ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit
የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ አስተምህሮና ስርዓትን የጠበቁ ትምህርቶች፣ ስንክሳር፣ መዝሙራትን ከነዜማቸው ለማግኘት ቻናላችንን ይጎብኙ። ለማንኛውም አስተያየት @Zimaredawitmessanger ላይ ቢያስቀምጡልን ይደርሰናል። ስለሚሰጡን ገንቢ ሃሳብ እናመሰግናለን። YouTube Page - https://bit.ly/2O1Z3d8 Facebook Page - https://www.fb.com/l/6lp1kJRRR
Show more📈 Analytical overview of Telegram channel ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit
Channel ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit (@ortodoxmezmur) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 169 234 subscribers, ranking 141 in the Religion & Spirituality category and 140 in the Ethiopia region.
📊 Audience metrics and dynamics
Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 169 234 subscribers.
According to the latest data from 06 September, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 745 over the last 30 days and by 25 over the last 24 hours, overall reach remains high.
- Verification status: Not verified
- Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 12.20%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 6.14% reactions from the total number of subscribers.
- Post reach: On average, each post receives 20 645 views. Within the first day, a publication typically gains 10 385 views.
- Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 121.
📝 Description and content policy
The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
“የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ አስተምህሮና ስርዓትን የጠበቁ ትምህርቶች፣ ስንክሳር፣ መዝሙራትን ከነዜማቸው ለማግኘት ቻናላችንን ይጎብኙ።
ለማንኛውም አስተያየት @Zimaredawitmessanger ላይ ቢያስቀምጡልን ይደርሰናል። ስለሚሰጡን ገንቢ ሃሳብ እናመሰግናለን።
