fa
Feedback
Tikvah-University

Tikvah-University

رفتن به کانال در Telegram

نمایش بیشتر

📈 تحلیل کانال تلگرام Tikvah-University

کانال Tikvah-University (@tikvahuniversity) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 366 242 مشترک است و جایگاه 125 را در دسته آموزش و رتبه 12 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 366 242 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 06 ژوئیه, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 6 380 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر 128 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 15.24% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 9.39% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 55 823 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 34 384 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 161 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

توضیحی برای کانال ارائه نشده است.

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 07 ژوئیه, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته آموزش تبدیل کرده‌اند.

366 242
مشترکین
+12824 ساعت
+4767 روز
+6 38030 روز
آرشیو پست ها
የትግራይ ክልል መምህራን ማኅበር በትግራይ ክልል የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ መልቀቂያ ፈተና የወረቀት ተፈታኞች የሚሰጥበት ጊዜ በትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ወደ ሐምሌ 22-24/2018 ዓ.ም መ
+1
የትግራይ ክልል መምህራን ማኅበር በትግራይ ክልል የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ መልቀቂያ ፈተና የወረቀት ተፈታኞች የሚሰጥበት ጊዜ በትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ወደ ሐምሌ 22-24/2018 ዓ.ም መራዘሙ ተገቢ አይደለም ሲል ወቅሷል። ማኅበሩ ዛሬ ባወጣው መግለጫ፣ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ቀድሞ ባወጣው መርሐግብር መሠረት የትግራይ ክልል ተማሪዎች ለፈተናው ተዘጋጅተው እንደነበር አስታውሷል። "ለትግራይ ተፈታኝ ተማሪዎች ብቻ መርሐግብሩ እንዲራዘም መደረጉ ተገቢ አይደለም" ያለው ማኅበሩ፤ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ቀድሞ ባወጣው መርሐግብር መሠረት ፈተናው እንዲሰጥ ጠይቋል። (የማኅበሩ መግለጫ ከላይ ተያይዟል።) @tikvahuniversity

የጤና ባለሙያዎች የሙያ ፈቃድ ፈተና በነሐሴ ወር 2018 ዓ.ም ይሰጣል። - ጤና ሚኒስቴር ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በመጀመሪያ ዲግሪ ለተመረቃችሁ የጤና ባለሙያዎች የሙያ ፈቃድ ፈተና በነሐሴ ወር 2
የጤና ባለሙያዎች የሙያ ፈቃድ ፈተና በነሐሴ ወር 2018 ዓ.ም ይሰጣል። - ጤና ሚኒስቴር ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በመጀመሪያ ዲግሪ ለተመረቃችሁ የጤና ባለሙያዎች የሙያ ፈቃድ ፈተና በነሐሴ ወር 2018 ዓ.ም ለመስጠት ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የጤና ሚኒስቴር ገልጿል። በመሆኑም መረጃችሁን ወደ ሲስተም ያላስገባችሁ ነባር እና አዲስ ተመዛኞች ከሰኔ 30 እስከ ሐምሌ 17/2018 ዓ.ም ድረስ ብቻ https://hple.moh.gov.et/ ላይ በመግባት የብሔራዊ መታወቂያ መለያ ቁጥር (FAN 16 Digit) በማስገባት አስፈላጊ መረጃዎችን በማሟላት ለምዝገባ እንድትዘጋጁ ሚኒስቴሩ አሳስቧል፡፡ መረጃ የማስተሳሰር ሂደት እንዳለቀ የፈተና ጣቢያ መረጣ ሂደት እንደሚቀጥል ተገልጿል፡፡ 🔔 በሰኔ 2018 ዓ.ም የመውጫ ፈተና ተፈትናችሁ ያለፉችሁ ተመዛኞች የስም ዝርዝራችሁን በተማራችሁበት ተቋም አማካኝነት ወደ ሲስተም ማስጫን ይጠበቅባችኋል ተብሏል። @tikvhauniversity

የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ የሁለተኛ ዙር ፈተና እየሠጠ ነው። ሰኔ 26/2018 ዓ.ም መሠጠት የጀመረው የሁለተኛ ዙር የኦንላይን ተፈታኝ የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች ነገ ማክሰኞ ይጠናቀቃል። የሦስተኛ ዙር
+3
የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ የሁለተኛ ዙር ፈተና እየሠጠ ነው። ሰኔ 26/2018 ዓ.ም መሠጠት የጀመረው የሁለተኛ ዙር የኦንላይን ተፈታኝ የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች ነገ ማክሰኞ ይጠናቀቃል። የሦስተኛ ዙር የተፈጥሮ ሳይንስ ተፈታኞች የወረቀት እና የኦንላይን ፈተና ከረቡዕ ሐምሌ 01/2018 ዓ.ም ጀምሮ ለሦስት ተከታታይ ቀናት ይሰጣል። ተፈታኞች ፈተናውን ወደሚወስዱበት ተቋማት መግባት ጀምረዋል። @tikvahuniversity

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ6ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና ካስፈተኑ 768 ትምህርት ቤቶች፥ 543ቱ ተማሪዎቻቸውን ሙሉ በሙሉ ማሳለፋቸው ተገለፀ። የአዲስ አበባ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የ2018
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ6ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና ካስፈተኑ 768 ትምህርት ቤቶች፥ 543ቱ ተማሪዎቻቸውን ሙሉ በሙሉ ማሳለፋቸው ተገለፀ። የአዲስ አበባ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የ2018 ዓ.ም የ6ኛ ክፍል ፈተና ውጤት ይፋ አድርጓል። በከተማ አስተዳደሩ በ2018 ዓ.ም የ6ኛ ክፍል ፈተና ከወሰዱ ተማሪዎች 97.48% የሚሆኑት 50% እና በላይ በማስመዝገብ ወደ 7ኛ ክፍል መዘዋወራቸውን ቢሮው አሳውቋል። በመዲናዋ ፈተናውን ከወሰዱ 84,257 የ6ኛ ክፍል ተማሪዎች መካከል 82,137 ተማሪዎች የማለፊያ ነጥብ ሆኖ የተቆረጠውን 50 በመቶ እና በላይ አስመዝግበዋል። ተማሪዎች ውጤት ለማየት 👇 https://aa6.ministry.et/#/result @tikvahuniversity

12ኛ ዙር የጋዜጠኝነት ስልጠና የፊታችን ቅዳሜ ሐምሌ 04/2018 ዓ.ም ይጀመራል። በስልጠናው 👉 መሠረታዊ የጋዜጠኝነት መርሆች ፣ የሚዲያ እና የጋዜጠኝነት አይነቶች 👉 የዜና አሰራር እና የቃለመ
12ኛ ዙር የጋዜጠኝነት ስልጠና የፊታችን ቅዳሜ ሐምሌ 04/2018 ዓ.ም ይጀመራል።  በስልጠናው 👉 መሠረታዊ የጋዜጠኝነት መርሆች ፣ የሚዲያ እና የጋዜጠኝነት አይነቶች  👉 የዜና አሰራር እና የቃለመጠይቅ አደራረግ 👉 የመዝናኛ ፕሮግራም ጋዜጠኝነት፣ የፕሮግራም ዝግጅት፣ የማስታወቂያ አሠራር እና የዶክመንተሪ ዝግጅት 👉 የሞባይል እና የዩቲዩብ ጋዜጠኝነት አካቷል፡፡ የበለጠ ይጠብቁ ... 💥 ሴጅ ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት 💥 ☎️  0906777799 / 0906777755 አድራሻ፦ ቁ.1: ፒያሣ ቸርችል ጎዳና ኤልያና ሆቴል 2ኛ ፎቅ፣ ቁ.2: መገናኛ ታሜጋስ ህንፃ 2ኛ ፎቅ እና ቁ.3: አዳማ ራስ ሆቴል 2ኛ ፎቅ ለመመዝገብ ድረ-ገጽ 👇 www.sageethiopia.com Telegram: https://t.me/sagetraininginstitute Tiktok: https://www.tiktok.com/@sage_training_institute

