en
Feedback
Tikvah-University

Tikvah-University

Open in Telegram

📈 Analytical overview of Telegram channel Tikvah-University

Channel Tikvah-University (@tikvahuniversity) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 381 173 subscribers, ranking 115 in the Education category and 13 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 381 173 subscribers.

According to the latest data from 02 September, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 11 301 over the last 30 days and by 310 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 19.91%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 11.43% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 75 885 views. Within the first day, a publication typically gains 43 569 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 199.

📝 Description and content policy

Channel description not provided.

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 03 September, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Education category.

381 173
Subscribers
+31024 hours
+2 7247 days
+11 30130 days
Posts Archive
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የራስ ገዝነት ሽግግር በመጠናቀቁ አዲስ ፕሬዝዳንት ለመሾም የውድድር ማስታወቂያ በቅርቡ ይወጣል፡፡ - ትምህርት ሚኒስቴር አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የራስ ገዝነት ሽግግር ጊዜው
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የራስ ገዝነት ሽግግር በመጠናቀቁ አዲስ ፕሬዝዳንት ለመሾም የውድድር ማስታወቂያ በቅርቡ ይወጣል፡፡ - ትምህርት ሚኒስቴር አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የራስ ገዝነት ሽግግር ጊዜው በማብቃቱ አዲስ ፕሬዝዳንት ለመሾም የሚያስችለውን የውድድር ማስታወቂያ ለማውጣት የመጨረሻ ዝግጅት ላይ እንደሚገኝ የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ኮራ ጡሽኔ ለሸገር ኤፍኤም ተናግረዋል፡፡ የውድድር ማስታወቂያው በቅርብ ቀናት እንደሚወጣ ሚኒስትር ዴኤታው ገልፀዋል። ሳሙኤል ክፍሌ (ዶ/ር) ከነሐሴ 24/2015 ዓ.ም ጀምሮ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተጠባባቂ ፕሬዝዳንት በመሆን እያገለገሉ ይገኛሉ፡፡ በሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ ውሳኔ፣ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የመጀመሪያው ራስ ገዝ ዩኒቨርሲቲ የሆነው ሐምሌ 28/ 2015 ዓ.ም እንደነበር አይዘነጋም፡፡ @tikvahuniversity

በሁለት ሳምንታት ጊዜ ውስጥ ለአስር ዩኒቨርሲቲዎች አዲስ አመራር ለመመደብ የሚያስችል የውድድር ማስታወቂያ ይፋ እንደሚሆን ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል፡፡ የአስሩ ዩኒቨርሲቲዎች አመራር ምደባ ከተጠናቀ
+1
በሁለት ሳምንታት ጊዜ ውስጥ ለአስር ዩኒቨርሲቲዎች አዲስ አመራር ለመመደብ የሚያስችል የውድድር ማስታወቂያ ይፋ እንደሚሆን ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል፡፡ የአስሩ ዩኒቨርሲቲዎች አመራር ምደባ ከተጠናቀቀ በኋላ ደግሞ ለ17 ዩኒቨርሲቲዎች አዲስ አመራር ለመመደብ የውድድር ማስታወቂያ እንደሚወጣ የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ኮራ ጡሽኔ ለሸገር ኤፍኤም ተናግረዋል። ከዚህ በኋላ የዩኒቨርሲቲ አመራሮች የሚመደቡት በውድድር ብቻ መሆኑን የጠቆሙት ሚኒስትር ዴኤታው፤ ውድድሩ ብቃትና ስብዕና ላይ መሰረት ያደረገ ትክክለኛ ውድድር እንደሚሆን ገልፀዋል። የዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ለመሆን ከዚህ በኋላ ግዴታ ሦስተኛ ዲግሪ የማይጠየቅ ሲሆን፣ ኢንዱስትሪዎችን ጨምሮ በየትኛውም ተቋም የሚገኙ ባለሙያዎች ለኃላፊነቱ መወዳደር ይችላሉ ብለዋል። @tikvahuniversity

