cookie

Utilizamos cookies para mejorar tu experiencia de navegación. Al hacer clic en "Aceptar todo", aceptas el uso de cookies.

avatar

Amharic Spritual Books

በዚህ ቻናል መንፈሳዊ መፅሐፍት ፣ መፅሐፍ ቅዱስን ለማጥናት የሚረዱ ... የመጽሐፍ ቅዱስ ማብራሪያዎች ፣ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናቶች እንዲሁም መንፈሳዊ ጹሑፎች ይቀርባሉ ። @mhbc74

Mostrar más
Publicaciones publicitarias
2 560
Suscriptores
+1324 horas
+747 días
+31830 días

Carga de datos en curso...

Tasa de crecimiento de suscriptores

Carga de datos en curso...

ፓስተር_አገኘሁ_ይደግ_አንድ_ቀን_Pastor_Agegnehu_Yideg_And_Ken128k.mp35.90 MB
በዚህ ምድር ስንኖር በሕይወት የሚያኖረን ክርስቶስ እንደሆነ ብናምንም በዚህች ሕይወት ብቻ እርሱን ተስፋ አናደርግም፤ ለኋለኛው ለዘላለም ቤታችንም ሕያውና የተባረከ ተስፋችን እርሱ ራሱ ነው። የዚህ ምድር ኑሮ፣ የምናልፍበት መንገድ ስንቴ ነው ተስፋ የሚያስቆርጠን? በሌላ ገጹ ደግሞ ስንቴ ነው ያሰብነው ተሳክቶ መቼም ምድርን ለቀን የማንሄድ እስኪመስለን ድረስ የተመቻቸነው? በዚህ ሁሉ ውስጥ ግን በምድር ከሚሆነው ነገር እልፍ ብለን፣ አሻግረን የሰማዩን ባናይ፣ አይኖቻችን ኢየሱስ ላይ ባይተከሉ ኖሮ፣ ክርስቶስን ተስፋ ያደረግነው ለዚህች ሕይወት ብቻ ከሆነ፣ ከሰው ሁሉ ይልቅ የምናሳዝን ነን፤ ከምድር እልፍ የማይሉ ለፍተው መና በተባልንም ነበር። ነገር ግን ተስፋችን በምድር ካለው፣ ከሚታየው፣ ከሚያዝለን፣ ከሚሞተው ያለፈ ነው፤ ሕያው ነው፤ ያቺ ቀን ስትደርስ እርሱ እኛን እንዳወቀን እኛም እናውቀዋለን! የተባረከው ተስፋችንን ፊት ለፊት እናየዋለን። ስለዚህ የዚህን ዘመን ሥቃይም ሆነ ተድላ ወደፊት ለእኛ ሊገለጥ ካለው ክብር ጋር አናወዳድረውም። ጌታችን ኢየሱስ ዳግም በመምጣቱ ለዘላለም እንደሚያሳርፈን እያመንን፣ እርሱን እያሰላሰልን፣ ከቤቱ ርቆ በእንግድነት እንደሚኖር ሰው ለእርሱ ታምነን፣ አይኖቻንን እርሱ ላይ ተክለን እንጠብቀዋለን!! #ኢየሱስ_በክብር_ተመልሶ_ይመጣል!! " በዚች ሕይወት ብቻ ክርስቶስን ተስፋ ያደረግን ከሆነ፥ ከሰው ሁሉ ይልቅ ምስኪኖች ነን።" (1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 15:19)
Mostrar todo...
Track-08-አለ-የሚገባው-Bereket-Lemma.m4a5.75 MB