በትግራይ ክልል በወረቀት ለመፈተን ለተመዘገቡ 15,325 የ12ኛ ክፍል ተፈታኞች ፈተናው ከሐምሌ 22-24/2018 ዓ.ም እንደሚሰጥ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቋል። ተፈታኞቹ በተገለ
በትግራይ ክልል በወረቀት ለመፈተን ለተመዘገቡ 15,325 የ12ኛ ክፍል ተፈታኞች ፈተናው ከሐምሌ 22-24/2018 ዓ.ም እንደሚሰጥ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቋል። ተፈታኞቹ በተገለፁት ቀናት በመቐለ እና በአክሱም ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ በወረቀት እንደሚፈተኑ አገልግሎቱ ገልጿል። ተፈታኞች ወደተገለፁት ዩኒቨርሲቲዎች ሐምሌ 20/2018 ዓ.ም በመግባት እና ሐምሌ 21/2018 ዓ.ም ላይ ኦሬንቴሽን በመውሰድ መፈተን የሚችሉ መሆኑን አገልግሎቱ አብራርቷል። በተያያዘ በትግራይ ክልል በበይነ መረብ ለመፈተን የተመዘገቡ 14,755 ተፈታኞች በስድስቱ ዙር ከሰኔ 23/2018 ዓ.ም ጀምሮ ፈተናው እየተሰጠ መሆኑ ተመልክቷል። @tikvahuniversity

"ትምህርት ቢሮው የራሱን ፈተና አዘጋጅቶ ላልተፈተኑ ተማሪዎች በአጭር ጊዜ ውስጥ ይሰጣል።" - የትግራይ ክልል ትምህርት ቢሮ "ማንኛውም ክልል የሀገር አቀፍ ፈተና የማውጣት እና የመፈተን ስልጣን የለውም" - የፌዴራል መንግሥት የወረቀት ፈተናውን ከሐምሌ 22-24/2018 ዓ.ም ለመስጠት ታቅዷል። - የፌዴራል መንግሥት "ትምህርት ሚኒስቴር በወረቀት ለሚፈተኑ የትግራይ ተማሪዎች የፈተና ወረቀት አላከም" ያለው የትግራይ ክልል ትምህርት ቢሮ፤ በአጭር ጊዜ ውስጥ የራሱን ፈተና አዘጋጅቶ ላልተፈተኑ ተማሪዎች ፈተናውን እንደሚሰጥ አሳውቋል። ሰኔ 29/2018 ዓ.ም ዩኒቨርሲቲ ገብተው ከሐምሌ 01/2018 ዓ.ም ጀምሮ በወረቀት ሊፈተኑ የነበሩ 15,349 ተማሪዎች ፈተናው ከፌደራል መንግሥት ስላልተላከ ወደ ዩኒቨርሲቲ እንዳይጓዙ መደረጉን የቢሮው ኃላፊ ኪሮስ ጉዕሽ (ዶ/ር) ተናግረዋል። "ፈተናው በአውሮፕላን የሚመጣና በፌዴራል ፖሊስ የሚጠበቅ በመሆኑ፣ ወደ ትግራይ እንዳይላክ የሚያደርግ ምንም ዓይነት ምክንያት የለም" ያሉት ኃላፊው፤ "ውሳኔ ፖለቲካዊ ነው" ሲሉ ገልፀዋል። "የክልል ካቢኔ የፈተና ወረቀቱ በወቅቱ እንዲላክ ለፌዴራል መንግሥት ደብዳቤ አስተላልፏል። እስካሁን አውንታዊ ምላሽ አላገኘም" ብለዋል። በዚህም ትምህርት ቢሮው የራሱን ፈተና አዘጋጅቶ ላልተፈተኑ ተማሪዎች ፈተናውን በአጭር ጊዜ ውስጥ እንደሚሰጥ አመልክተዋል። የትግራይ ክልል ትምህርት ቢሮ "በራሴ ፈተና አዘጋጅቼ እፈትናለሁ" ማለቱን ተከትሎ፣ ስማቸው እንዲጠቀስ ያልፈለጉ የፌዴራል መንግሥት የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ታማኝ የመረጃ ምንጭ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ምላሽ ሰጥተዋል። እኚሁ ምንጭ "ይህን ፈተና የማዘጋጀት ስልጣን የፌዴራል መንግሥት የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ብቻ ነው " ያሉ ሲሆን፤ ማንኛውም ክልል የሀገር አቀፍ ፈተና የማውጣት እና የመፈተን ህጋዊ ስልጣን እንደሌለው ገልፀዋል። የትግራይ ክልል "እራሴ ፈተና አውጥቼ እፈትናለሁ" የሚለው አካሄድ ፍፁም ቅቡልነት የሌለው መሆኑን የገለፁት አመራሩ፤ "እንፈትናለን ብለው ከወሰኑና ፈተናውን ከሰጡ የፈተናው ውጤት ተቀባይነት ስለማይኖረው የተማሪዎችን ቀጣይ የህይወት ጉዞ ነው የሚያበላሹት" ሲሉ አስጠንቅቀዋል። ቀደም ብሎ በትግራይ ክልል በተካሄደው የኦንላይን ፈተና ወቅት የነበረውን ሁኔታ ያነሱት አመራሩ ፤ የፌዴራል ፀጥታ አካላትና ፈታኞች በአግባቡ ስራቸውን እንዳይወጡ ጫና ተደርጎባቸው እንደነበር ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልፀዋል። ለአብነትም ለጸጥታ ማስከበር ስራ የተሰማሩ አካላት እንኳን መሳሪያ እንዳይዙ የማድረግ ጫና እንደነበረባቸው ጠቅሰው፣ በወቅቱ የተማሪዎች ቀጣይ ህይወት ጉዞ እንዳይበላሽ ሲባል ብቻ ትምህርት ሚኒስቴር ፈተናው በጫና ውስጥም ቢሆን ታግሶ እንዲሰጥ ማድረጉን አስታውሰዋል። የአሁኑ የወረቀት ፈተና አግባብ ባለው የፈተና አካሄድና ስርዓት ከሐምሌ 22-24/2018 ዓ.ም ድረስ እንዲሰጥ መታቀዱን እኚሁ አካል ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልፀዋል። @tikvahethiopia

