cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን። . #ዝማሬ_ዳዊት የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ አስተምህሮና ስርዓትን የጠበቁ ትምህርቶች, መዝሙራት እና ወረባትን ከነዜማቸው ለማግኘት ቻናላችንን ይጎብኙ። ለማንኛውም ሀሣብ, ጥቆማ, አስተያየት @zmaredawit_messengerbot ላይ ቢያስቀምጡልን ይደርሰናል

Show more
Advertising posts
135 362Subscribers
+5024 hours
+2707 days
+66430 days
Posting time distributions

Data loading in progress...

Find out who reads your channel

This graph will show you who besides your subscribers reads your channel and learn about other sources of traffic.
Views Sources
Publication analysis
PostsViewsSharesViews dynamics
01
#እስመለአለም_ምህረቱ እስመለአለም ምህረቱ/4/ አያልቅም ብዙነው የአምላክ ቸርነቱ/2/ ከማርያም የነሳው ያቅዱስ ስጋው/2/ ቀራንዮ ሲውል የሚያሳዝን ነው/2/ በፈጠረው ፍጥረት እጅግ ተሰቃይቶ/2/ ነፍሳትን አወጣ ከሲኦል ጎትቶ/2/ የማይሞተው ሞቶ የተቀበረው/2/ ከገሀነም እሳት እኛን ሊያድን ነው/2/ አመስግኑት ጌታን ሁላችሁ በአንድነት/2/ መሀሪ ነውና ለሰው ልጆች ህይወት/2/ ሊቀ መዘምራን ኪነጥበብ ወ/ቂርቆስ 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️
7 12358Loading...
02
መች ይረሳል የበገና መዝሙር መች ይረሳል የዋለልን ውለታ ቸርነቱ እፁብ ፍቅር የጌታ የታተመው በልባችን ፅላት ሞትን ገድሎ የሠጠንን ህይወት በጥፋቱ ቢወጣ አዳም ከገነት ቃል ገባለት ዳግም ሊሰጠው ህይወት ህያው ጌታ አምላክ ፈጣሪ ሳለ ስለ ቃሉ በእፀ መስቀል ላይ ዋለ አዝ በአይሁድ እጅ በፅኑ ተንገላታ የፍቅር አባት ክርስቶስ የእኛ ጌታ ሥጋው ደክሞ ቅዱስ ደሙ ፈሰሰ እዳችንን በሞቱ ደመሠሠ አዝ ስንጠላው እርሱ አብዝቶ ወደደን ስለ ፍቅሩ ሞትን ገድሎ አዳነን ባርነትን ኃጢአትን ከኛ ጥሎ ነፃ አወጣን በመስቀል ላይ ተሰቅሎ አዝ ሰላማችን የድንግል ማርያም ፍሬ ይገባዋል ምስጋና ዝማሬ ስለ ፍቅሩ ስላረገልን ሁሉ ተቀኙለት ፍጥረታት ዝም አትበሉ መምህር አቤል ተስፋዬ 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️
11 91890Loading...
03
በእጅ የያዙት ......... ። 👉 @ortodoxmezmur
18 42665Loading...
04
​​​​ኒቆዲሞስ 👉 የዐቢይ ጾም ሰባተኛ ሳምንት 🎤 በመምህር ቀሲስ ዶ/ር ዘበነ ለማ 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️
19 63555Loading...
05
ኒቆዲሞስ ኒቆዲሞስ ኒቆዲሞስ ክቡር ሌቱን በብርሃን የሚማር መምህር በጨለማው ግርማ ኮከብ የደመቀ በመከራው ፅናት ይህን ዓለም ናቀ መምህር ሆኖ ሳለ ከመማር ያልራቀ የትዕቢትን ጅረት በትህትና ተዋርዶ አደረቀ ረቢ ሰገደ በመንፈቀ ሌሊት ለረቢ አኮኑ አፅባይት እምነ አፅባይት የአቢ ረቢ ሰገደ በመንፈቀ ሌሊት ለረቢ አዝ ፍርሃትን በሚጥል ፍፁም ፍቅር ያደረ ከመስቀል አውርዶ ጌታውን ቀበረ የመግነዙን በፍታ በሽቶ አከበረ ከመቅደሱ አንቀፅ ላይረሳ አምድ ሆኖ ታጠረ ረቢ ሰገደ በመንፈቀ ሌሊት ለረቢ አኮኑ አፅባይት እምነ አፅባይት የአቢ ረቢ ሰገደ በመንፈቀ ሌሊት ለረቢ አዝ ለሊትም ለሊት ዕውቀትን ነገረች ህጉን ለሚያስበው ምክር አለኝ እያለች ከጨለማ ሀጢያት ነግታ ብርሃን ከአየች እንደ ኒቆዲሞስ ነፍስህም ተምራ ተመለሰች ረቢ ሰገደ በመንፈቀ ሌሊት ለረቢ አኮኑ አፅባይት እምነ አፅባይት የአቢ ረቢ ሰገደ በመንፈቀ ሌሊት ለረቢ ዲያቆን ዘማሪ ቀዳሚፀጋ 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️
19 693231Loading...
06
​​​​​​ኒቆዲሞስ - የዐብይ ጾም ሰባተኛ ሳምንት። ''እውነት እውነት እልሃለሁ፥ ሰው ዳግመኛ ካልተወለደ በቀር የእግዚአብሔርን መንግሥት ሊያይ አይችልም አለው። ሰው ከውኃና ከመንፈስ ካልተወለደ በቀር ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ሊገባ አይችልም። ከሥጋ የተወለደ ሥጋ ነው፥ ከመንፈስም የተወለደ መንፈስ ነው። (ዮሐ 3:3-6) ጌታችን ወደዚህ ምድር መጥቶ የምስራቹን ቃል ሲያውጅ እስራኤላውያን የተቀበሉት በተደበላለቀ ስሜት ነበር። በአንድ በኩል ሕዝቡ ለብዙ ዘመናት በባርነት ሲገዛ ስለነበር ከሮማውያን ቅኝ ግዛት ነጻ የሚያወጣቸው መሲህ ይፈልጋሉ፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ ሕዝቡ ለብዙ ዘመናት በባርነት ቀንበር ስለደከመ ተስፋ በመቁረጥ ተዳክሞ ነበር፡፡ መሲህ ቢመጣ እንኳ ይመጣል ብለው የሚጠብቁት ጦር ይዞ ሰራዊት አስከትሎ ነው ብለው ያምኑ ነበር፡፡ ስለዚህም ነው ክርስቶስን መሲህ ነኝ ብሎ ሲመጣ ለመቀበል ፈቃደኞች አልነበሩም፡፡ ምክንያቱ ደግሞ ጦር ሳይዝ ሰራዊት ሳያስከትል እንዲሁ ባዶ እጁን አርነት ላወጣችሁ መጥቻለሁ እያለ ደጋግሞ ተናግሯልና ነው፡፡ ምንም እንኳ አብዛኛው እስራኤላዊ የክርስቶስን መሲህነት ቢጠራጠርና ባይቀበለውም፣ በፍጹም እምነት እስከ መጨረሻው የተከተሉትም ነበሩ፡፡ ለዚህም ትልቅ ማሳያ የሚሆነን ከፈሪሳውያን ወገን የሆነ ኒቆዲሞስ የተባለ አይሁዳዊ ነው፡፡ ቅድስት ቤተክርስቲያንም ይህን ታላቅ ሰው ለማዘከር የዐቢይን ጾም ሰባተኛ እሁድ በእርሱ ስም ሰይማ ታከብረዋለች። ተከታዮቿ ምዕመናንም የእርሱን አሰረ ፍኖት እንዲከተሉ ትመክራለች ታስተምራለችም፡፡ => ኒቆዲሞስ ማነው? ፩. ኒቆዲሞስ ፈሪሳዊ ነው 《ዮሐ 3-1》 ፪. ኒቆዲሞስ የአይሁድ አለቃ ነው《ዮሐ 3-1》 ፫. ኒቆዲሞስ መምህረ እስራኤል ነው《ዮሐ 3-10》 ፬. ኒቆዲሞስ ምሁረ ኦሪት ነው 《ዮሐ 7-51》 => ኒቆዲሞስ ምን አደረገ? ለምስጢረ ጥምቀት መገለጥ ምክንያት ሆነ 《ዮሐ 3:1-21) አዋቂ ነን የሚሉትን አሳፈራቸው 《ዮሐ 7-51》 ጌታን ለመገነዝ በቃ 《ዮሐ 19-38》 => ከኒቆዲሞስ ምን እንማር? አትኅቶ ርእስ ጎደሎን ማወቅ የእውነት ምስክር《ስምዐ ጽድቅ》መሆን ትግሃ ሌሊት እስከ መጨረሻ መጽናት በአጠቃላይ ከኒቆዲሞስ ህይወት ብዙ ቁምነገሮችን እንማራለን፡፡ የኒቆዲሞስ በሌሊት ገስግሶ መምጣት ለምስጢረ ጥምቀት ትምህርት መገለጥ ምክንያት እንደሆነ ሁሉ በቅዳሴው በኪዳኑ በሰዓታቱ በማኅሌቱ መገኘትና መሳተፍ ረቂቅ የሆነው ሰማያዊ ምሥጢር ፍንትው ብሎ አንዲገለጥልን ምክንያት ነውና በምሥጢራት በመሳተፍ ራስን ዝቅ በማድረግ ለታላቅ ክብር እንድንበቃ የእርሱ መልካም ፈቃድ ይሁንልን፡፡ የዕለቱ ምስባክ፦ "ሐወጽከኒ ሌሊተ ወፈተንኮ ለልብየ። አመከርከኒ ወኢተረክበ ዓመፃ በላዕልየ። ከመ ኢይንብብ አፉየ ግብረ እጓለ እመ ሕያው"። መዝ17፥3-4። የሚነበበው ወንጌል ዮሐ3፥1-12። የሚቀደሰው ቅዳሴ የእመቤታችን የማርያም ቅዳሴ ነው። መልካም በዓልና የጾም ጊዜ ለሁላችንም ይሁንልን። ወስብሐት ለእግዚአብሔር 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️
19 920244Loading...