#በሚያስፈልገን_ጊዜ!! በእግዚአብሔር ጸጋ ፊት ድካም፣ ጉድለት፣ አለመቻል....አቅም አይኖረውም።እግዚአብሔርም ለትሁታን ጸጋ ሰጪ፤ የርህራሄ አባት ስለሆነ ሳንፈራ፣ ሳንሸማቀቅ፣ የሆንነውን ሆነን፣ ከነ ጉድለታችን፣ ሲደክመን ደክሞናል፣ ሲያቅተን አቃተን፣ ሳንችል አልቻልንም እያልን ወደ ጸጋው ዙፋን በእምነት እንቀርባለን። በክርስትና ሕይወታችን ከእግዚአብሔር ጸጋ ውጪ የሆነ እና የሚሆን ነገር የለም። የእግዚአብሔር ጸጋ አድኖናል፣ ሕይወት ሰጥቶናል፣ በኀጢአት መኖርንና ዓለማዊ ምኞትን አስክዶናል፣ በአሁኑ ዘመንም ራሳችንን በመግዛት በጽድቅ፣ በእውነተኛ መንፈሳዊ ሕይወት እንድንኖር ያስተምረናል። በእኛ ሕይወት የእግዚአብሔር ጸጋ ያላደረገው፣ ጎደለብን የምንለው ነገር የለም። ሁሉ በእርሱ ሆኖልናል፤ ነገም ለሚገጥመን ነገር፣ ለምናልፈው የሕይወት ጎዳና ጸጋው ዋስትናችን ነው። እኛ ስንዝል ጸጋው ብርቱ ነው፤ እኛ ስንስት ጸጋው ትክክል ነው፤ እኛ ሩጫውን መቀጠል ሲከብደን ጸጋው እግሮቻችንን ያጸናል። #የእግዚአብሔር_ጸጋ ያለመከልከል ለእኛ ተዘጋጅቶልናል፤ #ወደ_ጸጋው_ዙፋን_በእምነት በመቅረብ የዚህ ጸጋ ተካፋዮች እንሁን! ቀሪ ዘመናችንን ለእግዚአብሔር አደራ እንስጥ፤ ጸጋውን ብቻ እንደገፍ! #በሚያስፈልገን_ጊዜ የሚረዳን የእግዚአብሔር ጸጋ አለ!! “እንግዲህ ምሕረትን እንድንቀበልና በሚያስፈልገንም ጊዜ የሚረዳንን ጸጋ እንድናገኝ፣ ወደ ጸጋው ዙፋን በእምነት እንቅረብ።” — ዕብራውያን 4፥16 (አዲሱ መ.ት) “Let us then fearlessly and confidently and boldly draw near to the throne of grace (the throne of God's unmerited favor to us sinners), that we may receive mercy (for our failures) and find grace to help in good time for every need (appropriate help and well-timed help, coming just when we need it).” — Heb 4፥16 (AMP) ቲቶ 2 (አዲሱ መ.ት) ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹¹ ድነት የሚገኝበት የእግዚአብሔር ጸጋ ለሰዎች ሁሉ ተገልጦአልና፤ ¹² ይህም ጸጋ በኀጢአት መኖርንና ዓለማዊ ምኞትን ክደን፣ በአሁኑ ዘመን ራሳችንን በመግዛት በጽድቅ፣ በእውነተኛ መንፈሳዊ ሕይወት እንድንኖር ያስተምረናል፤
Mostrar todo...
5
#በመንፈስ_ቅዱስ_የእግዚአብሔር_Realm_access_ይደረጋል፤ #የእግዚአብሔር_ሕይወት_ይኖራል። ይሄማ በእኔ አቅም አይቻልም፣ ላደርገው አልችልም፣ ከዚህ ነገር መለየት ይከብደኛል፣ ይህን ማድረግ የማይታሰብ ነው....የመሳሰሉት እልፍ የውስንነት፣ የድካም፣ ያለመብቃት አይነቶች ዘወትር ወደ ራሳችን በተመለከትን ቁጥር ጎልተው ይታዩናል። እግዚአብሔር በእኛ መስራት የወደደውን ነገር የሚሰራው፣ እርሱ በእኛ ሊኖረው የፈለገውን ሕይወት የሚኖረው በእኛ አቅም እና በእኛ ልመና ልክ ሳይሆን ከለመንነውና ከምናስበው በላይ፣ በእኛ በሚሰራው ኃይሉ ልክ ነው። ይህ የእግዚአብሔር ኃይል ደግሞ መንፈስ ቅዱስ ነው። ለእግዚአብሔር ለመኖር መንፈስ ቅዱስን አብዝቶ መጠጋት፣ እርሱ ውስጥ መሰወር የግድ አስፈላጊ ነው!! በመንፈስ ቅዱስ ከሆነ የእግዚአብሔርን ሕይወት መኖር እጅግ ቀላል ነው!! ኤፌሶን 3 (አዲሱ መ.ት) ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ²⁰ እንግዲህ በእኛ ውስጥ እንደሚሠራው እንደ ኀይሉ መጠን፣ ከምንለምነው ወይም ከምናስበው ሁሉ በላይ እጅግ አብልጦ ማድረግ ለሚቻለው፣ ²¹ በቤተ ክርስቲያን እንዲሁም በክርስቶስ ኢየሱስ፣ በዘመናት ሁሉ ከዘላለም እስከ ዘላለም ለእርሱ ክብር ይሁን፤ አሜን።
