Tikvah-University
前往频道在 Telegram
📈 Telegram 频道 Tikvah-University 的分析概览
频道 Tikvah-University (@tikvahuniversity) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 366 242 名订阅者,在 教育 类别中位列第 125,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 12 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 366 242 名订阅者。
根据 06 七月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 6 380,过去 24 小时变化为 128,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 15.24%。内容发布后 24 小时内通常能获得 9.39% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 55 823 次浏览,首日通常累积 34 384 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 161。
📝 描述与内容策略
尚未提供频道描述。
凭借高频更新(最新数据采集于 07 七月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 教育 类别中的关键影响点。
366 242
订阅者
+12824 小时
+4767 天
+6 38030 天
帖子存档
366 242
+1
የትግራይ ክልል መምህራን ማኅበር በትግራይ ክልል የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ መልቀቂያ ፈተና የወረቀት ተፈታኞች የሚሰጥበት ጊዜ በትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ወደ ሐምሌ 22-24/2018 ዓ.ም መራዘሙ ተገቢ አይደለም ሲል ወቅሷል።
ማኅበሩ ዛሬ ባወጣው መግለጫ፣ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ቀድሞ ባወጣው መርሐግብር መሠረት የትግራይ ክልል ተማሪዎች ለፈተናው ተዘጋጅተው እንደነበር አስታውሷል።
"ለትግራይ ተፈታኝ ተማሪዎች ብቻ መርሐግብሩ እንዲራዘም መደረጉ ተገቢ አይደለም" ያለው ማኅበሩ፤ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ቀድሞ ባወጣው መርሐግብር መሠረት ፈተናው እንዲሰጥ ጠይቋል።
(የማኅበሩ መግለጫ ከላይ ተያይዟል።)
@tikvahuniversity
366 242
የጤና ባለሙያዎች የሙያ ፈቃድ ፈተና በነሐሴ ወር 2018 ዓ.ም ይሰጣል። - ጤና ሚኒስቴር
ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በመጀመሪያ ዲግሪ ለተመረቃችሁ የጤና ባለሙያዎች የሙያ ፈቃድ ፈተና በነሐሴ ወር 2018 ዓ.ም ለመስጠት ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የጤና ሚኒስቴር ገልጿል።
በመሆኑም መረጃችሁን ወደ ሲስተም ያላስገባችሁ ነባር እና አዲስ ተመዛኞች ከሰኔ 30 እስከ ሐምሌ 17/2018 ዓ.ም ድረስ ብቻ https://hple.moh.gov.et/ ላይ በመግባት የብሔራዊ መታወቂያ መለያ ቁጥር (FAN 16 Digit) በማስገባት አስፈላጊ መረጃዎችን በማሟላት ለምዝገባ እንድትዘጋጁ ሚኒስቴሩ አሳስቧል፡፡