photo content
+2

#ጥቆማ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት በ34 አጫጭር የስልጠና ፕሮግራሞች በቅርቡ ስልጠና መስጠት እንደሚጀምር አሳውቋል። ኢንስቲትዩቱ ከደረጃ 6 እስከ ደረጃ 8 (ከመጀመሪያ ዲግሪ እስከ ፒኤችዲ
#ጥቆማ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት በ34 አጫጭር የስልጠና ፕሮግራሞች በቅርቡ ስልጠና መስጠት እንደሚጀምር አሳውቋል። ኢንስቲትዩቱ ከደረጃ 6 እስከ ደረጃ 8 (ከመጀመሪያ ዲግሪ እስከ ፒኤችዲ) እያሰለጠነ ሲሆን፤ የገበያ ፍላጎት በማጥናት በ34 የስልጠና ዘርፎች አጫጭር ስልጠናዎች በቅርቡ መስጠት እንደሚጀምር ገልጿል። @tikvahuniversity

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ2018 ዓ.ም የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ከተማ አቀፍ ፈተና ውጤት ነገ ይፋ እንደሚደረግ የከተማ አስተዳደሩ ትምህርት ቢሮ ገልጿል። በመዲናዋ የ6ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተ
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ2018 ዓ.ም የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ከተማ አቀፍ ፈተና ውጤት ነገ ይፋ እንደሚደረግ የከተማ አስተዳደሩ ትምህርት ቢሮ ገልጿል። በመዲናዋ የ6ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና ከሰኔ 8 -10/2018 ዓ.ም በ199 የመፈተኛ ጣቢያዎች ለሦስት ቀናት መሰጠቱ ይታወሳል፡፡ @tikvahuniversity

ማክሰኞ ሰኔ 30/2018 ዓ.ም ይጠናቀቃል! የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ከ1ኛ-12ኛ ክፍል ለሆናችሁ ተማሪዎች በተከታዮቹ መስኮች ላይ የክረምት ስልጠና ዕድል አዘጋጅቷል። ➫ ፈንዳ
ማክሰኞ ሰኔ 30/2018 ዓ.ም ይጠናቀቃል! የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ከ1ኛ-12ኛ ክፍል ለሆናችሁ ተማሪዎች በተከታዮቹ መስኮች ላይ የክረምት ስልጠና ዕድል አዘጋጅቷል። ➫ ፈንዳሜንታል ኦፍ ኤ.አይ. ➫ ፕሮግራሚንግ ➫ ማሽን ለርኒንግ ➫ ሮቦቲክስ እና IOT ➫ ዳታ ሳይንስ እና በሌሎችም የኤ.አይ. ዘርፎች እስከ ማክሰኞ ሰኔ 30/2018 ዓ.ም ድረስ በ https://aii.et/summercamp ላይ በመግባት ምዝገባዎን ያድርጉ! @tikvahuniversity