07
13/08/2016 ዓ.ም ✝ በዕለቱ ቅዳሴ ሰዓት የሚነበቡ መልዕክታት፣ወንጌልና ምስባክ። ሮሜ. ፯፥፩ - ፲፪፤ ፩ ዮሐ. ፬፥፲፰ - ፍ፤ ግብ ሐዋ. ፭፥፴፬ - ፍ፤ የዕለቱ ምስባክ፦ መዝ ፲፮፥፫ ሐወፅከኒ ሌሊተ ወፈተንኮ ለልብየ፤ አመከርከኒ ወኢተረክበ ዓመፃ በላዕሌየ፤ ከመ ኢይንብብ አፉየ ግብረ እጓለ እመሕያው። ትርጉም፦ በሌሊት ጎበኘኸኝ ልቤንም ፈተንኸው፤ ፈተንኸኝ ዓመፅ አልተገኘብኝም፤ የሰውን ሥራ አፌ እንዳይናገር። የዕለቱ ወንጌል፦ ዮሐ ፫፥፩ - ፲፪ ቅዳሴ፦ ዘእግዝእትነ ማርያም 👉 @ortodoxmezmur
17 81879Loading...
08
Media files
17 1710Loading...
09
🔰የዘማሪት የትምወርቅ ሙላት የበገና መዝሙሮች © ቤተ ዕንዚራ 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️
23 94412Loading...
10
በገና ክራር እና ከበሮ መማር የምትፈልጉ ኦርቶዶክሳዊያን ምዝገባ ስለጀመርን። ሁላችሁም ደውላችሁ ትመዘገቡ እና በመንፈሳዊ ዝማሬ ልባችንን እናሳርፍ ዘንድ ጥሪያችንን እናቀርባለን። ማኅበረ ኀዳፌ ነፍስ ለበለጠ መረጃ ☎️0912085085
18 55155Loading...
11
✞ ቸር አገልጋይ ማነው? ✞ ቸር አገልጋይ ማነው ለንጉሥ የታመነ መክሊቱን ያልቀበረ አትርፎ የከበረ (፪) ባለ አምስቱ መክሊት መልካም ያደረገው በመውጣት በመውረድ አትርፎ መጥቶ ነው በጥቂቱ ታምኖ በብዙ የተሾመው ባለ አምስቱ መክሊት ሊቀ ጳጳሱ ነው አዝ ሳይሰለች የተጋ ባለሁለት መክሊት የታመነ እረኛ በፍቅርና በእምነት ግባ የተባለው ወደ ጌታው ደስታ አጥምቆ ያቆርባል ካህኑ የጌታ አዝ ለሚበልጠው ጸጋ ተጠርቶ የነበረ መክሊቱን ደብቆ ቆፍሮ የቀበረ ሰነፍ ባርያ ተብሎ ወደ ፍርድ ተጣለ ማኔ ቴቄል ፋሬስ በአምላክ ፊት ቀለለ አዝ ፈቃድህን ማድረግ ነፍሱ ለምትወደው ወንጌልህን መግለፅ የየዕለት ግብሩ ነው ህግህ ለዘለላም ተጽፎ ይኖራል በታላቅ ጉባኤ ጽድቅህ ይነገራል ዘማሪ ዲያቆን ቀዳሜጸጋ ዮሐንንስ 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️
27 496323Loading...
12
​​የቀጠለ 👆 በመሆኑም የባለ አምስትና የባለ ሁለት መክሊት ባለቤቶች የሆኑት ወጥተው ወርደው ደክመው፣ መከራ መስቀልን ሳይሳቀቁና ሳይፈሩ፤ ወድደው ፈቅደው የጀመሩትን አገልግሎት በማክበር ሕይወታቸውን ለታመነው አምላክ አደራ በመስጠት የተማሩትን ፍጹም ትምህርት ለሌላው አስተምረው፣ ሠርተው ያገኙትን ለሌላው አካፍለው ወገናቸውን እንደራሳቸው አድርገው ሲመለከቱ ባለ አንድ መክሊት የተባለው ግን ዓላውያን እሳት ስለት አሳይተው ሃይማኖቴን ሲያስክዱኝ መናፍቃን ተከራክረው ምላሽ ቢያሳጡኝ ብሎ ፈርቶ ሃይማኖቱን በልቡ ከመደበቅና ከመሠወር በቀር የተማረውን ትምህርት ሠርቶ ያገኘውን ሀብት ንብረት ለሌላው ሊያካፍልና የተሰጠውን አደራም ሊወጣ አልወደደም፡፡ ይህ የመክሊቱ ባለቤት የተባለው ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሲሆን የተሰጣቸውን ሓላፊነት በአግባቡና በጽንአት ለተወጡት ሁሉ እርሱ ፍጹም ዋጋን የሚሰጣቸው መሆኑን ያመለክታል፡፡ ይህም ሁኔታ “አንተ በጎ ታማኝ ባሪያ በጥቂቱ ታምነሃል በብዙ እሾምሃለሁ። ወደ ጌታህ ደስታ ግባ” በሚል ታላቅ የምስጋና ቃል ተገልጧል፡፡ ይህ ቃል በሃይማኖትና በበጎ ምግባር ለእግዚአብሔር የታመኑ ሁሉ ዘለዓለማዊና ፍጹም ደስታ ወደሚገኝበት መንግሥተ ሰማያት ለመግባት ለሚያደርጉት የእምነት ጉዞ እጅግ ተስፋ የሆነ ቃል ነው፡፡ በዚህ ምንባብ ላይ እንደተገለጸው እግዚአብሔር አምላክ ለሁላችንም እርሱን የምናገለግልበትንና ለእርሱ በመታመን ዘለዓለማዊ ክብርን የምናገኝበትን ዕውቀትን፣ ማስተዋልን፣ እምነትን፣ ተስፋን፣ የሥነ ምግባር ሀብትን፣ ልዩ ልዩ ስጦታዎችን እንጠቀምባቸው ዘንድ ለእኛ ለሰው ልጆች እንደየዓቅማችን መጠን ሰጥቶናል፡፡ እነዚህ ሁሉ ነገሮች የሥጋችንን ምኞት ለማስፈጸም የተሰጡ ሳይሆኑ ነፍሳችን የምትከብርበትን መልካም ሥራን የምንሠራባቸው መሣሪያዎቻችን ናቸው። በመሆኑም እርሱ በሰጠን የአገልግሎት በር ጸጋ በታማኝነት በማገልገል በሕይወት ዘመናችን ሁሉ መንፈሳዊውን ሀብት የምናተርፍ እንሆን ዘንድ የተላለፈልን አምላካዊ ምክር ነው፡፡ ምክንያቱም እኛ የተጠራነው ፍሬ ልናፈራና ሌላውንም ልናተርፍ መልካም ሥራን ልንሠራ እንጂ የሥጋችንን ፈቃድ በመከተል የኃጢአት ባሮች ልንሆን አይደለም፡፡ መጽሐፍ እንዲህ አለ “ወኲሉ ዘከመ ተጸውአ ከማሁ ለየሀሉ፤ ሁሉ እንደተጠራ እንዲሁ ይኑር” /፩ኛ ቆሮ. ፯፥፳/ ከላይ እንደተመለከትነው በልዑል አምላክ በእግዚአብሔር አንደበት አንተ በጎ ታማኝ አገልጋይ በጥቂቱ ታምነሃልና በብዙ እሾምሃለሁ መባልን የመሰለ አስደሳችና አስደናቂ ነገር የለም፡፡ ይህ ደግሞ የሚገኘው ሃይማኖትን በሥራ በመግለጥ እንጂ ሃይማኖትን በልቡና በመያዝ ብቻ /ሙያ በልብ ነው/ በማለት ብቻ የሚገኝ አይደለም፡፡ ከእነዚህ እንደ አቅማቸው መጠን መክሊት ተሰጥቷቸው በትጋታቸውና በቅንነታቸው ሌላ መክሊት ካተረፉት በጎና ታማኝ አገልጋዮች የምንማረው እውነታም ይህ ነው፡፡ በብዙ ለመሾም ለማደግ ለመጽደቅ በጥቂቱ መታመን መፈተን መጋደል ግድ ነው፡፡ አንድ መክሊት የተሰጠውን ሰው ስንመለከተው ጌታውን ጨካኝና ፈራጅ አድርጎ ከመቁጠር ውጪ በተሰጠው መክሊት ወጥቶ ወርዶ ሊያተርፍ አልወደደም፡፡ መክሊቱንም ባስረከበ ጊዜ በጌታው ላይ የተናገራቸው ቃላት የእርሱን አለመታዘዝና አመጸኝነት ይገልጡ ነበር፡፡ በመሆኑም ይህ ሰው በጥቂቱ መታመን ያቃተውና በአስተሳሰቡ ደካማነት እጅግ የተጎሳቆለ ሰው ነው፡፡ በዚህ ምሳሌ መሠረት ይህ ባለ አንድ መክሊት የተባለው ሰው ዓላውያን ነገሥታት እሳት ስለት አሳይተው ቢያስክዱኝ መናፍቃን ተከራክረው መልስ ቢያሳጡኝ በማለት ሃይማኖቱን በልቡ ሸሽጎና ቀብሮ በተቀደሰ ተግባር ሳይገልጠው ከመያዙ ባሻገር በጌታ ፊት በድፍረት ቆሞ አንተ ሕግ ሳትሠራ በአእምሮ ጠባይዕ አውቃችሁ፤ መምህራንንም ሳትመድብ በሥነ ፍጥረት ተመራምራችሁ በሠራችሁ ብለህ የምትፈርድ ጽኑ ጨካኝ መሆንክን አውቃለሁና ፈርቼ ሃይማኖቴን በልቡናዬ ይዠዋለው በአዕምሮዬ ጠብቄዋለሁ የሚል ሃይማኖቱን ግን በሥራ የማይገልጥ ሰነፍ ሰውን ያመለክታል፡፡ ለዚህ ዓይነት ሰው የጌታ መልስ ደግሞ በምሳሌው መሠረት የሚከተለው ነው። እኔ ሕግ ሳልሠራ በአእምሮ ጠባይዕ አውቃችሁ ፤ መምህር ሳልሰጥ በሥነ ፍጥረት ተመራምራችሁ አውቃችሁ በሠራችሁት ብዬ የምፈርድ ጽኑ ጨካኝ መሆኔን ታውቃለህን? እንዲህስ ካወቅህ ሹመትክን ልትመልስልኝ ይገባኝ ነበር፡፡ ወጥቶ ወርዶ ለሚያስተምር በሰጠሁት ነበር፡፡ አሁንም የእርሱን መምህርነት ሹመት ነሥታችሁ (ወስዳችሁ) ለዚያ ለባለ ዐራቱና ለባለ ዐሥሩ ደርቡለት! እርሱን ግን አውጡት የሚል ነው። ምክንያቱም ከበጎ ምግባር የተለየች እምነት የሞተች እንደሆነ ተጽፏልና። ዛሬም እያንዳንዳችን በዓቅማችን መጠን መክሊት ተሰጥቶናል፡፡ ነገር ግን መክሊቱን እንደቀበረው እንደዚያ ሰው የተሰጠንን ቀብረን ለወቀሳና ለፍርድ እንዳንሰጥ በአገልግሎታችን ልንተጋ ይገባናል፡፡ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ይህንኑ ሲገልጥ “ወዘሂ ይትለአክ በመልእክቱ፤ ወዘሂ ይሜህር በትምህርቱ. . .፤ አገልግሎት ቢሆን በአገልግሎታችን እንትጋ የሚያስተምርም በማስተማሩ ይትጋ የሚሰጥም በልግሥና ይስጥ›› (ሮሜ. ፲፪፥፯) በማለት ተናግሯል፡፡ ለመሆኑ አሁን ባለንበት የስግብግብነት ወቅት ዛሬ ‹‹አንተ በጎ ታማኝ አገልጋይ…›› ተብሎ በእግዚአብሔር ሊመሰገን የሚችል ሰው ማን ይሆን? በእውነት እንዲህ ተብሎ የሚመሰገን በጎና ታማኝ ካህን በጎና ታማኝ መምህር በጎና ታማኝ ምእመን ታማኝ ሰባኪና ታማኝ ዘማሪ ማግኘት ይቻል ይሆንን? ነገር ግን መቼም አምላካችን ቸር ነውና በየዘመናቱ አንዳንድ ታማኝ አባቶችን እንደማያሳጣን ተስፋ አለን። ምክንያቱም ዛሬም ቢሆን እንደአባቶቻችን እንደቅዱሳን ሐዋርያት በእምነት፣ በትዕግሥት በፍቅር በተጋድሎ በየውሐት በትሕርምት በጸሊዓ ንዋይ በትሕትናና በትጋት በማገልገል የተሰጣቸውን መክሊት የሚያበዙ አገልጋዮች አሉ፡፡ የእነዚህ ክብራቸው በምድርም በሰማይም እጅግ የበዛና ራሳቸውን አስመስለው በትምህርት የወለዷቸው ልጆቻቸውም ለቤተ ክርስቲያን የተወደዱ የተከበሩ ልጆች ናቸው፡፡ ለምሳሌ ነቢየ እግዚአብሔር ሙሴ ነቢየ እግዚአብሔር ኢያሱን ፤ ቅዱስ ጴጥሮስ ቀሌምንጦስን፣ ቅዱስ ጳውሎስም ቅዱስ ጢሞቴዎስን ለቤተ ክርስቲያን አበርክተዋል፡፡ ሌሎችም አበው ቅዱሳን በወንጌል ቃል መንፈሳውያንና ትጉሃን የሆኑ ምእመናንን በሚገባ አፍርተዋል፡፡ ያላመኑትንም አሳምነው ወደ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በመመለስ ለዘለዓለማዊ ክብር የበቁ እንዲሆኑ አስችለዋቸዋል። በተሰጣቸው ጸጋም አትርፈው አትረፍርፈው ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በሀብተ መንፈስ ቅዱስ እንድትጎበኝ አድርገዋል፡፡ የእነርሱም በረከታቸው ረድኤታቸው ቃል ኪዳናቸው ለሌሎች እንዲተርፍ ሆኖላቸዋል፡፡ በመሆኑም ክርስቶስ በደሙ የከፈለውን ወደር የሌለውን ዋጋ ዓለም አምኖና ተቀብሎ በክርስትና ሃይማኖት እንዲድንበትና እንዲጠቀምበት በማድረግ እንዲሁም በታማኝነትና በበጎነት አገልግሎታቸው ጥንትም ዛሬም ላለችዋና ወደፊትም ለምትኖረዋ ቅድስት ቤተክርስቲያን ድምቀትም ውበትም የሆኑት ቅዱሳን አበው ሊገኙ የቻሉት ከእግዚአብሔር ይልቅ ሰውን ደስ ለማሰኘት በመድከማቸው ሳይሆን የተጠሩበትን ዓላማና የጠራቸውን እርሱን በሚገባ አውቀውና ከልብ ተረድተው ለዘለዓለማዊ ሕይወት ተግተው በመሥራታቸው ነው። ወስብሐት ለእግዚአብሔር 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️
25 653143Loading...
