Tikvah-University
الذهاب إلى القناة على Telegram
إظهار المزيد
📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام Tikvah-University
تُعد قناة Tikvah-University (@tikvahuniversity) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 362 726 مشتركاً، محتلاً المرتبة 133 في فئة التعليم والمرتبة 13 في منطقة Ethiopia.
📊 مؤشرات الجمهور والحراك
منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 362 726 مشتركاً.
بحسب آخر البيانات بتاريخ 16 يونيو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار 4 142، وفي آخر 24 ساعة بمقدار 14، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.
- حالة التحقق: غير موثّقة
- معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 14.40%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 9.60% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
- وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 52 239 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 34 819 مشاهدة.
- التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 97.
📝 الوصف وسياسة المحتوى
وصف القناة غير متوفر.
بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 17 يونيو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة التعليم.
362 726
المشتركون
+1424 ساعات
+1 1087 أيام
+4 14230 أيام
أرشيف المشاركات
362 726
#ጥቆማ
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ለ2019 የትምህርት ዘመን የመጀመሪያ ሴሚስተር የድኅረ-ምረቃ ፕሮግራሞች አመልካቾችን መቀበል ጀምሯል፡፡
ዩኒቨርሲቲው ለ Masters ፕሮግራም በመደበኛ እና በኤክስቴንሽን መርሐግብሮች እንዲሁም ለ PhD ፕሮግራም በመደበኛ እና በኤክስቴንሽን መርሐግብሮች አመልካቾችን ይቀበላል፡፡
የድኅረ-ምረቃ ፕሮግራሞቹን ዝርዝር በ https://admission.aau.edu.et/GraduatePrograms መመልከት ይችላሉ፡፡
አመልካቾች በቅድሚያ በዩኒቨርሲቲው የሚሰጠውን የድኅረ-ምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (GAT) መውሰድና ማለፍ ይጠበቅባቸዋል፡፡
የ GAT ማመልከቻ ጊዜ የሚያበቃው 👇
ነሐሴ 05/2018 ዓ.ም
@tikvahuniversity
362 726
ለደዋዮችዎ ለየት ያለ የጥሪ ማሳመሪያ ሙዚቃ መጋበዝ ይችላሉ! አገልግሎቱን ለማግኘት አሁኑኑ ወደ 722 ይደውሉ!
በM-PESA ሲገዙ እስከ 25% የሚደርስ ቅናሽ አለው!
#SafaricomEthiopia
#furtheraheadtogether
362 726
የ4ኛ ቀን የቅድመ-ምረቃ ትምህርት የመውጫ ፈተናዎች እየተሰጡ ነው፡፡ በዛሬው ውሎ የ24 ትምህርት አይነት ፈተናዎች ይሰጣሉ፡፡
የመውጫ ፈተና የ4ኛ ቀን መርሐግብር (ሰኔ 09/2018 ዓ.ም)
✅ ፈረቃ 1: ጠዋት ከ2:00-4:30 ሰዓት
✅ ፈረቃ 2: ጠዋት ከ5፡00-7:30 ሰዓት
✅ ፈረቃ 3: ከሰዓት ከ08:30-11:00 ሰዓት
የመውጫ ፈተና እስከ ሰኔ 12/2018 ዓ.ም በኦንላይን ይሰጣል፡፡ ምስል፦ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ
@tikvahuniversity
362 726
#ጥቆማ
በ2018 ዓ.ም ሀገር አቀፍ የሬዚደንሲ ፈተና ወስዳችሁ ያለፋችሁና በተለያዩ ተቋማት የተመደባችሁ፤ ነገር ግን በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ በጤና ሳይንስና ህክምና ኮሌጅ School of Medicine, General Surgery ትምህርት ዘርፍ ለመማር የምትፈልጉ ሐኪሞች እንድታመለክቱ ዩኒቨርሲቲው ጋብዟል፡፡
የምዝገባ ጊዜ፦ ከሰኔ 08-12/2018 ዓ.ም
የማመልከቻ አማራጮች፦
● Email: registrar@wku.edu.et
● በአካል በዩኒቨርሲቲው ዋና ሬጅስትራር ጽ/ቤት
ለተጨማሪ መረጃ፦ 0920204770
@tikvahuniversity
362 726
💥 የክረምት ስልጠና (ከ40% እስከ 60% ቅናሽ እስከ ሰኔ 21/2018 ዓ.ም ለምትመዘገቡ) 💥
የጋዜጠኝነት ስልጠና ምዝገባ ላይ ነን!
