Amharic Spritual Books
前往频道在 Telegram
በዚህ ቻናል መንፈሳዊ መፅሐፍት ፣ መፅሐፍ ቅዱስን ለማጥናት የሚረዱ ... የመጽሐፍ ቅዱስ ማብራሪያዎች ፣ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናቶች እንዲሁም መንፈሳዊ ጹሑፎች ይቀርባሉ ። "Christlikeness is the goal of every true believer." @LovedandForgiven @Getu_Kebebe @mhbc74
显示更多6 511
订阅者
+1024 小时
+487 天
+13930 天
数据加载中...
吸引订阅者
六月 '26
六月 '26
+112
在2个频道中
五月 '26
+251
在3个频道中
Get PRO
四月 '26
+226
在1个频道中
Get PRO
三月 '26
+184
在1个频道中
Get PRO
二月 '26
+131
在1个频道中
Get PRO
一月 '26
+149
在2个频道中
Get PRO
十二月 '25
+149
在1个频道中
Get PRO
十一月 '25
+157
在1个频道中
Get PRO
十月 '25
+163
在2个频道中
Get PRO
九月 '25
+122
在1个频道中
Get PRO
八月 '25
+203
在0个频道中
Get PRO
七月 '25
+208
在2个频道中
Get PRO
六月 '25
+202
在1个频道中
Get PRO
五月 '25
+232
在3个频道中
Get PRO
四月 '25
+172
在0个频道中
Get PRO
三月 '25
+194
在0个频道中
Get PRO
二月 '25
+189
在1个频道中
Get PRO
一月 '25
+311
在1个频道中
Get PRO
十二月 '24
+314
在1个频道中
Get PRO
十一月 '24
+284
在1个频道中
Get PRO
十月 '24
+221
在2个频道中
Get PRO
九月 '24
+392
在0个频道中
Get PRO
八月 '24
+499
在1个频道中
Get PRO
七月 '24
+369
在1个频道中
Get PRO
六月 '24
+325
在1个频道中
Get PRO
五月 '24
+284
在1个频道中
Get PRO
四月 '24
+300
在0个频道中
Get PRO
三月 '24
+335
在0个频道中
Get PRO
二月 '24
+206
在1个频道中
Get PRO
一月 '24
+118
在0个频道中
Get PRO
十二月 '23
+72
在0个频道中
Get PRO
十一月 '23
+33
在0个频道中
Get PRO
十月 '23
+47
在0个频道中
Get PRO
九月 '23
+35
在0个频道中
Get PRO
八月 '23
+45
在0个频道中
Get PRO
七月 '23
+46
在0个频道中
Get PRO
六月 '23
+50
在0个频道中
Get PRO
五月 '23
+49
在0个频道中
Get PRO
四月 '23
+42
在0个频道中
Get PRO
三月 '23
+26
在0个频道中
Get PRO
二月 '23
+40
在0个频道中
Get PRO
一月 '23
+64
在0个频道中
Get PRO
十二月 '22
+51
在0个频道中
Get PRO
十一月 '22
+58
在0个频道中
Get PRO
十月 '22
+34
在0个频道中
Get PRO
九月 '22
+44
在0个频道中
Get PRO
八月 '22
+39
在0个频道中
Get PRO
七月 '22
+70
在0个频道中
Get PRO
六月 '22
+40
在0个频道中
Get PRO
五月 '22
+67
在0个频道中
Get PRO
四月 '22
+65
在0个频道中
Get PRO
三月 '22
+71
在0个频道中
Get PRO
二月 '22
+45
在0个频道中
Get PRO
一月 '22
+233
在0个频道中
| 日期 | 订阅者增长 | 提及 | 频道 | |
| 13 六月 | +2 | |||
| 12 六月 | +11 | |||
| 11 六月 | +7 | |||
| 10 六月 | +8 | |||
| 09 六月 | +4 | |||
| 08 六月 | +10 | |||
| 07 六月 | +8 | |||
| 06 六月 | +12 | |||
| 05 六月 | +10 | |||
| 04 六月 | +7 | |||
| 03 六月 | +16 | |||
| 02 六月 | +11 | |||
| 01 六月 | +6 |
频道帖子
ስምንት (8) እራቅ ሁለት (2) ሽሽ ✍️
:
#ክፍል 3
ሁለት ሽሽ (2)
በመሸሽ ማሸነፍ አለ 🙏
1 ገንዘብን ከሚወዱ ሰዎች ሽሽ !