13
​​​​​​የዐብይ ጾም ስድስተኛ ሳምንት ገብርኄር ይባላል፡፡ ገብርኄር ማለት ታማኝ አገልጋይ ማለት ነው፡፡ ስለ ታማኝ አገልጋይ አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዚህ ዓለም ስንኖር ለፈጣሪያችን ያለንን ታማኝነትና የምናገኘውን ዋጋ በመዋዕለ ሥጋዌው አስተምሯል፡፡ ቅዱስ ያሬድ ለዜማ መክፈያነት የዐብይ ጾምን ሳምንታትን ሲከፍል ገብርኄርን ተጠቅሟልና እኛም ስለ ገብር ሄር ጥቂት እንበል፡፡ ልዑል እግዚአብሔር አምላካችን በነቢዩ አንደበት አድሮ፤ “እከሥት በምሳሌ አፉየ፤ ወእነግር አምሳለ ዘእምትካት፤ አንደበቴን /ነገሬን/ በምሳሌ እገልጣለሁ፤ ከቀድሞ ጀምሮ የነበረ ታሪክና ምሳሌ እናገራለሁ” አለ፡፡ ይህም ማለት ወንጌልን በምሳሌ አስተምራለሁ፤ በመልከ ጼዴቅ ዘመን አስቀድማ የተሠራችና ታይታ የጠፋችውን ወንጌልን እናገራለሁ፡፡ ይህን ታላቅ ምሥጢር ሐዋርያው ሲያብራራ “ከመ በአሚን ያጸድቆሙ እግዚአብሔር ለአሕዛብ አቅደመ አሰፍዎቶ ለአብርሃም ከመ ቦቱ ይትባረኩ ኲሎሙ አሕዛብ ፤ በአንተ አሕዛብ ሁሉ ይባረካሉ ብሎ ወንጌልን ለአብርሃም አስቀድሞ ሰበከ” ብሏል፡፡ /ገላ. ፫፥፰፣ መዝ. ፸፯፥፪ በዚሁ መሠረት ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወንጌለ መንግሥተ ሰማያትን ለልዩ ልዩ ወገኖች በልዩ ልዩ ምሳሌ አስተምሯል፤ ከላይ በተገለጠው ኃይለ ቃል መነሻነት ሁለት ምሳሌያትና አንድ ቃለ ትንቢት ቀርበዋል፡፡ ከምሳሌያቱ የመጀመሪያው በዐሥሩ ደናግል አንጻር የቀረበው ምሥጢር ሲሆን፤ ሌላኛው ደግሞ ወጥተው ወርደው ነግደው ያተርፉበት ዘንድ ገንዘቡን ስለሰጠ አንድ ነጋዴ የሚናገረው ነው፡፡ የትንቢቱ ምሥጢራዊ ይዘት የሚያስረዳውም ስለ ኅልቀተ ዓለም አይቀሬነት ነው፡፡ ስለሆነም በዚህ ዕትማችን ወጥተው ወርደው ነግደው እንዲያተርፉበት ከጌታቸው የተሰጣቸውን መክሊት ስለተቀበሉት አገልጋዮች ሕይወት እንመለከታለን፡፡ ፈጣሪያችን አእምሮውን ለብዎውን /ማስተዋሉን/ ያድለን፡፡ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለደቀ መዛሙርቱ ያስተማራቸው ምሳሌያዊ ትምህርቶች በቅዱስ መጽሐፋችን በሰፊው ተጽፈው እናገኛለን፡፡ የእነዚህ ትምህርታዊ ምሳሌዎች መሠረታዊ ሀሳብና ዓላማም የእግዚአብሔርን መንግሥት የምናገኝበትን የታማኝነትን ሥራ እንዴት መሥራት እንደሚገባንና መሥራትም እንደምንችል ማስተማር ነው፡፡ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስለመንግሥተ ሰማያት ምሥጢር ያስተማራቸው ብዙ ምሳሌዎች ያሉ ሲሆን ከእነዚህ ብዙ ምሳሌያዊ ትምህርቶች መካከልም እንዲያተርፉበት መክሊት ስለተሰጣቸውና ስለተመሰገኑት መልካም አገልጋዮች፣ እንዲሁም መክሊቱን በመቅበሩ ምክንያት በጌታው ስለተወቀሰውና ፍርድን ስለተቀበለው ሰነፍ ሰው ታሪክ፣ የታሪኩም ምሥጢር ምን እንደሚመስል የተጻፈው ትምህርት ነው። ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ይህንን ምሳሌ የተናገረው /ያስተማረው/ በሚከተለው መልኩ ነበር፤ ‹‹ወደ ሌላ ሀገር የሚሔድ ሰው ባሮቹን ጠርቶ ያለውን ገንዘብ እንደሰጣቸው እንዲሁ ይሆናልና ለእያንዳንዱ እንደ ዓቅሙ ለአንዱ አምስት መክሊት ለአንዱ ሁለት ለአንዱም አንድ ሰጠና ወደ ሌላ ሀገር ወዲያውኑ ሔደ፡፡ አምስት መክሊትም የተቀበለው ሔዶ ነገደበት ሌላም አምስት አተረፈ፣ እንዲሁም ሁለት የተቀበለው ሌላ ሁለት አተረፈ፣ አንድ የተቀበለው ግን ሔዶ ምድርን ቆፈረና የጌታውን ገንዘብ ቀበረ፡፡ ከብዙ ዘመንም በኋላ የእነዚያ ባሮች ጌታ መጣና ተቆጣጠራቸው፡፡ አምስት መክሊት የተቀበለውም ቀረበና ሌላ አምስት መክሊት አስረክቦ፡- ጌታ ሆይ አምስት መክሊት ሰጥተኸኝ ነበር፤ እነሆ ሌላ አምስት መክሊት አተረፍሁበት አለ፡፡ ጌታውም፡- መልካም አንተ በጎ ታማኝ ባሪያ በጥቂቱ ታምነሃል በብዙ እሾምሃለሁ፤ ወደ ጌታህ ደስታ ግባ አለው፡፡ ሁለት መክሊት የተቀበለው ደግሞ ቀርቦ፡- ጌታ ሆይ ሁለት መክሊት ሰጥተኸኝ ነበር፡፡ እነሆ ሌላ ሁለት መክሊት አተረፍሁበት አለ፡፡ ጌታውም፡- መልካም አንተ በጎ ታማኝ ባሪያ በጥቂቱ ታምነሃልና በብዙ እሾምሃለሁ፤ ወደ ጌታህ ደስታ ግባ አለው። አንድ መክሊትም የተቀበለው ደግሞ ቀርቦ፡- ጌታ ሆይ ካልዘራህበት የምታጭድ ካልበተንህበትም የምትሰበስብ ጨካኝ ሰው መሆንህን አውቃለሁ፤ ፈራሁም ሔጄም መክሊትህን በምድር ቀበርሁት ፤ እነሆ መክሊትህ አለልህ አለው፡፡ ጌታውም መልሶ እንዲህ አለው፡- አንተ ክፉና ሐሰተኛ ባሪያ ካልዘራሁበት እንዳጭድ ካልበተንሁበትም እንድሰበስብ ታውቃለህን? ስለዚህ ገንዘቤን ለለዋጮች አደራ ልትሰጠው በተገባህ ነበር። እኔም መጥቼ ያለኝን ከትርፉ ጋር እወስደው ነበር፡፡ ስለዚህ መክሊቱን ውሰዱበት ዐሥር መክሊትም ላለው ስጡት። ላለው ሁሉ ይሰጠዋልና ይበዛለትማል። ከሌለው ግን ያው ያለው እንኳ ይወሰድበታል፡፡ የማይጠቅመውንም ባሪያ በውጭ ወዳለው ጨለማ አውጡት፤ በዚያ ልቅሶና ጥርስ ማፋጨት ይሆናል የሚል ነው፡፡ መክሊት ጥንት የክብደት መለኪያ ነበር:: አንድ መክሊት 30 ኪሎ ግራም ያህል ነው፡፡ በዚህ ምሳሌ ላይ እንደተገለጸውም መክሊት የሚለው ቃል ገንዘብን ያመለክታል፡፡ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዚህ ምሳሌ ውስጥ እርሱን የምናገለግል ሁላችን እንደየዓቅማችን ማድረግ የሚገባንን መንፈሳዊ የአገልግሎት ሥራንና በአገልግሎታችን ውጤታማ በመሆናችንም ከእርሱ የምናገኘውን ዘለዓለማዊ ክብርና ዋጋን እንዲሁም መሥራት የሚገባንን ባለማድረጋችንም ምክንያት የሚገጥመንን መለኮታዊ ቅጣትን አመልክቶናል፡፡ በዚህ ምሳሌ ውስጥ ባለ አምስት የተባለው በቂና ፍጹም ትምህርት ተምሮ ሌላውን መክሮ አስተምሮ ራሱን አስመስሎ የተካ ያወጣ ነው፡፡ በተመሳሳይም ባለ ሁለት የተባለው እንደ መጀመሪያው ሁሉ ተምሮ ሌላውን መክሮ አስተምሮ ራሱን አስመስሎ ያወጣ ሲሆን ባለ አንድ የተባለው ደግሞ ተምሮ ሳያስተምር የቀረ በስንፍና በቸልተኝነት በማን አለብኝነት ሕይወት ተገድቦ የቀረ ሰው ነው፡፡ ይቀጥላል 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️
23 581184Loading...