ትምህርት ሚኒስቴር የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ምደባን ለማዘመን ከቀጣዩ የትምህርት ዘመን ጀምሮ በቴክኖሎጂ የታገዘ አዲስ የአሰራር ስርዓት ሊዘረጋ ነው፡፡ የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) ከመንግ
ትምህርት ሚኒስቴር የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ምደባን ለማዘመን ከቀጣዩ የትምህርት ዘመን ጀምሮ በቴክኖሎጂ የታገዘ አዲስ የአሰራር ስርዓት ሊዘረጋ ነው፡፡ የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) ከመንግሥት ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንቶች ጋር ባደረጉት የምክክር መድረክ እንደገለፁት፣ የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ስብጥር ብዝሃነትን ባካተተ፣ መቻቻልንና ሀገራዊ አንድነትን በሚያጠናክር መልኩ ሊሆን ይገባል። ከዚሁ ጋር በተያያዘ በዩኒቨርሲቲዎች ከተማሪዎች ምደባና ዝውውር ጋር ተያይዘው የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመፍታት ከቀጣዩ የትምህርት ዘመን ጀምሮ በቴክኖሎጂ የታገዘ አዲስ የአሰራር ስርዓት በትምህርት ሚኒስቴር እንደሚዘረጋ ገልፀዋል። ከበጀት አጠቃቀም ጋር በተያያዘ ዩኒቨርሲቲዎች የተመደበላቸውን በጀት ለታቀደለት ዓላማ ብቻ በቁጠባና በተጠያቂነት መንፈስ መጠቀም እንዳለባቸው አሳስበዋል። የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ክንደያ ገብረህይወት (ፕ/ር) በበኩላቸው ዩኒቨርስቲዎቹ በስምምነት ተማሪዎችን ሲያዘዋውሩ ለትምህርት ሚኒስቴር ማሳወቅ እንዳለባቸው አስገንዝበዋል። @tikvahuniversity

#ሎርካን_ሜዲካል_ኮሌጅ የበርካታ ዓመታት ልምድ ባላቸው ሐኪሞችና ምሁራን ባለቤትነት የሚመራው ሎርካን ሜዲካል ኮሌጅ ምዝገባ ላይ ነው❗️ BSc Fields of Study: → Doctor of Medici
#ሎርካን_ሜዲካል_ኮሌጅ የበርካታ ዓመታት ልምድ ባላቸው ሐኪሞችና ምሁራን ባለቤትነት የሚመራው ሎርካን ሜዲካል ኮሌጅ ምዝገባ ላይ ነው❗️ BSc Fields of Study: → Doctor of Medicine → Doctor of Dental Medicine → Bachelor of Dental Science → Nursing TVET Programs: → Dental Therapy → Nursing → Medical Laboratory → Pharmacy → Radiography ⭐️ CPD ማዕከል አገልግሎት! ☎️ 0913398780 / 0911596059 አድራሻ፦ CMC አደባባይ ከፀሐይ ሪል እስቴት ጀርባ ከ ICMC ጠቅላላ ሆስፒታል አጠገብ 📍 Addis Ababa, CMC Square, Behind Tsehay Real Estate, next to ICMC General Hospital Facebook: https://www.facebook.com/Lorcanmedicalcollege Tiktok: https://www.tiktok.com/@lorcan.medical.co

#KiburCollege ክቡር ኮሌጅ የአፍሪካ የቢዝነስ ስኩል ማኅበር አባል ተቋም ሲሆን ክህሎትን መሠረት ያደረገ ተግባራዊ የትምህርት አሰጣጥን የሚከተል ከፍተኛ የትምህርት ተቋም ነው። ✅ በመጀመሪያ
#KiburCollege ክቡር ኮሌጅ የአፍሪካ የቢዝነስ ስኩል ማኅበር አባል ተቋም ሲሆን ክህሎትን መሠረት ያደረገ ተግባራዊ የትምህርት አሰጣጥን የሚከተል ከፍተኛ የትምህርት ተቋም ነው። ✅ በመጀመሪያ ዲግሪ ✅ ቴክኒክና ሙያ (TVET) ✅ በ Remedial Program ✅ አጫጭር ስልጠናዎች በዳግም ምዝገባ ፍቃድ ባገኘንባቸው የትምህርት ዘርፎች ተማሪዎችን ለመቀበል በምዝገባ ላይ ነን!! Website: https://kibur.net አድራሻ፦ ጀሞ ሚካኤል ከአፍሪካ ህንፃ አጠገብ ☎️ 0113854042 / 0904848586 Telegram: https://t.me/kiburcollege Facebook:  https://www.facebook.com/kiburcollege

