ch
Feedback
Tikvah-University

Tikvah-University

前往频道在 Telegram

📈 Telegram 频道 Tikvah-University 的分析概览

频道 Tikvah-University (@tikvahuniversity) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 381 068 名订阅者,在 教育 类别中位列第 114,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 13

📊 受众指标与增长动态

невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 381 068 名订阅者。

根据 01 九月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 11 442,过去 24 小时变化为 731,整体触达仍然可观。

  • 认证状态: 未认证
  • 互动率 (ER): 平均受众互动率为 19.41%。内容发布后 24 小时内通常能获得 11.34% 的反应,占订阅者总量。
  • 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 73 907 次浏览,首日通常累积 43 184 次浏览。
  • 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 172

📝 描述与内容策略

尚未提供频道描述。

凭借高频更新(最新数据采集于 02 九月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 教育 类别中的关键影响点。

381 068
订阅者
+73124 小时
+2 7267 天
+11 44230 天
帖子存档
በፌዴራል ልዩ አዳሪ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተመዝግባችሁ ለፈተና የተመረጣችሁ ተማሪዎች የሙከራ ፈተና ነገ ነሐሴ 28/2018 ዓ.ም ጠዋት 3:00 ጀምሮ የሚሰጥ በመሆኑ፤ በሚቀርባችሁ የፈተና መስጫ
በፌዴራል ልዩ አዳሪ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተመዝግባችሁ ለፈተና የተመረጣችሁ ተማሪዎች የሙከራ ፈተና ነገ ነሐሴ 28/2018 ዓ.ም ጠዋት 3:00 ጀምሮ የሚሰጥ በመሆኑ፤ በሚቀርባችሁ የፈተና መስጫ ማዕከል ከጠዋቱ 2:30 ተገኝታች የሙከራ ፈተናውን እድትወስዱ ትምህርት ሚኒስቴር አሳስቧል። Username እና Password መፈተኛ ማዕከሉ ስትደርሱ በጣቢያው ከሚመደቡ የፈተና ጣቢያ አስተባባሪዎች በኩል የምታገኙ መሆኑ ተገልጿል። @tikvahuniversity

#ጥቆማ በትምህርት ሚኒስቴር የመንግሥት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ፕሬዝዳንት እና ምክትል ፕሬዝዳንት አስያየም መመሪያ ቁጥር 1146/2018 መሰረት፤ ደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንቶችን አወ
+4
#ጥቆማ በትምህርት ሚኒስቴር የመንግሥት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ፕሬዝዳንት እና ምክትል ፕሬዝዳንት አስያየም መመሪያ ቁጥር 1146/2018 መሰረት፤ ደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንቶችን አወዳድሮ መመደብ ይፈልጋል፡፡ ዩኒቨርሲቲው ለውድድር ክፍት ያደረጋቸው የሥራ መደቦች፦ 1. የአካዳሚክ ምርምር፣ ቴክኖሎጂ ሽግግር እና ማኅበረሰብ አገልግሎት ምክትል ፕሬዝዳንት 2. የአስተዳደርና ልማት ምክትል ፕሬዝዳንት 3. ቺፍ ኤክስክዩቲቭ ዳይሬክተር ለጤና ሳይንስ ኮሌጅ (በምክትል ፕሬዝዳንት ማዕረግ) ለተጠቀሱት ክፍት የአመራር ቦታዎች ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት እንዲሁም ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ውጪ ባለ በመንግሥታዊና መንግሥታዊ ባልሆኑ መስሪያ ቤቶች እና ድርጅቶች ውስጥ የሚገኙ ተወዳዳሪዎችን መወዳደር ይችላሉ ተብሏል፡፡ (ለእያንዳንዱ የአመራር የሥራ መደብ የተቀመጡ ዝርዝር መስፈርቶችን ከላይ ከተያያዘው ምስል ይመለልከቱ፡፡) የምዝገባ ሁኔታ፦ ደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ፣ የብቃትና የሰው ሀብት አስተዳደር ሥራ አስፈፃሚ ህንፃ ቁ. 139፣ ቢሮ ቁ. 107 ወይም በኢሜይል አድራሻ፡ dtuhr2026@gmail.com ሰነዶችን በ PDF ፋይል በመላክ ወይም በፖ.ሳ.ቁ. 272 (ደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ) መመዝገብ ይቻላል፡፡ @tikvahuniversity