በስልጠናው የተካተቱ፦
👉 መሠረታዊ የጋዜጠኝነት መርሆች፣ የሚዲያ እና የጋዜጠኝነት ዓይነቶች
👉 የዜና አሰራር እና የቃለመጠይቅ አደራረግ
👉 የመዝናኛ ፕሮግራም ጋዜጠኝነት፣ የፕሮግራም ዝግጅት፣ የማስታወቂያ አሰራር እና ዶክመንተሪ ዝግጅት
👉 የሞባይል እና የዩቲዩብ ጋዜጠኝነት
ስልጠናው ሰኔ 29/2018 ዓ.ም ይጀምራል!
የበለጠ ይጠብቁ ...
💥 ሴጅ ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት 💥
☎️ 0906777799 / 0906777755
አድራሻ፦ ቁ.1: ፒያሣ ቸርችል ጎዳና ኤልያና ሆቴል 2ኛ ፎቅ ቁ.2: መገናኛ ታሜጋስ ህንፃ 2ኛ ፎቅ ቁ.3: አዳማ
ለመመዝገብ ድረ-ገጽ 👇 www.sageethiopia.com
Telegram: https://t.me/sagetraininginstitute
TikTok: https://www.tiktok.com/@sage_training_institute
LinkedIn: https://www.linkedin.com/company/sage-training-institute
362 726
#HawassaUniversity
ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ለዘጠኝ የተቋሙ መምህራን የሙሉ ፕሮፌሰርነት የደረጃ እድገት ሰጠ።
የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሥራ አመራር ቦርድ የዘጠኙ መምህራንን የሙሉ ፕሮፌሰርነት የደረጃ እድገት አፅድቋል።
የሙሉ ፕሮፌሰርነት የደረጃ እድገት ያገኙ፦
1. ዶ/ር አቻምየለሽ ገብረፃዲቅ ተክሌ - በ Public Health
2. ዶ/ር አለማየሁ ሙሉነህ ቢተው - በ Climate Change and Environmental Science
3. ዶ/ር አውደነገስት ሞገስ ባንጃው - በ Soil and Water Conservation
4. ዶ/ር ምህረት ዳናንቶ ዑልሲዶ - በ Water Supply and Environmental Engineering
5. ዶ/ር ሙሉጌታ ዳዲ በለጠ - በ Hydrology
6. ዶ/ር አንዳርጋቸው ገዴቦ አቢተአ - በ Plant Breeding
7. ዶ/ር ዘሪሁነ ግርማ ወ/ገብርኤል - በ Wildlife Ecology and Management
8. ዶ/ር ሁሴን ሞሐመድ በሽር- በ Horticultural Sciences
9. ዶ/ር ታረቀኝ ዮሴፍ ሳማጎ- በ Agronomy
@tikvahuniversity
362 726
#ጥቆማ
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሰብዓዊ መብቶች ማዕከል በ 2019 ዓ.ም በ Human Rights የትምህርት መስክ የ2ኛ ዲግሪ እና የ3ኛ ዲግሪ (PhD) ፕሮግራሞች ለመማር ያመለክቱ!
