en
Feedback
MINSTERY OF EDUCATION ©

MINSTERY OF EDUCATION ©

Open in Telegram

For more information! It’s all about education Official minstry of education telegram channel join and get more info About us ✅የተረጋገጠ የትምህርት ደረጃ ለማግኘት እኛን ይከተሉ!! https://www.youtube.com/@minster_of_education Ad:https://telega.io/c/minsterofeducation

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel MINSTERY OF EDUCATION ©

Channel MINSTERY OF EDUCATION © (@minster_of_education) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 43 031 subscribers, ranking 4 259 in the Education category and 752 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 43 031 subscribers.

According to the latest data from 17 June, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 76 over the last 30 days and by 4 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 10.54%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 4.72% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 4 536 views. Within the first day, a publication typically gains 2 030 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 7.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
For more information! It’s all about education Official minstry of education telegram channel join and get more info About us ✅የተረጋገጠ የትምህርት ደረጃ ለማግኘት እኛን ይከተሉ!! https://www.youtube.com/@minster_of_education Ad:https://telega.io/c/minsterofeduca...

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 18 June, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Education category.

43 031
Subscribers
+424 hours
+957 days
+7630 days
Posts Archive
#ቅሬታ ትናንት ሰኔ 10/2018 ዓ.ም በተሰጠው የፋርማሲ ትምህርት የመውጫ ፈተና ላይ ስርቆት ተፈፅሟል ሲሉ በርካታ ተፈታኝ ተማሪዎች ቅሬታቸውን እያቀረቡ ነው፡፡ "የፋርማሲ ትምህርት የመውጫ ፈተና
#ቅሬታ ትናንት ሰኔ 10/2018 ዓ.ም በተሰጠው የፋርማሲ ትምህርት የመውጫ ፈተና ላይ ስርቆት ተፈፅሟል ሲሉ በርካታ ተፈታኝ ተማሪዎች ቅሬታቸውን እያቀረቡ ነው፡፡ "የፋርማሲ ትምህርት የመውጫ ፈተና አስቀድሞ ተሰርቋል" ያሉት ቅሬታ አቅራቢ ተማሪዎቹ፤ የሚመለከተው የመንግሥት አካል ማብራሪያ እንዲሰጥም ጠይቀዋል። ለፈተናው ዝግጅት ሲያደርጉ ቢቆዩም፣ ኃላፊነት በማይሰማቸው አካላት አማካኝነት ፈተናው ቀድሞ ወጥቶ መሰራጨቱን የሚያሳዩ መረጃዎች እንደደረሷቸው ቅሬታ አቅራቢ ተማሪዎቹ ገልፀዋል። ይህ መሆኑም በከፍተኛ ጥረትና በራሳቸው ልፋት የተፈተኑ ተማሪዎችን ስነ-ልቦና በእጅጉ የጎዳና ፍትሃዊነትን የጎደለው ተግባር መሆኑን ጠቁመዋል። ጉዳዩ በትምህርት ሚኒስቴር፣ በትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት እንዲሁም በኢትዮጵያ ፋርማሲስቶች ማኅበር በኩል በአስቸኳይ ታይቶ፣ አስፈላጊው ማጣሪያ እንዲደረግና ተገቢው ምላሽ እንዲሰጣቸው ተፈታኞቹ ጠይቀዋል። ቲክቫህ ዩኒቨርሲቲ ከተፈታኝ ተማሪዎች የቀረበውን ይህንን ቅሬታ መነሻ በማድረግ፣ በጉዳዩ ላይ ከሚመለከታቸው የመንግሥት ሥራ ኃላፊዎች ማብራሪያ ለማግኘት ያደረገው ሙከራ አልተሳካም። ተጨማሪ ማብራሪያ እንዳገኘን የምናደርሳችሁ ይሆናል። ምስል፦ ተፈታኝ ተማሪዎች ወጥቷበማለት ያጋሩን የመልስ ማውጫ

