uz
Feedback
ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit

Kanalga Telegram’da o‘tish

የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ አስተምህሮና ስርዓትን የጠበቁ ትምህርቶች፣ ስንክሳር፣ መዝሙራትን ከነዜማቸው ለማግኘት ቻናላችንን ይጎብኙ። ለማንኛውም አስተያየት @Zimaredawitmessanger ላይ ቢያስቀምጡልን ይደርሰናል። ስለሚሰጡን ገንቢ ሃሳብ እናመሰግናለን። YouTube Page - https://bit.ly/2O1Z3d8 Facebook Page - https://www.fb.com/l/6lp1kJRRR

Ko'proq ko'rsatish

📈 Telegram kanali ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit analitikasi

ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit (@ortodoxmezmur) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 167 805 obunachidan iborat bo'lib, Din & Maʼnaviyat toifasida 149-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 140-o'rinni egallagan.

📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika

невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 167 805 obunachiga ega bo‘ldi.

13 Iyul, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni 422 ga, so‘nggi 24 soatda esa -51 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.

  • Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
  • Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 12.58% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 5.93% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
  • Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 21 116 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 9 954 ta ko‘rish yig‘iladi.
  • Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 143 ta reaksiya keladi.

📝 Tavsif va kontent siyosati

Muallif resursni shaxsiy fikrni ifoda etish maydoni sifatida ta’riflaydi:
የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ አስተምህሮና ስርዓትን የጠበቁ ትምህርቶች፣ ስንክሳር፣ መዝሙራትን ከነዜማቸው ለማግኘት ቻናላችንን ይጎብኙ። ለማንኛውም አስተያየት @Zimaredawitmessanger ላይ ቢያስቀምጡልን ይደርሰናል። ስለሚሰጡን ገንቢ ሃሳብ እናመሰግናለን። YouTube Page - https://bit.ly/2O1Z3d8 Facebook Page - https://www.fb.com/l/6lp1kJRRR

Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 14 Iyul, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Din & Maʼnaviyat toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.

167 805
Obunachilar
-5124 soatlar
+587 kunlar
+42230 kunlar
Postlar arxiv
ሥላሴ መታመኛዬ ሥላሴ መታመኛዬ አምላኬ መጠለያዬ/2/ ጉልበቴ ነህ ማሸነፍያዬ ሥላሴ መታመኛዬ  
አዝ
ጠፈሩም እርሱ መሠረቱም እርሱ ፍጥረታት በሙሉ ስሙን አውድሱ ሱራፌልን ልክህ ከንፋሮቼን ዳሰኝ ለምፄን ተመልክተህ አምላክ አትጣለኝ ለምፄን ተመልክተህ ጌታዬ አትጣለኝ
አዝ
እንዴት ያለ አንደበት ስምህን ይጠራል ግርማህን አይቼ ልቤ ተሸብሯል ኦዝያን አለፈ ክፋት እጅግ በዝቶ አምላኬን አየሁት በዙፋኑ ፀንቶ/2/
አዝ
አልአዛር ያንተ ነው መንገድ የወደቀ ከእጅ ያላመለጠ ነዌ ባለፀጋ ንገሥታትም ያንተ በሥልጣን ያሉት ለስምህ ይንበርከክ ይህ ሁሉ ፍጥረት/2/
አዝ
በድቅድቅ ጨለማ ተስፋ በሌለበት ብርሃን ሆኖ አየሁት የጌታዬን ምሕረት ኃይል ማሸነፍን ጽናትንም ስጠኝ ጠላት እንዳይጥለኝ ፀጋህን አልብሰኝ/2/ ዘማሪ ቀሲስ ምንዳዬ ብርሃኑ 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️

+3
ሥላሴ መታመኛዬ ሥላሴ መታመኛዬ አምላኬ መጠለያዬ/2/ ጉልበቴ ነህ ማሸነፍያዬ ሥላሴ መታመኛዬ  
አዝ
ጠፈሩም እርሱ መሠረቱም እርሱ ፍጥረታት በሙሉ ስሙን አውድሱ ሱራፌልን ልክህ ከንፋሮቼን ዳሰኝ ለምፄን ተመልክተህ አምላክ አትጣለኝ ለምፄን ተመልክተህ ጌታዬ አትጣለኝ
አዝ
እንዴት ያለ አንደበት ስምህን ይጠራል ግርማህን አይቼ ልቤ ተሸብሯል ኦዝያን አለፈ ክፋት እጅግ በዝቶ አምላኬን አየሁት በዙፋኑ ፀንቶ/2/
አዝ
አልአዛር ያንተ ነው መንገድ የወደቀ ከእጅ ያላመለጠ ነዌ ባለፀጋ ንገሥታትም ያንተ በሥልጣን ያሉት ለስምህ ይንበርከክ ይህ ሁሉ ፍጥረት/2/
አዝ
በድቅድቅ ጨለማ ተስፋ በሌለበት ብርሃን ሆኖ አየሁት የጌታዬን ምሕረት ኃይል ማሸነፍን ጽናትንም ስጠኝ ጠላት እንዳይጥለኝ ፀጋህን አልብሰኝ/2/ ዘማሪ ቀሲስ ምንዳዬ ብርሃኑ 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️

