213 598
Subscribers
+7924 hours
+5267 days
+3 38030 days
Posting time distributions
Data loading in progress...
Find out who reads your channel
This graph will show you who besides your subscribers reads your channel and learn about other sources of traffic.Publication analysis
Posts | Views | Shares | Views dynamics |
01 #ጥቆማ
የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት በክረምት የስልጠና መርሐግብር የሚሳተፉ ተማሪዎች ምዝገባ ጀምሯል።
እነማን ይመዘገባሉ?
የመጀመሪያ እና የሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች
የምዝገባ ጊዜ፦
ከሚያዝያ 17 እስከ ግንቦት 7/2016 ዓ.ም
ስልጠናው መቼ ይጀምራል?
ከሐምሌ 1 እስከ ጳጉሜን 1/2016 ዓ.ም
(ለሁለት ወራት) (በሳምንት ለአራት ቀናት)
ስልጠናው ትኩረት የሚያደርግባቸው፦
➭ የሰው ሰራሽ አስተውሎት መሰረታውያን፣
➭ ሮቦቲክስ፣
➭ ፕሮግራሚንግ፣
➭ ማሽን ለርኒንግ እና ሌሎችም።
ምዝገባ የማድረጊያ አማራጮች፦
👉 forms.gle/9B79pzGLdo84W2LY8
👉 https://www.aii.et/summer-camp-registration-form-for-student/
@tikvahuniversity | 20 152 | 104 | Loading... |
02 ሠመራ ዩኒቨርሲቲ ያቋቋመው 'አፋር ታለንት አካዳሚ' የመጀመሪያ ዙር ሰልጣኞቹን ተቀብሏል፡፡
አካዳሚው 103 የዘጠነኛ ክፍል ተማሪዎችን በዚህ ሳምንት መቀበሉን የኒቨርሲቲው ገልጿል፡፡
ባለፈው ጥቅምት በሠመራ ዩኒቨርሲቲ እና በአፋር ክልል ትምህርት ቢሮ ትብብር የተቋቋመው አካዳሚው፤ በስምንተኛ ክፍል ሚኒስትሪ ፈተና ከፍተኛ ነጥብ ያስመዘገቡና ባለልዩ ተሰጥኦ ተማሪዎችን በመመልመል የሚቀበል መሆኑ ተገልጿል።
@tikvahuniversity | 22 279 | 4 | Loading... |
03 #MoE
የ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና በተመረጡ 25 የክልል ከተሞች ለመስጠት ዝግጅት እየተደረገ ነው።
በወረቀት ከሚሰጠው ፈተና በተጨማሪ የሚሰጠው የኦንላይን ፈተና ተማሪዎች ከቦታ ቦታ ሳይጓጓዙ በየአካባቢያቸው ቤተሰቦቻቸው ጋር እያደሩ ፈተናውን እንዲወስዱ እንደሚያስችላቸው የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ አየለች እሸቴ ተናግረዋል።
የፈተና አሰጣጡን ስኬታማ ለማድረግ ባለድርሻ አካላት በቅንጅት በመስራት ኃላፊነታቸውን ሊወጡ እንደሚገባ ሚኒስትር ድኤታዋ ጠቁመዋል።
የኦንላይን ተፈታኞች ፈተናውን ከመውሰዳቸው በፊት ደጋግመው እንዲለማመዱ የሚያስችል ቅድመ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑንም ተገልጿል።
@tikvahuniversity | 38 329 | 297 | Loading... |
04 በአዲስ አበባ የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተናን በበይነ መረብ / ኦንላይን ለመስጠት እየተከናወኑ በሚገኙ የቅድመ ዝግጅት ተግባራት ዙሪያ ውይይት ተካሂዷል።
በውውይይቱ ፦
- የክፍለ ከተማ ትምህርት ጽህፈት ቤት ኃላፊዎችን
- የመንግስትና የግል ትምህርት ቤት ርዕሳነ መምህራን ተሳትፈዋል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ዘላለም ሙላቱ ፤ የ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና በከተማ አስተዳደሩ በበይነ መረብ ለመስጠት ከወዲሁ የተለያዩ የቅድመ ዝግጅት ተግባራት በመከናወን ላይ ይገኛሉ ብለዋል።
ፈተናው ኦን ላይን እንደመሰጠቱ ኮምፒውተሮች ፣ ላፕቶፖች እና ታብሌቶችን ጨምሮ ሎሎች አስፈላጊ ግብአቶችን የማሟላት ስራ መጀመሩን አስታውቀዋል።
የግል ትምህርት ቤቶች ለፈተናው አስፈላጊ የሆኑ ግብአቶችን የማዘጋጀት ተግባራቸውን ከወዲሁ በመጀመር ፈተናው በታቀደለት መርሀ ግብር እንዲሰጥ የበኩላቸውን ኃላፊነት ሊወጡ ይገበል ብለዋል።
የ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ከሀምሌ 3 እስከ 5 የማህበራዊ ሳይንስ እንዲሁም ከሀምሌ 9 እስከ 11/2016 ዓ.ም የተፈጥሮ ሳይንስ ፈተና እንደሚሰጥ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች ኤጀንሲ በትላንትናው እለት መግለጹ ይታወቃል።