መረጃ የማስተሳሰር ሂደት እንዳለቀ የፈተና ጣቢያ መረጣ ሂደት እንደሚቀጥል ተገልጿል፡፡
🔔 በሰኔ 2018 ዓ.ም የመውጫ ፈተና ተፈትናችሁ ያለፉችሁ ተመዛኞች የስም ዝርዝራችሁን በተማራችሁበት ተቋም አማካኝነት ወደ ሲስተም ማስጫን ይጠበቅባችኋል ተብሏል።
@tikvhauniversity
366 242
+3
የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ የሁለተኛ ዙር ፈተና እየሠጠ ነው።
ሰኔ 26/2018 ዓ.ም መሠጠት የጀመረው የሁለተኛ ዙር የኦንላይን ተፈታኝ የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች ነገ ማክሰኞ ይጠናቀቃል።
የሦስተኛ ዙር የተፈጥሮ ሳይንስ ተፈታኞች የወረቀት እና የኦንላይን ፈተና ከረቡዕ ሐምሌ 01/2018 ዓ.ም ጀምሮ ለሦስት ተከታታይ ቀናት ይሰጣል። ተፈታኞች ፈተናውን ወደሚወስዱበት ተቋማት መግባት ጀምረዋል።
@tikvahuniversity
366 242
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ6ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና ካስፈተኑ 768 ትምህርት ቤቶች፥ 543ቱ ተማሪዎቻቸውን ሙሉ በሙሉ ማሳለፋቸው ተገለፀ።
የአዲስ አበባ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የ2018 ዓ.ም የ6ኛ ክፍል ፈተና ውጤት ይፋ አድርጓል።
በከተማ አስተዳደሩ በ2018 ዓ.ም የ6ኛ ክፍል ፈተና ከወሰዱ ተማሪዎች 97.48% የሚሆኑት 50% እና በላይ በማስመዝገብ ወደ 7ኛ ክፍል መዘዋወራቸውን ቢሮው አሳውቋል።
በመዲናዋ ፈተናውን ከወሰዱ 84,257 የ6ኛ ክፍል ተማሪዎች መካከል 82,137 ተማሪዎች የማለፊያ ነጥብ ሆኖ የተቆረጠውን 50 በመቶ እና በላይ አስመዝግበዋል።
ተማሪዎች ውጤት ለማየት 👇 https://aa6.ministry.et/#/result
@tikvahuniversity
366 242
12ኛ ዙር የጋዜጠኝነት ስልጠና የፊታችን ቅዳሜ ሐምሌ 04/2018 ዓ.ም ይጀመራል።
በስልጠናው
👉 መሠረታዊ የጋዜጠኝነት መርሆች ፣ የሚዲያ እና የጋዜጠኝነት አይነቶች
👉 የዜና አሰራር እና የቃለመጠይቅ አደራረግ
👉 የመዝናኛ ፕሮግራም ጋዜጠኝነት፣ የፕሮግራም ዝግጅት፣ የማስታወቂያ አሠራር እና የዶክመንተሪ ዝግጅት
👉 የሞባይል እና የዩቲዩብ ጋዜጠኝነት አካቷል፡፡
የበለጠ ይጠብቁ ...
💥 ሴጅ ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት 💥
☎️ 0906777799 / 0906777755
አድራሻ፦ ቁ.1: ፒያሣ ቸርችል ጎዳና ኤልያና ሆቴል 2ኛ ፎቅ፣ ቁ.2: መገናኛ ታሜጋስ ህንፃ 2ኛ ፎቅ እና ቁ.3: አዳማ ራስ ሆቴል 2ኛ ፎቅ
ለመመዝገብ ድረ-ገጽ 👇 www.sageethiopia.com
Telegram: https://t.me/sagetraininginstitute
Tiktok: https://www.tiktok.com/@sage_training_institute
366 242
በትግራይ ክልል በወረቀት ለመፈተን ለተመዘገቡ 15,325 የ12ኛ ክፍል ተፈታኞች ፈተናው ከሐምሌ 22-24/2018 ዓ.ም እንደሚሰጥ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቋል።