ሐምሌ ፯ /7/ በዚችም ቀን የአባ መቃቢስና የአባ ጊዮርጊስ የአግራጥስም መታሰቢያቸው ነው በረከታቸውም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን። በዚችም ቀን የሮሜ ከተማ ሊቀ ጳጳሳት ቅዱስ አግናጥዮስ በሰማ
ሐምሌ ፯ /7/ በዚችም ቀን የአባ መቃቢስና የአባ ጊዮርጊስ የአግራጥስም መታሰቢያቸው ነው በረከታቸውም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን። በዚችም ቀን የሮሜ ከተማ ሊቀ ጳጳሳት ቅዱስ አግናጥዮስ በሰማዕትነት ሞተ እርሱም ከቅዱስ ጴጥሮስ በኋላ በከሀዲው ንጉሥ በጠራብያኖስ ዘመን ሆነ። ይህም ንጉሥ ስለ አባት አግናጥዮስ የጣዖት አምልኮን እንደሚያቃልል ሕዝቡንም ሁሉ እንደሚያስተምር ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ወደ ማመን እንደሚያስገባቸው በሰማ ጊዜ ወደ እርሱ አስቀርቦ ለአማልክት መሥዋዕት አቅርብ አለው ቅዱሱም እኔ ለረከሱ ጣዖታት አልሠዋም ብሎ መለሰለት። ንጉሡም ብዙ ቃል ኪዳኖችን በመግባት አባበለው በአልተቀበለውም ጊዜ ለአንበሳ ሰጠው ያን ጊዜም ቅዱስ አግናጥዮስ በቀናች ሃይማኖት እንዲጸኑ ሕዝቡን አዘዛቸው። ከዚህም በኋላ አንዱ አንበሳ ቀርቦ አንገቱን ያዘው ያን ጊዜም ክብር ይግባውና በጌታችን እጅ ነፍሱን ሰጠ ። ከዚህ በኋላ ያ አንበሳ ወደ ሥጋው አልቀረበም ምእመናንም መጥተው ሥጋውን ወሰዱ በመልካም ቦታም አኖሩት። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በዚህ አባት ጸሎት ይማረን ለዘላለሙ አሜን። ወስብሐት ለእግዚአብሔር ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur

እንኳን ለአጋእዝተ ዓለም ሥላሴ እና ለቅዱሳን አበው አብርሃም አባ_ሲኖዳ እና አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ ሥሉስ ቅዱስ በአንድነቱ ምንታዌ (ሁለትነት): በሦስትነቱ ርባዔ (አራትነት) የሌለበት የዘለዓለም አምላክ: የፍጥረታት ሁሉ ፈጣሪ እግዚአብሔር ነው:: አብ :ወልድ : መንፈስ ቅዱስ በስም: በአካል: በግብር ሦስትነት: በባሕርይ: በሕልውናና በፈቃድ አንድነት የጸኑ ናቸው:: በዚህ ጊዜ ተገኙ: በዚህ ጊዜ ያልፋሉ አይባሉም:: መጀመሪያም መጨረሻም እነርሱ ናቸውና:: ርሕሩሐን ናቸውና በእናት ሥርዓት "ቅድስት ሥላሴ" እንላቸዋለን:: የሚጠላቸው (የማያምንባቸውን) አይጠሉም:: የሚወዳቸውን ግን እጽፍ ድርብ ይወዱታል:: በቤቱም መጥተው ያድራሉ:: ከፍጥረታት ወገን ከእመቤታችን ቀጥሎ የአብርሃምን ያህል በሥላሴ ዘንድ የተወደደ ፍጡር የለም:: አባታችን ቅዱስ አብርሃም የደግነት ሁሉ አባት ነውና በኬብሮን በመምሬ ዛፍ ሥር ሥላሴን ተቀብሎ አስተናግዷል:: ሥላሴ አኀዜ ዓለም (ዓለምን በእጁ የያዘ) ነው:: ነገር ግን በፍቅር ለሚሻው በፍቅር ይመጣል:: አባታችን አብርሃም በ99 ዓመቱ: እናታችን ሣራ በ89 ዓመቷ ሥላሴን በድንኩዋናቸው አስተናገዱ:: አብርሃም እግራቸውን አጠበ:: (ወይ መታደል!) በጀርባውም አዘላቸው:: (ድንቅ አባት!) ምሳቸውንም አቀረበላቸው:: እንደሚበሉ ሆኑለት:: በዚያው ዕለትም የይስሐቅን መወለድ አበሠሩት:: ቅድስት ሣራ ሳቀች:: እንደ ዘንድሮ ወገኖቻችን የማሾፍ አይደለም:: ደስታና ጉጉት የፈጠረው እንጂ:: ሥላሴ "ምንት አስሐቃ ለሣራ በባሕቲታ" ብለው ነበርና በዚህም ምክንያት ነው "ይስሐቅ" የተባለው:: ሥላሴን ያስተናገደች ድንኩዋን (ሐይመት) የድንግል እመቤታችን ማርያም ምሳሌ ናት:: በድንግል ላይ አብ ለአጽንኦ: መንፈስ ቅዱስ ለአንጽሖ: ወልድ በተለየ አካሉ ለሥጋዌ በእርሷ ላይ አርፈዋል / አድረዋልና:: ሐምሌ 7 ሥሉስ ቅዱስ ለአብርሃም የተገለጠለት በቤቱም የተስተናገዱበት ዕለት ነው። ©ዝክረ ቅዱሳን ለወዳጅዎ ሼር ያድርጉ! 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️

🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉🎉 በያንጎ የጥሪ ቡፌ ቀረበላችሁ! 📢 ከአዲሱ Order Pool ጋር ምርጫው ሙሉ በሙሉ በእርስዎ እጅ ነው! ጉዞውን ከመቀበልዎ በፊት መነሻውን፣ መድረሻውን እና ትርፉን አስቀድመው ማየት ይችላሉ። የጥሪ ቡፌውን ይቃኙ፣ የፈለጉትን መርጠው ይውሰዱ! 📈 📲 አሁኑኑ የያንጎ ፕሮ መተግበሪያን ያውርዱ! 🔽🔽🔽ሊንኩን ይጫኑ🔽🔽🔽 https://ya.cc/t/3nVOkmT99fvrCa ለበለጠ መረጃ የቴሌግራም ቻናላችን ይቀላቀሉ 💬 : https://t.me/YangoETH ❗️❗️❗️

