es
Feedback
Tikvah-University

Tikvah-University

Ir al canal en Telegram

📈 Análisis del canal de Telegram Tikvah-University

El canal Tikvah-University (@tikvahuniversity) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 380 835 suscriptores, ocupando la posición 114 en la categoría Educación y el puesto 13 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 380 835 suscriptores.

Según los últimos datos del 01 septiembre, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de 11 442, y en las últimas 24 horas de 731, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificación: No verificado
  • Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 19.41%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 11.34% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 73 907 visualizaciones. En el primer día suele acumular 43 184 visualizaciones.
  • Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 172.

📝 Descripción y política de contenido

No se ha proporcionado la descripción del canal.

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 02 septiembre, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Educación.

380 835
Suscriptores
+73124 horas
+2 7267 días
+11 44230 días
Archivo de publicaciones
#Update ትምህርት ሚኒስቴር ለ2019 የትምህርት ዘመን ትምህርት በሚሰጥባቸው ነባር እና አዲስ የፌዴራል ልዩ አዳሪ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የ9ኛ እና 10ኛ ክፍል ተማሪዎችን አወዳድሮ ለመቀበል
#Update ትምህርት ሚኒስቴር ለ2019 የትምህርት ዘመን ትምህርት በሚሰጥባቸው ነባር እና አዲስ የፌዴራል ልዩ አዳሪ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የ9ኛ እና 10ኛ ክፍል ተማሪዎችን አወዳድሮ ለመቀበል ባወጣው ማስታወቂያ መሰረት ተመዝግባችሁ በመጠባበቅ ላይ ያላችሁ ተማሪዎች የፈተና ፕሮግራም መውጣቱ ይታወቃል።   ይሁን እንጂ አንዳንድ ተማሪዎች የመፈተኛ ቦታቸውን ባለማወቃቸው ምክንያት የፈተና ቀኑን በአንድ ቀን ማራዘም አስፈላጊ ሆኖ መገኘቱን ሚኒስቴሩ ገልጿል።   🔔 በመሆኑም የሙከራ ፈተና ነሐሴ 28/2018 ዓ.ም እና ዋናው ፈተና ነሐሴ 29/2018 ዓ.ም የሚሰጥ መሆኑ ተገልጿል። በተገለፁት ቀናት ጠዋት 2:30 በየተመደባችሁባቸው ጣቢያዎች ራሳችሁን የሚገልፅ መታወቂያ በመያዝ እንድትገኙ ተብሏል። @tikvahuniversity

#Remedial_Complaint ዛሬ ይፋ ከተደረገው የ2018 ዓ.ም የሪሚዲያል ፕሮግራም ተማሪዎች ውጤት ጋር በተያያዘ እጅግ በርካታ ተማሪዎች ቅሬታቸውን ለቲክቫህ ዩኒቨርሲቲ አድርሰዋል። በርካታ ተማ
+4
#Remedial_Complaint ዛሬ ይፋ ከተደረገው የ2018 ዓ.ም የሪሚዲያል ፕሮግራም ተማሪዎች ውጤት ጋር በተያያዘ እጅግ በርካታ ተማሪዎች ቅሬታቸውን ለቲክቫህ ዩኒቨርሲቲ አድርሰዋል። በርካታ ተማሪዎች ውጤታቸው ሙሉ በሙሉ 'Disqualified' የተባለባቸው መሆኑን በመግለፅ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት እንዲሁም ትምህርት ሚኒስቴር ማብራሪያ እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል። ሌሎች በርካታ ተማሪዎች ደግሞ የሂሳብ ትምህርት ውጤታቸው ብቻ 'Disqualified' እንደሚል ገልፀዋል። የተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች ተማሪዎች የሆኑት ቅሬታ አቅራቢዎቹ፤ "በፈተና ወቅት ምንም አይነት የስነ-ምግባር ግድፈት አልፈፀንም" በማለት በእርማት ወቅት ቴክኒካል ችግር ከነበረ እንዲታይላቸው በትህትና ጠይቀዋል። ቅሬታችሁን በኦንላይን አስገቡ 👇 https://result.ethernet.edu.et ከውጤታችሁ ስር መጨረሻ ላይ ያለውን Submit Complaint የሚለውን ይጫኑ፣ Select a category የሚለውን ይክፈቱ፣ My result disqualified without reason የሚለውን ይምረጡ፣ አጠር ያለ መግለጫ ይፃፉ፣ የስልክ ቁጥርዎን ይሙሉ እና Submit Complaint የሚለውን በመጫን ቅሬታዎን ያስገቡ። የሪሚዲያል ፕሮግራም የማለፊያ ነጥብ 250 ለተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች (5 የትምህርት አይነቶች) እና 200 ለማኅበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች (4 የትምህርት አይነቶች) መሆኑ ታውቋል። የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት እንዲሁም ትምህርት ሚኒስቴር በተማሪዎቹ በቀረቡ ቅሬታዎች ላይ የሚሰጡትን ምላሽ ቲክቫህ ዩኒቨርሲቲ የሚያደርሳችሁ ይሆናል። @tikvahuniversity

