es
Feedback
PARO EDU

PARO EDU

Ir al canal en Telegram

📖 Paro Edu | ትክክለኛና ፈጣን የትምህርት መረጃዎች፣ የፈተና ውጤቶች እና ወቅታዊ ዜናዎች የሚገኙበት ቻናል! 🎓 ዕውቀትዎን ያሳድጉ፤ ከእኛ ጋር ይማሩ! @ParoEdu @Paro_media @ParoLink 🎥 የዩቲዩብ ቻናላችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ 👇 🔗 https://www.youtube.com/@Paroedu

Mostrar más

📈 Análisis del canal de Telegram PARO EDU

El canal PARO EDU (@paroedu) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 45 858 suscriptores, ocupando la posición 3 806 en la categoría Educación y el puesto 736 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 45 858 suscriptores.

Según los últimos datos del 18 septiembre, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de 236, y en las últimas 24 horas de -196, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificación: No verificado
  • Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 11.31%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 5.72% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 5 207 visualizaciones. En el primer día suele acumular 2 631 visualizaciones.
  • Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 7.

📝 Descripción y política de contenido

El autor describe el recurso como un espacio para expresar opiniones subjetivas:
📖 Paro Edu | ትክክለኛና ፈጣን የትምህርት መረጃዎች፣ የፈተና ውጤቶች እና ወቅታዊ ዜናዎች የሚገኙበት ቻናል! 🎓 ዕውቀትዎን ያሳድጉ፤ ከእኛ ጋር ይማሩ! @ParoEdu @Paro_media @ParoLink 🎥 የዩቲዩብ ቻናላችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ 👇 🔗 https://www.youtube.com/@Paroedu

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 19 septiembre, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Educación.

45 858
Suscriptores
-19624 horas
-1 1867 días
+23630 días
Archivo de publicaciones
PARO EDU
45 708
በአማራ ክልል ለ2019 የትምህርት ዘመን ከ4.7 ሚሊዮን በላይ ተማሪዎች ተመዝግበዋል። - የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ በክልሉ በ2019 የትምህርት ዘመን 7.6 ሚሊዮን ተማሪዎች ለመመዝገብ ታቅዶ እስ
በአማራ ክልል ለ2019 የትምህርት ዘመን ከ4.7 ሚሊዮን በላይ ተማሪዎች ተመዝግበዋል። - የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ በክልሉ በ2019 የትምህርት ዘመን 7.6 ሚሊዮን ተማሪዎች ለመመዝገብ ታቅዶ እስከ ጳጉሜን 5 ቀን 2018 ዓ.ም በተካሄደ ምዝገባ ከ4.7 ሚሊዮን በላይ (62 በመቶ) ተማሪዎች መመዝገባቸውን ቢሮው ገልጿል፡፡ የትምህርት ቀናት እንዳይባክኑ ምዝገባን በአጭር ጊዜ ለማጠናቀቅ ሲሠራ መቆየቱን የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ጌታቸው ቢያዝን ለሪፖርተር ተናግረዋል። ምዝገባ ያላደረጉ 38 በመቶ ቀሪ ተማሪዎችን ምዝገባ በአጭር ጊዜ ውስጥ ለማጠናቀቅ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ገልፀዋል። የተመዘገበው አፈጻጸም ከዚህ ቀደም እስከ ጥቅምት፣ ኅዳር እና ታኅሳስ ወራት ድረስ ይቀጥል የነበረው የምዝገባ ሥራ በዚህ ዓመት እንደማይኖር አመላካች ነው ብለዋል። ከዚህ ጋር ተያይዞ የሚያጋጥሙ ችግሮችን ከማኅበረሰቡና ከተፅዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦች ጋር ውይይት በማድረግ ለመፍታት ጥረት እየተደረገ መሆኑንም ጠቁመዋል። #ሪፖርተር https://t.me/ParoEdu