Video xabar00:24

በጎ መዓዛ በጎ መዓዛ ሽቶዬ ነሽ በሰው ሁሉ ፊት ዘመርኩልሽ በአንቺ ጣፈጠ አልጫነቴ እጠራሻለሁ ነይ እመቤቴ
አዝ
ምሳሌ የሌለሽ ነይ እመቤቴ ዘመዴ ነሽ ነይ እመቤቴ ያን ክፉ ዘመንን ነይ እመቤቴ ያለፍኩብሽ ነይ እመቤቴ በፍቅርሽ እሳት ነይ እመቤቴ ልቤ ነደደ ነይ እመቤቴ እናትነትሽን ነይ እመቤቴ ስለወደደ ነይ እመቤቴ
አዝ
የሰውስ ውበት  ነይ እመቤቴ ምን ይረባኛል ነይ እመቤቴ ሰረገላዬስ ነይ እመቤቴ መች ያድነኛል ነይ እመቤቴ ከተሠወረ  ነይ እመቤቴ ክፉ መከራ ነይ እመቤቴ እድናለሁኝ ነይ እመቤቴ አንችን ስጠራ ነይ እመቤቴ
አዝ
ለስንፍናዬስ ነይ እመቤቴ መቼ ልክ አለው ነይ እመቤቴ ስለ በደሌ ነይ እመቤቴ እተክዛለው ነይ እመቤቴ ለአነጋገሬ ነይ እመቤቴ ማጣፈጫ ነሽ ነይ እመቤቴ ተሰምቻለው ነይ እመቤቴ ድንግል ሆይ ስልሽ ነይ እመቤቴ
አዝ
ለመንገዴ ስንቅ ነይ እመቤቴ ለራቤ መርሻ ነይ እመቤቴ ለታመመ ሰው ነይ እመቤቴ ነሽ መፈወሻ ነይ እመቤቴ የተማጸነ ነይ እመቤቴ በስምሽ አምኖ ነይ እመቤቴ ማን አፍሮ ያውቃል ነይ እመቤቴ ፊትሽ ለምኖ ነይ እመቤቴ ዘማሪት ፋንቱ ወልዴ 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️

ሐምሌ ፮ /6/ በዚችም ዕለት ቅድስት ንስተሮኒን አረፈች። እርሷም ከኢየሩሳሌም ሰዎች ውስጥ ነበረች። እርሷም አስቀድማ ኃጢአተኛ ነበረች ከዚያም በኋላ ንስሓ ገብታ ወደ እግዚአብሔር በተቃጠለ ልብ ተመ
ሐምሌ ፮ /6/
በዚችም ዕለት ቅድስት ንስተሮኒን አረፈች። እርሷም ከኢየሩሳሌም ሰዎች ውስጥ ነበረች። እርሷም አስቀድማ ኃጢአተኛ ነበረች ከዚያም በኋላ ንስሓ ገብታ ወደ እግዚአብሔር በተቃጠለ ልብ ተመለሰች የሥጋን ፍላጐቶች ሁሉ ናቀች እመምኔት እስከ ሆነች ድረስ በበጎ ሥራ ሁሉ ትሩፋትንና ተጋድሎን አበዛች። እኀቶችም ከገድል ብዛትና ምግብን ከመተው የተነሣ ሥጋዋ እንዳለቀ አይተው ሥጋሽን እንድትረጂ ጥቂት እህል በወጥ ብዪ አሏት። አብዝተውም ግድ ባሏት ጊዜ ልጆቼ ሆይወደ ቀድሞ ልማዴ እንዳልመለስ ጥቂት ወጥ ስለመብላት አትድከሙ ስለዚህ ወጥ አልበላም አለቻቸው። ከዚህ በኋላ በሰላም አረፈች። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በጸሎቷ ይማረን ለዘላለሙ አሜን። ወስብሐት ለእግዚአብሔር ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur

እግዚአብሔር ስራው ድንቅ ነው እግዚአብሔር ስራው ድንቅ ነው ለእኔ ያደረገው ብዙ ነው እግዚአብሔር ስራው ድንቅ ነው ለእኔ ያደረገልኝ ብዙ ነው
አዝ
እረዳት እርሱ ነው ከሰማያት እግዚአብሔር ጠባቂ የኔን ሕይወት ብርሃኑን በፊቴ የሚያበራ አምላኬ ድንቅ ነው የእርሱ ስራ
አዝ
በመንገዴ ሁሉ የሚመራኝ ስነሳ ስወድቅም የሚያስበኝ ማንም አልመጣልኝ ከወገኔ ከሁሉም ይበልጣል እርሱ ለኔ
አዝ
የእዳዬን ደብዳቤ ውድቅ አድርጎ ሕይወቴን መራልኝ ወደ በጎ ኧረ እንደእግዚአብሔር ማን ይሆናል እሱን ለሚፈሩት ይታመናል
አዝ
እንድ ቀን አስቤ ተጨንቄ ለመኖር አልቻልኩም ተጠንቅቄ ሁሉን ነገር ለእርሱ ትቼዋለሁ በምሕረቱ ጥላ እኖራለሁ ዘማሪ እንዳልካቸው 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️