የዩኒቨርሲቲ እና የትምህርት መስክ ምርጫ ያድርጉ! በ2018 ዓ.ም የ2ኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ሀገር አቀፍ ፈተና ወስዳችሁ በመደበኛው የትምህርት መርሐግብር የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ውጤት ያስመዘገባ
የዩኒቨርሲቲ እና የትምህርት መስክ ምርጫ ያድርጉ!   በ2018 ዓ.ም የ2ኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ሀገር አቀፍ ፈተና ወስዳችሁ በመደበኛው የትምህርት መርሐግብር የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ውጤት ያስመዘገባችሁ ተማሪዎች በሙሉ የዩኒቨርሲቲ እና የትምህርት መስክ ምርጫ እንድታደርጉ ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል፡፡   የዩኒቨርሲቲ እና የትምህርት መስክ ምርጫ ማድረጊያ ጊዜ 👇 ከነሐሴ 28/2018 ዓ.ም እስከ ጳጉሜን 05/2018 ዓ.ም   የዩኒቨርሲቲ እና የትምህርት መስክ ምርጫ የሚያደርጉበት ሊንክ 👇 https://student.ethernet.edu.et/   የሕክምና፣ የአካል ጉዳተኝነት፣ ተመሳሳይ ጾታ ያላቸው መንትያዎች እና ከስድስት ወር በታች ህጻን የሚያጠቡ እናቶች አስፈላጊውን ሕጋዊ ማስረጃ ማያያዝ ይኖርባችኋል ተብሏል።   @tikvahuniversity

በፌዴራል ልዩ አዳሪ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተመዝግባችሁ ለፈተና የተመረጣችሁ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳዳር ተማሪዎች የሙከራ ፈተና የሚሰጠው ዛሬ ነሐሴ 28/2018 ዓ.ም ከሰዓት ከ9:00 ጀምሮ
በፌዴራል ልዩ አዳሪ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተመዝግባችሁ ለፈተና የተመረጣችሁ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳዳር ተማሪዎች የሙከራ ፈተና የሚሰጠው ዛሬ ነሐሴ 28/2018 ዓ.ም ከሰዓት ከ9:00 ጀምሮ መሆኑ ተገልጿል፡፡   ለሙከራ ፈተናው የተመረጡ የፈተና መስጫ ማዕከላት፦ ➻ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ (6 ኪሎ ዋናው ግቢ) ➻ ዳግማዊ ምኒልክ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ➻ የእቴጌ መነን የልጃገረዶች መካከለኛና 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት Username እና Password በመፈተኛ ማዕከላቱ ስትደርሱ በጣቢያው ከሚመደቡ የፈተና ጣቢያ አስተባባሪዎች ታገኛላችሁ ተብሏል። @tikvahuniversity

በተልዕኮ የተለዩ የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች የሚሰጧቸውን የትምህርት አይነቶች ክለሳ እያደረጉ ይገኛሉ፡፡ - ትምህርት ሚኒስቴር ዩኒቨርሲቲዎች ራሳቸውን በተልዕኮ ሲለዩ በአካባቢያቸው ካለው ፀጋ ጋር በማ
በተልዕኮ የተለዩ የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች የሚሰጧቸውን የትምህርት አይነቶች ክለሳ እያደረጉ ይገኛሉ፡፡ - ትምህርት ሚኒስቴር ዩኒቨርሲቲዎች ራሳቸውን በተልዕኮ ሲለዩ በአካባቢያቸው ካለው ፀጋ ጋር በማስተሳሰር ትኩረታቸውን ይበልጥ እንዲያጠቡ ወይም በልዩ ሁኔታ እንዲለዩ እየተደረገ መሆኑን ትምህርት ሚኒስቴር ገልጿል፡፡ ዩኒቨርሲቲዎች በሚገኙበት አካባቢ ባሉ ሀብቶች ላይ በመመስረት በማዕድን፣ በቱሪዝም፣ በግብርና እና በመሳሰሉት ዘርፎች ተልዕኳቸውን እንዲለዩ እየተደረገ ይገኛል። በአሁኑ ወቅት ከሚሰጡ 297 ፕሮግራሞች ውስጥ 111 ያህሉ መከለሳቸውን በትምህርት ሚኒስቴር የአካዳሚክ ጉዳዮች መሪ ሥራ አስፈጻሚ ኤባ ሜጀና (ዶ/ር) ለሸገር ኤፍኤም ተናግረዋል። ዩኒቨርሲቲዎቹ የትምህርት፣ የሳይንስና ቴክኖሎጂ፣ የአፕላይድ ሳይንስ፣ የምርምር እና የአጠቃላይ ትምህርት ተብለው የተከፈሉ መሆኑን ያስታወሱት ኃላፊው፣ ተቋማቱ የሚሰጧቸው የትምህርት አይነቶችም በተመደቡበት ተልዕኮ መሰረት እንዲከልሱ እየተደረገ ይገኛል ብለዋል፡፡ ይህ ክለሳ ተቋማቱ የበለጠ ተወዳዳሪ እንዲሆኑና ብቃት ያለው ተማሪ እንዲያፈሩ የሚያስችል መሆኑ ተገልጿል፡፡ ከዚህ በኋላ ከመረጡት ተልዕኮ ውጪ ዩኒቨርሲቲዎች የሚሰጡት ትምህርት እንደማይኖር ያስረዱት ኃላፊው፤ ተማሪዎች በአዲሱ የትምህርት ዘመን በሚገባ መረጃ ኖሯቸው እንዲመጡ ለማድረግ ዩኒቨርሲቲዎች ራሳቸውን በአግባቡ ማስተዋወቅ እንዳለባቸው አሳስበዋል። #ShegerFM @tikvahuniversity

