ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit
የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ አስተምህሮና ስርዓትን የጠበቁ ትምህርቶች፣ ስንክሳር፣ መዝሙራትን ከነዜማቸው ለማግኘት ቻናላችንን ይጎብኙ። ለማንኛውም አስተያየት @Zimaredawitmessanger ላይ ቢያስቀምጡልን ይደርሰናል። ስለሚሰጡን ገንቢ ሃሳብ እናመሰግናለን። YouTube Page - https://bit.ly/2O1Z3d8 Facebook Page - https://www.fb.com/l/6lp1kJRRR
إظهار المزيد📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit
تُعد قناة ዝማሬ ዳዊት - Zemare Dawit (@ortodoxmezmur) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 167 424 مشتركاً، محتلاً المرتبة 152 في فئة الدين والقيم الروحية والمرتبة 146 في منطقة Ethiopia.
📊 مؤشرات الجمهور والحراك
منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 167 424 مشتركاً.
بحسب آخر البيانات بتاريخ 19 يونيو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار -222، وفي آخر 24 ساعة بمقدار 93، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.
- حالة التحقق: غير موثّقة
- معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 14.45%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 6.03% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
- وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 24 200 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 10 095 مشاهدة.
- التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 168.
📝 الوصف وسياسة المحتوى
يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
“የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ አስተምህሮና ስርዓትን የጠበቁ ትምህርቶች፣ ስንክሳር፣ መዝሙራትን ከነዜማቸው ለማግኘት ቻናላችንን ይጎብኙ።
ለማንኛውም አስተያየት @Zimaredawitmessanger ላይ ቢያስቀምጡልን ይደርሰናል። ስለሚሰጡን ገንቢ ሃሳብ እናመሰግናለን።
YouTube Page - https://bit.ly/2O1Z3d8
Facebook Page - https://www.fb.com/l/6lp1kJRRR”
بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 20 يونيو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة الدين والقيم الروحية.
ሰኔ ፲፫ /13/በዚችም ዕለት ለከበረ መልአክ አዲስ የምሥራች ነጋሪ ለሆነ የመላእክት አለቃ ገብርኤል በዓልን ያደርጉለት ዘንድ መምህራን በግብጽ አገር ለክርስቲያን ወገኖች ሥርዓት ሠሩላቸው ። ይህ የከበረ መልአክ የእስራአል ልጆች ከሰይጣን እጅ ስለመዳናቸውና ከምርኮም ስለ መመለሳቸው ነቢዩ ዳንኤል ወደ እግዚአብሔር በሚጸልይና በሚማልድ ጊዜ አስቀድሞ የተገለጠለትና ስለ ድኅነታቸውና ስለ ቤተ መቅደስም መታነፅ የነገረው ነውና ። ዳግመኛም ክብር ይግባውና ስለ ክርስቶስ መምጣትና መገደል ስለ ቤተ መቅደስም መፍረስ ከዚያም በኋላ ስለ ሐሳዊ መሲሕ መምጣት ነገረው ። ለመድኀን መምጣትም በሱባዔ የወሰናቸው ዘመናት በተፈጸሙ ጊዜ ይህ የከበረ መልአክ የመላእክት አለቃ ገብርኤል ከእግዚአብሔር ዘንድ ተልኮ ወደ ቅድስት ድንግል ወደ እመቤታችን ማርያም መጣ ዓለምን ስለ ማዳን የእግዚአብሔር ልጅ ከእርሷ ሰው ስለመሆኑ ነገራት ። ስለዚህም የበዓላቶቹን መታሰቢያ እንድናደርግ የቤተ ክርስቲያን መምህራን አባቶቻችን አዘዙን ። እኛም ከጠላታችን ሰይጣን እጅ ያድነን ዘንድ ለመንግሥቱም የተዘጋጀን ያደርገን ዘንድ ክብር ይግባውና በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ፊት ስለ እኛ እንዲማልድ እንለምነው ። ልዕልና ችሎታም ገንዘቡ ለሆነ ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን የዚህም የከበረ መልአክረድኤቱ ከእኛ ጋራ ይኑር ለዘላለሙ አሜን። ወስብሐት ለእግዚአብሔር ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤
አዝበክንፎቹ እኔን በእጁ ሰይፍ ይዟል ሚካኤል ሊረዳኝ ቆሟል እንዳስፈሪ እንደ ንጉሥ ሰራዊት በቀኜ ነው በቀንና በሌሊት ሚካኤል አባቴ ለዚህ እኮ ነው መመካቴ ሚካኤል አባቴ ጋሻ ክብሬ ነው ማለቴ ሚካኤል አባቴ ጎኔ ቆመህ እንዳቆምከኝ ሚካኤል አባቴ እኔ ለዓለም ምስክር ነኝ
አዝልናገር ላውራ ላዚም ልዘምር ከፍ አርጌ ልመስክር መች ይረሳል ልጅነቴ ያሳደገኝ እቅፍ አርጎ በክንፎቹ የከለለኝ ሚካኤል አባቴ እስከዛሬ ያላልኩትን ሚካኤል አባቴ በልቤ ውስጥ ያኖርኩትን ሚካኤል አባቴ ዛሬ ላውራው በአደባባይ ሚካኤል አባቴ እረድቶኛል ከአባት በላይ
አዝከተኛሁበት ከእንቅልፌ አንቅቶ ነጻ አወጣኝ እስሬን ፈቶ በጨለማ በወኅኒው ቤት በእስር አብሮኝ ነበር ጠባቂዬ ሚካኤል ሚካኤል አባቴ በክፋ ቀን ያለ ጎኔ ሚካኤል አባቴ ያልተለየኝ በድካሜ ሚካኤል አባቴ ሰው የሚወድ የማይንቅ ሚካኤል አባቴ በጌታ ፊት የሚያስታርቅ
አዝብርቱና ኃያል ጽኑ ነው ስሙ ሚካኤል ሞገስ የሆነው ምን ይሆናል ሚካኤልን የያዘ ሰው ምግቡ መና ደመና ነው ሚጋርደው ሚካኤል አባቴ የአባቶቼ መንገድ መሪ ሚካኤል አባቴ በእኔም ሕይወት ተዓምር ሰሪ ሚካኤል አባቴ በመንገዴ ቀድሞ ፊቴ ሚካኤል አባቴ ይስበኛል ወደ ርስቴ ዘማሪ ዲያቆን አቤል መክብብ 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️