ምንጭ፦ የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ
@tikvahethiopia | 40 972 | 113 | Loading... |
05 #DambiDolloUniversity
ደምቢ ዶሎ ዩኒቨርሲቲ ዘንድሮ የመውጫ ፈተና ለሚወስዱ ዕጩ የቅድመ ምረቃ ተመራቂ ተማሪዎች #ሞዴል የመውጫ ፈተና መስጠት ጀምሯል፡፡
የ2016 ዓ.ም የመውጫ ፈተና ከሰኔ 14-21/2016 ዓ.ም እንደሚሰጥ መገለፁ ይወቃል፡፡
ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ለዕጩ የቅድመ ምረቃ ተመራቂ ተማሪዎቻቸው #ሞዴል የመውጫ ፈተና እንዲሰጡ የትምህርት ሚኒስቴር መመሪያ ያስገድዳል፡፡
@tikvahuniversity | 38 287 | 19 | Loading... |
06 አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የስታርት አፕ ማዕከል በቅርቡ ሥራ እንደሚያስጀምር ገልጿል፡፡
መንግሥት የቴክኖሎጂ ፈጠራዎችን ለማስፋፋት የስታርት አፕ ልማትን የሚያጎለብቱ የተለያዩ ፖሊሲዎች እያተዘጋጁ እንደሆነ ይገልጻል፡፡
በቅርቡም የፈጠራ ሐሳብ ያላቸው ወጣቶች ሐሳባቸውን ወደ ተግባር ለማዋል በሚፈልጉበት ወቅት ያለምንም የንግድ ቤት ኪራይ ውል ሥራ መጀመር የሚችሉበትን አዲስ አሠራር መዘርጋቱን ይፋ ማድረጉ ይታወቃል፡፡
በተጨማሪም ማንኛውም የውጭ አገር ፈንድ ያገኘ ስታርት አፕ ሙሉ በሙሉ የውጭ ምንዛሪውን ለሚፈልገው ሥራ ማዋል የሚችልበት አሠራር ተግባራዊ መደረጉ ተገልጾ ነበር።
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሚከፍተው የስታርት አፕ ማዕከል በዘርፉ የተጀመሩ ሥራዎችን የበለጠ ለማጠናከር አጋዥ እንደሚሆን ይታመናል፡፡
@tikvahuniversity | 34 850 | 27 | Loading... |
07 #ምስላዊ_መረጃ
የ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ከሐምሌ 3-11/2016 ዓ.ም ይሰጣል።
በዚህ ዓመት የሚሰጠውን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ለመውሰድ ከ670 ሺህ በላይ ተማሪዎች ምዝገባ እንዳደረጉ መገለፁ ይታወሳል፡፡
@tikvahuniversity | 32 947 | 70 | Loading... |
08 #የቻናል_ጥቆማ
🔔 ለኢንጂነሪንግ ተማሪዎች እና Construction ዘርፍ ላይ ለተሰማራችሁ በሙሉ‼️
የኮንስትራክሽን፣ ሲቪል ኢንጂነሪንግ፣ የአርክቴክቸር ተማሪ ነዎት? በጠቅላላ ኮንስትራክሽን የተሰማሩ ባለሙያ ነዎት?
📚 በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ የሌክቸር ትምህርቶች፣ መጻሕፍት፣ ቪዲዮዎች እና ጠቃሚ የኮንስትራክሽን ዕውቀት ለማግኘት ከታች ያለውን ሊንክ በመጫን ይቀላቀሉን!
👉 ክፍት የሥራ መደብ ማስታወቂያዎች፣
👉 አዲስ የሚወጡ የግንባታ ጨረታዎች፣
👉 እጅግ ጠቃሚ የኮንስትራክሽን መረጃዎች፣
👉 በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ሌክቸር የምታገኙበት፡፡
Join Us :-
✅on Telegram 👇
https://t.me/ethioengineers1
https://t.me/ethioengineers1
✅on TikTok
tiktok.com/@ethiocons
tiktok.com/@ethiocons | 29 269 | 22 | Loading... |
09 #Update
የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና የሚሰጥበት ቀን ይፋ ሆነ።
የ2016 የትምህርት ዘመን የኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ (12ኛ ክፍል) ፈተና የሚሰጥበት ቀን ይፋ ሆኗል።
የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ሐምሌ 3 እስከ 5 ለማህበራዊ ሳይንስ ፤ ሐምሌ 9 እስከ 11/2016 ዓ/ም ለተፈጥሮ ሳይንስ ተፈታኞች በበይነ መረብ (Online) እና በዩኒቨርሲቲ ውስጥ በወረቀት ይሰጣል።
በወረቀት ላይ የሚፈተኑ የማህበራዊ ሳይንስ ተፈታኞች ሰኔ 30-ሐምሌ 01/2016 ዓ/ም እንዲሁም የተፈጥሮ ሳይንስ ሐምሌ 6-7/2016 ዓ/ም ወደ ዩኒቨርስቲ የሚገቡ ይሆናል።