ቶኩማ ሀርቨስቲንግ የተባለ የግብርና ማሽን የሠራው ወጣት 👏 ሰለሞን ቡታ ከፍቼ ከተማ የተገኘ የክህሎት ኢትዮጵያ ውድድር ቴክኖሎጂ ፈጣሪ ወጣት ነው፡፡ "ቶኩማ ሀርቨስቲንግ" የተሰኘ በውስጡ ሦስት አ
+1
ቶኩማ ሀርቨስቲንግ የተባለ የግብርና ማሽን የሠራው ወጣት 👏 ሰለሞን ቡታ ከፍቼ ከተማ የተገኘ የክህሎት ኢትዮጵያ ውድድር ቴክኖሎጂ ፈጣሪ ወጣት ነው፡፡ "ቶኩማ ሀርቨስቲንግ" የተሰኘ በውስጡ ሦስት አገልግሎቶችን የሚሰጥ ዘመናዊ የግብርና ማሽን ፈጥሯል፡፡ ማሽኑ መሬት ማረስ፣ ምርት መሰብሰብ እና ውሃ ፓምፕ ማድረግ የሚችል መሆኑ ተገልጿል፡፡ ይህ ፈጠራ የጊር ቦክስ ስርዓቱን በመቀየር በጋዝ፣ በሶላር እንዲሁም በኤሌክትሪክ ኃይል መስራት የሚያስችል አማራጭ አለው፡፡ ከመሬት ያለው ከፍታ ለየትኛውም የሀገሪቱ የመሬት አቀማመጥ ምቹ እንዲሆን ተደርጎ የተሠራ ነው፡፡ አጠቃላይ የማሽኑ ክብደት 150 ኪሎ ግራም ቢሆንም፣ ሲነቃቀል እያንዳንዱ ክፍል 25 ኪሎ ግራም ብቻ ስለሚመዝን በቀላሉ ተነቃቅሎ እንዲጓጓዝና እንዲገጣጠም አስችሎታል፡፡ ከኢንጂኑ በስተቀር ሁሉም የማሽኑ ክፍሎች በሀገር ውስጥ የተሠራ እንደሆነ ተመላክቷል፡፡ ይህ ቴክኖሎጂ በኢትዮጵያ ግብርና ውስጥ ያሉ ችግሮችን የመፍታት አቅም ያለው ሲሆን፣ በምርት መሰብሰብ ሒደት ጣለን ብክነት ከ30 ፐርሰንት ወደ 5 ፐርሰንት ዝቅ ያደርገዋል ተብሏል፡፡ 👏 @tikvahuniversity

🔔 የህክምና ትምህርትዎን በሀገር ውስጥ እና በዓለም አቀፍ ተቋማት ዕውቅና ባለው ሚዮንግሰንግ ሜዲካል ኮሌጅ ይማሩ! ► በዘመናዊ መልክ የተደራጀ ► የራሱ የሆነ ምቹ የተማሪዎች መኖሪያ ያለው ► የኮ
🔔 የህክምና ትምህርትዎን በሀገር ውስጥ እና በዓለም አቀፍ ተቋማት ዕውቅና ባለው ሚዮንግሰንግ ሜዲካል ኮሌጅ ይማሩ! ► በዘመናዊ መልክ የተደራጀ ► የራሱ የሆነ ምቹ የተማሪዎች መኖሪያ ያለው ► የኮሪያ ሆስፒታል እህት ኩባንያ 15ኛ ዙር የህክምና ትምህርት ምዝገባ ላይ ነን! 🎓 ኮሌጃችን ያስተማራቸውን ተማሪዎች በሙሉ የብቃት ምዘና ፈተና ማሳለፍ ችሏል! ለማመልከት 👇 https://maps.app.goo.gl/oxRezU99L2DqnngD6 አድራሻ፦ አዲስ አባባ፣ ገርጂ ኮሪያ ሆስፒታል ቅጥር ግቢ ሬጅስትራር ቢሮ የምዝገባ ጊዜ 👇 እስከ ጳጉሜን 02/2018 ዓ.ም ድረስ። አሁኑኑ ይመዝገቡ! ☎️ 0116395020 ድረ-ገጽ፦ www.mmc-edu.net Facebook: https://web.facebook.com/MMCmedcollege/ #MyungsungMedicalCollege