በሀገር አቀፍ ደረጃ በተካሔደ የተማሪዎች የእርካታ ዳሰሳ ጥናት እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ቀዳሚ ደረጃን አጊኝቷል፡፡ በትምህርት ሚኒስቴር አስተባባሪነት በተካሔደው የተማሪዎች የእርካታ ዳሰሳ ጥናት (Stud
+3
በሀገር አቀፍ ደረጃ በተካሔደ የተማሪዎች የእርካታ ዳሰሳ ጥናት እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ቀዳሚ ደረጃን አጊኝቷል፡፡ በትምህርት ሚኒስቴር አስተባባሪነት በተካሔደው የተማሪዎች የእርካታ ዳሰሳ ጥናት (Students' Satisfaction Survey)፤ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ 1ኛ ደረጃ በመውጣት በተማሪዎች ተመራጭ ሆኗል። ኦዳ ቡልቱም ዩኒቨርሲቲ 2ኛ ደረጃ እና ወልድያ ዩኒቨርሲቲ 3ኛ ደረጃን አጊኝተዋል። ጥናቱ ዩኒቨርሲቲዎች ለተማሪዎች የሚያቀርቧቸው የምኝታ እና የምግብ አገልግሎቶች፣ የትምህርት ጥራት፣ የአመራር እና የመምህራንን ተደራሽነት፣ የግቢ ውበት እና ምቹነት፣ እንዲሁም የግቢ ሠላምና ደኅንነት መሠረት ያደረጉ መለኪያዎችን ማካተቱ ታውቋል። (ምስል፦ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ) @tikvahuniversity

ትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት አመራሮች አቅም ግንባታ፣ የፖሊሲ ጥናቶች ውጤት እና ዓመታዊ የሥራ አፈጻጸም አውደጥናት እያካሔደ ነው፡፡ ትናንት የተጀመረውና በአገራዊ የከፍተኛ ትምህርት ጉዳዮች
+1
ትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት አመራሮች አቅም ግንባታ፣ የፖሊሲ ጥናቶች ውጤት እና ዓመታዊ የሥራ አፈጻጸም አውደጥናት እያካሔደ ነው፡፡ ትናንት የተጀመረውና በአገራዊ የከፍተኛ ትምህርት ጉዳዮች ላይ እየመከረ ያለው አውደጥናቱ፤ እስከ ነገ ነሐሴ 27/2018 ዓ.ም ይቆያል። የአውደጥናቱ አበይት አጀንዳዎች፦ ➻ የከፍተኛ ት/ት ተቋማት ሪፎርም ሥራዎች ➻ የመውጫ ፈተና አፈፃፀም ➻ የድህረ-ምረቃ ተማሪዎች የትምህርት ወጪ ➻ የተመራቂ ተማሪዎች የመቀጠር ምጣኔ ➻ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የእርካታ ዳሰሳ ጥናት የዩኒቨርሲቲ ሥራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢዎች፣ የዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንቶች፣ ምክትል ፕሬዝዳንቶች እና አጋር አካላት በአውደጥናቱ በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ። አውደጥናቱ ትምህርት ሚኒስቴር ከማስተር ካርድ ፋውንዴሽን፣ ከአሪዞና ዩኒቨርሲቲ እና ከሽያሾኔ ተቋም ጋር በመተባበር የተዘጋጀ መሆኑ ተገልጿል፡፡ @tikvahuniversity