14
08/06/16 ዓ.ም መዝሙር ዘገብር ኄር መኑ ውእቱ ገብርኄር የዕለቱ ምስባክ :- መዝ ፴፱(፵)፥፰ ከመ እንግር ፈቃደከ መከርኩ አምላኪየ፡፡ ወሕግከኒ በማዕከለ ከርሥየ፡፡ ዜኖኩ ጽድቀከ በማኅበር ዐቢይ፡፡ ትርጒም፦ አምላኬ ሆይ ፈቃድህን ለማድረግ ወደድሁ ፤ ሕግህም በልቤ ውስጥ ነው፡፡ በታላቅ ጉባኤ ጽድቅን አወራሁ፡፡ የዕለቱ ወንጌል፦ ማቴ ፳፭ ፥ ፲፬ -፴፩ ቅዳሴ፦ ዘባስልዮስ 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️
21 94863Loading...
15
#ማረኝ ማረኝ /3/ መመኪያዬ አርጅቻለሁ እኔስ በኃጢያት ጎስቁዬ/2/ ከፊቴ ናትና ኃጢያቴ ሁል ጊዜ ተዉጫለሁ እኔስ በሐዘን በትካዜ በፊትህ ክፋትን አድርጌያለሁ እኔ ምንም ጽድቅ አልሰራሁ በሕይወት ዘመኔ #አዝ ከፊትህ መቅበዝበዝ መሰደድ ፈለኩኝ ኃጢያት ከኋላዬ እያሳደደችኝ ወዴት እሄዳለሁ መሸሸጊያም የለኝ ምህረትህ መጠጊያ ዋሻ ካልሆነችኝ #አዝ የተሰባበረዉ አጥንቴ እንዲጠገን በምህረት እና በቸርነት ዳሰኝ የቀና መንፈስን አድስ በልቤ ዉስጥ ነፍሴ በእልልታ በተስፋ ትለወጥ #አዝ ቅዱስ መንፈስህን ከእኔ ላይ አትዉሰድ በንስሐ ድኜ በተስፋ እንድራመድ አቤቱ ንፁህ ልብ ፍጠርልኝ እና በደስታ ልስገድ በፍቅርህ ልፅናና ሊቀ መዘምራን ይልማ ኃይሉ 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️
27 407414Loading...
16
Media files
27 89780Loading...
17
Media files
28 41779Loading...
18
Media files
31 10072Loading...
19
Media files
32 62080Loading...
20
Media files
30 47678Loading...
21
Media files
29 69288Loading...
22
Media files
29 56195Loading...
23
Media files
27 13980Loading...
24
Media files
23 55480Loading...
25
Media files
22 689108Loading...
26
🔰የዲ/ን አቤል ተስፋዬ መዝሙሮች © ቤተ ዕንዚራ 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️
23 99421Loading...
27
​​ደብረ ዘይት፡- ዳግም ምጽአት ዘመነ ሥጋዌ የጌታችን መገለጥ ለመጀመሪያ ጊዜ የተመለከትንበት፣ ይህም ከሰማያት ወርዶ እኛን ለማዳን ከንጽሕት ቅድስት ድንግል ማርያም ከሥጋዋ ሥጋ ከነፍሷ ነፍስ ነሥቶ ሰው በመሆን ዓለምን ያዳነበት ነው፡፡ እርሱ እንደ ሰው ተወልዶ፣ እንደ ሕፃናት በጨርቅ ተጠቅልሎ፣ ጡት ጠብቶ፣ በየጥቂቱ አድጎ፣ በአጭር ቁመት በጠባብ ደረት ተወስኖ፣ በእግር ተመላልሶ፣ እንደ ሰው ተርቦና ተጠምቶ፣ ኀዘን መከራን ተቀብሎ በፍጹም ፍቅሩ አድኖናል፡፡ ፈውሰ ነፍስ በሆኑት ትምህርቶቹ ዓለምን አጣፍቶ፣ አዳኝ በሆኑት እጆቹ ልምሾዎችን፣ ድዊዎችንና አንካሶችን አድኖ፣ ጎባጣን አቅንቶ፣ የዕውራንን ዓይን አብርቷል፡፡ የእግዚአብሔር አንድያ ልጅ መሆኑንም በፈለገ ዮርዳኖስ በመጥምቀ መለኮት እጅ ተጠምቆ አስመስክራል፡፡ ብርሃነ መለኮቱ በታየበት በደብረ ታቦር ተራራም አምላክነቱን ገልጧል፡፡ (ማቴ.፫፥፲፫-፲፯፣፲፯፥፩-፰) ይህን ሁሉ ያደረገው ሰዎች አምላክነቱን አውቀን፣ ከሰማየ ሰማያት የወረደውና መከራን ተቀብሎ በመስቀል ላይ የሞተው ለእኛ ድኅነት መሆኑን እንዲሁም ድንቅ ሥራውን የፈጸመበት ይህን ጥበቡን ተረድቶና፣ የእጁን ሥራ፣ የቃሉን ተእምራት ያመነውን ሁሉም እንደሚድነን ሲያበስረን ነው፡፡ በተጓዳኝም በመዋዕለ ስብከቱ ስለ ዳግም ምጽአቱና ምልክቶቹ በደብረ ዘይት ተራራ ላይ በዝርዝር በደቀ መዛምርቱ በኩል አሳውቆናል፡፡ ሐዋርያው ቅዱስ ማርቆስ በወንጌሉ እንዲህ ይገልጸዋል፡፡ (ማር.፲፫፥፫-፴፯) “መቅደስም ትይዩ በደብረ ዘይት ተቀምጦ ሳለ፥ ጴጥሮስና ያዕቆብ ዮሐንስም እንድርያስም ንገረን፥ ይህ መቼ ይሆናል? ይህስ ሁሉ ይፈጸም ዘንድ እንዳለው ምልክቱ ምንድር ነው? ብለው ለብቻቸው ጠየቁት። ኢየሱስም መልሶ እንዲህ ይላቸው ጀመር። ማንም እንዳያስታችሁ ተጠንቀቁ። ብዙዎች እኔ ነኝ እያሉ በስሜ ይመጣሉና፥ ብዙዎችንም ያስታሉ። ጦርንም የጦርንም ወሬ በሰማችሁ ጊዜ አትደንግጡ፤ ይህ ሊሆን ግድ ነውና፥ ነገር ግን መጨረሻው ገና ነው። ሕዝብ በሕዝብ ላይ መንግሥትም በመንግሥት ላይ ይነሣልና፤ በልዩ ልዩ ስፍራ የምድር መናወጥ ይሆናል፤ ራብ ይሆናል፤ እነዚህ የምጥ ጣር መጀመሪያ ናቸው። እናንተ ግን ለራሳችሁ ተጠንቀቁ፤ ወደ ሸንጎ አሳልፈው ይሰጡአችኋል፤ በምኵራብም ትገረፋላችሁ፤ ምስክርም ይሆንባቸው ዘንድ ስለ እኔ በገዥዎችና በነገሥታት ፊት ትቆማላችሁ። አስቀድሞም ወንጌል ለአሕዛብ ሁሉ ይሰበክ ዘንድ ይገባል። ሲጐትቱአችሁና አሳልፈው ሲሰጡአችሁም ምን እንድትናገሩ አስቀድማችሁ አትጨነቁ፤ ዳሩ ግን በዚያች ሰዓት የሚሰጣችሁን ተናገሩ፤ የሚነግረው መንፈስ ቅዱስ ነው እንጂ እናንተ አይደላችሁምና። ወንድምም ወንድሙን አባትም ልጁን