የ2018 ትምህርት ዘመን የ8ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ የመልቀቂያ ፈተና መሰጠት ጀምሯል፡፡ ፈተናው በሁሉም ክልሎች፣ በድሬዳዋ አስተዳደር እና በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሰኔ 11 እና 12/2018 ዓ
+2
የ2018 ትምህርት ዘመን የ8ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ የመልቀቂያ ፈተና መሰጠት ጀምሯል፡፡ ፈተናው በሁሉም ክልሎች፣ በድሬዳዋ አስተዳደር እና በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሰኔ 11 እና 12/2018 ዓ.ም ይሰጣል፡፡ በአዲስ አበባ ከተማ ፈተናው በ201 የፈተና ጣቢያዎች በዛሬው ዕለት መሰጠት የተጀመረ ሲሆን፤ በከተማ አስተዳደሩ 86,783 የ8ኛ ክፍል ተማሪዎች ፈተናውን ለመውሰድ ተመዝግበዋል፡፡ ምስል፦ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እና የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ትምህርት ቢሮዎች

ከሰኔ 08/2018 ዓ.ም ጀምሮ ለሦስት ተከታታይ ቀናት የተሰጠው የ2018 ትምህርት ዘመን የ6ኛ ክፍል ክልል እና ከተማ አቀፍ ፈተና ተጠናቋል። ፈተናው በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በ199 የፈተና
ከሰኔ 08/2018 ዓ.ም ጀምሮ ለሦስት ተከታታይ ቀናት የተሰጠው የ2018 ትምህርት ዘመን የ6ኛ ክፍል ክልል እና ከተማ አቀፍ ፈተና ተጠናቋል። ፈተናው በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በ199 የፈተና ጣቢያዎች ለ85 ተማሪዎች ተሰጥቷል። በመዲናዋ በተሰጠው ፈተና፤ 199 የፈተና ጣቢያ ኃላፊዎች፣ 767 አስፈታኝ ትምህርት ቤቶች፣ 782 ሱፐርቫይዘሮች እና 2414 ፈታኞች መሳተፋቸው ተገልጿል። ምስል፦ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ

💥 የክረምት ስልጠና (ከ40% እስከ 60% ቅናሽ እስከ ሰኔ 21/2018 ዓ.ም ለምትመዘገቡ) 💥 የተለያዩ የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ እና የቴክኒካል ሙያዎች ስልጠና ምዝገባ ላይ ነን! ስልጠናው ሰኔ
💥 የክረምት ስልጠና (ከ40% እስከ 60% ቅናሽ እስከ ሰኔ 21/2018 ዓ.ም ለምትመዘገቡ) 💥 የተለያዩ የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ እና የቴክኒካል ሙያዎች ስልጠና ምዝገባ ላይ ነን! ስልጠናው ሰኔ 29/2018 ዓ.ም ይጀምራል። የበለጠ ይጠብቁ ... 💥 ሴጅ ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት 💥 ☎️  0906777799 / 0906777755 አድራሻ፦ ቁ.1: ፒያሣ ቸርችል ጎዳና ኤልያና ሆቴል 2ኛ ፎቅ ቁ.2: መገናኛ ታሜጋስ ህንፃ 2ኛ ፎቅ ቁ.3: አዳማ ራስ ሆቴል 2ኛ ፎቅ ለመመዝገብ ድረ-ገጽ 👇 www.sageethiopia.com Telegram: https://t.me/sagetraininginstitute TikTok: https://www.tiktok.com/@sage_training_institute LinkedIn: https://www.linkedin.com/company/sage-training-institute

እነሆ ለቴሌግራም ቻናልዎ የሚሆን አጭር እና ማራኪ የማስታወቂያ ጥሪ ፅሁፍ፡ 📢 ማስታወቂያ ለምትፈልጉ ሁሉ! በቻናላችን @minster_of_education ላይ ምርትዎን፣ አገልግሎትዎን ወይም ድርጅትዎን በብዙ ሺህ ለሚቆጠሩ ተከታታዮቻችን ማስተዋወቅ ይፈልጋሉ? ✅ተደራሽነታችን፡ ንቁ እና እያደገ የመጣ ማህበረሰብ ✅ ዋጋችን፡ በጣም ተመጣጣኝ እና ኪስ የማይጎዳ ለማስታወቂያ ስራ እና ለተጨማሪ መረጃ በውስጥ መስመር ያናግሩን፡ 👉 @Minofedu ጥራት ያለው ማስታወቂያ ለተሻለ ውጤት!

ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ በኢኮኖሚክስ መስክ የሦስተኛ ዲግሪ (PhD) ትምህርት መስጠት ሊጀምር ነው፡፡ ዩኒቨርሲቲው በኢኮኖሚክስ የትምህርት መስክ አዲስ የዶክትሬት መርሐግብር ለመጀመር የስርዓተ-ትምህርት ግ
ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ በኢኮኖሚክስ መስክ የሦስተኛ ዲግሪ (PhD) ትምህርት መስጠት ሊጀምር ነው፡፡ ዩኒቨርሲቲው በኢኮኖሚክስ የትምህርት መስክ አዲስ የዶክትሬት መርሐግብር ለመጀመር የስርዓተ-ትምህርት ግምገማ አካሒዷል። በግምገማ መድረኩ ላይ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ፣ ከኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ፣ ከኢትዮጵያ ካፒታል ማርኬት ባለስልጣን እና ከፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት የተወከሉ ባለሙያዎች በአካል እና በዌቢናር ተሳትፈዋል። በምስራቅ የሀገሪቱ ክፍል በኢኮኖሚክስ የትምህርት መስክ በዶክትሬት ደረጃ ትምህርት የሚሰጥ ተቋም ባለመኖሩ ፕሮግራሙን በአካባቢው የመጀመሪያ ያደርገዋል ተብሏል። ግምገማውን ተከትሎ የፀደቀው ስርዓተ-ትምህርት፣ የልማት ኢኮኖሚክስ፣ ዓለም አቀፍ ኢኮኖሚክስና ንግድ እንዲሁም የፋይናንስ ኢኮኖሚክስ መስኮችን በዶክትሬት ዲግሪ ለማስተማር የተዘጋጁ መሆኑ ተገልጿል።

በ Lomi Study ፈተናዎች 10 ሺህ ብር ያሸንፉ! ብቃትን የሚመዝኑ ፈተናዎችን በመውሰድ እውቀታችሁን አሳድጉ፤ ሳምንታዊ ተሸላሚ ሁኑ! ዛሬውኑ ይቀላቀሉ! በ Lomi Study ምን ያገኛሉ? ● የፈ
በ Lomi Study ፈተናዎች 10 ሺህ ብር ያሸንፉ! ብቃትን የሚመዝኑ ፈተናዎችን በመውሰድ እውቀታችሁን አሳድጉ፤ ሳምንታዊ ተሸላሚ ሁኑ! ዛሬውኑ ይቀላቀሉ! በ Lomi Study ምን ያገኛሉ? ● የፈተና ልምምድ ● ከተለያዩ ትምህርት ቤቶች ጋር ውድድር ● ሳምንታዊ ፈተናዎች ላይ በመሳተፍ የ 10,000 ብር  ልዩ ሽልማት   Website: https://lomistudy.com/r/lomi28       Telegram Bot: https://t.me/Lomistudybot?start=lomi28

የቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሌኒየም ሕክምና ኮሌጅ የሥራ አመራር ቦርድ ለሁለት የተቋሙ መምህራን፣ ተመራማሪዎች እና የሕክምና ባለሙያዎች የሙሉ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ ሰጥቷል። ቦርዱ የሁለቱን ባለሙያዎች
+3
የቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሌኒየም ሕክምና ኮሌጅ የሥራ አመራር ቦርድ ለሁለት የተቋሙ መምህራን፣ ተመራማሪዎች እና የሕክምና ባለሙያዎች የሙሉ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ ሰጥቷል።   ቦርዱ የሁለቱን ባለሙያዎች የአካዳሚክ፣ የምርምር፣ የሕክምና አገልግሎት እና ተቋማዊ አበርክቶ ከገመገመ በኋላ የሙሉ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ አፅድቋል፡፡ በዚህም ዶ/ር ሰለሞን አሊ እና ዶ/ር በረከት ፋንታሁን የሙሉ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ እድገት አጊኝተዋል፡፡ ዶ/ር ሰለሞን አሊ ማይክሮባዮሎጅስትና የሕክምና ምርምር ስፔሻሊስት ሲሆኑ፤ ከ20 ዓመታት በላይ በቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሌኒየም ሕክምና ኮሌጅ እና በጅማ ዩኒቨርሲቲ በመምህርነት፣ በምርምር እና በሕክምና አገልግሎት እያገለገሉ የሚገኙ ባለሙያ ናቸው። በተመሳሳይ ዶ/ር በረከት ፋንታሁን በኮሌጁ ታሪክ የመጀመሪያዋ ሴት ፕሮፌሰር ሲሆኑ፤ በሙያቸው የህጻናት ሕክምና ስፔሻሊስት ናቸው፡፡ በሕጻናት ኢንዶክራይኖሎጂ ሕክምና ደግሞ የሰብ ስፔሻሊስት ስልጠና አላቸው፡፡ በሕክምና ትምህርት፣ በምርምር እና በጤና ሥርዓት ማጠናከር ላይ ከፍተኛ አስተዋፅኦ አበርክቶ ያላቸውና በአሁኑ ጊዜ በኮሌጅ በማገልገል ላይ የሚገኙ መሆኑ ከኮሌጁ የተገኘ መረጃ ያሳያል፡፡  