🔔 የህክምና ትምህርትዎን በሀገር ውስጥ እና በዓለም አቀፍ ተቋማት ዕውቅና ባለው ሚዮንግሰንግ ሜዲካል ኮሌጅ ይማሩ! ► በዘመናዊ መልክ የተደራጀ ► የራሱ የሆነ ምቹ የተማሪዎች መኖሪያ ያለው ► የኮ
🔔 የህክምና ትምህርትዎን በሀገር ውስጥ እና በዓለም አቀፍ ተቋማት ዕውቅና ባለው ሚዮንግሰንግ ሜዲካል ኮሌጅ ይማሩ! ► በዘመናዊ መልክ የተደራጀ ► የራሱ የሆነ ምቹ የተማሪዎች መኖሪያ ያለው ► የኮሪያ ሆስፒታል እህት ኩባንያ 15ኛ ዙር የህክምና ትምህርት ምዝገባ ላይ ነን! 🎓 ኮሌጃችን ያስተማራቸውን ተማሪዎች በሙሉ የብቃት ምዘና ፈተና ማሳለፍ ችሏል! ለማመልከት 👇 https://maps.app.goo.gl/oxRezU99L2DqnngD6 አድራሻ፦ አዲስ አባባ፣ ገርጂ ኮሪያ ሆስፒታል ቅጥር ግቢ ሬጅስትራር ቢሮ የምዝገባ ጊዜ 👇 እስከ ጳጉሜን 02/2018 ዓ.ም ድረስ። አሁኑኑ ይመዝገቡ! ☎️ 0116395020 ድረ-ገጽ፦ www.mmc-edu.net Facebook: https://web.facebook.com/MMCmedcollege/ #MyungsungMedicalCollege

#RemedialResult በ2018 ዓ.ም የሪሚዲያል ፕሮግራም ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የቆዩ ተማሪዎች ውጤት ተለቋል። https://result.ethernet.edu.et ላይ በመግባት Remedial Ex
#RemedialResult በ2018 ዓ.ም የሪሚዲያል ፕሮግራም ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የቆዩ ተማሪዎች ውጤት ተለቋል። https://result.ethernet.edu.et ላይ በመግባት Remedial Examination ከሚለው ስር View Results የሚለውን በመጫንና Username በማስገባት ውጤትዎን ይመልከቱ። ከግንቦት 27 እስከ ሰኔ 03/2018 ዓ.ም የተሰጠውን ሀገር አቀፍ የሪሚዲያል ፕሮግራም ፈተና 53,620 ተፈታኞች መውሰዳቸውን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት መግለፁ ይታወሳል። @tikvahuniversity

#ጥቆማ የአማራ ክልል ስቴት ዩኒቨርሲቲ በ2ኛ ዲግሪ በመደበኛ እና በኤክስቴንሽን መርሐግብር እንዲሁም በ3ኛ ዲግሪ በመደበኛ መርሐግብር በተመረጡ የትምህርት ፕሮግራሞች ተማሪዎችን ተቀብሎ ማስተማር ይፈ
#ጥቆማ የአማራ ክልል ስቴት ዩኒቨርሲቲ በ2ኛ ዲግሪ በመደበኛ እና በኤክስቴንሽን መርሐግብር እንዲሁም በ3ኛ ዲግሪ በመደበኛ መርሐግብር በተመረጡ የትምህርት ፕሮግራሞች ተማሪዎችን ተቀብሎ ማስተማር ይፈልጋል፡፡ በ3ኛ ዲግሪ የሚሰጡ የትምህርት ፕሮግራሞች ➫ PhD in Public Policy and Leadership ➫ PhD in Political Economy and Governance ➫ PhD in Peace and Security Studies በ2ኛ ዲግሪ የሚሰጡ የትምህርት ፕሮግራሞች ➫ Masters of Business Administration ➫ MSc in Project Management ➫ MA in Public Policy and Leadership ➫ MA in Political Economy ➫ MA in Peace and Development ➫ LLM in Law and Economics ➫ MA in Urban Governance and Leadership በ2019 የትምህርት ዘመን በግል ወይም በተቋማት ስፖንሰርሺፕ ትምህርት ለመማር ፍላጎት ያላችሁና ሀገር አቀፍ የድኅረ-ምረቃ መግቢያ ፈተና (NGAT) ተፈትናችሁ ያለፋችሁ በዩኒቨርሲቲው ሬጅስትራር ቢሮ ቁጥር 10 በመቅረብ ወይም በ https://forms.gle/j6owxvQw36rjMTG9A መመዝገብ የምትችሉ መሆኑ ተገልጿል፡፡ የምዝገባ ጊዜ 👇 ከነሐሴ 25/2018 ዓ.ም እስከ መስከረም 30/2019 ዓ.ም @tikvahuniversity

