en
Feedback
Amharic Spritual Books

Amharic Spritual Books

Open in Telegram

በዚህ ቻናል መንፈሳዊ መፅሐፍት ፣ መፅሐፍ ቅዱስን ለማጥናት የሚረዱ ... የመጽሐፍ ቅዱስ ማብራሪያዎች ፣ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናቶች እንዲሁም መንፈሳዊ ጹሑፎች ይቀርባሉ ። "Christlikeness is the goal of every true believer."  @LovedandForgiven @Getu_Kebebe @mhbc74

Show more
6 528
Subscribers
+124 hours
+207 days
+13030 days

Data loading in progress...

Attracting Subscribers
June '26
June '26
+159
in 2 channels
May '26
+251
in 3 channels
Get PRO
April '26
+226
in 1 channels
Get PRO
March '26
+184
in 1 channels
Get PRO
February '26
+131
in 1 channels
Get PRO
January '26
+149
in 2 channels
Get PRO
December '25
+149
in 1 channels
Get PRO
November '25
+157
in 1 channels
Get PRO
October '25
+163
in 2 channels
Get PRO
September '25
+122
in 1 channels
Get PRO
August '25
+203
in 0 channels
Get PRO
July '25
+208
in 2 channels
Get PRO
June '25
+202
in 1 channels
Get PRO
May '25
+232
in 3 channels
Get PRO
April '25
+172
in 0 channels
Get PRO
March '25
+194
in 0 channels
Get PRO
February '25
+189
in 1 channels
Get PRO
January '25
+311
in 1 channels
Get PRO
December '24
+314
in 1 channels
Get PRO
November '24
+284
in 1 channels
Get PRO
October '24
+221
in 2 channels
Get PRO
September '24
+392
in 0 channels
Get PRO
August '24
+499
in 1 channels
Get PRO
July '24
+369
in 1 channels
Get PRO
June '24
+325
in 1 channels
Get PRO
May '24
+284
in 1 channels
Get PRO
April '24
+300
in 0 channels
Get PRO
March '24
+335
in 0 channels
Get PRO
February '24
+206
in 1 channels
Get PRO
January '24
+118
in 0 channels
Get PRO
December '23
+72
in 0 channels
Get PRO
November '23
+33
in 0 channels
Get PRO
October '23
+47
in 0 channels
Get PRO
September '23
+35
in 0 channels
Get PRO
August '23
+45
in 0 channels
Get PRO
July '23
+46
in 0 channels
Get PRO
June '23
+50
in 0 channels
Get PRO
May '23
+49