​​ቅዱስ ጳውሎስ ጳውሎስ ማለት ንዋይ ህሩይ ማለት ነው። ሐዋ. ፱፡ ፲፭ (9፡15) አንድም ብርሃን ማለት ነው። ዘዳ.፲፬፡፪ አንድም መድቅዕ ማለት ነው። ቀዳሚ ስሙ ሳዖል ነው። ሳዖል ማለት ጸጋ እግዚአብሔር የበዛለት ማለት ነው። ትውልዱ ከነገደ ቢኒያም ነው። ፊሊ. ፫፡፭ አባቱ ዮስአስ ይባላል። የተወለደው ጌታ በተወለደ በ፭ (5) ዓመት በጠርሴስ ነው። ከ፲፭ ዓመቱ ጀምሮ ኢየሩሳሌም በታላቅ እህቱ ቤት ተቀምጦ ከመምህር ገማልያል ሕገ ኦሪትን ተምሯል። በወንጌል ያመነው ጌታ ባረገ በ፰ኛው ዓመት ነበር። ጌታም በደማቆ መብረቅ ጥሎበት ሳኦል ሳኦል ስለምን ታሳደኛለህ ብሎ ታርቆታል። ከ፸፪ (72) አርድእት አንዱ የሆነው ሐናንያ ጌታ በራዕይ ታይቶት ጳውሎን አስተምረህ አሳምነህ አጥምቀው አለው። እርሱም በእጁ ገና አይኑ በዳሰሰው ጊዜ አይኑን አሳውሮት የነበረው እንደ ቅርፊት ወድቆለታል። ሐዋ.፱፡፩-፲፱ (9፡1¬-19) ከዚያ በኋላ በክርስቶስ እመኑ እያለ አስተምሯል። ብዙዎችንም አስተምሮ አጥምቋል። ሐዋ. ፲፬፡፰-፲፰ ብዙውንም አሳምኗል። በወይኒም ታስሮ በነበረበት ወቅት ብዙ ሰዎችን አሳምኗል። ጳውሎስ ግን ተቸገረና ዘወር ብሎ መንፈሱ፤ ከእርስዋ እንድትወጣ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም አዝሃለሁ አለው፤ በዚያም ሰዓት ወጣ። ጌቶችዋም የትርፋቸው ተስፋ እንደ ወጣ ባዩ ጊዜ ጳውሎስንና ሲላስን ይዘው ወደ ገበያ በሹማምት ፊት ጐተቱአቸው፤ ወደ ገዢዎችም አቅርበው። እነዚህ ሰዎች አይሁድ ሆነው ከተማችንን እጅግ ያናውጣሉ። እኛም የሮሜ ሰዎች ሆነን እንቀበላቸውና እናደርጋቸው ዘንድ ያልተፈቀደልንን ልማዶች ይናገራሉ አሉ። ሕዝቡም አብረው ተነሡባቸው፥ ገዢዎቹም ልብሳቸውን ገፈው በበትር ይመቱአቸው ዘንድ አዘዙ፤ በብዙም ከደበደቡአቸው በኋላ ወደ ወኅኒ ጣሉአቸው፥ የወኅኒውንም ጠባቂ ተጠንቅቆ እንዲጠብቃቸው አዘዙት። እርሱም የዚህን ዓይነት ትእዛዝ ተቀብሎ ወደ ውስጠኛው ወኅኒ ጣላቸው፥ እግራቸውንም በግንድ አጣብቆ ጠረቃቸው። በመንፈቀ ሌሊት ግን ጳውሎስና ሲላስ እየጸለዩ እግዚአብሔርን በዜማ ያመሰግኑ ነበር፥ እስረኞቹም ያደምጡአቸው ነበር ድንገትም የወኅኒው መሠረት እስኪናወጥ ድረስ ታላቅ የምድር መንቀጥቀጥ ሆነ፤ በዚያን ጊዜም ደጆቹ ሁሉ ተከፈቱ የሁሉም እስራት ተፈታ። የወኅኒውም ጠባቂ ከእንቅልፉ ነቅቶ የወኅኒው ደጆች ተከፍተው ባየ ጊዜ፥ እስረኞቹ ያመለጡ መስሎት ራሱን ይገድል ዘንድ አስቦ ሰይፉን መዘዘ። ጳውሎስ ግን በታላቅ ድምፅ ሁላችን ከዚህ አለንና በራስህ ክፉ ነገር አታድርግ ብሎ ጮኸ። መብራትም ለምኖ ወደ ውስጥ ሮጠ፥ እየተንቀጠቀጠም ከጳውሎስና ከሲላስ ፊት ተደፋ፤ ወደ ውጭም አውጥቶ። ጌቶች ሆይ፥ እድን ዘንድ ምን ማድረግ ይገባኛል? ኣላቸው። እነርሱም በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ እመን አንተና ቤተ ሰዎችህ ትድናላችሁ አሉት። ለእርሱና በቤቱም ላሉት ሁሉ የእግዚአብሔርን ቃል ተናገሩአቸው። በሌሊትም በዚያች ሰዓት ወስዶ ቍስላቸውን አጠበላቸው፥ ያን ጊዜውንም እርሱ ከቤተ ሰዎቹ ሁሉ ጋር ተጠመቀ፤ ወደ ቤቱም አውጥቶ ማዕድ አቀረበላቸው ፥ በእግዚአብሔርም ስላመነ ከቤተ ሰዎቹ ሁሉ ጋር ሐሤት አደረገ። ሐዋ. ፲፮፡፲፰-፴፬ (16፡18-34) ሕሙማንንም ሕሙም መስሎ አስተምሯል። ፩ቆሮ.፱፡፳፪ (1ቆሮ.9፡22) ፲፬ መልዕክታትንም ጽፏል። ከዚህ በኋላ በ69 ዓ.ም ሮም ሲያስተምር ኔሮን ቄሣር አስጠሩት ሲል በንጉሱ ፊት ሲቀርብ መስቀሉን ይዞ ቀረበ። ንጉሱ ተቆጥቶ በሰይፍ ቅጡ አለ። በመጎናጸፊያም ሸፍኖ ሰይፎታል። ደሙም ሰማየ ሰማይ ወጥቶ ቀተሉኒ በዓመጻ እያለ ተካሷቸዋል። ሲያልፍም የ72 ዓመት አረጋዊ ነበር። ከቅዱስ ጴጥሮስ ጋር የሞቱት በአንድ ቦታ በአንድ ቀን ነበር። ይህም ሐምሌ ፭ ነው። ምንጭ፡- ገድለ ሐዋርያት፣ ዜና ሐዋርያት፣ ነገረ ቅዱሳን ቁጥር ፪፣ መዝገበ ታሪክ የእግዚአብሔር ቸርነት የድንግል ማርያም አማላጅነት፣ የቅዱሳን መላእክት ተራዳኢነት፣ የጻድቃን፣ የሰማዕታት፣ የቅዱሳን ሐዋርያት፣ የቅዱሳን አበው መነኮሳት፣ የቅዱሳት አንስት፣ የደናግላንና የቅዱሳን ሁሉ ምልጃና ቃል-ኪዳናቸው ባለንበት ከሁላችን ጋር ይሁን ይቆየን፡፡ ወስብሐት ለእግዚአብሔር ለዘበቅዱሳኒሁ ይሴባሕ ይእዜኒ ወዘልፈኒ ወለዓለም ዓለም አሜን፡፡ ወአሜን ለይኩን ለይኩን፡፡ አነሳስቶ ያስጀመረኝ አስጀምሮ ያስጨረሰኝ የቅዱሳን አባቶቻችን አምላክ ይክበር ይመስገን አሜን፡፡ ለወዳጅዎ ሼር ያድርጉ! 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️