#EthiopianPoliceUniversity የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት ፕሮግራሞች ለ2019 የትምህርት ዘመን አዲስ ተማሪዎችን ተቀብሎ ለማስተማር የመግቢያ ፈተና ለመስጠት ዝግጅት
#EthiopianPoliceUniversity የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት ፕሮግራሞች ለ2019 የትምህርት ዘመን አዲስ ተማሪዎችን ተቀብሎ ለማስተማር የመግቢያ ፈተና ለመስጠት ዝግጅት ማጠናቀቁን ገልጿል። ይህ ማስታወቂያ በሁሉም የማስተርስ ዲግሪ፣ የቅድመ-ምረቃ ዲግሪ፣ የፖሊስ ሳይንስ ዲግሪ (ለሲቪል ተመልማዮች)፣ በደረጃ 4 (ክሊኒካል ነርሲንግ፣ ሜዲካል ላቦራቶሪ እና ፋርማሲ) እንዲሁም በሁሉም ዲፕሎማ (ፖሊስ ሳይንስ፣ ፖሊስ ኢንተለጀንስ እና አቪዬሽን ፖሊስ) ፕሮግራሞች የተመዘገባችሁ አመልካቾችን በሙሉ የሚመለከት መሆኑ ተገልጿል፡፡ የተፈታኞች የትምህርት ማስረጃ ማጣራትና ኦሬንቴሽን መስከረም 04 እና 05/2019 ዓ.ም ከጠዋቱ 2:30 እስከ 6:00 እንዲሁም ከሰዓት ከ8:00 እስከ 11:00 ሰዓት በየተመደቡበት ማዕከል የሚከናወን መሆኑ ተመላክቷል፡፡ የመግቢያ ፈተና መስከረም 06/2019 ዓ.ም ከጠዋቱ 3:00 እስከ 5:00 ሰዓት በሁሉም የፈተና ማዕከላት ይሰጣል ተብሏል። አመልካቾች አስፈላጊ የትምህርት ማስረጃችሁን ዋናውና ኮፒውን በመያዝ በተጠቀሱት ቀናት በፈተና ማዕከላት እንድትገኙ ዩኒቨርሲቲው አሳስቧል። @tikvahuniversity

#Pioneer_College 🔥 አስደሳች ዜና ከፓዩኒዬር ኮሌጅ የዕውቅና ፈቃድ ያለው ፓዩኒዬር ኮሌጅ፤ ለ2019 ዓ.ም ተማሪዎች ብቻ የሚያገለግል የትምህርት ክፍያ ዋጋ ቅናሽ አድርገናል❗️ ከትምህርት
#Pioneer_College 🔥 አስደሳች ዜና ከፓዩኒዬር ኮሌጅ    የዕውቅና ፈቃድ ያለው ፓዩኒዬር ኮሌጅ፤ ለ2019 ዓ.ም ተማሪዎች ብቻ የሚያገለግል የትምህርት ክፍያ ዋጋ ቅናሽ አድርገናል❗️ ከትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን ዕውቅና ባገኘንባቸው የዲግሪ ፕሮግራሞች፦ ► የሕክምና ዶክትሬት ► የጥርስ ሕክምና ዶክትሬት ► ፋርማሲ ► ሜዴካል ላብራቶሪ ሳይንስ 🔔 ምዝገባ ጀምረናል! በጤናው መስክ ተወዳደሪ ሆኖ ለመገኘት ካሰቡ አሁኑኑ ፓዩኒዬር ኮሌጅ ይመዝገቡ! አድራሻ ከጀርመን አደባባይ ወደ ለቡ መብራት በሚሰደው መንገድ ☎️  0902442244 / 0902443344 www.pioneercollege.edu.et

የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ በዓለም አቀፉ የኢንጂነሪንግና ቴክኖሎጂ ዕውቅና ሰጪ ቦርድ (ABET) ተጨማሪ ሁለት ፕሮግራሞቹ ሙሉ የጊዜ-ዑደት ዕውቅና አጊኝተዋል። ዩኒቨርሲቲው የኬሚካል
የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ በዓለም አቀፉ የኢንጂነሪንግና ቴክኖሎጂ ዕውቅና ሰጪ ቦርድ (ABET) ተጨማሪ ሁለት ፕሮግራሞቹ ሙሉ የጊዜ-ዑደት ዕውቅና አጊኝተዋል። ዩኒቨርሲቲው የኬሚካል ኢንጂነሪንግ እና የኢንቫይሮንመንታል ኢንጂነሪንግ የመጀመሪያ ዲግሪ ፕሮግራሞቹ እስከ መስከረም 19/2025 ዓ.ም ድረስ የሚቆይ ሙሉ የጊዜ-ዑደት ዕውቅና ማግኘታቸውን አሳውቋል። ከዚህ ቀደም የዩኒቨርሲቲው የባዮቴክኖሎጂ፣ የምግብ ሳይንስና አፕላይድ ኑትሪሽን፣ የጂኦሎጂ እና የኢንዱስትሪያል ኬሚስትሪ የመጀመሪያ ዲግሪ ፕሮግራሞቹ እስከ መስከረም 20/2024 ዓ.ም ድረስ የሚቆይ ዕውቅና ማግኘታቸው ይታወሳል። ዕውቅናዎቹ የዩኒቨርሲቲውን ዓለም አቀፍ የትምህርት ጥራት የሚያረጋግጥ መሆኑ ተገልጿል። @tikvahuniversity