#Pioneer_College 🔥 አስደሳች ዜና ከፓዩኒዬር ኮሌጅ የዕውቅና ፈቃድ ያለው ፓዩኒዬር ኮሌጅ፤ ለ2019 ዓ.ም ተማሪዎች ብቻ የሚያገለግል የትምህርት ክፍያ ዋጋ ቅናሽ አድርገናል❗️ ከትምህርት
#Pioneer_College 🔥 አስደሳች ዜና ከፓዩኒዬር ኮሌጅ    የዕውቅና ፈቃድ ያለው ፓዩኒዬር ኮሌጅ፤ ለ2019 ዓ.ም ተማሪዎች ብቻ የሚያገለግል የትምህርት ክፍያ ዋጋ ቅናሽ አድርገናል❗️ ከትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን ዕውቅና ባገኘንባቸው የዲግሪ ፕሮግራሞች፦ ► የሕክምና ዶክትሬት ► የጥርስ ሕክምና ዶክትሬት ► ፋርማሲ ► ሜዴካል ላብራቶሪ ሳይንስ 🔔 ምዝገባ ጀምረናል! በጤናው መስክ ተወዳደሪ ሆኖ ለመገኘት ካሰቡ አሁኑኑ ፓዩኒዬር ኮሌጅ ይመዝገቡ! አድራሻ ከጀርመን አደባባይ ወደ ለቡ መብራት በሚሰደው መንገድ ☎️  0902442244 / 0902443344 www.pioneercollege.edu.et

🌻 የአዲስ ዓመት 25% ቅናሽ ከነሐሴ 27/2018 ዓ.ም እስከ መስከረም 21/2019 ዓ.ም🌻 89ኛ ዙር የግራፊክ ዲዛይን፣ ቪዲዮ ኤዲቲንግ እና ሞሽን ግራፊክ ስልጠና ምዝገባ ላይ ነን! 👉 ተግባ
🌻 የአዲስ ዓመት 25% ቅናሽ ከነሐሴ 27/2018 ዓ.ም እስከ መስከረም 21/2019 ዓ.ም🌻 89ኛ ዙር የግራፊክ ዲዛይን፣ ቪዲዮ ኤዲቲንግ እና  ሞሽን ግራፊክ ስልጠና ምዝገባ ላይ ነን! 👉 ተግባርን ከንድፈ ሀሳብ ያስተሳሰረ ስልጠና 👉 Advanced Graphic + Video Editing + Motion Graphic በአንድ ላይ 👉 ከ50 በላይ ፕሮጀክቶች ያሉት የበለጠ ይጠብቁ ... 💥 ሴጅ ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት 💥 ☎️  0906777799 / 0906777755 አድራሻ፦ ቁ.1: ፒያሣ ቸርችል ጎዳና ኤልያና ሆቴል 2ኛ ፎቅ፣ ቁ.2: መገናኛ ደራርቱ ህንፃ 5ኛ ፎቅ እና ቁ.3: አዳማ ራስ ሆቴል 2ኛ ፎቅ ለመመዝገብ ድረ-ገጽ 👇 www.sageethiopia.com Telegram: https://t.me/sagetraininginstitute Tiktok: https://www.tiktok.com/@sage_training_institute

የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ልዩ የስኮላርሺፕ ዕድል ለመምህራን ትምህርት አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በ2019 የትምህርት ዘመን ልዩ የስኮላርሺፕ ዕድል ለ500 የቅድመ-ምረቃ ተማሪዎች #በመምህራን_ትምህርት
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ልዩ የስኮላርሺፕ ዕድል ለመምህራን ትምህርት አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በ2019 የትምህርት ዘመን ልዩ የስኮላርሺፕ ዕድል ለ500 የቅድመ-ምረቃ ተማሪዎች #በመምህራን_ትምህርት መስኮች አዘጋጅቷል። የስኮላርሺፑ ተጠቃሚ ሁሉንም መመዘኛ ያሟሉ እና ዩኒቨርሲቲው ያዘጋጀውን የመግቢያ ፈተና በብቃት አልፈው አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲን የተቀላቀሉ መሆን ይጠበቅባቸዋል። የዚህ ስኮላርሺፕ ዕድል ተጠቃሚዎች በተፈጥሮ እና ኮምፕዩቴሽናል ሳይንስ የትምህርት መስክ (በፊዚክስ፣ በኬምስትሪ፣ በባዮሎጂ እና በሂሳብ) እንዲሁም በማኅበራዊ ሳይንስ የትምህርት መስክ (በእንግሊዘኛ፣ በኢኮኖሚክስ፣ በታሪክ እና በጂኦግራፊ የመምህርነት ትምህርት) የሚከታተሉ ይሆናሉ። የስኮላርሽፕ ተጠቃሚዎች ሙሉ ነፃ የትምህርት ዕድል፣ መጠነኛ የኪስ ገንዘብ እና ከአጋር ተቋማት ጋር በሚኖር ትብብር ተጨማሪ የስልጠና ዕድሎችን እንደሚያገኙ ተገልጿል። የዚህ ልዩ ዕድል ተጠቃሚ መሆን የምትፈልጉና ከስልጠና በኋላ በመምህርነት ለማገልገል የምትሹ ሁሉ ከቅበላ በኋላ ውል ፈርማችሁ ትምህርታችሁን መከታተል የምትችሉ መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል። የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የቅድመ-ምረቃ ፕሮግራሞች የ2019 ዓ.ም ምዝገባ እስከ ነሐሴ 29/2018 ዓ.ም እንደሚከናወን መገለፁ ይታወቃል፡፡ ለተጨማሪ መረጃ 👇 https://admission.aau.edu.et/UGAnnouncements @tikvahuniversity