ዕብ 13፥5
ገንዘብን የሚወድ አማላኩን ይክዳል በምንም አይደራደርም ገንዘብን አምላኩ አድርጓልና
የገንዘብ ገዢ እንጂ ተገዢ አትሁኑ የሚባለው ለዚህ ነው
ገንዘብን የሚወድ ሰው ህይወቱ የተመሰረተው በገንዘብ እንደሆነ ስለሚያምን ገንዘብን ከሚያጣ አምላኩን ቢተው ይመርጣል
ገንዘብን የሚወድ ህይወቱን በመስጠት ለገንዘብ ይገዛል
:
ገንዘብ ደስታ ይሰጣል በሚል እምነት ውስጥ ይገባል ገንዘብን ካጣ መኖር እደማይችል ለራሱ ይናግራል ህይወቱም የገንዘብ ተገዢ ይሆናል
:
ይሆን አትርሱ ገንዘብ ያስፈልጋል ግን ደስታን አይሰጥም ደስታን የሚሰጠው እግዚአብሔር ብቻ ነው ገንዘብ ቢገኝ ባይገኝ እኛ ግን በእግዚአብሔር ሁሌም ደስ ይለናል ደስታችሁን በእግዚአብሔር ላይ አድርጉ
:
2 ከክፉ የወጣትነት ምኞት ሽሽ !
2 ጢሞ 2፥22
በወጣትነት ከምንመኛቸው ክፉ እግዚአብሔር ከማያከብረው ምኞቶች መሸሽ
ዳዊት ከተሰወረ ሀጥያቴ ሲል ይህን ያለበት ምክንያት ሰው ሳያውቅ ሳንናገር በምናባችን የምንሰራቸው ሀጥያቶች አሉ የእግዚአብሔር ፈቃድ የሌለበት ሀጥያትን የሚወልድ ምኞት መሸሽ አለብን
:
መፀሀፍ ሲናገር ምኞት ሀጥያትን ትወልዳለች ይላል በዚህ በወጣትነት እድሜ በአይምሮ የሚታሰብ እግዚአብሔር የማይከብርበት በሀጥያት የተሞላ ምኞት አለ ከዚህም መሸሽ ተገቢና አስፈላጊ ነው !
:
እግዚአብሔር የማይወደውን አንወድም እግዚአብሔር ሀጥያትን የሚጸየፍ ቅዱስ ነው እኛም ክርስቶስ ስለሀጥያታችን በከፈለው ዋጋ ከሀጥያታችን ታጥበናል አሁን በእርሱ ቅዱሳን ሆነናል ስለዚህም ከሀጥያት በመራቅ አምላካችን በሚከብርበት እንገኝ
:
#ተባረኩልኝ 🙏
:
https://t.me/mhbc5
ለጥያቄ:@msalewoch
https://t.me/lifewithchristjesus| 2 | በሕንጸት የመጽሐፍ ክበብ፣ እሑድ፥ ሰኔ 07 ቀን፥ 2018 ዓ.ም. ለውይይት የሚቀርበው መጽሐፍ፣ “በዓለቱ ላይ፥ የኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት ታሪክ" የተሠኘው፥ በሊድያ ተስፋዬ የተጻፈው መጽሐፍ ይኾናል። በውይይቱ ላይ መታደም የምትሹ ኹሉ፣ ከሣር ቤት ወደ ቫቲካን ኢምባሲ በሚወስደው መንገድ ላይ በሚገኘው የኢትዮጵያ ሥነ መለኮት ድኅረ ምረቃ ት/ቤት (EGST) መሰብሰቢያ አዳራሽ በ9 ሰዓት ላይ እንድትገኙ በአክብሮት እንጋብዛለን።
ሕንጸት የመጽሐፍ ክበብ
በፌስቡክ ገጻችን ይከተሉን:- http://facebook.com/hintset
ቴሌግራም ላይ ይከተሉን:- https://t.me/hintset
ዩትዩብ ላይ ሰብስክራይብ ያድርጉ:- http://youtube.com/hintsetube
በቲክቶክ፡- https://www.tiktok.com/@hintsetethiopia
ድረ ገጻችንን ይጎብኙ:- http://www.hintset.org | 317 |
| 3 | ስምንት (8) እራቅ ሁለት (2) ሽሽ✍️
:
#ክፍል 2
👉በህይወታችን ልንርቃቸው የሚገቡ 8 አይነት ሰዎች አሉ ፦
:
6 ፀብን ከሚጭሩ (ከሚዘሩ) ሰዎች እራቅ !