​​​​ወበዛቲ ዕለት ሐምሌ ፭ “ቅዱስ ጴጥሮስ ወቅዱስ ጳውሎስ” “ክበር ሞቱ ለጻድቅ በቅድመ እግዚአብሔር፤ (የቅዱሳኑ ሞት በእግዚአብሔር ፊት የከበረ ነው።”) መዝ. ፻፲፭/ ፻፲፮፡፲፭ (115/116፡15) “ለእናንተ የመንግሥተ ሰማያትን ምሥጢር ማወቅ ተሰጥቶአችኋል፥ ለእነርሱ ግን አልተሰጣቸውም።” ማቴ.፲፫፡፲፩ እንኳን ለቅዱሳን ሰማዕታቱ ለቅዱስ ጴጥሮስ ወቅዱስ ጳውሎስ የሰማዕትነት ቀን በዓላቸው በሰላም አደረሰን አደረሳችሁ አሜን። ቅዱስ ጴጥሮስ ቅዱስ ጴጥሮስ የተወለደው በገሊላ ባሕር ዳር በምትገኘው ቤተ ሳይዳ ነው፡፡ ጴጥሮስ ማለት ኰኩሐ ሃይማኖት ማለት ነው። ማቴ. ፲፮፡፲፰ (16፡18) በዕራይስጥ ኬፋ ይለዋል። ቀዳሚ ስሙ ስምዖን ነው። ዮሐ.፩፡፵፭ (1፥45)፡፡ የአባቱ ስም ዮና ሲሆን ትውልዱም ከነገደ ሮቤል ነው፡፡ ዮና ከነገደ ስምዖን የምትሆን አንዲት ሴት አግብቶ ቅዱስ ጴጥሮስን ወለደ፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስም ከተወለደ በኋላ እንደ ሕገ ኦሪት ትእዛዝ በስምንተኛው ቀን ወደ ግዝረት ቤት አግብተው ስሙን በእናቱ ነገድ ስም ስምዖን ብለው ሰይመውታል። እድሜው አምስት ዓመት ሲሆን እንደ አይሁድ ሥርዓት ሕገ ኦሪትን እየተማረ እንዲያድግ በቤተ ሳይዳ አጠግብ ወደሚገኘው ወደ ቅፍርናሆም ሰደዱት፡፡ በዘመኑ በባህር ዳር በምትገኘውና ታላቅ የንግድ መነኸርያ በነበረችው ቅፍርናሆም የሮም ጭፍሮች አለቃ የነበረችው በቅፍርናሆም የሮም ጭፍሮች አለቃ የነበረው ኢያኢሮስ አይሁድን ደስ ለማሰኘት አሰርቶት በነበረው ምኩራብ እየተማረ አደገ፡፡ ከዚያም በኋላ በዚያ ከተማ ቤት ሰርቶ ኮን ኮርድያ (ጴርጴቱዋ) የምትባል ሚስት አግብቶ እንደ አባቱ እንደ ዮና ይተዳደር የነበረው ከወንድሙ እንድርያስ ጋር ዓሣ በማጥመድ ነበር። ዓሣ እያጠመደና እየሸጠ ይኖር ነበር፡፡ ዓሣ ከሚያጠምድበት ተጠርቶ ሐዋርያ ሆኗለ። ማቴ. ፬፡፲፱ (4:19) ሐዋርያት መንፈስ ቅዱስ ከተቀበሉ በኋላ መዲናቸው ኢየሩሳሌም አንድ ዓመት ካስተማሩ በኋላ ወንጌል ካልደረሰበት ለማድረስ ዓለምን ዕዳ በዕዳ ከተከፋፈሉ ጊዜ ርዕሰ ሐዋያ ነውና ሮምን ደርቦ ሰርቶታል። በሮምም ፳፭ (25) አስተምሯል። ከዚያ በፊ ግን በሰማርያ፣ በልዳ፣ በኢዮጴ፣ በአንጾኪያ፣ጳንጦስ፣ በገላቲያ፣በቀጳዶያና በቢታኒያ አስተምራል። በትምህርቱም ጣቢታ ከሞት አስነስቷል። ሐዋ. ፱፡፴፪-፴፬ (9፡32¬-34) ያስተማራቸው ምዕመናም ከሃማኖታቸው እንዳይወጡ ፪ (2) መዕክታትን ጽፎላቸዋል። ንጉሱ ኔሮን ቄሳር ጣኦት አምላኪ ነበርና በሃይማኖት ምክንያት አስሮት ነበር። ለጣዖትም እንዲሰግድ ባስገደደው ጊዜ ለጣኦ አልሰግድም በማለቱ በችንካር ተቸንክሮ በመስቀል ተሰቅሎ ይሙት ብሎ ፈረደበት። አይሁድ ሲጣሉት ወደ ጌታ ቢያመለክት እሳት ከሰማይ ወርዳ ታጠፋለት ነበር። ይዞ ዳግም ቢሰቅሉትም ፈቃድህስ ከሆነ ብሎ እንደ ጌታ አቁማችሁ ሳይሆን ቁልቁል ዘቅዝቃችሁ ስቀሉኝ አላቸው። በራሱ ዘቅዝቀው ሰቅሎታል። ሥጋውን ደቀመዝሙሩ መርቄሎስ ከመስቀሉ አውርዶ በወተት በወይን አጥቦ ሽቱ ቀብቶ በነጭ ሐር ገንቦ እንዳይፈርስ በማረ በተመላ ሣጥን አድርጎ ቀብሮታል። ለወዳጅዎ ሼር ያድርጉ! 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️