PARO EDU
45 708
የዳግማዊ ምኒልክ ሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ በተለያዩ የጤና መስኮች ያስተማራቸውን 556 ተማሪዎች አስመረቀ፡፡ ኮሌጁ በቅድመ-ምረቃ ፕሮግራሞች ያስተማራቸውን 475 ተማሪዎች እንዲሁም 81 ተማሪዎችን
+3
የዳግማዊ ምኒልክ ሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ በተለያዩ የጤና መስኮች ያስተማራቸውን 556 ተማሪዎች አስመረቀ፡፡ ኮሌጁ በቅድመ-ምረቃ ፕሮግራሞች ያስተማራቸውን 475 ተማሪዎች እንዲሁም 81 ተማሪዎችን በድኅረ-ምረቃ ፕሮግራም በድምሩ 556 ተማሪዎችን በዛሬው ዕለት አስመርቋል። ከአኔስቴዢያ ትምህርት ክፍል CGPA 3.99 የላቀ ውጤት ያጣችው ናርዶስ ተስፋዬ የወርቅ ሜዳሊያ ተሸላሚ ሆናለች። ናርዶስ እና ሌሎች ሁለት እጅግ ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገቡ ተመራቂዎች በኮሌጁ በማስተማር እንዲቀጥሉ የኮሌጁ ሴኔት ወስኗል። ኮሌጁን በሚቀጥሉት 10 ዓመታት ውስጥ ሙሉ የሆስፒታል ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ (Hospital University College) ለማድረግ እየተሠራ እንደሚገኝ ከአዲስ አበባ ጤና ቢሮ ያገኘነው መረጃ ያሳያል። https://t.me/ParoEdu

PARO EDU
45 708
በስራዎቻችሁ ወይም በትምህርታችሁ AI (Artificial Intelligence) መሳሪያዎችን ምን ያህል ይጠቀማሉ?"
Anonymous voting

PARO EDU
45 708

PARO EDU
45 708
🚀 0 → 1,000 Subscribers! በፍጥነት ለማሳደግ 10 ኃይለኛ የYouTube ስልቶች | YouTube Growth 2026 ✅ተጨማሪ ጠቃሚ መረጃዎችን ለማግኘት 👇👇👇 ቪዲዮውን ይመልከቱ: https://youtu.be/v8dCGYI-GDg?si=eq11-qzZp2aCaRF5 ⭕️የቴሌግራፊ ቻናላችንን ይቀላቀሉ: @Paro_media ⭕️ለሌሎችም እንዲደርስ ሼር ያድርጉ! @Paroedu

PARO EDU
45 708
አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ (AI) ሰዎችን ይተካል ብላችሁ ታስባላችሁ?"
Anonymous voting

PARO EDU
45 708

PARO EDU
45 708
አካል ጉዳተኝነት ከውጤት ያልገደባት ተማሪ ‎ ተማሪ ሶሊያና ማሩ፣ ‎በ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ፈተና ወስደው ከፍተኛ ውጤት ካስመዘገቡ አካል ጉዳተኛ ተማሪዎች መካከል አንዷ ናት። ‎ ‎የማኅበራዊ
አካል ጉዳተኝነት ከውጤት ያልገደባት ተማሪ ‎ ተማሪ ሶሊያና ማሩ፣ ‎በ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ፈተና ወስደው ከፍተኛ ውጤት ካስመዘገቡ አካል ጉዳተኛ ተማሪዎች መካከል አንዷ ናት። ‎ ‎የማኅበራዊ ሳይንስ ተማሪዋ ሶሊያና፣ ከ600 ውስጥ 437 በማምጣት የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ውጤት አሳክታለች። ‎ ‎አካል ጉዳተኛ ብትሆንም፣ አልችልም ብላ ተስፋ ሳትቆርጥ ፈተናዎችን ተሻግራ ከፍተኛ የሚባል ውጤት አስመዝግባለች። 👏👏 ላስመዘገበችው ውጤት የቤተሰቦቿ እና የመምህራን ልዩ ድጋፍ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳረገላት ትገልጻለች። ‎በዩኒቨርሲቲ ቆይታዋ የሕግ ትምህርት ለመቀጠል ፍላጎት እንዳላት የምትገልፀው ተማሪ ሶሊያና፤ በኤሌክትሪክ የሚሠራ ዘመናዊ ዊልቼሮች ድጋፍ እንዲደረግላት ጠይቃለች። #አሚኮ 📣ለትምህርታዊ መረጃዎች ​📚 Join & Share with friends! Help others learn and grow with @ParoEdu. ​👉 Join @ParoEdu