በቤተክርስቲያን በስራ ስፍራ በተለያዩ ቦታዎች እንደነዚህ አይነት ሰዎች አሉ ፀብን የሚዘሩ ወንድምን ከወንድም የሚያጋጩ ፍቅርን የሚያቀዘቅዙ ከነዚህ ጥላቻን ከሚያሰፉ ሰዎች መራቅ አለብህ በነዚህ ምክንያት ወደ ንዴት እድትገባ እና አንተ ከእግዚአብሔር ጋር ያለህን ግንኑነት እንድታቋርጥ ያደርግሀል
7 ሞኝነት ካለባቸው ሰዎች እራቅ !
ቲቶ 3፥9
የአይምሮ ብስለት ከሌላቸው መንፈሳዊ እድገት ከሌላቸው ፍሬ ከማያፈሩ ማደግ ከማይፈልጉ ሰዎች እራቅ
8 ከጠማማ ሰዎች እራቅ!
ቲቶ 3፥10-11
ሁሌም ጠማማ ነገር ከሚያስብ ሁሉ ውድቀትን አለመሳካትን ተስፋ መቁረጥን ከሚነገሩ መልካም ነገር እደማይገጥም ከሚያውጁ ከሚነገሩ ስደክም በቃ ይበቃልሀል መቀጠል አትችልም ከሚሉ ጠሞሞ ሀሳብ ካላቸው ሰዎች እራቅ ። ምክንያቱም በእግዚአብሔር ላይ ያለህን እምነት እድታጣ እና ተስፋ እድትቆርጥ ያደርግሀል ።
:
ሰለዚህ ከነዚህ 8 አይነት ሰዎች መራቅ አለብህ እነዚህ ሰዎች ለእድገታችን መሰናክል ይሆናሉ ወደ ውድቀትም ይመራሉ ስለዚህ በማሰተዋል ከነዚህ ሰዎች መራቅ አለብን ።
:
በህይወታችን ልንሸሽ የሚገባን
ሁለት (2) ነገሮች ✍️
:
እነዚህ ሁለት ነገሮች በመንፈሳዊ ህይወታችን እንዳናድግ ከማያደርጉን ዋና ነገሮች ውስጥ የመጀመሪያዎቹ ናቸው ፍሬ እዳናፈራ በተለይም በወጣትነት እድሜ ላይ እግዚአብሔር እዳንቀርብ ከምያደርጉን ነገሮች ውስጥ ዋናዎቹ ናቸው ። እነሱም ፦ .....
ይቀጥላል 🙏
:
https://t.me/mhbc5
ለጥያቄ:@msalewoch
https://t.me/lifewithchristjesus | 399 |
| 4 | እግዚአብሔር ክፍተታችን፣ ጉድለታችን፤ ሙላታችንም ነው።
📖 Hear. Obey. Practice.
#HOPMinistry #HearObeyPractice
#DailyDevotional
t.me/hopministry10 | 384 |
| 5 | #ክፍተታችንን_በልባችን_ሰሪ_መሙላት!
ክፍተታችንን፣ ጉድለታችንን እግዚአብሔር ያውቀዋል፣ ሆነ ብሎም ሰርቶታል፤ ደግሞ እርሱ ብቻ ይሞላዋል፣ በእርሱ ብቻ ይሞላል።
ልብን በሚያዝል፣ በሚያጎድል፣ ብርታት በማይሰጥ፣ በሚያደርቅ፣ ወከባ እና ግርግር በበዛበት ዓለም እየኖርን ልባችንን መሙላት፣ ማሳረፍ፣ መደገፍ፣ መጠበቅ የምንችለው በልባችን ሰሪ፣ ሙሉ አድራጊ፣ በክፍተታችን በእግዚአብሔር ብቻ ነው።
ክፍተታችን፣ ጉድለታችን እግዚአብሔር፤ የሚሞላው፣ አሳራፊያችንም ያው እርሱ ነው፤ አይደለም ጉድለታችንን ሊሞላው ይቅርና ልባችን ላይ ጠብ ብሎ በማያርሰን ነገር ክፍተታችንን ለመሙላት እንባክን። ይልቁንም ሙላታችን፣ ሁሉ በሁሉ ወደ ሆነው ወደ እግዚአብሔር አብዝተን እየተጠጋን በሙላት እንኑር።
✍️ መክሊት አየለ
📆 June 12, 2026
#HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional | 363 |
| 6 | 9_Azeb_Hailu_6_Feligut(128k).m4a | 471 |
| 7 | 🔐 #Our_Quality_Time_with_God
ከአምላክ ጋር እንደመዋል፣ ከእግዚአብሔር ጋር እንደመቆየት፣ በእርሱ መገኘት ውስጥ ለመክረም ሁሉን ከመጣልና ወደ እርሱ ከመገስገስ ጋር የሚገናኝ ሌላ መልካም እድል የለም።