ብርቱዎቹ የ12ኛ ክፍል ተፈታኝ እናቶች እንዚህ እናቶች የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ለመፈተን ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ የተገኙ ተማሪዎች ናቸው፡፡ የእናትነት ኃላፊነትን እየተወጡ በተመሳሳይ ጊዜ የ
+1
ብርቱዎቹ የ12ኛ ክፍል ተፈታኝ እናቶች እንዚህ እናቶች የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ለመፈተን ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ የተገኙ ተማሪዎች ናቸው፡፡ የእናትነት ኃላፊነትን እየተወጡ በተመሳሳይ ጊዜ የትምህርት ህልማቸውን ለማሳካት ያሳዩት ጥንካሬና ትጋት ከፍተኛ አድናቆት የሚቸረው ነው። 👏👏 @tikvahuniversity

85ኛ፣ እና 86ኛ ዙር የግራፊክ ዲዛይን፣ ቪዲዮ ኤዲቲንግ እና ሞሽን ግራፊክ ስልጠና ምዝገባ ላይ ነን። 👉 ተግባርን ከንድፈ ሀሳብ ያስተሳሰረ ስልጠና 👉 Advanced Graphic + Video E
85ኛ፣ እና 86ኛ ዙር የግራፊክ ዲዛይን፣ ቪዲዮ ኤዲቲንግ እና  ሞሽን ግራፊክ ስልጠና ምዝገባ ላይ ነን። 👉 ተግባርን ከንድፈ ሀሳብ ያስተሳሰረ ስልጠና 👉 Advanced Graphic + Video Editing + Motion Graphic በአንድ ላይ 👉 ከ50 በላይ ፕሮጀክቶች ያሉት ስልጠናው ሰኔ 29/2018 ዓ.ም ይጀምራል። የበለጠ ይጠብቁ ... 💥 ሴጅ ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት 💥 ☎️  0906777799 / 0906777755 አድራሻ፦ ቁ.1: ፒያሣ ቸርችል ጎዳና ኤልያና ሆቴል 2ኛ ፎቅ፣ ቁ.2: መገናኛ ታሜጋስ ህንፃ 2ኛ ፎቅ እና ቁ.3: አዳማ ራስ ሆቴል 2ኛ ፎቅ ለመመዝገብ ድረ-ገጽ 👇 www.sageethiopia.com Telegram: https://t.me/sagetraininginstitute Tiktok: https://www.tiktok.com/@sage_training_institute

#AAEB የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የ2019 ትምህርት ዘመን ዓመታዊ የጊዜ ሰሌዳ ለሁሉም ክ/ከተሞች ትምህርት ጽ/ቤቶች እና በከተማ አስተዳደር ስር ለሚገኙ ሦስት አዳሪ ትምህርት
+5
#AAEB የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የ2019 ትምህርት ዘመን ዓመታዊ የጊዜ ሰሌዳ ለሁሉም ክ/ከተሞች ትምህርት ጽ/ቤቶች እና በከተማ አስተዳደር ስር ለሚገኙ ሦስት አዳሪ ትምህርት ቤቶች ልኳል። በዚህም፦ ከሐምሌ 19 እስከ ነሐሴ 22/2018 ዓ.ም የነባር እና አዲስ ተማሪዎች ምዝገባ ይከናወናል። ከነሐሴ 26 እስከ ጳጉሜን 5/2018 ዓ.ም የአዲስ ገቢ የ7ኛ እና የ9ኛ ክፍል ተማሪዎች ምዝገባ ይከናወናል። መስከረም 05/2019 ዓ.ም የመጀመሪያ ቀን የመጀመሪያ መደበኛ ትምህርት ክፍለ ጊዜ ይጀመራል። (የከተማ አስተዳደሩ ትምህርት ቢሮ ለሁሉም ክ/ከተሞች ትምህርት ጽ/ቤቶች እና በከተማ አስተዳደር ስር ለሚገኙ ሦስት አዳሪ ት/ቤቶች የላከው ሙሉ የ2019 ዓ.ም የትምህርት ካሌንደር ከላይ ተያይዟል።) @tikvahuniversity