PARO EDU
45 708
🔹 ሰላም የፓሮ ሚዲያ ቤተሰቦች! ዛሬ በነፃ (Free) ከምንም በላይ በፈጣን ሁኔታ በ AI ቪዲዮዎችን ማመንጨት የሚያስችሉ ምርጥ ሶፍትዌሮችን ይዘን መጥተናል! ⭕️ ቴክኖሎጂን በመጠቀም የራሶትን ቪ
🔹 ሰላም የፓሮ ሚዲያ ቤተሰቦች! ዛሬ በነፃ (Free) ከምንም በላይ በፈጣን ሁኔታ በ AI ቪዲዮዎችን ማመንጨት የሚያስችሉ ምርጥ ሶፍትዌሮችን ይዘን መጥተናል! ⭕️ ቴክኖሎጂን በመጠቀም የራሶትን ቪዲዮዎች በቀላሉ መስራት ከፈለጉ እነዚህን ነፃ መሣሪያዎች ሊጠቀሙ ይገባል፦ ✅️ 1. InVideo AI ✔️ ለጀማሪዎች በጣም ቀላል እና ምቹ የሆነ ሶፍትዌር ነው። ✔️ የፅሁፍ ትዕዛዝ (Prompt) በመጻፍ ብቻ ሙሉ ቪዲዮ ከድምጽ እና ከቪዲዮ ክሊፖች ጋር አብሮ ያዘጋጅልዎታል። ✅️ 2. Luma Dream Machine ✔️ እጅግ አስደናቂ እና ጥራታቸው የጠበቁ የሲኒማቲክ ቪዲዮዎችን በነፃ ለመፍጠር የሚያስችል ድንቅ AI መሳሪያ ነው። ✅️ 3. Kling AI ✔️ እንቅስቃሴዎችን (Motion) በሚገባ በመረዳት ተጨባጭ እና ሕያው የሆኑ ቪዲዮዎችን ማመንጨት የሚችል ዘመናዊ ሶፍትዌር ነው። ✅️ 4. Leonardo AI ✔️ ለቪዲዮ መነሻ የሚሆኑ ውብ ምስሎችን እና የአኒሜሽን ዲዛይኖችን በነፃ ለማግኘት ይጠቀሙበት። ❇️ ማጠቃለያ፦ እነዚህን ነፃ የ AI መሳሪያዎች በመጠቀም የትኛውንም የቪዲዮ ይዘት ያለ ምንም ወጪ በፍጥነት ማዘጋጀት ይችላሉ። አሁኑኑ ሞክሯቸው! 👇 ተጨማሪ ጠቃሚ የቴክኖሎጂ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉ! 🔗 https://t.me/Paro_media