ትናንትን፣ ከትናንት ወዲያን፣ አምናን አቻምናን ወደ ኋላ ዘወር ብለን አይተን ከእግዚአብሔር ጋር የነበርንበትን ጊዜ፣ ፊቱን የፈለግንበትን ወቅት ብንመረምር ብዙ የጸሎት ፍቅር፣ የማይረሳ የእግዚአብሔር መገኘት፣ በእግዚአብሔር ፊት ያለዝለት እንድንንበረከክ የሚያደርግ የፊቱ ረሃብ ሊኖረን ይችላል።
ዛሬ ላይ ቆመን ራሳችንን ስናይ ግን ያ ያኔ የተነካንበት መነካት እግዚአብሔርን ደግሞ ላለመፈለግ በቂ ሆኖ ከፊቱ ሲያርቀን አላየንም፤ ይልቁንም ያ መነካት ሌላ እልፍ ረሃብ ወልዶ፣ ጥቂት የቀረብነው እግዚአብሔር ከምንም ነገር በላይ ልንቀርበው የተገባ ብቸኛው ክፍተታችን መሆኑን ተረድተን፣ ያለ እርሱ ህልውና መኖር ለነፍሳችን ክሳት መሆኑን አውቀን፣ ጸሎትና የእግዚአብሔርን ፊት መፈለግ የማይለመድ ዋና ነገራችን መሆኑ ገብቶን በእግዚአብሔር እግር ስር አለን።
የጸሎት ትልቁ ስራውና ዋና ጥቅሙ እኛን ከእግዚአብሔር ጋር ከማጣበቁ የተነሳ በእግዚአብሔር ፍቅር የተያዙ፣ ከመጸለይና ፊቱን ከመፈለግ ውጪ ሌላ አማራጭ የሌላቸው የእግዚአብሔር ወዳጆች ማድረጉ ነው።
የዛሬው መቃተት፣ የዛሬው በእግዚአብሔር ፊት መቆየት ለነገው ፍለጋ አቅም የሚወልድ፣ የጸሎትን ረሃብ ዘር በልባችን የሚዘራ ትልቅ መነሻ ነውና ነገን በብዙ እግዚአብሔርን ለመፈለግ ዛሬን በእግዚአብሔር ፊት እንቆይ፤ ዛሬ ከጸለይን ነገን ሳንጸልይ መዋል ይከብደናል፣ የለመድነው የእግዚአብሔር ጠረን ሊያባክኑን ከሚጥሩ ብዙ ነገሮች መሃል አልፎ ስለሚሸተን ሁሉን ጥለን ወደ እርሱ፣ ወደ ፊቱ፣ ወደ ህልውናው ለመገስገስ አቅም ይሆነናል።
እየጸለይን እንጸልይ!!
✍️ መክሊት አየለ
📆 November 10, 2023
#HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional | 469 |
| 8 | የጸሎት ትልቁ ስራውና ዋና ጥቅሙ እኛን ከእግዚአብሔር ጋር ከማጣበቁ የተነሳ በእግዚአብሔር ፍቅር የተያዙ፣ ከመጸለይና ፊቱን ከመፈለግ ውጪ ሌላ አማራጭ የሌላቸው የእግዚአብሔር ወዳጆች ማድረጉ ነው።
📖 Hear. Obey. Practice.
#HOPMinistry #HearObeyPractice
#DailyDevotional
t.me/hopministry10 | 387 |
| 9 | 📖 Hear. Obey. Practice.
“ወደ እርሱ የሚመለከቱ ያበራሉ፤ ፊታቸውም ከቶ አያፍርም።”
— መዝሙር 34፥5 (አዲሱ መ.ት)
“ወደ እርሱ ቅረቡ ያበራላችሁማል፥ ፊታችሁም አያፍርም።”
— መዝሙር 34፥5
#HOPMinistry #HearObeyPractice
#DailyDevotional
t.me/hopministry10 | 439 |
| 10 | ቤተልሔም_ወልዴ_አንተ_ብቻህን_በቂ_ነህ_Ante_Bchahin_Beki_Neh_Bethelihem_wolde.m4a | 372 |
| 11 | "እንግዲህ ጥበብ እንደሌላቸው ሳይሆን እንደ ጥበበኞች እንዴት እንደምትኖሩ ተጠንቀቁ። ቀኖቹ ክፉ ናቸውና ዘመኑን በሚገባ ዋጁ። ስለዚህ ሞኞች አትሁኑ፤ የጌታ ፈቃድ ምን እንደ ሆነ አስተውሉ እንጂ።"
ኤፌሶን 5፥15-17 | 418 |
| 12 | ስምንት (8) እራቅ ሁለት (2) ሽሽ ✍️
:
#ክፍል 1
ከማይጠቅም ነገር በመራቅ ህይወትን ማሳደግ አስፈላጊ ነው
👉በህይወታችን ልንርቃቸው የሚገቡ 8 አይነት ሰዎች አሉ ፦
ከእነዚህ ሰዎች አለመራቅ መበከልን ያመጣል እናስተውል !
