cookie

ما از کوکی‌ها برای بهبود تجربه مرور شما استفاده می‌کنیم. با کلیک کردن بر روی «پذیرش همه»، شما با استفاده از کوکی‌ها موافقت می‌کنید.

avatar

ዝማሬ ዳዊት - Zimare Dawit

በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን። . ዝማሬ ዳዊት የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ አስተምህሮና ስርዓትን የጠበቁ ትምህርቶች, መዝሙራት እና ወረባትን ከነዜማቸው ለማግኘት ቻናላችንን ይጎብኙ። ለማንኛውም ሀሣብ, ጥቆማ, አስተያየት @zmaredawit_messengerbot ላይ ቢያስቀምጡልን ይደርሰናል

نمایش بیشتر
پست‌های تبلیغاتی
136 529
مشترکین
-4824 ساعت
+5957 روز
+1 44730 روز
آرشیو پست ها
​​❖ ሚያዝያ ፴ ❖ ❖ እንኳን አደረሳችሁ ❖ እንዲህ ኃጢአታችን ጽዋዑን ሞልቶ በተረፈበት በዚህ ዘመን አንዲት ሰዓትም ውድ የሆነች የንስሃ ዕድሜ ናት:: እግዚአብሔር ግን ደግ ነውና ይሔው ሚያዝያን አስፈጸመን:: + ባይገባን ነው እንጂ በዚሕች ወር ውስጥ:- - ሚሊየኖች በደዌ የአልጋ ቁራኛ ሁነዋል:: - ሚሊየኖችም ለንስሃ ሳይበቁ እንዲሁ አንቀላፍተዋል (ሙተዋል):: + እስኪ እርሱ አምላካችን ቀሪዋን ዘመን ደግሞ ለንስሃና ለመልካም ሥራ ባርኮ ይስጠን:: " ቅዱስ ማርቆስ ወንጌላዊ " በዚሕች ዕለት ከ72ቱ አርድእት አንዱ የሆነ: ወንጌላዊ: ሐዋርያ: ሰማዕት: ዘአንበሳና ርዕሰ ሊቃነ ዻዻሳት የተባለ ቅዱስ ማርቆስ በሰማዕትነት ግብፅ ውስጥ ዐርፏል:: + ቅዱስ ማርቆስ እናቱ ማርያም: አባቱ አርስጥቦሎስ ይባላሉ:: በልጅነቱ ኦሪትንና የዘመኑን ጥበብ ሥጋዊ በሚገባ ተምሮ ክርስቶስን ከቤተሰቦቹ ጋር ተከትሏል:: + የመጀመሪያ ስሙ ዮሐንስ ሲሆን ከ120ው ቤተሰብ በእድሜ በጣም ትንሹ (20 ዓመት) እርሱ ነበር:: ለ3 ዓመታት ከጌታ እግር ሥር ተምሮ: በበዓለ ሃምሳ ጸጋ መንፈስ ቅዱስን ተቀብሎ ለሐዋርያዊ አገልግሎት ብዙ ደክሟል:: በተለይ የግብፅና የኢትዮዽያ ቤተ ክርስቲያን አባት ነው:: ክህነትን ያገኘን ከርሱ ነውና:: ቅዱስ ማርቆስ 16 ምዕራፍ ያለውን ወንጌሉን ሲጽፍ ኪሩብ ገጸ አንበሳ በቀኙ: ሊቀ ሐዋርያት በግራው ሆነው ይራዱት ነበር:: ቅዱሱ ክቅዱስ ዻውሎስ: ከበርናባስና ዼጥሮስ ጋር ተጉዟል:: ከብዙ ስቃይና መከራ በኋላ ሰሜን አፍሪካ አካባቢ በዚህ ቀን በ60 ዓ/ም አካባቢ አረማውያን ገድለውታል:: ዳግመኛ በዚህ ቀን የቅዱስ ማርቆስን ወላጆችን እናስባቸው ዘንድ ይገባል:: ❖ ቅዱስ አርስጥቦሎስ (አባቱ) የጌታ ቅን አገልጋይ የነበረ፡፡ ❖ ቅድስት ማርያም (እናቱ) - ከ36ቱ ቅዱሳት አንስት አንዷ: - ጌታችንን ያገለገለች: - ቤቷን ለሐዋርያትና ለጌታ በስጦታ ያበረከተች ቅድስት ናት:: + ቤቷም (ጽርሐ ጽዮን) የመጀመሪያዋ ቤተ ክርስቲያን ስትሆን ይህች ቤት መንፈስ ቅዱስ ወርዶባታል:: የእመቤታችን ግንዘትም ተከናውኖባታል:: ❖ እግዚአብሔር ከሐዋርያዊው ቅዱስ ቤተሰብ በረከትን ያድለን:: ሚያዝያ 30 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት 1.ቅዱስ ማርቆስ ሐዋርያ 2.ቅዱስ አርስጥቦሎስ (አባቱ) 3.ቅድስት ማርያም (እናቱ) ወርኀዊ በዓላት 1.ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቀ መለኮት 2.አባ ሣሉሲ ክቡር 3.ቅዱስ ጐርጐርዮስ ነባቤ መለኮት 4.ቅድስት ሶፍያ ሰማዕት "+ . . . እጅግ ሰዎች ተከማችተው ይጸልዩበት ወደ ነበረው ማርቆስ ወደ ተባለው ወደ ዮሐንስ እናት ወደ ማርያም ቤት መጣ:: ዼጥሮስም የደጁን መዝጊያ ባንኩዋኩዋ ጊዜ ሮዴ የሚሏት አንዲት አገልጋይ ትሰማ ዘንድ ቀረበች:: የዼጥሮስ ድምጽ መሆኑንም ባወቀች ጊዜ ከደስታዋ የተነሳ ደጁን አልከፈተችም:: ነገር ግን ወደ ውስጥ ሮጣ ዼጥሮስ በደጅ ፊት ቆሞ እንዳለ አወራች:: +" (ሐዋ. 12:12-15) ዝክረ ቅዱሳን ወስብሐት ለእግዚአብሔር 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️
نمایش همه...
26
በእርሱ ቁስል እኛ ተፈወስን #ሼር 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️
نمایش همه...
36🕊 2😍 2
ሼር ያድርጉ 🔺
ክርስቶስ በኲር ክርስቶስ በኲር ቀደመ ተንሥዖ እምኲሎሙ ኲሎሙ ሙታን /2/ ወያርእዩ ብርሃነ ወያጸድቆ ለዘይትቀነይ ለጽድቅ ወለሰናይ ወለብዙኃን ኃጢአቶሙ ውእቱ ይደመስስ /2/ ትርጉም፡- በኩር ክርስቶስ የብዙዎችን ኀጢአት ይደመስስ ዘንድ ለእውነትና ለመልካም ነገር የሚገዙትንም ብርሃንን ያሳይ ዘንድ ከሙታን ሁሉ ቀድሞ ተነሣ፡፡ 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️
نمایش همه...
39🕊 2
ለሁሉም ሼር ያድርጉ 🔺
ሰሙነ ትንሳኤ /በዓለ ኀምሳ/ #ሼር 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️
نمایش همه...