🌻 የአዲስ ዓመት 25% ቅናሽ ከነሐሴ 27/2018 ዓ.ም እስከ መስከረም 21/2019 ዓ.ም🌻 8ኛ ዙር የእንግሊዘኛ ቋንቋ ስልጠና ምዝገባ ላይ ነን! ስልጠናዎቹ በሦስት ደረጃ ተከፍለው መሰረታዊ (
🌻 የአዲስ ዓመት 25% ቅናሽ ከነሐሴ 27/2018 ዓ.ም እስከ መስከረም 21/2019 ዓ.ም🌻 8ኛ ዙር የእንግሊዘኛ ቋንቋ ስልጠና ምዝገባ ላይ ነን!  ስልጠናዎቹ በሦስት ደረጃ ተከፍለው መሰረታዊ (A1 and A2)፣ ማዕከላዊ (B1 and B2) እና በከፍተኛ ደረጃ (C1 and C2) ተብለው የሚሰጥ ይሆናል። የበለጠ ይጠብቁ ... 💥 ሴጅ ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት 💥 ☎️  0906777799 / 0906777755 አድራሻ፦ ቁ.1: ፒያሣ ቸርችል ጎዳና ኤልያና ሆቴል 2ኛ ፎቅ፣ ቁ.2: መገናኛ ደራርቱ ህንፃ 5ኛ ፎቅ እና ቁ.3: አዳማ ራስ ሆቴል 2ኛ ፎቅ ለመመዝገብ ድረ-ገጽ 👇 www.sageethiopia.com Telegram: https://t.me/sagetraininginstitute Tiktok: https://www.tiktok.com/@sage_training_institute Linkedin: https://www.linkedin.com/company/sage-training-institute

በፌዴራል ልዩ አዳሪ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተመዝግባችሁ ለፈተና የተመረጣችሁ ተማሪዎች የሙከራ ፈተና ነገ ነሐሴ 28/2018 ዓ.ም ጠዋት 3:00 ጀምሮ የሚሰጥ በመሆኑ፤ በሚቀርባችሁ የፈተና መስጫ
በፌዴራል ልዩ አዳሪ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተመዝግባችሁ ለፈተና የተመረጣችሁ ተማሪዎች የሙከራ ፈተና ነገ ነሐሴ 28/2018 ዓ.ም ጠዋት 3:00 ጀምሮ የሚሰጥ በመሆኑ፤ በሚቀርባችሁ የፈተና መስጫ ማዕከል ከጠዋቱ 2:30 ተገኝታች የሙከራ ፈተናውን እድትወስዱ ትምህርት ሚኒስቴር አሳስቧል። Username እና Password መፈተኛ ማዕከሉ ስትደርሱ በጣቢያው ከሚመደቡ የፈተና ጣቢያ አስተባባሪዎች በኩል የምታገኙ መሆኑ ተገልጿል። @tikvahuniversity

#ጥቆማ በትምህርት ሚኒስቴር የመንግሥት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ፕሬዝዳንት እና ምክትል ፕሬዝዳንት አስያየም መመሪያ ቁጥር 1146/2018 መሰረት፤ ደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንቶችን አወ
+4
#ጥቆማ በትምህርት ሚኒስቴር የመንግሥት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ፕሬዝዳንት እና ምክትል ፕሬዝዳንት አስያየም መመሪያ ቁጥር 1146/2018 መሰረት፤ ደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንቶችን አወዳድሮ መመደብ ይፈልጋል፡፡ ዩኒቨርሲቲው ለውድድር ክፍት ያደረጋቸው የሥራ መደቦች፦ 1. የአካዳሚክ ምርምር፣ ቴክኖሎጂ ሽግግር እና ማኅበረሰብ አገልግሎት ምክትል ፕሬዝዳንት 2. የአስተዳደርና ልማት ምክትል ፕሬዝዳንት 3. ቺፍ ኤክስክዩቲቭ ዳይሬክተር ለጤና ሳይንስ ኮሌጅ (በምክትል ፕሬዝዳንት ማዕረግ) ለተጠቀሱት ክፍት የአመራር ቦታዎች ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት እንዲሁም ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ውጪ ባለ በመንግሥታዊና መንግሥታዊ ባልሆኑ መስሪያ ቤቶች እና ድርጅቶች ውስጥ የሚገኙ ተወዳዳሪዎችን መወዳደር ይችላሉ ተብሏል፡፡ (ለእያንዳንዱ የአመራር የሥራ መደብ የተቀመጡ ዝርዝር መስፈርቶችን ከላይ ከተያያዘው ምስል ይመለልከቱ፡፡) የምዝገባ ሁኔታ፦ ደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ፣ የብቃትና የሰው ሀብት አስተዳደር ሥራ አስፈፃሚ ህንፃ ቁ. 139፣ ቢሮ ቁ. 107 ወይም በኢሜይል አድራሻ፡ dtuhr2026@gmail.com ሰነዶችን በ PDF ፋይል በመላክ ወይም በፖ.ሳ.ቁ. 272 (ደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ) መመዝገብ ይቻላል፡፡ @tikvahuniversity