:
1 ለዚህ አለም ከሚመች ሰዎች እራቅ !
1ጢሞ 6፥4-7
ዓለም እንደወደደው ከሚሰራበት ሰው አላማ ከሌለው ሰው እራቅ
2 እግዚአብሔር መምሰል ማትረፊያ ከሚመስላቸው ሰዎች እራቅ !
2ጢሞ 2፥16 ይህ ማለት እግዚአብሔር በሰጣቸው ፀጋ የሚነግዱ እረሳቸውን ከፍ ከሚያደርጉ ስዎች መራቅ አለብህ
3 ዝም ብለው ከሚያወሩ እና ከሚከራከሩ ሰዎች እራቅ (ውሸትን እውነት ከሚያደርጉ ሰዎች ) ! 2ጢሞ 2፥16
ምክንያቱም ጊዜህን ይበላል ህይወትህን ይበላል ጥርጣሬ ውስጥ ያስገባሀል
4 ከአመፃ እራቅ !
ማመፅ በብዙ መንገድ ይከፈላል ግን የትኛውም አመፃ ለክርስቶስ የተለየ ሰው ተግባር አይደለም
5 የአምልኮ መልክ ካላቸው ግን ውስጣቸው ባዶ ከሆኑ ስዎች እራቅ ! 2 ጢሞ 3፥5
⋕ አባት በሌለበት ቤት ከሚመላለስ ሰው ማለት ነው
በሀጥያት (ክህደት) ውስጥ ሆነው እግዚአብሔርን እያመለኩ ከሚመስሉ ስዎች እራቅ ምክንያቱም ፍሬ ስለማያፈሩ ያንተን ነገር ያቀጭጫሉ
:
ይቀጥላል 🙏
ለጥያቄ:@msalewoch
https://t.me/lifewithchristjesus
https://t.me/mhbc5 | 477 |
| 13 | #ምስክርነቴ!
እግዚአብሔር እንዴት ልጆቹን ማሳደግ እንዳለበት ያውቃል። የራሱ የሆነ መመሪያ (Manual)፣ ጥበብ፣ አሠራር፣ አመራር፣ ስርዓት፣ መግቦት፣ ምክር፣ ትምህርት፣ ተግሳጽ አለው።
እርሱ ቤት ከመጣኹ፣ በልጁ በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል ልጁ ከሆንኹ ጀምሮ አቀማጥሎ ነው ያሳደገኝ፤ ከሚያስፈልገኝም ነገር አንዳች አላጎደለብኝም።
እርሱን በግርግር መሃል፣ ብዙ ነገሮች በከበቡኝ ጊዜ አላወቅኹትም። የከበቡኝን ነገሮች ከዙሪያዬ ገለል አድርጎ ለብቻዬ ሲያስቀረኝ ግን በግል፣ በግልጥ አጊኝቼዋለሁ፣ አውቄዋለሁ።
እኔ እና እርሱ ለብቻችን ሆነን ያሳየኝ ፍቅሩ፣ የገለጠልኝ ማንነቱ፣ እኔን የነካበት መንካት፦ እርሱ ጋር ተጠግቼ እንድኖር፣ በፍቅሩ ታስሬ እንድቀር አድርጎኛል።
ያ ማንም ከእኔ ጋር በሌለ ሰዓት ያቀመሰኝ አብሮነቱ ከግርግር ገሸሽ እያልኹ በሬን እንድዘጋ፣ ልሰማውም በእግሮቹ ሥር እንድሆን ምክንያት ሆኖኛል።
በዚህ መንገድ ከእርሱ ጋር ስኖር ሳለሁ ሰው ነኝና ቆይ እስት አሁን ደግሞ ወጣ ብዬ ውጪውን ልይ፣ አዲስ ነገር ካለ ልፈልግ፣ እንደዚህ #ችክ፣ #ግግም ብሎ እግዚአብሔር፣ እግዚአብሔር ማለቱን ገታ ላድርግ ብዬ በሬን ዘግቶ ከእርሱ ጋር መቀመጥ፣ ፊቱን ፊቱን ማለት ሳቆም ሁሉ ነገር ጨለማ ሲለብስ፣ አንድ እርምጃ ነው ብዬ የጀመርኹት #Walk ጭልጥ አድርጎ ሲወስደኝ፣ ለብታ ላዬ ላይ ቤቱን ሲሰራ፣ መንፈሳዊ ረሃቤ ሲከስም፣ እግዚአብሔርን መፈለግ ዳገት፣ ሬት ሲሆንብኝ ራሴን አገኘሁ።