🔔 የህክምና ትምህርትዎን በሀገር ውስጥ እና በዓለም አቀፍ ተቋማት ዕውቅና ባለው ሚዮንግሰንግ ሜዲካል ኮሌጅ ይማሩ! ► በዘመናዊ መልክ የተደራጀ ► የራሱ የሆነ ምቹ የተማሪዎች መኖሪያ ያለው ► የኮ
🔔 የህክምና ትምህርትዎን በሀገር ውስጥ እና በዓለም አቀፍ ተቋማት ዕውቅና ባለው ሚዮንግሰንግ ሜዲካል ኮሌጅ ይማሩ! ► በዘመናዊ መልክ የተደራጀ ► የራሱ የሆነ ምቹ የተማሪዎች መኖሪያ ያለው ► የኮሪያ ሆስፒታል እህት ኩባንያ 15ኛ ዙር የህክምና ትምህርት ምዝገባ ላይ ነን! 🎓 ኮሌጃችን ያስተማራቸውን ተማሪዎች በሙሉ የብቃት ምዘና ፈተና ማሳለፍ ችሏል! ለማመልከት 👇 https://maps.app.goo.gl/oxRezU99L2DqnngD6 አድራሻ፦ አዲስ አባባ፣ ገርጂ ኮሪያ ሆስፒታል ቅጥር ግቢ ሬጅስትራር ቢሮ የምዝገባ ጊዜ 👇 እስከ ጳጉሜን 02/2018 ዓ.ም ድረስ። አሁኑኑ ይመዝገቡ! ☎️ 0116395020 ድረ-ገጽ፦ www.mmc-edu.net Facebook: https://web.facebook.com/MMCmedcollege/ #MyungsungMedicalCollege

ትምህርት ሚኒስቴር ለ2019 የትምህርት ዘመን ትምህርት በሚሰጥባቸው ነባር እና አዲስ የፌዴራል ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤቶች የ9ኛ እና 10ኛ ክፍል ተማሪዎችን አወዳድሮ ለመቀበል ባወጣው ማስታወቂያ መሰ
ትምህርት ሚኒስቴር ለ2019 የትምህርት ዘመን ትምህርት በሚሰጥባቸው ነባር እና አዲስ የፌዴራል ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤቶች የ9ኛ እና 10ኛ ክፍል ተማሪዎችን አወዳድሮ ለመቀበል ባወጣው ማስታወቂያ መሰረት ለፈተና የሚቀርቡ ተማሪዎችን መልምሎ ይፋ ማድረጉ ይታወቃል።   በአመላመሉ ሒደቱ ላይ ቅሬታ ያላችሁ ተመዝጋቢ ተማሪዎች፣ በተመዘገባችሁበት ሊንክ (https://sbs.moe.gov.et/apply) በመግባትና Complaint የሚለውን በመጫን ቅሬታችሁን ማስገባት የምትችሉ መሆኑን ሚኒስቴሩ ገልጿል። @tikvahuniversity

የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ልዩ ፕሬዝዴንሻል ስኮላርሺፕ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በ2019 ዓ.ም 200 (ሁለት መቶ) ልዩ የፕሬዝዴንሻል ስኮላርሺፕ ዕድል አዘጋጅቷል። በ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ልዩ ፕሬዝዴንሻል ስኮላርሺፕ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በ2019 ዓ.ም 200 (ሁለት መቶ) ልዩ የፕሬዝዴንሻል ስኮላርሺፕ ዕድል አዘጋጅቷል። በ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ መልቀቂያ ፈተና ወስደው 500 እና ከዚያ በላይ ያስመዘገቡ፣ የተቀመጡ መመዘኛዎችን የሚያሟሉ እና ዩኒቨርሲቲው የሚሰጠውን የመግቢያ ፈተና በብቃት የሚያልፉ ተማሪዎች የስኮላርሺፕ ዕድሉ ተጠቃሚዎች ይሆናሉ ተብሏል፡፡ የ Presidential Scholarship Program ዕድሉ ተጠቃሚዎች፣ ዩኒቨርሲቲው ባሉት ሰባት ኮሌጆች እና የሕግ ትምህርት ቤት ስር ባሉ የቅድመ ምረቃ ፕሮግራሞች ይመደባሉ። ነጻ የትምህርት ዕድሉ ሙሉ ነፃ የትምህርት ዕድል፣ መጠነኛ የኪስ ገንዘብ እና ከአጋር ተቋማት ጋር በሚኖር ትብብር ተጨማሪ ድጋፍና የስልጠና ዕድሎችን ያስገኛል፡፡ በዚህ የትምህርት ዕድል በወጥነት ተጠቃሚ ለመሆን፣ የዕድሉ ተጠቃሚዎች በየሴሚስተሩ አጠቃላይ ውጤት (CGPA) 3.50 እና ከዚያ በላይ ማስመዝገብ ይጠበቅባቸዋል። በተጨማሪም የዕድሉ ተጠቃሚዎች በተመደቡበት የትምህርት ዘርፍ መቀጠል ይኖርባቸዋል። የዚህ ስኮላርሺፕ ተጠቃሚዎች በቀጣይነት ዩኒቨርሲቲው የድኅረ-ምረቃ (Masters እና PhD) የትምህርት ዕድል ያገኛሉ። የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የቅድመ-ምረቃ ፕሮግራሞች የ2019 ዓ.ም ምዝገባ እስከ ነሐሴ 29/2018 ዓ.ም እንደሚከናወን መገለፁ ይታወቃል፡፡ ለተጨማሪ መረጃ 👇 https://admission.aau.edu.et/UGAnnouncements @tikvahuniversity

ተመሳሳይ የ12ኛ ክፍል ውጤት ያስመዘገቡት መንትዮች 👏 የባሕር ዳር ከተማ ካቶሊክ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች የሆኑት መንትዮቹ በዕምነት መልካሙ እና ዮርዳኖስ መልካሙ ተመሳሳይ ውጤት ማስመዝ
+1
ተመሳሳይ የ12ኛ ክፍል ውጤት ያስመዘገቡት መንትዮች 👏 የባሕር ዳር ከተማ ካቶሊክ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች የሆኑት መንትዮቹ በዕምነት መልካሙ እና ዮርዳኖስ መልካሙ ተመሳሳይ ውጤት ማስመዝገባቸው አስደናቂ ክስተት ሆኗል። የተፈጥሮ ሳይንስ መስክ ተማሪዎች የሆኑት መንትዮቹ፣ ተመሳሳይ 413 ከ 600 ውጤት ማስመዝገባቸው ብዙዎችን አስገርሟል። @tikvahuniversity

🌻 የአዲስ ዓመት 25% ቅናሽ ከነሐሴ 27/2018 ዓ.ም እስከ መስከረም 21/2019 ዓ.ም🌻 59ኛ ዙር ሙሉ የሒሳብ መዝገብ አያያዝ ስልጠና ምዝገባ ላይ ነን! 👉 ተግባርን ከንድፈ ሀሳብ ያስተሳ
🌻 የአዲስ ዓመት 25% ቅናሽ ከነሐሴ 27/2018 ዓ.ም እስከ መስከረም 21/2019 ዓ.ም🌻 59ኛ ዙር ሙሉ የሒሳብ መዝገብ አያያዝ ስልጠና ምዝገባ ላይ ነን! 👉 ተግባርን ከንድፈ ሀሳብ ያስተሳሰረ ስልጠና 👉 የድርጅቶች ሒሳብ አያያዝ ስርዓት በፒስችሪ ተደግፎ የሚሰጥ 👉 VAT፣ Excise Tax፣ የትርፍ ግብር፣ ዓመታዊ ግብር አሰራር እና ሪፖርት አቀራረብና ሌሎችም የግብር ዓይነቶችን በተግባር እየሠሩ የሚሰለጥኑበት የበለጠ ይጠብቁ ... 💥 ሴጅ ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት 💥 ☎️ 0906777799 / 0906777755 አድራሻ፦ ቁ.1: ፒያሣ ቸርችል ጎዳና ኤልያና ሆቴል 2ኛ ፎቅ፣ ቁ.2: መገናኛ ደራርቱ ህንፃ 5ኛ ፎቅ እና ቁ.3: አዳማ ራስ ሆቴል 2ኛ ፎቅ ለመመዝገብ ድረ-ገጽ 👇 www.sageethiopia.com Telegram: https://t.me/sagetraininginstitute Tiktok: https://www.tiktok.com/@sage_training_instituter Linkedin: https://www.linkedin.com/company/sage-training-institute

የሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲዎች የ2019 ዓ.ም የቅድመ-ምረቃ የመግቢያ ፈተና ምዝገባ የአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ እና የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ በ2018 ዓ.ም የ12ኛ
የሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲዎች የ2019 ዓ.ም የቅድመ-ምረቃ የመግቢያ ፈተና ምዝገባ የአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ እና የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ በ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ወስዳችሁ 50% እና ከዚያ በላይ ያስመዘገባችሁ የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎችን የመግቢያ ፈተና በኦንላይን በመስጠት ለ2019 ዓ.ም መቀበል ይፈልጋሉ፡፡ የትምህርች ዘርፎች በአፕላይድ ሳይንስ እና በኢንጂነሪንግ የትምህርት ዘርፎች ለትምህርት መስኮች ዝርዝር 👇 https://www.facebook.com/share/p/19EMVmakWg/ or https://www.facebook.com/share/p/18zZo4rxUj/ የምዝገባ ጊዜ ከነሐሴ 25 እስከ ጳጉሜን 03/2018 ዓ.ም ለሊት 6:00 ሰዓት ድረስ የምዝገባ ቦታ የምዝገባ መስፈርቱን የምታሟሉ አመልካቾች በኦንላይን https://stuoexam.astu.edu.et ወይም www.aastu.edu.et / www.astu.edu.et በመጠቀም መመዝገብ ትችላላችሁ፡፡ ፈተናው የሚሰጥበት ቀን የምዝገባው ጊዜ ካበቃ በኋላ ይገለጻል ተብሏል። ፈተናው የሚሰጥበት ቦታ በምዝገባ ወቅት በመረጡት የፈተና ጣቢያ በአካል በመቅረብ። በቂ አመላካቾች የሌሉባቸው የፈተና ጣቢያዎች በቅርበት ወደሚገኙ የፈተና ጣቢያዎች ሊታጠፉ እንደሚችሉ ተገልጿል፡፡ 🔔 አመልካቾች የመግቢያ ፈተና በሚሰጥባቸው የትምህርት አይነቶች ማለትም (ከ9-12ኛ ክፍል) ባዮሎጂ፣ ኬሚስትሪ፣ ፊዚክስ፣ ሂሳብ እና እንግሊዝኛ ከወዲሁ እንድትዘጋጁ ዩኒቨርሲቲዎቹ መክረዋል። አመልካቾች ለፈተና ስትቀርቡ የ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ውጤት፣ የፈተና አድሚሽን ካርድ (ወይም መታወቂያ) እና የምዝገባ ማረጋገጫ ኮፒ መያዝ ይጠበቅባችኋል፡፡ @tikvahuniversity

የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የ2019 ዓ.ም የቅድመ-ምረቃ ፕሮግራሞች ምዝገባ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በ2019 የትምህርት ዘመን በቅድመ-ምረቃ በቀን መደበኛ መርሐግብር (በመንግሥት ስኮላርሺፕ እና በግል
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የ2019 ዓ.ም የቅድመ-ምረቃ ፕሮግራሞች ምዝገባ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በ2019 የትምህርት ዘመን በቅድመ-ምረቃ በቀን መደበኛ መርሐግብር (በመንግሥት ስኮላርሺፕ እና በግል ክፍያ) እንዲሁም በማታና ተከታታይ መርሐግብር አዲስ ተማሪዎችን ተቀብሎ ማስተማር ይፈልጋል። መስፈርቶች ➻ በ2015፣ 2016፣ 2017 እና 2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ መልቀቂያ ፈተና ወስደው የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ነጥብ ያመጡ ወይም ደረጃ 4 አጠናቀው (COC) ያለፉ ➻ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሚሰጠውን የመግቢያ ፈተና (UAT) ይወስዳሉ የምዝገባ ጊዜ 👇 እስከ ነሐሴ 29/2018 ዓ.ም ድረስ ኦንላይን ይመዝገቡ 👇 https://admission.aau.edu.et የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የመግቢያ ፈተና (UAT) ከጳጉሜን 02-04/2018 ዓ.ም ይሰጣል፡፡ @tikvahuniversity