YouTube Page - https://bit.ly/2O1Z3d8
Facebook Page - https://www.fb.com/l/6lp1kJRRR”
Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 07 September, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Religion & Spirituality category.
አዝምድርን በአበባ አጊጠህ አሳምረህ ክረምትና በጋን ታፈራርቃለህ የማታንቀላፋ ሳተፍ እንኳ ለአፍታ ተመስገን አዲስ ቀን በሰጠኸን ጌታ 2 እንኳን ለዚህ ቀን አደረሳችሁ እንኳን እግዚአብሔር አብሮ አደረሰን 2
አዝየመከራ ዘመን ታለፈና ዛሬ ለአዲስ አመት በቃን ይኸውና ዛሬ ዘመን ለፍስሃ ሰተኸናልና የዘመናት ጌታ ይድረስህ ምስጋና 2 እንኳን ለዚህ ቀን አደረሳችሁ እንኳን እግዚአብሔር አብሮ አደረሰን 2
አዝበአመቱ ያድርሰን ብለን ተመራርቀን የዓመታት ባለቤት ይኸው አደረሰን እድሜ ጤና ሰጥተህ ለዚህ ቀን ደርሰናል የጊዜ ባለቤት በብዙ ረድቶናል 2 እንኳን ለዚህ ቀን አደረሳችሁ እንኳን እግዚአብሔር አብሮ አደረሰን 2
አዝከሩቅ ሀገር ያለው ላገሩ አብቃውና የአባቶች ምርቃት ያግኝ እንደገና ውዳሴ ምስጋና ለአንተ እናቀረባለን 2 እንኳን ለዚህ ቀን አደረሳችሁ እንኳን እግዚአብሔር አብሮ አደረሰን 2
አዝየመከራ ዘመን ታለፈና ዛሬ ለአዲስ አመት በቃን ይኸውና ዛሬ ዘመን ለፍስሃ ሰተኸናልና የዘመናት ጌታ ይድረስህ ምስጋና 2 እንኳን ለዚህ ቀን አደረሳችሁ እንኳን እግዚአብሔር አብሮ አደረሰን 2 ዘማሪ ዳግማዊ ደርቤ 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️
ነሐሴ ፴ /30/በዚህች ዕለት ከዐሥራ ሁለቱ ደቂቀ ነቢያት አንዱ የሆነው ታላቁ ነቢይ ሚልክያስ አረፈ። እግዚአብሔር አምላክ በነቢዩ አንደበት አድሮ እንዲህ ይለናል። ሰው እግዚአብሔርን ይሰርቃልን? እናንተ ግን እኔን ሰርቃችኋል። እናንተም። የሰረቅንህ በምንድር ነው? ብላችኋል። በአሥራትና በበኵራት ነው። ትንቢተ ሚልክያስ 3:8 እንዴት አድርጌ ነው ከ5ሺህ ብር ደሞዝ በዛ ላይ የኑሮ ውድነቱ ተጨምሮበት አስራት የማወጣው? ብላችሁ ብትጠይቁም እግዚአብሔር በነቢዩ አድሮ እንዲህ ይለናል። በቤቴ ውስጥ መብል እንዲሆን አሥራቱን ሁሉ ወደ ጎተራ አግቡ፤ የሰማይንም መስኮት ባልከፍትላችሁ፥ በረከትንም አትረፍርፌ ባላፈስላችሁ በዚህ ፈትኑኝ፥ ይላል የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር። ትንቢተ ሚልክያስ 3:10 ቅዱስ ሚልክያስም በበጎ ተጋድሎው እግዚአብሔርን ከአገለገለ በኋላ በዛሬዋ ዕለት ከዚህ ዓለም በመፍለስ በሰላም አረፈ። ሚልክያስ ማለት መልዐክ አንድም የተላከ ማለት ነው። ወስብሐት ለእግዚአብሔር ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️
አዝበለስም ባታፈራ ዘይትም ባይኖር የህሊና ሰላም አለኝ ካንተ ጋር ስኖር በአባቶቼ በረከት የባረከኝ የእስራኤል ታዳጊያቸው ክበርልኝ ዘላለም ተመስገን ከፍ በልልኝ