የመውጫ ፈተና እየወሰዱ የሚገኙ እናቶች በዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ እጩ ተመራቂ የሆኑ ሴት ተማሪዎች ልጆቻቸውን ከወለዱ ከተወሰኑ ቀናት በኋላ ሀገር አቀፍ የመውጫ ፈተና (Exit Exam) በመውሰድ ላይ ይ
+3
የመውጫ ፈተና እየወሰዱ የሚገኙ እናቶች   በዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ እጩ ተመራቂ የሆኑ ሴት ተማሪዎች ልጆቻቸውን ከወለዱ ከተወሰኑ ቀናት በኋላ ሀገር አቀፍ የመውጫ ፈተና (Exit Exam) በመውሰድ ላይ ይገኛሉ። እነዚህ ተማሪዎች የእናትነትን ኃላፊነት ከትምህርታዊ ግዴታቸው ጋር በማስታረቅ የመውጫ ፈተና በብርታት እየወሰዱ ይገኛሉ።   በተመሳሳይ ልጇን አዝላ የመውጫ ፈተና በመውሰድ ላይ የምትገኝ ብርቱ እናት በአክሱም ዩኒቨርሲቲ ተመልክትናል፡፡   የፅናት ምሳሌ ለሆኑ ለእነዚህ ተፈታኝ እናቶች መልካም ዕድል እንመኛለን።  

#ጥቆማ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ለ2019 የትምህርት ዘመን የመጀመሪያ ሴሚስተር የድኅረ-ምረቃ ፕሮግራሞች አመልካቾችን መቀበል ጀምሯል፡፡ ዩኒቨርሲቲው ለ Masters ፕሮግራም በመደበኛ እና በኤክስቴን
#ጥቆማ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ለ2019 የትምህርት ዘመን የመጀመሪያ ሴሚስተር የድኅረ-ምረቃ ፕሮግራሞች አመልካቾችን መቀበል ጀምሯል፡፡   ዩኒቨርሲቲው ለ Masters ፕሮግራም በመደበኛ እና በኤክስቴንሽን መርሐግብሮች እንዲሁም ለ PhD ፕሮግራም በመደበኛ እና በኤክስቴንሽን መርሐግብሮች አመልካቾችን ይቀበላል፡፡ የድኅረ-ምረቃ ፕሮግራሞቹን ዝርዝር በ https://admission.aau.edu.et/GraduatePrograms መመልከት ይችላሉ፡፡ አመልካቾች በቅድሚያ በዩኒቨርሲቲው የሚሰጠውን የድኅረ-ምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (GAT) መውሰድና ማለፍ ይጠበቅባቸዋል፡፡ የ GAT ማመልከቻ ጊዜ የሚያበቃው 👇 ነሐሴ 05/2018 ዓ.ም

የ4ኛ ቀን የቅድመ-ምረቃ ትምህርት የመውጫ ፈተናዎች እየተሰጡ ነው፡፡ በዛሬው ውሎ የ24 ትምህርት አይነት ፈተናዎች ይሰጣሉ፡፡ የመውጫ ፈተና የ4ኛ ቀን መርሐግብር (ሰኔ 09/2018 ዓ.ም) ✅ ፈረቃ
የ4ኛ ቀን የቅድመ-ምረቃ ትምህርት የመውጫ ፈተናዎች እየተሰጡ ነው፡፡ በዛሬው ውሎ የ24 ትምህርት አይነት ፈተናዎች ይሰጣሉ፡፡   የመውጫ ፈተና የ4ኛ ቀን መርሐግብር (ሰኔ 09/2018 ዓ.ም) ✅ ፈረቃ 1: ጠዋት ከ2:00-4:30 ሰዓት ✅ ፈረቃ 2: ጠዋት ከ5፡00-7:30 ሰዓት ✅ ፈረቃ 3: ከሰዓት ከ08:30-11:00 ሰዓት   የመውጫ ፈተና እስከ ሰኔ 12/2018 ዓ.ም በኦንላይን ይሰጣል፡፡ ምስል፦ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ

#ጥቆማ በ2018 ዓ.ም ሀገር አቀፍ የሬዚደንሲ ፈተና ወስዳችሁ ያለፋችሁና በተለያዩ ተቋማት የተመደባችሁ፤ ነገር ግን በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ በጤና ሳይንስና ህክምና ኮሌጅ School of Medicine,
#ጥቆማ   በ2018 ዓ.ም ሀገር አቀፍ የሬዚደንሲ ፈተና ወስዳችሁ ያለፋችሁና በተለያዩ ተቋማት የተመደባችሁ፤ ነገር ግን በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ በጤና ሳይንስና ህክምና ኮሌጅ School of Medicine, General Surgery ትምህርት ዘርፍ ለመማር የምትፈልጉ ሐኪሞች እንድታመለክቱ ዩኒቨርሲቲው ጋብዟል፡፡   የምዝገባ ጊዜ፦ ከሰኔ 08-12/2018 ዓ.ም   የማመልከቻ አማራጮች፦ ● Email: registrar@wku.edu.et ● በአካል በዩኒቨርሲቲው ዋና ሬጅስትራር ጽ/ቤት   ለተጨማሪ መረጃ፦ 0920204770  

💥 የክረምት ስልጠና (ከ40% እስከ 60% ቅናሽ እስከ ሰኔ 21/2018 ዓ.ም ለምትመዘገቡ) 💥 የጋዜጠኝነት ስልጠና ምዝገባ ላይ ነን! በስልጠናው የተካተቱ፦ 👉 መሠረታዊ የጋዜጠኝነት መርሆች፣
💥 የክረምት ስልጠና (ከ40% እስከ 60% ቅናሽ እስከ ሰኔ 21/2018 ዓ.ም ለምትመዘገቡ) 💥 የጋዜጠኝነት ስልጠና ምዝገባ ላይ ነን! በስልጠናው የተካተቱ፦ 👉 መሠረታዊ የጋዜጠኝነት መርሆች፣ የሚዲያ እና የጋዜጠኝነት ዓይነቶች  👉 የዜና አሰራር እና የቃለመጠይቅ አደራረግ 👉 የመዝናኛ ፕሮግራም ጋዜጠኝነት፣ የፕሮግራም ዝግጅት፣ የማስታወቂያ አሰራር እና ዶክመንተሪ ዝግጅት 👉 የሞባይል እና የዩቲዩብ ጋዜጠኝነት ስልጠናው ሰኔ 29/2018 ዓ.ም ይጀምራል! የበለጠ ይጠብቁ ... 💥 ሴጅ ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት 💥 ☎️  0906777799 / 0906777755 አድራሻ፦ ቁ.1: ፒያሣ ቸርችል ጎዳና ኤልያና ሆቴል 2ኛ ፎቅ ቁ.2: መገናኛ ታሜጋስ ህንፃ 2ኛ ፎቅ ቁ.3: አዳማ ለመመዝገብ ድረ-ገጽ 👇 www.sageethiopia.com Telegram: https://t.me/sagetraininginstitute TikTok: https://www.tiktok.com/@sage_training_institute LinkedIn: https://www.linkedin.com/company/sage-training-institute

#HawassaUniversity ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ለዘጠኝ የተቋሙ መምህራን የሙሉ ፕሮፌሰርነት የደረጃ እድገት ሰጠ። የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሥራ አመራር ቦርድ የዘጠኙ መምህራንን የሙሉ ፕሮፌሰርነት የደረጃ
#HawassaUniversity ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ለዘጠኝ የተቋሙ መምህራን የሙሉ ፕሮፌሰርነት የደረጃ እድገት ሰጠ። የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሥራ አመራር ቦርድ የዘጠኙ መምህራንን የሙሉ ፕሮፌሰርነት የደረጃ እድገት አፅድቋል። የሙሉ ፕሮፌሰርነት የደረጃ እድገት ያገኙ፦ 1. ዶ/ር አቻምየለሽ ገብረፃዲቅ ተክሌ - በ Public Health 2. ዶ/ር አለማየሁ ሙሉነህ ቢተው - በ Climate Change and Environmental Science 3. ዶ/ር አውደነገስት ሞገስ ባንጃው - በ Soil and Water Conservation 4. ዶ/ር ምህረት ዳናንቶ ዑልሲዶ - በ Water Supply and Environmental Engineering 5. ዶ/ር ሙሉጌታ ዳዲ በለጠ - በ Hydrology 6. ዶ/ር አንዳርጋቸው ገዴቦ አቢተአ - በ Plant Breeding 7. ዶ/ር ዘሪሁነ ግርማ ወ/ገብርኤል - በ Wildlife Ecology and Management 8. ዶ/ር ሁሴን ሞሐመድ በሽር- በ Horticultural Sciences 9. ዶ/ር ታረቀኝ ዮሴፍ ሳማጎ- በ Agronomy https://t.me/minster_of_education