#EthiopianPoliceUniversity የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት ፕሮግራሞች ለ2019 የትምህርት ዘመን አዲስ ተማሪዎችን ተቀብሎ ለማስተማር የመግቢያ ፈተና ለመስጠት ዝግጅት
#EthiopianPoliceUniversity የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት ፕሮግራሞች ለ2019 የትምህርት ዘመን አዲስ ተማሪዎችን ተቀብሎ ለማስተማር የመግቢያ ፈተና ለመስጠት ዝግጅት ማጠናቀቁን ገልጿል። ይህ ማስታወቂያ በሁሉም የማስተርስ ዲግሪ፣ የቅድመ-ምረቃ ዲግሪ፣ የፖሊስ ሳይንስ ዲግሪ (ለሲቪል ተመልማዮች)፣ በደረጃ 4 (ክሊኒካል ነርሲንግ፣ ሜዲካል ላቦራቶሪ እና ፋርማሲ) እንዲሁም በሁሉም ዲፕሎማ (ፖሊስ ሳይንስ፣ ፖሊስ ኢንተለጀንስ እና አቪዬሽን ፖሊስ) ፕሮግራሞች የተመዘገባችሁ አመልካቾችን በሙሉ የሚመለከት መሆኑ ተገልጿል፡፡ የተፈታኞች የትምህርት ማስረጃ ማጣራትና ኦሬንቴሽን መስከረም 04 እና 05/2019 ዓ.ም ከጠዋቱ 2:30 እስከ 6:00 እንዲሁም ከሰዓት ከ8:00 እስከ 11:00 ሰዓት በየተመደቡበት ማዕከል የሚከናወን መሆኑ ተመላክቷል፡፡ የመግቢያ ፈተና መስከረም 06/2019 ዓ.ም ከጠዋቱ 3:00 እስከ 5:00 ሰዓት በሁሉም የፈተና ማዕከላት ይሰጣል ተብሏል። አመልካቾች አስፈላጊ የትምህርት ማስረጃችሁን ዋናውና ኮፒውን በመያዝ በተጠቀሱት ቀናት በፈተና ማዕከላት እንድትገኙ ዩኒቨርሲቲው አሳስቧል። @tikvahuniversity

#Pioneer_College 🔥 አስደሳች ዜና ከፓዩኒዬር ኮሌጅ የዕውቅና ፈቃድ ያለው ፓዩኒዬር ኮሌጅ፤ ለ2019 ዓ.ም ተማሪዎች ብቻ የሚያገለግል የትምህርት ክፍያ ዋጋ ቅናሽ አድርገናል❗️ ከትምህርት
#Pioneer_College 🔥 አስደሳች ዜና ከፓዩኒዬር ኮሌጅ    የዕውቅና ፈቃድ ያለው ፓዩኒዬር ኮሌጅ፤ ለ2019 ዓ.ም ተማሪዎች ብቻ የሚያገለግል የትምህርት ክፍያ ዋጋ ቅናሽ አድርገናል❗️ ከትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን ዕውቅና ባገኘንባቸው የዲግሪ ፕሮግራሞች፦ ► የሕክምና ዶክትሬት ► የጥርስ ሕክምና ዶክትሬት ► ፋርማሲ ► ሜዴካል ላብራቶሪ ሳይንስ 🔔 ምዝገባ ጀምረናል! በጤናው መስክ ተወዳደሪ ሆኖ ለመገኘት ካሰቡ አሁኑኑ ፓዩኒዬር ኮሌጅ ይመዝገቡ! አድራሻ ከጀርመን አደባባይ ወደ ለቡ መብራት በሚሰደው መንገድ ☎️  0902442244 / 0902443344 www.pioneercollege.edu.et

የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ በዓለም አቀፉ የኢንጂነሪንግና ቴክኖሎጂ ዕውቅና ሰጪ ቦርድ (ABET) ተጨማሪ ሁለት ፕሮግራሞቹ ሙሉ የጊዜ-ዑደት ዕውቅና አጊኝተዋል። ዩኒቨርሲቲው የኬሚካል
የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ በዓለም አቀፉ የኢንጂነሪንግና ቴክኖሎጂ ዕውቅና ሰጪ ቦርድ (ABET) ተጨማሪ ሁለት ፕሮግራሞቹ ሙሉ የጊዜ-ዑደት ዕውቅና አጊኝተዋል። ዩኒቨርሲቲው የኬሚካል ኢንጂነሪንግ እና የኢንቫይሮንመንታል ኢንጂነሪንግ የመጀመሪያ ዲግሪ ፕሮግራሞቹ እስከ መስከረም 19/2025 ዓ.ም ድረስ የሚቆይ ሙሉ የጊዜ-ዑደት ዕውቅና ማግኘታቸውን አሳውቋል። ከዚህ ቀደም የዩኒቨርሲቲው የባዮቴክኖሎጂ፣ የምግብ ሳይንስና አፕላይድ ኑትሪሽን፣ የጂኦሎጂ እና የኢንዱስትሪያል ኬሚስትሪ የመጀመሪያ ዲግሪ ፕሮግራሞቹ እስከ መስከረም 20/2024 ዓ.ም ድረስ የሚቆይ ዕውቅና ማግኘታቸው ይታወሳል። ዕውቅናዎቹ የዩኒቨርሲቲውን ዓለም አቀፍ የትምህርት ጥራት የሚያረጋግጥ መሆኑ ተገልጿል። @tikvahuniversity

#ሎርካን_ሜዲካል_ኮሌጅ የበርካታ ዓመታት ልምድ ባላቸው ሐኪሞችና ምሁራን ባለቤትነት የሚመራው ሎርካን ሜዲካል ኮሌጅ ምዝገባ ላይ ነው❗️ BSc Fields of Study: → Doctor of Medici
#ሎርካን_ሜዲካል_ኮሌጅ የበርካታ ዓመታት ልምድ ባላቸው ሐኪሞችና ምሁራን ባለቤትነት የሚመራው ሎርካን ሜዲካል ኮሌጅ ምዝገባ ላይ ነው❗️ BSc Fields of Study: → Doctor of Medicine → Doctor of Dental Medicine → Bachelor of Dental Science → Nursing TVET Programs: → Dental Therapy → Nursing → Medical Laboratory → Pharmacy → Radiography ⭐️ CPD ማዕከል አገልግሎት! ☎️ 0913398780 / 0911596059 አድራሻ፦ CMC አደባባይ ከፀሐይ ሪል እስቴት ጀርባ ከ ICMC ጠቅላላ ሆስፒታል አጠገብ 📍 Addis Ababa, CMC Square, Behind Tsehay Real Estate, next to ICMC General Hospital Facebook: https://www.facebook.com/Lorcanmedicalcollege Tiktok: https://www.tiktok.com/@lorcan.medical.co

