ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit
የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ አስተምህሮና ስርዓትን የጠበቁ ትምህርቶች፣ ስንክሳር፣ መዝሙራትን ከነዜማቸው ለማግኘት ቻናላችንን ይጎብኙ። ለማንኛውም አስተያየት @Zimaredawitmessanger ላይ ቢያስቀምጡልን ይደርሰናል። ስለሚሰጡን ገንቢ ሃሳብ እናመሰግናለን። YouTube Page - https://bit.ly/2O1Z3d8 Facebook Page - https://www.fb.com/l/6lp1kJRRR
Show more📈 Analytical overview of Telegram channel ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit
Channel ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit (@ortodoxmezmur) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 167 493 subscribers, ranking 150 in the Religion & Spirituality category and 145 in the Ethiopia region.
📊 Audience metrics and dynamics
Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 167 493 subscribers.
According to the latest data from 22 June, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by -117 over the last 30 days and by 22 over the last 24 hours, overall reach remains high.
- Verification status: Not verified
- Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 14.30%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 6.37% reactions from the total number of subscribers.
- Post reach: On average, each post receives 23 947 views. Within the first day, a publication typically gains 10 665 views.
- Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 172.
📝 Description and content policy
The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
“የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ አስተምህሮና ስርዓትን የጠበቁ ትምህርቶች፣ ስንክሳር፣ መዝሙራትን ከነዜማቸው ለማግኘት ቻናላችንን ይጎብኙ።
ለማንኛውም አስተያየት @Zimaredawitmessanger ላይ ቢያስቀምጡልን ይደርሰናል። ስለሚሰጡን ገንቢ ሃሳብ እናመሰግናለን።
YouTube Page - https://bit.ly/2O1Z3d8
Facebook Page - https://www.fb.com/l/6lp1kJRRR”
Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 23 June, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Religion & Spirituality category.
✅ ምዝገባውን ለማካሄድ ሙሉ ስም እና ስልክ ቍጥር በዚህ ልኮ መመዝገብ ነው ✅ @Geez180 @Geez180 @Geez180 👈⛳️ ለበለጠ መረጃ በአድራሻዎቻችን አግኙን። መማር ለሚፈልጉ ወገኖች በሙሉ ሼር Share በማድረግ እንጋብዛቸው። ሠናይ፡ጊዜ። @MerfaqeGeez 🏵 ም ር ፋ ቀ ፡ ግ እ ዝ 🏵 0975760575
ሰኔ ፲፮ /16/አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ሰኔ ዐሥራ ስድስት በዚች ዕለት የእግዚአብሔር መልአክ ለዮሴፍ በሕልም ተገለጠለት ሕፃኑንና እናቱንም ይዞ ወደ እስራኤል አገር እንዲመለስ አዘዘው። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም ስለ እናቱ ስለ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም መከራና ስደት ይቅርይበለን ለዘላለሙ አሜን። ወስብሐት ለእግዚአብሔር ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤
30% ቅናሽ አድርገንላችኋል⁕ Photoshop ⁕ Illustrator ⁕ Indesign ⁕ XD ⁕ Figma ⁕ Canva ⁕ Photopea → 25+ Projects አስተምረን ፣ ሸልመን ይህን ሁሉ ባንድ ላይ _______________ Upwork + Fiverr ደግሞ ሙሉ ኮርስ በነጻ _______________ 🎯 በ300 ብር ቅድመ ክፍያ ተመዝግባቹ የትም ሳትሄዱ ቤታቹ ሆናቹ ተማሩ። በ2 ወራት ብቁ ግራፊክስ ዲዛይነር ሁኑ ። @Greenbirdtechnology ላይ ተመዝገቡ ። _______________ ምን ያስፈልጋል ? ● ላፕቶፕ ● ኢንተርኔት ወይም ዋይፋይ ● ለኮርስና ፕሮጀክት በቂ ጊዜ ___________________ የኮርስ ቀናት ሰኞ ፡ ማክሰኞ ፡ ረቡዕ ምሽት 2፡00 - 4፡00 _______________ ለአሸናፊዎች ሽልማት Video Editing Course 1ኛ አሸናፊ 100% በነጻ 2ኛ አሸናፊ 50% በነጻ 3ኛ አሸናፊ 25% በነጻ _______________ ጠቅላላ ክፍያ በተናጠል ዋጋ ግራፊክስ ዲዛይን 5000 ብር ቪዲዮ ኤዲቲንግ 5000 ብር ቪዲዮ ኤዲቲንግ + ግራፊክስ ዲዛይን በአንድ ላይ 7000 ብር [ 30% ቅናሽ ] _______________ @greenbirdtechs @greenbirdtechs የለውጥዎ ክንፍ 🔑 🐥
አዝከምናየው ከምንሰማው ይከልለን ቸርነትህ መቼም እኛ በድለናል እግዚአብሔር ግን ይቅር ባይ ነህ ሾተል ስቦ የነበረው አበባን ይስጥ ለወንድሙ ከመቅበዝበዝ ከጸብ ይውጣ አብሮት ይኑር በሰላሙ
አዝአዛውንቱ ሕጻናቱ አለቅንብህ በሰቀቀን መቼም ለአንተ አይሳንህ አቅርብልን የሳቁን ቀን ዳግም ያብብ በልባችን የረገፈው የፍቅር ዘር በሚያልፍ ሐሳብ ተደግፈን ተጠላልፈን እንዳንቀር