PARO EDU
45 708
#ጥቆማ ‎የቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሌኒየም ሕክምና ኮሌጅ የነርሲንግ ትምህርት ቤት አዲስ ለሚጀመረው የአጠቃላይ ነርሲንግ የዲግሪ ፕሮግራም (BSc in Comprehensive Nursing) የማመልከቻ
#ጥቆማ ‎የቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሌኒየም ሕክምና ኮሌጅ የነርሲንግ ትምህርት ቤት አዲስ ለሚጀመረው የአጠቃላይ ነርሲንግ የዲግሪ ፕሮግራም (BSc in Comprehensive Nursing) የማመልከቻ ጊዜ እስከ መስከረም 13/2019 ዓ.ም ድረስ አራዝሟል። በፕሮግራሙ የሚታቀፉ ተማሪዎች፦ ➻ የተሟላ የዶርሚተሪ፣ የምግብ እና ሌሎች አገልግሎቶችን ያገኛሉ። ➻ አዳዲስ ኮርሶችን፣ ይዘቶችን እና የስልጠና አካሔዶችን ያካተተ ስልጠና ያገኛሉ። ➻ የተደራጀ ሲሙሌሽን እና ተግባር ተኮር ስልጠና ያገኛሉ። የምዝገባ ጊዜ 👇 እስከ መስከረም 13/2019 ዓ.ም ከቀኑ 11፡00 ድረስ ብቻ ይመዝገቡ 👇 https://portal.sphmmc.edu.et/Web/Announcement ለተጨማሪ መረጃ፦ 0118965125 / 0112756089 ​📚 Join & Share with friends! Help others learn and grow with @ParoEdu. ​👉 Join @ParoEdu

PARO EDU
45 708
#MoE በ2019 ዓ.ም ወደ ፌዴራል ልዩ አዳሪ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለ9ኛ እና 10ኛ ክፍል ለመማር ተመዝግባችሁ ላለፋችሁና እስካሁን ድረስ ምዝገባ ያላደረጋችሁ ተማሪዎች፣ ቀደም ሲል ለምዝገባ
#MoE በ2019 ዓ.ም ወደ ፌዴራል ልዩ አዳሪ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለ9ኛ እና 10ኛ ክፍል ለመማር ተመዝግባችሁ ላለፋችሁና እስካሁን ድረስ ምዝገባ ያላደረጋችሁ ተማሪዎች፣ ቀደም ሲል ለምዝገባ በተጠቀማችሁበት ሊንክ (https://sbs.moe.gov.et/apply) በመግባት እስከ እሑድ መስከረም 10/2019 ዓ.ም ድረስ እንድትመዘገቡ ትምህርት ሚኒስቴር አሳስቧል። ​📚 Join & Share with friends! Help others learn and grow with @ParoEdu. ​👉 Join @ParoEdu

PARO EDU
45 708
#LorcanMedicalCollege ሎርካን ሜዲካል ኮሌጅ ለ2019 ዓ.ም አዲስ ገቢ ተማሪዎቹ የመግቢያ እና የትምህርት መጀመርያ የጊዜ ሰሌዳ ይፋ አድርጓል። ​በወጣው የጊዜ ሰሌዳ መሠረት የመግቢያ ፈ
+3
#LorcanMedicalCollege ሎርካን ሜዲካል ኮሌጅ ለ2019 ዓ.ም አዲስ ገቢ ተማሪዎቹ የመግቢያ እና የትምህርት መጀመርያ የጊዜ ሰሌዳ ይፋ አድርጓል። ​በወጣው የጊዜ ሰሌዳ መሠረት የመግቢያ ፈተና መስከረም 20/2019 ዓ.ም የሚሰጥ ሲሆን፣ የቃል ፈተና መስከረም 21/2019 ዓ.ም ይሰጣል። የዲግሪ ተማሪዎች ኦረንቴሽን መስከረም 22/2019 ዓ.ም እንደሚሰጥ ተገልጿል። የምዝገባ ማጠናቀቂያ ጊዜ 👇 መስከረም 25 እና 26/2019 ዓ.ም መደበኛ ትምህርት የሚጀመረው መስከረም 27/2019 ዓ.ም መሆኑ ተመላክቷል። አዲስ ገቢ ተማሪዎቹ በሕክምና፣ በጥርስ ሕክምና፣ በጥርስ ሳይንስ እንዲሁም በነርሲንግ የትምህርት መስኮች ትምህርታቸውን የሚከታተሉ መሆናቸውን የሎርካን ሜዲካል ኮሌጁ ፕሮቮስት ሔኖክ አለሙ ገልፀዋል። (የመግቢያ ፈተና አወጣጥ ዝርዝር እንዲሁም አካዳሚክ ካላንደሩ ከላይ ተያይዟል።) ​📚 Join & Share with friends! Help others learn and grow with @ParoEdu. ​👉 Join @ParoEdu

PARO EDU
45 708
አካል ጉዳተኝነት ከውጤት ያልገደባት ተማሪ ‎ ተማሪ ሶሊያና ማሩ፣ ‎በ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ፈተና ወስደው ከፍተኛ ውጤት ካስመዘገቡ አካል ጉዳተኛ ተማሪዎች መካከል አንዷ ናት። ‎ ‎የማኅበራዊ
አካል ጉዳተኝነት ከውጤት ያልገደባት ተማሪ ‎ ተማሪ ሶሊያና ማሩ፣ ‎በ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ፈተና ወስደው ከፍተኛ ውጤት ካስመዘገቡ አካል ጉዳተኛ ተማሪዎች መካከል አንዷ ናት። ‎ ‎የማኅበራዊ ሳይንስ ተማሪዋ ሶሊያና፣ 437 ነጥብ የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ውጤት አሳክታለች። ‎ ‎አካል ጉዳተኛ ብትሆንም፣ አልችልም ብላ ተስፋ ሳትቆርጥ ፈተናዎችን ተሻግራ ከፍተኛ የሚባል ውጤት አስመዝግባለች። 👏👏 ላስመዘገበችው ውጤት የቤተሰቦቿ እና የመምህራን ልዩ ድጋፍ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳረገላት ትገልጻለች። ‎በዩኒቨርሲቲ ቆይታዋ የሕግ ትምህርት ለመቀጠል ፍላጎት እንዳላት የምትገልፀው ተማሪ ሶሊያና፤ በኤሌክትሪክ የሚሠራ ዘመናዊ ዊልቼሮች ድጋፍ እንዲደረግላት ጠይቃለች። #አሚኮ ​📚 Join & Share with friends! Help others learn and grow with @ParoEdu. ​👉 Join @ParoEdu

PARO EDU
45 708
📣 REGISTRATION NOW OPEN!!! Jimma University has brought selected master’s programs right to the capital city, which are tail
📣 REGISTRATION NOW OPEN!!! Jimma University has brought selected master’s programs right to the capital city, which are tailored to the demands of today's dynamic job market, and is now accepting applications! 🎓   𝙒𝙝𝙞𝙘𝙝 𝙥𝙧𝙤𝙜𝙧𝙖𝙢 𝙖𝙧𝙚 𝙮𝙤𝙪 𝙞𝙣𝙩𝙚𝙧𝙚𝙨𝙩𝙚𝙙 𝙞𝙣 𝙚𝙣𝙧𝙤𝙡𝙡𝙞𝙣𝙜 𝙞𝙣? MSc in Artificial Intelligence MA in Project Management and Finance MBA in Business Administration MA in Logistics and Supply Chain Management MA in International Relations and Diplomacy MPH in General Public Health MPH in Epidemiology MSc in Health Monitoring and Evaluation MSc in Health Economics   Ready to Join? Register: https://portal.ju.edu.et/announce/show/6   𝐅𝐨𝐫 𝐌𝐨𝐫𝐞 𝐈𝐧𝐟𝐨𝐫𝐦𝐚𝐭𝐢𝐨𝐧 📞 +251978464748 📍 Kazanchis, Infront of Radisson Blu Hotel (the former HQ of Zemen Bank) 🔗 Telegram   𝙀𝙖𝙧𝙣 𝙖 𝙅𝙞𝙢𝙢𝙖 𝙐𝙣𝙞𝙫𝙚𝙧𝙨𝙞𝙩𝙮 𝘿𝙚𝙜𝙧𝙚𝙚 𝙞𝙣 𝘼𝙙𝙙𝙞𝙨 𝘼𝙗𝙖𝙗𝙖!   #JimmaUniversity #PostgraduateProgram #MastersDegree #HigherEducation #ApplicationOpen #ApplyNow ​📚 Join & Share with friends! Help others learn and grow with @ParoEdu. ​👉 Join @ParoEdu

PARO EDU
45 708
#DebreTaborUniversity ደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ የሁሉም የተቋሙ ነባር የቅድመ እና የድኅረ-ምረቃ ተማሪዎች ምዝገባ የሚካሔደው መስከረም 28 እና 29/2019 ዓ.ም መሆኑን አሳውቋል፡፡ በ2
+1
#DebreTaborUniversity ደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ የሁሉም የተቋሙ ነባር የቅድመ እና የድኅረ-ምረቃ ተማሪዎች ምዝገባ የሚካሔደው መስከረም 28 እና 29/2019 ዓ.ም መሆኑን አሳውቋል፡፡ በ2019 ዓ.ም ደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ አዲስ ገቢ የአንደኛ ዓመት (Freshman) እና የሪሚዲያል ተማሪዎች እንዲሁም በ2018 ዓ.ም በደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ የሪሚዲያል ፕሮግራም ትምህርታችሁን ስትከታተሉ ቆይታችሁ የማለፊያ ውጤት ያመጣችሁ ተማሪዎች የ2019 ዓ.ም ትምህርት ዘመን ምዝገባ በሌላ ማስታወቂያ ጥሪ የሚደረግ መሆኑን ዩኒቨርሲቲው ገልጿል፡፡ ​📚 Join & Share with friends! Help others learn and grow with @ParoEdu. ​👉 Join @ParoEdu

PARO EDU
45 708
#HUCMHS የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ከስር የተዘረዘሩት ትምህርት መስክ ተማሪዎች የ2019 ዓ.ም የመጀመርያ ሴሚስተር ምዝገባ የሚከናወነው መስከረም 14 እና 15/2019 ዓ.
#HUCMHS የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ከስር የተዘረዘሩት ትምህርት መስክ ተማሪዎች የ2019 ዓ.ም የመጀመርያ ሴሚስተር ምዝገባ የሚከናወነው መስከረም 14 እና 15/2019 ዓ.ም መሆኑን አሳውቋል፡፡ 1. ፋርማሲ ➻ ከ2015-2018 ዓ.ም ባቾች 2. ሕክምና ➻ የ2018 ዓ.ም ባች 3. HO, Health Informatics, Nursing, Psychiatry Nursing, Environmental Health, Midwifery, Optometry, MLS, Anesthesia, and MRT ➻ ከ2016-2018 ዓ.ም የገባችሁ ባቾች በ2015 ዓ.ም የገባችሁና በተራ ቁ. 3 ላይ የተዘረዘሩት ፕሮግራም ተማሪዎች ትምህርት የምትቀጥሉበትን ቀን በቀጣይ የሚያሳውቅ መሆኑን ዩኒቨርሲቲው ገልጿል። ​📚 Join & Share with friends! Help others learn and grow with @ParoEdu. ​👉 Join @ParoEdu

