ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit
የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ አስተምህሮና ስርዓትን የጠበቁ ትምህርቶች፣ ስንክሳር፣ መዝሙራትን ከነዜማቸው ለማግኘት ቻናላችንን ይጎብኙ። ለማንኛውም አስተያየት @Zimaredawitmessanger ላይ ቢያስቀምጡልን ይደርሰናል። ስለሚሰጡን ገንቢ ሃሳብ እናመሰግናለን። YouTube Page - https://bit.ly/2O1Z3d8 Facebook Page - https://www.fb.com/l/6lp1kJRRR
Show more📈 Analytical overview of Telegram channel ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit
Channel ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit (@ortodoxmezmur) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 167 786 subscribers, ranking 149 in the Religion & Spirituality category and 140 in the Ethiopia region.
📊 Audience metrics and dynamics
Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 167 786 subscribers.
According to the latest data from 13 July, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 422 over the last 30 days and by -51 over the last 24 hours, overall reach remains high.
- Verification status: Not verified
- Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 12.58%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 5.93% reactions from the total number of subscribers.
- Post reach: On average, each post receives 21 116 views. Within the first day, a publication typically gains 9 954 views.
- Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 143.
📝 Description and content policy
The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
“የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ አስተምህሮና ስርዓትን የጠበቁ ትምህርቶች፣ ስንክሳር፣ መዝሙራትን ከነዜማቸው ለማግኘት ቻናላችንን ይጎብኙ።
ለማንኛውም አስተያየት @Zimaredawitmessanger ላይ ቢያስቀምጡልን ይደርሰናል። ስለሚሰጡን ገንቢ ሃሳብ እናመሰግናለን።
YouTube Page - https://bit.ly/2O1Z3d8
Facebook Page - https://www.fb.com/l/6lp1kJRRR”
Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 14 July, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Religion & Spirituality category.