#ሎርካን_ሜዲካል_ኮሌጅ የበርካታ ዓመታት ልምድ ባላቸው ሐኪሞችና ምሁራን ባለቤትነት የሚመራው ሎርካን ሜዲካል ኮሌጅ ምዝገባ ላይ ነው❗️ BSc Fields of Study: → Doctor of Medici
#ሎርካን_ሜዲካል_ኮሌጅ የበርካታ ዓመታት ልምድ ባላቸው ሐኪሞችና ምሁራን ባለቤትነት የሚመራው ሎርካን ሜዲካል ኮሌጅ ምዝገባ ላይ ነው❗️ BSc Fields of Study: → Doctor of Medicine → Doctor of Dental Medicine → Bachelor of Dental Science → Nursing TVET Programs: → Dental Therapy → Nursing → Medical Laboratory → Pharmacy → Radiography ⭐️ CPD ማዕከል አገልግሎት! ☎️ 0913398780 / 0911596059 አድራሻ፦ CMC አደባባይ ከፀሐይ ሪል እስቴት ጀርባ ከ ICMC ጠቅላላ ሆስፒታል አጠገብ 📍 Addis Ababa, CMC Square, Behind Tsehay Real Estate, next to ICMC General Hospital Facebook: https://www.facebook.com/Lorcanmedicalcollege Tiktok: https://www.tiktok.com/@lorcan.medical.co

በነሐሴ 2018 ዓ.ም የጤና ሙያ ፈቃድ ፈተና የወሰዱ የጤና ባለሙያዎች ውጤት ተለቋል፡፡ በነሐሴ 2018 ዓ.ም በጤና ሚኒስቴር የተሰጠውን የጤና ሙያ የብቃት መዘና ፈተና የወሰዳችሁ ተመዛኞች ከዛሬ ነ
በነሐሴ 2018 ዓ.ም የጤና ሙያ ፈቃድ ፈተና የወሰዱ የጤና ባለሙያዎች ውጤት ተለቋል፡፡ በነሐሴ 2018 ዓ.ም በጤና ሚኒስቴር የተሰጠውን የጤና ሙያ የብቃት መዘና ፈተና የወሰዳችሁ ተመዛኞች ከዛሬ ነሐሴ 27/2018 ዓ.ም ጀምሮ https://hple.moh.gov.et ላይ በመግባትና የብሔራዊ መለያ ቁጥር (FAN) እና Password በማስገባት የፈተና ውጤታችሁን መመልከት የምትችሉ መሆኑን ጤና ሚኒስቴር አሳውቋል፡፡ በውጤታችሁ ላይ ቅሬታ ያላችሁ ተመዛኞች ውጤት ከዛሬ ነሐሴ 27/2018 ዓ.ም ጀምሮ ባሉት 10 (አስር) ተከታታይ የሥራ ቀናት በስልክ ቁ. 952 በሥራ ሰዓት በመደወል ሙሉ ስም፣ ዲፓርትመንት እና የተማራችሁበትን የትምህርት ተቋም ስም በማሳወቅ ጥያቄዎቻችሁን ማቅረብ እንደምትችሉ ተገልጿል፡፡ በዚህ ዙር ለመጀመሪያ ጊዜ ተመዛኞች በተናጠል የውጤት ትንተና (Domain Analysis) ማየት እንደምትችሉ የተገለፀ ሲሆን፣ ይህም ራችሁን ለማሻሻልና የበለጠ ለማብቃት የሚያስችል ነው ተብሏል፡፡ የጤና ሙያ ፈቃድ ፈተናውን ያለፋችሁ ተመዛኞች ከሰኞ ዻጉሜን 02/2018 ዓ.ም ጀምሮ ስም ዝርዝራችሁ ወደ ክልል የሚላክ ስለሆነ የሙያ ፍቃዳችሁን 12ኛ ክፍል በተማራችሁበት ክልል ማውጣት የምትችሉ መሆኑን ሚኒስቱሩ አሳውቋል፡፡ @tikvahuniversity