44🔥 2
ሼር ያድርጉ 🔺
​​👉 ከትንሣኤ እሁድ በኋላ ያሉ ዕለታት ስያሜ ⚡⚡⚡ሰኞ⚡⚡⚡ 👉ማዕዶት ይባላል፡- ማዕዶት ማለት መሻገር፣ ማለፍ ማለት ነው፡፡ በዚህ ዕለት በፋሲካችን በክርስቶስ ትንሣኤ ከድቅድቅ ጨለማ ወደ ሚደነቅ ብርሃን፣ ከሞት ወደ ሕይወት፣ ከሲኦል ወደ ገነት፣ ከሃሳር ወደ ክብር መሻገራችንን እናስባለን፡፡ ⚡⚡⚡ማክሰኞ⚡⚡⚡ 👉ቶማስ ይባላል፡- በዚህ ዕለት ቶማስ ጌታን አይቶ ማመኑ፤ ጌታዬና አምላኬ ብሎ መመስከሩ ይዘከራል፡፡ ዮሐ. 20፡27-29 ⚡⚡⚡ረቡዕ⚡⚡⚡ 👉አልአዛር ይባላል፡- በዚህ ዕለት ትንሣኤና ሕይወት የሆነው ጌታ ኢየሱስ አልአዛርን ከሞት እንዳስነሳው እናስባለን፡፡ ክርስቶስ የሞትን ስልጣን የሻረ የሕይወት ራስ፤ የመቃብርን ሥርዓት ያጠፋ ትንሣኤ፡ በድልም ያረገ ንጉሥ መሆኑን እንመሰክራለን፡፡ ⚡⚡⚡ሐሙስ⚡⚡⚡ 👉አዳም ሐሙስ ይባላል፡- በዚህ ዕለት ለአዳም የተሰጠው ተስፋ እና የተገባለት ኪዳን እንደተፈጸመ አዳምና ልጆቹ ነጻ እንደወጣን እናስባለን፡፡ ⚡⚡⚡ዓርብ⚡⚡⚡ 👉ቅድስት ቤተክርስቲያን ይባላል፡- በዚህ ዕለት ቤተክርስቲያን በክርስቶስ ሞትና ትንሣኤ ስለመመስረቷ ይሰበካል፡፡ ክርስቶስ ስለ እርሷ ራሱን አሳልፎ ሰጥቶ ቤዛ ሆኖ በደሙ አንጽቶ በትንሣኤው ድል ሰጥቶ እንዳከበራት ይነገራል፡፡ ቤተክርስቲያን ስንል ሕንፃውን ሳይሆን አማኞችን ነው፤ ክርስቶስ ለሕንፃ አልሞተምና፡፡ ⚡⚡⚡ቅዳሜ⚡⚡⚡ 👉ቅዱሳት አንስት ይባላል፡- በዚህ ዕለት ቅዱሳት አንስት የክርስቶስን አካል ሽቶ ለመቀባት ጨለማ አቋርጠው ወደ መቃብር መምጣታቸውና ትንሣኤውንም ቀድመው ማየታቸው ይሰበካል፡፡ ⚡⚡⚡እሁድ⚡⚡⚡ 👉ዳግም ትንሣኤ ይባላል፡- በዚህ ዕለት ክርስቶስ ለሦስተኛ ጊዜ ለደቀመዛሙርቱ ተገልጦ ሰላምን መስበኩ እና ሥልጣንን መስጠቱ ይሰበካል፡፡ #ሼር 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️
نمایش همه...
138🥰 18🔥 2🕊 2
​​​​ለመሆኑ ስለ #ፋሲካ ምን ያህሎቻችን እናውቃለን ✍የፋሲካ ትርጉም በእብራይስጥ <<ፖሳህ>>ሲሆን ትርጉሙ አለፈ ማለት ነው። ✍እስራኤላውያን ከግብፅ ለመውጣት የቻሉት የፋሲካን በግ አርደው ስጋውን በመብላት ደሙን ደሞ እንደታዘዙት በጎበናቸው ላይ በመቀባት የሞት መላእክ ቤታቸው ሳይገባ በማለፉ ነበር። ✍ክርስቶስም ታልፎ የተሠጠው በዚው ወቅት ስለነበር ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ፍሲካችን ክርስቶስ ስለኛ ታርዶአል ብሎ የጻፈልን። ✍እየሱስ ከሰማይ ሰማያት ወርዶ ሰው ተብሎ ክብሩን ጥሎ ስለእኛ የሞተው የፉሲካ በአል ነው እያልን እንድንበላ፣እንድንጠጣ፣እንድንዝናና ነው ብዬ አላምንም። ✍አልፎም አምሽቶ በወይን ጠጅ፣በቢራ፣በድራፍት እየተረጫጩ ማምሸት እንዲሁም ከሴት ጋር የመተኛት ቀን አይደለም። ✍ይሄ ቀን የሀጢያታችን እዳ የተከፈለበት ቀን ነው። #ሼር 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️
نمایش همه...
143😭 3🥰 2🕊 2
ክብርህ ገነነ ክብርህ ገነነ ቅዱስ ስምህ አልተከደነም መልካም ስራህ መቃብር ድንጋይ ያላስቀረህ ኃያል ጌታ ነህ ሞት ማይገዛህ የወይን ስካር እንደለቀቀው እንደ ኃያል ሰው እንደታጠቀው በዝግ መቃብር ጌታ ተነሳ ጠላትን ጥሎ እኛን አነሳ አዝ የሞተልንን እንሰብካለን የተነሳውን እናመልካለን ኃያል ነው በእውነት ታላቅ ነው ጌታ በራሱ ስልጣን ሞትን የረታ አዝ በኩር ነውና የትንሳኤያችን ልባችን ጸና ሞላ ተስፋችን ሞተን አንቀርም እንነሳለን ጥልቁን ተሻግረን እንዘምራለን 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️
نمایش همه...
30🕊 2
የምስራች እንበል የምስራች እንበል (፪) እናመስግን ጌታን በመስቀል ላይ ውሎ ከኃጢአት ላነጻን ሞትን ድል አድርጎ ለሰጠን ትንሳኤን ታላቁ ጌታችን የዓለም መድኃኒት አደረ በመቃብር ሦስት ቀን ሦስት ሌሊት #አዝ ፈጣሪ ሆኖ ሳለ የፍጥረታት ጌታ በሰው ፊት ተዋረደ በሰዎች ተንገላታ #አዝ አሳልፎ ሰጠ ስለኛ ራሱን በመስቀል ተቸንክሮ መረጠ መሞትን #አዝ አይሁዶች ተሞኙ ትንሳኤን ሳያምኑ ሳያምኑ መቃብሩን ወታደር አስጠበቁ #አዝ ዘቦችም ወደቁ ሞትም ተሸነፈ ሰይጣንም ተዋረደ ስልጣኑ ተገፈፈ #አዝ በማለዳ ሄዳ ማርያም መግደላዊት የጌታዋን ትንሳኤ መላዕክት አበሰሯት 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️
نمایش همه...
28
ወምድርኒ ወምድርኒ ትገብር ፋሲካ/2/  ተሐጺባ በደመ ክርስቶስ /4/  ምደር ጸዳች ሐሴት አደረገች /2/  በክርስቶስ ደም በእውነት ታጠበች/4/  💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️
نمایش همه...