in 0 channels
Get PRO
April '23
+42
in 0 channels
Get PRO
March '23
+26
in 0 channels
Get PRO
February '23
+40
in 0 channels
Get PRO
January '23
+64
in 0 channels
Get PRO
December '22
+51
in 0 channels
Get PRO
November '22
+58
in 0 channels
Get PRO
October '22
+34
in 0 channels
Get PRO
September '22
+44
in 0 channels
Get PRO
August '22
+39
in 0 channels
Get PRO
July '22
+70
in 0 channels
Get PRO
June '22
+40
in 0 channels
Get PRO
May '22
+67
in 0 channels
Get PRO
April '22
+65
in 0 channels
Get PRO
March '22
+71
in 0 channels
Get PRO
February '22
+45
in 0 channels
Get PRO
January '22
+233
in 0 channels
Date
Subscriber Growth
Mentions
Channels
22 June+3
21 June+3
20 June+4
19 June+8
18 June+3
17 June+4
16 June+14
15 June+4
14 June+4
13 June+2
12 June+11
11 June+7
10 June+8
09 June+4
08 June+10
07 June+8
06 June+12
05 June+10
04 June+7
03 June+16
02 June+11
01 June+6
Channel Posts
“ልባችሁ አይጨነቅ፤ በእግዚአብሔር እመኑ፤ በእኔም ደግሞ እመኑ። በአባቴ ቤት ብዙ መኖሪያ አለ፤ ይህ ባይሆንማ ኖሮ እነግራችሁ ነበር፤ የምሄደውም ስፍራ ላዘጋጅላችሁ ነው። ሄጄም ስፍራ ካዘጋጀሁላችሁ በኋላ፣ እኔ ባለሁበት እናንተም ከእኔ ጋራ እንድትሆኑ ልወስዳችሁ ዳግመኛ እመጣለሁ። እኔ ወደምሄድበትም ስፍራ የሚያደርሰውን መንገድ ታውቃላችሁ።” ዮሐንስ 14፥1-4

2
#ያለ_ቅድመ_ሁኔታ_የሆነ_እምነት! ለአብርሃም ከእግዚአብሔር በመጀመሪያ የቀረበለት ጥሪ እንተዋወቅ የሚል አልነበረም። ምንም የመሰረቱት ግንኙነት፣ ትውውቅ ሳይኖር የራሴ የሚለውን ነገር ሁሉ የሚያስጥል፣ የሚያስክድ እንዲሁም እግዚአብሔር ወደሚያሳየው ምድር የመውጣት፣ እግዚአብሔርን የመከተል ጥሪ ነበር። እግዚአብሔር ለአብርሃም ተለይቶ የመውጣት ጥሪ ሲያቀርብለት አብርሃም  #WH_QUESTIONS? (What, why, How, who, when, Where, Which, whom) አላቀረበም፤ ቆም ብሎም አላሰበበትም፣ አላንገራገረም፣ አልተከራከረም፣ ስለ መንገዱም ማብራሪያ አልጠየቀም፤ ይልቁንም በደፈናው እግዚአብሔርን አመነውና እግዚአብሔር እንደ ነገረው ሄደ፣ ተከትሎት ሄደ፣ እግዚአብሔር ወደ ሚያሳየው ምድር ለመሄድ ወጣ። የአብርሃም እምነት እጅግ ያስገርማል! የተናገረውን፣....ተለይተህ እኔ ወደማሳይህ ምድር ውጣ ያለውን እግዚአብሔርን የሰማበት መስማት ምን አይነት ይሆን? እርሱ ይናገር እንጂ፣ የእርሱ ይሁን እንጂ የትስ ቢሆን በሚል ልበ ሙሉነት፤ በመንገዴ ላይ፣ በመንገዴም መጨረሻ ላይ ምን ይገጥመኝ ይሆን? ብሎ ሳይጠይቅ የተናገረውን እግዚአብሔርን ለመከተል ወጣ። ከመንገዱ፣ ከማያውቀው አገር፣ ሊገጥመው ከሚችለው ችግር ፍርሃት በላይ የጠራውን እግዚአብሔርን አመነ። እግዚአብሔር ከተናገረ፦ በምን፣ በማን፣ መቼ፣ እንዴት...