#AAU_Undergraduate_Admission በ2019 የትምህርት ዘመን በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በቅድመ-ምረቃ ፕሮግራም ለመማር የምትፈልጉ አመልካቾች የምዝገባ ጊዜ አርብ ነሐሴ 29/2018 ዓ.ም
#AAU_Undergraduate_Admission በ2019 የትምህርት ዘመን በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በቅድመ-ምረቃ ፕሮግራም ለመማር የምትፈልጉ አመልካቾች የምዝገባ ጊዜ አርብ ነሐሴ 29/2018 ዓ.ም ይጠናቀቃል፡፡ በቀሩት ጥቂት ቀናት ምዝገባዎን ያድርጉ! ለተጨማሪ መረጃ 👇 https://admission.aau.edu.et/UGAnnouncements የዩኒቨርሲቲ የመግቢያ ፈተና (UAT) ከጳጉሜን 02-04/2018 ዓ.ም በየመረጣችሁበት የፈተና ማዕከል እንደሚሰጥ ዩነቨርሲቲው ገልጿል፡፡ @tikvahuniversity

#ጥቆማ የሐረር ሞዴል 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ለ2019 የትምህርት ዘመን የ9ኛ ክፍል ተማሪዎችን ‎በነጻ የትምህርት ዕድል ተቀብሎ ማስተማር ይፈልጋል። ‎ ‎በመሆኑም በሞዴል 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቱ
#ጥቆማ የሐረር ሞዴል 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ለ2019 የትምህርት ዘመን የ9ኛ ክፍል ተማሪዎችን ‎በነጻ የትምህርት ዕድል ተቀብሎ ማስተማር ይፈልጋል። ‎ ‎በመሆኑም በሞዴል 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቱ ለመማር ፍላጎት ያላችሁና መስፈርቱን የምታሟሉ ተማሪዎች በሐረሪ ክልል ትምህርት ቢሮ በመገኘት መመዝገብ የምትችሉ መሆኑ ተገልጿል። ‎ መስፈርቶች፦ ‌‌‎➻ ጥሩ ስነ-ምግባር ያለው/ያላት ➻ በ2018 ዓ.ም የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና በሐረሪ ክልል ተፈትኖ አማካይ ውጤት 70 እና በላይ ለሴቶች እና 75 እና በላይ ለወንዶች አማካይ ውጤት ያለው/ያላት ‎➻ በእንግሊዝኛ እና በሂሳብ ትምህርት አይነቶች ውጤት 70 እና በላይ ለሴቶች እና 75 እና በላይ በመቶ ለወንዶች አማካይ ውጤት ያለው/ያላት ‌‎➻ በ2017 እና 2018 የትምህርት ዘመን በ7ኛ እና 8ኛ ክፍል ትራንስክሪፕት 70 እና በላይ በመቶ ለሴቶች እና 75 እና በላይ በመቶ ለወንዶች አማካይ ውጤት ያለው/ያላት የምዝገባ ጊዜ 👇 ከነሐሴ 26/2018 ዓ.ም ጀምሮ @tikvahuniversity

🔔 የህክምና ትምህርትዎን በሀገር ውስጥ እና በዓለም አቀፍ ተቋማት ዕውቅና ባለው ሚዮንግሰንግ ሜዲካል ኮሌጅ ይማሩ! ► በዘመናዊ መልክ የተደራጀ ► የራሱ የሆነ ምቹ የተማሪዎች መኖሪያ ያለው ► የኮ
🔔 የህክምና ትምህርትዎን በሀገር ውስጥ እና በዓለም አቀፍ ተቋማት ዕውቅና ባለው ሚዮንግሰንግ ሜዲካል ኮሌጅ ይማሩ! ► በዘመናዊ መልክ የተደራጀ ► የራሱ የሆነ ምቹ የተማሪዎች መኖሪያ ያለው ► የኮሪያ ሆስፒታል እህት ኩባንያ 15ኛ ዙር የህክምና ትምህርት ምዝገባ ላይ ነን! 🎓 ኮሌጃችን ያስተማራቸውን ተማሪዎች በሙሉ የብቃት ምዘና ፈተና ማሳለፍ ችሏል! ለማመልከት 👇 https://maps.app.goo.gl/oxRezU99L2DqnngD6 አድራሻ፦ አዲስ አባባ፣ ገርጂ ኮሪያ ሆስፒታል ቅጥር ግቢ ሬጅስትራር ቢሮ የምዝገባ ጊዜ 👇 እስከ ጳጉሜን 02/2018 ዓ.ም ድረስ። አሁኑኑ ይመዝገቡ! ☎️ 0116395020 ድረ-ገጽ፦ www.mmc-edu.net Facebook: https://web.facebook.com/MMCmedcollege/ #MyungsungMedicalCollege