ፍላጎት ያላቸውና ብቁ የሆኑ አመልካቾች እንዲያመለክቱ ማዕከሉ ጥሪ አድርጓል፡፡
ለዝርዝር መረጃ፣ መስፈርቶችን ለማየት እና የማመልከቻ መመሪያ ለማግኘት 👇
https://www.aau.edu.et/announcements/detail?title=Call~for~applications~for~admission~to~graduate~programs~for~the~First~Semester~of~2026/27~(2019~E.C.)~Academic~Year
አመልካቾች በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሚሰጠውን የድኅረ-ምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (GAT) ወስደው ማለፍ ይጠበቅባቸዋል፡፡
@tikvahuniversity
362 726
+3
የ2018 ትምህርት ዘመን የ6ኛ ክፍል ክልል/ከተማ አቀፍ ፈተና በተለያዩ ክልሎች እና በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር መሰጠት ጀምሯል።
ፈተናው ከዛሬ ሰኔ 08/2018 ዓ.ም ጀምሮ ለሦስት ተከታታይ ቀናት ይሰጣል፡፡
@tikvahuniversity
362 726
+3
በኢንተርኔት የታገዘ የመስኖ መቆጣጠሪያ ሲስተም (IoT Smart Irrigation System) የሠሩ ወጣቶች የቴክኒክና ሙያ ሥልጠና ኢንስቲትዩት የመጀመሪያው የቴክኖሎጂ ውድድር አሸናፊዎች ሆነዋል፡፡
ኢንስቲትዩቱ ያዘጋጀው የመጀመሪያው ዓለም አቀፍ የቴክኒክና ሙያ ምርምር ኮንፈረንስና የቴክኖሎጂ ውድድር ተጠናቋል።
በቴክኖሎጂ ውድድሩ ከ10 ሀገራት የተውጣጡ 35 ፈጠራዎች ለውድድር የቀረቡ ሲሆን፤ ኢትዮጵያውያን ወጣቶች አንደኛ እና ሁለተኛ ደረጃን ሲይዙ፣ ናይጄሪያዊው ወጣት የፈጠራ ባለሙያ ሦስተኛ ደረጃን በማግኘት የነሐስ ሜዳሊያ ተሸላሚ ሆኗል።
የቴክኖሎጂ ውድድሩ አሸናፊዎች የሆኑት IoT Smart Irrigation System አንደኛ፣ የCerebro Logic ሁለተኛ እንዲሁም የናይጄሪያው Eco-Bin Revenue Intelligence and Traceability System ሦስተኛ ደረጃን አግኝተዋል።
የመስኖ መቆጣጠሪያ ሲስተም ቴክኖሎጂው እስከ 10ኪሜ ርቀት ላይ ያሉ የመስኖ እርሻዎችን ለመከታተልና አስፈጊውን ግባዓት ለማቅረብ የሚረዳ ነው።
@tikvahuniversity
362 726
+3
ሴጅ ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት ቁጥር ሦስት በአዳማ ራስ ሆቴል 2ኛ ፎቅ ላይ ትናንት ሰኔ 07/2018 ዓ.ም ተመርቋል።
የበለጠ ይጠብቁ ...
💥 ሴጅ ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት 💥
☎️ 0906777799 / 0906777755
አድራሻ፦ ቁ.1: ፒያሣ ቸርችል ጎዳና ኤልያና ሆቴል 2ኛ ፎቅ ቁ.2: መገናኛ ታሜጋስ ህንፃ 2ኛ ፎቅ ቁ.3: አዳማ ራስ ሆቴል 2ኛ ፎቅ
ለመመዝገብ ድረ-ገጽ 👇 www.sageethiopia.com
Telegram: https://t.me/sagetraininginstitute
TikTok: https://www.tiktok.com/@sage_training_institute
LinkedIn: https://www.linkedin.com/company/sage-training-institute
362 726
#ጥቆማ
ነጻ የክረምት ስልጠና ይከታተሉ!
የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ከ1ኛ-12ኛ ክፍል ለሆነ ተማሪዎች የክረምት ስልጠና አዘጋጅቷል።
የክረምት ስልጠና መስኮች፦
● ፋንዳሜንታልስ ኦፍ ኤ.አይ.