ሐምሌ ፭ /5/ አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ሐምሌ አምስት በዚች ቀን የክቡራንና የዐበይት አባቶቻችን ሐዋርያት የጴጥሮስና የጳውሎስ የሰማዕትነታቸው መታሰቢያ ነው። ይህም ጴ
ሐምሌ ፭ /5/ አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ሐምሌ አምስት በዚች ቀን የክቡራንና የዐበይት አባቶቻችን ሐዋርያት የጴጥሮስና የጳውሎስ የሰማዕትነታቸው መታሰቢያ ነው። ይህም ጴጥሮስ ከቤተ ሳይዳ ነበር ዓሣ አጥማጅም ነበር ጌታችንም ከተጠመቀባት ዕለት ማግሥት አግኝቶ መረጠው ከእርሱ አስቀድሞም ወንድሙ እንድርያስን አግኝቶ መረጠው። መድኃኒታችንንም እስከ መከራው ጊዜ ሲአገለግለው ኖረ ፍጹም ሃይማኖት ለጌታውም ቅንዓትና ፍቅር ነበረው ። ስለዚህም በሐዋርያት ሁሉ ላይ አለቃ አድርጎ ሾመው። በመጨረሻም ተጋድሎውን ፈጽሞ ቁልቁል ተሰቅሎ በሰማዕትነት አረፈ። ይህም ጳውሎስ አስቀድሞ በክርስቶስ ያመኑትን የሚያሳድድ ነበረ እርሱም ከብንያም ወገን የፈሪሳዊ ልጅ ነው። ወላጆቹም ሳውል ብለው ስም አወጡለት ትርጓሜውም ስጦታ ማለት ነው። እርሱም ሕገ ኦሪትን አዋቂ ነበረ። ለሕጉም ቀናተኛ ሆኖ ምእመናን አሳዳጅ ነበረ። እግዚአብሔርም በመብረቅ ገስጾ ምርጥ እቃ አደረገው። በመጨረሻም ሐዋርያዊ አገልግሎቱን በሰማዕትነት ፈጽሞ አንገቱን ተሰይፏል። አስራ አራት መልዕክታትንም ጽፏል። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በጸሎታቸው ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ወስብሐት ለእግዚአብሔር ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur

በስልካቹ ብቻ 🙈 1 ወር ባልሞላ ጊዜ ውስጥ እንዲህ መሥራት የምትችሉ ይመስላችኋል ? 🤗 ለዚህ ነው እኛ ጋር ተማሩ የምንላቹ ለዛውም ቤታቹ ሆናቹ የ1000 ብር ቅናሹ ሊያበቃ የቀሩን ጥቂት ሰዓታት ብቻ ናቸው እጃቹ ላይ ባለው ስልክ ቤታቹ ሆናቹ » ተማሩ » ተሸለሙ ______________________________ ✓ ሙያን መማር እንዲህ ቀላል ሆኖ አያውቅም ✓ Capcut ✓ Alight Motion ✓ Inshot ✓ Kine Master ሁሉንም አንድ ላይ አሁኑኑ ተመዝገቡ @greenbirdtechnology ___________________________ Click Here For Details . . . @greenbirdtechs @greenbirdtechs የለውጥዎ ክንፍ 🔑 🐥

የወደደኝ ጌታ የወደደኝ ጌታ ምን አድርጌለት ነው ብዘምርለትም ያንስበታል ይኸው ከውድቀቴ አንስተህ ድካሜን ያገዝከኝ ሰባራውን ድልድይ ገጥመህ ያሳለፍከኝ
አዝ
በኢያሪኮ መንገድ ስለምን ቁጭብዬ ብርሃን እጅግ ናፍቆኝ ከሰው ተገልዬ የብርሃን ጌታ ወደ እኔ መጣና ዓይኔን አበራልኝ በእጁ ዳሰሰና
አዝ
ለብዙ ዘመናት አልጋ ላይ ተኝቼ የሚረዳኝ አጣሁ ጠሉኝ ዘመዶቼ የእኔ ጌታ አምላኬ ወደ እኔ መጣና አልጋህን ተሸከም አለኝ ፈወሰና
አዝ
አሥራ ሁለት ዓመት ደም የፈሰሰኝ ምራቅ እየተፋ ሁሉም ቢያንቋሽሹኝ የጌታዬ ልብሱን ጫፉን ብዳስሰው ኃይልም ከእርሱ ወጣ ደሜን ቀጥአረገው
አዝ
ሰካራም ዘማዊ ወንበዴ ነበርኩኝ የአመጸኞች መሪ ደምን ያፈሰስኩኝ ዛሬ ግን ታሪኬን ጌታ ቀይሮታል ለኃያሉ ጌታ ምስጋና ይገባል ዘማሪ ዳግማዊ ደርቤ 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️