ተፈታኞቹ በተገለፁት ቀናት በመቐለ እና በአክሱም ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ በወረቀት እንደሚፈተኑ አገልግሎቱ ገልጿል።
ተፈታኞች ወደተገለፁት ዩኒቨርሲቲዎች ሐምሌ 20/2018 ዓ.ም በመግባት እና ሐምሌ 21/2018 ዓ.ም ላይ ኦሬንቴሽን በመውሰድ መፈተን የሚችሉ መሆኑን አገልግሎቱ አብራርቷል።
በተያያዘ በትግራይ ክልል በበይነ መረብ ለመፈተን የተመዘገቡ 14,755 ተፈታኞች በስድስቱ ዙር ከሰኔ 23/2018 ዓ.ም ጀምሮ ፈተናው እየተሰጠ መሆኑ ተመልክቷል።
@tikvahuniversity
366 242
"ትምህርት ቢሮው የራሱን ፈተና አዘጋጅቶ ላልተፈተኑ ተማሪዎች በአጭር ጊዜ ውስጥ ይሰጣል።" - የትግራይ ክልል ትምህርት ቢሮ
"ማንኛውም ክልል የሀገር አቀፍ ፈተና የማውጣት እና የመፈተን ስልጣን የለውም" - የፌዴራል መንግሥት
የወረቀት ፈተናውን ከሐምሌ 22-24/2018 ዓ.ም ለመስጠት ታቅዷል። - የፌዴራል መንግሥት
"ትምህርት ሚኒስቴር በወረቀት ለሚፈተኑ የትግራይ ተማሪዎች የፈተና ወረቀት አላከም" ያለው የትግራይ ክልል ትምህርት ቢሮ፤ በአጭር ጊዜ ውስጥ የራሱን ፈተና አዘጋጅቶ ላልተፈተኑ ተማሪዎች ፈተናውን እንደሚሰጥ አሳውቋል።
ሰኔ 29/2018 ዓ.ም ዩኒቨርሲቲ ገብተው ከሐምሌ 01/2018 ዓ.ም ጀምሮ በወረቀት ሊፈተኑ የነበሩ 15,349 ተማሪዎች ፈተናው ከፌደራል መንግሥት ስላልተላከ ወደ ዩኒቨርሲቲ እንዳይጓዙ መደረጉን የቢሮው ኃላፊ ኪሮስ ጉዕሽ (ዶ/ር) ተናግረዋል።
"ፈተናው በአውሮፕላን የሚመጣና በፌዴራል ፖሊስ የሚጠበቅ በመሆኑ፣ ወደ ትግራይ እንዳይላክ የሚያደርግ ምንም ዓይነት ምክንያት የለም" ያሉት ኃላፊው፤ "ውሳኔ ፖለቲካዊ ነው" ሲሉ ገልፀዋል።
"የክልል ካቢኔ የፈተና ወረቀቱ በወቅቱ እንዲላክ ለፌዴራል መንግሥት ደብዳቤ አስተላልፏል። እስካሁን አውንታዊ ምላሽ አላገኘም" ብለዋል።
በዚህም ትምህርት ቢሮው የራሱን ፈተና አዘጋጅቶ ላልተፈተኑ ተማሪዎች ፈተናውን በአጭር ጊዜ ውስጥ እንደሚሰጥ አመልክተዋል።
የትግራይ ክልል ትምህርት ቢሮ "በራሴ ፈተና አዘጋጅቼ እፈትናለሁ" ማለቱን ተከትሎ፣ ስማቸው እንዲጠቀስ ያልፈለጉ የፌዴራል መንግሥት የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ታማኝ የመረጃ ምንጭ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ምላሽ ሰጥተዋል።
እኚሁ ምንጭ "ይህን ፈተና የማዘጋጀት ስልጣን የፌዴራል መንግሥት የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ብቻ ነው " ያሉ ሲሆን፤ ማንኛውም ክልል የሀገር አቀፍ ፈተና የማውጣት እና የመፈተን ህጋዊ ስልጣን እንደሌለው ገልፀዋል።
የትግራይ ክልል "እራሴ ፈተና አውጥቼ እፈትናለሁ" የሚለው አካሄድ ፍፁም ቅቡልነት የሌለው መሆኑን የገለፁት አመራሩ፤ "እንፈትናለን ብለው ከወሰኑና ፈተናውን ከሰጡ የፈተናው ውጤት ተቀባይነት ስለማይኖረው የተማሪዎችን ቀጣይ የህይወት ጉዞ ነው የሚያበላሹት" ሲሉ አስጠንቅቀዋል።
ቀደም ብሎ በትግራይ ክልል በተካሄደው የኦንላይን ፈተና ወቅት የነበረውን ሁኔታ ያነሱት አመራሩ ፤ የፌዴራል ፀጥታ አካላትና ፈታኞች በአግባቡ ስራቸውን እንዳይወጡ ጫና ተደርጎባቸው እንደነበር ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልፀዋል።