● ፕሮግራሚንግ
● ማሽን ለርኒንግ
● ሮቦቲክስ እና IOT
● ዳታ ሳይንስ
የምዝገባ ጊዜ የሚያበቃው 👇
ሰኔ 30/2018 ዓ.ም
በተከታዩ የጉግል ፎርም ይመዝገቡ 👇
https://forms.gle/uDGPmQsiZcWWeNuRA
@tikvahuniversity
362 726
+8
#HawassaUniversity
ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ በ2.8 ቢሊዮን ብር ወጪ የተሠሩ ፕሮጀክቶችን አስመርቋል።
ዩኒቨርሲቲው በህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የኮምፕሪሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ማስፋፊያ ፕሮጀክቶችን አስመርቋል።
በዩኒቨርሲቲው የተመረቁ ስድስት ፕሮጀክቶች፦
● ልዩ የቀዶ ሕክምናና የወሊድ ፅኑ ህሙማን ክፍል
● የክሊኒካል ሙከራ ማዕከል (Clinical Trial Unit)
● የሕፃናት ቀዶ ሕክምና የልህቀት ማዕከል
● የጡት ወተት ባንክ (በኢትዮጵያ የመጀመሪያው)
● የኦክሲጅን ማምረቻና የሕክምና ጋዝ ሥርዓት
● የሕክምና ቆሻሻ ማቃጠያ (Incinerator)
ፕሮጀክቶቹ የጤና አገልግሎትን ለማስፋፋት፣ የኅብረተሰቡን ጤና ለመጠበቅ እና ጥራት ያለው ሕክምና ለማቅረብ ጉልህ አስተዋጽኦ ይኖራቸዋል ተብሏል።
@tikvahuniversity
362 726
በሚገኙበት ክልል ወይም ከተማ አስተዳደር የመኖሪያ ቤት ወይም የመኖሪያ ቤት መስሪያ ቦታ ያልተሰጣቸው የዩኒቨርሲቲ መምህራን ስም ዝርዝርን እንዲልኩ ትምህርት ሚኒስቴር ሁሉንም የመንግሥት ዩኒቨርሲዎች ጠይቋል።
በቀን 04/10/2018 ዓ.ም በትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ደኤታ ኮራ ጡሹ ለሁሉም የመንግሥት ዩኒቨርሲዎች የተጻፈ ደብዳቤ፣ ከሰኔ 04/2018 ዓ.ም ጀምሮ ባሉት ተከታታይ 15 ቀናት ውስጥ የመምህራኑ ዝርዝር ለሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ እንዲላክ አዟል።
@tikvahuniversity
362 726
#ጥቆማ
የሞሮኮ መንግሥት በ2026/27 የትምህርት ዘመን መስፈርቱን ለሚያሟሉ 50 ኢትዮጵያውያን ተማሪዎች ነጻ የትምህርት ዕድል ሰጥቷል።
በመሆኑም መስፈርቱን የሚያሟሉ አመልካቾች ለዚሁ ዓላማ ተብሎ በተከፈተው ድረ-ገፅ www.marccalumni.ma በማመልከት የትምህርት ዕድሉ ተጠቃሚ መሆን እንደሚችሉ ትምህርት ሚኒስቴር በቀን 26/09/2018 ዓ.ም ለሁሉም የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች በጻፈው ደብዳቤ ገልጿል።
ለማመልከት 👇
www.marccalumni.ma
የምዝገባ ጊዜ የሚያበቃው 👇
ሰኞ ሰኔ 08/2018 ዓ.ም
@tikvahuniversity
362 726
#ጥቆማ
የነርሲንግ አመራርና ሙያዊ አቅም ማጠናከሪያ ፕሮግራም ስልጠና ይውሰዱ!
ፍላጎት ያላችሁ የነርሲንግ ባለሙያዎች ምዝገባ እንድታደርጉ ጤና ሚኒስቴር ጋብዟል።
ብቃትን መሠረት ያደረገ ምልመላ ተከትሎ ሰልጣኞች አድቫንስድ ክሊኒካል የተግባር ዝግጁነት ስልጠና ይወስዳሉ። ስልጠናውን ሲያጠናቅቁ የተረጋገጠ ዲጂታል ሰርተፊኬት የሚያገኙ ይሆናል።
የምዝገባ ጊዜ 👇
ከሰኔ 04-10/2018 ዓ.ም
ለማመልከት 👇
https://ncep.mohdigitalhealth.gov.et
@tikvahuniversity
362 726
በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የ2018 ዓ.ም የ6ኛ እና የ8ኛ ክፍል ፈተናዎች ከሰኔ 09-12/2018 ዓ.ም ይሰጣሉ። - የክልሉ ትምህርት ቢሮ
የ6ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና
➫ ሰኔ 09 እና 10/2018 ዓ.ም ይሰጣል፡፡
የ8ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና
➫ ሰኔ 11 እና 12/2018 ዓ.ም ይሰጣል፡፡
@tikvahuniversity
362 726
💥 የክረምት ስልጠና (ከ40% እስከ 60% ቅናሽ እስከ ሰኔ 21/2018 ዓ.ም ለምትመዘገቡ) 💥
የጥናታዊ ጽሑፍ አሰራር እና አቀራረብ (Research Methods and Analysis) ስልጠና ምዝገባ ላይ ነን!