አዝምሳሌ የሌለሽ ነይ እመቤቴ ዘመዴ ነሽ ነይ እመቤቴ ያን ክፉ ዘመንን ነይ እመቤቴ ያለፍኩብሽ ነይ እመቤቴ በፍቅርሽ እሳት ነይ እመቤቴ ልቤ ነደደ ነይ እመቤቴ እናትነትሽን ነይ እመቤቴ ስለወደደ ነይ እመቤቴ
አዝየሰውስ ውበት ነይ እመቤቴ ምን ይረባኛል ነይ እመቤቴ ሰረገላዬስ ነይ እመቤቴ መች ያድነኛል ነይ እመቤቴ ከተሠወረ ነይ እመቤቴ ክፉ መከራ ነይ እመቤቴ እድናለሁኝ ነይ እመቤቴ አንችን ስጠራ ነይ እመቤቴ
አዝለስንፍናዬስ ነይ እመቤቴ መቼ ልክ አለው ነይ እመቤቴ ስለ በደሌ ነይ እመቤቴ እተክዛለው ነይ እመቤቴ ለአነጋገሬ ነይ እመቤቴ ማጣፈጫ ነሽ ነይ እመቤቴ ተሰምቻለው ነይ እመቤቴ ድንግል ሆይ ስልሽ ነይ እመቤቴ
አዝለመንገዴ ስንቅ ነይ እመቤቴ ለራቤ መርሻ ነይ እመቤቴ ለታመመ ሰው ነይ እመቤቴ ነሽ መፈወሻ ነይ እመቤቴ የተማጸነ ነይ እመቤቴ በስምሽ አምኖ ነይ እመቤቴ ማን አፍሮ ያውቃል ነይ እመቤቴ ፊትሽ ለምኖ ነይ እመቤቴ ዘማሪት ፋንቱ ወልዴ 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️
ሐምሌ ፮ /6/በዚችም ዕለት ቅድስት ንስተሮኒን አረፈች። እርሷም ከኢየሩሳሌም ሰዎች ውስጥ ነበረች። እርሷም አስቀድማ ኃጢአተኛ ነበረች ከዚያም በኋላ ንስሓ ገብታ ወደ እግዚአብሔር በተቃጠለ ልብ ተመለሰች የሥጋን ፍላጐቶች ሁሉ ናቀች እመምኔት እስከ ሆነች ድረስ በበጎ ሥራ ሁሉ ትሩፋትንና ተጋድሎን አበዛች። እኀቶችም ከገድል ብዛትና ምግብን ከመተው የተነሣ ሥጋዋ እንዳለቀ አይተው ሥጋሽን እንድትረጂ ጥቂት እህል በወጥ ብዪ አሏት። አብዝተውም ግድ ባሏት ጊዜ ልጆቼ ሆይወደ ቀድሞ ልማዴ እንዳልመለስ ጥቂት ወጥ ስለመብላት አትድከሙ ስለዚህ ወጥ አልበላም አለቻቸው። ከዚህ በኋላ በሰላም አረፈች። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በጸሎቷ ይማረን ለዘላለሙ አሜን። ወስብሐት ለእግዚአብሔር ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤
አዝእረዳት እርሱ ነው ከሰማያት እግዚአብሔር ጠባቂ የኔን ሕይወት ብርሃኑን በፊቴ የሚያበራ አምላኬ ድንቅ ነው የእርሱ ስራ
አዝበመንገዴ ሁሉ የሚመራኝ ስነሳ ስወድቅም የሚያስበኝ ማንም አልመጣልኝ ከወገኔ ከሁሉም ይበልጣል እርሱ ለኔ
አዝየእዳዬን ደብዳቤ ውድቅ አድርጎ ሕይወቴን መራልኝ ወደ በጎ ኧረ እንደእግዚአብሔር ማን ይሆናል እሱን ለሚፈሩት ይታመናል
አዝእንድ ቀን አስቤ ተጨንቄ ለመኖር አልቻልኩም ተጠንቅቄ ሁሉን ነገር ለእርሱ ትቼዋለሁ በምሕረቱ ጥላ እኖራለሁ ዘማሪ እንዳልካቸው 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️
አዝበኢያሪኮ መንገድ ስለምን ቁጭብዬ ብርሃን እጅግ ናፍቆኝ ከሰው ተገልዬ የብርሃን ጌታ ወደ እኔ መጣና ዓይኔን አበራልኝ በእጁ ዳሰሰና
አዝለብዙ ዘመናት አልጋ ላይ ተኝቼ የሚረዳኝ አጣሁ ጠሉኝ ዘመዶቼ የእኔ ጌታ አምላኬ ወደ እኔ መጣና አልጋህን ተሸከም አለኝ ፈወሰና
አዝአሥራ ሁለት ዓመት ደም የፈሰሰኝ ምራቅ እየተፋ ሁሉም ቢያንቋሽሹኝ የጌታዬ ልብሱን ጫፉን ብዳስሰው ኃይልም ከእርሱ ወጣ ደሜን ቀጥአረገው
አዝሰካራም ዘማዊ ወንበዴ ነበርኩኝ የአመጸኞች መሪ ደምን ያፈሰስኩኝ ዛሬ ግን ታሪኬን ጌታ ቀይሮታል ለኃያሉ ጌታ ምስጋና ይገባል ዘማሪ ዳግማዊ ደርቤ 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️