🔔 እስከ ሰኔ 30/2018 ዓ.ም በሁሉም ስልጠናዎቻችን ላይ የ 40% ቅናሽ አድርገናል! በሦስቱም ቅርንጫፎቻችን (መገናኛ፣ ሜክሲኮ እና ጀሞ) እንዲሁም በኦንላይን በምንሰጣቸው ስልጠናዎች በ Adva
🔔 እስከ ሰኔ 30/2018 ዓ.ም በሁሉም ስልጠናዎቻችን ላይ የ 40% ቅናሽ አድርገናል! በሦስቱም ቅርንጫፎቻችን (መገናኛ፣ ሜክሲኮ እና ጀሞ) እንዲሁም በኦንላይን በምንሰጣቸው ስልጠናዎች በ Advanced Level እና 90% Practical በሆነ ካሪኩለም፣ ዘመኑ ያፈራቸውን የላብራቶሪና የስቱዲዮ እቃዎችን በማሟላት በሁሉም ስልጠናዎቻችን ላይ ታላቅ የዋጋ ቅናሽ አድርገናል! አሁኑኑ ይመዝገቡና ትልቅ ለውጥ ወደሚያመጡበት ተቋም ይቀላቀሉ! ከትምህርትና ስልጠና ጥራትና ቁጥጥር ባለስልጣን ሙሉ ዕውቅና ካለው ሰርተፊኬት ጋር! የብዙ ዓመት ልምድ እና ብቃት ባላቸው አሰልጣኞች! 🎯 Graphics Design 🎯 Video Editing 🎯 Digital Marketing 🎯 Photography 🎯 Videography 🎯 Cinematography 🎯 Basic Computer 🎯 English Language 🎯 Fullstack Web App Development  🎯 Programming Language 🎯 Interior Design 🎯 English Language 🎯 Accounting Softwares 🎯 Engineering Softwares 🎯 SPSS & STATA 🎯 MS-Project 🎯  Foreign & Local Languages አድራሻ 1ኛ. መገናኛ መተባበር ህንፃ 2ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 114 ☎️ 0991929303 2ኛ. ሜክሲኮ ኬኬር ህንፃ 3ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 319 ☎️ 0991929304 3ኛ. ጀሞ 1 አንደኛ በር ካኩ ቢዝነስ ሴንተር 3ኛ ፎቅ ☎️ 0991926707 Telegram 👇 https://t.me/topinstitutes

#SamaraUniversity ሠመራ ዩኒቨርሲቲ 'የአፋር ጥናት ኢንስቲትዩት' / Institute of Afar Studies ሊያቋቁም ነው። የሚቋቋመው ኢንስቲትዩት በአሊ አሪፍ ቡርሃን ስም የሚሰየም መሆ
#SamaraUniversity ሠመራ ዩኒቨርሲቲ 'የአፋር ጥናት ኢንስቲትዩት' / Institute of Afar Studies ሊያቋቁም ነው። የሚቋቋመው ኢንስቲትዩት በአሊ አሪፍ ቡርሃን ስም የሚሰየም መሆኑንም የዩኒቨርሲቲው ሴኔት ወስኗል። በሌላ በኩል የዩኒቨርሲቲው ሴኔት በፓሊዎአንትሮፖሎጂ የትምህርት መስክ የሁለተኛ ዲግሪ ፕሮግራም (MA in Paleoanthropology) እንዲከፈቱ አፅድቋል፡፡ @tikvahuniversity