👉 Stata እና SPSS ሶፍትዌሮችን በመጠቀም Quantitative እና Qualitative ሪሰርቾችን መስራትን በአንድ ላይ አካቶ የሚሰጥ
👉 ከፕሮፖዛል ቀረፃ ጀምሮ እስከ ሪሰርች ሪፖርት አቀራረብ ያለውን አሰራር የሚሰለጥኑበት
👉 በታላላቅ የአገራችን የጥናታዊ ፅሑፍ ባለሙያዎች የሚሰጥ ስልጠና
🔔 ስልጠናው ሰኔ 29/2018 ዓ.ም ይጀምራል!
የበለጠ ይጠብቁ ...
💥 ሴጅ ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት 💥
☎️ 0906777799 / 0906777755
አድራሻ፦ ቁ.1: ፒያሣ ቸርችል ጎዳና ኤልያና ሆቴል 2ኛ ፎቅ ቁ.2: መገናኛ ታሜጋስ ህንፃ 2ኛ ፎቅ ቁ.3: አዳማ
ለመመዝገብ ድረ-ገጽ 👇 www.sageethiopia.com
Telegram: https://t.me/sagetraininginstitute
TikTok: https://www.tiktok.com/@sage_training_institute
LinkedIn: https://www.linkedin.com/company/sage-training-institute
362 726
ነጻ የኦንላይን ስልጠና!
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የቅድመ-ምረቃ ፕሮግራም ተማሪ ከሆኑ፣ የሰብዓዊ መብቶች ማዕከል በመሠረታዊ ሰብዓዊ መብቶች ላይ የሚሰጠውን ነጻ የኦንላይን ስልጠና ይውሰዱ!
የሚሰጡ ነጻ የኦንላይን ስልጠና ኮርሶች
➫ የሴቶች መብቶች
➫ የአካል ጉዳተኛ ሰዎች መብቶች
➫ የህጻናት መብቶች
የምዝገባ ጊዜ የሚያበቃው 👇
ሰኞ ሰኔ 08/2018 ዓ.ም
ለመመዝገብ 👇
https://forms.gle/sJQcuU21tfXFuTbC6
ወይም በምስሉ ላይ ያለውን QR Code ስካን ያደርጉ።
@tikvahuniversity
362 726
በስልክዎ ያለገደብ ያውሩ! ⏳
ጥሩ ወሬ መሃል ካርድ እያለቀ ተቸገራችኋል? በ1 ብር ብቻ የአንድ ሰዓት የስልክ ጥቅል ገዝተው ለሚወዷቸው ደውለው እንደልብዎ ያውሩ!
ለመግዛት ወደ *777# ይደውሉ ወይም በ M-PESA ሳፋሪኮም መተግበሪያ ይግዙ!
#SafaricomEthiopia
362 726
ትናንት መሰጠት የጀመረው የቅድመ-ምረቃ ትምህርት የመውጫ ፈተና በዛሬው ውሎ የማኔጅመንት፣ ቢዝነስ ማኔጅመንት፣ ቢዝነስ አድሚንስትሬሽን እንዲሁም ቢዝነስ ማኔጅመንትና ኢንተርፕሬነርሺፕ ፈተናዎች ይሰጣሉ፡፡
የመውጫ ፈተና የሁለተኛ ቀን መርሐግብር (ሰኔ 05/2018 ዓ.ም)
ፈተናው በሦስት ክፍለ-ጊዜ ይሰጣል፦
✅ ፈረቃ 1: ጠዋት ከ2:30-5:00 ሰዓት
✅ ፈረቃ 2: ከሰዓት ከ7:30-10:00 ሰዓት
✅ ፈረቃ 3: ከሰዓት ከ10:15-12:45 ሰዓት
የመውጫ ፈተናው እስከ ሰኔ 12/2018 ዓ.ም ለሰባት ቀናት (ቅዳሜ እና እሑድ ሳይጨምር) በኦንላይን ይሰጣል፡፡ ምስል፦ ጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ
@tikvahuniversity
متاح الآن! بحث تيليغرام 2025 — أهم رؤى العام 