አዝማዕዳችን ሙሉ ይሁን ገበያውን ጥጋብ አርገው እንዳለፈው መልካም ጊዜ አንዱም አንዱን ይደግፈው አትረፍርፈን በበረከት ጥቂት ዘርተን ብዙ እንጨድ የአበባውን ዘመን መልስ እርስ በእርስም እንዋደድ
አዝየኀዘናችን ካባ ይውለቅ ደስታ አልብሰን እንደድሮው እናት በኀዘን አትጎዳ አባት አይኑር አቀርቅሮ ትላንትናን አስረስተህ በአዲስ ዘመን አዲስ አርገን ቂም በቀልን አርቅልን አንደገናም አስተቃቅፈን ሊቀ መዘምራን ዲ/ን ቴድሮስ ዮሴፍ 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️
አዝበምድረበዳ ላይ የጮኅኩለት ንጉሥ የሃያላን ሀያል ተገልጧል ኢየሱስ ለኃጢአት ስርየት ይሰዋል ይሄ በግ ለዓለም ሁሉ መዳን በቀራንዮ ሰርግ
አዝለንስሐ የሚሆን ፍሬ ዛሬ አድርጉ በሰርጉ ሊጠራን መጥቷልና በጉ ከሚመጣው ቁጣ በእርሱ እድታመልጡ የእፉኝት ልጆች ከባቢሎን ውጡ
አዝየአብርሃም ልጆች ነን በማለት ላትድኑ የማዳኑን ሰዓት ቀኑን አታባክኑ ለአብርሃም ልጆች ከድንጋይ ያስነሳል መንሹም በእጁ ነው አውድማው ይጠራል
አዝጠማማው ልብ ይቅና ጥርጊያው ይደላደል ፍሬ የሌለው ዛፍ በቶን ሳይቃጠል ምሳር በዛፎች ስር ዛሬም ተቀምጧል ንስሐ ግቡ ነው የመጨረሻው ቃል ሊቀ መዘምራን ቴዎድሮስ ዮሴፍ 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️
ሰኔ ፲፬ /14/በዚች ቀን ቅዱሳን አባ አክራና፣ ዮሐንስ፣ አብጥልማና ፊልጶስ በሰማዕትነት ሞቱ። ይህም ቅዱስ አክራ ከግብጽ ደቡብ ይምንሑር ከሚባል አገር ሰዎች ወገን ነው ስሙ ፊልጶስ የሚባል ወንድም ነበረው እነርሱም ባለጸጎች ነበሩ ስማቸው ዮሐንስና፣ አብጥልማ ከሚባል ሁለት ቀሳውስት ጋራ ሰማዕታት ይሆኑ ዘንድ ተስማሙ አራቱም ቀርጥስ ወደሚባል አገር ሔዱ ክብር ይግባውና በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ በመኰንኑ ፊት ታመኑ። መኰንኑም በቀስቶች እንዲነድፏቸው አዘዘ ግን ቀስቶች አልነኳቸውም። ሁለተኛም እሳትን አንድደው በሚነድ የእሳት ምድጃ ውስጥ ይጨምሩአቸው ዘንድ አዘዘ እንዲሁም አደረጉባቸው ጌታም መልአኩን ልኮ አዳናቸው። ከዚህም በኋላ በፈረስ ጅራት ላይ አሥረው ከቀርጥስ ከተማ እስከ ይምንሑር አገርድረስ ይጐትቷቸው ዘንድ አዘዘና ይህንንም አድረጉባቸው ግን ምንም ምን ጉዳት አልደረሰባቸውም። ከዚህም በኋላ ራሶቻቸውን በሰይፍ እንዲቆርጧችው አዘዘ ከይምንሑር ከተማም አውጥተው ራሶቻቸውን ቆረጡአቸው። ፃ ከሚባል አገር ሰዎች መጥተው የቅዱስ አባ አክራን ሥጋውን ወሰዱ ውብ የሆነች ቤተ ክርስቲያንም ሠርተው ሥጋውን በውስጧ አኖሩ ከእርሱም ታላላቅ ድንቆችና ተአምራት በብዛት ተገለጡ። እንዲሁም የእነዚያን የሦስቱን ቅዳሳን የፊልጶስን፣ ለአብጥልማንና የዮሐንስን ሥጋቸውን ከይምንሑር ከተማ ሰዎች መጥተው ወሰዱ በመልካም ልብሶችም ገነዙአቸው ጥሩ ቤተ ክርስቲያንም ሠርተው ሥጋቸውን በውስጧ አኖሩ ከእነርሳቸውም ቁጥር የሌለው ድንቅ ተአምርተገለጠ። ወስብሐት ለእግዚአብሔር ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤
ሰኔ ፲፫ /13/በዚችም ዕለት ለከበረ መልአክ አዲስ የምሥራች ነጋሪ ለሆነ የመላእክት አለቃ ገብርኤል በዓልን ያደርጉለት ዘንድ መምህራን በግብጽ አገር ለክርስቲያን ወገኖች ሥርዓት ሠሩላቸው ። ይህ የከበረ መልአክ የእስራአል ልጆች ከሰይጣን እጅ ስለመዳናቸውና ከምርኮም ስለ መመለሳቸው ነቢዩ ዳንኤል ወደ እግዚአብሔር በሚጸልይና በሚማልድ ጊዜ አስቀድሞ የተገለጠለትና ስለ ድኅነታቸውና ስለ ቤተ መቅደስም መታነፅ የነገረው ነውና ። ዳግመኛም ክብር ይግባውና ስለ ክርስቶስ መምጣትና መገደል ስለ ቤተ መቅደስም መፍረስ ከዚያም በኋላ ስለ ሐሳዊ መሲሕ መምጣት ነገረው ። ለመድኀን መምጣትም በሱባዔ የወሰናቸው ዘመናት በተፈጸሙ ጊዜ ይህ የከበረ መልአክ የመላእክት አለቃ ገብርኤል ከእግዚአብሔር ዘንድ ተልኮ ወደ ቅድስት ድንግል ወደ እመቤታችን ማርያም መጣ ዓለምን ስለ ማዳን የእግዚአብሔር ልጅ ከእርሷ ሰው ስለመሆኑ ነገራት ። ስለዚህም የበዓላቶቹን መታሰቢያ እንድናደርግ የቤተ ክርስቲያን መምህራን አባቶቻችን አዘዙን ። እኛም ከጠላታችን ሰይጣን እጅ ያድነን ዘንድ ለመንግሥቱም የተዘጋጀን ያደርገን ዘንድ ክብር ይግባውና በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ፊት ስለ እኛ እንዲማልድ እንለምነው ። ልዕልና ችሎታም ገንዘቡ ለሆነ ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን የዚህም የከበረ መልአክረድኤቱ ከእኛ ጋራ ይኑር ለዘላለሙ አሜን። ወስብሐት ለእግዚአብሔር ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤
አዝበክንፎቹ እኔን በእጁ ሰይፍ ይዟል ሚካኤል ሊረዳኝ ቆሟል እንዳስፈሪ እንደ ንጉሥ ሰራዊት በቀኜ ነው በቀንና በሌሊት ሚካኤል አባቴ ለዚህ እኮ ነው መመካቴ ሚካኤል አባቴ ጋሻ ክብሬ ነው ማለቴ ሚካኤል አባቴ ጎኔ ቆመህ እንዳቆምከኝ ሚካኤል አባቴ እኔ ለዓለም ምስክር ነኝ
አዝልናገር ላውራ ላዚም ልዘምር ከፍ አርጌ ልመስክር መች ይረሳል ልጅነቴ ያሳደገኝ እቅፍ አርጎ በክንፎቹ የከለለኝ ሚካኤል አባቴ እስከዛሬ ያላልኩትን ሚካኤል አባቴ በልቤ ውስጥ ያኖርኩትን ሚካኤል አባቴ ዛሬ ላውራው በአደባባይ ሚካኤል አባቴ እረድቶኛል ከአባት በላይ
አዝከተኛሁበት ከእንቅልፌ አንቅቶ ነጻ አወጣኝ እስሬን ፈቶ በጨለማ በወኅኒው ቤት በእስር አብሮኝ ነበር ጠባቂዬ ሚካኤል ሚካኤል አባቴ በክፋ ቀን ያለ ጎኔ ሚካኤል አባቴ ያልተለየኝ በድካሜ ሚካኤል አባቴ ሰው የሚወድ የማይንቅ ሚካኤል አባቴ በጌታ ፊት የሚያስታርቅ
አዝብርቱና ኃያል ጽኑ ነው ስሙ ሚካኤል ሞገስ የሆነው ምን ይሆናል ሚካኤልን የያዘ ሰው ምግቡ መና ደመና ነው ሚጋርደው ሚካኤል አባቴ የአባቶቼ መንገድ መሪ ሚካኤል አባቴ በእኔም ሕይወት ተዓምር ሰሪ ሚካኤል አባቴ በመንገዴ ቀድሞ ፊቴ ሚካኤል አባቴ ይስበኛል ወደ ርስቴ ዘማሪ ዲያቆን አቤል መክብብ 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️
አዝበክንፎቹ እኔን በእጁ ሰይፍ ይዟል ሚካኤል ሊረዳኝ ቆሟል እንዳስፈሪ እንደ ንጉሥ ሰራዊት በቀኜ ነው በቀንና በሌሊት ሚካኤል አባቴ ለዚህ እኮ ነው መመካቴ ሚካኤል አባቴ ጋሻ ክብሬ ነው ማለቴ ሚካኤል አባቴ ጎኔ ቆመህ እንዳቆምከኝ ሚካኤል አባቴ እኔ ለዓለም ምስክር ነኝ