አዝየፈተናዬ መውጫ መልሴ ነህ አንተ ጨለማውን አሻግረኝ እልፍኙን ከፍተህ ስታፅናናኝ ኖሬአለሁ ለብዙ ዘመን ተገፍቶ መች ይወድቃል በአንተ የሚታመን አይሞትም ይኖራል በአንተ የሚታመን
አዝይቅርታና ምህረትህ እነሱ ይምሩኝ ወጥመድና እንቅፋቱ እንዳያደክሙኝ በጽድቅህ ሀሴት ላድርግ በአንተ ልበርታ መተከዝ ማልቀስ ይብቃኝ አፅናናኝ ጌታ ተነግሮ አያልቅም የአምላኬ ውለታ ዘማሪት ጽጌረዳ ጥላሁን 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️
ነሐሴ ፳፱ /29/በዚህች ዕለት በትሕትናው፣ በትዕግስቱ ይበልጡንም ደግሞ በመታዘዙ የሚታወቀው አባት ቅዱስ ዮሐንስ ሐጺር የፍልሰቱ ዕለት ናት። በአንድ ወቅት አባ ባይሞይ ቅዱስ ዮሐንስን ጠራውና ተፈልጦ የወደቀ ደረቅ እንጨት ሠጠው ከዚያም "ትከለውና እንዲያፈራ አድርገው። ከዚያ አምጥተህ አብላኝ" አለው። ይህ ነገር ከተፈጥሮ ሥርዓት ውጪ መሆኑን እያወቀ ቅዱስ ዮሐንስ "እሺ" ብሎ ወስዶ ተከለው። ከ10ኪ.ሜ በላይ እየተጓዘ ወሃ እየቀዳ ለ2 ዓመታት ሳይታክት አጠጣው። በሦስተኛው ዓመት ግን ለመለመ ወስዶም ለመምህሩ "አባቴ እንካ ብላ " ብሎ ሰጠው። መምህሩም ወዲያው ያን ፍሬ ታቅፎ ወስዶ ለገዳሙ መነኮሳት:- "ንሱ ብሉ: በረከትንም አግኙ:: ይህ የዛፍ ሳይሆን የመታዘዝ ፍሬ ነው አላቸው::" ቁመቱ እጅግ ያጠረ: ጽድቁ ግን ከሰማይ የደረሰ ቅዱስ ዮሐንስን ሰላም ሰላም እንለዋለን። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን: እኛንም በዚህ የጻድቅ ጸሎት ይማረን። በረከቱም ትድረሰን: ለዘላለሙ አሜን። ወስብሐት ለእግዚአብሔር ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር 💚@ortodoxmezmur💚 💛@ortodoxmezmur💛 ❤️@ortodoxmezmur❤️
አዝብሄድ ብርቅ ተለይቼ ንፁ ፍቅርን እረስቼ ጌታዬ ነህና አባቴ ራርተህ መልሰኝ ከቤቴ /2/
አዝምንም ብሆን በደለኛ ብበድልህም ዳግመኛ ጌታ ሞቴን አትፈልግም አንተ ፍቅር ነህ ዘላለም /2/
አዝከመንጋው ወጥቼ ብጣል በድካም በኃጢያት ብዝል የቀድሞ ትጋቴን ስጠኝ ፅናትና ብርታት ሁነኝ /2/
አዝቅዱስ ስጋህን ቆርሰህ ክቡር ደምህን አፍሰህ ሞተህ ህይወት የሰጠኸኝ አንተ ፈጥረህ የምትገዛኝ /2/ ሊቀ መዘምራን ቀሲስ ምንዳዬ ብርሃኑ 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️
አዝክብርህ ገናና ነው ባንተ ከብሬያለሁ ዘላለማዊ ነው ባንተ እኖራለሁ በሰልፉ መካከል አለህ ከእኔ ጋራ የሰራዊት ጌታ እፁብ የአንተ ስራ
አዝከላይ ከአርያም ከዙፋንህ ግርማ ቅዱስ አለ ኪሩብ ምስጋናው ተሰማ ውዳሴ ከበበው መንበሩን እልልታ ባሪያህ ላመስግንህ ፍቀድልኝ ጌታ
አዝየአማልክት አምላክ የሚመስልህ የለም አይኔ ያየው ሁሉ ያላንተ አልሆነም አይኔ ያየው ገንዘብህ ነውና አልፋና ኦሜጋ ይድረስህ ምስጋና
አዝየምድር ኃያላን አይቆሙም ከፊትህ ይህን ሰራህ ብሎ የለም የሚወቅስህ ሰማይ እና ምድርን ፈጥረህ የምትገዛ እናመልክሃለን የህይወታችን ቤዛ 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️