የሚሉት ጥያቄዎች ሳያሳስቡት የተናገረውን ይፈጽማል። እኛስ ይህንን ከቅድመ ሁኔታ በላይ፣ ከእኛ ስጋት በላይ፣ ከእኛ አለመቻልና ውስንነት በላይ፣ ከምንለምነውና ከምናስበው በላይ መስራት የሚችለውን እግዚአብሔርን ያለ ምንም ቅድመ ሁኔታ፣ ያለማንገራገር ለማመን፣ እንደ ነገረን ተለይተን ለመውጣት ምን ያህል ቅርብ ነን? ✍️ መክሊት አየለ 📆 August 21, 2024 #HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional
93
3
እግዚአብሔርን ማስረጃ ሳንጠይቅ፣ ቅድመ ሁኔታ ሳናስቀምጥ ማመን፣ ልባችንን እርሱ ላይ መጣል፤ የሕይወታችንን መሪ ሙሉ በሙሉ ለእርሱ መልቀቅ ይሁንልን!! #HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional t.me/hopministry10
84
4
በታጠቁ፣ በተሰሩ፣ በተዘጋጁ ሰዎች መስራት የእግዚአብሔር ደስታው ነውና በእርሱ እንሰራ፣ እንታጠቅ፣ ለአገልግሎቱ እንደሚገባ እንዘጋጅ!! #HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional t.me/hopministry10
351
5
#ምርጥ_ምርጡን_ለእግዚአብሔር! አገልግሎት የእኛን ትጋት፣ ጥረት መጋደል ቢጠይቅም "Content wise" ከመልዕክት ይዘት አንጻር ግን የእኛን ምንም አይፈልግም። የምናቀርበው መልዕክት እግዚአብሔር ራሱ፣ የመልዕክቱ ሰጪም እርሱ ራሱ፣ መልዕክቱ የሚያወራውና የሚሰብከው እርሱን፣ ሥራውን፣  ማዳኑን፣  ፍቅሩን ነውና የእኛ የምንለው ምንም ነገር አያስፈልግም፤ ሊኖርበትም አይገባም። "Presentation wise" ከአቀራረብ አንጻር፣ መልዕክቱን ከምናቀርብበት መንገድ (Technics) አንጻር ግን መማር፣ መሰልጠን አለብን። የእግዚአብሔር የሆነውን ነገር ለማቅረብ ልህቀት (Excellence) ያስፈልገናል። ዘመኑ ያመጣቸውን የተለያዩ መንገዶች (Technologies) በጥበብ መጠቀም፣ በአግባቡ ለእግዚአብሔር ሥራ መዋጀት አለብን። የመልዕክቱ ሰጪ እና መልዕክቱ ዘመን አመጣሽ፣ ደግሞም ዘመን ያለፈበትና ዘመን የሚሽረው አይደለም። የምናዘምነው እግዚአብሔርም የለም። እርሱ ከዘመናት በፊት የነበረ፣ ያለ፣ ለዘላለምም የሚኖር ሕያው አምላክ ነው። ነገር ግን ይሄን ዘላለማዊ አምላክ የምንገልጥበት፣ መልዕክቱንም ለትውልዶች የምናስተላልፍበት መንገድ እንደየ ዘመናቱ ሊቃኝ፣ ዘመን አመጣሽ ነገሮችን ዋጅቶ ሊጠቀም ይችላል። እግዚአብሔርን ለማገልገል ሸክሙ ካለን፣ ጥሪውን እግዚአብሔር ካቀረበልን መልዕክቱንም ይሰጠናል፤ እድል፣ ጊዜ፣ ትውልድና መድረክም ይቸረናል። ይሄ ሁሉ ሲሆን ግን እኛ ለአገልግሎቱ እንደሚገባ ያልተዘጋጀን፣ ያልታጠቅን፣ ያልተሰራን፣ ያልተገራን፣ ያልሰለጠንን፣ መማር የሚገባንን ነገር ሁሉ ያልተማርን ከሆንን ከእግዚአብሔር አሳብ ጋር እንተላለፋለን፤ የእግዚአብሔርንም አሳብ በልህቀት (Excellence) ለትውልዶች ማቅረብ አንችልም። የእግዚአብሔር መንግሥት፣ ሥራውም ምርጥ የተባለ ነገር ሁሉ ይገባዋል። ምርጥ የተባሉ የቴክኖሎጂ ውጤቶችን፣ መንገዶችን በጥበብ እየዋጀን ለመንግሥቱ ሥራ ልናውል ይገባናል። እኛ የመንግሥቱ አገልጋዮችም የነቃን፣ የበቃን (የታጠቅን፣ የተማርን፣ የሰለጠንን)፣ ከእግዚአብሔር ጋር በመክረም፣ በመሰንበት