ዘመድ፣ አባት ወይንም ጓደኛ ብሆንም የሚሰጠውና የሚያበድረው፥ የተበዳሪው ሁኔታ አይቶ፣ ከዚህ በፊት ከእኔ ጋር ምን ያህል ቅርርቦሽ አለው? ዛሬ ስለተቸገረ ብቻ ነው የቀረበው ወይስ በፊትም ከእኔ ጋር ጥብቅ ግኑኝነት አለው? ብሎ ከመስጠት በፊት ጀርባውን ያጠናል። ሃማ ለመርዶክዮስ የ50 ክንድ እንጨት አዘጋጅቶ እንድሰቀል በወሰነ ጊዜ፥ የንጉሡ ምስት አስቴር ለንጉሡ ሄዳ ብትነግርም ከተናገረችው ቃላት ይልቅ መፍትሔ ያመጣው መርዶክዮስ በደጉ ጊዜ ለንጉሡ ያደረገው መልካምነትና ቸርነት በንጉሡ መዝገብ ውስጥ ተመዝግቦ መገኘት ነው። ንጉሡ አርጠክስስ የሃማ ውሳኔ ከሰማ በኋላ ቶሎ ቤት ገብቶ መንገቡን ፈትሹኝ ብሎዋል፤ በፊት ያለው የንጉሡና የመርዶክዮስን ቅርርቦሽ ለመፈተሽ ተገዷል። በዛው ቀን ለመርዶክዮስ በንጉሡ ፊት የሠራው በደልና ሀጥያት ብገኝ ኖሮ የአስቴር ልመና አያድነውም፤ ከመርዶክዮስ አልፎ 127 አገራት ውስጥ የሚኖሩ አይሁድ ሙሉ በሙሉ ተደምስሰው ነበረ። መርዶክዮስ በንጉሡ ፊት መልካም ሆኖ መገኘቱ አዳነው። በዛውም ልክ ወደ እግዚአብሔር ጸሎታችን ስናቀርብ እግዚአብሔር መጀመሪያ ቶሎ የሚያየው በደህና ጊዜ የሚንሰራው ሥራችን ነው። በእግዚአብሔር ፊት የሐጥአት ነው ወይስ የጽድቅ መዝገብ ነው የሚታይልን? በእርግጥ እግዚአብሔር የማይሰማና የማይመልስ ጥያቄ የለም፤ ነገር ግን ሀጥያት የሚባል ግድግዳ ወይንም መጋረጃ በመሀላችን ገብቶ እንዳንገናኝያደርጋል። እግዚአብሔር ወደ ሰው እንዳይመጣ የሚያደርገው ጨለማ አይደለም፣ ዝናብ አይደለም፣ ፀሀይ አይደለም፣.... ሀጥያት ብቻ ነው። በት/ኢሳ 59፥1 ላይ የተጻፈው ዋናው የጸሎት እንቅፋት የሚሆን መጋረጃ ሀጥያት መሆኑን ይናገራል ። ይህ ሀጢያት የተባለ መጋረጃ በሰውና በእግዚአብሔር መካከል ገብቶ ጸሎቱ እንዳይደርስ፣ ደርሶም መልስ እንዳይመለስ አድርጎ የሚከለክል በሽታ ነው። ይህ እንዳይሆን የፈለግነውን ነገር ስጠን እያልን ጸሎታችን ከማቅረብ በፊት በመጀመሪያ ሀጢያተኛ ነኝና ማረኝ ከዛም ጸሎተን አድምጠኝ ማለት አለብን። አቤቱ፥ ወደ አንተ የጮኽሁትን ቃሌን ስማኝ፤ ማረኝና አድምጠኝ። (መዝ 27፥7) ት/ኢሳ 59፥1-3 "እነሆ፥ የእግዚአብሔር እጅ ከማዳን አላጠረችም፥ ጆሮውም ከመስማት አልደነቈረችም፤ ነገር ግን በደላችሁ በእናንተና በአምላካችሁ መካከል ለይታለች፥ እንዳይሰማም ኃጢአታችሁ ፊቱን ከእናንተ ሰውሮታል። እጃችሁ በደም ጣታችሁም በበደል ረክሳለች፥ ከንፈራችሁም ሐሰትን ተናግሮአል፥ ምላሳችሁም ኃጢአትን አሰምቶአል።" እያለ ይቀጥላል። ነገር ግን ሰው ከእግዚአብሔር ጋር ለመስማማት ያለው ብቸኛ አማራጭ ምሕረት መጠየቅ ብቻ ነው። ኢዮብ 22፥21-30 አሁንም ከእርሱ ጋር ተስማማ፥ ሰላምም ይኑርህ፤በዚያም በጎነት ታገኛለህ። . ሁሉን ወደሚችል አምላክ ብትመለስ፥ ብትዋረድም፥ኃጢአትንም ከድንኳንህ ብታርቅ... ወደ እርሱም ትጸልያለህ፥ እርሱም ይሰማሃል፤ስእለትህንም ትሰጣለህ። . እያለ ይቀጥላል። የቀረውን እናንተም አምብቡ። የዚህ የመጽሐፍ ቅድስ ክፍል ማብራሪያ ከዚህ በላይ መስጠት የሚያስፈልግ አይመስለኝም። ምክንያቱም ከእግዚአብሔር ጋር የተስማማ ሰው ብቻ የጸሎቱን መልስ እንደሚያገኝ በግልጽ አስቀምጧልና። የጸሎታችን መልስ ዋና እንቅፋት ሀጢያት እስከሆነ ድረስ ሀጥአታችን እንቅፋት እንዳይሆንብን መጀመሪያ ሀጥአታችን ከውስጣችን ማስወገድና ቀጥለን የሚያስፈልገንን ነገር መጠየቅ ያዋጣናል። ት/ሕዝ 18፥20 "...ንስሐ ግቡ ኃጢአትም ዕንቅፋት እንዳይሆንባችሁ ከኃጢአታችሁ ሁሉ ተመለሱ። የበደላችሁትን በደል ሁሉ ከእናንተ ጣሉ አዲስ ልብና አዲስ መንፈስም ለእናንተ አድርጉ፤ የእስራኤል ቤት ሆይ፥ ስለ ምን ትሞታላችሁ?" እግዚአብሔር ከሀብታም ጋር አይደለም፣ ከተማረ ሰው ጋር አይደለም፣ ብዙ ጥሩ ዘመድ ካለው ሰው ጋር አይደለም፤ እግዚአብሔር ሁሌ ከጻድቅ ሰው ጋር ብቻ ነው። ይህ ማለቴ ግን የተማረና ሀብታም ሰው ጻድቅና እግዚአብሔርን የሚፈራ የለም ማለቴ አይደለም ። በአጠቃላይ ማንኛውም ሰው ጽድቅን እየሰራ ብለምን መልሱ አይዘገይም። በመሳፍ ም.6 ላይ እግዚአብሔር ገድዎንን "አንተ ብርቱ፣ ሀያል ሰው" ያለው በሥጋ በኩል ስናይ ገድዎን ለራሱ ሚድያማውያንን ፈርቶ ተደብቆ ያለበት ቦታ ሄዶ አግኝቶት ነው። ገዴዎን ግን ጠላቶቹን ይፍራ እንጅ ውስጡ ጻድቅ ነው፣ ከሀጢአት የተለየ ነው፣ስለዘመዶቹ እየጸለየ የአባቶቻችን አምላክ ትቶናል እያለ በቁጭት ስተክዝ ወዳለበት ቦታ ሄዶ ነው። ከሀጢአት የራቀ ሰው፣ ቅድስና የጠበቀ ሰው፣ ምሕረትን የሚጠይቅ ሰው እርሱ ሀያል ሰው ነው። ለጸሎቱ መልሱን ቶሎ ያገኛል። ስለዚህ በአጠቃላይ የጸሎታችን መልስ የሚያዘገየው ዋነኛ እንቅፋት ወይንም መጋረጃ ሀጢያት ነውና ሀጢያትን ከድንኳናችን አስወግደን እንጸልይ። @MARANATHAWOCH @MARANATHAWOCH COMMENT INBOX @Thaddyapostolic GROUP @Marantawoch

አይቶ እንዳላየ አይቶ እንዳላየ፣ ሰምቶ እንዳልሰማ፣ መተላለፋችንን ሳይቆጥር፣ አመፃችንን ሳይለካ እንዲሁ እንደ ቀላል ልጆቹን ይቅር አለን፤ ሁሉን ተወልን፤ እዚህም አደረሰን። የአባትነቱ ፍቅር ልጆቹን ማረከ፣ ይቅርታው ፀጋን አበዛልን፣ ምህረቱ በረከትን አደለን። ዛሬ ነገ ጠፋን፣ ዛሬ ነገ ሔድን ስንል ሁሉን ማበጀት የሚያውቅ አምላክ ደንቅን አድርጎ ሌላ እድል ሰጠን፤ ከፊቱ አቆመን፣ ስሙን እንድንጠራ፣ እንድናመሰግነው፣ እንድናወድሰው ፀጋውን አደለን፤ ብርታት በረከቱን ጨመረልን። የሚሰጥ እርሱ የሚነሳ እርሱ፣ የሚያከብር እርሱ የሚያዋርድ እርሱ። ነገር ግን እንደስልጣኑ ሳይሆን እንደ ቸርነቱና እንደ ርህራሔው ስጦታውን አበዛልን፤ ክብርን ጨመረልን፤ በሰው ፊት ሞገስን አደለን፤ በቤቱ አቆየን፤ በመላዕክት ዘንድ ዘወትር የሚወደሰው ስሙን እናወድስና እናከብር ዘንድ እድሉን ሰጠን፤ ወደ እራሱም አስጠጋን። አይቶ እንዳላየ፣ ሰምቶ እንዳልሰማ ሁሉን ትቶልህ፣ ሁሉን ረስቶልህ የተወልህን አምላክህን ለማመስን፣ ስሙን ለመጥራት፣ ከፍከፍም ለማድረግ አንደበትህ ባይፈታ፣ ቃላት ባይሰናዱልህ እንዲህ እያልክ ስራውን አክብር፤ ለምህረቱ አመስግን፤ ይቅርታውንም ዳግም ተማፀን። " ሁሉን እያወክብኝ ዝም አልክልኝ፣ ሁሉን እያየህብኝ አለፍክልኝ። ስራዬ ይቅርታ ባይገባውም፣ ተግባሬ አንተ ፊት ባያቆመኝም፣ ክፋቴ ስምህን ለመጥራት ባያበቃኝም አንተ ግን ሁሉን ተውክልኝ፤ ይቅር አልክልኝ፤ ከፊትህም በምህረት አቆምከኝ፤ ስምህን እንድጠራ ፈቀድክልኝ። ምንም ባወራ፣ ምንም ባደርግ በምላሴ እንዳልጠፋ፣ በተግባሬ እንዳልሰናከል ዘወትር የምትጠብቀኝ፣ የከፋውን መንገድ ለልጆችህ እንዳልጠቁም፣ ከእኔ መጥፋት በላይ ሌሎችን ወደ ጥፋት እንዳልመራ ዘወትር እየጠበክ የምትገስፀኝ፣ መንገዱን የምትመራኝ ደጉ አባቴ አመሰግናለሁ። ክፋት ያደክማል፤ ህግጋትህን መተላለፍ ያስጨንቃል፤ ከቤትህ መራቅ ያስፈራል ነገር ግን ይህን ሁሉ በማስጨነቁ አልተወኩትም፤ በማድከሙ አላቆምኩትም፤ በአስፈሪነቱ አልተለየውትም። ህግጋትህን እያወኩ ሰበርኩት፣ ትዕዛዝህን ተረድጄ ከመተግበረ አፈነገጥኩ። አምላኬ እንደ ምህረትህ እንጂ እንደ ጥፋቴ፣ እንደ ቸርነትህ እንጂ እንደ በደሌ እዚህ አልደረስኩምና እንደ ቀድሞው ሁሉ መተላለፌን አትቁጠርብኝ፤ ጥፋቴን አትይብኝ። ማድረግ የሚገባኝን ረስቼ ማድረግ የማይገባኝን፣ የማይወክለኝ፣ የማይገልፀኝን እርሱን አደርጋለሁና አንተ አስተዋይ ልቦናን ስጠኝ፤ በምህረት እጆችህ ዳሰኝ፤ አንደበቴን ጠብቅልኝ፤ ተግባሬንም ቀድስልኝ። " በማለት አክብሮት ልመናህን አድርስ። ልመናህ እንደሚሆንም በሙሉ ልብህ አምነህ ተቀበል። ውብ ምሽት ይሁንልን!