Mostrar todo...
4_5904409198145310654.mp34.86 MB
የሚቀይር፣ የሚያድስ፣ የሚለውጥ፣ የሚያሳድግ፣ በሕይወት የሚያኖር #ቆይታ! #ከእግዚአብሔር_ጋር፣ #በእርሱ_ውስጥ፣ #በፊቱ_የሚደረግ_ቆይታ! ከእግዚአብሔር ጋር ሆኖ፣ በፊቱ ቆይቶ እንደነበረ፣ እንደ ቀድሞው የሚቀጥል አንድም የለም፤ ሕያው እግዚአብሔር ሕያው ያደርጋል፣ ይሰራል፣ ያሳድጋል፣ ያለመልማል። የእግዚአብሔር ቃል፦ "እግዚአብሔርን ፈልጉ ሕያዋንም ሁኑ።" እንደሚል እኛም ለሕያውነት፣ ለልምላሜ ዘወትር ወደ እርሱ እንገሰግሳለን። ነፍሳችንን ከመድረቅ የሚጠብቃት፣ እኛን ከውስጥ ሰውነት ክሳት የሚገላግለን ራሱ እግዚአብሔር እንደሆነ ስለገባን እርሱን ከመፈለግ ወደኋላ አንልም። ብርታት የማይሰጡ፣ የሚያዝሉ፣ ትኩረታችንንም የሚወስዱ ብዙ ነገሮች እያሉ እኛ ግን ለእግዚአብሔር ለመገኘት፣ እርሱንም ለማግኘት እንበረታለን፤ እርሱን ለማግኘት ሁሉን እናጣለን። በሕይወት አኗሪያችን፣ መኖሪያችን እግዚአብሔርም ራሱን ሳይደብቅ፣ መገኘቱን ሳይሰስት እንደ ንጋት ብርሃን ይገለጥልናል!! እናንተ ሳትታክቱ እግዚአብሔርን የምትፈልጉ፣ ፊቱን የምትሹ ሁሉ ጽኑ!! ልባችሁም ይበርታ!!
Mostrar todo...
1
4_5866176335579190512.mp314.07 MB
መንፈስ ቅዱስ ሰሞነኛ ወሬ፣ ጊዜያዊ ትኩረት፣ የአንድ ወቅት ጩኸት አይደለም። ይልቁንም ክርስትናን ለመኖር፣ ሕያው ሆኖ ለእግዚአብሔር ለመሰንበት አስፈላጊ መሰረት እንጂ። የመንፈስ ቅዱስ ማንነት ሲገባን፤ ያለ እርሱም ለእግዚአብሔር መኖር፣ ኢየሱስን ማክበር እንደማይቻል ስንረዳ የያዝናቸውን ትኩረት ሊሆኑ ያልተገቡ ትኩረቶች እንለቃለን፣ መንፈስ ቅዱስ የእግዚአብሔርን ሕይወት በእኛ እንዲገልጥ እንፈቅዳለን፣ ከመንፈስ ቅዱስ ጋር ያለንን ቁርኝት ጥብቅ! እናደርጋለን። ኢየሱስን ለማክበር ሌላ ሌላ ነገር ሳይሆን #መንፈስ_ቅዱስ_ብቻ! እንደሚያስፈልግ ሲገባን የእኛን መባከን አቁመን ሁለንተናችንን፣ ስፍራውን ሁሉ ለመንፈስ ቅዱስ እናስገዛለን።ጌታ እግዚአብሔር የልቦና አይኖቻችንን ያብራ!!
Mostrar todo...
🔥 3👍 1
"Apart from dependence on and desperation for God, we will not only miss the ultimate point of our mission, but we will also neglect the ultimate need of our souls."
Mostrar todo...
Elige un Plan Diferente

Tu plan actual sólo permite el análisis de 5 canales. Para obtener más, elige otro plan.