#MekelleUniversity መቐለ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያስተማራቸውን ከ2900 በላይ ተማሪዎች በዛሬው ዕለት አስመርቋል። ተመራቂዎቹ ከመጀመሪያ ዲግሪ እስከ ሦስተኛ ዲግሪ (PhD
+2
#MekelleUniversity መቐለ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያስተማራቸውን ከ2900 በላይ ተማሪዎች በዛሬው ዕለት አስመርቋል። ተመራቂዎቹ ከመጀመሪያ ዲግሪ እስከ ሦስተኛ ዲግሪ (PhD) ትምህርታቸውን ተከታትለው ያጠናቀቁ ናቸው። የመቐለ ዩኒቨርሲቲ 33ኛ ዙር ተመራቂዎች፦ 45 ➫ በሦስተኛ ዲግሪ (PhD) 939 ➫ በሁለተኛ ዲግሪ 83 ➫ በስፔሻሊቲ 1864 ➫ በመጀመሪያ ዲግሪ ከተመራቂዎቹ መካከል 45 የውጭ አገራት ተማሪዎች ይገኛሉ። @tikvahuniversity

#EthiopianDefenseUniversity የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያሰለጠናቸውን 371 ተማሪዎች አስመርቋል። ተመራቂዎቹ በዩኒቨርሲቲው ሦስት ኮሌጆች ከመጀመሪያ
+2
#EthiopianDefenseUniversity የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያሰለጠናቸውን 371 ተማሪዎች አስመርቋል። ተመራቂዎቹ በዩኒቨርሲቲው ሦስት ኮሌጆች ከመጀመሪያ እስከ ሦስተኛ ዲግሪ ፕሮግራሞች ትምህርታቸውን ተከታትለው ያጠናቀቁ ናቸው። በኢንጅነሪንግ፣ በጤና ሳይንስ እንዲሁም በቢዝነስና ማኅበራዊ ጥናት ዘርፎች ከተመረቁት የሀገር ውስጥ ተማሪዎች በተጨማሪ ከውጭ አገራት የመጡ ሰልጣኝ ተማሪዎች እንደሚገኙም ተገልጿል። @tikvahuniversity

ስራ በዝቶብዎታል፣ ስብሰባ ላይ ነዎት ወይስ ትንሽ እረፍት መውሰድ ፈልገዋል? እንግዲያውስ ለሚደውልልዎ ሰው ሁሉ በራሱ ጊዜ አሁን ምን ላይ እንዳሉ መልዕክት ያስቀምጡና ያለምንም ረብሻ ስራዎን ያከናው
ስራ በዝቶብዎታል፣ ስብሰባ ላይ ነዎት ወይስ ትንሽ እረፍት መውሰድ ፈልገዋል? እንግዲያውስ ለሚደውልልዎ ሰው ሁሉ በራሱ ጊዜ አሁን ምን ላይ እንዳሉ መልዕክት ያስቀምጡና ያለምንም ረብሻ ስራዎን ያከናውኑ! ለግል መልዕክት ወደ *723*2# እንዲሁም ለቢዝነስ መልዕክት ደግሞ ወደ *723*3# እንደውል! #CallSignature #Safaricom

11ኛ እና 12ኛ ዙር Software Development, Programming and Database ስልጠና ምዝገባ ላይ ነን። 👉 በተግባር ሶፍትዌር እያበለፀጉ የሚሰለጥኑበት በስልጠናው የተካተቱ 👉
11ኛ እና 12ኛ ዙር Software Development, Programming and Database ስልጠና ምዝገባ ላይ ነን። 👉 በተግባር ሶፍትዌር እያበለፀጉ የሚሰለጥኑበት በስልጠናው የተካተቱ 👉 Foundation of Programming Using C++ 👉 Java & Frontend Development using JavaFX 👉 Python & Backend Development using Django 👉 Database Systems, Architecture & Modeling 👉 PostgreSQL ስልጠናው ሰኔ 29/2018 ዓ.ም ይጀምራል። የበለጠ ይጠብቁ ... 💥 ሴጅ ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት 💥 ☎️  0906777799 / 0906777755 አድራሻ፦ ቁ.1: ፒያሣ ቸርችል ጎዳና ኤልያና ሆቴል 2ኛ ፎቅ፣ ቁ.2: መገናኛ ታሜጋስ ህንፃ 2ኛ ፎቅ እና ቁ.3: አዳማ ራስ ሆቴል 2ኛ ፎቅ ለመመዝገብ ድረ-ገጽ 👇 www.sageethiopia.com Telegram: https://t.me/sagetraininginstitute Tiktok: https://www.tiktok.com/@sage_training_institute