መረጃው የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ነው።
@tikvahethiopia | 38 035 | 600 | Loading... |
10 "ትምህርት ለትውልድ" በተባለውና የትምህርት ቤቶችን መሠረተ ልማት ለማሻሻል በተጀመረው ሕዝባዊ ንቅናቄ ከ25.3 ቢሊየን ብር በላይ ሀብት መሰብሰቡን ትምህርት ሚኒስቴር ገለፀ፡፡
ባለፈው ዓመት መጨረሻ በተጀመረው ሕዝባዊ ንቅናቄ፤ በሁሉም ክልሎች እና በሁለቱ የከተማ አሰተዳደሮች ከ25.3 ቢሊየን ብር በላይ የሚገመት ሀብት መሰብሰቡን በሚኒስቴሩ የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አየለች እሸቴ ገልፀዋል።
በ2016 ዓ.ም ብቻ በትምህርት ለትውልድ መርሐግብር ከ4 ሺህ በላይ አዳዲስ የቅድመ አንደኛ፣ አንደኛ እና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች መገንባታቸውን ከሚኒስቴሩ የተገኘ መረጃ ያሳያል፡፡
የትምህርት ቤቶች ማሻሻያ እና ማስፋፊያ ሥራ በሚቀጥሉት አምስት ዓመታት ለማጠናቀቅ እየተሠራ እንደሚገኝ ተገልጿል።
@tikvahuniversity | 36 394 | 4 | Loading... |
11 ዲላ ዩኒቨርሲቲ በጌዴኦ ዞን ለሚገኙና ዘንድሮ የመልቀቂያ ፈተና ለሚወስዱ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች የማጠናከሪያ ትምህርት መስጠት ጀመረ፡፡
ዩኒቨርሲቲው በበጎ ፍቃደኛ መምህራን በመታገዝ በተለያዩ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለሚገኙ ተማሪዎች የማጠናከሪያ ትምህርት ለመስጠት የማስጀመሪያ መርሐግብር አከናውኗል፡፡
በጉዲኦ ዞን ከሚገኙ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች መካከል አምስት ትምህርት ቤቶች ላለፉት ሦስት ዓመታት አንድም ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ አለማሳለፋቸውን የዲላ ዩኒቨርሲቲ የትምህርት እና ስነ-ባህሪ ተቋም ያደረገው ጥናት ያሳያል፡፡
በመሆኑም የማጠናከሪያ ትምህርቱ በጌዴኦ ዞን የሚታየውን ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገቡ ተማሪዎች ቁጥር ማነስን ለማሻሻል ትልቅ ፋይዳ ይኖረዋል ተብሏል፡፡
የማጠናከሪያ ትምህርቱ ለአንድ ወር ከአንድ ሳምንት የሚቆይ ሲሆን፤ በተመረጡት ትምህርት ቤቶች አርብ፣ ቅዳሜ እና እሁድ የሚሰጥ መሆኑ ተገልጿል።
@tikvahuniversity | 37 493 | 13 | Loading... |
12 #ጥቆማ
የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት በክረምት የስልጠና መርሐግብር የሚሳተፉ ተማሪዎች ምዝገባ ጀምሯል።
እነማን ይመዘገባሉ?
የመጀመሪያ እና የሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች
የምዝገባ ጊዜ፦
ከሚያዝያ 17 እስከ ግንቦት 7/2016 ዓ.ም
ስልጠናው መቼ ይጀምራል?
ከሐምሌ 1 እስከ ጳጉሜን 1/2016 ዓ.ም
(ለሁለት ወራት) (በሳምንት ለአራት ቀናት)
ስልጠናው ትኩረት የሚያደርግባቸው፦
➭ የሰው ሰራሽ አስተውሎት መሰረታውያን፣
➭ ሮቦቲክስ፣
➭ ፕሮግራሚንግ፣
➭ ማሽን ለርኒንግ እና ሌሎችም።
ምዝገባ የማድረጊያ አማራጮች፦
👉 forms.gle/9B79pzGLdo84W2LY8
👉 https://www.aii.et/summer-camp-registration-form-for-student/
@tikvahuniversity | 41 115 | 214 | Loading... |
13 #ጥቆማ
በ Ethiopian Capital Market (ካፒታል ገበያ) የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ላይ ይሳተፉ!
መቼ?
ነገ ሰኞ ሚያዚያ 21/2016 ዓ.ም ጠዋት 2:30
የት?
በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ዋናው ግቢ አፍሪካ ህብረት አዳራሽ
ስልጠናውን ማን ይሰጠዋል?
የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለስልጣን ባለሙያዎች
@tikvahuniversity | 36 222 | 20 | Loading... |
14 #የቻናል_ጥቆማ
🔔 ለኢንጂነሪንግ ተማሪዎች እና Construction ዘርፍ ላይ ለተሰማራችሁ በሙሉ‼️
የኮንስትራክሽን፣ ሲቪል ኢንጂነሪንግ፣ የአርክቴክቸር ተማሪ ነዎት? በጠቅላላ ኮንስትራክሽን የተሰማሩ ባለሙያ ነዎት?