ሐምሌ ፬ /4/አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ሐምሌ አራት በዚች ቀን የቅዱሳን አቡቂርና ዮሐንስ የሥጋቸው ፍልሰት ሆነ። ይህም እንዲህ ነው እሊህ ቅዱሳን የካቲት ስድስት ቀን ሰማዕታት ሆነው በሞቱ ጊዜ ምእመናን ሥጋቸውን ተሸክመው ወስደው በእስክንድርያ ከተማ በስተሰሜን ባለች በቅዱስ ወንጌላዊ ማርቆስ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ በሥውር አኖሩዋቸው እስከ ሊቀ ጳጳሳት ቄርሎስ ዘመንም በዚያ ኖሩ። የእግዚአብሔር መልአክም ለቅዱስ ቄርሎስ ተገለጸለት ወደ ወንጌላዊ ቅዱስ ማርቆስ ቤተ ክርስቲያንም ሔዶ የቅዱሳን የአቡቂርንና የዮሐንስን ሥጋቸውን አውጥቶ እንዲሸከም አዘዘው። እርሱም ተነሥቶ ሔደ ከእርሱም ጋራ ብዙ ሕዝቦች ነበሩ በደረሱም ጊዜ ጸለዩ ምድሩንም ሲቆፍሩ ሥጋቸው በውስጡ ያለበት ቦታ ተገለጠላቸው በባሕር ዳርቻ ወደ አለች ወደ ሌላዪቱም የቅዱስ ማርቆስ ቤተ ክርስቲያን በታላቅ ክብርየቅዱሳኑን ሥጋቸውን ተሸክመው አድርሰው በዚያ አኖሩ። በዚያም ቤተ ክርስቲያን ሠሩላቸው በዚችም ቀን ታላቅ በዓል አደረጉ ከሥጋዎቻቸውም ድንቆች ተአምራት ተገለጡ አረማውያንም ተሰበሰቡ ይህንንም ድንቅ ተአምር በአዩ ጊዜ ጣዖቶቻቸውን ትተው ክርስቲያኖች ሆኑ ። በዚያቺም የጣዖቶች ቤት አሸዋ በላይዋ ተከመረባት ታላቅ ኮረብታም ሆነ። የቅዱሳንም ሥጋቸው ታምራትንና ለበሽተኞች ታላቅ ፈውስን ያደርጋል። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በጸሎታቸው ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ወስብሐት ለእግዚአብሔር ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤
አዝአንተ መዝሙረኛ ነብዩ ዳዊት እንድታሸበሽብ በታቦቱ ፊት ሜልኮም ብትንቅህ ሰገነት ላይ ሆና እግዚያብሔር አይትዋታል ሳትናገር ገና እኔስ ለመቤቴ እዘምራለሁ ፍቅርዋ በደሜ ውስጥ እንዳለ አውቃለሁ ስምዋን ለምን ጠራህ ተብየ ስተየቅ አድምጡልኝ መልሴን ድንግልን እኔ አለቅ በአማን /2/እረዳቴ ናት እመቤታችን
አዝየኤልዛቤት ጭፍሮች መጥተው ይዘውኝ ጭው ያለ በረሃ እስርቤት ጣሉኝ ስለ እስራቴ ጌታየ አይቶልኛል ሁሉን ተመልክቶ ተበቅሎልኛል ከዝምታየ የተነሳ እንደ ዲዳ ሆንኩኝ ለበጎ ነገርን እንኩዋ ዝምም ያልኩኝ በእኩለ ለሊት ሊያስፈራሩኝ መጥተው ሳህሊለነ ብዬ ብርታትን አገኘሁ በአማን /2/እረዳቴ ናት እመቤታችን
አዝእረበናት ዛሬም መስክረው ሀሰት ወደ ፍርድ ወሰዱኝ ከማላውቅበት ከሳሾችም ቀርበው ሲከራከሩኝ እውነተኛው ዳኛ አሰናብበተኝ የምስጋናም ዘውድም ጌታ ደፍቶልኛል ለድንግል ውዳሴን ላቀርብ ፈቅዶልኛል ባለምዋልናትና ለቅድስት ስላሴ እስከ መጨረሻው ታመስግናት ነፍሴ በአማን /2/እረዳቴ ናት እመቤታችን ዝማሬ በቀሲስ እንግዳወርቅ በቀለ 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️
አዝተጨንቄአለሁ ልንገርሽ ምስጢረኛዬ እናቴ ነሽ ሰው ያልሰማውን ብርቱ ምስጢር ድንግል ሆይ ላንቺ ላማክር የቁስለኛው መድኃኒቱ የአዳም ዘር ሁሉ ነሽ ህይወቱ መፍትሄ አለ በእጅሽ ተንበርክኬ ልማጸንሽ