69🤬 1
ለሁሉም ሼር ያድርጉ 🔺
👉 ትንሳኤ ክርስቶስ 🎤 በሊቃውንት አንደበት #ሼር 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️
نمایش همه...
41🕊 2😍 1
ሼር ያድርጉ 🔺
ክርስቶስ ሕያው ነው ክርስቶስ ሕያው ነው ሞት ይዞ ያላስቀረው የለም ከመቃብር ተነሰቷል በክብር /2/ በገዛ ፈቃዱ ነፍሱን ስለሰጠ የጨለመው ዓለም በብርሃን ተዋጠ ሲኦል ድል መንሳቱ መውጊያውም ታጠፈ የሞት ስልጣን በሞት ስለተሸነፈ የጥሉ ግድግዳ በሞቱ ፈረሰ የነፍሳችን ቁስል በእርሱ ተፈወሰ ከቶ አላስቀረውም የመቃብር ድንጋይ ኢየሱስ ክርስቶስ ነውና ኤልሻዳይ ዓለሙን እንዲሁ እግዚአብሔር ወዶ የሰው ልጅ ከበረ ዲያብሎስ ተዋርዶ ይገዛን ይነዳን ያስጨንቀን ነበር በሞት ላይ ተራመድን አምላካችን ይክበር ሕይወት ይሰጠን ዘንድ ስለኛ የሞተው ቤዛችን ክርስቶስ ሞትን ድል አረገው የሞተው ተነስቷል በመቃብር የለም ዳግመኛም ይመጣል ሊፈርድ በዓለም 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️
نمایش همه...
42😍 3🥰 2
ሼር ያድርጉ 🔺
ትንሳኤከ ትንሳኤከ ለእለ አመነ /2/ ብርሃነ ከፈኑ ዲቤነ/2/ ትንሣኤህን ለምናምን ለኛ /2/ ብርሃንህን ላክልን ወደኛ /2/ 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️
نمایش همه...
71😍 4😭 2
ለሁሉም ሼር ያድርጉ 🔺
እዩና እመኑ ሰዎች እዩና እመኑ ሰዎች ድንጋዩ ተፈነቃቅሏል ኢየሱስ በኩለ ሌሊት በሀይሉ ሞትን ድል ነስቷል/2/ እልልታ ለዚህ ይገባል ግርግርታ ለዚህ ይገባል የሞት ሀይል ተዋርዷል ዛሬ ሲኦልም ተመሰቃቅሏል/2/ መላዕክቱ ነጭ ለብሰዉ ምስራቹን አበሰሩ ተነስቷል ኢየሱስ ብለው ለዓለም እዲናገሩ/2/ 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️
نمایش همه...
46🥰 3🔥 1
ለሁሉም ሼር ያድርጉ 🔺
Photo unavailableShow in Telegram
#ትንሳኤ ለእናንተ Profile ካዘጋጀናቸው ፎቶዎች ሼር 👉 @ortodoxmezmur
نمایش همه...
40
Photo unavailableShow in Telegram
#ትንሳኤ ለእናንተ Profile ካዘጋጀናቸው ፎቶዎች ሼር 👉 @ortodoxmezmur
نمایش همه...
40
Photo unavailableShow in Telegram
#ትንሳኤ ለእናንተ Profile ካዘጋጀናቸው ፎቶዎች ሼር 👉 @ortodoxmezmur
نمایش همه...
42
Photo unavailableShow in Telegram
#ትንሳኤ ለእናንተ Profile ካዘጋጀናቸው ፎቶዎች ሼር 👉 @ortodoxmezmur
نمایش همه...
68🕊 8🥰 1
Photo unavailableShow in Telegram
''ክርስቶስ ተንስአ እሙታን ▸ በዐቢይ ኃይል ወስልጣን ፤ አሰሮ ለሰይጣን አግአዞ ለአዳም ፤ ሰላም ▸ እምይእዜሰ ፤ ኮነ ▸ ፍስሐ ወሰላም'' ''ክርስቶስ በታላቅ በኃይልና ስልጣን ከሙታን ተነሳ ፤ ሰይጣንን አሰረው አዳምንም ነጻ አወጣው ፤ ስለዚህም ከእንግዲህ ወዲህ ፍፁም ሰላም እና ደስታ ሆነ'' ውድ የዝማሬ ዳዊት ቻናል ቤተሰቦች በሙሉ ፥ እንኳን ለጌታችን ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ ብርሃነ ትንሣኤው በሰላም አደረሳችሁ። በዓሉ የሰላም የፍቅር እና የአንድነት በዓል ይሁንልን አሜን። ዝማሬ ዳዊት On Telegram ሚያዚያ 08|2015 ዓ.ም
نمایش همه...
212🕊 29🥰 18
​​​​የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም 5ቱ ታላላቅ ሀዘናት ክብር ምስጋና ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን በእኔ ምክንያት ካገኙሽ ኅዘናት የትኛው ይበልጣል ብሎ በጠየቃት ጊዜ እመቤታችንም ልጄ ወዳጄ ሆይ ባንተ ምክንያት ካገኙኝ ኅዘናት እነዚህን አምስቱ ይበልጣሉ ብላ እመቤታችን የጠቀሰቻቸው ታላላቅ ኅዘናት የሚከተሉት ሲሆኑ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም እነዚህን ያንችን ኅዘናት እያሰበ የጸለየ ኃጢአቱን ይቅር እለዋለሁ ብሎ ቃል ኪዳን ሰጥቷታል። ፩ኛ - ስምዖን በቤተ መቅደስ ትንቢት በተናገረ ጊዜ። => ስምዖን የተባለው ፦ አረጋዊው ስምኦን ነው የእመቤታችን ሐዘን የሚጀምረው ገና አንድዬ ልጇን ከመውለዷ በስምተኛው ቀን ነው ቤተመቅደስ ይዛው በሄደች ጊዜ አረጋዊው ስምዖን “በአንቺም ደግሞ በነፍስሽ ሰይፍ ያልፋል (ልጅሽ በቀራንዮ ይሞታል)” ሉቃስ 2፥34-35 ብሎ በነገራት ጊዜ ድንግል