🌻 የአዲስ ዓመት 25% ቅናሽ ከነሐሴ 27/2018 ዓ.ም እስከ መስከረም 21/2019 ዓ.ም🌻 32ኛ ዙር የድረ-ገፅ እና ሞባይል መተግበሪያ ማበልፀግ (Full-Stack Website and Mobil
🌻 የአዲስ ዓመት 25% ቅናሽ ከነሐሴ 27/2018 ዓ.ም እስከ መስከረም 21/2019 ዓ.ም🌻 32ኛ ዙር የድረ-ገፅ እና ሞባይል መተግበሪያ ማበልፀግ (Full-Stack Website and Mobile Application Development) ስልጠና ምዝገባ ላይ ነን! 👉 ተግባርን ከንድፈ ሀሳብ ያስተሳሰረ ስልጠና 👉 Front-end እና Back-end በአንድ ላይ እስከ Deployment ያካተተ 👉 በተግባር ድረ-ገጾችን እና የሞባይል መተግበሪያዎችን እያበለፀጉ የሚሰለጥኑበት 👉 UI እና UX ዲዛይንን በፊግማ ያካተተ ስልጠና የበለጠ ይጠብቁ ... 💥 ሴጅ ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት 💥 ☎️  0906777799 / 0906777755 አድራሻ፦ ቁ.1: ፒያሣ ቸርችል ጎዳና ኤልያና ሆቴል 2ኛ ፎቅ፣ ቁ.2: መገናኛ ደራርቱ ህንፃ 5ኛ ፎቅ እና ቁ.3: አዳማ ራስ ሆቴል 2ኛ ፎቅ ለመመዝገብ ድረ-ገጽ 👇 www.sageethiopia.com Telegram: https://t.me/sagetraininginstitute Tiktok: https://www.tiktok.com/@sage_training_institute

#Update ትምህርት ሚኒስቴር ለ2019 የትምህርት ዘመን ትምህርት በሚሰጥባቸው ነባር እና አዲስ የፌዴራል ልዩ አዳሪ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የ9ኛ እና 10ኛ ክፍል ተማሪዎችን አወዳድሮ ለመቀበል
#Update ትምህርት ሚኒስቴር ለ2019 የትምህርት ዘመን ትምህርት በሚሰጥባቸው ነባር እና አዲስ የፌዴራል ልዩ አዳሪ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የ9ኛ እና 10ኛ ክፍል ተማሪዎችን አወዳድሮ ለመቀበል ባወጣው ማስታወቂያ መሰረት ተመዝግባችሁ በመጠባበቅ ላይ ያላችሁ ተማሪዎች የፈተና ፕሮግራም መውጣቱ ይታወቃል።   ይሁን እንጂ አንዳንድ ተማሪዎች የመፈተኛ ቦታቸውን ባለማወቃቸው ምክንያት የፈተና ቀኑን በአንድ ቀን ማራዘም አስፈላጊ ሆኖ መገኘቱን ሚኒስቴሩ ገልጿል።   🔔 በመሆኑም የሙከራ ፈተና ነሐሴ 28/2018 ዓ.ም እና ዋናው ፈተና ነሐሴ 29/2018 ዓ.ም የሚሰጥ መሆኑ ተገልጿል። በተገለፁት ቀናት ጠዋት 2:30 በየተመደባችሁባቸው ጣቢያዎች ራሳችሁን የሚገልፅ መታወቂያ በመያዝ እንድትገኙ ተብሏል። @tikvahuniversity