በነሐሴ 2018 ዓ.ም የጤና ሙያ ፈቃድ ፈተና የወሰዱ የጤና ባለሙያዎች ውጤት ተለቋል፡፡ በነሐሴ 2018 ዓ.ም በጤና ሚኒስቴር የተሰጠውን የጤና ሙያ የብቃት መዘና ፈተና የወሰዳችሁ ተመዛኞች ከዛሬ ነ
በነሐሴ 2018 ዓ.ም የጤና ሙያ ፈቃድ ፈተና የወሰዱ የጤና ባለሙያዎች ውጤት ተለቋል፡፡ በነሐሴ 2018 ዓ.ም በጤና ሚኒስቴር የተሰጠውን የጤና ሙያ የብቃት መዘና ፈተና የወሰዳችሁ ተመዛኞች ከዛሬ ነሐሴ 27/2018 ዓ.ም ጀምሮ https://hple.moh.gov.et ላይ በመግባትና የብሔራዊ መለያ ቁጥር (FAN) እና Password በማስገባት የፈተና ውጤታችሁን መመልከት የምትችሉ መሆኑን ጤና ሚኒስቴር አሳውቋል፡፡ በውጤታችሁ ላይ ቅሬታ ያላችሁ ተመዛኞች ውጤት ከዛሬ ነሐሴ 27/2018 ዓ.ም ጀምሮ ባሉት 10 (አስር) ተከታታይ የሥራ ቀናት በስልክ ቁ. 952 በሥራ ሰዓት በመደወል ሙሉ ስም፣ ዲፓርትመንት እና የተማራችሁበትን የትምህርት ተቋም ስም በማሳወቅ ጥያቄዎቻችሁን ማቅረብ እንደምትችሉ ተገልጿል፡፡ በዚህ ዙር ለመጀመሪያ ጊዜ ተመዛኞች በተናጠል የውጤት ትንተና (Domain Analysis) ማየት እንደምትችሉ የተገለፀ ሲሆን፣ ይህም ራችሁን ለማሻሻልና የበለጠ ለማብቃት የሚያስችል ነው ተብሏል፡፡ የጤና ሙያ ፈቃድ ፈተናውን ያለፋችሁ ተመዛኞች ከሰኞ ዻጉሜን 02/2018 ዓ.ም ጀምሮ ስም ዝርዝራችሁ ወደ ክልል የሚላክ ስለሆነ የሙያ ፍቃዳችሁን 12ኛ ክፍል በተማራችሁበት ክልል ማውጣት የምትችሉ መሆኑን ሚኒስቱሩ አሳውቋል፡፡ @tikvahuniversity

#AAU_Undergraduate_Admission በ2019 የትምህርት ዘመን በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በቅድመ-ምረቃ ፕሮግራም ለመማር የምትፈልጉ አመልካቾች የምዝገባ ጊዜ አርብ ነሐሴ 29/2018 ዓ.ም
#AAU_Undergraduate_Admission በ2019 የትምህርት ዘመን በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በቅድመ-ምረቃ ፕሮግራም ለመማር የምትፈልጉ አመልካቾች የምዝገባ ጊዜ አርብ ነሐሴ 29/2018 ዓ.ም ይጠናቀቃል፡፡ በቀሩት ጥቂት ቀናት ምዝገባዎን ያድርጉ! ለተጨማሪ መረጃ 👇 https://admission.aau.edu.et/UGAnnouncements የዩኒቨርሲቲ የመግቢያ ፈተና (UAT) ከጳጉሜን 02-04/2018 ዓ.ም በየመረጣችሁበት የፈተና ማዕከል እንደሚሰጥ ዩነቨርሲቲው ገልጿል፡፡ @tikvahuniversity

#ጥቆማ የሐረር ሞዴል 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ለ2019 የትምህርት ዘመን የ9ኛ ክፍል ተማሪዎችን ‎በነጻ የትምህርት ዕድል ተቀብሎ ማስተማር ይፈልጋል። ‎ ‎በመሆኑም በሞዴል 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቱ
#ጥቆማ የሐረር ሞዴል 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ለ2019 የትምህርት ዘመን የ9ኛ ክፍል ተማሪዎችን ‎በነጻ የትምህርት ዕድል ተቀብሎ ማስተማር ይፈልጋል። ‎ ‎በመሆኑም በሞዴል 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቱ ለመማር ፍላጎት ያላችሁና መስፈርቱን የምታሟሉ ተማሪዎች በሐረሪ ክልል ትምህርት ቢሮ በመገኘት መመዝገብ የምትችሉ መሆኑ ተገልጿል። ‎ መስፈርቶች፦ ‌‌‎➻ ጥሩ ስነ-ምግባር ያለው/ያላት ➻ በ2018 ዓ.ም የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና በሐረሪ ክልል ተፈትኖ አማካይ ውጤት 70 እና በላይ ለሴቶች እና 75 እና በላይ ለወንዶች አማካይ ውጤት ያለው/ያላት ‎➻ በእንግሊዝኛ እና በሂሳብ ትምህርት አይነቶች ውጤት 70 እና በላይ ለሴቶች እና 75 እና በላይ በመቶ ለወንዶች አማካይ ውጤት ያለው/ያላት ‌‎➻ በ2017 እና 2018 የትምህርት ዘመን በ7ኛ እና 8ኛ ክፍል ትራንስክሪፕት 70 እና በላይ በመቶ ለሴቶች እና 75 እና በላይ በመቶ ለወንዶች አማካይ ውጤት ያለው/ያላት የምዝገባ ጊዜ 👇 ከነሐሴ 26/2018 ዓ.ም ጀምሮ @tikvahuniversity