ሐምሌ ፬ /4/ አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ሐምሌ አራት በዚች ቀን የቅዱሳን አቡቂርና ዮሐንስ የሥጋቸው ፍልሰት ሆነ። ይህም እንዲህ ነው እሊህ ቅዱሳን የካቲት ስድስት ቀን
ሐምሌ ፬ /4/
አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ሐምሌ አራት በዚች ቀን የቅዱሳን አቡቂርና ዮሐንስ የሥጋቸው ፍልሰት ሆነ። ይህም እንዲህ ነው እሊህ ቅዱሳን የካቲት ስድስት ቀን ሰማዕታት ሆነው በሞቱ ጊዜ ምእመናን ሥጋቸውን ተሸክመው ወስደው በእስክንድርያ ከተማ በስተሰሜን ባለች በቅዱስ ወንጌላዊ ማርቆስ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ በሥውር አኖሩዋቸው እስከ ሊቀ ጳጳሳት ቄርሎስ ዘመንም በዚያ ኖሩ። የእግዚአብሔር መልአክም ለቅዱስ ቄርሎስ ተገለጸለት ወደ ወንጌላዊ ቅዱስ ማርቆስ ቤተ ክርስቲያንም ሔዶ የቅዱሳን የአቡቂርንና የዮሐንስን ሥጋቸውን አውጥቶ እንዲሸከም አዘዘው። እርሱም ተነሥቶ ሔደ ከእርሱም ጋራ ብዙ ሕዝቦች ነበሩ በደረሱም ጊዜ ጸለዩ ምድሩንም ሲቆፍሩ ሥጋቸው በውስጡ ያለበት ቦታ ተገለጠላቸው በባሕር ዳርቻ ወደ አለች ወደ ሌላዪቱም የቅዱስ ማርቆስ ቤተ ክርስቲያን በታላቅ ክብርየቅዱሳኑን ሥጋቸውን ተሸክመው አድርሰው በዚያ አኖሩ። በዚያም ቤተ ክርስቲያን ሠሩላቸው በዚችም ቀን ታላቅ በዓል አደረጉ ከሥጋዎቻቸውም ድንቆች ተአምራት ተገለጡ አረማውያንም ተሰበሰቡ ይህንንም ድንቅ ተአምር በአዩ ጊዜ ጣዖቶቻቸውን ትተው ክርስቲያኖች ሆኑ ። በዚያቺም የጣዖቶች ቤት አሸዋ በላይዋ ተከመረባት ታላቅ ኮረብታም ሆነ። የቅዱሳንም ሥጋቸው ታምራትንና ለበሽተኞች ታላቅ ፈውስን ያደርጋል። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በጸሎታቸው ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ወስብሐት ለእግዚአብሔር ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur

2 ቀናት ብቻ ቀሩት 🤗 የ1000 ብር ቅናሹ ሊያበቃ ነው እጃቹ ላይ ባለው ስልክ ቤታቹ ሆናቹ » ተማሩ » ተሸለሙ ______________________________ ✓ ሙያን መማር እንዲህ ቀላል ሆኖ
2 ቀናት ብቻ ቀሩት 🤗 የ1000 ብር ቅናሹ ሊያበቃ ነው እጃቹ ላይ ባለው ስልክ ቤታቹ ሆናቹ » ተማሩ » ተሸለሙ ______________________________ ✓ ሙያን መማር እንዲህ ቀላል ሆኖ አያውቅም ✓ Capcut ✓ Alight Motion ✓ Inshot ✓ Kine Master ሁሉንም አንድ ላይ አሁኑኑ ተመዝገቡ @greenbirdtechnology ___________________________ Click Here For Details . . . @greenbirdtechs @greenbirdtechs የለውጥዎ ክንፍ 🔑 🐥

በእስራቴ አላፍርም በእስራቴ አላፍርም እኔ የማርያም ነኝ  እሮማዊ አይደለሁ ፍጹም ክርስትያን ነኝ ከመቤቴ ፍቅር የሚለየኝ ማነው መከራ ነው ችግር ወይስ እስራት ነው /2/
አዝ
አንተ መዝሙረኛ ነብዩ ዳዊት እንድታሸበሽብ በታቦቱ ፊት ሜልኮም ብትንቅህ ሰገነት ላይ ሆና እግዚያብሔር አይትዋታል ሳትናገር ገና እኔስ ለመቤቴ እዘምራለሁ ፍቅርዋ በደሜ ውስጥ እንዳለ አውቃለሁ ስምዋን ለምን ጠራህ ተብየ ስተየቅ አድምጡልኝ መልሴን ድንግልን እኔ አለቅ በአማን /2/እረዳቴ ናት እመቤታችን
አዝ
የኤልዛቤት ጭፍሮች መጥተው ይዘውኝ ጭው ያለ በረሃ እስርቤት ጣሉኝ ስለ እስራቴ ጌታየ አይቶልኛል ሁሉን ተመልክቶ ተበቅሎልኛል ከዝምታየ የተነሳ እንደ ዲዳ ሆንኩኝ ለበጎ ነገርን እንኩዋ ዝምም ያልኩኝ በእኩለ ለሊት ሊያስፈራሩኝ መጥተው ሳህሊለነ ብዬ ብርታትን አገኘሁ በአማን /2/እረዳቴ ናት እመቤታችን
አዝ
እረበናት ዛሬም መስክረው ሀሰት ወደ ፍርድ ወሰዱኝ ከማላውቅበት ከሳሾችም ቀርበው ሲከራከሩኝ እውነተኛው ዳኛ አሰናብበተኝ የምስጋናም ዘውድም ጌታ ደፍቶልኛል ለድንግል ውዳሴን ላቀርብ ፈቅዶልኛል ባለምዋልናትና ለቅድስት ስላሴ እስከ መጨረሻው ታመስግናት ነፍሴ በአማን /2/እረዳቴ ናት እመቤታችን ዝማሬ በቀሲስ እንግዳወርቅ በቀለ 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️