አዝሳልናገረው ይገባሻል የውስጤ ሁሉ ይታይሻል ድረሽ እናቴ ተራጅኝ ያላንቺ ለኔ ማን አለኝ ደስታዬ ደሰታ የሚሆነው በሀዘኔ የምጽናናው አንቺ ከእኔ ጋር ስለሆንሽ ተጽናንቻለው በስምሽ
አዝወንድሞቼ እንኳን ቢሸጡኝ ሰው ሁሉ ጠላት ቢሆነኝ በእመ አምላክ ኃይል ከብሬአለሁ በጠላቴ ላይ ሰልጥኛለሁ የረሰኙ ሁሉ ያስቡኛል የተጣሉኝም ያከብሩኛል አንቺ አንግሰሽኝ አልወድቅም እቆማለሁኝ ዘለዓለም
አዝመንገዴ እረዝሞ ደክሜብሽ መከራው በዝቶ ታምሜብሽ ወድቄ ሳዝን ድረሽልኝ ለባሪያሽ ሃይሉን እንድትሰጭኝ ፍቅርሽ በውስጤ ተንሰራፋ በእናትነትሽ ልቤ ሰፋ የሚለያየን ማንም የለም ማርያም ልበልሽ ለዘለዓለም ዘማሪ ቀሲስ ምንዳዬ ብርሃኑ 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️
ሐምሌ ፫ /3/በዚች ቀን ለአባቶች ሊቃነ ጳጳሳት ሃያ አራተኛ የሆነ የእስክንድርያ ሊቀ ጳጳሳት ቅዱስ አባት ቄርሎስ አረፈ። ይህም ቅዱስ የእናቱ ወንድም በሆነው በአባ ቴዎፍሎስ ዘንድ አደገ ጥቂት ከፍ ባለ ጊዜም ወደ አስቄጥስ ወደ መቃርስ ገዳም ላከው በዚያም አምላካውያት የሆኑ መጻሕፍትን ተማረ እግዚአብሔርም መጽሐፍን አንድ ጊዜ አንብቦ እስከሚአጸናው ድረስ ዕውቀትንና ማስተዋልን ሰጠው። ከዚህም በኃላ ደግሞ ያስተምረው ዘንድ ለአባ ሰራብዮን ሰጠው ከእርሱም ዘንድ ያለውን ትምህርቱን በፈጸመ ጊዜ ወደ ሊቀ ጳጳሳት ቴዎፍሎስ መለሰው ። እርሱም እጅግ ደስ ተሰኘበት እግዚአብሔርንም አመሰገነው። ከዚህም በኃላ ሁልጊዜ መጻሕፍትን እንዲያነብና ሕዝቡን እንዲያስተምር በሊቀ ጵጵስና ሥራ ውስጥ ሾመው። ከትምህርቱም ጣዕም የተነሣ ዝም ይል ዘንድ ማንም አይወድም ነበር። አባ ቴዎፍሎስም ከአረፈ በኃላ በእስክንድርያ ከተማ ላይ ይህን አባ ቄርሎስን ሊቀ ጵጵስና ሾሙት በዘመኑም በትምህርቱ ቤተ ክርስቲያን በራች። ይኸው አባት ቄርሎስ የቁስጥንጥንያ ሊቀ ጳጳሳት የነበረው ንስጥሮስ በካደ ጊዜ ተከራከረው ከስሕተቱም ባልተመለሰ ጊዜ አውግዘው ከመንበረ ሢመቱ አሳደዱት። ከዚህ በኋላ ብዙዎች ድርሳናትን ተግሣጻትንና መልእክቶችን ደረሰ። በወንጌላዊ ማርቆስ መንበር ላይ ሠላሳ ሁለት ዓመት ኖረ መልካም የሆነ ሥራውንም ፈጽሞ በሰላም አረፈ ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በዚህ አባት ጸሎተወ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ወስብሐት ለእግዚአብሔር ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤
አዝመክሊቴን ቀብሬ ባሳዝንህ መብራቴንም ይዤ ባልጠብቅህ በታላቅ ይቅርታ እንዳትረሳኝ በፍቅር ጎብኝተህ ከሞት አውጣኝ ከቤትህ እርቄ መች ጠገብኩኝ በረሐብ በእርዛት ተቸገርኩኝ አምናለሁ አምላኬ እንድትምረኝ ለይቅርታ መጣሁ ተቀበለኝ በለኝ
አዝአንዳች እንደሌለኝ አውቀዋለሁ ባንተ ቸርነት ግን እመካለሁ የከበደው ሸክሜ ይቀለኛል ይቅርታ ለባርያህ ይደርሰኛል በመቅደስህ ቆሜ ለመዘመር ስራህን ለትውልድ ለመመስከር እኔ ማነኝ ብዬ አስባለሁ አምላክ ቸርነትህን አደንቃለሁ
አዝበሰው እጅ መመካት አቁሚያለሁ እረዳቴ አንተ ነህ አውቄያለሁ አንተ ከጠበከኝ በህይወቴ ቅጥሬ አይደፈርም መድኃኒቴ የኔን ስራ ተወው ተግባሬንም የመስቀሉን ነገር መርሳቴንም አዚሜን አንስተህ አንተን ልይህ ኢየሱስ ክርስቶስ አምላኬ ነህ ዘማሪ ቀሲስ ምንዳዬ ብርሃኑ 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️