አዝልናገር ላውራ ላዚም ልዘምር ከፍ አርጌ ልመስክር መች ይረሳል ልጅነቴ ያሳደገኝ እቅፍ አርጎ በክንፎቹ የከለለኝ ሚካኤል አባቴ እስከዛሬ ያላልኩትን ሚካኤል አባቴ በልቤ ውስጥ ያኖርኩትን ሚካኤል አባቴ ዛሬ ላውራው በአደባባይ ሚካኤል አባቴ እረድቶኛል ከአባት በላይ
አዝከተኛሁበት ከእንቅልፌ አንቅቶ ነጻ አወጣኝ እስሬን ፈቶ በጨለማ በወኅኒው ቤት በእስር አብሮኝ ነበር ጠባቂዬ ሚካኤል ሚካኤል አባቴ በክፋ ቀን ያለ ጎኔ ሚካኤል አባቴ ያልተለየኝ በድካሜ ሚካኤል አባቴ ሰው የሚወድ የማይንቅ ሚካኤል አባቴ በጌታ ፊት የሚያስታርቅ
አዝብርቱና ኃያል ጽኑ ነው ስሙ ሚካኤል ሞገስ የሆነው ምን ይሆናል ሚካኤልን የያዘ ሰው ምግቡ መና ደመና ነው ሚጋርደው ሚካኤል አባቴ የአባቶቼ መንገድ መሪ ሚካኤል አባቴ በእኔም ሕይወት ተዓምር ሰሪ ሚካኤል አባቴ በመንገዴ ቀድሞ ፊቴ ሚካኤል አባቴ ይስበኛል ወደ ርስቴ ዘማሪ ዲያቆን አቤል መክብብ 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️
ሰኔ ፲፪ /12/በዚች ዕለት የተባረከና የተመሰገነ በሰማያት ያለ ምሥጢርን ያየ የኢትዮጵያ ንጉሥ ላሊበላ የዕረፍቱ መታሰቢያ ሆነ። ይህንንም ቅዱስ ወላጆቹ በወለዱት ጊዜ እግዚአብሔርን በመፍራትና በበጎ ሥራ ሁሉ አሳደጉት ። አድጎ አካለ መጠን በአደረሰ ጊዜ ታላቅ ወንድሙ ንጉሥ ቀናበት መልእክተኞችንም ልኮ ወደርሱ አስመጣው ምክንያትም ሽቶ ከሦስት ሰዓት እስከ ሰባት ሰዓት እንዲገርፉት አዘዘ ። ከዚህም በኋላ በፊቱ እንዲአቆሙት አዘዘ በአቆሙትም ጊዜ የደረሰበት ጉዳት እንደሌለ አይተው ንጉሡና መኳንንቶቹ ሁሉ አደነቁ የእግዚአብሔር መልአክ ከግርፋት ሠውሮታልና ። ከዚህ በኋላም ወንድሙ ንጉሥ በአንተ ላይ ስለአደረግሁት ክፉ ሥራ ወንድሜ ሆይ ይቅር በለኝ ብሎ ለመነውና እርስ በርሳቸው ታረቁ ። ከዚህ በኋላም እግዚአብሔር መንግሥትን አወረሰው ። ክብር ይግባውና ጌታችንም የፍቅሩን ጽናት በአየ ጊዜ የእግዚአብሔር መልአክ ተገለጠለት ወደ እርሱም ወደ ሰማያት አወጣው ዐሥሩን አብያተ ክርስቲያንም እንዴት እንደሚሠራቸው አሳየው እነርሱም ሥራቸው የየራሳቸው የሆነ ልዩ ነው ተመልሶም መንፈስ ቅዱስ እንደአራቀቀው በአስደናቂ ጥበብ አነፃቸው ። እሊህንም አብያተ ክርስቲያናት አንፆ በፈጸመ ጊዜ መንግሥቱን ለወንድሙ ልጅ አወረሰ ። ከዚህም በኋላ ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ እርሱ መቶ ብዙ ቃልኪዳን ገባለት ቅዱስ ላሊበላም ጌታችንን እያመሰገነ በምድርላይ ወድቆ ሰገደ ። ጌታችንም ሰላምታ ሰጥቶት በክብርና በምስጋና ወደ ሰማያት ዐረገ ። ከዚህም በኋላ ጥቂት ሕማም ታሞ በሰላም አረፈ። ወስብሐት ለእግዚአብሔር ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤
አዝቸሩ ሆይ ለዓይነ ስውር መሪ ቸሩ ሆይ ምርኩዝ መመኪያ ነህ ቸሩ ሆይ አንተን የሚመስል ቸሩ ሆይ ምንም ነገር የለም ቸሩ ሆይ ምሕረትና ፍቅርህ ቸሩ ሆይ ወሰን ወደር የለው ቸሩ ሆይ ሳንወድህ ወደኽን ቸሩ ሆይ ፈልገህ ጠራህን