አዝበክንፎቹ እኔን በእጁ ሰይፍ ይዟል ሚካኤል ሊረዳኝ ቆሟል እንዳስፈሪ እንደ ንጉሥ ሰራዊት በቀኜ ነው በቀንና በሌሊት ሚካኤል አባቴ ለዚህ እኮ ነው መመካቴ ሚካኤል አባቴ ጋሻ ክብሬ ነው ማለቴ ሚካኤል አባቴ ጎኔ ቆመህ እንዳቆምከኝ ሚካኤል አባቴ እኔ ለዓለም ምስክር ነኝ
አዝልናገር ላውራ ላዚም ልዘምር ከፍ አርጌ ልመስክር መች ይረሳል ልጅነቴ ያሳደገኝ እቅፍ አርጎ በክንፎቹ የከለለኝ ሚካኤል አባቴ እስከዛሬ ያላልኩትን ሚካኤል አባቴ በልቤ ውስጥ ያኖርኩትን ሚካኤል አባቴ ዛሬ ላውራው በአደባባይ ሚካኤል አባቴ እረድቶኛል ከአባት በላይ
አዝከተኛሁበት ከእንቅልፌ አንቅቶ ነጻ አወጣኝ እስሬን ፈቶ በጨለማ በወኅኒው ቤት በእስር አብሮኝ ነበር ጠባቂዬ ሚካኤል ሚካኤል አባቴ በክፋ ቀን ያለ ጎኔ ሚካኤል አባቴ ያልተለየኝ በድካሜ ሚካኤል አባቴ ሰው የሚወድ የማይንቅ ሚካኤል አባቴ በጌታ ፊት የሚያስታርቅ
አዝብርቱና ኃያል ጽኑ ነው ስሙ ሚካኤል ሞገስ የሆነው ምን ይሆናል ሚካኤልን የያዘ ሰው ምግቡ መና ደመና ነው ሚጋርደው ሚካኤል አባቴ የአባቶቼ መንገድ መሪ ሚካኤል አባቴ በእኔም ሕይወት ተዓምር ሰሪ ሚካኤል አባቴ በመንገዴ ቀድሞ ፊቴ ሚካኤል አባቴ ይስበኛል ወደ ርስቴ ዘማሪ ዲያቆን አቤል መክብብ 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️
ሰኔ ፲፪ /12/በዚች ዕለት የተባረከና የተመሰገነ በሰማያት ያለ ምሥጢርን ያየ የኢትዮጵያ ንጉሥ ላሊበላ የዕረፍቱ መታሰቢያ ሆነ። ይህንንም ቅዱስ ወላጆቹ በወለዱት ጊዜ እግዚአብሔርን በመፍራትና በበጎ ሥራ ሁሉ አሳደጉት ። አድጎ አካለ መጠን በአደረሰ ጊዜ ታላቅ ወንድሙ ንጉሥ ቀናበት መልእክተኞችንም ልኮ ወደርሱ አስመጣው ምክንያትም ሽቶ ከሦስት ሰዓት እስከ ሰባት ሰዓት እንዲገርፉት አዘዘ ። ከዚህም በኋላ በፊቱ እንዲአቆሙት አዘዘ በአቆሙትም ጊዜ የደረሰበት ጉዳት እንደሌለ አይተው ንጉሡና መኳንንቶቹ ሁሉ አደነቁ የእግዚአብሔር መልአክ ከግርፋት ሠውሮታልና ። ከዚህ በኋላም ወንድሙ ንጉሥ በአንተ ላይ ስለአደረግሁት ክፉ ሥራ ወንድሜ ሆይ ይቅር በለኝ ብሎ ለመነውና እርስ በርሳቸው ታረቁ ። ከዚህ በኋላም እግዚአብሔር መንግሥትን አወረሰው ። ክብር ይግባውና ጌታችንም የፍቅሩን ጽናት በአየ ጊዜ የእግዚአብሔር መልአክ ተገለጠለት ወደ እርሱም ወደ ሰማያት አወጣው ዐሥሩን አብያተ ክርስቲያንም እንዴት እንደሚሠራቸው አሳየው እነርሱም ሥራቸው የየራሳቸው የሆነ ልዩ ነው ተመልሶም መንፈስ ቅዱስ እንደአራቀቀው በአስደናቂ ጥበብ አነፃቸው ። እሊህንም አብያተ ክርስቲያናት አንፆ በፈጸመ ጊዜ መንግሥቱን ለወንድሙ ልጅ አወረሰ ። ከዚህም በኋላ ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ እርሱ መቶ ብዙ ቃልኪዳን ገባለት ቅዱስ ላሊበላም ጌታችንን እያመሰገነ በምድርላይ ወድቆ ሰገደ ። ጌታችንም ሰላምታ ሰጥቶት በክብርና በምስጋና ወደ ሰማያት ዐረገ ። ከዚህም በኋላ ጥቂት ሕማም ታሞ በሰላም አረፈ። ወስብሐት ለእግዚአብሔር ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤
አዝቸሩ ሆይ ለዓይነ ስውር መሪ ቸሩ ሆይ ምርኩዝ መመኪያ ነህ ቸሩ ሆይ አንተን የሚመስል ቸሩ ሆይ ምንም ነገር የለም ቸሩ ሆይ ምሕረትና ፍቅርህ ቸሩ ሆይ ወሰን ወደር የለው ቸሩ ሆይ ሳንወድህ ወደኽን ቸሩ ሆይ ፈልገህ ጠራህን
አዝቸሩ ሆይ ሰምተህ እዳልሰማህ ቸሩ ሆይ አይተህ እንዳላየህ ቸሩ ሆይ ሁሉን ታልፈዋለህ ቸሩ ሆይ ፍቅራዊ አባት ነህ ቸሩ ሆይ አማኑኤል ጌታ ቸሩ ሆይ ቸሩ ፈጣሪያችን ቸሩ ሆይ ውለታህ ብዙ ነው ቸሩ ሆይ ለእኛ የዋልክልን
አዝቸሩ ሆይ በከብቶች ማደሪያ ቸሩ ሆይ በዚያች ትንሽ ግርግም ቸሩ ሆይ ተወልዶ አዳነን ቸሩ ሆይ ጌታ መድኃኔዓለም ቸሩ ሆይ እልል በሉ ሰዎች ቸሩ ሆይ አንድ ላይ ዘመሩ ቸሩ ሆይ ስብሃት ለእግዚአብሔር ቸሩ ሆይ በአርያም በሉ ዘማሪ ቀሲስ ምንዳዬ ብርሃኑ 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️
ሰኔ ፲፩ /11/በዚችው ቀን በጦርነት ድል አድራጊው ከቤተ መንግሥት ወገን የሆነ የመላእክት አርአያ ያለው የከበረ ሰማዕት ገላውዴዎስ የተጋድሎው ፍጻሜ ነው ። ይህ ቅዱስ ምድራዊ መንግሥትንና የዚህን ዓለም ክብር የናቀ ነበረ መልካም ገድልንም ተጋደለ ። የማይጠፋ ሰማያዊ መንግሥትንና የማያልቅ ክብርንም ወረሰ ። የዚህም ቅዱስ የአባቱ ስም አብጥልዎስ ነው እርሱም ለሮም ንጉሥ ለኑማርያኖስ ወንድሙ ነው መልኩም እንደ እስራኤል ያዕቆብ ልጅ እንደ ዮሴፍ እጅግ ውብ ነበር ። ዲዮቅልጢአኖስም ሊሸነግለው ቢሞክር አልደሳካለትም በመጨረሻም ከወዳጁ ፊቅጦር ጋር ወደ ግብፅ ንጉስ እንዲሸነግላቸው ላካቸው። ወደ እንዴናው ገዥ ወደ አርያኖስም በደረሰ ጊዜ አርያኖስ አይቶ ደነገጠ ተነሥቶም እጁን ሳመው እንዲህም ብሎ ለመነው ። ጌታዬ ገላውዴዎስ ሆይ ይህን ሥራ አትሥራ የንጉሥንም ትዕዛዝ አትተላለፍ ። ቅዱስ ገላውዴዎስም እንዲህ ሲል መለሰለት ንጉሥ ያዘዘህን ልትፈፅም እንጂ በነገርህ ልታስተኝ አልተላክሁም አለው ። መኰንኑም እስከሚቆጣ ድረስ እንዲህ እርስበርሳቸው ይነጋገሩ ነበር በመኰንኑም እጅ ጦር ነበረ ቅዱስ ገላውዴዎስንም ወጋው ነፍሱንም ክብርይግባውና በጌታችን እጅ ሰጠ በመንግሥተ ሰማያትም የሰማዕትነት አክሊልን ተቀበለ ። ወስብሐት ለእግዚአብሔር ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤
ሰኔ ፲ /10/በዚች ዕለት ለክርስቲያን ወገኖች በዓለሙ ሁሉ ታላቅ ደስታ ሆነ መላእክትም በሰማያት ደስ ተሰኙባት። በዚች ቀን ዕውነተኛ ምእመን ከሆነ ከንጉሥ ቈስጠንጢኖስ ዘንድ የጣዖት ቤቶች እንዲዘጉ አብያተ ክርስቲያናትም እንዲከፈቱ ትእዛዝ ወጥቷልና። ደስታን የተመላች ያች መልእክት ወደ እስክንድርያ ከተማ እንደ በዛሬዋ ቀን በደረሰች ጊዜ ፈጽሞ ደስ ተሰኙ ወደ ግብጽ አውራጃዎችም ሁሉ ላኳት ምእመናን ሁሉ ስለ ቤተ ክርስቲያን ክብር ከፍ ከፍ ማለት ደስ አላቸው። የጣዖታት ቤቶችንም ዘጓቸው አብያተ ክርስቲያናትንም ከፈቱአቸው እንደ ዛሬም በዚች ዕለት በዓል አደረጉ ይኸውም ቈስጠንጢኖስ በነገሠ በዐሥራ አንድ ዓመቱ ነበር እለእስክንድሮስም ሊቀ ጵጵስና በተሾመባት በመጀመሪያ ዓመት ነበር። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን በእኛ ላይም ይቅርታውና ቸርነቱ ይደረግልን ለዘላለሙ አሜን። ወስብሐት ለእግዚአብሔር ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤
አዝየአንተ መንገላታት ሁልጊዜ ያሳዝነኛል ሲወራ በመስቀል ላይ ሆነህ ያየኸው መከራ ኢየሱስ የህይወት እንጀራ ስብሐት ለከ
አዝስለአላወቁ አንተን የዓለም መድኃኒት መሆንክን መቱት በጭካኔ ብርሃን ፊትህን አፌዙብህ ከጌታችን ስብሐት ለከ
አዝይቻለው ነበር ማጥፋት ክፉ አድራጊዎችን ያን እለት ግን እሱ ለእነሱ ለመነ ድህነት ኢየሱስ አምላከ ምሕረት ስብሐት ለከ
አዝመሐሪ ጌታ አሁንም እንደ ቸርነትህ ብዛት የእኛን በደል ሁሉ ሳትመለከት አድነን ከዳግም ሞት ስብሐት ለከ
አዝበደምህ አድነን እኛን ከክፉ መከራ አውጣን ኃጢአታችንን አስተስርይልን ኢየሱስ መድኃኒታችን ስብሐት ለከ ሊቀ መዘምራን ኪነጥበብ ወ/ቂርቆስ 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️
ሰኔ ፱ /9/በዚችም ዕለት ቅዱስ ሉክያኖስ ከሌሎች አራት ሰማዕታት ጋራ ሰማዕት ሆነ። ይህም ቅዱስ አስቀድሞ የጣዖት ካህን ነበረ የሰማዕታትንም መከራቸውን በእሳት ሲአቃጥሏቸውና ሕዋሳታቸውን ሲቆራርጧቸው ሲሰቅሏቸው ከእሳት ምድጃ ውስጥም ሲጥሏቸው ምንም ምን ጉዳት እንዳልደረሰባቸው በአየ ጊዜ ከዚህ ሥራ የተነሣ አደነቀ ክብር ይግባውና በጌታችን አመነ ያገለግላቸው የነበሩ ጣዖታት ከእሳት ቢጥሏቸው ፈጥነው ይቃጠላሉ እንጂ ይህን ሥራ ሊሠሩ እንደማይችሉ ተረድቷልና። ከዚህ በኋላም በንጉሥ ፊት እኔ ክርስቲያን ነኝ ብሎ ተናገረ። ንጉሡም ወደርሱ አቅርቦ ጣዖት ማምለክን እንዳይተው መከረውና ብዙ ቃል ኪዳኖችን ገባላት። እርሱ ግን አልሰማውም ሥቃዩንም አልፈራም ከዚህም በኋላ ንጉሡ ጽኑዕ ሥቃይን ሊአሠቃየው ጀመረ ዘቅዝቀው እንዲሰቅሉት መንጋጋውንም በደንጊያ እንዲሰብሩት ታላቅ ግርፋትንም እንዲገርፉት አዘዘ። ከዚህ በኋላም አራት ክርስቲያን እሥረኞች ቀረቡና ከእርሱ ጋራ አቆሟቸው ንጉሡም ለአማልክት ዕጣን ዕጠኑ ይህ ካልሆነ ግን ታላቅ ሥቃይን አሠቃያችኋለሁ አላቸው። እነርሱም ለስሕተቱ አልታዘዙለትም በላያቸውም ተቆጥቶ በእሳት ምድጃ ውስጥ ጨመራቸው ያንጊዜ ዝናብ ዘነበ እሳቱንም አጠፋው። ቅዱስ ሉክዮስን ግን እንደ አምላክህ እሰቅልሃለሁ ብሎ በዕንጨት መስቀል ላይ እንዲሰቅሉት አዘዘ በረጃጅም ችንካሮችም ሥጋውን ሁሉ ቸነከሩት ነፍሱንም በእግዚአብሔር እጅ ሰጠ። እነዚያን አራቱን ሰዎችም ራሶቻቸውን በሰይፍ እንዲቆርጡ አዘዘና ቆረጡአቸው የሰማዕትነትንም አክሊል በመንግሥተ ሰማያት ተቀበሉ። ወስብሐት ለእግዚአብሔር ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤
አዝስመጣ ባልጋ ነበረ ተስፋዬም የተሰበረ በእምነትሽ በጠበልሽ ሰው ሆኜ ቆምኩኝ ደጅሽ ልናገር ዝናሽን ላውራ ይደነቅ የአምላክሽ ስራ ተጋድሎሽ የእምነትሽ ፅናት ሆኖኛል የእምነቴ መብራት
አዝደምግባት ከንቱ ብለሽ ለሰማይ ክብር የታጨሽ የእምነቴ ሐሰረ ፍኖት በምልጃሽ አለሁኝ በህይወት የልቡን ለነገረሽ ፈጥኖ ይደርሳል መልስሽ ዘንባባሽ ህይወት ይዘራል የጠራሽ ማን አፍሮ ያውቃል
አዝእርዳታሽ የደረሰለት ያመጣል የልቡን ስለት ላመኑሽ ፈውስሽ ቅርብ ነው ባንቺ አፍሮ የሄደ ማነው የልቡን ለነገረሽ ፈጥኖ ይደርሳል መልስሽ ዘንባባሽ ህይወት ይዘራል የጠራሽ ማን አፍሮ ያውቃል
አዝስመጣ ባልጋ ነበረ ተስፋዬም የተሰበረ በእምነትሽ በፀበልሽ ሰው ሆኜ ቆምኩኝ ደጅሽ ልናገር ዝናሽን ላውራ ይደነቅ የአምላክሽ ስራ ተጋድሎሽ የእምነትሽ ፅናት ሆኖኛል የእምነቴ መብራት። ዘማሪት ሲስተር ሊድያ ታደሠ 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️
ሰኔ ፰ /8/በዚች ቀን አምላክን የወለደች በሁለት ወገን ድንግል የሆነች የእመቤታችን ማርያም የታወቀችው በውኃ ምንጭ ዘንድ ያለች የቤተ ክርስቲያንዋ ቅዳሴ ነው። እርሱም ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከእርሷ ጋር ወደ ግብጽ አገር ተሰዶ ሲመለስ ያፈለቀው የተባረከ መታጠቢያ ነው። ይህም እንዲህ ነው ለጻድቁ ዮሴፍ የእግዚአብሔር መልአክ በሕልም ተገልጾለት ሕፃኑንና እናቱን ይዘህ ወደ ግብጽ አገር ሒድ አለው። ዮሴፍም ነቅቶ ተነሣ ክብር ይግባውና ሕፃኑን ጌታችንን እናቱንና እኅቷ ሰሎሜን ይዞ ወደ ግብጽ አገር ሔዱ በዚያም በውስጧ ባሉ በብዙ አገሮች እየዞሩ ሦስት ዓመት ከስድስት ወር ኖሩ። ሄሮድስም ከሞተ በኋላ የእግዚአብሔር መልአክ ለዮሴፍ ሁለተኛ ተገለጠለት ወደ እስራኤልም አገር ሕፃኑንና እናቱን ይዞ እንዲመለስ አዘዘው። በሚመለሱም ጊዜ ወደ መዓልቃ ደረሱ ከዚያም ወደ መጣርያ አገር ደረሱ ይቺም ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ውኃ ያፈለቀባትና የመታጠቢያ ቦታ የሆነች ናት እርሷም እስከ ዛሬ አለች ሰዎችም ከአገሩ ሁሉ ከየነገዱ ሁሉ መጥተው አምላክን ወደ ወለደችና በድንጋሌ ሥጋ በድንጋሌ ነፍስ ወደ ጸናች ቅድስት ድንግል እመቤታችን ማርያም ይለምናሉ ከተባረከውም የውኃ ምንጭ ታጥበው ከደዌያቸው ሁሉ ይድናሉ በዛሬዪቱ ቀን ከከበረች ቤተ ክርስቲያንም ይባረካሉ። እርሷን እመቤታችንን ለመረጣትና ለወደዳት በሥጋም እናቱ ላደረጋት ስለርሷም ዘመድ ለሆነንና ወደርሱ ላቀረበን ወራሾቹም ላደረገን ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን ለዘላለሙ አሜን። ወስብሐት ለእግዚአብሔር ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤
متاح الآن! بحث تيليغرام 2025 — أهم رؤى العام 