ለሞት አሳልፎ ይሰጣል፤ ልጆችም በወላጆቻቸው ላይ ይነሣሉ። ይገድሉአቸውማል፤ በሁሉም ዘንድ ስለ ስሜ የተጠላችሁ ትሆናላችሁ፤ እስከ መጨረሻ የሚጸና ግን እርሱ ይድናል። ነገር ግን በነቢዩ በዳንኤል የተባለውን የጥፋት ርኵሰት በማይገባው ስፍራ ቆሞ ብታዩ፥ አንባቢው ያስተውል፤ በዚያን ጊዜ በይሁዳ ያሉ ወደ ተራሮች ይሽሹ፤ በሰገነትም ያለ ወደ ቤት አይውረድ፤ ከቤቱም አንዳች ይወስድ ዘንድ አይግባ፤ በእርሻም ያለ ልብሱን ይወስድ ዘንድ ወደ ኋላው አይመለስ። በዚያን ወራትም ለርጉዞችና ለሚያጠቡ ወዮላቸው። ነገር ግን ሽሽታችሁ በክረምት እንዳይሆን ጸልዩ፤ በዚያን ወራት እግዚአብሔር ከፈጠረው ከፍጥረት መጀመሪያ ጀምሮ እስከ አሁን ድረስ ያልሆነ ደግሞም የማይሆን የመከራ ዓይነት ይሆናልና። ጌታስ ወራቶቹን ባያሳጥር፥ ሥጋ የለበሰ ሁሉ ባልዳነም፤ ነገር ግን ስለ መረጣቸው ምርጦች ወራቶቹን አሳጠረ። በዚያን ጊዜም ማንም እነሆ፥ ክርስቶስ ከዚህ አለ፥ ወይም እነሆ፥ ከዚያ አለ ቢላችሁ አትመኑ፤ ሐሰተኞች ክርስቶሶችና ሐሰተኞች ነቢያት ይነሣሉና፥ ቢቻላቸውስ የተመረጡትን እንኳን ያስቱ ዘንድ ምልክትና ድንቅ ያደርጋሉ። እናንተ ግን ተጠንቀቁ፤ እነሆ፥ አስቀድሜ ሁሉን ነገርኋችሁ። በዚያን ወራት ግን ከዚያ መከራ በኋላ ፀሐይ ይጨልማል፤ ጨረቃም ብርሃንዋን አትሰጥም፤ ከዋክብትም ከሰማይ ይወድቃሉ፤ የሰማያትም ኃይላት ይናወጣሉ። በዚያን ጊዜም የሰው ልጅ በብዙ ኃይልና ክብር በደመና ሲመጣ ያዩታል። በዚያን ጊዜም መላእክትን ይልካል፤ ከአራቱ ነፋሳትም ከምድር ዳርቻ እስከ ሰማይ ዳርቻ የተመረጡትን ይሰበስባቸዋል። ምሳሌውንም ከበለስ ተማሩ፤ ጫፍዋ ሲለሰልስ ቅጠልዋም ሲያቈጠቍጥ፥ ያን ጊዜ በጋ እንደ ቀረበ ታውቃላችሁ፤ እንዲሁ ደግሞ እናንተ ይህን ሁሉ መሆኑን ስታዩ ቀርቦ በደጅ እንደ ሆነ እወቁ። እውነት እላችኋለሁ፥ ይህ ሁሉ እስኪሆን ድረስ ይህ ትውልድ አያልፍም።ሰ ማይና ምድር ያልፋሉ ቃሌ ግን አያልፍም። ስለዚያች ቀን ወይም ስለዚያች ሰዓት ግን የሰማይ መላእክትም ቢሆኑ ልጅም ቢሆን ከአባት በቀር የሚያውቅ የለም። ጊዜው መቼ እንዲሆን አታውቁምና ተጠንቀቁ፤ ትጉ፤ ጸልዩም። ቤቱን ትቶ ወደ ሌላ አገር እንደ ሄደ ሰው ነው፤ ለባሮቹም ሥልጣን ለእያንዳንዱም ሥራውን ሰጥቶ በረኛውን እንዲተጋ አዘዘ። እንግዲህ በማታ ቢሆን ወይም በእኩለ ሌሊት ወይም ዶሮ ሲጮህ ወይም በማለዳ ቢሆን ባለቤቱ መቼ እንዲመጣ አታውቁምና፤ ድንገት መጥቶ ተኝታችሁ እንዳያገኛችሁ ስለዚህ ትጉ። ለእናንተም የምነግራችሁ ለሁሉ እላለሁ፤ ትጉ።” ወንድሞች ሆይ! ጊዜ ዋጋው የላቀ በመሆኑና የጌታችንንም የፍርድ ቀን የሚያውቅ አለመኖሩን በቅዱስ ወንጌል ስለተነገረን በበጎነት፣ በቅንነትና በእምነት ጽናት ሆነን በጸሎት እንዲሁም በጾም፣ በትጋትና በክርስቲያናዊ ምግባር በመታነጽ በሃይማኖት ልንኖር ይገባናል፡፡ ዘወትርም ለሕጉ በመገዛትና ትእዛዙን በመፈጸም እስከ መጨረሻው ጸንተን “ንጉሡም በቀኙ ያሉትን እንዲህ ይላቸዋል። እናንተ የአባቴ ቡሩካን፥ ኑ፤ ዓለም ከተፈጠረበት ጊዜ ጀምሮ የተዘጋጀላችሁን መንግሥት ውረሱ። ተርቤ አብልታችሁኛልና፥ ተጠምቼ አጠጥታችሁኛልና፥ እንግዳ ሆኜ ተቀብላችሁኛልና፥ ታርዤ አልብሳችሁኛልና፥ ታምሜ ጠይቃችሁኛልና፥ ታስሬ ወደ እኔ መጥታችኋልና” ልንባል ያስፈልጋል፡፡ (ማቴ.፳፭፥፴፬‐፴፮) ዕድል ፈንታችን መንግሥተ ሰማያት መውረስ ይሆን ዘንድም በምድራዊ ሕይወታችን መከራ ሥቃይ ተቀብለንና ለነፍሳችን መሥዋዕት መክፈል ይገባል እንጂ “እናንተ ርጉማን፥ ለሰይጣንና ለመላእክቱ ወደ ተዘጋጀ ወደ ዘለዓለም እሳት ከእኔ ሂዱ። ተርቤ አላበላችሁኝምና፥ ተጠምቼ አላጠጣችሁኝምና፥ እንግዳ ሆኜ አልተቀበላችሁኝምና፥ ታርዤ አላለበሳችሁኝምና፥ ታምሜ ታስሬም አልጠየቃችሁኝምና” ከመባል ይሠውረን፡፡ (ማቴ. ፳፭፥፵፩‐፵፫) የአምላካችን ቸርነትና ረድኤት አይለየን፤ አሜን! 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️
25 461132Loading...
28
ደብረ ዘይት - ምጽዓተ እግዚእነ 🎤 በመጋቤ ሐዲስ ሮዳስ ታደሰ 🙏ለመምህራችን ቃለ ሕይወት ያሰማልን #ሼር 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️
25 66697Loading...
29
#በስራዬ በስራዬ የት ይሆን መግቢያዬ(፬) ጨነቀኝ ጠበበኝ ኸረ ወዲያልኝ ጨነቀኝ ጠበበኝ ነፍሴ ወዲያልኝ ተሽክሜ የኃጢያት ክምር(፪) ይመሻል ይነጋል በከንቱ ስዞር(፪) ገሰገሰ ቀኑ ጨለመብኝ(፪) ዋ ለነብሴ ምንም ስንቅ አልያዝኩኝ(፪) #አዝ በድያለሁ ወዳንተ ጮሃለሁ ይቅር በለኝ እማፀንሃለሁ ችላ አትበለኝ ከፊትህ ቆሜያለሁ(፪) #አዝ አለፈብኝ በከንቱ ጊዜዬ(፪) እየጓጓሁ ለዚች ለሥጋዬ(፪) በንስሐ ሳላጥበው እድፌን(፪) ልትደርስ ነው ያች ፈተና ቀን(፪) መዝሙር ኪነጥበብ ወልደቂርቆስ "በደላችንን ይቅር በለን" ማቴ፮፥፲፪ 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️
24 432229Loading...