የሲሎንዲስ ጥበብ የሲሎንዲስ ጥበብ እወድሻለው የናሆም መድኃኒት እወድሻለው ማርያም አከብርሻለው ማርያም እወድሻለው
አዝ
ተጨንቄአለሁ ልንገርሽ ምስጢረኛዬ እናቴ ነሽ ሰው ያልሰማውን ብርቱ ምስጢር ድንግል ሆይ ላንቺ ላማክር የቁስለኛው መድኃኒቱ የአዳም ዘር ሁሉ ነሽ ህይወቱ መፍትሄ አለ በእጅሽ ተንበርክኬ ልማጸንሽ
አዝ
ሳልናገረው ይገባሻል የውስጤ ሁሉ ይታይሻል ድረሽ እናቴ ተራጅኝ ያላንቺ ለኔ ማን አለኝ ደስታዬ ደሰታ የሚሆነው በሀዘኔ የምጽናናው አንቺ ከእኔ ጋር ስለሆንሽ ተጽናንቻለው በስምሽ
አዝ
ወንድሞቼ እንኳን ቢሸጡኝ ሰው ሁሉ ጠላት ቢሆነኝ በእመ አምላክ ኃይል ከብሬአለሁ በጠላቴ ላይ ሰልጥኛለሁ የረሰኙ ሁሉ ያስቡኛል የተጣሉኝም ያከብሩኛል አንቺ አንግሰሽኝ አልወድቅም እቆማለሁኝ ዘለዓለም
አዝ
መንገዴ እረዝሞ ደክሜብሽ መከራው በዝቶ ታምሜብሽ ወድቄ ሳዝን ድረሽልኝ ለባሪያሽ ሃይሉን እንድትሰጭኝ ፍቅርሽ በውስጤ ተንሰራፋ በእናትነትሽ ልቤ ሰፋ የሚለያየን ማንም የለም ማርያም ልበልሽ ለዘለዓለም ዘማሪ ቀሲስ ምንዳዬ ብርሃኑ 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️

ሐምሌ ፫ /3/ በዚች ቀን ለአባቶች ሊቃነ ጳጳሳት ሃያ አራተኛ የሆነ የእስክንድርያ ሊቀ ጳጳሳት ቅዱስ አባት ቄርሎስ አረፈ። ይህም ቅዱስ የእናቱ ወንድም በሆነው በአባ ቴዎፍሎስ ዘንድ አደገ ጥቂት ከ
ሐምሌ ፫ /3/
በዚች ቀን ለአባቶች ሊቃነ ጳጳሳት ሃያ አራተኛ የሆነ የእስክንድርያ ሊቀ ጳጳሳት ቅዱስ አባት ቄርሎስ አረፈ። ይህም ቅዱስ የእናቱ ወንድም በሆነው በአባ ቴዎፍሎስ ዘንድ አደገ ጥቂት ከፍ ባለ ጊዜም ወደ አስቄጥስ ወደ መቃርስ ገዳም ላከው በዚያም አምላካውያት የሆኑ መጻሕፍትን ተማረ እግዚአብሔርም መጽሐፍን አንድ ጊዜ አንብቦ እስከሚአጸናው ድረስ ዕውቀትንና ማስተዋልን ሰጠው። ከዚህም በኃላ ደግሞ ያስተምረው ዘንድ ለአባ ሰራብዮን ሰጠው ከእርሱም ዘንድ ያለውን ትምህርቱን በፈጸመ ጊዜ ወደ ሊቀ ጳጳሳት ቴዎፍሎስ መለሰው ። እርሱም እጅግ ደስ ተሰኘበት እግዚአብሔርንም አመሰገነው። ከዚህም በኃላ ሁልጊዜ መጻሕፍትን እንዲያነብና ሕዝቡን እንዲያስተምር በሊቀ ጵጵስና ሥራ ውስጥ ሾመው። ከትምህርቱም ጣዕም የተነሣ ዝም ይል ዘንድ ማንም አይወድም ነበር። አባ ቴዎፍሎስም ከአረፈ በኃላ በእስክንድርያ ከተማ ላይ ይህን አባ ቄርሎስን ሊቀ ጵጵስና ሾሙት በዘመኑም በትምህርቱ ቤተ ክርስቲያን በራች። ይኸው አባት ቄርሎስ የቁስጥንጥንያ ሊቀ ጳጳሳት የነበረው ንስጥሮስ በካደ ጊዜ ተከራከረው ከስሕተቱም ባልተመለሰ ጊዜ አውግዘው ከመንበረ ሢመቱ አሳደዱት። ከዚህ በኋላ ብዙዎች ድርሳናትን ተግሣጻትንና መልእክቶችን ደረሰ። በወንጌላዊ ማርቆስ መንበር ላይ ሠላሳ ሁለት ዓመት ኖረ መልካም የሆነ ሥራውንም ፈጽሞ በሰላም አረፈ ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በዚህ አባት ጸሎተወ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ወስብሐት ለእግዚአብሔር ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur

ቤታቹ ሆናቹ ባላቹበት በስልካቹ ተማሩ ተሸለሙ ~ ለ3 ቀናት ብቻ የ1000 ብር ቅናሽ አድርገንላችኋል 🎉 እያንዳንዱን ጽንሰ ሀሳብ በተግባር ፍንትው አድርጋቹ የምትረዱበት ኮርስ ይሄው _________
ቤታቹ ሆናቹ ባላቹበት በስልካቹ ተማሩ ተሸለሙ ~ ለ3 ቀናት ብቻ የ1000 ብር ቅናሽ አድርገንላችኋል 🎉 እያንዳንዱን ጽንሰ ሀሳብ በተግባር ፍንትው አድርጋቹ የምትረዱበት ኮርስ ይሄው _______________ በ2 ወራት ብቁ ቪዲዮ ኤዲተር ሁኑ ። @Greenbirdtechnology ላይ ተመዝገቡ ። _______________ ምን ያስፈልጋል ? ● ስልክ ● ኢንተርኔት ወይም ዋይፋይ ● ለኮርስና ፕሮጀክት በቂ ጊዜ ___________________ የኮርስ ቀናት ዓርብ ምሽት 2፡00 - 4፡00 ቅዳሜ + እሑድ ምሽት 1፡00 - 3፡00 _______________ ለአሸናፊዎች ሽልማት Wordpress Course 1ኛ አሸናፊ 100% በነጻ 2ኛ አሸናፊ 50% በነጻ 3ኛ አሸናፊ 25% በነጻ _______________ Upwork + Fiverr ደግሞ ሙሉ ኮርስ በነጻ ጠቅላላ ክፍያ [ 5000 -1000 ] 4000 ብር ለ3 ቀናት ብቻ የሚቆይ ቅናሽ _______________ . . . @greenbirdtechs @greenbirdtechs የለውጥዎ ክንፍ 🔑 🐥