ከእርሱ፣ ከቃሉ የተማርን፣ በጸሎት የተጋን፣ ከእግዚአብሔር ሥራ በፊት ሕይወታችን በእርሱ የተሰራ ልንሆን ይገባናል። ስለዚህ ሰከን ሳንል፣ ለእግዚአብሔር ሳንገኝ፣ በእርሱ ለመሰራት ፈቃደኛ ሳንሆን፣ በትምህርት እና በስልጠና፣ በዝግጅትም ራሳችንን ሳናበቃ እናገለግላለን ብለን አንጋጋጥ። ለአገልግሎት ያለንን መሻት፣ ትጋት ያህል፤ ለመማር፣ ለመዘጋጀት፣ ለእግዚአብሔር ለመገኘት፣ በእርሱ ለመሰራት፣ ለመገራት፣ ከእርሱ ጋር ለመዋል፣ ከእርሱ ለመቅዳት መሻት፣ ትጋት ይኑረን። ምርጥ ምርጡ ሁሉ ለእግዚአብሔር፣ ለመንግሥቱ ሥራም ያስፈልጋልና በጥበብ እየዋጀን ለመንግሥቱ ሥራ እናውለው። የእግዚአብሔርንም መንግሥት እናስፋበት!! በታጠቁ፣ በተሰሩ፣ በተዘጋጁ ሰዎች መስራት የእግዚአብሔር ደስታው ነውና በእርሱ እንሰራ፣ እንታጠቅ፣ ለአገልግሎቱ እንደሚገባ እንዘጋጅ!! ✍️ መክሊት አየለ 📆 June 21, 2026 #HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional
332
6
"እግዚአብሔር ሆይ፤ እንደ አንተ ያለ ማንም የለም፤ አንተ ታላቅ ነህ፤ የስምህም ሥልጣን ታላቅ ነው።" ኤርምያስ 10፥6
322
7
4_5998844439378793047.mp3
510
8
"ቀኖቹ ክፉ ናቸውና ዘመኑን በሚገባ ዋጁ።" ኤፌሶን 5፥16
518
9
ሊያገኘን፣ ከእኛ ጋር ሕብረት ሊያደርግ ናፍቆ እየጠበቀን ነው!! “እግዚአብሔር በሚገኝበት ጊዜ ፈልጉት፤ ቀርቦም ሳለ ጥሩት።” — ኢሳይያስ 55፥6 (አዲሱ መ.ት) #HOPMinistry #HearObey
ሊያገኘን፣ ከእኛ ጋር ሕብረት ሊያደርግ ናፍቆ እየጠበቀን ነው!! “እግዚአብሔር በሚገኝበት ጊዜ ፈልጉት፤ ቀርቦም ሳለ ጥሩት።”   — ኢሳይያስ 55፥6 (አዲሱ መ.ት) #HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional t.me/hopministry10
502
10
ሊያገኘን፣ ከእኛ ጋር ሕብረት ሊያደርግ ናፍቆ እየጠበቀን ነው!! “እግዚአብሔር በሚገኝበት ጊዜ ፈልጉት፤ ቀርቦም ሳለ ጥሩት።”   — ኢሳይያስ 55፥6 (አዲሱ መ.ት) #HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional t.me/hopministry10
390
11
"The greatest thing is to be found faithful where God has placed you."
473
12
#የዘላለም_ሕይወት እውነተኛ አምላክ ከሆነው ከእግዚአብሔር እንዲሁም የሕይወት ምንጭ ከሆነው ከልጁ ከኢየሱስ ክርስቶስ ውጪ በምንም አይገኝም። እውነተኛ እና ብቸኛ አምላክ የሆነውን እግዚአብሔርን ፤ እርሱ የላከውንም ልጁን ኢየሱስ ክርስቶስን ማወቅ ጊዜያዊ ጉዳይ ሳይሆን የዘላለም ሕይወት ነው። እውነተኛ አምላክ የሆነውን እግዚአብሔር አብን፣ እርሱም የላከውን አንድያ ልጁን ኢየሱስ ክርስቶስን ማወቅ እንደ ሌሎች የእውቀት አይነቶች አዕምሮን ለማስፋት፣ ለመረጃ ምንጭነት፣ ጠቢብ እና አዋቂ ለመባል፣ የተለያዩ ክህሎቶችን ለማግኘት ማወቅ ያለብን እውቀት ሳይሆን የሕይወት ጉዳይ ነው፤ ያውም የዘላለም ሕይወት ነው። እግዚአብሔር አብን፣ ልጁንም ኢየሱስ ክርስቶስን ያወቁ እርሱን ያዩ፣ ከእርሱ ሕይወትን የተካፈሉ ሰዎች ምስጉኖች ናቸው፤ የዘላለም ሕይወት አላቸው። የዘላለም ሕይወት የሆነ፣ የዘላለም ሕይወት የሚገኝበት እውቀት እግዚአብሔርን ማወቅ ነው። እግዚአብሔርን ላለማወቅ ልባችንን ስናደነድን እና ቸልተኞች ስንሆን የዘላለም ሕይወትን ችላ እያልን እንደሆነ እናስተውል!! አስተማሪ የሆነው፣ የእውነት መንፈስ፦ መንፈስ ቅዱስ ዕለት ዕለት እግዚአብሔርን እንድናውቅ፣ ከእርሱ ጋር ይበልጥ እንድንወዳጅ ይርዳን!! “እውነተኛ አምላክ የሆንኸውን አንተንና የላክኸውንም ኢየሱስ ክርስቶስን ያውቁ ዘንድ ይህች የዘላለም ሕይወት ናት።”   — ዮሐንስ 17፥3 (አዲሱ መ.ት) ✍️ መክሊት አየለ 📆 January 20 & August 19, 2022 #HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional
517
13
#ኢየሱስ_ይወደናል!! 📖 Hear. Obey. Practice. #HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional t.me/hopministry10+5
#ኢየሱስ_ይወደናል!! 📖 Hear. Obey. Practice. #HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional t.me/hopministry10
479
14
07_Fiker_Neh___ፍቅር_ነህ___Meskerem_Getu(128k).m4a
389
15
#እኔ_ምስክር_ነኝ! የእኔ ማንነት፣ የኋላ ታሪኬ፣ ባህሪዬ ታይቶ እና ሚዛን ላይ ተቀምጦ ቢሆን እግዚአብሔር እኔን የመረጠኝ፦ ከክብሩ የጎደልኹ፣ ለመንግሥቱ የማልበቃ፣ ከእግዚአብሔር ሕይወት የተለየሁ፣ ከሙታን መካከል አንዷ ነበርኹ። ነገር ግን በበደሌ እና በኃጢአቴ ሙት በነበርኹ ጊዜ እግዚአብሔር ከወደደኝ ከታላቅ ፍቅሩ የተነሣ ከክርስቶስ ጋር ሕይወትን ሰጠኝ፤ በእኔ ሥራ ሳይሆን በጸጋው አዳነኝ፣ የመንግሥቱ ወራሽ አደረገኝ። እግዚአብሔር ኃጢአተኞችን እንደሚወድ፤ በልጁ በክርስቶስ ኢየሱስ በኩልም ቀርቦ እንደሚታረቃቸው፤ ዳግም ልደት ሰጥቶ አዲስ ፍጥረት እንደሚያደርጋቸው፤ ኃጢአት፣ በደል፣ መተላለፋቸውን ሁሉ በልጁ በኢየሱስ ደም እንደሚያነጻ፣ ልጆቹ እንደሚያደርጋቸው እኔ ማሳያ ነኝ፣ እኔ ምስክር ነኝ። ዛሬ፣ ጌታ ፈቅዶ በሚጨምርልኝም ቀሪ እድሜ ጸጋው ቢበዛልኝና መንፈሱ ቢያግዘኝ የምተጋው፦ እንዲህ ለወደደኝ ኢየሱስ ታማኝ አፍቃሪው ለመሆን፣ ሞቴን ለሞተልኝ ኢየሱስ ሕይወቱን ልኖርለት ነው። #ኢየሱስ_ይወደናል!! ✍️ መክሊት አየለ 📆 June 19, 2026 #HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional
423
16
https://youtu.be/XKF-9NmmPRE?list=RDXKF-9NmmPRE
466
17
#እንደራሴ እንደራሴነቱ ለወከለው አካል እንጂ ለራሱ እና ለግል ጉዳዩ አይደለም። እንደራሴ በላኪው፣ በውክልና ሰጪው ቦታ ሆኖ እርሱ ቢሆን የሚያደርገውን ሁሉ ያደርጋል። የእንደራሴ ስራና ሀላፊነቱን በአግባቡ መወጣቱ በወካዩ (በላኪው) አካል ይገመገማል። አንድ እንደራሴ (አምባሳደር) አገሩን እና የአገሩን መንግሥት ወክሎ ወደ ሌላ አገር ሲሄድ፣ በዚያ በሚኖረው ቆይታ የላከውን መንግሥት ሳይሆን የራሱን አጀንዳ ሲያስፈጽም ቢሰነብት፣ ላኪውንም ባይወክል እንደራሴነቱ (አምባሳደርነቱ) ምን ላይ ነው? 2ኛ ቆሮንቶስ 5 (አዲሱ መ.