እኔው ራሴ እስቲ ልየው፣ አንድ ቀን አይደል? ዛሬ ባልጸልይና ቃሉን ባላነብስ? ትንሽ አረፍ ብልስ? ብዬ የጀመርኹት ጉዞ ረሃቤንና በውስጤ ያለውን መሻት ሙጥጥ አድርጎ ጨርሶ አእምሮዬ ጊዜ የለኝም የሚለውን ውሸት እንዲቀበል፤ ለስንፍናዬም ምክንያት እንድደረድር አደረገኝ።
በዚህ ሁሉ ውስጥ ሳልፍ የውስጥ ሰውነቴ በድካም ሲማቅቅ፣ እግዚአብሔርን አለመፈለጉና አለመጠጋቱ ልቤን ሲከነክነው ይሰማኛል። ከጉትጎታው ትንሽ ልረፍ ብዬ በእግዚአብሔር ፊት በርከክ ለማለት፣ ቃሉንም ገለጥ አድርጌ ለማየት ስሞክር ትልቅ ዓለት እንደተጫነው ሰው ሸክም ይሆንብኛል፤ ለመቀጠልም አቅም አጣ እና ትቼው እነሳለኹ።
ይሄ አዙሪት ምርኮዬን በስንፍና እና በቸልታዬ እንዳስወሰድኹ፣ ለማስመለስም እንዳቃተኝ አምኜ እግዚአብሔር ፊት እስክመጣ፣ እንዳመመኝ፣ ለመፈወስና ለማገገምም በራሴ አቅም እንዳጣሁ ለእግዚአብሔር እስክነግረው ድረስ ቀጠለ።
የልቤን ሕመም፣ የውስጤን ስብራት ለብቸኛው አካሚዬ የነገርኹት ዕለት ግን እርሱ በእውነት በፊቱ ለሚቀርቡ፣ ለሚመለሱ፣ ልባቸውን በትህትና፣ ሰብረው ለሚያቀርቡለት #ቅርብ መሆኑን ተማርኹበት። ሲረዳኝም አየሁት።
አሁን የተወሰደውን ምርኮዬን ለማስመለስ፣ የደከመውን ጉልበቴን ለማበርታት፣ የደረቀ የውስጥ ሰውነቴን ለማለምለም፣ በፊቱም በደስታ ለመቅረብ ራሱ እግዚአብሔር አቅም ሆኖኛልና #ብረትን_በጋለበት ብዬ የፈረሰ መሰውያዬን ለማደስ፣ የተዳፈነ እሳቴን እንደገና ለማንደድ ከእግዚአብሔር ጋር እየሰራሁ፣ እየተጋሁ እገኛለሁ።
በሬን ዘጋ አድርጌ ከእግዚአብሔር ጋር ክትት ለማለት፣ ቃሉን፣ የልቡንም አሳብ ለመስማት ሰከን፣ በእግሮቹ ሥር እርፍ ለማለት ኃይል ሆኖልኛል። ፍቅሩም በመንፈስ ቅዱስ በልቤ እየፈሰሰ ነውና አሁንም አሁንም እርሱን ያስናፍቀኛል፤ ከእርሱ ጋር ያለኝ የግል ጊዜም (Our quality time) ብዙ ነገር እየተጨዋወትንበት ነው። ከአባትዬ ጋር እንደ ልጅነቴ፣ እርሱን እንዳወቅኹበት የልጅነቴ ወራት በፍቅሩ ወድቅ! ለማለት፣ ከእርሱ ውጪ ሌላ ላለማየት ልቤን በፊቱ እያፈሰስኹ ነው።
ድካሜን ሰምታችሁ፣ ከስብራቴ እንድትማሩ፤ እኔን የመታ እንቅፋት እንዳይመታችሁ፤ እኔን የረዳ፣ ዳግም መልሶ ያቆመኝ እግዚአብሔር እንደሚረዳ፣ ለእኛም ከእርሱ ውጪ ተስፋ፣ ሕይወት አለመኖሩን እንድታስተውሉ ስል ይህን ጻፍኹ።
በእግዚአብሔር ፍቅር መውደቅ፤ ከፊቱ፣ ከእግሮቹ ሥር አለመጥፋት ዘወትር የምትመርጡት መልካም ዕድል ይሁንላችሁ!!! ጸጋ ይብዛላችሁ።
✍️ መክሊት አየለ
📆 June 11, 2026
#HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional | 418 |
| 14 | በእግዚአብሔር ፍቅር መውደቅ፤ ከፊቱ፣ ከእግሮቹ ሥር አለመጥፋት ዘወትር የምትመርጡት መልካም ዕድል ይሁንላችሁ!!!