#ጥቆማ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሰብዓዊ መብቶች ማዕከል በ 2019 ዓ.ም በ Human Rights የትምህርት መስክ የ2ኛ ዲግሪ እና የ3ኛ ዲግሪ (PhD) ፕሮግራሞች ለመማር ያመለክቱ! ፍላጎት ያላ
#ጥቆማ   በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሰብዓዊ መብቶች ማዕከል በ 2019 ዓ.ም በ Human Rights የትምህርት መስክ የ2ኛ ዲግሪ እና የ3ኛ ዲግሪ (PhD) ፕሮግራሞች ለመማር ያመለክቱ!   ፍላጎት ያላቸውና ብቁ የሆኑ አመልካቾች እንዲያመለክቱ ማዕከሉ ጥሪ አድርጓል፡፡   ለዝርዝር መረጃ፣ መስፈርቶችን ለማየት እና የማመልከቻ መመሪያ ለማግኘት 👇 https://www.aau.edu.et/announcements/detail?title=Call~for~applications~for~admission~to~graduate~programs~for~the~First~Semester~of~2026/27~(2019~E.C.)~Academic~Year   አመልካቾች በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሚሰጠውን የድኅረ-ምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (GAT) ወስደው ማለፍ ይጠበቅባቸዋል፡፡   https://t.me/minster_of_education

የ2018 ትምህርት ዘመን የ6ኛ ክፍል ክልል/ከተማ አቀፍ ፈተና በተለያዩ ክልሎች እና በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር መሰጠት ጀምሯል። ፈተናው ከዛሬ ሰኔ 08/2018 ዓ.ም ጀምሮ ለሦስት ተከታታይ ቀ
+3
የ2018 ትምህርት ዘመን የ6ኛ ክፍል ክልል/ከተማ አቀፍ ፈተና በተለያዩ ክልሎች እና በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር መሰጠት ጀምሯል።   ፈተናው ከዛሬ ሰኔ 08/2018 ዓ.ም ጀምሮ ለሦስት ተከታታይ ቀናት ይሰጣል፡፡   https://t.me/minster_of_education

በኢንተርኔት የታገዘ የመስኖ መቆጣጠሪያ ሲስተም (IoT Smart Irrigation System) የሠሩ ወጣቶች የቴክኒክና ሙያ ሥልጠና ኢንስቲትዩት የመጀመሪያው የቴክኖሎጂ ውድድር አሸናፊዎች ሆነዋል፡፡
+3
በኢንተርኔት የታገዘ የመስኖ መቆጣጠሪያ ሲስተም (IoT Smart Irrigation System) የሠሩ ወጣቶች የቴክኒክና ሙያ ሥልጠና ኢንስቲትዩት የመጀመሪያው የቴክኖሎጂ ውድድር አሸናፊዎች ሆነዋል፡፡   ኢንስቲትዩቱ ያዘጋጀው የመጀመሪያው ዓለም አቀፍ የቴክኒክና ሙያ ምርምር ኮንፈረንስና የቴክኖሎጂ ውድድር ተጠናቋል።   በቴክኖሎጂ ውድድሩ ከ10 ሀገራት የተውጣጡ 35 ፈጠራዎች ለውድድር የቀረቡ ሲሆን፤ ኢትዮጵያውያን ወጣቶች አንደኛ እና ሁለተኛ ደረጃን ሲይዙ፣ ናይጄሪያዊው ወጣት የፈጠራ ባለሙያ ሦስተኛ ደረጃን በማግኘት የነሐስ ሜዳሊያ ተሸላሚ ሆኗል።   የቴክኖሎጂ ውድድሩ አሸናፊዎች የሆኑት IoT Smart Irrigation System አንደኛ፣ የCerebro Logic ሁለተኛ እንዲሁም የናይጄሪያው Eco-Bin Revenue Intelligence and Traceability System ሦስተኛ ደረጃን አግኝተዋል።   የመስኖ መቆጣጠሪያ ሲስተም ቴክኖሎጂው እስከ 10ኪሜ ርቀት ላይ ያሉ የመስኖ እርሻዎችን ለመከታተልና አስፈጊውን ግባዓት ለማቅረብ የሚረዳ ነው።   https://t.me/minster_of_education

ሴጅ ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት ቁጥር ሦስት በአዳማ ራስ ሆቴል 2ኛ ፎቅ ላይ ትናንት ሰኔ 07/2018 ዓ.ም ተመርቋል። የበለጠ ይጠብቁ ... 💥 ሴጅ ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት 💥 ☎️ 0906777799 /
+3
ሴጅ ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት ቁጥር ሦስት በአዳማ ራስ ሆቴል 2ኛ ፎቅ ላይ ትናንት ሰኔ 07/2018 ዓ.ም ተመርቋል። የበለጠ ይጠብቁ ... 💥 ሴጅ ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት 💥 ☎️  0906777799 / 0906777755 አድራሻ፦ ቁ.1: ፒያሣ ቸርችል ጎዳና ኤልያና ሆቴል 2ኛ ፎቅ ቁ.2: መገናኛ ታሜጋስ ህንፃ 2ኛ ፎቅ ቁ.3: አዳማ ራስ ሆቴል 2ኛ ፎቅ ለመመዝገብ ድረ-ገጽ 👇 www.sageethiopia.com Telegram: https://t.me/sagetraininginstitute TikTok: https://www.tiktok.com/@sage_training_institute LinkedIn: https://www.linkedin.com/company/sage-training-institute

#ጥቆማ ነጻ የክረምት ስልጠና ይከታተሉ! የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ከ1ኛ-12ኛ ክፍል ለሆነ ተማሪዎች የክረምት ስልጠና አዘጋጅቷል። የክረምት ስልጠና መስኮች፦ ● ፋንዳሜንታልስ
#ጥቆማ ነጻ የክረምት ስልጠና ይከታተሉ! የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ከ1ኛ-12ኛ ክፍል ለሆነ ተማሪዎች የክረምት ስልጠና አዘጋጅቷል። የክረምት ስልጠና መስኮች፦ ● ፋንዳሜንታልስ ኦፍ ኤ.አይ. ● ፕሮግራሚንግ ● ማሽን ለርኒንግ ● ሮቦቲክስ እና IOT ● ዳታ ሳይንስ የምዝገባ ጊዜ የሚያበቃው 👇 ሰኔ 30/2018 ዓ.ም በተከታዩ የጉግል ፎርም ይመዝገቡ 👇 https://forms.gle/uDGPmQsiZcWWeNuRA

#HawassaUniversity ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ በ2.8 ቢሊዮን ብር ወጪ የተሠሩ ፕሮጀክቶችን አስመርቋል። ዩኒቨርሲቲው በህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የኮምፕሪሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ማስፋፊያ ፕ
+8
#HawassaUniversity ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ በ2.8 ቢሊዮን ብር ወጪ የተሠሩ ፕሮጀክቶችን አስመርቋል። ዩኒቨርሲቲው በህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የኮምፕሪሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ማስፋፊያ ፕሮጀክቶችን አስመርቋል። በዩኒቨርሲቲው የተመረቁ ስድስት ፕሮጀክቶች፦ ● ልዩ የቀዶ ሕክምናና የወሊድ ፅኑ ህሙማን ክፍል ● የክሊኒካል ሙከራ ማዕከል (Clinical Trial Unit) ● የሕፃናት ቀዶ ሕክምና የልህቀት ማዕከል ● የጡት ወተት ባንክ (በኢትዮጵያ የመጀመሪያው) ● የኦክሲጅን ማምረቻና የሕክምና ጋዝ ሥርዓት ● የሕክምና ቆሻሻ ማቃጠያ (Incinerator) ፕሮጀክቶቹ የጤና አገልግሎትን ለማስፋፋት፣ የኅብረተሰቡን ጤና ለመጠበቅ እና ጥራት ያለው ሕክምና ለማቅረብ ጉልህ አስተዋጽኦ ይኖራቸዋል ተብሏል።

MINSTERY OF EDUCATION © - Statistics & analytics of Telegram channel @minster_of_education