📚 በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ የሌክቸር ትምህርቶች፣ መጻሕፍት፣ ቪዲዮዎች እና ጠቃሚ የኮንስትራክሽን ዕውቀት ለማግኘት ከታች ያለውን ሊንክ በመጫን ይቀላቀሉን!
👉 ክፍት የሥራ መደብ ማስታወቂያዎች፣
👉 አዲስ የሚወጡ የግንባታ ጨረታዎች፣
👉 እጅግ ጠቃሚ የኮንስትራክሽን መረጃዎች፣
👉 በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ሌክቸር የምታገኙበት፡፡
Join Us :-
✅on Telegram 👇
https://t.me/ethioengineers1
https://t.me/ethioengineers1
✅on TikTok
tiktok.com/@ethiocons
tiktok.com/@ethiocons | 27 173 | 14 | Loading... |
15 አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያሰለጠናቸውን 154 ተማሪዎች አስመርቋል፡፡
ዩኒቨርሲቲው በመጀመሪያ ዲግሪ ፕሮግራም የሰለጠኑ 110 እንዲሁም በሁለተኛ ዲግሪ ፕሮግራም ትምህርታቸውን የተከታተሉ 44 ተማሪዎችን በዛሬው ዕለት አስመርቋል።
በመጀመሪያ ዲግሪ ከተመረቁት መካከል107ቱ በጤና ሳይንስ የትምህርት መስኮች የሰለጠኑ መሆናቸው ተገልጿል፡፡
@tikvahuniversity | 41 718 | 16 | Loading... |
16 #HawassaUniversity👏
የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የፊታችን ሰኞ የጨረር ህክምና መስጠት ይጀምራል።
ማዕከሉ ለመጀመሪያ ዙር ፈቃደኛ ሆነው በተገኙ 30 ታካሚዎች ነው የጨረር ህክምና አገልግሎት መስጠት የሚጀምረው። #ኢፕድ
@tikvahethiopia | 37 836 | 11 | Loading... |
17 " የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና በተመረጡ ከተሞች በኦንላይን ይሰጣል " - ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ
የ2016 ዓ.ም 12ኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተና በተመረጡ ከተሞች በኦንላይን እንደሚሰጥ ትምህርት ሚኒስቴር አስታውቋል።
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ ፤ " ፈተናው ሙሉ በሙሉ በኦንላይን ለመስጠት ባይቻልም በክልሎች በተመረጡ ከተሞች ለመስጠት እየተሠራ ነው " ብለዋል።
በሁሉም ክልሎች ያሉ የተመረጡ ተማሪዎች በኦንላይን ፈተናቸውን ይወስዳሉ ሲሉ አሳውቀዋል።
ቀሪዎቹ ደግሞ በተለመደው አግባብ ፈተናቸውን እንደሚወስዱ ገልጸዋል።
የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ዳይሬክተር ዶ/ር እሸቱ ከበደ በበኩላቸው ፤ ፈተናው በኦንላይን ለመሥጠት የሚያስችል የቅድመ ዝግጅት ሥራ እየተሠራ ነው ብለዋል።
ተማሪዎች በሙከራ ፈተና እንዲለማመዱ እንደሚደረግ ገልጸዋል።
የአሰልጣኞች ስልጠና በመስጠት ተማሪዎች ተደጋጋሚ ስልጠና እንደሚሰጣቸው አመልክተዋል።
ከቀጣይ ሳምንት ጀምሮ የአሰልጣኞች ስልጠና መስጠት ይጀመራል ብለዋል።
#MoE
@tikvahethiopia | 31 460 | 264 | Loading... |
18 #DebreBerhanUniversity
የደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ንጉስ ታደሰ (ዶ/ር) በሥራ ገበታቸው ላይ ከታዩ አንድ ወር እንዳለፋቸው አል-ዐይን አማርኛ የተቋሙን አንድ አመራር በመጥቀስ ዘግቧል፡፡ ፕሬዝዳንቱ "የት እንዳሉ እንደማይታወቅ" ዘገባው ጠቅሷል፡፡
ከሦስት ዓመት በፊት የደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ሆነው የተሾሙት ንጉስ ታደሰ (ዶ/ር) በቢሯቸው ከታዩ አንድ ወር አልፏቸዋል ተብሏል።
"ፕሬዝዳንቱ ከመጋቢት 17 ቀን 2016 ዓ. ም ጀምሮ በሥራ ላይ አይተናቸው አናውቅም" ሲሉ ስማቸው እንዳይጠቀስ የፈለጉ አንድ የዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ አመራር ለአል-ዐይን አማርኛ ተናግረዋል፡፡
"ከተጠቀሰው ቀን አንስቶ ፕሬዝዳንቱ የት እንደሔዱና መቼ እንደሚመለሱ አናውቅም" ያሉት የተቋሙ አመራር፤ "ፕሬዝዳንቱ በቢሮ መታየት ካቆሙ ከተወሰኑ ቀናት በኋላ ባልታወቁ ኃይሎች መታገታቸውን ሰምተናል" ሲሉም አክለዋል።
የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት መሰወርን አስመልክቶ አል-ዐይን አማርኛ የሰሜን ሸዋ ዞን ፖሊስ፣ የሰሜን ሸዋ ኮማንድ ፖስት፣ ትምህርት ሚኒስቴር እና የደብረ ብረሃን ከተማ ፖሊስ ምላሽ እንዲሰጡ ያደረገው ጥረት አለመሳካቱን ገልጿል። የፕሬዝዳንቱ ቤተሰብ ተጨማሪ መረጃ እንዲሰጡ አል-ዐይን ያደረገው ተደጋጋሚ ጥረትም አልተሳካም።
የደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንትን በተመለከተ ዩኒቨርሲቲው እንዲሁም ትምህርት ሚኒስቴር የሚሉትን ወደናንተ እናደርሳለን፡፡ #አልዐይንአማርኛ
@tikvahuniversity | 29 879 | 35 | Loading... |
19 Ready to empower the next generation of learners?
Join us on EdTech Mondays for an eye-opening discussion on Financing EdTech Startups in Ethiopia! Discover how investors are igniting innovation and driving change in the education landscape, overcoming unique challenges to support promising ventures. From bridging the digital divide to enhancing learning outcomes, explore the transformative potential of investing in EdTech startups. Tune in and be part of the movement to revolutionize education in Ethiopia!
Monday, April 29th at 8:10 pm on Fana FM 98.1 for insights that matter.
#EdTechEthiopia #EducationInnovation #JoinTheConversation #Ethiopia #DigitalLiteracy #TechnologyInEducation #EdTechMondaysEthiopia #EquityInEducation #Ethiopia #DigitalLiteracy #ShegaMedia #MastercardFoundation | 35 123 | 10 | Loading... |
20 #ይጠንቀቁ
"ሰርተፊኬት የሚያሰጡ ነጻ የኦንላይን ስልጠና " የሚሉ ማስታወቂያዎች በማኅበራዊ ትስስር ገጾች እየተዘዋወሩ መሆኑን ተመልክተናል፡፡ ማስታወቂያዎቹ የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎችን እንዲሁም የትምህርት ሚኒስቴርን ስም ይጠቅሳሉ፡፡
ይሁን እንጂ እነዚህ ማስታወቂያዎች ሐሰተኛ መሆናቸውን ዩኒቨርሲዎቹ አረጋግጠዋል፡፡
"የተቋሜን ስም በመጠቀም የሚፈፀም የማጭበርበር ተግባር ሰለሆነ የሚመለከተው ሁሉ አስፈላጊውን ጥንቃቄ እንዲያደርግ አሳስባለው" ብሏል መቐለ ዩኒቨርሲቲ፡፡
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተመሳሳይ የማስጠንቀቂያ መልዕክት ከጥቂት ሳምንታት በፊት አውጥቶ እንደደነበር አይዘነጋም፡፡
"በተለያዩ ድረ-ገጾች እና ማኅበራዊ ሚዲያዎች የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲን ስም እና አርማ በመጠቀም ከሚተላለፉ ሐሰተኛ መረጃዎች እንዲጠነቀቁ" ብሏል ዩኒቨርሲቲው፡፡
@tikvahuniversity | 45 128 | 42 | Loading... |
21 #የሥራ_ቅጥር_ጥቆማ
ድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የሥራ መደቦች መምህራንና ቴክኒካል ረዳቶች አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል፡፡
➤ ተፈላጊ ባለሙያዎች ብዛት፦ 19
➤ የትምህርት ደረጃ፦ የመጀመሪያ እና 2ኛ ዲግሪ
➤ የሥራ ልምድ፦ ዜሮ ዓመትና ከዚያ በላይ
➤ የሥራ ቦታ፦ ድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ
➤ የማመልከቻ ጊዜ፦ ከሚያዝያ 17/2016 ዓ.ም ጀምሮ ባሉት 10 ተከታታይ የሥራ ቀናት
➤ የምዝገባ ቦታ፦ አዲስ አበባ አሜሪካ ኤምባሲ ፊት ለፊት በሚገኘው የትምህርት መሳሪያዎች ማምረቻና ማከፋፈያ ድርጅት ቢሮ ወይም ድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ የአስተዳደር ህንጻ 3ኛ ፎቅ ቢሮ ቁ. B-4
ለተጨማሪ መረጃ፦ አ.አ. 0111-26-01-24 ፖ.ሳ.ቁ. 1362
@tikvahuniversity | 50 370 | 130 | Loading... |
22 ማክሰኞ ሚያዚያ 22/2016 ዓ.ም 20ኛ ዙር የግራፊክስ ዲዛይን፣ ቪዲዮ ኢዲቲንግ፣ ሞሽን ግራፊክስ እና ዲጂታል ማርኬቲንግ ስልጠና ይጀምራል።
🔔 ቀድመው ይመዝገቡ!
👉 100% በተግባር የተደገፈ ስልጠና
👉 ከ15 በላይ ፕሮጀክቶች ያሉት
👉 የሥራ ላይ ስልጠና (Internship) የተመቻቸለት
👉 Advanced Graphics + Video Editing + Motion Graphics + Digital Marketing በአንድ ላይ
☎️ ለበለጠ መረጃ፦ 0906777799 / 0906777755
አድራሻ፦ ፒያሣ ቸርችል ጎዳና ኤልያና ሆቴል 2ኛ ፎቅ
የበለጠ ይጠብቁ ...
ሴጅ ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት
Facebook | Telegram | Instagram | LinkedIn | 33 037 | 26 | Loading... |
23 ወልድያ ዩኒቨርሲቲ አዲስ ምክትል ፕሬዝዳንቶች ተመድበውለታል፡፡
ካሳሁን አህመድ (ዶ/ር) የወልድያ ዩኒቨርሲቲ የአካዳሚክ፣ ምርምር ቴክኖሎጂ ሽግግርና ማህበረሰብ አገልግሎት ምክትል ፕሬዝዳንት ሆነው ተመድበዋል፡፡
ማርየ በለጠ (ዶ/ር) የዩኒቨርሲቲው አስተዳደርና ቢዝነስ ልማት ምክትል ፕሬዝዳንት ሆነው በትምህርት ሚኒስቴር እና በቦርድ አፅዳቂነት ተመድበዋል፡፡
አዲስ የተሾሙት አመራሮች ከተቋሙ የሥራ ኃላፊዎች ጋር ትውውቅ አድርገዋል፡፡
@tikvahuniversity | 42 134 | 15 | Loading... |
24 #YHMC
የካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ ለመጀመሪያ ጊዜ በዲግሪ መርሐግብር ማስተማር ጀመረ።
ኮሌጁ በዛሬው ዕለት 79 ተማሪዎችን በመቀበል በዲግሪ መርሐግብር ትምህርት መስጠት መጀመሩ ተሰምቷል።
ኮሌጁ በመጀመሪያ ዲግሪ ፕሮግራም ማስተማር የጀመረባቸው መስኮች፦
➤ በድንገተኛ ሕክምና ነርስነት (Emergency and Critical Nursing)
➤ በጨቅላ ሕጻናት ነርስነት (Neonatal Nursing)
➤ በአጠቃላይ ነርስነት (Comprehensive Nursing)
➤ በላቦራቶሪ ባለሙያ (Medical Lab)
@tikvahuniversity | 44 840 | 26 | Loading... |
25 #የፈተና_ጥሪ
ደባርቅ ዩኒቨርሲቲ በመምህርነት እና በቴክኒካል አሲስታንት የሥራ መደቦች ባለሙያዎችን አወዳድሮ ለመቅጠር በቅርቡ ላወጣው ማስታወቂያ ላመለከቱ የፈተና ጥሪ አድርጓል።
ለፈተና የተመረጡ ባለሙያዎች በተቋሙ የቴሌግራም ገፅ በመግባት መመረጣቸውን ይመልከቱ 👇
https://t.me/dkulatestnews/74
ለፈተና የተመረጣችሁ ሚያዝያ 21/2016 ዓ.ም የተጠየቀውን መስፈርት አሟልታችሁ በዩኒቨርሲቲው የሰው ሃብት አስተዳደር ቢሮ እንድትቀርቡ ተብሏል።
@tikvahuniversity | 39 323 | 7 | Loading... |
26 Media files | 2 | 0 | Loading... |
27 ስትጠብቁት የነበረው የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና አጋዥ አፕሊኬሽናችን አሁን Play Store ላይ ይገኛል። Download እና Upgrade በማድረግ ይጠቀሙባቸው!!
✅ በነጻ ለውስን ቀናት
✅ አዲሱን ስርአተ ትምህርት ያካተተ
✅ አጫጭር ኖቶችና አጋዥ ቪድዮዎች የያዘ
አሁኑኑ ይሞክሩት!!
ለማውረድ ይህን ማስፈንጠሪያ መጠቀም ይቻላል ➝ Playstore
የማህበራዊ ትስስር ገፆቻችን ቤተሰብ ይሁኑ፦
Instagam | Telegram | YouTube | Facebook | TikTok | 25 188 | 84 | Loading... |
Photo unavailableShow in Telegram
#ጥቆማ
የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት በክረምት የስልጠና መርሐግብር የሚሳተፉ ተማሪዎች ምዝገባ ጀምሯል።
እነማን ይመዘገባሉ?
የመጀመሪያ እና የሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች
የምዝገባ ጊዜ፦
ከሚያዝያ 17 እስከ ግንቦት 7/2016 ዓ.ም
ስልጠናው መቼ ይጀምራል?