ጸጋ ይብዛላችሁ።
📖 Hear. Obey. Practice.
#HOPMinistry #HearObeyPractice
#DailyDevotional
t.me/hopministry10 | 408 |
| 15 | በእድሜ መጎልመስ እንዲሁም በእግዚአብሔር ቤት ብዙ ጊዜ መቆየት እግዚአብሔርን ለማወቅ ያለንን መቃተት፣ መናፈቅ፣ መበርታት ሊያጠፋብን አይገባም። | 475 |
| 16 | ዛሬም ገና ያልያዝነው፣ ያወቅው ግን ደግሞ ተረድተን ያልጨረስነው እግዚአብሔር እንዳለ እናስተውል።
📖 Hear. Obey. Practice.
#HOPMinistry #HearObeyPractice
#DailyDevotional
t.me/hopministry10 | 486 |
| 17 | በእድሜ መጎልመስ እንዲሁም በእግዚአብሔር ቤት ብዙ ጊዜ መቆየት አንድ ነገርን ሊያጠፋብን አይገባም። እርሱም፦ እግዚአብሔርን ለማወቅ መቃተት፣ መናፈቅ፣ መበርታትን። የሁልጊዜ ስራችን እርሱን ለማወቅ መበርታት ከሆነ በእግዚአብሔር ላይ ሳናድግ ዘወትር እንደ ልጆች፣ እንደ ህጻናት የቃሉን ወተት እንመኛለን። ዋል አደር እያልን ስንሄድም ገና እንዳልያዝነው እየገባን ዱካውን መከታተል እናበዛለን።
ዛሬም ገና ያልያዝነው፣ ያወቅው ግን ደግሞ ተረድተን ያልጨረስነው እግዚአብሔር እንዳለ እናስተውል። በዙሪያችን የሚሆነው ነገር፣ የሕይወት አዙሪት እየወጣ እየገባ፣ እየበላ እየጠጣ፣ እየተኛ እየተነሳ.... መደበኛ ኑሮው ላይ ብቻ ተጠምዶ የሚኖር #አማኝ፣ እግዚአብሔርን አዋቂ ነኝ ባይ ሰው ሊያደርገን የተጋ ነው። እኛ ግን በዚህ አዙሪት መሃል ቆም ብለን በየዕለቱ ልባችንን፣ አሳባችንን፣ ጊዜያችንን፣ ትኩረታችንን ልንሰጠው የሚገባ እግዚአብሔር እንዳለ ማሰብ፣ ማወቅም ይኖርብናል። እግዚአብሔር የየዕለት ነው፤ የሁሌ ነው፤ የዕለት እንጀራችን ነው። በሕይወት ለመሰንበታችን ወሳኙ መብል፣ መናም እርሱ ነው።
ሌላው በዚህ እርሱን የማወቅ ፍለጋ ውስጥ መታደስ አለ። ይህም ለሕይወታችን እንዲሁም ለሕይወት ትርጉማችን (ስንኖር ልናደርገው ለተገባን ዓላማችን) ነው። ከጊዜ ብዛት ዘንግተነው ሕይወት ጣዕም ካጣብን እንኳን፤ ወደ እርሱ ቀርበን የልባችንን ስናወጋው፣ የልቡንም ስንጠይቀው፦ በልብ በነፍሱ ያለውን አሳቡን ሹክ ይለናል፤ የልቡን መሻት እንደገና ያስረዳናል። እኛ ብቻ ልንፈልገው፣ ልናውቀው፣ ልንከተለው እንበርታ እንጂ እርሱ እንደ ወገግታ ተዘጋጅቶ እንደምናገኘው ቃሉ ዋስትናችን ነው።
“እንወቅ፤ እናውቀውም ዘንድ እግዚአብሔርን እንከተል፤ እንደ ወገግታም ተዘጋጅቶ እናገኘዋለን፤ እንደ ዝናብም ምድርንም እንደሚያጠጣ እንደ መጨረሻ ዝናብ ይመጣል።”
— ሆሴዕ 6፥3
1ኛ ጴጥሮስ 2
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹ እንግዲህ ክፋትን ሁሉ ተንኰልንም ሁሉ ግብዝነትንም ቅንዓትንም ሐሜትንም ሁሉ አስወግዳችሁ፥
²-³ ጌታ ቸር መሆኑን ቀምሳችሁ እንደ ሆነ፥ ለመዳን በእርሱ እንድታድጉ አሁን እንደ ተወለዱ ሕፃናት ተንኰል የሌለበትን የቃልን ወተት ተመኙ።
✍️ መክሊት አየለ
📆 October 2, 2025
#HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional | 508 |
| 18 | ቤተልሄም_ተዘራ_Bethelhem_Tezera_የእግዚአብሔር_ጊዜ128k.m4a | 531 |
| 19 | 📖 Hear. Obey. Practice.
