Tikvah-University
الذهاب إلى القناة على Telegram
إظهار المزيد
📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام Tikvah-University
تُعد قناة Tikvah-University (@tikvahuniversity) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 380 835 مشتركاً، محتلاً المرتبة 114 في فئة التعليم والمرتبة 13 في منطقة Ethiopia.
📊 مؤشرات الجمهور والحراك
منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 380 835 مشتركاً.
بحسب آخر البيانات بتاريخ 01 سبتمبر, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار 11 442، وفي آخر 24 ساعة بمقدار 731، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.
- حالة التحقق: غير موثّقة
- معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 19.41%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 11.34% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
- وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 73 907 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 43 184 مشاهدة.
- التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 172.
📝 الوصف وسياسة المحتوى
وصف القناة غير متوفر.
بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 02 سبتمبر, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة التعليم.
380 835
المشتركون
+73124 ساعات
+2 7267 أيام
+11 44230 أيام
أرشيف المشاركات
380 835
#Update
ትምህርት ሚኒስቴር ለ2019 የትምህርት ዘመን ትምህርት በሚሰጥባቸው ነባር እና አዲስ የፌዴራል ልዩ አዳሪ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የ9ኛ እና 10ኛ ክፍል ተማሪዎችን አወዳድሮ ለመቀበል ባወጣው ማስታወቂያ መሰረት ተመዝግባችሁ በመጠባበቅ ላይ ያላችሁ ተማሪዎች የፈተና ፕሮግራም መውጣቱ ይታወቃል።
ይሁን እንጂ አንዳንድ ተማሪዎች የመፈተኛ ቦታቸውን ባለማወቃቸው ምክንያት የፈተና ቀኑን በአንድ ቀን ማራዘም አስፈላጊ ሆኖ መገኘቱን ሚኒስቴሩ ገልጿል።
🔔 በመሆኑም የሙከራ ፈተና ነሐሴ 28/2018 ዓ.ም እና ዋናው ፈተና ነሐሴ 29/2018 ዓ.ም የሚሰጥ መሆኑ ተገልጿል።
በተገለፁት ቀናት ጠዋት 2:30 በየተመደባችሁባቸው ጣቢያዎች ራሳችሁን የሚገልፅ መታወቂያ በመያዝ እንድትገኙ ተብሏል።
@tikvahuniversity
380 835
+4
#Remedial_Complaint
ዛሬ ይፋ ከተደረገው የ2018 ዓ.ም የሪሚዲያል ፕሮግራም ተማሪዎች ውጤት ጋር በተያያዘ እጅግ በርካታ ተማሪዎች ቅሬታቸውን ለቲክቫህ ዩኒቨርሲቲ አድርሰዋል።
በርካታ ተማሪዎች ውጤታቸው ሙሉ በሙሉ 'Disqualified' የተባለባቸው መሆኑን በመግለፅ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት እንዲሁም ትምህርት ሚኒስቴር ማብራሪያ እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል።
ሌሎች በርካታ ተማሪዎች ደግሞ የሂሳብ ትምህርት ውጤታቸው ብቻ 'Disqualified' እንደሚል ገልፀዋል።
የተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች ተማሪዎች የሆኑት ቅሬታ አቅራቢዎቹ፤ "በፈተና ወቅት ምንም አይነት የስነ-ምግባር ግድፈት አልፈፀንም" በማለት በእርማት ወቅት ቴክኒካል ችግር ከነበረ እንዲታይላቸው በትህትና ጠይቀዋል።
ቅሬታችሁን በኦንላይን አስገቡ 👇
https://result.ethernet.edu.et
ከውጤታችሁ ስር መጨረሻ ላይ ያለውን Submit Complaint የሚለውን ይጫኑ፣ Select a category የሚለውን ይክፈቱ፣ My result disqualified without reason የሚለውን ይምረጡ፣ አጠር ያለ መግለጫ ይፃፉ፣ የስልክ ቁጥርዎን ይሙሉ እና Submit Complaint የሚለውን በመጫን ቅሬታዎን ያስገቡ።
የሪሚዲያል ፕሮግራም የማለፊያ ነጥብ 250 ለተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች (5 የትምህርት አይነቶች) እና 200 ለማኅበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች (4 የትምህርት አይነቶች) መሆኑ ታውቋል።
የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት እንዲሁም ትምህርት ሚኒስቴር በተማሪዎቹ በቀረቡ ቅሬታዎች ላይ የሚሰጡትን ምላሽ ቲክቫህ ዩኒቨርሲቲ የሚያደርሳችሁ ይሆናል።
@tikvahuniversity
380 835
+3
በሀገር አቀፍ ደረጃ በተካሔደ የተማሪዎች የእርካታ ዳሰሳ ጥናት እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ቀዳሚ ደረጃን አጊኝቷል፡፡
በትምህርት ሚኒስቴር አስተባባሪነት በተካሔደው የተማሪዎች የእርካታ ዳሰሳ ጥናት (Students' Satisfaction Survey)፤ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ 1ኛ ደረጃ በመውጣት በተማሪዎች ተመራጭ ሆኗል።
ኦዳ ቡልቱም ዩኒቨርሲቲ 2ኛ ደረጃ እና ወልድያ ዩኒቨርሲቲ 3ኛ ደረጃን አጊኝተዋል።
ጥናቱ ዩኒቨርሲቲዎች ለተማሪዎች የሚያቀርቧቸው የምኝታ እና የምግብ አገልግሎቶች፣ የትምህርት ጥራት፣ የአመራር እና የመምህራንን ተደራሽነት፣ የግቢ ውበት እና ምቹነት፣ እንዲሁም የግቢ ሠላምና ደኅንነት መሠረት ያደረጉ መለኪያዎችን ማካተቱ ታውቋል። (ምስል፦ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ)
@tikvahuniversity
380 835
+1
ትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት አመራሮች አቅም ግንባታ፣ የፖሊሲ ጥናቶች ውጤት እና ዓመታዊ የሥራ አፈጻጸም አውደጥናት እያካሔደ ነው፡፡
ትናንት የተጀመረውና በአገራዊ የከፍተኛ ትምህርት ጉዳዮች ላይ እየመከረ ያለው አውደጥናቱ፤ እስከ ነገ ነሐሴ 27/2018 ዓ.ም ይቆያል።
የአውደጥናቱ አበይት አጀንዳዎች፦
➻ የከፍተኛ ት/ት ተቋማት ሪፎርም ሥራዎች
➻ የመውጫ ፈተና አፈፃፀም
➻ የድህረ-ምረቃ ተማሪዎች የትምህርት ወጪ
➻ የተመራቂ ተማሪዎች የመቀጠር ምጣኔ
➻ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የእርካታ ዳሰሳ ጥናት
የዩኒቨርሲቲ ሥራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢዎች፣ የዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንቶች፣ ምክትል ፕሬዝዳንቶች እና አጋር አካላት በአውደጥናቱ በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ።
አውደጥናቱ ትምህርት ሚኒስቴር ከማስተር ካርድ ፋውንዴሽን፣ ከአሪዞና ዩኒቨርሲቲ እና ከሽያሾኔ ተቋም ጋር በመተባበር የተዘጋጀ መሆኑ ተገልጿል፡፡
@tikvahuniversity
380 835
🔔 የህክምና ትምህርትዎን በሀገር ውስጥ እና በዓለም አቀፍ ተቋማት ዕውቅና ባለው ሚዮንግሰንግ ሜዲካል ኮሌጅ ይማሩ!
► በዘመናዊ መልክ የተደራጀ
► የራሱ የሆነ ምቹ የተማሪዎች መኖሪያ ያለው
► የኮሪያ ሆስፒታል እህት ኩባንያ
15ኛ ዙር የህክምና ትምህርት ምዝገባ ላይ ነን!
🎓 ኮሌጃችን ያስተማራቸውን ተማሪዎች በሙሉ የብቃት ምዘና ፈተና ማሳለፍ ችሏል!
ለማመልከት 👇
https://maps.app.goo.gl/oxRezU99L2DqnngD6
አድራሻ፦
አዲስ አባባ፣ ገርጂ ኮሪያ ሆስፒታል ቅጥር ግቢ ሬጅስትራር ቢሮ
የምዝገባ ጊዜ 👇
እስከ ጳጉሜን 02/2018 ዓ.ም ድረስ። አሁኑኑ ይመዝገቡ!
☎️ 0116395020
ድረ-ገጽ፦ www.mmc-edu.net
Facebook: https://web.facebook.com/MMCmedcollege/
#MyungsungMedicalCollege
380 835
#RemedialResult
በ2018 ዓ.ም የሪሚዲያል ፕሮግራም ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የቆዩ ተማሪዎች ውጤት ተለቋል።
https://result.ethernet.edu.et ላይ በመግባት Remedial Examination ከሚለው ስር View Results የሚለውን በመጫንና Username በማስገባት ውጤትዎን ይመልከቱ።
ከግንቦት 27 እስከ ሰኔ 03/2018 ዓ.ም የተሰጠውን ሀገር አቀፍ የሪሚዲያል ፕሮግራም ፈተና 53,620 ተፈታኞች መውሰዳቸውን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት መግለፁ ይታወሳል።
@tikvahuniversity
380 835
#ጥቆማ
የአማራ ክልል ስቴት ዩኒቨርሲቲ በ2ኛ ዲግሪ በመደበኛ እና በኤክስቴንሽን መርሐግብር እንዲሁም በ3ኛ ዲግሪ በመደበኛ መርሐግብር በተመረጡ የትምህርት ፕሮግራሞች ተማሪዎችን ተቀብሎ ማስተማር ይፈልጋል፡፡
በ3ኛ ዲግሪ የሚሰጡ የትምህርት ፕሮግራሞች
➫ PhD in Public Policy and Leadership
➫ PhD in Political Economy and Governance
➫ PhD in Peace and Security Studies
በ2ኛ ዲግሪ የሚሰጡ የትምህርት ፕሮግራሞች
➫ Masters of Business Administration
➫ MSc in Project Management
➫ MA in Public Policy and Leadership
➫ MA in Political Economy
➫ MA in Peace and Development
➫ LLM in Law and Economics
➫ MA in Urban Governance and Leadership
በ2019 የትምህርት ዘመን በግል ወይም በተቋማት ስፖንሰርሺፕ ትምህርት ለመማር ፍላጎት ያላችሁና ሀገር አቀፍ የድኅረ-ምረቃ መግቢያ ፈተና (NGAT) ተፈትናችሁ ያለፋችሁ በዩኒቨርሲቲው ሬጅስትራር ቢሮ ቁጥር 10 በመቅረብ ወይም በ https://forms.gle/j6owxvQw36rjMTG9A መመዝገብ የምትችሉ መሆኑ ተገልጿል፡፡
የምዝገባ ጊዜ 👇
ከነሐሴ 25/2018 ዓ.ም እስከ መስከረም 30/2019 ዓ.ም
@tikvahuniversity
380 835
#Pioneer_College
🔥 አስደሳች ዜና ከፓዩኒዬር ኮሌጅ
የዕውቅና ፈቃድ ያለው ፓዩኒዬር ኮሌጅ፤ ለ2019 ዓ.ም ተማሪዎች ብቻ የሚያገለግል የትምህርት ክፍያ ዋጋ ቅናሽ አድርገናል❗️
ከትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን ዕውቅና ባገኘንባቸው የዲግሪ ፕሮግራሞች፦
► የሕክምና ዶክትሬት
► የጥርስ ሕክምና ዶክትሬት
► ፋርማሲ
► ሜዴካል ላብራቶሪ ሳይንስ
🔔 ምዝገባ ጀምረናል!
በጤናው መስክ ተወዳደሪ ሆኖ ለመገኘት ካሰቡ አሁኑኑ ፓዩኒዬር ኮሌጅ ይመዝገቡ!
አድራሻ
ከጀርመን አደባባይ ወደ ለቡ መብራት በሚሰደው መንገድ
☎️ 0902442244 / 0902443344
www.pioneercollege.edu.et
380 835
🌻 የአዲስ ዓመት 25% ቅናሽ ከነሐሴ 27/2018 ዓ.ም እስከ መስከረም 21/2019 ዓ.ም🌻
89ኛ ዙር የግራፊክ ዲዛይን፣ ቪዲዮ ኤዲቲንግ እና ሞሽን ግራፊክ ስልጠና ምዝገባ ላይ ነን!
👉 ተግባርን ከንድፈ ሀሳብ ያስተሳሰረ ስልጠና
👉 Advanced Graphic + Video Editing + Motion Graphic በአንድ ላይ
👉 ከ50 በላይ ፕሮጀክቶች ያሉት
የበለጠ ይጠብቁ ...
💥 ሴጅ ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት 💥
☎️ 0906777799 / 0906777755
አድራሻ፦ ቁ.1: ፒያሣ ቸርችል ጎዳና ኤልያና ሆቴል 2ኛ ፎቅ፣ ቁ.2: መገናኛ ደራርቱ ህንፃ 5ኛ ፎቅ እና ቁ.3: አዳማ ራስ ሆቴል 2ኛ ፎቅ
ለመመዝገብ ድረ-ገጽ 👇 www.sageethiopia.com
Telegram: https://t.me/sagetraininginstitute
Tiktok: https://www.tiktok.com/@sage_training_institute
380 835
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ልዩ የስኮላርሺፕ ዕድል ለመምህራን ትምህርት
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በ2019 የትምህርት ዘመን ልዩ የስኮላርሺፕ ዕድል ለ500 የቅድመ-ምረቃ ተማሪዎች #በመምህራን_ትምህርት መስኮች አዘጋጅቷል።
የስኮላርሺፑ ተጠቃሚ ሁሉንም መመዘኛ ያሟሉ እና ዩኒቨርሲቲው ያዘጋጀውን የመግቢያ ፈተና በብቃት አልፈው አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲን የተቀላቀሉ መሆን ይጠበቅባቸዋል።
የዚህ ስኮላርሺፕ ዕድል ተጠቃሚዎች በተፈጥሮ እና ኮምፕዩቴሽናል ሳይንስ የትምህርት መስክ (በፊዚክስ፣ በኬምስትሪ፣ በባዮሎጂ እና በሂሳብ) እንዲሁም በማኅበራዊ ሳይንስ የትምህርት መስክ (በእንግሊዘኛ፣ በኢኮኖሚክስ፣ በታሪክ እና በጂኦግራፊ የመምህርነት ትምህርት) የሚከታተሉ ይሆናሉ።
የስኮላርሽፕ ተጠቃሚዎች ሙሉ ነፃ የትምህርት ዕድል፣ መጠነኛ የኪስ ገንዘብ እና ከአጋር ተቋማት ጋር በሚኖር ትብብር ተጨማሪ የስልጠና ዕድሎችን እንደሚያገኙ ተገልጿል።
የዚህ ልዩ ዕድል ተጠቃሚ መሆን የምትፈልጉና ከስልጠና በኋላ በመምህርነት ለማገልገል የምትሹ ሁሉ ከቅበላ በኋላ ውል ፈርማችሁ ትምህርታችሁን መከታተል የምትችሉ መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል።
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የቅድመ-ምረቃ ፕሮግራሞች የ2019 ዓ.ም ምዝገባ እስከ ነሐሴ 29/2018 ዓ.ም እንደሚከናወን መገለፁ ይታወቃል፡፡
ለተጨማሪ መረጃ 👇
https://admission.aau.edu.et/UGAnnouncements
@tikvahuniversity
380 835
🔔 የህክምና ትምህርትዎን በሀገር ውስጥ እና በዓለም አቀፍ ተቋማት ዕውቅና ባለው ሚዮንግሰንግ ሜዲካል ኮሌጅ ይማሩ!
► በዘመናዊ መልክ የተደራጀ
► የራሱ የሆነ ምቹ የተማሪዎች መኖሪያ ያለው
► የኮሪያ ሆስፒታል እህት ኩባንያ
15ኛ ዙር የህክምና ትምህርት ምዝገባ ላይ ነን!
🎓 ኮሌጃችን ያስተማራቸውን ተማሪዎች በሙሉ የብቃት ምዘና ፈተና ማሳለፍ ችሏል!
ለማመልከት 👇
https://maps.app.goo.gl/oxRezU99L2DqnngD6
አድራሻ፦
አዲስ አባባ፣ ገርጂ ኮሪያ ሆስፒታል ቅጥር ግቢ ሬጅስትራር ቢሮ
የምዝገባ ጊዜ 👇
እስከ ጳጉሜን 02/2018 ዓ.ም ድረስ። አሁኑኑ ይመዝገቡ!
☎️ 0116395020
ድረ-ገጽ፦ www.mmc-edu.net
Facebook: https://web.facebook.com/MMCmedcollege/
#MyungsungMedicalCollege
380 835
ትምህርት ሚኒስቴር ለ2019 የትምህርት ዘመን ትምህርት በሚሰጥባቸው ነባር እና አዲስ የፌዴራል ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤቶች የ9ኛ እና 10ኛ ክፍል ተማሪዎችን አወዳድሮ ለመቀበል ባወጣው ማስታወቂያ መሰረት ለፈተና የሚቀርቡ ተማሪዎችን መልምሎ ይፋ ማድረጉ ይታወቃል።
በአመላመሉ ሒደቱ ላይ ቅሬታ ያላችሁ ተመዝጋቢ ተማሪዎች፣ በተመዘገባችሁበት ሊንክ (https://sbs.moe.gov.et/apply) በመግባትና Complaint የሚለውን በመጫን ቅሬታችሁን ማስገባት የምትችሉ መሆኑን ሚኒስቴሩ ገልጿል።
@tikvahuniversity
380 835
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ልዩ ፕሬዝዴንሻል ስኮላርሺፕ
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በ2019 ዓ.ም 200 (ሁለት መቶ) ልዩ የፕሬዝዴንሻል ስኮላርሺፕ ዕድል አዘጋጅቷል።
በ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ መልቀቂያ ፈተና ወስደው 500 እና ከዚያ በላይ ያስመዘገቡ፣ የተቀመጡ መመዘኛዎችን የሚያሟሉ እና ዩኒቨርሲቲው የሚሰጠውን የመግቢያ ፈተና በብቃት የሚያልፉ ተማሪዎች የስኮላርሺፕ ዕድሉ ተጠቃሚዎች ይሆናሉ ተብሏል፡፡
የ Presidential Scholarship Program ዕድሉ ተጠቃሚዎች፣ ዩኒቨርሲቲው ባሉት ሰባት ኮሌጆች እና የሕግ ትምህርት ቤት ስር ባሉ የቅድመ ምረቃ ፕሮግራሞች ይመደባሉ።
ነጻ የትምህርት ዕድሉ ሙሉ ነፃ የትምህርት ዕድል፣ መጠነኛ የኪስ ገንዘብ እና ከአጋር ተቋማት ጋር በሚኖር ትብብር ተጨማሪ ድጋፍና የስልጠና ዕድሎችን ያስገኛል፡፡
በዚህ የትምህርት ዕድል በወጥነት ተጠቃሚ ለመሆን፣ የዕድሉ ተጠቃሚዎች በየሴሚስተሩ አጠቃላይ ውጤት (CGPA) 3.50 እና ከዚያ በላይ ማስመዝገብ ይጠበቅባቸዋል። በተጨማሪም የዕድሉ ተጠቃሚዎች በተመደቡበት የትምህርት ዘርፍ መቀጠል ይኖርባቸዋል።
የዚህ ስኮላርሺፕ ተጠቃሚዎች በቀጣይነት ዩኒቨርሲቲው የድኅረ-ምረቃ (Masters እና PhD) የትምህርት ዕድል ያገኛሉ።
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የቅድመ-ምረቃ ፕሮግራሞች የ2019 ዓ.ም ምዝገባ እስከ ነሐሴ 29/2018 ዓ.ም እንደሚከናወን መገለፁ ይታወቃል፡፡
ለተጨማሪ መረጃ 👇
https://admission.aau.edu.et/UGAnnouncements
@tikvahuniversity
380 835
+1
ተመሳሳይ የ12ኛ ክፍል ውጤት ያስመዘገቡት መንትዮች 👏
የባሕር ዳር ከተማ ካቶሊክ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች የሆኑት መንትዮቹ በዕምነት መልካሙ እና ዮርዳኖስ መልካሙ ተመሳሳይ ውጤት ማስመዝገባቸው አስደናቂ ክስተት ሆኗል።
የተፈጥሮ ሳይንስ መስክ ተማሪዎች የሆኑት መንትዮቹ፣ ተመሳሳይ 413 ከ 600 ውጤት ማስመዝገባቸው ብዙዎችን አስገርሟል።
@tikvahuniversity
380 835
🌻 የአዲስ ዓመት 25% ቅናሽ ከነሐሴ 27/2018 ዓ.ም እስከ መስከረም 21/2019 ዓ.ም🌻
59ኛ ዙር ሙሉ የሒሳብ መዝገብ አያያዝ ስልጠና ምዝገባ ላይ ነን!
👉 ተግባርን ከንድፈ ሀሳብ ያስተሳሰረ ስልጠና
👉 የድርጅቶች ሒሳብ አያያዝ ስርዓት በፒስችሪ ተደግፎ የሚሰጥ
👉 VAT፣ Excise Tax፣ የትርፍ ግብር፣ ዓመታዊ ግብር አሰራር እና ሪፖርት አቀራረብና ሌሎችም የግብር ዓይነቶችን በተግባር እየሠሩ የሚሰለጥኑበት
የበለጠ ይጠብቁ ...
💥 ሴጅ ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት 💥
☎️ 0906777799 / 0906777755
አድራሻ፦
ቁ.1: ፒያሣ ቸርችል ጎዳና ኤልያና ሆቴል 2ኛ ፎቅ፣ ቁ.2: መገናኛ ደራርቱ ህንፃ 5ኛ ፎቅ እና ቁ.3: አዳማ ራስ ሆቴል 2ኛ ፎቅ
ለመመዝገብ ድረ-ገጽ 👇 www.sageethiopia.com
Telegram: https://t.me/sagetraininginstitute
Tiktok: https://www.tiktok.com/@sage_training_instituter
Linkedin: https://www.linkedin.com/company/sage-training-institute
380 835
የሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲዎች የ2019 ዓ.ም የቅድመ-ምረቃ የመግቢያ ፈተና ምዝገባ
የአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ እና የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ በ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ወስዳችሁ 50% እና ከዚያ በላይ ያስመዘገባችሁ የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎችን የመግቢያ ፈተና በኦንላይን በመስጠት ለ2019 ዓ.ም መቀበል ይፈልጋሉ፡፡
የትምህርች ዘርፎች
በአፕላይድ ሳይንስ እና በኢንጂነሪንግ የትምህርት ዘርፎች
ለትምህርት መስኮች ዝርዝር 👇
https://www.facebook.com/share/p/19EMVmakWg/ or
https://www.facebook.com/share/p/18zZo4rxUj/
የምዝገባ ጊዜ
ከነሐሴ 25 እስከ ጳጉሜን 03/2018 ዓ.ም ለሊት 6:00 ሰዓት ድረስ
የምዝገባ ቦታ
የምዝገባ መስፈርቱን የምታሟሉ አመልካቾች በኦንላይን https://stuoexam.astu.edu.et ወይም www.aastu.edu.et / www.astu.edu.et በመጠቀም መመዝገብ ትችላላችሁ፡፡
ፈተናው የሚሰጥበት ቀን የምዝገባው ጊዜ ካበቃ በኋላ ይገለጻል ተብሏል።
ፈተናው የሚሰጥበት ቦታ
በምዝገባ ወቅት በመረጡት የፈተና ጣቢያ በአካል በመቅረብ።
በቂ አመላካቾች የሌሉባቸው የፈተና ጣቢያዎች በቅርበት ወደሚገኙ የፈተና ጣቢያዎች ሊታጠፉ እንደሚችሉ ተገልጿል፡፡
🔔 አመልካቾች የመግቢያ ፈተና በሚሰጥባቸው የትምህርት አይነቶች ማለትም (ከ9-12ኛ ክፍል) ባዮሎጂ፣ ኬሚስትሪ፣ ፊዚክስ፣ ሂሳብ እና እንግሊዝኛ ከወዲሁ እንድትዘጋጁ ዩኒቨርሲቲዎቹ መክረዋል።
አመልካቾች ለፈተና ስትቀርቡ የ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ውጤት፣ የፈተና አድሚሽን ካርድ (ወይም መታወቂያ) እና የምዝገባ ማረጋገጫ ኮፒ መያዝ ይጠበቅባችኋል፡፡
@tikvahuniversity
380 835
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የ2019 ዓ.ም የቅድመ-ምረቃ ፕሮግራሞች ምዝገባ
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በ2019 የትምህርት ዘመን በቅድመ-ምረቃ በቀን መደበኛ መርሐግብር (በመንግሥት ስኮላርሺፕ እና በግል ክፍያ) እንዲሁም በማታና ተከታታይ መርሐግብር አዲስ ተማሪዎችን ተቀብሎ ማስተማር ይፈልጋል።