ነሐሴ ፳፯ /27/በዚችም ቀን በሊቀ ካህናት ኤሊ ዘመን ነቢይ ሳሙኤል ለመጠራቱ መታሰቢያ ሆነ። ይህንንም ነቢይ ተኝቶ ሳለ እግዚአብሔር ጠራው በኤሊም ፈንታ ነቢይና ካህን አድርጎ ለእስራኤል ልጆች ሾመው በረከቱም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን። በዚችም ቀን የእስክንድራዊ ፊቅጦርና የእናቱ ሣራ መታሰቢያቸው ነው በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። በዚችም ቀን ከሰባቱ ሊቃነ መላእክት አራተኛ የሆነ የመላእክት አለቃ የሱርያል የበዓሉ መታሰቢያ ነው ። አማላጅነቱም ከኛ ጋር ይኑር ለዘላለሙ አሜን። በዚችም ቀን ዳግመኛ አባቶቻችን ዐሥራ ሁለቱን የያዕቆብን ልጆች ያስቧቸዋል ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን በረከታቸውም ትድረሰን ለዘላለሙ አሜን። ወስብሐት ለእግዚአብሔር ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤
አዝእንቺ በመሆንሽ የሕይወቴ ፋና አልፈራም ጨለማ ብርሃን አለኝና አይጠፋም ዘላለም ፍቅርሽ ከአንደበቴ አለ በደሜ ውስጥ ፍቅርሽ በሕይወቴ አልቀርም ደጅሽ ለዘላለም /2/ ከአንቺ የሚለየኝ ማንም የለም /2/
አዝእጅግ የተገፋ ደካማ ሰው አለ መቅደስሽ የቆመ አማልጂኝ እያለ ይቁም ይሄ ልጅሽ ሃዘን የሰበረው ከአንቺ በቀር ወገን መጠጊያ የሌለው ያነሳው ኪዳንሽ ከውድቀቱ/2/ ያርግ በእጆሽ ያ ፀሎቱ/2/
አዝፅልመት የለበሰ ፈታኝ ያደከመኝ የምቋቋምበት ጉልበት አስፈለገኝ በርትቼ እንድጸና ሳትጎዳ ነፍሴ ሁኚኝ እናቴ ሆይ ግርማዬ ሞገሴ ልፅና ደግፊኝ እመቤቴ/2/ ይውለቅ ከእጄ ላይ ሰንሰለቴ/2/
አዝአበው የለበሱሽ የክብራቸው ካባ መአዛሽ የሚስብ የሮማን አበባ ለውጪው በምልጃሽ የሕይወቴን ቃና ባዶ ጋኔን ምልጃሽ ወይን ያስሞላውና አፅጂልኝ በእጅሽ ማድጋዬን/2/ በወይን አስሞይው እንስራዬን/2/ ዘማሪ ቀሲስ ምንዳዬ ብርሃኑ 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️
ነሐሴ ፳፮ /26/በዚችም ቀን ለአብርሃም ሚስት ለተመሰገነች ሣራ መታሰቢያዋን እናደርግ ዘንድ የቤተ ክርስቲያን መምህራን አባቶች አዘዙ። ይቺንም ክብርተ ማሕፀን የሆነች ጡቶቿም የተባረኩ ክብርት ሣራን የጌራራ ንጉሥ አቤሜሌክ ባል እንዳላት ሳያውቅ በወሰዳት ጊዜ እንዳይቀርባት እግዚአብሔር ገሠጸው በደዌም ቀሠፈው ባሏ አብርሃምም በጸለየለት ጊዜ ከደዌው ተፈወሰ ከዚህም በኋላ ከብዙ ገንዘብ ጋራ ወደ ባሏ መለሳት። ከዚህም በኋላ እግዚአብሔር በሦስትነቱ ተገልጦ ወደ ቤቷ እንግድነት በመጣ ጊዜ ለአብርሃምም የይስሐቅን መወለድ በነገረው ጊዜ ሣራም በድንኳኑ ውስጥ ሳቀች እንዲህ ስትል እስከ ዛሬ ገና ነኝን ጌታዬም አርጅቷል። እግዚአብሔርም አብርሃምን እንዲህ አለው ሣራን ለብቻዋ ምን አሳቃት እስከ ዛሬ ገና ነኝን ጌታዬም አርጅቷል እኔም አሁን አርጅቻለሁ ብላ በውኑ ለእግዚአብሔር የሚሳነው ነገር አለን። ከዚህም በኋላ ሣራ ፀንሳ እግዚአብሔር ባለው ወራት በርጅናዋ ለአብርሃም ወንድ ልጅን ወለደች። ከዚህም በኋላ በበጎ እርጅና በአረፈች ጊዜ ከኬጢያዊ ኤሞርልጆች በገዛው ቦታ ቀበራት። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በከበረች እናታችን ሣራ በጸሎቷ ይማረን በረከቷም ከእኛ ጋር ይኑር ለዘላለሙ አሜን። ወስብሐት ለእግዚአብሔር ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤
አዝእጄን በአፌ እያስጫነ አስገረመኝ ደጉ ልብህ ፊትህ አይጠቁር በኃጢአቴ እንዳላየህ ታልፈዋለህ ሳታሳጣኝ በሰው መሐል የእኔ ከዳኝ የልቤ ጥግ አላነስኩም ካየኽልኝ ከከፍታህ ከዚያ ማዕረግ
አዝበእርሱ ምሕረት ከድቅድቁ ከወጣሁኝ ከጨለማ ለይሁዳ ክፉ ወሬ ልቤ አይሰጋ ለዓለም ዜማ በነበልባል ሲያቃጥለኝ የስምዖን አንደበቱ የእሳት ልሳን ሆነኽልኝ በአንተ አለፈ ያ ክረምቱ
አዝከበለስ ሥር የሠራሁት ዓለም ተፍቶ ያቃለለው ረሳሁት ትቼዋለሁ እንዳንተ ያለኝ ከቶ ማነው ሰው ሲሸሸኝ የቀረብከኝ አንተ እኮ ነህ መድኃኒቴ ዐይንህ ዐይቶኝ መች አለፍከኝ አነሳኸኝ ቸር አባቴ
አዝመክሮ መክሮ ሲታክተው ውጣ ብሎ እየጣለ ስንቱ አለፈ በመከራ ሰው ወገኑን ስላልቻለ የኔ ጌታ ፍቅሩ ችሎኝ ሰፊው ክንዱ አሻገረኝ ለውለታው ከእንባ በላይ የሚያረካው ምን ቃል አለኝ ዘማሪ ዲ/ን አቤል መክብብ 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️
I want to attend Day 1+2+3 of
Graphics Design Course »
~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~
ብላቹ ለምትልኩልን link እንሰጣችኋለን
___________________________
@greenbirdtechs
@greenbirdtechs
የለውጥዎ ክንፍ 🔑 🐥ነሐሴ ፳፭ /25/በዚችም ቀን ቅዱሱ አባት አባ ቢጻርዮን አረፈ። የዚህም ቅዱስ ወላጆቹ እግዚአብሔርን የሚፈሩ ምእመናን ነበሩ። በአደገም ጊዜ የምንኵስና ልብስን ለብሶ እግዚአብሔርን ሊአገለግል ወደደ ዓለምንም ንቆ ወደ ኣባ እንጦንስ ሔደ ለእርሱም ደቀ መዝሙር ሆኖ ብዙ ዘመናት አገለገለው። ከዚህም በኃላ ወደ አባ መቃርስ ሒዶ ቅዱሳን አረጋውያን መነኰሳትንም አገለገላቸው። በአስቄጥስም ገዳም ይዘዋወር ነበር በቤት ውስጥም አያድርም ነበር ። አባቶችም ጭንቅ የነበረ ተጋድሎውን ስለርሱ ይናገሩ ነበር። እርሱ አርባ መዓልትና አርባ ሌሊት ከቶ ሳይተኛ ቁሞ ኖሮአልና። በምንኩስናውም ወራት ብዙ ጊዜ በየአርባ ቀን ጾመ እነሆ እንዲህ እየተጋደለ ድንቆችንም እያደረገ ኀምሳ ሰባት ዓመታት ኖረ። ቅዱሳን አባ ዱላስና አባ ዮሐንስም ከተአምራቱ ተናገሩ እነርሱ ከርሱ ጋር ወደ ኤርትራ ባሕር ዳርቻ ሔዱ። እጅግም በተጠሙ ጊዜ እንደተጠሙ አውቆ ወደ እግዚአብሔር ጸለየ መራራውንም ውኃ ጣፋጭአድርጎላቸው ጠጥተዋል። የዚህም ቅዱስ ተአምራቶቹ ከነገርናችሁ የበዙ ናቸው እግዚአብሔርንም አገልገሎ በሰላም አረፈ ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በዚህ ጻድቅ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ወስብሐት ለእግዚአብሔር ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤
I want to attend Day 1+2+3 of Graphics Design Course »
~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~
ብላቹ ለምትልኩልን link እንሰጣችኋለን
___________________________
@greenbirdtechs
@greenbirdtechs
የለውጥዎ ክንፍ 🔑 🐥አዝባሕር ሳያሰጥመን ደርሶልን አለፍን በደረቅ ከፍሎልን ኢትዮጵያዊው ሙሴ ተክለሃይማኖት የሚሳነው የለም በሃይማኖት
አዝጸሎቱ ምህላው ቅዳሴው ገብቷል ከቤታችን መዓዛው ጸጋ በረከትህ በዝቶልናል በአማላጅነትህ ተምረናል
አዝድካም በሌለበት በምስጋና አምላኩን ያከብራል በትህትና ስለ እኛም ዝም አይልም ይማጸናል የአባታችን አምላክ ይሰማናል
አዝዘመናችን ሲረክስ መንገዳችን ፈጥኖ ደረሰልን አባታችን ተክለሃይማኖት እርዳን ልጆችህን አታርቀው ከእኛ ኪዳንህን ዘማሪት ጸዳለ ጎበዜ 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️
ነሐሴ ፳፬ /24/በዚች ቀን የክርስቶስ ምስክሩና ሐዋርያው የሆነ የመርዓስ ኤጲስቆጶስ ተጋዳይ ቅዱስ አባት ቶማስ አረፈ። ይህም አባት የመርዓስ አገር ኤጲስቆጶስ ነበር። በከሀዲ ዲዮቅልጥያኖስም ዘመን ይህን አባት መኳንንት እየደበደቡት ወሰዱት። ከዚህም በኃላ መኮንኑ ቅዱስ ቶማስን ለአማልክት ስገድ አለው ቅዱሱም ለጣዖት እንደማይሰግድ ነገረው። በዚህም በብዙ አሰቃዩት። ከዚህም በኋላ በጨለማ ቦታ ጣሉት በዚያም ሃያ ሁለት ዓመት ኖረ። በዚያም አካላቱን ይቆርጡት ነበር። መንጋዎቹም ያረፈ መስሏቸው በየዓመቱ መታሰቢያውን ሲያደርጉ ኖሩ። ነገር ግን አንዲት ሴት አይታው ስለነበር በድብቅ ትመግበው ነበር። ጻድቅ ቁስጠንጢኖስም እስከ ነገሠና የቀናች የክርስቶስን ሃይማኖት ክብር እስከ ገለጠ ድረስ እንዲህ ሲሠቃይ ኖረ። ይቺም ሴትስለ ቅዱሱ ለካህናቱ ነገረቻቸው በውስጡ ወደሚኖርበትም ቦታ መራቻቸው። እነርሱም አንሥተው ተሸከሙት እየዘመሩና እያመሰገኑ ወደ ቤተ ክርስቲያን አደረሱት በቤተ መቅደሱም ፊት ለፊት በወንበሩ ላይ አስቀመጡት ምእመናንም ሁሉ ወደርሱ እየመጡ ከእርሱ ይባረኩና የተቆረጡ ሕዋሳቱን ይሳለሙ ነበር። ይህም ቅዱስ ከ318ቱ ሊቃውንት አንዱ ነው። ንጉሱም ስለ ቅዱሱ በሰማ ጊዜ ሰገደለት። ከዚህም በኃላ ቅዱስ ቶማስ ወደ መንበረ ሢመቱ ሔደ ካህናቱንና መንጋዎቹን ሁሉ ሰብስቦ አነበበላቸው እርሱንም እንዲአስተውሉት እንዲጠብቁትም በመጠበቅም እንዲጸኑ አዘዛቸው። ጥቂት ዘመናትም ከኖረ በኃላ በሰላም በፍቅር አረፈ የሹመቱም ዘመን አርባ ዓመት ነው በዚህም እግዚአብሔርን አገለገለው። ወስብሐት ለእግዚአብሔር ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤
