es
Feedback
MINSTERY OF EDUCATION ©

MINSTERY OF EDUCATION ©

Ir al canal en Telegram

For more information! It’s all about education Official minstry of education telegram channel join and get more info About us ✅የተረጋገጠ የትምህርት ደረጃ ለማግኘት እኛን ይከተሉ!! https://www.youtube.com/@minster_of_education Ad:https://telega.io/c/minsterofeducation

Mostrar más

📈 Análisis del canal de Telegram MINSTERY OF EDUCATION ©

El canal MINSTERY OF EDUCATION © (@minster_of_education) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 43 029 suscriptores, ocupando la posición 4 254 en la categoría Educación y el puesto 750 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 43 029 suscriptores.

Según los últimos datos del 16 junio, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de 77, y en las últimas 24 horas de 13, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificación: No verificado
  • Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 10.42%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 4.99% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 4 485 visualizaciones. En el primer día suele acumular 2 148 visualizaciones.
  • Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 7.

📝 Descripción y política de contenido

El autor describe el recurso como un espacio para expresar opiniones subjetivas:
For more information! It’s all about education Official minstry of education telegram channel join and get more info About us ✅የተረጋገጠ የትምህርት ደረጃ ለማግኘት እኛን ይከተሉ!! https://www.youtube.com/@minster_of_education Ad:https://telega.io/c/minsterofeduca...

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 17 junio, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Educación.

43 029
Suscriptores
+1324 horas
+1467 días
+7730 días
Archivo de publicaciones
እነሆ ለቴሌግራም ቻናልዎ የሚሆን አጭር እና ማራኪ የማስታወቂያ ጥሪ ፅሁፍ፡ 📢 ማስታወቂያ ለምትፈልጉ ሁሉ! በቻናላችን @minster_of_education ላይ ምርትዎን፣ አገልግሎትዎን ወይም ድርጅትዎን በብዙ ሺህ ለሚቆጠሩ ተከታታዮቻችን ማስተዋወቅ ይፈልጋሉ? ✅ተደራሽነታችን፡ ንቁ እና እያደገ የመጣ ማህበረሰብ ✅ ዋጋችን፡ በጣም ተመጣጣኝ እና ኪስ የማይጎዳ ለማስታወቂያ ስራ እና ለተጨማሪ መረጃ በውስጥ መስመር ያናግሩን፡ 👉 @Minofedu ጥራት ያለው ማስታወቂያ ለተሻለ ውጤት!

ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ በኢኮኖሚክስ መስክ የሦስተኛ ዲግሪ (PhD) ትምህርት መስጠት ሊጀምር ነው፡፡ ዩኒቨርሲቲው በኢኮኖሚክስ የትምህርት መስክ አዲስ የዶክትሬት መርሐግብር ለመጀመር የስርዓተ-ትምህርት ግ
ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ በኢኮኖሚክስ መስክ የሦስተኛ ዲግሪ (PhD) ትምህርት መስጠት ሊጀምር ነው፡፡ ዩኒቨርሲቲው በኢኮኖሚክስ የትምህርት መስክ አዲስ የዶክትሬት መርሐግብር ለመጀመር የስርዓተ-ትምህርት ግምገማ አካሒዷል። በግምገማ መድረኩ ላይ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ፣ ከኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ፣ ከኢትዮጵያ ካፒታል ማርኬት ባለስልጣን እና ከፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት የተወከሉ ባለሙያዎች በአካል እና በዌቢናር ተሳትፈዋል። በምስራቅ የሀገሪቱ ክፍል በኢኮኖሚክስ የትምህርት መስክ በዶክትሬት ደረጃ ትምህርት የሚሰጥ ተቋም ባለመኖሩ ፕሮግራሙን በአካባቢው የመጀመሪያ ያደርገዋል ተብሏል። ግምገማውን ተከትሎ የፀደቀው ስርዓተ-ትምህርት፣ የልማት ኢኮኖሚክስ፣ ዓለም አቀፍ ኢኮኖሚክስና ንግድ እንዲሁም የፋይናንስ ኢኮኖሚክስ መስኮችን በዶክትሬት ዲግሪ ለማስተማር የተዘጋጁ መሆኑ ተገልጿል።

በ Lomi Study ፈተናዎች 10 ሺህ ብር ያሸንፉ! ብቃትን የሚመዝኑ ፈተናዎችን በመውሰድ እውቀታችሁን አሳድጉ፤ ሳምንታዊ ተሸላሚ ሁኑ! ዛሬውኑ ይቀላቀሉ! በ Lomi Study ምን ያገኛሉ? ● የፈ
በ Lomi Study ፈተናዎች 10 ሺህ ብር ያሸንፉ! ብቃትን የሚመዝኑ ፈተናዎችን በመውሰድ እውቀታችሁን አሳድጉ፤ ሳምንታዊ ተሸላሚ ሁኑ! ዛሬውኑ ይቀላቀሉ! በ Lomi Study ምን ያገኛሉ? ● የፈተና ልምምድ ● ከተለያዩ ትምህርት ቤቶች ጋር ውድድር ● ሳምንታዊ ፈተናዎች ላይ በመሳተፍ የ 10,000 ብር  ልዩ ሽልማት   Website: https://lomistudy.com/r/lomi28       Telegram Bot: https://t.me/Lomistudybot?start=lomi28

የቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሌኒየም ሕክምና ኮሌጅ የሥራ አመራር ቦርድ ለሁለት የተቋሙ መምህራን፣ ተመራማሪዎች እና የሕክምና ባለሙያዎች የሙሉ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ ሰጥቷል። ቦርዱ የሁለቱን ባለሙያዎች
+3
የቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሌኒየም ሕክምና ኮሌጅ የሥራ አመራር ቦርድ ለሁለት የተቋሙ መምህራን፣ ተመራማሪዎች እና የሕክምና ባለሙያዎች የሙሉ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ ሰጥቷል።   ቦርዱ የሁለቱን ባለሙያዎች የአካዳሚክ፣ የምርምር፣ የሕክምና አገልግሎት እና ተቋማዊ አበርክቶ ከገመገመ በኋላ የሙሉ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ አፅድቋል፡፡ በዚህም ዶ/ር ሰለሞን አሊ እና ዶ/ር በረከት ፋንታሁን የሙሉ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ እድገት አጊኝተዋል፡፡ ዶ/ር ሰለሞን አሊ ማይክሮባዮሎጅስትና የሕክምና ምርምር ስፔሻሊስት ሲሆኑ፤ ከ20 ዓመታት በላይ በቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሌኒየም ሕክምና ኮሌጅ እና በጅማ ዩኒቨርሲቲ በመምህርነት፣ በምርምር እና በሕክምና አገልግሎት እያገለገሉ የሚገኙ ባለሙያ ናቸው። በተመሳሳይ ዶ/ር በረከት ፋንታሁን በኮሌጁ ታሪክ የመጀመሪያዋ ሴት ፕሮፌሰር ሲሆኑ፤ በሙያቸው የህጻናት ሕክምና ስፔሻሊስት ናቸው፡፡ በሕጻናት ኢንዶክራይኖሎጂ ሕክምና ደግሞ የሰብ ስፔሻሊስት ስልጠና አላቸው፡፡ በሕክምና ትምህርት፣ በምርምር እና በጤና ሥርዓት ማጠናከር ላይ ከፍተኛ አስተዋፅኦ አበርክቶ ያላቸውና በአሁኑ ጊዜ በኮሌጅ በማገልገል ላይ የሚገኙ መሆኑ ከኮሌጁ የተገኘ መረጃ ያሳያል፡፡  

የመውጫ ፈተና እየወሰዱ የሚገኙ እናቶች በዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ እጩ ተመራቂ የሆኑ ሴት ተማሪዎች ልጆቻቸውን ከወለዱ ከተወሰኑ ቀናት በኋላ ሀገር አቀፍ የመውጫ ፈተና (Exit Exam) በመውሰድ ላይ ይ
+3
የመውጫ ፈተና እየወሰዱ የሚገኙ እናቶች   በዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ እጩ ተመራቂ የሆኑ ሴት ተማሪዎች ልጆቻቸውን ከወለዱ ከተወሰኑ ቀናት በኋላ ሀገር አቀፍ የመውጫ ፈተና (Exit Exam) በመውሰድ ላይ ይገኛሉ። እነዚህ ተማሪዎች የእናትነትን ኃላፊነት ከትምህርታዊ ግዴታቸው ጋር በማስታረቅ የመውጫ ፈተና በብርታት እየወሰዱ ይገኛሉ።   በተመሳሳይ ልጇን አዝላ የመውጫ ፈተና በመውሰድ ላይ የምትገኝ ብርቱ እናት በአክሱም ዩኒቨርሲቲ ተመልክትናል፡፡   የፅናት ምሳሌ ለሆኑ ለእነዚህ ተፈታኝ እናቶች መልካም ዕድል እንመኛለን።  

#ጥቆማ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ለ2019 የትምህርት ዘመን የመጀመሪያ ሴሚስተር የድኅረ-ምረቃ ፕሮግራሞች አመልካቾችን መቀበል ጀምሯል፡፡ ዩኒቨርሲቲው ለ Masters ፕሮግራም በመደበኛ እና በኤክስቴን
#ጥቆማ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ለ2019 የትምህርት ዘመን የመጀመሪያ ሴሚስተር የድኅረ-ምረቃ ፕሮግራሞች አመልካቾችን መቀበል ጀምሯል፡፡   ዩኒቨርሲቲው ለ Masters ፕሮግራም በመደበኛ እና በኤክስቴንሽን መርሐግብሮች እንዲሁም ለ PhD ፕሮግራም በመደበኛ እና በኤክስቴንሽን መርሐግብሮች አመልካቾችን ይቀበላል፡፡ የድኅረ-ምረቃ ፕሮግራሞቹን ዝርዝር በ https://admission.aau.edu.et/GraduatePrograms መመልከት ይችላሉ፡፡ አመልካቾች በቅድሚያ በዩኒቨርሲቲው የሚሰጠውን የድኅረ-ምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (GAT) መውሰድና ማለፍ ይጠበቅባቸዋል፡፡ የ GAT ማመልከቻ ጊዜ የሚያበቃው 👇 ነሐሴ 05/2018 ዓ.ም

የ4ኛ ቀን የቅድመ-ምረቃ ትምህርት የመውጫ ፈተናዎች እየተሰጡ ነው፡፡ በዛሬው ውሎ የ24 ትምህርት አይነት ፈተናዎች ይሰጣሉ፡፡ የመውጫ ፈተና የ4ኛ ቀን መርሐግብር (ሰኔ 09/2018 ዓ.ም) ✅ ፈረቃ
የ4ኛ ቀን የቅድመ-ምረቃ ትምህርት የመውጫ ፈተናዎች እየተሰጡ ነው፡፡ በዛሬው ውሎ የ24 ትምህርት አይነት ፈተናዎች ይሰጣሉ፡፡   የመውጫ ፈተና የ4ኛ ቀን መርሐግብር (ሰኔ 09/2018 ዓ.ም) ✅ ፈረቃ 1: ጠዋት ከ2:00-4:30 ሰዓት ✅ ፈረቃ 2: ጠዋት ከ5፡00-7:30 ሰዓት ✅ ፈረቃ 3: ከሰዓት ከ08:30-11:00 ሰዓት   የመውጫ ፈተና እስከ ሰኔ 12/2018 ዓ.ም በኦንላይን ይሰጣል፡፡ ምስል፦ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ

#ጥቆማ በ2018 ዓ.ም ሀገር አቀፍ የሬዚደንሲ ፈተና ወስዳችሁ ያለፋችሁና በተለያዩ ተቋማት የተመደባችሁ፤ ነገር ግን በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ በጤና ሳይንስና ህክምና ኮሌጅ School of Medicine,
#ጥቆማ   በ2018 ዓ.ም ሀገር አቀፍ የሬዚደንሲ ፈተና ወስዳችሁ ያለፋችሁና በተለያዩ ተቋማት የተመደባችሁ፤ ነገር ግን በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ በጤና ሳይንስና ህክምና ኮሌጅ School of Medicine, General Surgery ትምህርት ዘርፍ ለመማር የምትፈልጉ ሐኪሞች እንድታመለክቱ ዩኒቨርሲቲው ጋብዟል፡፡   የምዝገባ ጊዜ፦ ከሰኔ 08-12/2018 ዓ.ም   የማመልከቻ አማራጮች፦ ● Email: registrar@wku.edu.et ● በአካል በዩኒቨርሲቲው ዋና ሬጅስትራር ጽ/ቤት   ለተጨማሪ መረጃ፦ 0920204770  

💥 የክረምት ስልጠና (ከ40% እስከ 60% ቅናሽ እስከ ሰኔ 21/2018 ዓ.ም ለምትመዘገቡ) 💥 የጋዜጠኝነት ስልጠና ምዝገባ ላይ ነን! በስልጠናው የተካተቱ፦ 👉 መሠረታዊ የጋዜጠኝነት መርሆች፣
💥 የክረምት ስልጠና (ከ40% እስከ 60% ቅናሽ እስከ ሰኔ 21/2018 ዓ.ም ለምትመዘገቡ) 💥 የጋዜጠኝነት ስልጠና ምዝገባ ላይ ነን! በስልጠናው የተካተቱ፦ 👉 መሠረታዊ የጋዜጠኝነት መርሆች፣ የሚዲያ እና የጋዜጠኝነት ዓይነቶች  👉 የዜና አሰራር እና የቃለመጠይቅ አደራረግ 👉 የመዝናኛ ፕሮግራም ጋዜጠኝነት፣ የፕሮግራም ዝግጅት፣ የማስታወቂያ አሰራር እና ዶክመንተሪ ዝግጅት 👉 የሞባይል እና የዩቲዩብ ጋዜጠኝነት ስልጠናው ሰኔ 29/2018 ዓ.ም ይጀምራል! የበለጠ ይጠብቁ ... 💥 ሴጅ ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት 💥 ☎️  0906777799 / 0906777755 አድራሻ፦ ቁ.1: ፒያሣ ቸርችል ጎዳና ኤልያና ሆቴል 2ኛ ፎቅ ቁ.2: መገናኛ ታሜጋስ ህንፃ 2ኛ ፎቅ ቁ.3: አዳማ ለመመዝገብ ድረ-ገጽ 👇 www.sageethiopia.com Telegram: https://t.me/sagetraininginstitute TikTok: https://www.tiktok.com/@sage_training_institute LinkedIn: https://www.linkedin.com/company/sage-training-institute

#HawassaUniversity ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ለዘጠኝ የተቋሙ መምህራን የሙሉ ፕሮፌሰርነት የደረጃ እድገት ሰጠ። የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሥራ አመራር ቦርድ የዘጠኙ መምህራንን የሙሉ ፕሮፌሰርነት የደረጃ
#HawassaUniversity ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ለዘጠኝ የተቋሙ መምህራን የሙሉ ፕሮፌሰርነት የደረጃ እድገት ሰጠ። የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሥራ አመራር ቦርድ የዘጠኙ መምህራንን የሙሉ ፕሮፌሰርነት የደረጃ እድገት አፅድቋል። የሙሉ ፕሮፌሰርነት የደረጃ እድገት ያገኙ፦ 1. ዶ/ር አቻምየለሽ ገብረፃዲቅ ተክሌ - በ Public Health 2. ዶ/ር አለማየሁ ሙሉነህ ቢተው - በ Climate Change and Environmental Science 3. ዶ/ር አውደነገስት ሞገስ ባንጃው - በ Soil and Water Conservation 4. ዶ/ር ምህረት ዳናንቶ ዑልሲዶ - በ Water Supply and Environmental Engineering 5. ዶ/ር ሙሉጌታ ዳዲ በለጠ - በ Hydrology 6. ዶ/ር አንዳርጋቸው ገዴቦ አቢተአ - በ Plant Breeding 7. ዶ/ር ዘሪሁነ ግርማ ወ/ገብርኤል - በ Wildlife Ecology and Management 8. ዶ/ር ሁሴን ሞሐመድ በሽር- በ Horticultural Sciences 9. ዶ/ር ታረቀኝ ዮሴፍ ሳማጎ- በ Agronomy https://t.me/minster_of_education

#ጥቆማ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሰብዓዊ መብቶች ማዕከል በ 2019 ዓ.ም በ Human Rights የትምህርት መስክ የ2ኛ ዲግሪ እና የ3ኛ ዲግሪ (PhD) ፕሮግራሞች ለመማር ያመለክቱ! ፍላጎት ያላ
#ጥቆማ   በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሰብዓዊ መብቶች ማዕከል በ 2019 ዓ.ም በ Human Rights የትምህርት መስክ የ2ኛ ዲግሪ እና የ3ኛ ዲግሪ (PhD) ፕሮግራሞች ለመማር ያመለክቱ!   ፍላጎት ያላቸውና ብቁ የሆኑ አመልካቾች እንዲያመለክቱ ማዕከሉ ጥሪ አድርጓል፡፡   ለዝርዝር መረጃ፣ መስፈርቶችን ለማየት እና የማመልከቻ መመሪያ ለማግኘት 👇 https://www.aau.edu.et/announcements/detail?title=Call~for~applications~for~admission~to~graduate~programs~for~the~First~Semester~of~2026/27~(2019~E.C.)~Academic~Year   አመልካቾች በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሚሰጠውን የድኅረ-ምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (GAT) ወስደው ማለፍ ይጠበቅባቸዋል፡፡   https://t.me/minster_of_education

የ2018 ትምህርት ዘመን የ6ኛ ክፍል ክልል/ከተማ አቀፍ ፈተና በተለያዩ ክልሎች እና በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር መሰጠት ጀምሯል። ፈተናው ከዛሬ ሰኔ 08/2018 ዓ.ም ጀምሮ ለሦስት ተከታታይ ቀ
+3
የ2018 ትምህርት ዘመን የ6ኛ ክፍል ክልል/ከተማ አቀፍ ፈተና በተለያዩ ክልሎች እና በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር መሰጠት ጀምሯል።   ፈተናው ከዛሬ ሰኔ 08/2018 ዓ.ም ጀምሮ ለሦስት ተከታታይ ቀናት ይሰጣል፡፡   https://t.me/minster_of_education

በኢንተርኔት የታገዘ የመስኖ መቆጣጠሪያ ሲስተም (IoT Smart Irrigation System) የሠሩ ወጣቶች የቴክኒክና ሙያ ሥልጠና ኢንስቲትዩት የመጀመሪያው የቴክኖሎጂ ውድድር አሸናፊዎች ሆነዋል፡፡
+3
በኢንተርኔት የታገዘ የመስኖ መቆጣጠሪያ ሲስተም (IoT Smart Irrigation System) የሠሩ ወጣቶች የቴክኒክና ሙያ ሥልጠና ኢንስቲትዩት የመጀመሪያው የቴክኖሎጂ ውድድር አሸናፊዎች ሆነዋል፡፡   ኢንስቲትዩቱ ያዘጋጀው የመጀመሪያው ዓለም አቀፍ የቴክኒክና ሙያ ምርምር ኮንፈረንስና የቴክኖሎጂ ውድድር ተጠናቋል።   በቴክኖሎጂ ውድድሩ ከ10 ሀገራት የተውጣጡ 35 ፈጠራዎች ለውድድር የቀረቡ ሲሆን፤ ኢትዮጵያውያን ወጣቶች አንደኛ እና ሁለተኛ ደረጃን ሲይዙ፣ ናይጄሪያዊው ወጣት የፈጠራ ባለሙያ ሦስተኛ ደረጃን በማግኘት የነሐስ ሜዳሊያ ተሸላሚ ሆኗል።   የቴክኖሎጂ ውድድሩ አሸናፊዎች የሆኑት IoT Smart Irrigation System አንደኛ፣ የCerebro Logic ሁለተኛ እንዲሁም የናይጄሪያው Eco-Bin Revenue Intelligence and Traceability System ሦስተኛ ደረጃን አግኝተዋል።   የመስኖ መቆጣጠሪያ ሲስተም ቴክኖሎጂው እስከ 10ኪሜ ርቀት ላይ ያሉ የመስኖ እርሻዎችን ለመከታተልና አስፈጊውን ግባዓት ለማቅረብ የሚረዳ ነው።   https://t.me/minster_of_education

ሴጅ ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት ቁጥር ሦስት በአዳማ ራስ ሆቴል 2ኛ ፎቅ ላይ ትናንት ሰኔ 07/2018 ዓ.ም ተመርቋል። የበለጠ ይጠብቁ ... 💥 ሴጅ ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት 💥 ☎️ 0906777799 /
+3
ሴጅ ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት ቁጥር ሦስት በአዳማ ራስ ሆቴል 2ኛ ፎቅ ላይ ትናንት ሰኔ 07/2018 ዓ.ም ተመርቋል። የበለጠ ይጠብቁ ... 💥 ሴጅ ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት 💥 ☎️  0906777799 / 0906777755 አድራሻ፦ ቁ.1: ፒያሣ ቸርችል ጎዳና ኤልያና ሆቴል 2ኛ ፎቅ ቁ.2: መገናኛ ታሜጋስ ህንፃ 2ኛ ፎቅ ቁ.3: አዳማ ራስ ሆቴል 2ኛ ፎቅ ለመመዝገብ ድረ-ገጽ 👇 www.sageethiopia.com Telegram: https://t.me/sagetraininginstitute TikTok: https://www.tiktok.com/@sage_training_institute LinkedIn: https://www.linkedin.com/company/sage-training-institute

#ጥቆማ ነጻ የክረምት ስልጠና ይከታተሉ! የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ከ1ኛ-12ኛ ክፍል ለሆነ ተማሪዎች የክረምት ስልጠና አዘጋጅቷል። የክረምት ስልጠና መስኮች፦ ● ፋንዳሜንታልስ
#ጥቆማ ነጻ የክረምት ስልጠና ይከታተሉ! የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ከ1ኛ-12ኛ ክፍል ለሆነ ተማሪዎች የክረምት ስልጠና አዘጋጅቷል። የክረምት ስልጠና መስኮች፦ ● ፋንዳሜንታልስ ኦፍ ኤ.አይ. ● ፕሮግራሚንግ ● ማሽን ለርኒንግ ● ሮቦቲክስ እና IOT ● ዳታ ሳይንስ የምዝገባ ጊዜ የሚያበቃው 👇 ሰኔ 30/2018 ዓ.ም በተከታዩ የጉግል ፎርም ይመዝገቡ 👇 https://forms.gle/uDGPmQsiZcWWeNuRA

#HawassaUniversity ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ በ2.8 ቢሊዮን ብር ወጪ የተሠሩ ፕሮጀክቶችን አስመርቋል። ዩኒቨርሲቲው በህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የኮምፕሪሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ማስፋፊያ ፕ
+8
#HawassaUniversity ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ በ2.8 ቢሊዮን ብር ወጪ የተሠሩ ፕሮጀክቶችን አስመርቋል። ዩኒቨርሲቲው በህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የኮምፕሪሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ማስፋፊያ ፕሮጀክቶችን አስመርቋል። በዩኒቨርሲቲው የተመረቁ ስድስት ፕሮጀክቶች፦ ● ልዩ የቀዶ ሕክምናና የወሊድ ፅኑ ህሙማን ክፍል ● የክሊኒካል ሙከራ ማዕከል (Clinical Trial Unit) ● የሕፃናት ቀዶ ሕክምና የልህቀት ማዕከል ● የጡት ወተት ባንክ (በኢትዮጵያ የመጀመሪያው) ● የኦክሲጅን ማምረቻና የሕክምና ጋዝ ሥርዓት ● የሕክምና ቆሻሻ ማቃጠያ (Incinerator) ፕሮጀክቶቹ የጤና አገልግሎትን ለማስፋፋት፣ የኅብረተሰቡን ጤና ለመጠበቅ እና ጥራት ያለው ሕክምና ለማቅረብ ጉልህ አስተዋጽኦ ይኖራቸዋል ተብሏል።

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የ2018 ዓ.ም የ6ኛ እና የ8ኛ ክፍል ፈተናዎች ከሰኔ 09-12/2018 ዓ.ም ይሰጣሉ። - የክልሉ ትምህርት ቢሮ የ6ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና ➫ ሰኔ 09
በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የ2018 ዓ.ም የ6ኛ እና የ8ኛ ክፍል ፈተናዎች ከሰኔ 09-12/2018 ዓ.ም ይሰጣሉ። - የክልሉ ትምህርት ቢሮ የ6ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና ➫ ሰኔ 09 እና 10/2018 ዓ.ም ይሰጣል፡፡ የ8ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ➫ ሰኔ 11 እና 12/2018 ዓ.ም ይሰጣል፡፡

#ጥቆማ የነርሲንግ አመራርና ሙያዊ አቅም ማጠናከሪያ ፕሮግራም ስልጠና ይውሰዱ! ፍላጎት ያላችሁ የነርሲንግ ባለሙያዎች ምዝገባ እንድታደርጉ ጤና ሚኒስቴር ጋብዟል። ብቃትን መሠረት ያደረገ ምልመላ ተከት
#ጥቆማ የነርሲንግ አመራርና ሙያዊ አቅም ማጠናከሪያ ፕሮግራም ስልጠና ይውሰዱ! ፍላጎት ያላችሁ የነርሲንግ ባለሙያዎች ምዝገባ እንድታደርጉ ጤና ሚኒስቴር ጋብዟል። ብቃትን መሠረት ያደረገ ምልመላ ተከትሎ ሰልጣኞች አድቫንስድ ክሊኒካል የተግባር ዝግጁነት ስልጠና ይወስዳሉ። ስልጠናውን ሲያጠናቅቁ የተረጋገጠ ዲጂታል ሰርተፊኬት የሚያገኙ ይሆናል። የምዝገባ ጊዜ 👇 ከሰኔ 04-10/2018 ዓ.ም ለማመልከት 👇 https://ncep.mohdigitalhealth.gov.et

#ጥቆማ የሞሮኮ መንግሥት በ2026/27 የትምህርት ዘመን መስፈርቱን ለሚያሟሉ 50 ኢትዮጵያውያን ተማሪዎች ነጻ የትምህርት ዕድል ሰጥቷል። በመሆኑም መስፈርቱን የሚያሟሉ አመልካቾች ለዚሁ ዓላማ ተብሎ
#ጥቆማ የሞሮኮ መንግሥት በ2026/27 የትምህርት ዘመን መስፈርቱን ለሚያሟሉ 50 ኢትዮጵያውያን ተማሪዎች ነጻ የትምህርት ዕድል ሰጥቷል። በመሆኑም መስፈርቱን የሚያሟሉ አመልካቾች ለዚሁ ዓላማ ተብሎ በተከፈተው ድረ-ገፅ www.marccalumni.ma በማመልከት የትምህርት ዕድሉ ተጠቃሚ መሆን እንደሚችሉ ትምህርት ሚኒስቴር በቀን 26/09/2018 ዓ.ም ለሁሉም የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች በጻፈው ደብዳቤ ገልጿል። ለማመልከት 👇 www.marccalumni.ma የምዝገባ ጊዜ የሚያበቃው 👇 ሰኞ ሰኔ 08/2018 ዓ.ም

በሚገኙበት ክልል ወይም ከተማ አስተዳደር የመኖሪያ ቤት ወይም የመኖሪያ ቤት መስሪያ ቦታ ያልተሰጣቸው የዩኒቨርሲቲ መምህራን ስም ዝርዝርን እንዲልኩ ትምህርት ሚኒስቴር ሁሉንም የመንግሥት ዩኒቨርሲዎች
በሚገኙበት ክልል ወይም ከተማ አስተዳደር የመኖሪያ ቤት ወይም የመኖሪያ ቤት መስሪያ ቦታ ያልተሰጣቸው የዩኒቨርሲቲ መምህራን ስም ዝርዝርን እንዲልኩ ትምህርት ሚኒስቴር ሁሉንም የመንግሥት ዩኒቨርሲዎች ጠይቋል። በቀን 04/10/2018 ዓ.ም በትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ደኤታ ኮራ ጡሹ ለሁሉም የመንግሥት ዩኒቨርሲዎች የተጻፈ ደብዳቤ፣ ከሰኔ 04/2018 ዓ.ም ጀምሮ ባሉት ተከታታይ 15 ቀናት ውስጥ የመምህራኑ ዝርዝር ለሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ እንዲላክ አዟል።