#Pioneer_College 🔥 አስደሳች ዜና ከፓዩኒዬር ኮሌጅ የዕውቅና ፈቃድ ያለው ፓዩኒዬር ኮሌጅ፤ ለ2019 ዓ.ም ተማሪዎች ብቻ የሚያገለግል የትምህርት ክፍያ ዋጋ ቅናሽ አድርገናል❗️ ከትምህርት
#Pioneer_College 🔥 አስደሳች ዜና ከፓዩኒዬር ኮሌጅ    የዕውቅና ፈቃድ ያለው ፓዩኒዬር ኮሌጅ፤ ለ2019 ዓ.ም ተማሪዎች ብቻ የሚያገለግል የትምህርት ክፍያ ዋጋ ቅናሽ አድርገናል❗️ ከትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን ዕውቅና ባገኘንባቸው የዲግሪ ፕሮግራሞች፦ ► የሕክምና ዶክትሬት ► የጥርስ ሕክምና ዶክትሬት ► ፋርማሲ ► ሜዴካል ላብራቶሪ ሳይንስ 🔔 ምዝገባ ጀምረናል! በጤናው መስክ ተወዳደሪ ሆኖ ለመገኘት ካሰቡ አሁኑኑ ፓዩኒዬር ኮሌጅ ይመዝገቡ! አድራሻ ከጀርመን አደባባይ ወደ ለቡ መብራት በሚሰደው መንገድ ☎️  0902442244 / 0902443344 www.pioneercollege.edu.et

#MoE በ2019 ዓ.ም በፌዴራል ልዩ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለመማር የተመዘገባችሁና ለፈተና የተመረጣችሁ ተማሪዎች በሙሉ በተመዘገባችሁበት ሊንክ ውጤታችሁን ማየት እንደምትችሉ ትምህርት
#MoE በ2019 ዓ.ም በፌዴራል ልዩ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለመማር የተመዘገባችሁና ለፈተና የተመረጣችሁ ተማሪዎች በሙሉ በተመዘገባችሁበት ሊንክ ውጤታችሁን ማየት እንደምትችሉ ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል። ትምህርት በሚሰጥባቸው በነባር እና አዲስ የፌዴራል ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤቶች በ9ኛ እና 10ኛ ክፍል ለመማር ተመዝግባችሁ በመጠባበቅ ላይ ያላችሁና ለፈተና የተመረጣችሁ ተማሪዎች፤ በተመዘገባችሁበት ሊንክ መለያ ኮዳችሁን ( Reference Number) በማስገባት ውጤታችሁን ማየት የምትችሉ መሆኑ ተገልጿል። 🔔 ለፈተና የተመረጣችሁ ተማሪዎች፣ በኦንላይን ለሚሰጠው ፈተና የሚቀርባችሁን የፈተና መስጫ ማዕከል በተመዘገባችሁበት ሊንክ በመግባት መምረጥ የምትችሉ መሆኑን ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል። የሙከራ ፈተና ረቡዕ ነሐሴ 27/2018 ዓ.ም የሚሰጥ ሲሆን፣ ዋና ፈተናው ነሐሴ 28/2018 ዓ.ም ይሰጣል። @tikvahuniversity

በሰሜን ሸዋ ዞን ማረሚያ ቤቶች መምሪያ ሥር የሚገኘው ተሐድሶ አምባ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ፈተና ከወሰዱ ታራሚ ተፈታኞች መካከል 91% ታራሚዎችን አሳልፏል። 👏👏
በሰሜን ሸዋ ዞን ማረሚያ ቤቶች መምሪያ ሥር የሚገኘው ተሐድሶ አምባ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ፈተና ከወሰዱ ታራሚ ተፈታኞች መካከል 91% ታራሚዎችን አሳልፏል። 👏👏 ትምህርት ቤቱ ላለፉት አራት ዓመታት አንድም ተማሪ ማሳለፍ ያልቻለ ቢሆንም፣ ዘንድሮ 91 በመቶ ታራሚ ተፈታኞቹን ማሳለፍ መቻሉ ተገልጿል። ታራሚ ተፈታኞቹ ጥሩ ውጤት እንዲያመጡ የማጠናከሪያ ትምህርት ይሰጣቸው እንደነበር የሰሜን ሸዋ ዞን ማረሚያ ቤቶች መምሪያ ኃላፊ ኮማንደር የቻለሰው አሰፋ ለአሚኮ ተናግረዋል። @tikvahuniversity