ማርያም አምርራ አዘነች አለቀሰች። እነሆ፥ የብዙዎች ልብ አሳብ ይገለጥ ዘንድ፥ ይህ በእስራኤል ላሉት ለብዙዎቹ ለመውደቃቸውና ለመነሣታቸው ለሚቃወሙትም ምልክት ተሾሞአል፥ በአንቺም ደግሞ በነፍስሽ ሰይፍ ያልፋል አላት። ሉቃ (2፡34-35) ፪ኛ - ከቤተ መቅደስ ፈልጌህ ባጣሁህ ጊዜ። ወላጆቹም በያመቱ በፋሲካ በዓል ወደ ኢየሩሳሌም ይወጡ ነበር። የአሥራ ሁለት ዓመት ልጅ በሆነ ጊዜ፥ እንደ በዓሉ ሥርዓት ወደ ኢየሩሳሌም ወጡ፤ ቀኖቹንም ከፈጸሙ በኋላ፥ ሲመለሱ ብላቴናው ኢየሱስ በኢየሩሳሌም ቀርቶ ነበር፥ ዮሴፍም እናቱም አላወቁም ነበር። ከመንገደኞች ጋር የነበረ ስለመሰላቸው የአንድ ቀን መንገድ ሄዱ፥ ከዘመዶቻቸውም ከሚያውቋቸውም ዘንድ ፈለጉት፤ ባጡትም ጊዜ እየፈለጉት ወደ ኢየሩሳሌም ተመለሱ። ከሦስት ቀንም በኋላ በመምህራን መካከል ተቀምጦ ሲሰማቸውም ሲጠይቃቸውም በመቅደስ አገኙት፤ የሰሙትም ሁሉ በማስተዋሉና በመልሱ ተገረሙ። ባዩትም ጊዜ ተገረሙ እናቱም። ልጄ ሆይ፥ ለምን እንዲህ አደረግህብን? እነሆ፥ አባትህና እኔ እየተጨነቅን ስንፈልግህ ነበርን አለችው። ሉቃ (2፡41-48) ፫ኛ - በጲላጦስ አደባባይ በገረፉህ ጊዜ። በዚያን ጊዜም ጲላጦስ ኢየሱስን ይዞ ገረፈው። ወታደሮችም ከእሾህ አክሊል ጐንጕነው በራሱ ላይ አኖሩ ቀይ ልብስም አለበሱት፤ እየቀረቡም። የአይሁድ ንጉሥ ሆይ፥ ሰላም ለአንተ ይሁን ይሉት ነበር፤ በጥፊም ይመቱት ነበር። ጲላጦስም ደግሞ ወደ ውጭ ወጥቶ። እነሆ፥ አንዲት በደል ስንኳ እንዳላገኘሁበት ታውቁ ዘንድ እርሱን ወደ ውጭ አወጣላችኋለሁ አላቸው። ኢየሱስም የእሾህ አክሊል ደፍቶ ቀይ ልብስም ለብሶ ወደ ውጭ ወጣ። ዮሐ (19፡1-5) ፬ኛ - በዕለተ ዓርብ በሰቀሉህ ጊዜ። ኢየሱስንም ይዘው ወሰዱት፤ መስቀሉንም ተሸክሞ በዕብራይስጥ ጎልጎታ ወደ ተባለው የራስ ቅል ስፍራ ወደሚሉት ወጣ። በዚያም ሰቀሉት፥ ከእርሱም ጋር ሌሎች ሁለት፥ አንዱን በዚህ አንዱን በዚያ ኢየሱስንም በመካከላቸው ሰቀሉ። ጲላጦስም ደግሞ ጽሕፈት ጽፎ በመስቀሉ ላይ አኖረው፤ ጽሕፈቱም። የአይሁድ ንጉሥ የናዝሬቱ ኢየሱስ የሚል ነበረ። ኢየሱስም የተሰቀለበት ስፍራ ለከተማ ቅርብ ነበረና ከአይሁድ ብዙዎች ይህን ጽሕፈት አነበቡት፤ በዕብራይስጥና በሮማይስጥ በግሪክም ተጽፎ ነበር። ስለዚህ የአይሁድ ካህናት አለቆች ጲላጦስን እርሱ። የአይሁድ ንጉስ ነኝ እንዳለ እንጂ የአይሁድ ንጉሥ ብለህ አትጻፍ አሉት። ጲላጦስም። የጻፍሁትን ጽፌአለሁ ብሎ መለሰ። ዮሐ. (19፡17-2 ፭ኛ- ዮሴፍና ኒቆዲሞስ ገንዘው ወደ አዲስ መቃብር ባወረዱህ ጊዜ። ከዚህም በኋላ አይሁድን ስለ ፈራ በስውር የኢየሱስ ደቀ መዝሙር የነበረ የአርማትያስ ዮሴፍ የኢየሱስን ሥጋ ሊወስድ ጲላጦስን ለመነ፤ ጲላጦስም ፈቀደለት። ስለዚህም መጥቶ የኢየሱስን ሥጋ ወሰደ። ደግሞም አስቀድሞ በሌሊት ወደ ኢየሱስ መጥቶ የነበረ ኒቆዲሞስ መቶ ንጥር የሚያህል የከርቤና የእሬት ቅልቅል ይዞ መጣ። የኢየሱስንም ሥጋ ወስደው እንደ አይሁድ አገናነዝ ልማድ ከሽቱ ጋር በተልባ እግር ልብስ ከፈኑት። በተሰቀለበትም ስፍራ አትክልት ነበረ፥ በአትክልቱም ማንም ገና ያልተቀበረበት አዲስ መቃብር ነበረ።ስለዚህ መቃብሩ ቅርብ ነበረና ስለ አይሁድ ማዘጋጀት ቀን ኢየሱስን በዚያ አኖሩት። ዮሐ (19፡38-42) እንዚህን አምስቱን የእመቤታችን ሐዘናት እያሰበ ያዘነ ዝክሯን የዘከረ በአማላጅነቷ የታመነ ዋጋው ከቶ አይጠፋበትም፡፡ ቅድስት ሆይ ለምኝልን ቅድስት ሆይ ለምኝልን ቅድስት ሆይ ለምኝልን አሜን ወስብሐት ለእግዚአብሔር 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️
نمایش همه...
😭 77 12
08/08/15 ዓ.ም ዕለተ ትንሣኤሁ ለክርስቶስ በዕለቱ ቅዳሴ ሰዓት የሚነበ መልዕክታት ወንጌልና ምስባክ፡፡ ዲ/ን - ቆሮ15÷20-41 ን/ዲ - 1ጴጥ 1÷1-13 ን/ካ - ግብ፡ሐዋ 2÷22-37 የዕለቱ_ምስባክ:- መዝ 117÷24 ዛቲ ዕለት እንተ ገብረ እግዚአብሔር ። ንትፈሣሕ ወንትሐሠይ ባቲ። ኦ እግዚኦ አድኅንሶ። ትርጒም፦ እግዚአብሔር የሠራት ቀን ይህች ናት። ሐሴትን እናድርግ በእርሷም ደስ ይበለን። አቤቱ እባክህ አሁን አድን። የዕለቱ ወንጌል፦ ዮሐ፥20 ÷1- 19 ቅዳሴ፦ ዘዲዮስቆሮስ 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️
نمایش همه...
39🕊 7🤬 1
ምስባክ ዘትንሣኤ (ዘማሕሌት) መዝ 77÷65 ወተንሥአ እግዚአብሔር ከመ ዘንቃህ እምንዋም። ወከመ ኃያል ወኅዳገ ወይን። ወቀተለ ፀሮ በድኅሬሁ። 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️
نمایش همه...