30
​​ሳማ ሰንበት ወደ ሳማ ሰንበት-ዓመታዊው የመንፈሳዊ ጉዞ መዳረሻ ተጓዡ ጋዜጠኛ ሄኖክ ስዩም በእኩለ ጾም መንፈሳዊ ተጓዦች ሊሳለሙበት የሚያቀኑትን ስፍራ በሀገራችን ከሚገኙ የመንፈሳዊ ቱሪዝም መዳረሻዎች አንዱ ነው ሲል ሳማ ሰንበትን እንዲህ ያስጎበኘናል፡፡ (ሔኖክ ስዮም)  ይህ ጉዞ ከዛሬ ሁለት መቶ ሃምሳ ዓመታት በፊት እንደጀመረ የሳማ ቀበሌ አባቶች ይናገራሉ፡፡ ይሁን እንጂ ባለፉት ሃያ ዓመታት ከዓመት ዓመት ተአምር እየሆነ መጥቷል፡፡ ከአዲስ አበባ ምስራቃዊ አቅጣጫ የሚገኘውን ሳማ ሰንበት ልንጎበኝ እየሄድን ነው፡፡ ብቻችንን አይደለም እየሄድን ያለንው፤ በሺዎች የሚቆጠሩ አውቶቢሶችና ሚኒባሶች ሰው ሞልተው እንደኛው ጉዞ ላይ ናቸው፡፡ ዋና ዋና ለሚባሉ ከተሞች ማለትም ለአዲስ አበባ፣ ለቢሸፍቱ፣ ለሞጆ፣ ለአዳማ፣ ለዝዋይና ለአረርቲ የሚቀርብ በመሆኑ በዓመት አንዴ ከተሜዎች የማይቀሩበት መንፈሳዊ ስፍራ ሆኗል፡፡ በኦርቶዶክስ ምዕመናን ዘንድ ታላቅ ስፍራ የሚሰጠው የአብይ ጾም እኩሌት ደብረ ዘይት ይባላል፡፡ ይህንን ቀን ደብረ ዘይትን ተሻግረው ሳማ ሰንበት የሚያሳልፉ መቶ ሺዎች ናቸው፡፡ ከአዲስ አበባ 110 ኪሎ ሜትር ተጉዘን መጥተናል፡፡ ሰሜን ሸዋ ዞን ምንጃር ሸንኮራ በሚባለው ወረዳ እንገኛለን፡፡ ይህቺ በዓመት አንድ ቀን ሰው መርፌ ሳያስጥል የሚጠቀጥቃት ስፍራ ሳማ ቀበሌ ውስጥ ትገኛለች፡፡ ሳማ ሰንበት ደርሰናል፡፡ ክቧ ቤተ ክርስቲያን ግንባሯ ላይ እንደሻሽ የጠመጠመችው በሚመስለው አረንጓዴ ቢጫ ቀይ ቀለም አሸብርቃለች፡፡ ይህቺ ቤተ ክርስቲያን ህንጻዋ ዘመናዊ ይሁን እንጂ ሳማ ሰንበት ከተተከለ ሶስት መቶ ዓመታትን ያለፈ እድሜ እንዳለው የአካባቢው አባቶች ይናገራሉ፡፡ ሰው ቁጥር የለውም፡፡ የቤተክርስቲያኗ ቅጥር ጊቢ እንዲህ መፈናፈኛ ያጣው ብዙው ሺ ከደጃፉ ቆሞ ነው፡፡ ሳማ ሰንበት በዓመት አንድ ግዜ የደብረ ዘይት በዓል የሚከበርባት ስፍራ ስትሆን እንደ አንዳንዶች ግምት ይሄ ስፍራ በዚህ መልኩ በዓለም ሁለተኛው ብቸኛ ደብረ ዘይት በድምቀት የሚከበርበት እንደሆነ ይናገራሉ፡፡ ስፍራውን የተለዩ ካደረጉት ውስጥ ለመውረድ የሚያስፈራው የጠበሉ መንገድና ዋሻው የተለየ ቦታ የሚሰጣቸው ናቸው፡፡ ከሳማ ሰንበት እየወጣን ነው፡፡ የሰው ብዛት መንገዳችንን ሰዓት የሚበላ ሊያደርገው ይችላል፡፡ የምንጃርን ሸንኮራ እየከሰከስን በምዕመናኑ ዝማሬ ተመስጠን ዳግም አዲስ አበባን አሰብናት፡፡ በሰላም ለቀዋት የወጡ አውቶቢሶች በሰላም ደጃፏን ርግጠው ተሳላሚዎቹ በየቤታቸው ይገቡ ዘንድ። የቻላችሁ ነገ ሄዳችሁ አድራችሁ የበረከት ተካፋይ ሁኑ! አላሰብኩበትም አትበሉ ሁሉን ፈፃሚ እግዚአብሔር አምላክ ነው በችግር ምክንያት የማትችሉ ግን እርሱ በፈቀደ ግዜ እንዲያደርሳችሁ ጸልዩ! 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️
24 63254Loading...
#እስመለአለም_ምህረቱ እስመለአለም ምህረቱ/4/ አያልቅም ብዙነው የአምላክ ቸርነቱ/2/ ከማርያም የነሳው ያቅዱስ ስጋው/2/ ቀራንዮ ሲውል የሚያሳዝን ነው/2/ በፈጠረው ፍጥረት እጅግ ተሰቃይቶ/2/ ነፍሳትን አወጣ ከሲኦል ጎትቶ/2/ የማይሞተው ሞቶ የተቀበረው/2/ ከገሀነም እሳት እኛን ሊያድን ነው/2/ አመስግኑት ጌታን ሁላችሁ በአንድነት/2/ መሀሪ ነውና ለሰው ልጆች ህይወት/2/ ሊቀ መዘምራን ኪነጥበብ ወ/ቂርቆስ 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️
Show all...
53🕊 6
መች ይረሳል የበገና መዝሙር መች ይረሳል የዋለልን ውለታ ቸርነቱ እፁብ ፍቅር የጌታ የታተመው በልባችን ፅላት ሞትን ገድሎ የሠጠንን ህይወት በጥፋቱ ቢወጣ አዳም ከገነት ቃል ገባለት ዳግም ሊሰጠው ህይወት ህያው ጌታ አምላክ ፈጣሪ ሳለ ስለ ቃሉ በእፀ መስቀል ላይ ዋለ አዝ በአይሁድ እጅ በፅኑ ተንገላታ የፍቅር አባት ክርስቶስ የእኛ ጌታ ሥጋው ደክሞ ቅዱስ ደሙ ፈሰሰ እዳችንን በሞቱ ደመሠሠ አዝ ስንጠላው እርሱ አብዝቶ ወደደን ስለ ፍቅሩ ሞትን ገድሎ አዳነን ባርነትን ኃጢአትን ከኛ ጥሎ ነፃ አወጣን በመስቀል ላይ ተሰቅሎ አዝ ሰላማችን የድንግል ማርያም ፍሬ ይገባዋል ምስጋና ዝማሬ ስለ ፍቅሩ ስላረገልን ሁሉ ተቀኙለት ፍጥረታት ዝም አትበሉ መምህር አቤል ተስፋዬ 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️
Show all...
59🥰 6
በእጅ የያዙት ......... ። 👉 @ortodoxmezmur
Show all...
94😍 16
​​​​ኒቆዲሞስ 👉 የዐቢይ ጾም ሰባተኛ ሳምንት 🎤 በመምህር ቀሲስ ዶ/ር ዘበነ ለማ 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️
Show all...