ከሐምሌ 1 እስከ ጳጉሜን 1/2016 ዓ.ም
(ለሁለት ወራት) (በሳምንት ለአራት ቀናት)
ስልጠናው ትኩረት የሚያደርግባቸው፦
➭ የሰው ሰራሽ አስተውሎት መሰረታውያን፣
➭ ሮቦቲክስ፣
➭ ፕሮግራሚንግ፣
➭ ማሽን ለርኒንግ እና ሌሎችም።
ምዝገባ የማድረጊያ አማራጮች፦
👉 forms.gle/9B79pzGLdo84W2LY8
👉 https://www.aii.et/summer-camp-registration-form-for-student/
@tikvahuniversity
👍 56❤ 10🙏 1
ሠመራ ዩኒቨርሲቲ ያቋቋመው 'አፋር ታለንት አካዳሚ' የመጀመሪያ ዙር ሰልጣኞቹን ተቀብሏል፡፡
አካዳሚው 103 የዘጠነኛ ክፍል ተማሪዎችን በዚህ ሳምንት መቀበሉን የኒቨርሲቲው ገልጿል፡፡
ባለፈው ጥቅምት በሠመራ ዩኒቨርሲቲ እና በአፋር ክልል ትምህርት ቢሮ ትብብር የተቋቋመው አካዳሚው፤ በስምንተኛ ክፍል ሚኒስትሪ ፈተና ከፍተኛ ነጥብ ያስመዘገቡና ባለልዩ ተሰጥኦ ተማሪዎችን በመመልመል የሚቀበል መሆኑ ተገልጿል።
@tikvahuniversity
👍 49😢 4👎 1❤ 1
#MoE
የ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና በተመረጡ 25 የክልል ከተሞች ለመስጠት ዝግጅት እየተደረገ ነው።
በወረቀት ከሚሰጠው ፈተና በተጨማሪ የሚሰጠው የኦንላይን ፈተና ተማሪዎች ከቦታ ቦታ ሳይጓጓዙ በየአካባቢያቸው ቤተሰቦቻቸው ጋር እያደሩ ፈተናውን እንዲወስዱ እንደሚያስችላቸው የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ አየለች እሸቴ ተናግረዋል።
የፈተና አሰጣጡን ስኬታማ ለማድረግ ባለድርሻ አካላት በቅንጅት በመስራት ኃላፊነታቸውን ሊወጡ እንደሚገባ ሚኒስትር ድኤታዋ ጠቁመዋል።
የኦንላይን ተፈታኞች ፈተናውን ከመውሰዳቸው በፊት ደጋግመው እንዲለማመዱ የሚያስችል ቅድመ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑንም ተገልጿል።
@tikvahuniversity
👍 120👎 110❤ 15😢 14👏 6🥰 3🙏 1
በአዲስ አበባ የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተናን በበይነ መረብ / ኦንላይን ለመስጠት እየተከናወኑ በሚገኙ የቅድመ ዝግጅት ተግባራት ዙሪያ ውይይት ተካሂዷል።
በውውይይቱ ፦
- የክፍለ ከተማ ትምህርት ጽህፈት ቤት ኃላፊዎችን
- የመንግስትና የግል ትምህርት ቤት ርዕሳነ መምህራን ተሳትፈዋል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ዘላለም ሙላቱ ፤ የ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና በከተማ አስተዳደሩ በበይነ መረብ ለመስጠት ከወዲሁ የተለያዩ የቅድመ ዝግጅት ተግባራት በመከናወን ላይ ይገኛሉ ብለዋል።
ፈተናው ኦን ላይን እንደመሰጠቱ ኮምፒውተሮች ፣ ላፕቶፖች እና ታብሌቶችን ጨምሮ ሎሎች አስፈላጊ ግብአቶችን የማሟላት ስራ መጀመሩን አስታውቀዋል።
የግል ትምህርት ቤቶች ለፈተናው አስፈላጊ የሆኑ ግብአቶችን የማዘጋጀት ተግባራቸውን ከወዲሁ በመጀመር ፈተናው በታቀደለት መርሀ ግብር እንዲሰጥ የበኩላቸውን ኃላፊነት ሊወጡ ይገበል ብለዋል።
የ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ከሀምሌ 3 እስከ 5 የማህበራዊ ሳይንስ እንዲሁም ከሀምሌ 9 እስከ 11/2016 ዓ.ም የተፈጥሮ ሳይንስ ፈተና እንደሚሰጥ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች ኤጀንሲ በትላንትናው እለት መግለጹ ይታወቃል።
ምንጭ፦ የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ
@tikvahethiopia
👍 117👎 29❤ 14😱 1
#DambiDolloUniversity
ደምቢ ዶሎ ዩኒቨርሲቲ ዘንድሮ የመውጫ ፈተና ለሚወስዱ ዕጩ የቅድመ ምረቃ ተመራቂ ተማሪዎች #ሞዴል የመውጫ ፈተና መስጠት ጀምሯል፡፡
የ2016 ዓ.ም የመውጫ ፈተና ከሰኔ 14-21/2016 ዓ.ም እንደሚሰጥ መገለፁ ይወቃል፡፡
ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ለዕጩ የቅድመ ምረቃ ተመራቂ ተማሪዎቻቸው #ሞዴል የመውጫ ፈተና እንዲሰጡ የትምህርት ሚኒስቴር መመሪያ ያስገድዳል፡፡
@tikvahuniversity
👍 59❤ 15👎 4🙏 1
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የስታርት አፕ ማዕከል በቅርቡ ሥራ እንደሚያስጀምር ገልጿል፡፡
መንግሥት የቴክኖሎጂ ፈጠራዎችን ለማስፋፋት የስታርት አፕ ልማትን የሚያጎለብቱ የተለያዩ ፖሊሲዎች እያተዘጋጁ እንደሆነ ይገልጻል፡፡