13
Photo unavailableShow in Telegram
የማርያም ለቅሶ ልጄ ወዳጄ ሆይ ለእኔ ወዮታ አለብኝ ... በጦር ሲወጉህና ሲገድሉህ ዓይኖቼ ከምያዩ ይልቅ ልጄ ወዳጄ ሆይ ነፍሴን ከስጋዬ ትለያት ዘንድ እማልድሃለሁ። ልጄ ወዳጄ ሆይ ይህ በራስህ የተቀዳጀኸው የእሾህ አክሊል ምነው እኔ በተቀዳጀሁትና የመከራህ ተሳታፊ በሆንኩ። ልጄ ወዳጄ ሆይ አንተን በእሱ ላይ በሰቀሉበት መስቀልህ በሰላም እሰናበትሃለሁ። ልጄ ወዳጄ ሆይ አይሁድ መራቃቸውን በተፉበት ብርሃንንም በተሞላ ፊትህ እሰናበትሃለሁ: ንጉስ ሆይ በሁለት ወንበዴዎች መካከል እርቃኑን ለቆመው አካልህ እጅ እየነሳሁ እሰናበትሃለሁ። ልጄ ወዳጄ ሆይ እጣ በተጣጣሉበት ክብር ልብስህ እጅ እየነሳሁ እሰናበትሃለሁ። ልጄ ወዳጄ ሆይ አክሊለ ሶክክን ለተቀዳጀ እራስህ ሰላም እያልኩና እጅ እየነሳሁ እሰናበትሃለሁ። ምንጭ ግብረ ሕማማት 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️
نمایش همه...
102😭 63🕊 9
👉 ድርሳነ ማሕየዊ ዘቀዳሚት 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️
نمایش همه...
17
​​​​👉 ቅዳሜ ቀዳም ስዑር ትባላለች ፦ ይህች እለት ከድሮ በተለየ መልኩ የጌታችንን መከራ በማሰብ በጾም ታስባ ስለምትውል የተሻረች ቅዳሜ ይባላል። ለምለም ቅዳሜ ይባላል፡- ካህናቱ ለምእመናን ለምለም ቀጤማ የሚያድሉበት ዕለት በመሆኑም ለምለም ቅዳሜ ይባላል። ምዕመናንም ይህንን ለምለም ቀጤማ እስከ ትንሣኤ ለሊት በራሳቸው ላይ ያስሩታል። ቅዱስ ቅዳሜ ይባላል፡- ቅዱስ የሆነው እግዚአብሔር በጥንተ ተፈጥሮ ፍጥረታትን አከናውኖ ያረፈበት ቀን ሲሆን በዘመነ ሐዲስ ደግሞ የማዳን ስራውን ሁሉ ፈጽሞ በሥጋው በመቃብር ሲያርፍ በነፍሱ ወደ ሲኦል ወርዶ ሲኦልን በርብሮ ባዶዋን ሲያስቀራት በዚያ የነበሩትን ነፍሳት የዘላለም ዕረፍትን ያወረሰበት ዕለት ስለሆነ ቅዱስ ቅዳሜ ይባላል። ዝርዝሩን - https://youtu.be/NMHnlH0YLEE 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️
نمایش همه...
45🕊 6
ጌታ ሆይ ጌታ ሆይ አይሁድ አማጽያን ሰቀሉህ ወይ  የዓለም መድኃኒት የዓለም ሲሳይ ሰቀሉህ ወይ /2/  የአዳም በደል አደረሰህ አንተን ለመሰቀል  የሔዋን ስህተት አበቃህ ለሞት ቸሩ አባት/2/ አዝ ንጹሕ ክርስቶስ ሆንክ ወንጀለኛ ብለህ ስለእኛ  መሰቀል አሸክመው አስረው ገፈፉህ እያዳፉህ/2/  አዝ እጅና እግርህን በብረት ተመታ የዓለም ጌታ  የሾህ አክሊል ደፍተህ ጎንህን ተወጋህ አልፋ ኦሜጋ/2/ አዝ ግብዞች እንደራሳቸው መስሏቸው  ምራቅ እየተፉ በፊትህ ቀለዱ አንተን ሊጎዱ/2/ አዝ  በመሰቀል ላይ ተጠማሁ ስትል ታላቅ በደል  ሀሞትና ከርቤ ሰጡህ ቀላቅለው ጠጣ ብለው/2/ አዝ ይቅር ባይ ግልጽ በደላችንን ሁሉ ሳታይ  አንተ ይቅር በለን በእኛ ሳትከፋ እንዳንጠፋ /2/  💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️
نمایش همه...
😭 56 25
ለሁሉም ሼር ያድርጉ 🔺
#በዕጸ_መስቀል_ላይ በዕጸ መስቀል ላይ በዚያ አደባባይ  አምላክ ሆይ ጌታ ሆይ ተንገላታህ ወይ  አምላክ ሆይ ጌታ ሆይ መከራ አየህ ወይ  #አዝ መስቀል አስይዘው ኪራያላይሶን  ወደ ጎልጎታ   " " ሲገራፉ ሲዳፉ  " " ስትንገላታ  " " #አዝ ያንን አቀበት ኪርያላይሶን  ያንን ዳገት  " " ጀርባህ ተገርፎ  " " ስትቃትት  " " #አዝ አንተን እያዩ ኪርያላይሶን  ሴቶች ሲያለቅሱ  " " እናቶች ቀርበው  " " ላብህን ዳበሱ  " " #አዝ መስቀል አስይዘው ኪያላይሶን  እንዲያ ሲያዳፉህ  " " የቀሬናው ሰው  " " ስምኦን አገዘው  " " 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️
نمایش همه...
😭 19 11🔥 3🕊 1
ንሴብሖ ንሴብሖ /2/ ለእግዚአብሔር /2/  ስቡሐ ዘተሰብሐ /4  እናመስግነው /2/ እግዚአብሔርን /2/  ምስጉን ነው የተመሰገነ /4/  ባህሩን ተሻግረን ወንዙ ደረቅ ሆነ በጠላታችን ላይ ድሉ የኛ ሆነ ከባርነት ቀንበር ፍፁም ነፃ ወጣን ህይወት የሚሰጠን መና ነው ምግባችን አስፈሪ ነው ያልነው ብዙ ነገር ነበር ሁሉንም አለፍነው አምላካችን ይክበር ጉልበታችን ቢዝል መከራም ቢበዛ ሃይላችን ጌታ ነው የዓለም ቤዛ ከአለት ላይ ውሃ ፈልቆ እንደጠጣነው ይህን ታላቅ አምላክ ኑ እናመስግነው ሰዎች ደስ ይበለን ሕይወታችን ድኗል ሰይጣን ጠላታችን አፍሮ ተመልሷል አስፈሪ ነው ያልነው ብዙ ነገር ነበር ሁሉንም አለፍነው አምላካችን ይክበር ጉልበታችን ቢዝል ፈተናው ቢበዛ ሃይላችን ጌታ ነው የዓለሙ ቤዛ 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️
نمایش همه...