#HOPMinistry #HearObeyPractice
#DailyDevotional
t.me/hopministry10 | 520 |
| 20 | #እኔ_እንደምፈልገው_ሳይሆን_አንተ_እንደምትፈልገው_ይሁን የሚለው ጸሎት እጅግ በጣም ቅልል ያለ፤ በምቹ ጊዜ፣ ጥቅማችን ባልጎደለ ሰዓት፣ የእኛ የምንለው ሁሉ ሳይነካ ብቻ የሚጸለይ ጸሎት ነው? ተግባሩስ እንደ ንግግሩ ቀላል ነው?
ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ይሄን ጸሎት የጸለየባት ወቅት ሁሉ ሊያበቃ ተቃርቦ፣ የሞት አፏፍ ላይ ቆሞ ነው። መከራን ሊቀበል እንደሆነ፣ ወደ ሞት እንደተቃረበ ያውቃል። #ቢቻል ይህ ጽዋ ከእርሱ ቢያልፍ ይሻል፤ ነገር ግን ብሎ ሲቀጥል ግን የአባቱን ፈቃድ መፈጸም የእርሱ ዋና ጉዳይ ነው።
የትኛውንም ዋጋ ከፍሎ አባቱ የሚፈልገውን ነገር ማድረግ የእርሱ ደስታው፣ ምግቡም ነው። እርሱን ተመችቶት፣ እርሱ የሚፈልገው ሆኖ፤ ነገር ግን አብ ደስ ባይሰኝ፣ አብ የሚፈልገው ባይሆን የወልድ ልብ አያርፍም።
የምሳሌያችን የእግዚአብሔር ወልድ ደስታና እረፍት ያለው፦ ፍላጎቱን ትቶ እግዚአብሔር አብ የሚፈልገውን በማድረግ ውስጥ ነበር። እያዘነ፣ እየተከዘ፣እየተጨነቀ፣ ነፍሱ እስከ ሞት ድረስ አዝና ቅድሚያ የሚሰጠው ለአባቱ ፈቃድ ነው። " #እኔ_እንደምፈልገው_ሳይሆን_አንተ_እንደምትፈልገው_ይሁን" የማይቀየር ጸሎቱ ነው።
እኛስ? አይደለም የሞት አፋፍ ላይ ቆመን በደህናው ጊዜ፣ አገር ሰላም በሆነበት ወቅት እንኳን ልባችን ለእግዚአብሔር ፈቃድ ምን ያህል ይገዛል? እኛና የእኛ ወደ ኋላ ቀርተን እግዚአብሔርን፣ የእግዚአብሔርን ለማስቀደም ምን ያህል ታዛዦች ነን? #እኔ_ልቅደም፣ #የእኔ_ይቅደም ከማለት ይልቅ እኔ እንደምፈልገው ሳይሆን አንተ እንደምትፈልገው ይሁን ብለን ሁሉን ለፈቃዱ ለመሰዋት ምን ያህል ቅርብ ነን?
ጌታ ይርዳን!! ጸጋ ይብዛልን!!
ማቴዎስ 26 (አዲሱ መ.ት)
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
³⁹ ጥቂት ዕልፍ ብሎ በግንባሩ በመደፋት፣ “አባቴ ሆይ፤ ቢቻል ይህ ጽዋ ከእኔ ይለፍ፤ ነገር ግን እኔ እንደምፈልገው ሳይሆን አንተ እንደምትፈልገው ይሁን” ብሎ ጸለየ።
…
⁴² እንደ ገና ለሁለተኛ ጊዜ ሄዶ፣ “አባት ሆይ፤ ይህ ሳልጠጣው የማያልፍ ጽዋ ከሆነ፣ ፈቃድህ ይፈጸም” ብሎ ጸለየ።
…
⁴⁴ ትቶአቸውም እንደ ገና በመሄድ ለሦስተኛ ጊዜ ቀደም ብሎ የጸለየውን ጸሎት ደገመ።
✍️ መክሊት አየለ
📆 February 19, 2025
#HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional | 559 |
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