ሰው ያለውን ነው የሚሰጠው ።        በልባችን ምንድነው የሞላው❓ በልብ ሞልቶ ከተረፈው አፉ ይናገራልና መልካም ሰው ከልብ መልካም መዝገብ መልካሙን ያወጣል፥ ክፉ ሰውም ከልብ ክፉ መዝገብ ክፉውን ያወጣል።" ሉቃስ 6:45 #በልባችን ምን ሞላቷል ❓በልባችን የሞላው ስራችንን ይገልፃል ። ✍ በልባችን የሞላው መልካም ከሆነ የምናደርገው የምንሰራው መልካም ነው ። ክፉ ከሆነ ከልባችን ክፋትን እናውጣለን። ✍ አንድ ታሪክ ላስታውሳቹ በአንድ መንደር የሚኖሩ ሰዎች ነበሩ በአንዳንድ ጉዳይ ላይ ባለመስማማታቸው  የሚኖሩበትን መሬት ለሁለት ተካፈሉ አንደኞች በግራ ሌሎች በቀኝ መኖር ቀጠሉ ። በግራ ያሉት ወደ ቀኝ የተጠቀሙበትን ቆሻሻ  መጣል ጀመሩ ። በቀኝ ያሉት ደሞ ወደ ግራ ፍራፍሬ ሙዝ ፣ ማንጎ ብርትኳን ... ይጥሉ ጀመር ። በግራ ያሉት ወደ ቀኝ ቆሻሻ መጣል በቀኝ ያሉት ወደ ግራ ፍራፍሬ አዘውትረው ሁል ጊዜ መጣላቸውን ቀጠሉ ። ከእለታት አንድ ቀን በግራ ያሉት በቀኝ ያሉትን እንዲ ሲሉ ጥያቄ ይጠይቃሉ ፦ እኛ ቆሻሻ ስንጥልባቹ እናንተ ግን የሚበላ ጥሩ ነገር ትጥሉልናላቹ             ግን ለምን ❓ አሉ በቀኝ ያሉት እንዲ ሲሉ መለሱ ፦ ሰው ለሰው የሚሰጠው ያለውን ነገር ነው። ውስጡ ክፋት ካለ ክፋትን መልካምነት ካለ ደግሞ መልካምነትን ይሰጣል እኛም ለናንተ የሰጠነው ያለንን ነገር ነው አሉ ። እኛስ በውስጣችን ምን አለ❓ መልካም የምናደርገው ሰው መልካም ሰላረገልን ሳይሆን ያለንን ነው የምናሳየው መልካም ነን ወይስ ክፉ❓ ስራችንን እንመልከት ስራችን መልስ ይሆነናል ። ሰው የሚሰጠው ያለው ነው ምን አለን ❓ @MARANATHAWOCH

የማለዳ ትምህርት የጸሎታችን መልስ ለምን ይዘገያል? ክፍል 6 ለሰዎች ለመተያየት ብለን ስንጸልይ ኢየሱስ በማቴ 6፥5 ላይ ለሰዎች እንዳስተማረው ብዙ ሰዎች ችግራቸውን ለእግዚአብሔር ከመናገር ይልቅ ለአጠገባቸው ላሉ ሰዎች ለማሳየት የሚናገሩ የሚመስል ጸሎት ይጸልያሉ። የጎረቤት ሰዎች እገለ ጸላይ ነው፤ ምሽት ተነስቶ እየጸለየ ነው እንድባሉ ፈልገው ብቻ ድምጻቸውን ከፍ አድርገው ይጸልያሉ። ኢየሱስ ግን ስያስተምር ያለው በሰማይ ያለው አባታችሁ ገና ሳትነግሩ የልባችሁን መሻትና ፍላጎት ያውቃልና ድምጻችሁን ሳታወጡ በሰውር ጸልዩ አላቸው። ለሰው ለመታየት ብሎ የሚጸለየው ጸሎት ወደ ሰማይ አይደርስም፣ በከንቱ ድካም ሆኖ ይቀራል። ምክንያቱም ዋጋቸውን ከዚህ ምድር ተቀብሎዋሉና ይላል። ጸሎት ግን ሰማይ  ደርሶ ከሰማይ መልስ ይዞ መምጣት አለበት። አለበለዚያ መልሳችን ለምን ዘገየ እያልን ከመኖር ውጭ ጥቅም አይኖርም። ጸሎታችን እኛና እግዚአብሔር ብቻ የሚንነጋገርበትና የሚናወቅ መሆን አለበት። ጸሎት የግል ጉዳይ እስከሆን ድረስ የአጠገባችን ሰው መስማት የለበትም። በእርግጥ የጋራ ጸሎትም አለ፤ እዚህ ቦታ እኔ እያልኩ ያለሁትኝ ስለ ግል ጸሎት ነው። ነገር