47🕊 9🔥 1
ለሁሉም ሼር ያድርጉ 🔺
የማኅበረ ቅዱሳን ሰብሳቢ ሊቀ ትጉሃን ቀሲስ ዶ/ር ሙሉጌታ ሥዩም እና የማኅበሩ ዋና ጸሐፊ መ/ር ዋሲሁን በላይ በትናንትናው ዕለት ሚያዚያ 24 ቀን 2016 ዓ.ም በመንግሥት የጸጥታ አካላት ከመኖሪያ ቤታቸው ተወስደው ሜክሲኮ በሚገኘው የፌደራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ቢሮ እንደሚገኙ አሳውቀን ነበር። በዛሬው ዕለት ሚያዚያ 25 ቀን 2016 ዓ.ም ወደ ቤታቸው መመለሳቸውን እየገለጽን፣ በሂደቱ ጉዳዩን በመረዳት አፋጣኝ ምላሽ የሰጡንን የመንግሥት የጸጥታ አካላት እናመሰግናለን። በተጨማሪም በትዕግሥት ስትከታተሉና በጸሎት ስታስቡ ለነበራችሁ አባቶች፣ ምእመናን እና የማኅበረ ቅዱሳን አባላት እያመሰገንን፣ በዓሉ የሰላምና የበረከት እንዲሆንላችሁ እንመኛለን። ማኅበረ ቅዱሳን!
نمایش همه...
66🕊 7
Photo unavailableShow in Telegram
ክርስቲያኖች ሁላችሁ ኑ እናፅናናት "ክርስቲያን ሁላችሁ ኑ ድንግል ማርያምን እናፅናናት፤ በልጇ ስቃይ ሆድ ብሷታልና፥ እንባን ከመጠጧ ጋር አመድንም ከምግቧ ጋር ቀላቅላለችና። የተወደደ ልጇ በመስቀል ተሰቅሎ ስታየው አንድ ጊዜ ከእሾህ አንድ ጊዜ ከድንጋይ ላይ እየወደቀች አለቀሰች። ወንድም የሌለው አንድ ልጇ እንዲህ ሲሰቃይ የወለደ አንጀቷ እንደምን ይቻል? ምንስ ብላ ትፅናና? ያፅናኗት ዘንድ ሊቃነ መልአክት በዙሪያዋ መጡ ግን አልተፅናናችም፤ ልጄ እያለ የሚጠራት አባቷ ዳዊትም መጣ ድንግል ግን እርቃኑን የተሰቀለው ልጇን እያየች መሪር እንባን አፈሰሰች። ስለ ልጇ ብዙ መከራ አሳልፋለች፥ ያሁኑ የልጇ መከራ ግን ከሀዘኖች ሁሉ የከፋ ሆነባት። አንድ ልጇ እየሞተ ምን ብላ ትፅናና ? የእናቱን አለመፅናናት ያየ ጌታ ኢየሱስ ከሃዘን ብዛት እንዳትሞት ያፅናናት ዘንድ ቁጽረ ገፅ ለተባለው ለዮሐንስ እነኋት እናትህ አለው። በእውነት እነኋት እናታችን በልጇ ስቃይ ሆድ ብሷታልና ክርስቲያን ሁላችሁ ኑ እናፅናናት።" 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️
نمایش همه...
89😭 47🥰 2🕊 1
​​#አዘነች_ድንግል_አለቀሰች አዘነች ድንግል አለቀሰች ፍጹም አምርራ በአንድ ልጇ ምክንያት ደርሶባት መከራ በአንድ ልጇ ምክንያት ደርሶባት መከራ/፪/ #አዝ በመንጻቱ ወር በዓርባኛው ቀን ሥምዖን አረጋዊ ታቀፈ እና ጌታን ትንቢት ተናገረ ተገልጾለት ሞቱ በነፍስሽ ሠይፍ ያልፋል አንቺም እናቲቱ ይኽንን መከራ ሲሠማ ጆሮዋ አምርራ አለቀሰች አልቆም አለ ዕንባዋ #አዝ በአሥራ ሁለት ዓመቱ ለማክበር በዓል በኢየሩሳሌም ቢገኝ አማኑኤል ሲጠይቅ ሲሠማ በቤተ መቅደሱ የኦሪት ካኅናት ሲደነቁ በእርሱ እስከ ሦስት ቀን ድረስ ብትልጣው ፈልጋ ልቧ ተሠበረ በሐዘን አለንጋ #አዝ ጠዋት በማለዳ በጲላጦስ ደጅ ሲጸናበት አይታ የጨካኞች እጅ ርቃኑን አድርገው ያለ አንዳች ጥፋት ከግንድ ጋር አስረው ጀርባውን ሲገርፉት እንዴትስ አታለቅስ እንዴት አታነባ ሲገርፉት ሲያዳፉት ልጇን እንደ ሌባ #አዝ የዓለሙን ፈጣሪ የዓለሙን ዳኛ ንጹሑን ጌታ መሥሏቸው ቀማኛ እጁን እና እግሮቹን በችንካር ወጥረው በወንበዴ መሐል ሠቅለውን ብታየው ድንግል አለቀሰች አልቻለች መጽናናት ዕንባዋ ወረደ እንደ ክረምት ጅረት #አዝ ዮሴፍ ኒቆዲሞስ በአንድ ሲማከሩ ቅዱሥ ሐያል ብለድ ገንዘው ሊቀብሩ በአዲስ መቃብር በአሥራ አንደኛው ሠዓት ሥጋውን አኑረው በድንጋይ ቢዘጉት እያለች ዐነባች አንድ ልጄ እኮ ነው ከእርሱ የሚቀድም ተከታይ የሌለው። 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️
نمایش همه...
😭 14 7🔥 1
Photo unavailableShow in Telegram
"ኢየሱስም በታላቅ ድምፅ ጮኾ። አባት ሆይ፥ ነፍሴን በእጅህ አደራ እሰጣለሁ አለ። ይህንም ብሎ ነፍሱን ሰጠ።" (የሉቃስ ወንጌል 23:46) "ኢየሱስም ሁለተኛ በታላቅ ድምፅ ጮኾ ነፍሱን ተወ።" (የማቴዎስ ወንጌል 27:50) "ኢየሱስም በታላቅ ድምፅ ጮኸ ነፍሱንም ሰጠ።" (የማርቆስ ወንጌል 15:37) "ኢየሱስም ሆምጣጤውን ከተቀበለ በኋላ። ተፈጸመ አለ፥ ራሱንም አዘንብሎ ነፍሱን አሳልፎ ሰጠ።" (የዮሐንስ ወንጌል 19:30) 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️
نمایش همه...
😭 84 18🕊 1
ዘጠኝ ሰዓት ሲሆን ዘጠኝ ሰዓት ሲሆን አባት ሆይ በመስቀል ሆነህ አባት ሆይ ድምጽህን በማሰማት አባት ሆይ ነፍስህን ሰጠህ አባት ሆይ ከዋክብተ ሰማይ በሙሉ ረገፉ ጨረቃና ፀሐይ ደምን አጎረፉ ብርሃናት ጨለሙ ጠፍተው ተለያዩ ሥጋህን በመስቀል ተገልጦ ስላዩ #አዝ ጌታችን ክርስቶስ በመስቀል ላይ ሳለ አሰምቶ ጮኸ ተጠማሁ እያለ ማርና ወተትን ለሚመግበው ሐሞት አመጡለት ይቅመሰው ብለው #አዝ አካሉ ሲወጋ ውኃ ደም ፈሰሰ በምድር ተረጭቶ ዓለምን ቀደሰ የእሥራኤል ሴቶች ዋይ ዋይ ሲሉልህ ለእነርሱ አዘንክ እንጂ ለአንተስ አላሰብክም #አዝ እናትህ ስታለቅስ በመስቃል ሥር ሆና ዮሐንስን ሰጠህ ጠብቆ እንዲያፅናና መላእክትም ታዩ አጋንንትም ሸሹ የአይሁድ ሠራዊት ፈርተው ተረበሹ ሊቀ-መዘምራን ኪነ-ጥበብ ወልደ-ቂርቆስ 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️
نمایش همه...