አዝቸሩ ሆይ ሰምተህ እዳልሰማህ ቸሩ ሆይ አይተህ እንዳላየህ ቸሩ ሆይ ሁሉን ታልፈዋለህ ቸሩ ሆይ ፍቅራዊ አባት ነህ ቸሩ ሆይ አማኑኤል ጌታ ቸሩ ሆይ ቸሩ ፈጣሪያችን ቸሩ ሆይ ውለታህ ብዙ ነው ቸሩ ሆይ ለእኛ የዋልክልን
አዝቸሩ ሆይ በከብቶች ማደሪያ ቸሩ ሆይ በዚያች ትንሽ ግርግም ቸሩ ሆይ ተወልዶ አዳነን ቸሩ ሆይ ጌታ መድኃኔዓለም ቸሩ ሆይ እልል በሉ ሰዎች ቸሩ ሆይ አንድ ላይ ዘመሩ ቸሩ ሆይ ስብሃት ለእግዚአብሔር ቸሩ ሆይ በአርያም በሉ ዘማሪ ቀሲስ ምንዳዬ ብርሃኑ 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️
ሰኔ ፲፩ /11/በዚችው ቀን በጦርነት ድል አድራጊው ከቤተ መንግሥት ወገን የሆነ የመላእክት አርአያ ያለው የከበረ ሰማዕት ገላውዴዎስ የተጋድሎው ፍጻሜ ነው ። ይህ ቅዱስ ምድራዊ መንግሥትንና የዚህን ዓለም ክብር የናቀ ነበረ መልካም ገድልንም ተጋደለ ። የማይጠፋ ሰማያዊ መንግሥትንና የማያልቅ ክብርንም ወረሰ ። የዚህም ቅዱስ የአባቱ ስም አብጥልዎስ ነው እርሱም ለሮም ንጉሥ ለኑማርያኖስ ወንድሙ ነው መልኩም እንደ እስራኤል ያዕቆብ ልጅ እንደ ዮሴፍ እጅግ ውብ ነበር ። ዲዮቅልጢአኖስም ሊሸነግለው ቢሞክር አልደሳካለትም በመጨረሻም ከወዳጁ ፊቅጦር ጋር ወደ ግብፅ ንጉስ እንዲሸነግላቸው ላካቸው። ወደ እንዴናው ገዥ ወደ አርያኖስም በደረሰ ጊዜ አርያኖስ አይቶ ደነገጠ ተነሥቶም እጁን ሳመው እንዲህም ብሎ ለመነው ። ጌታዬ ገላውዴዎስ ሆይ ይህን ሥራ አትሥራ የንጉሥንም ትዕዛዝ አትተላለፍ ። ቅዱስ ገላውዴዎስም እንዲህ ሲል መለሰለት ንጉሥ ያዘዘህን ልትፈፅም እንጂ በነገርህ ልታስተኝ አልተላክሁም አለው ። መኰንኑም እስከሚቆጣ ድረስ እንዲህ እርስበርሳቸው ይነጋገሩ ነበር በመኰንኑም እጅ ጦር ነበረ ቅዱስ ገላውዴዎስንም ወጋው ነፍሱንም ክብርይግባውና በጌታችን እጅ ሰጠ በመንግሥተ ሰማያትም የሰማዕትነት አክሊልን ተቀበለ ። ወስብሐት ለእግዚአብሔር ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤
ሰኔ ፲ /10/በዚች ዕለት ለክርስቲያን ወገኖች በዓለሙ ሁሉ ታላቅ ደስታ ሆነ መላእክትም በሰማያት ደስ ተሰኙባት። በዚች ቀን ዕውነተኛ ምእመን ከሆነ ከንጉሥ ቈስጠንጢኖስ ዘንድ የጣዖት ቤቶች እንዲዘጉ አብያተ ክርስቲያናትም እንዲከፈቱ ትእዛዝ ወጥቷልና። ደስታን የተመላች ያች መልእክት ወደ እስክንድርያ ከተማ እንደ በዛሬዋ ቀን በደረሰች ጊዜ ፈጽሞ ደስ ተሰኙ ወደ ግብጽ አውራጃዎችም ሁሉ ላኳት ምእመናን ሁሉ ስለ ቤተ ክርስቲያን ክብር ከፍ ከፍ ማለት ደስ አላቸው። የጣዖታት ቤቶችንም ዘጓቸው አብያተ ክርስቲያናትንም ከፈቱአቸው እንደ ዛሬም በዚች ዕለት በዓል አደረጉ ይኸውም ቈስጠንጢኖስ በነገሠ በዐሥራ አንድ ዓመቱ ነበር እለእስክንድሮስም ሊቀ ጵጵስና በተሾመባት በመጀመሪያ ዓመት ነበር። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን በእኛ ላይም ይቅርታውና ቸርነቱ ይደረግልን ለዘላለሙ አሜን። ወስብሐት ለእግዚአብሔር ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤
Available now! Telegram Research 2025 — the year's key insights 