ለአብነትም ለጸጥታ ማስከበር ስራ የተሰማሩ አካላት እንኳን መሳሪያ እንዳይዙ የማድረግ ጫና እንደነበረባቸው ጠቅሰው፣ በወቅቱ የተማሪዎች ቀጣይ ህይወት ጉዞ እንዳይበላሽ ሲባል ብቻ ትምህርት ሚኒስቴር ፈተናው በጫና ውስጥም ቢሆን ታግሶ እንዲሰጥ ማድረጉን አስታውሰዋል።
የአሁኑ የወረቀት ፈተና አግባብ ባለው የፈተና አካሄድና ስርዓት ከሐምሌ 22-24/2018 ዓ.ም ድረስ እንዲሰጥ መታቀዱን እኚሁ አካል ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልፀዋል።
@tikvahethiopia
366 242
#ጥቆማ
የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት በ34 አጫጭር የስልጠና ፕሮግራሞች በቅርቡ ስልጠና መስጠት እንደሚጀምር አሳውቋል።
ኢንስቲትዩቱ ከደረጃ 6 እስከ ደረጃ 8 (ከመጀመሪያ ዲግሪ እስከ ፒኤችዲ) እያሰለጠነ ሲሆን፤ የገበያ ፍላጎት በማጥናት በ34 የስልጠና ዘርፎች አጫጭር ስልጠናዎች በቅርቡ መስጠት እንደሚጀምር ገልጿል።
@tikvahuniversity
366 242
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ2018 ዓ.ም የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ከተማ አቀፍ ፈተና ውጤት ነገ ይፋ እንደሚደረግ የከተማ አስተዳደሩ ትምህርት ቢሮ ገልጿል።
በመዲናዋ የ6ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና ከሰኔ 8 -10/2018 ዓ.ም በ199 የመፈተኛ ጣቢያዎች ለሦስት ቀናት መሰጠቱ ይታወሳል፡፡
@tikvahuniversity
366 242
ማክሰኞ ሰኔ 30/2018 ዓ.ም ይጠናቀቃል!
የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ከ1ኛ-12ኛ ክፍል ለሆናችሁ ተማሪዎች በተከታዮቹ መስኮች ላይ የክረምት ስልጠና ዕድል አዘጋጅቷል።
➫ ፈንዳሜንታል ኦፍ ኤ.አይ.
➫ ፕሮግራሚንግ
➫ ማሽን ለርኒንግ
➫ ሮቦቲክስ እና IOT
➫ ዳታ ሳይንስ እና በሌሎችም የኤ.አይ. ዘርፎች
እስከ ማክሰኞ ሰኔ 30/2018 ዓ.ም ድረስ በ https://aii.et/summercamp ላይ በመግባት ምዝገባዎን ያድርጉ!
@tikvahuniversity
366 242
+1
ብርቱዎቹ የ12ኛ ክፍል ተፈታኝ እናቶች
እንዚህ እናቶች የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ለመፈተን ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ የተገኙ ተማሪዎች ናቸው፡፡
የእናትነት ኃላፊነትን እየተወጡ በተመሳሳይ ጊዜ የትምህርት ህልማቸውን ለማሳካት ያሳዩት ጥንካሬና ትጋት ከፍተኛ አድናቆት የሚቸረው ነው። 👏👏
@tikvahuniversity
366 242
85ኛ፣ እና 86ኛ ዙር የግራፊክ ዲዛይን፣ ቪዲዮ ኤዲቲንግ እና ሞሽን ግራፊክ ስልጠና ምዝገባ ላይ ነን።
👉 ተግባርን ከንድፈ ሀሳብ ያስተሳሰረ ስልጠና
👉 Advanced Graphic + Video Editing + Motion Graphic በአንድ ላይ
👉 ከ50 በላይ ፕሮጀክቶች ያሉት
ስልጠናው ሰኔ 29/2018 ዓ.ም ይጀምራል።
የበለጠ ይጠብቁ ...