#Remedial_Complaint ዛሬ ይፋ ከተደረገው የ2018 ዓ.ም የሪሚዲያል ፕሮግራም ተማሪዎች ውጤት ጋር በተያያዘ እጅግ በርካታ ተማሪዎች ቅሬታቸውን ለቲክቫህ ዩኒቨርሲቲ አድርሰዋል። በርካታ ተማ
+4
#Remedial_Complaint ዛሬ ይፋ ከተደረገው የ2018 ዓ.ም የሪሚዲያል ፕሮግራም ተማሪዎች ውጤት ጋር በተያያዘ እጅግ በርካታ ተማሪዎች ቅሬታቸውን ለቲክቫህ ዩኒቨርሲቲ አድርሰዋል። በርካታ ተማሪዎች ውጤታቸው ሙሉ በሙሉ 'Disqualified' የተባለባቸው መሆኑን በመግለፅ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት እንዲሁም ትምህርት ሚኒስቴር ማብራሪያ እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል። ሌሎች በርካታ ተማሪዎች ደግሞ የሂሳብ ትምህርት ውጤታቸው ብቻ 'Disqualified' እንደሚል ገልፀዋል። የተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች ተማሪዎች የሆኑት ቅሬታ አቅራቢዎቹ፤ "በፈተና ወቅት ምንም አይነት የስነ-ምግባር ግድፈት አልፈፀንም" በማለት በእርማት ወቅት ቴክኒካል ችግር ከነበረ እንዲታይላቸው በትህትና ጠይቀዋል። ቅሬታችሁን በኦንላይን አስገቡ 👇 https://result.ethernet.edu.et ከውጤታችሁ ስር መጨረሻ ላይ ያለውን Submit Complaint የሚለውን ይጫኑ፣ Select a category የሚለውን ይክፈቱ፣ My result disqualified without reason የሚለውን ይምረጡ፣ አጠር ያለ መግለጫ ይፃፉ፣ የስልክ ቁጥርዎን ይሙሉ እና Submit Complaint የሚለውን በመጫን ቅሬታዎን ያስገቡ። የሪሚዲያል ፕሮግራም የማለፊያ ነጥብ 250 ለተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች (5 የትምህርት አይነቶች) እና 200 ለማኅበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች (4 የትምህርት አይነቶች) መሆኑ ታውቋል። የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት እንዲሁም ትምህርት ሚኒስቴር በተማሪዎቹ በቀረቡ ቅሬታዎች ላይ የሚሰጡትን ምላሽ ቲክቫህ ዩኒቨርሲቲ የሚያደርሳችሁ ይሆናል። @tikvahuniversity

በሀገር አቀፍ ደረጃ በተካሔደ የተማሪዎች የእርካታ ዳሰሳ ጥናት እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ቀዳሚ ደረጃን አጊኝቷል፡፡ በትምህርት ሚኒስቴር አስተባባሪነት በተካሔደው የተማሪዎች የእርካታ ዳሰሳ ጥናት (Stud
+3
በሀገር አቀፍ ደረጃ በተካሔደ የተማሪዎች የእርካታ ዳሰሳ ጥናት እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ቀዳሚ ደረጃን አጊኝቷል፡፡ በትምህርት ሚኒስቴር አስተባባሪነት በተካሔደው የተማሪዎች የእርካታ ዳሰሳ ጥናት (Students' Satisfaction Survey)፤ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ 1ኛ ደረጃ በመውጣት በተማሪዎች ተመራጭ ሆኗል። ኦዳ ቡልቱም ዩኒቨርሲቲ 2ኛ ደረጃ እና ወልድያ ዩኒቨርሲቲ 3ኛ ደረጃን አጊኝተዋል። ጥናቱ ዩኒቨርሲቲዎች ለተማሪዎች የሚያቀርቧቸው የምኝታ እና የምግብ አገልግሎቶች፣ የትምህርት ጥራት፣ የአመራር እና የመምህራንን ተደራሽነት፣ የግቢ ውበት እና ምቹነት፣ እንዲሁም የግቢ ሠላምና ደኅንነት መሠረት ያደረጉ መለኪያዎችን ማካተቱ ታውቋል። (ምስል፦ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ) @tikvahuniversity

ትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት አመራሮች አቅም ግንባታ፣ የፖሊሲ ጥናቶች ውጤት እና ዓመታዊ የሥራ አፈጻጸም አውደጥናት እያካሔደ ነው፡፡ ትናንት የተጀመረውና በአገራዊ የከፍተኛ ትምህርት ጉዳዮች
+1
ትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት አመራሮች አቅም ግንባታ፣ የፖሊሲ ጥናቶች ውጤት እና ዓመታዊ የሥራ አፈጻጸም አውደጥናት እያካሔደ ነው፡፡ ትናንት የተጀመረውና በአገራዊ የከፍተኛ ትምህርት ጉዳዮች ላይ እየመከረ ያለው አውደጥናቱ፤ እስከ ነገ ነሐሴ 27/2018 ዓ.ም ይቆያል። የአውደጥናቱ አበይት አጀንዳዎች፦ ➻ የከፍተኛ ት/ት ተቋማት ሪፎርም ሥራዎች ➻ የመውጫ ፈተና አፈፃፀም ➻ የድህረ-ምረቃ ተማሪዎች የትምህርት ወጪ ➻ የተመራቂ ተማሪዎች የመቀጠር ምጣኔ ➻ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የእርካታ ዳሰሳ ጥናት የዩኒቨርሲቲ ሥራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢዎች፣ የዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንቶች፣ ምክትል ፕሬዝዳንቶች እና አጋር አካላት በአውደጥናቱ በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ። አውደጥናቱ ትምህርት ሚኒስቴር ከማስተር ካርድ ፋውንዴሽን፣ ከአሪዞና ዩኒቨርሲቲ እና ከሽያሾኔ ተቋም ጋር በመተባበር የተዘጋጀ መሆኑ ተገልጿል፡፡ @tikvahuniversity

🔔 የህክምና ትምህርትዎን በሀገር ውስጥ እና በዓለም አቀፍ ተቋማት ዕውቅና ባለው ሚዮንግሰንግ ሜዲካል ኮሌጅ ይማሩ! ► በዘመናዊ መልክ የተደራጀ ► የራሱ የሆነ ምቹ የተማሪዎች መኖሪያ ያለው ► የኮ
🔔 የህክምና ትምህርትዎን በሀገር ውስጥ እና በዓለም አቀፍ ተቋማት ዕውቅና ባለው ሚዮንግሰንግ ሜዲካል ኮሌጅ ይማሩ! ► በዘመናዊ መልክ የተደራጀ ► የራሱ የሆነ ምቹ የተማሪዎች መኖሪያ ያለው ► የኮሪያ ሆስፒታል እህት ኩባንያ 15ኛ ዙር የህክምና ትምህርት ምዝገባ ላይ ነን! 🎓 ኮሌጃችን ያስተማራቸውን ተማሪዎች በሙሉ የብቃት ምዘና ፈተና ማሳለፍ ችሏል! ለማመልከት 👇 https://maps.app.goo.gl/oxRezU99L2DqnngD6 አድራሻ፦ አዲስ አባባ፣ ገርጂ ኮሪያ ሆስፒታል ቅጥር ግቢ ሬጅስትራር ቢሮ የምዝገባ ጊዜ 👇 እስከ ጳጉሜን 02/2018 ዓ.ም ድረስ። አሁኑኑ ይመዝገቡ! ☎️ 0116395020 ድረ-ገጽ፦ www.mmc-edu.net Facebook: https://web.facebook.com/MMCmedcollege/ #MyungsungMedicalCollege

#RemedialResult በ2018 ዓ.ም የሪሚዲያል ፕሮግራም ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የቆዩ ተማሪዎች ውጤት ተለቋል። https://result.ethernet.edu.et ላይ በመግባት Remedial Ex
#RemedialResult በ2018 ዓ.ም የሪሚዲያል ፕሮግራም ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የቆዩ ተማሪዎች ውጤት ተለቋል። https://result.ethernet.edu.et ላይ በመግባት Remedial Examination ከሚለው ስር View Results የሚለውን በመጫንና Username በማስገባት ውጤትዎን ይመልከቱ። ከግንቦት 27 እስከ ሰኔ 03/2018 ዓ.ም የተሰጠውን ሀገር አቀፍ የሪሚዲያል ፕሮግራም ፈተና 53,620 ተፈታኞች መውሰዳቸውን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት መግለፁ ይታወሳል። @tikvahuniversity