ት) ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹⁸ ይህ ሁሉ ከእግዚአብሔር ነው፤ እርሱ በክርስቶስ አማካይነት ከራሱ ጋር አስታረቀን፤ የማስታረቅንም አገልግሎት ሰጠን፤ ¹⁹ እግዚአብሔር በክርስቶስ ዓለምን ከራሱ ጋር ሲያስታርቅ የሰዎችን በደል አይቈጥርባቸውም ነበር፤ ለእኛም ደግሞ የማስታረቅ ቃል ሰጠን። ²⁰ ስለዚህ እኛ የክርስቶስ እንደራሴዎች ነን፤ እግዚአብሔርም በእኛ አማካይነት ጥሪውን ያቀርባል፤ እኛም ከእግዚአብሔር ጋር ታረቁ ብለን በክርስቶስ እንለምናችኋለን።   ✍️ መክሊት አየለ 📆 February 23, 2025 #HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional
520
18
#እንደራሴ እንደራሴነቱ ለወከለው አካል እንጂ ለራሱ እና ለግል ጉዳዩ አይደለም። 📖 Hear. Obey. Practice. #HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional t.me/hopministry10
403
19
#ከምድሩ_የሚበልጥ_ተስፋ_አለን! ተስፋችን ወንዝ የማያሻግር፣ ወንዝ የማይሻገር አይደለም። ተስፋችን ራሱ የተባረከ ተስፋ ነው፤ የሚዳሰስ የሚጨበጥ አካል ያለው ነው። ተስፋችን በተለምዶው "ተስፋዬ እየመነመነ ሄደ" እንደምንለው አይነት ተስፋ አይደለም። ይልቁንም ተስፋ እያደረግነው እና እየጠበቅነው በሄድን ቁጥር የምንገናኝበት፣ ፊት ለፊት የምንተያይበት ቀን እየፈጠነ ነው። ቀን ሲጨምር ከሚያባብለን፣ ሊያዘገየን ከሚጣጣረው የዓለም ብልጭልጭ እያፈተለክን ወደ ተስፋችን እየተቃረብን ነው። በየመስሪያ ቤቱ፣ በየተቋማቱ የ5፣ የ10፣ የ30፣ የ50....ከዚያም በላይ ዓመት፦ እቅድ፣ ስትራቴጂካዊ ንድፍ እየተባለ የሚነገረን ነገር የምድርን ሕይወት ለማበጃጀት፣ በዚህ ያለንን ቆይታ የተሳካ ለማድረግ ቢጠቅምም፤ ማብቂያ፣ የቁርጥ ቀን፣ ፍጻሜ ግን አለው። ሁሉን እያስጌጥን፣ እያስዋብን እዚህ መኖራችን አይቀጥልም። ከዚህኛው ሕይወት የሚበልጥ ሕይወት፣ ከዚህ ምድር ያለፈ ተስፋ አለን። ክርስቶስም ለዚህች ሕይወት ብቻ ተስፋ አይደረግም። የተባረከውን ተስፋችንን ተስፋ እያደረግን፦ በጽናት፣ በትጋት ነቅቶ መጠበቅ፣ መኖር ይሁንልን!! “ክርስቶስን ተስፋ ያደረግነው ለዚህች ሕይወት ብቻ ከሆነ፣ ከሰው ሁሉ ይልቅ የምናሳዝን ነን።”   — 1ኛ ቆሮንቶስ 15፥19 (አዲሱ መ.ት) “እኛ ግን አገራችን በሰማይ ነው፤ ከዚያ የሚመጣውንም አዳኝ፣ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስን በናፍቆት እንጠባበቃለን፤”   — ፊልጵስዩስ 3፥20 (አዲሱ መ.ት) ዮሐንስ 14 (አዲሱ መ.ት) ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹ “ልባችሁ አይጨነቅ፤ በእግዚአብሔር እመኑ ፤ በእኔም ደግሞ እመኑ። ² በአባቴ ቤት ብዙ መኖሪያ አለ፤ ይህ ባይሆንማ ኖሮ እነግራችሁ ነበር፤ የምሄደውም ስፍራ ላዘጋጅላችሁ ነው። ³ ሄጄም ስፍራ ካዘጋጀሁላችሁ በኋላ፣ እኔ ባለሁበት እናንተም ከእኔ ጋር እንድትሆኑ ልወስዳችሁ ዳግመኛ እመጣለሁ። ✍️ መክሊት አየለ 📆 June 18, 2026 #HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional
495
20
የተባረከውን ተስፋችንን ተስፋ እያደረግን፦ በጽናት፣ በትጋት ነቅቶ መጠበቅ፣ መኖር ይሁንልን!! 📖 Hear. Obey. Practice. #HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional t.me/hopministry10
422