💥 ሴጅ ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት 💥
☎️ 0906777799 / 0906777755
አድራሻ፦ ቁ.1: ፒያሣ ቸርችል ጎዳና ኤልያና ሆቴል 2ኛ ፎቅ፣ ቁ.2: መገናኛ ታሜጋስ ህንፃ 2ኛ ፎቅ እና ቁ.3: አዳማ ራስ ሆቴል 2ኛ ፎቅ
ለመመዝገብ ድረ-ገጽ 👇 www.sageethiopia.com
Telegram: https://t.me/sagetraininginstitute
Tiktok: https://www.tiktok.com/@sage_training_institute
366 242
+5
#AAEB
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የ2019 ትምህርት ዘመን ዓመታዊ የጊዜ ሰሌዳ ለሁሉም ክ/ከተሞች ትምህርት ጽ/ቤቶች እና በከተማ አስተዳደር ስር ለሚገኙ ሦስት አዳሪ ትምህርት ቤቶች ልኳል።
በዚህም፦
ከሐምሌ 19 እስከ ነሐሴ 22/2018 ዓ.ም
የነባር እና አዲስ ተማሪዎች ምዝገባ ይከናወናል።
ከነሐሴ 26 እስከ ጳጉሜን 5/2018 ዓ.ም
የአዲስ ገቢ የ7ኛ እና የ9ኛ ክፍል ተማሪዎች ምዝገባ ይከናወናል።
መስከረም 05/2019 ዓ.ም
የመጀመሪያ ቀን የመጀመሪያ መደበኛ ትምህርት ክፍለ ጊዜ ይጀመራል።
(የከተማ አስተዳደሩ ትምህርት ቢሮ ለሁሉም ክ/ከተሞች ትምህርት ጽ/ቤቶች እና በከተማ አስተዳደር ስር ለሚገኙ ሦስት አዳሪ ት/ቤቶች የላከው ሙሉ የ2019 ዓ.ም የትምህርት ካሌንደር ከላይ ተያይዟል።)
@tikvahuniversity
366 242
🔔 እስከ ሰኔ 30/2018 ዓ.ም በሁሉም ስልጠናዎቻችን ላይ የ 40% ቅናሽ አድርገናል!
በሦስቱም ቅርንጫፎቻችን (መገናኛ፣ ሜክሲኮ እና ጀሞ) እንዲሁም በኦንላይን በምንሰጣቸው ስልጠናዎች በ Advanced Level እና 90% Practical በሆነ ካሪኩለም፣ ዘመኑ ያፈራቸውን የላብራቶሪና የስቱዲዮ እቃዎችን በማሟላት በሁሉም ስልጠናዎቻችን ላይ ታላቅ የዋጋ ቅናሽ አድርገናል!
አሁኑኑ ይመዝገቡና ትልቅ ለውጥ ወደሚያመጡበት ተቋም ይቀላቀሉ!
ከትምህርትና ስልጠና ጥራትና ቁጥጥር ባለስልጣን ሙሉ ዕውቅና ካለው ሰርተፊኬት ጋር! የብዙ ዓመት ልምድ እና ብቃት ባላቸው አሰልጣኞች!