በቅርቡም የፈጠራ ሐሳብ ያላቸው ወጣቶች ሐሳባቸውን ወደ ተግባር ለማዋል በሚፈልጉበት ወቅት ያለምንም የንግድ ቤት ኪራይ ውል ሥራ መጀመር የሚችሉበትን አዲስ አሠራር መዘርጋቱን ይፋ ማድረጉ ይታወቃል፡፡
በተጨማሪም ማንኛውም የውጭ አገር ፈንድ ያገኘ ስታርት አፕ ሙሉ በሙሉ የውጭ ምንዛሪውን ለሚፈልገው ሥራ ማዋል የሚችልበት አሠራር ተግባራዊ መደረጉ ተገልጾ ነበር።
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሚከፍተው የስታርት አፕ ማዕከል በዘርፉ የተጀመሩ ሥራዎችን የበለጠ ለማጠናከር አጋዥ እንደሚሆን ይታመናል፡፡
@tikvahuniversity
👍 62👏 9❤ 8
Photo unavailableShow in Telegram
#ምስላዊ_መረጃ
የ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ከሐምሌ 3-11/2016 ዓ.ም ይሰጣል።
በዚህ ዓመት የሚሰጠውን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ለመውሰድ ከ670 ሺህ በላይ ተማሪዎች ምዝገባ እንዳደረጉ መገለፁ ይታወሳል፡፡
@tikvahuniversity
👍 39❤ 5👏 2
Photo unavailableShow in Telegram
#የቻናል_ጥቆማ
🔔 ለኢንጂነሪንግ ተማሪዎች እና Construction ዘርፍ ላይ ለተሰማራችሁ በሙሉ‼️
የኮንስትራክሽን፣ ሲቪል ኢንጂነሪንግ፣ የአርክቴክቸር ተማሪ ነዎት? በጠቅላላ ኮንስትራክሽን የተሰማሩ ባለሙያ ነዎት?
📚 በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ የሌክቸር ትምህርቶች፣ መጻሕፍት፣ ቪዲዮዎች እና ጠቃሚ የኮንስትራክሽን ዕውቀት ለማግኘት ከታች ያለውን ሊንክ በመጫን ይቀላቀሉን!
👉 ክፍት የሥራ መደብ ማስታወቂያዎች፣
👉 አዲስ የሚወጡ የግንባታ ጨረታዎች፣
👉 እጅግ ጠቃሚ የኮንስትራክሽን መረጃዎች፣
👉 በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ሌክቸር የምታገኙበት፡፡
Join Us :-
✅on Telegram 👇
https://t.me/ethioengineers1
https://t.me/ethioengineers1
✅on TikTok
tiktok.com/@ethiocons
tiktok.com/@ethiocons
👍 24👎 5❤ 3😢 3
Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
#Update
የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና የሚሰጥበት ቀን ይፋ ሆነ።
የ2016 የትምህርት ዘመን የኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ (12ኛ ክፍል) ፈተና የሚሰጥበት ቀን ይፋ ሆኗል።
የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ሐምሌ 3 እስከ 5 ለማህበራዊ ሳይንስ ፤ ሐምሌ 9 እስከ 11/2016 ዓ/ም ለተፈጥሮ ሳይንስ ተፈታኞች በበይነ መረብ (Online) እና በዩኒቨርሲቲ ውስጥ በወረቀት ይሰጣል።
በወረቀት ላይ የሚፈተኑ የማህበራዊ ሳይንስ ተፈታኞች ሰኔ 30-ሐምሌ 01/2016 ዓ/ም እንዲሁም የተፈጥሮ ሳይንስ ሐምሌ 6-7/2016 ዓ/ም ወደ ዩኒቨርስቲ የሚገቡ ይሆናል።
መረጃው የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ነው።
@tikvahethiopia
👍 213😱 19❤ 18👎 12🙏 4👏 2
Photo unavailableShow in Telegram
"ትምህርት ለትውልድ" በተባለውና የትምህርት ቤቶችን መሠረተ ልማት ለማሻሻል በተጀመረው ሕዝባዊ ንቅናቄ ከ25.3 ቢሊየን ብር በላይ ሀብት መሰብሰቡን ትምህርት ሚኒስቴር ገለፀ፡፡
ባለፈው ዓመት መጨረሻ በተጀመረው ሕዝባዊ ንቅናቄ፤ በሁሉም ክልሎች እና በሁለቱ የከተማ አሰተዳደሮች ከ25.3 ቢሊየን ብር በላይ የሚገመት ሀብት መሰብሰቡን በሚኒስቴሩ የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አየለች እሸቴ ገልፀዋል።
በ2016 ዓ.ም ብቻ በትምህርት ለትውልድ መርሐግብር ከ4 ሺህ በላይ አዳዲስ የቅድመ አንደኛ፣ አንደኛ እና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች መገንባታቸውን ከሚኒስቴሩ የተገኘ መረጃ ያሳያል፡፡
የትምህርት ቤቶች ማሻሻያ እና ማስፋፊያ ሥራ በሚቀጥሉት አምስት ዓመታት ለማጠናቀቅ እየተሠራ እንደሚገኝ ተገልጿል።
@tikvahuniversity
👍 44👎 17😢 2❤ 1