27😭 22🕊 3
Photo unavailableShow in Telegram
ዓርብ ዘጠኝ ሰዓት በዚህች ዕለት በዚህች ሰዓት የዓለም መድኃኒት ጌታችን ኢየሱስ ለአዳም ልጆች ድኅነት በመስቀል ላይ ሆኖ በታላቅ ድምፅ ጮሆ “ኤሎሄ ኤሎሄ” ብሎ “ሁሉ ተፈጸመ” በማለት በባሕርይው ሞት የሌለበት አምላክ ነፍሱን በፈቃዱ ለሞት አሳልፎ ሰጠ። “ቀትር በሆነ ጊዜም በስድስት ሰዓት ፀሐይ ጨለመ፤ እስከ ዘጠኝ ሰዓት ድረስም ዓለም ሁሉ ጨለማ ሆነ። ፀሐዩም በጨለመ ጊዜ የቤተ መቅደሱ መጋረጃ ከላይ እስከ ታች ከመካከሉ ተቀደደ። ያን ጊዜ ጌታችን ኢየሱስ ድምፁን ከፍ አድርጎ፥ “አባት ሆይ፥ ነፍሴን በአንተ እጅ አደራ እሰጣለሁ”’ ብሎ ጮኸ፤ ይህንም ብሎ ነፍሱን ሰጠ።” (ሉቃ.፳፫÷፵፬-፵፮)
نمایش همه...
😭 110 18
መስቀል ላይ ያየሁት ፍቅር መስቀል ላይ ያየሁት ፍቅር (2) ይቀሰቅሰኛል ለስሙ እንድዘምር (2) ፊቱን እየፀፉት/ እየተንገላታ (2) በጦር እየወጉት /ይሰጣል ይቅርታ (2) እነርሱ እየጠሉት/ እርሱ ይወዳቸዋል (2) አስረው ሲጎትቱት/ ይከተላቸዋል (2) #አዝ ፃድቁን ሃጥእ ነው/ እውነትን ሃሰት (2) እያሉ ሲጮሁ /ይሰቀል ይሙት (2) እየመረመረው/ ፍጡር ፈጣሪን (2) ክርስቶስን አስሮ/ ፈታው በርባንን (2) #አዝ ጀርባውን ሲገርፉት በሚያቃጥል ጅራፍ በምህረት ያዛቸው በይቅርታው እቅፍ (2) ጨክነው ሲያጠጡት መራራ ሃሞት (2) ደሙን አፈሰሰ ጎኑን ሲወጉት (2) #አዝ ግምጃን አለበሱት/ ቀሚሱን ገፈው (2) በራሱም አኖሩ/ እሾህ ጎንጉነው (2) የአይሁድ ንጉስ ሆይ/ እያሉ ዘበቱ (2) ለህይወት ሆናቸው/ የክርስቶስ ሞቱ (2) ሊቀ-መዘምራን ዲያቆን ቴዎድሮስ ዮሴፍ 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️
نمایش همه...
28😍 6
ለሁሉም ሼር ያድርጉ 🔺
•✞ #አልፋና_ኦሜጋ ✞• አልፋና ኦሜጋ ፈጣሪ የሆንክ (2) በከሃዲዎች እጅ ተይዘክ ቀረብክ (2) ተገፋህ ተደፋህ በጥፊ ተመታህ እየደበደቡ ክርስቶስ ሆይ አሉህ ጽድቅን ስለሰራህ በወንጀል ከሰሱህ ለአዳም ቤዛ ብለህ ብዙ ተንገላታህ #አዝ••• ቅዱሳን እጆችህ የፍጥኝ ታስርው እንደ በግ ተጎትተህ ልትመራቸው የትም ቦታ ያለህ ሁሉን የምታውቅ ፊትህን ሸፈኑት ለመመጻደቅ #አዝ••• በአውደ ምኩና ከጲላጦስ ዘንድ አሳልፈው ሰጡ አጋልጠው ለፍርድ ከሃና ቀያፋ ከመሳፍንቱ ደጅ ከነሄሮድስ ዘንድ አቀረቡ በአዋጅ #አዝ••• ግርፋት ሕማሙ አልበቃ ብሎህ በመስቀል ላይ ልትውል ተፈረደብህ ሳዶርና አላዶር ዳናትና አዴራ ተፈልገው መጡ ለችንካር በተራ #አዝ••• የሰላም ባለቤት ደረትህ ተወጋ ሊያያዝ በችንካር እጅህ ተዘረጋ ግፈኞች አይሁዶች ባንተ ላይ ቀለዱ ምራቅን ተፉብህ እራስህን ሊጎዱ 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️
نمایش همه...
25🕊 3🥰 1
​​​​👉 ሰባቱ የመስቀሉ ቃላት 1. አምላኬ አምላኬ ለምን ተውኸኝ (ማቴ 27፡46) 2. አባት ሆይ የሚያደርጉትን አያውቁምና ይቅር በላቸው (ሉቃ 23፡34) 3. ዛሬ በገነት ከእኔ ጋር እንድትኖር በእውነት እነግርሃለሁ (ሉቃ 23፡43) 4. እነሆ ልጅሽ አነኋት እናትህ (ዮሐ 19፡26-27) 5. ተጠማሁ (ዮሐ 19፡28) 6. አባት ሆይ ነፍሴን በእጅህ አደራ እሰጣለሁ (ሉቃ 23፡46) 7. የተጻፈው ሁሉ ደረሰ ተፈጸመ አለ (ዮሐ 19፡30) 👉 ሰባቱ ተዐምራት ጌታ እኛን ለማዳን በመስቀል ላይ በተሰቀለ ጊዜ የተፈጸሙ ተዐምራት 1. ፀሐይ ጨልሟል 2. ጨረቃ ደም ሆነ 3. ከዋክብት ረገፉ 4. ዐለቶች ተሠነጠቁ 5. መቃብራት ተከፈቱ 6. ሙታን ተነሡ 7. የቤተ መቅደስም መጋረጃ ለሁለት ተቀደደ 👉 አምስቱ ችንካሮች ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተቸነከረባቸው አምስቱ ችንካሮች 1. ሳዶር ፦ በሚባል ችንካር ቀኝ እጁን ቸነከሩት 2. አላዶር ፦ በሚባል ችንካር ግራ እጁን ቸነከሩት 3. ዳናት ፦ በሚባል ችንካር ሁለት እግሩን ቸነከሩት 4. አዴራ ፦ በሚባል ችንካር ማሀል ልቡን ቸነከሩት 5. ሮዳስ ፦ በሚባል ችንካር ደረቱን ቸነከሩት 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️
نمایش همه...