56🕊 8
ኒቆዲሞስ ኒቆዲሞስ ኒቆዲሞስ ክቡር ሌቱን በብርሃን የሚማር መምህር በጨለማው ግርማ ኮከብ የደመቀ በመከራው ፅናት ይህን ዓለም ናቀ መምህር ሆኖ ሳለ ከመማር ያልራቀ የትዕቢትን ጅረት በትህትና ተዋርዶ አደረቀ ረቢ ሰገደ በመንፈቀ ሌሊት ለረቢ አኮኑ አፅባይት እምነ አፅባይት የአቢ ረቢ ሰገደ በመንፈቀ ሌሊት ለረቢ አዝ ፍርሃትን በሚጥል ፍፁም ፍቅር ያደረ ከመስቀል አውርዶ ጌታውን ቀበረ የመግነዙን በፍታ በሽቶ አከበረ ከመቅደሱ አንቀፅ ላይረሳ አምድ ሆኖ ታጠረ ረቢ ሰገደ በመንፈቀ ሌሊት ለረቢ አኮኑ አፅባይት እምነ አፅባይት የአቢ ረቢ ሰገደ በመንፈቀ ሌሊት ለረቢ አዝ ለሊትም ለሊት ዕውቀትን ነገረች ህጉን ለሚያስበው ምክር አለኝ እያለች ከጨለማ ሀጢያት ነግታ ብርሃን ከአየች እንደ ኒቆዲሞስ ነፍስህም ተምራ ተመለሰች ረቢ ሰገደ በመንፈቀ ሌሊት ለረቢ አኮኑ አፅባይት እምነ አፅባይት የአቢ ረቢ ሰገደ በመንፈቀ ሌሊት ለረቢ ዲያቆን ዘማሪ ቀዳሚፀጋ 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️
Show all...
81🥰 6😍 6🕊 3🔥 2
​​​​​​ኒቆዲሞስ - የዐብይ ጾም ሰባተኛ ሳምንት። ''እውነት እውነት እልሃለሁ፥ ሰው ዳግመኛ ካልተወለደ በቀር የእግዚአብሔርን መንግሥት ሊያይ አይችልም አለው። ሰው ከውኃና ከመንፈስ ካልተወለደ በቀር ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ሊገባ አይችልም። ከሥጋ የተወለደ ሥጋ ነው፥ ከመንፈስም የተወለደ መንፈስ ነው። (ዮሐ 3:3-6) ጌታችን ወደዚህ ምድር መጥቶ የምስራቹን ቃል ሲያውጅ እስራኤላውያን የተቀበሉት በተደበላለቀ ስሜት ነበር። በአንድ በኩል ሕዝቡ ለብዙ ዘመናት በባርነት ሲገዛ ስለነበር ከሮማውያን ቅኝ ግዛት ነጻ የሚያወጣቸው መሲህ ይፈልጋሉ፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ ሕዝቡ ለብዙ ዘመናት በባርነት ቀንበር ስለደከመ ተስፋ በመቁረጥ ተዳክሞ ነበር፡፡ መሲህ ቢመጣ እንኳ ይመጣል ብለው የሚጠብቁት ጦር ይዞ ሰራዊት አስከትሎ ነው ብለው ያምኑ ነበር፡፡ ስለዚህም ነው ክርስቶስን መሲህ ነኝ ብሎ ሲመጣ ለመቀበል ፈቃደኞች አልነበሩም፡፡ ምክንያቱ ደግሞ ጦር ሳይዝ ሰራዊት ሳያስከትል እንዲሁ ባዶ እጁን አርነት ላወጣችሁ መጥቻለሁ እያለ ደጋግሞ ተናግሯልና ነው፡፡ ምንም እንኳ አብዛኛው እስራኤላዊ የክርስቶስን መሲህነት ቢጠራጠርና ባይቀበለውም፣ በፍጹም እምነት እስከ መጨረሻው የተከተሉትም ነበሩ፡፡ ለዚህም ትልቅ ማሳያ የሚሆነን ከፈሪሳውያን ወገን የሆነ ኒቆዲሞስ የተባለ አይሁዳዊ ነው፡፡ ቅድስት ቤተክርስቲያንም ይህን ታላቅ ሰው ለማዘከር የዐቢይን ጾም ሰባተኛ እሁድ በእርሱ ስም ሰይማ ታከብረዋለች። ተከታዮቿ ምዕመናንም የእርሱን አሰረ ፍኖት እንዲከተሉ ትመክራለች ታስተምራለችም፡፡ => ኒቆዲሞስ ማነው? ፩. ኒቆዲሞስ ፈሪሳዊ ነው 《ዮሐ 3-1》 ፪. ኒቆዲሞስ የአይሁድ አለቃ ነው《ዮሐ 3-1》 ፫. ኒቆዲሞስ መምህረ እስራኤል ነው《ዮሐ 3-10》 ፬. ኒቆዲሞስ ምሁረ ኦሪት ነው 《ዮሐ 7-51》 => ኒቆዲሞስ ምን አደረገ? ለምስጢረ ጥምቀት መገለጥ ምክንያት ሆነ 《ዮሐ 3:1-21) አዋቂ ነን የሚሉትን አሳፈራቸው 《ዮሐ 7-51》 ጌታን ለመገነዝ በቃ 《ዮሐ 19-38》 => ከኒቆዲሞስ ምን እንማር? አትኅቶ ርእስ ጎደሎን ማወቅ የእውነት ምስክር《ስምዐ ጽድቅ》መሆን ትግሃ ሌሊት እስከ መጨረሻ መጽናት በአጠቃላይ ከኒቆዲሞስ ህይወት ብዙ ቁምነገሮችን እንማራለን፡፡ የኒቆዲሞስ በሌሊት ገስግሶ መምጣት ለምስጢረ ጥምቀት ትምህርት መገለጥ ምክንያት እንደሆነ ሁሉ በቅዳሴው በኪዳኑ በሰዓታቱ በማኅሌቱ መገኘትና መሳተፍ ረቂቅ የሆነው ሰማያዊ ምሥጢር ፍንትው ብሎ አንዲገለጥልን ምክንያት ነውና በምሥጢራት በመሳተፍ ራስን ዝቅ በማድረግ ለታላቅ ክብር እንድንበቃ የእርሱ መልካም ፈቃድ ይሁንልን፡፡ የዕለቱ ምስባክ፦ "ሐወጽከኒ ሌሊተ ወፈተንኮ ለልብየ። አመከርከኒ ወኢተረክበ ዓመፃ በላዕልየ። ከመ ኢይንብብ አፉየ ግብረ እጓለ እመ ሕያው"። መዝ17፥3-4። የሚነበበው ወንጌል ዮሐ3፥1-12። የሚቀደሰው ቅዳሴ የእመቤታችን የማርያም ቅዳሴ ነው። መልካም በዓልና የጾም ጊዜ ለሁላችንም ይሁንልን። ወስብሐት ለእግዚአብሔር 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️
Show all...

170🕊 9🔥 3😍 1
13/08/2016 ዓ.ምበዕለቱ ቅዳሴ ሰዓት የሚነበቡ መልዕክታት፣ወንጌልና ምስባክ። ሮሜ. ፯፥፩ - ፲፪፤ ፩ ዮሐ. ፬፥፲፰ - ፍ፤ ግብ ሐዋ. ፭፥፴፬ - ፍ፤ የዕለቱ ምስባክመዝ ፲፮፥፫ ሐወፅከኒ ሌሊተ ወፈተንኮ ለልብየ፤ አመከርከኒ ወኢተረክበ ዓመፃ በላዕሌየ፤ ከመ ኢይንብብ አፉየ ግብረ እጓለ እመሕያው። ትርጉም፦ በሌሊት ጎበኘኸኝ ልቤንም ፈተንኸው፤ ፈተንኸኝ ዓመፅ አልተገኘብኝም፤ የሰውን ሥራ አፌ እንዳይናገር። የዕለቱ ወንጌል፦ ዮሐ ፫፥፩ - ፲፪ ቅዳሴ፦ ዘእግዝእትነ ማርያም 👉 @ortodoxmezmur
Show all...
63🕊 5🥰 2
🔰የዘማሪት የትምወርቅ ሙላት የበገና መዝሙሮች © ቤተ ዕንዚራ 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️
Show all...
46🥰 8😍 5
በገና ክራር እና ከበሮ መማር የምትፈልጉ ኦርቶዶክሳዊያን ምዝገባ ስለጀመርን። ሁላችሁም ደውላችሁ ትመዘገቡ እና በመንፈሳዊ ዝማሬ ልባችንን እናሳርፍ ዘንድ ጥሪያችንን እናቀርባለን። ማኅበረ ኀዳፌ ነፍስ ለበለጠ መረጃ ☎️0912085085
Show all...
66🥰 17🔥 3