#ጥቆማ የአማራ ክልል ስቴት ዩኒቨርሲቲ በ2ኛ ዲግሪ በመደበኛ እና በኤክስቴንሽን መርሐግብር እንዲሁም በ3ኛ ዲግሪ በመደበኛ መርሐግብር በተመረጡ የትምህርት ፕሮግራሞች ተማሪዎችን ተቀብሎ ማስተማር ይፈ
#ጥቆማ የአማራ ክልል ስቴት ዩኒቨርሲቲ በ2ኛ ዲግሪ በመደበኛ እና በኤክስቴንሽን መርሐግብር እንዲሁም በ3ኛ ዲግሪ በመደበኛ መርሐግብር በተመረጡ የትምህርት ፕሮግራሞች ተማሪዎችን ተቀብሎ ማስተማር ይፈልጋል፡፡ በ3ኛ ዲግሪ የሚሰጡ የትምህርት ፕሮግራሞች ➫ PhD in Public Policy and Leadership ➫ PhD in Political Economy and Governance ➫ PhD in Peace and Security Studies በ2ኛ ዲግሪ የሚሰጡ የትምህርት ፕሮግራሞች ➫ Masters of Business Administration ➫ MSc in Project Management ➫ MA in Public Policy and Leadership ➫ MA in Political Economy ➫ MA in Peace and Development ➫ LLM in Law and Economics ➫ MA in Urban Governance and Leadership በ2019 የትምህርት ዘመን በግል ወይም በተቋማት ስፖንሰርሺፕ ትምህርት ለመማር ፍላጎት ያላችሁና ሀገር አቀፍ የድኅረ-ምረቃ መግቢያ ፈተና (NGAT) ተፈትናችሁ ያለፋችሁ በዩኒቨርሲቲው ሬጅስትራር ቢሮ ቁጥር 10 በመቅረብ ወይም በ https://forms.gle/j6owxvQw36rjMTG9A መመዝገብ የምትችሉ መሆኑ ተገልጿል፡፡ የምዝገባ ጊዜ 👇 ከነሐሴ 25/2018 ዓ.ም እስከ መስከረም 30/2019 ዓ.ም @tikvahuniversity

#Pioneer_College 🔥 አስደሳች ዜና ከፓዩኒዬር ኮሌጅ የዕውቅና ፈቃድ ያለው ፓዩኒዬር ኮሌጅ፤ ለ2019 ዓ.ም ተማሪዎች ብቻ የሚያገለግል የትምህርት ክፍያ ዋጋ ቅናሽ አድርገናል❗️ ከትምህርት
#Pioneer_College 🔥 አስደሳች ዜና ከፓዩኒዬር ኮሌጅ    የዕውቅና ፈቃድ ያለው ፓዩኒዬር ኮሌጅ፤ ለ2019 ዓ.ም ተማሪዎች ብቻ የሚያገለግል የትምህርት ክፍያ ዋጋ ቅናሽ አድርገናል❗️ ከትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን ዕውቅና ባገኘንባቸው የዲግሪ ፕሮግራሞች፦ ► የሕክምና ዶክትሬት ► የጥርስ ሕክምና ዶክትሬት ► ፋርማሲ ► ሜዴካል ላብራቶሪ ሳይንስ 🔔 ምዝገባ ጀምረናል! በጤናው መስክ ተወዳደሪ ሆኖ ለመገኘት ካሰቡ አሁኑኑ ፓዩኒዬር ኮሌጅ ይመዝገቡ! አድራሻ ከጀርመን አደባባይ ወደ ለቡ መብራት በሚሰደው መንገድ ☎️  0902442244 / 0902443344 www.pioneercollege.edu.et

🌻 የአዲስ ዓመት 25% ቅናሽ ከነሐሴ 27/2018 ዓ.ም እስከ መስከረም 21/2019 ዓ.ም🌻 89ኛ ዙር የግራፊክ ዲዛይን፣ ቪዲዮ ኤዲቲንግ እና ሞሽን ግራፊክ ስልጠና ምዝገባ ላይ ነን! 👉 ተግባ
🌻 የአዲስ ዓመት 25% ቅናሽ ከነሐሴ 27/2018 ዓ.ም እስከ መስከረም 21/2019 ዓ.ም🌻 89ኛ ዙር የግራፊክ ዲዛይን፣ ቪዲዮ ኤዲቲንግ እና  ሞሽን ግራፊክ ስልጠና ምዝገባ ላይ ነን! 👉 ተግባርን ከንድፈ ሀሳብ ያስተሳሰረ ስልጠና 👉 Advanced Graphic + Video Editing + Motion Graphic በአንድ ላይ 👉 ከ50 በላይ ፕሮጀክቶች ያሉት የበለጠ ይጠብቁ ... 💥 ሴጅ ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት 💥 ☎️  0906777799 / 0906777755 አድራሻ፦ ቁ.1: ፒያሣ ቸርችል ጎዳና ኤልያና ሆቴል 2ኛ ፎቅ፣ ቁ.2: መገናኛ ደራርቱ ህንፃ 5ኛ ፎቅ እና ቁ.3: አዳማ ራስ ሆቴል 2ኛ ፎቅ ለመመዝገብ ድረ-ገጽ 👇 www.sageethiopia.com Telegram: https://t.me/sagetraininginstitute Tiktok: https://www.tiktok.com/@sage_training_institute