መስፈርቶች
➻ በ2015፣ 2016፣ 2017 እና 2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ መልቀቂያ ፈተና ወስደው የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ነጥብ ያመጡ ወይም ደረጃ 4 አጠናቀው (COC) ያለፉ
➻ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሚሰጠውን የመግቢያ ፈተና (UAT) ይወስዳሉ
የምዝገባ ጊዜ 👇
እስከ ነሐሴ 29/2018 ዓ.ም ድረስ
ኦንላይን ይመዝገቡ 👇
https://admission.aau.edu.et
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የመግቢያ ፈተና (UAT) ከጳጉሜን 02-04/2018 ዓ.ም ይሰጣል፡፡
@tikvahuniversity
380 835
#Pioneer_College
🔥 አስደሳች ዜና ከፓዩኒዬር ኮሌጅ
የዕውቅና ፈቃድ ያለው ፓዩኒዬር ኮሌጅ፤ ለ2019 ዓ.ም ተማሪዎች ብቻ የሚያገለግል የትምህርት ክፍያ ዋጋ ቅናሽ አድርገናል❗️
ከትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን ዕውቅና ባገኘንባቸው የዲግሪ ፕሮግራሞች፦
► የሕክምና ዶክትሬት
► የጥርስ ሕክምና ዶክትሬት
► ፋርማሲ
► ሜዴካል ላብራቶሪ ሳይንስ
🔔 ምዝገባ ጀምረናል!
በጤናው መስክ ተወዳደሪ ሆኖ ለመገኘት ካሰቡ አሁኑኑ ፓዩኒዬር ኮሌጅ ይመዝገቡ!
አድራሻ
ከጀርመን አደባባይ ወደ ለቡ መብራት በሚሰደው መንገድ
☎️ 0902442244 / 0902443344
www.pioneercollege.edu.et
380 835
#MoE
በ2019 ዓ.ም በፌዴራል ልዩ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለመማር የተመዘገባችሁና ለፈተና የተመረጣችሁ ተማሪዎች በሙሉ በተመዘገባችሁበት ሊንክ ውጤታችሁን ማየት እንደምትችሉ ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል።
ትምህርት በሚሰጥባቸው በነባር እና አዲስ የፌዴራል ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤቶች በ9ኛ እና 10ኛ ክፍል ለመማር ተመዝግባችሁ በመጠባበቅ ላይ ያላችሁና ለፈተና የተመረጣችሁ ተማሪዎች፤ በተመዘገባችሁበት ሊንክ መለያ ኮዳችሁን ( Reference Number) በማስገባት ውጤታችሁን ማየት የምትችሉ መሆኑ ተገልጿል።
🔔 ለፈተና የተመረጣችሁ ተማሪዎች፣ በኦንላይን ለሚሰጠው ፈተና የሚቀርባችሁን የፈተና መስጫ ማዕከል በተመዘገባችሁበት ሊንክ በመግባት መምረጥ የምትችሉ መሆኑን ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል።
የሙከራ ፈተና ረቡዕ ነሐሴ 27/2018 ዓ.ም የሚሰጥ ሲሆን፣ ዋና ፈተናው ነሐሴ 28/2018 ዓ.ም ይሰጣል።
@tikvahuniversity
380 835
በሰሜን ሸዋ ዞን ማረሚያ ቤቶች መምሪያ ሥር የሚገኘው ተሐድሶ አምባ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ፈተና ከወሰዱ ታራሚ ተፈታኞች መካከል 91% ታራሚዎችን አሳልፏል። 👏👏
ትምህርት ቤቱ ላለፉት አራት ዓመታት አንድም ተማሪ ማሳለፍ ያልቻለ ቢሆንም፣ ዘንድሮ 91 በመቶ ታራሚ ተፈታኞቹን ማሳለፍ መቻሉ ተገልጿል።
ታራሚ ተፈታኞቹ ጥሩ ውጤት እንዲያመጡ የማጠናከሪያ ትምህርት ይሰጣቸው እንደነበር የሰሜን ሸዋ ዞን ማረሚያ ቤቶች መምሪያ ኃላፊ ኮማንደር የቻለሰው አሰፋ ለአሚኮ ተናግረዋል።
@tikvahuniversity