45😭 23🔥 1🥰 1
Photo unavailableShow in Telegram
ዓርብ ስድስት ሰዓት በዚህች ዕለት በዚህች ሰዓት ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን አይሁድ መስቀል አሸክመው፣ ከለሜዳ አልብሰው፣ ምራቅ እየተፉ ከተዘባበቱበት በኋላ ከለሜዳውን ገፍፈው፣ ልብሱን አልብሰው፣ እየገፉ፣ እያዳፉ ቀራንዮ አደባባይ አደረሱት፤ ልብሱንም ገፍፈው ራቁቱን በሁለት ወንበዴዎች መካከል በመስቀል ላይ ሰቀሉት። “ከዚህም በኋላ የመስፍኑ ጭፍሮች ጌታችን ኢየሱስን ተቀብለው ወደ ፍርድ ሸንጎ ወሰዱት፤ ጭፍራውንም ሁሉ ወደ እርሱ ሰበሰቡ። ልብሱንም ገፈው ቀይ ልብስ አለበሱት። የእሾህም አክሊል ጎንጉነው በራሱ ላይ አቀዳጁት፤ በቀኝ እጁም ዘንግ አሲያዙት፤ በፊቱም ተንበርክከው፥ “የአይሁድ ንጉሥ ሆይ፥ ሰላም ለአንተ ይሁን” እያሉ ተዘባበቱበት፤ በላዩም ተፉበት፤  ዘንጉንም ነጥቀው ራሱን መቱት። ከተዘባበቱበትም በኋላ ቀዩን ልብስ ገፍፈው ልብሱንም አለበሱት፤ ሊሰቅሉትም ወሰዱት።” (ማቴ ፳፯÷፳፯-፴) “በወሰዱትም ጊዜ የቀሬና ሰው ስምዖንን ከዱር ሲመለስ ያዙት ከጌታችን ከኢየሱስ በስተኋላ መስቀሉን አሸከሙት።” (ሉቃ.፳፫÷፳፮) “ከዚህ በኋላ ሊሰቅሉት አሳልፎ ሰጣቸው፤ ጌታችን ኢየሱስንም ተቀብለው ወሰዱት። መስቀሉንም ተሸክሞ በዕብራይስጥ ጎልጎታ ወደ ተባለው ቀራንዮ ወደሚባል ቦታ ወጣ። በዚያም ሰቀሉት፥ ከእርሱም ጋር አንዱን በቀኝ፥ አንዱንም በግራ አድርገው ሌሎች ሁለት ወንበዴዎችን ሰቀሉ፤ ኢየሱስንም በመካከላቸው ሰቀሉ። ጲላጦስም ጽሕፈት ጽፎ በመስቀሉ ላይ አኖረ፤ ጽሕፈቱም። ‘የአይሁድ ንጉሥ የናዝሬቱ ኢየሱስ’ የሚል ነበር።” (ዮሐ.፲፱÷፲፮-፲፱)
نمایش همه...
😭 98 5😍 1
Photo unavailableShow in Telegram
(የሉቃስ ወንጌል ምዕ. 23) 25፤ ያንን የለመኑትንም፥ ስለ ሁከት ሰውንም ስለ መግደል በወኅኒ ታስሮ የነበረውን አስፈታላቸው፥ ኢየሱስን ግን ለፈቃዳቸው አሳልፎ ሰጠው። 26፤ በወሰዱትም ጊዜ ስምዖን የተባለ የቀሬናን ሰው ከገጠር ሲመጣ ይዘው ከኢየሱስ በኋላ መስቀሉን እንዲሸከም ጫኑበት። 27፤ ዋይ ዋይ ከሚሉና ሙሾ ከሚያወጡ ሴቶችና ከሕዝቡ እጅግ ብዙዎች ተከተሉት። 28-29፤ ኢየሱስ ግን ወደ እነርሱ ዘወር ብሎ እንዲህ አለ። እናንተ የኢየሩሳሌም ልጆች፥ ለእኔስ አታልቅሱልኝ፤ ዳሩ ግን። መካኖችና ያልወለዱ ማኅፀኖች ያላጠቡ ጡቶችም ብፁዓን ናቸው የሚሉበት ጊዜ እነሆ ይመጣልና ለራሳችሁና ለልጆቻችሁ አልቅሱ። 30፤ በዚያን ጊዜ ተራራዎችን። በላያችን ውደቁ፥ ኮረብቶችንም። ሰውሩን ይሉ ዘንድ ይጀምራሉ፤ 31፤ በእርጥብ እንጨት እንዲህ የሚያደርጉ ከሆኑ፥ በደረቀውስ እንዴት ይሆን? 32፤ ሌሎችንም ሁለት ክፉ አድራጊዎች ደግሞ ከእርሱ ጋር ይገድሉ ዘንድ ወሰዱ። 33፤ ቀራንዮም ወደሚባል ስፍራ በደረሱ ጊዜ፥ በዚያ እርሱን ክፉ አድራጊዎቹንም አንዱን በቀኝ ሁለተኛውንም በግራ ሰቀሉ። 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️
نمایش همه...
😭 27 1
Photo unavailableShow in Telegram
(የሉቃስ ወንጌል ምዕ. 23) 24፤ ጲላጦስም ልመናቸው እንዲሆንላቸው ፈረደበት። 25፤ ያንን የለመኑትንም፥ ስለ ሁከት ሰውንም ስለ መግደል በወኅኒ ታስሮ የነበረውን አስፈታላቸው፥ ኢየሱስን ግን ለፈቃዳቸው አሳልፎ ሰጠው። 26፤ በወሰዱትም ጊዜ ስምዖን የተባለ የቀሬናን ሰው ከገጠር ሲመጣ ይዘው ከኢየሱስ በኋላ መስቀሉን እንዲሸከም ጫኑበት። 27፤ ዋይ ዋይ ከሚሉና ሙሾ ከሚያወጡ ሴቶችና ከሕዝቡ እጅግ ብዙዎች ተከተሉት። 28-29፤ ኢየሱስ ግን ወደ እነርሱ ዘወር ብሎ እንዲህ አለ። እናንተ የኢየሩሳሌም ልጆች፥ ለእኔስ አታልቅሱልኝ፤ ዳሩ ግን። መካኖችና ያልወለዱ ማኅፀኖች ያላጠቡ ጡቶችም ብፁዓን ናቸው የሚሉበት ጊዜ እነሆ ይመጣልና ለራሳችሁና ለልጆቻችሁ አልቅሱ። 30፤ በዚያን ጊዜ ተራራዎችን። በላያችን ውደቁ፥ ኮረብቶችንም። ሰውሩን ይሉ ዘንድ ይጀምራሉ፤ 31፤ በእርጥብ እንጨት እንዲህ የሚያደርጉ ከሆኑ፥ በደረቀውስ እንዴት ይሆን? 32፤ ሌሎችንም ሁለት ክፉ አድራጊዎች ደግሞ ከእርሱ ጋር ይገድሉ ዘንድ ወሰዱ። 33፤ ቀራንዮም ወደሚባል ስፍራ በደረሱ ጊዜ፥ በዚያ እርሱን ክፉ አድራጊዎቹንም አንዱን በቀኝ ሁለተኛውንም በግራ ሰቀሉ። 💚 @ortodoxmezmur 💚 💛 @ortodoxmezmur 💛 ❤️ @ortodoxmezmur ❤️
نمایش همه...
😭 24 4🕊 2