ግን ድምጽ ከፍ አድርጎ ለሰው ለመተያየት የሚጸለየው ጸሎት የግብዞች ነው ይላል። እንደዚህ አይነት ጸሎት መኩራቦች ይወዳሉ፤ ለሰዎች ለመተያየት ብለው መንገድ ይወጣሉ፤ ዋጋቸውን ከሰማይ ሳይሆን ከዚህ ይቀበላሉ። ማቴ 6፥5 ስትጸልዩም እንደ ግብዞች አትሁኑ፤ ለሰው ይታዩ ዘንድ በምኩራብና በመንገድ ማዕዘን ቆመው መጸለይን ይወዳሉና፤ እውነት እላችኋለሁ፥ ዋጋቸውን ተቀብለዋል። አንተ ግን ስትጸልይ፥ ወደ እልፍኝህ ግባ መዝጊያህንም ዘግተህ በስውር ላለው አባትህ ጸልይ፤ በስውር የሚያይ አባትህም በግልጥ ይከፍልሃል። አሕዛብም በመናገራቸው ብዛት እንዲሰሙ ይመስላቸዋልና ስትጸልዩ እንደ እነርሱ በከንቱ አትድገሙ። ስለዚህ አትምሰሉአቸው፤ ሳትለምኑት አባታችሁ የሚያስፈልጋችሁን ያውቃልና። የቃላት መደጋገም፦ ለመተያየት ብለን ቃላቶችን መደጋገም አያስፈልገንም። እኛ ሳንነግረው እንኳ የልባችን መሻትና ፍላጎት የሚያውቅ አምላክ ነው። የሐና ጸሎትን አስተውሉ፦ ስንጸልይ እንደ ሐና እብድ እስክንመስል ድረስ ከንፈራችንን ብቻ እያንቀሳቀስን እንጸልይ። ሐና ስትጸልይ በልቧና በከንፈርዋ ነው እንጅ በአፏ አውጥታ ኦየተናገረች ያዙኝ ልቀቁኝ አይነት ጸሎት አልጸለየችም። እንደው ካህኑ ዔል "ስካርሽ እስከመቼ ነው? የወይን ጠጅሽን ከአንቺ አርቂው" እስክላት ድረስ ከንፈሩዋን ብቻ እያንቀሳቀሰች ነበረ። 1ሳሙ 1፥12-14 ጸሎትዋንም በእግዚአብሔር ፊት ባበዛች ጊዜ ዔሊ አፏን ይመለከት ነበር። ሐናም በልብዋ ትናገር ነበር፤ ድምፅዋም ሳይሰማ ከንፈርዋን ታንቀሳቅስ ነበር፤ ዔሊም እንደ ሰከረች ቈጠራት። ዔሊም። ስካርሽ እስከ መቼ ነው? የወይን ጠጅሽን ከአንቺ አርቂው አላት። ሐናም። ጌታዬ ሆይ፥ አይደለም፥ እኔስ ልብዋ ያዘነባት ሴት ነኝ፤ ጠጅና ሌላ የሚያሰክር ነገር አልጠጣሁም፥ ነገር ግን በእግዚአብሔር ፊት ነፍሴን አፈሰስሁ፤..... መልስ ይዞ የሚመጣ ጸሎት ይህ ነው ማለት ነው። እግዚአብሔር የልብ ጸሎት እንጅ የአፍ ጸሎት አይፈልግም። ይህ ማለት ከልብህ የሚመነጭ ወይንም ምርር ያለ ጸሎት ይፈልጋል እንጅ ሰው ለማየት ብቻ ወይንም ጸሎት ነው ስለተባለ ብቻ ምዛን የሌለ፤ ያልተመሰጠ ጸሎት መጸለይ መልሳችንን ያዘገያልና እንጠነቀቅ። ሐና በሰውር የለመነችውን ልመና በግልጥ ከፍሎላታል። ሰው ስደረገልን ወይም ስሆንልን ብቻ ነው መስማት ያለበት እንጅ ስንጸልይ ማየት የለበትም። እግዚአብሔር የመተያየት ጸሎት አይፈልግም፤ እሱ የግብዞች ጸሎት ነውና። ጸሎታችን ለምን ዘገየ ማለት ብቻ ትተን በምን ምክንያት ነው፣ ምኑ ጋር ነው የተበላሸው የሚለውን ለመፈተሽ እነዚህ ትምህርት ክፍሎች መከታተል ወሳኝ ነው ብዬ አምናለሁ። ትምህርት በዚህ ሁኔታ ከተመቻችሁ ይቀጥላልና ይቀጥል በሉኝ። ይቀጥላል........ @MARANATHAWOCH @MARANATHAWOCH COMMENT Inbox  @Thaddyapostolic Group @Marantawoch