🎯 Graphics Design
🎯 Video Editing
🎯 Digital Marketing
🎯 Photography
🎯 Videography
🎯 Cinematography
🎯 Basic Computer
🎯 English Language
🎯 Fullstack Web App Development
🎯 Programming Language
🎯 Interior Design
🎯 English Language
🎯 Accounting Softwares
🎯 Engineering Softwares
🎯 SPSS & STATA
🎯 MS-Project
🎯 Foreign & Local Languages
አድራሻ
1ኛ. መገናኛ መተባበር ህንፃ 2ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 114 ☎️ 0991929303
2ኛ. ሜክሲኮ ኬኬር ህንፃ 3ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 319 ☎️ 0991929304
3ኛ. ጀሞ 1 አንደኛ በር ካኩ ቢዝነስ ሴንተር 3ኛ ፎቅ ☎️ 0991926707
Telegram 👇
https://t.me/topinstitutes
366 242
#SamaraUniversity
ሠመራ ዩኒቨርሲቲ 'የአፋር ጥናት ኢንስቲትዩት' / Institute of Afar Studies ሊያቋቁም ነው።
የሚቋቋመው ኢንስቲትዩት በአሊ አሪፍ ቡርሃን ስም የሚሰየም መሆኑንም የዩኒቨርሲቲው ሴኔት ወስኗል።
በሌላ በኩል የዩኒቨርሲቲው ሴኔት በፓሊዎአንትሮፖሎጂ የትምህርት መስክ የሁለተኛ ዲግሪ ፕሮግራም (MA in Paleoanthropology) እንዲከፈቱ አፅድቋል፡፡
@tikvahuniversity
366 242
+2
#MekelleUniversity
መቐለ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያስተማራቸውን ከ2900 በላይ ተማሪዎች በዛሬው ዕለት አስመርቋል።
ተመራቂዎቹ ከመጀመሪያ ዲግሪ እስከ ሦስተኛ ዲግሪ (PhD) ትምህርታቸውን ተከታትለው ያጠናቀቁ ናቸው።
የመቐለ ዩኒቨርሲቲ 33ኛ ዙር ተመራቂዎች፦
45 ➫ በሦስተኛ ዲግሪ (PhD)
939 ➫ በሁለተኛ ዲግሪ
83 ➫ በስፔሻሊቲ
1864 ➫ በመጀመሪያ ዲግሪ
ከተመራቂዎቹ መካከል 45 የውጭ አገራት ተማሪዎች ይገኛሉ።
@tikvahuniversity
366 242
+2
#EthiopianDefenseUniversity
የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያሰለጠናቸውን 371 ተማሪዎች አስመርቋል።
ተመራቂዎቹ በዩኒቨርሲቲው ሦስት ኮሌጆች ከመጀመሪያ እስከ ሦስተኛ ዲግሪ ፕሮግራሞች ትምህርታቸውን ተከታትለው ያጠናቀቁ ናቸው።
በኢንጅነሪንግ፣ በጤና ሳይንስ እንዲሁም በቢዝነስና ማኅበራዊ ጥናት ዘርፎች ከተመረቁት የሀገር ውስጥ ተማሪዎች በተጨማሪ ከውጭ አገራት የመጡ ሰልጣኝ ተማሪዎች እንደሚገኙም ተገልጿል።
@tikvahuniversity
366 242
ስራ በዝቶብዎታል፣ ስብሰባ ላይ ነዎት ወይስ ትንሽ እረፍት መውሰድ ፈልገዋል? እንግዲያውስ ለሚደውልልዎ ሰው ሁሉ በራሱ ጊዜ አሁን ምን ላይ እንዳሉ መልዕክት ያስቀምጡና ያለምንም ረብሻ ስራዎን ያከናውኑ!
ለግል መልዕክት ወደ *723*2# እንዲሁም ለቢዝነስ መልዕክት ደግሞ ወደ *723*3# እንደውል!
#CallSignature
#Safaricom
366 242
11ኛ እና 12ኛ ዙር Software Development, Programming and Database ስልጠና ምዝገባ ላይ ነን።
👉 በተግባር ሶፍትዌር እያበለፀጉ የሚሰለጥኑበት
በስልጠናው የተካተቱ
👉 Foundation of Programming Using C++
👉 Java & Frontend Development using JavaFX
👉 Python & Backend Development using Django
👉 Database Systems, Architecture & Modeling
👉 PostgreSQL
ስልጠናው ሰኔ 29/2018 ዓ.ም ይጀምራል።
የበለጠ ይጠብቁ ...
💥 ሴጅ ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት 💥
☎️ 0906777799 / 0906777755
አድራሻ፦ ቁ.1: ፒያሣ ቸርችል ጎዳና ኤልያና ሆቴል 2ኛ ፎቅ፣ ቁ.2: መገናኛ ታሜጋስ ህንፃ 2ኛ ፎቅ እና ቁ.3: አዳማ ራስ ሆቴል 2ኛ ፎቅ
ለመመዝገብ ድረ-ገጽ 👇 www.sageethiopia.com
Telegram: https://t.me/sagetraininginstitute
Tiktok: https://www.tiktok.com/@sage_training_institute
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