PARO EDU
45 708
በግጭት ምክንያት ከትግራይ ክልል የሚወጡ #መምህራን ካሉ በሌሎች የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች እንዲያስተምሩ ይደረጋል፡፡ - ትምህርት ሚኒስቴር በትግራይ ክልል የሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች የሚያስተምሩ መምህራን
በግጭት ምክንያት ከትግራይ ክልል የሚወጡ #መምህራን ካሉ በሌሎች የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች እንዲያስተምሩ ይደረጋል፡፡ - ትምህርት ሚኒስቴር በትግራይ ክልል የሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች የሚያስተምሩ መምህራን በበጸጥታ ችግር ምክንያት ከክልሉ የሚወጡ ከሆነ በሌሎች የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች እንዲያስተምሩ እንደሚደረግ የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) አረጋግጠዋል። በትግራይ ክልል ይማሩ የነበሩ ተማሪዎች በክልሉ ያለው ወቅታዊ ሁኔታ እስኪስተካከል ድረስ በጊዜያዊነት ከትግራይ ክልል ውጪ ወደሚገኙ ሌሎች የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች እንዲመደቡ የሚደረግ መሆኑን ትምህርት ሚኒስቴር መግለፁ ይታወቃል፡፡ ከ5 ሺህ በላይ ነባር ተማሪዎች የዝውውር ማመልከቻ እንዳስገቡ የገለፀው ሚኒስቴሩ፤ ተማሪዎቹ በጊዚያዊነት የሚመደቡበትን ዩኒቨርሲቲ በቅርቡ አሳውቃለሁ ብሏል፡፡   በተያያዘ ትግራይ ክልል በሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች መቀጠል የሚፈልጉ ነባር እና አዲስ ተማሪዎችን በተመለከተ ከዩኒቨርስቲዎቹ ጋር እየተነጋገረ መሆኑን ሚኒስቴሩ ገልጿል፡፡   ​📚 Join & Share with friends! Help others learn and grow with @ParoEdu

PARO EDU
45 708
#ጥቆማ: በጋዜጠኝነት ሞያ አዲስ ለተመረቃችሁና በሞያው መስራት ለምትፈልጉ የተዘጋጀ ነፃ ስልጠና በአሁን ወቅት ​በሚዲያ ዘርፍ በጋዜጠኝነት፣ በሪፓርተርነት ለመስራት ተወዳዳሪ ለመሆን ከአዲስ ተመራቂዎ
#ጥቆማ: በጋዜጠኝነት ሞያ አዲስ ለተመረቃችሁና በሞያው መስራት ለምትፈልጉ የተዘጋጀ ነፃ ስልጠና በአሁን ወቅት ​በሚዲያ ዘርፍ በጋዜጠኝነት፣ በሪፓርተርነት ለመስራት ተወዳዳሪ ለመሆን ከአዲስ ተመራቂዎች ወይም በቅርብ ከሚመረቁ የመጨረሻ አመት ተማሪዎቾ ምን ይጠበቃል ?በተግባር የተደገፈ የሦስት ሰዓታት የሥልጠና በነጻ ተዘጋጅቷል። ሥልጠናው በነገው ዕለት ቅዳሜ መስከረም 9 ቀን 2019 በመገናኛ ስለሺ ሕንጻ 10ኛ ፎቅ በሚገኘው ዘ third ስፔስ (The Third Space) ሞያው ላይ እየሰሩ ባሉ ባለሞያዎች ይሰጣል። መርሃ-ግብሩ ሙሉ በሙሉ ነፃ ቢሆንም የቦታው መጠን የተወሰነ በመሆኑ ፍላጎት ያላቸው ተሳታፊዎች 👉 https://forms.gle/ph5TSRS9crgHJUMJ9 በሚለው ማስፈንጠሪያ አስቀድመው መመዝገብ ይኖርባቸዋል። #ConceptHub ​📚 Join & Share with friends! Help others learn and grow with @ParoEdu. ​👉 Join @ParoEdu

PARO EDU
45 708
"በቀጣይ ከኛ ምን ዓይነት ትምህርታዊ ወይም ቴክኖሎጅያዊ መረጃዎችን ማየት ትፈልጋላችሁ?"
Anonymous voting

PARO EDU
45 708
የሪሚዲያል ተማሪዎች የውጤት ቅሬታ እና የቀረበው ጥያቄ በ2018 ዓ.ም. የሪሚዲያል (Remedial) ፕሮግራም ተከታትለው የነበሩ ተማሪዎች የፈተና ውጤታቸው ከጥረታቸው ውጪ እጅግ ዝቅተኛ በመሆኑ ለት
የሪሚዲያል ተማሪዎች የውጤት ቅሬታ እና የቀረበው ጥያቄ በ2018 ዓ.ም. የሪሚዲያል (Remedial) ፕሮግራም ተከታትለው የነበሩ ተማሪዎች የፈተና ውጤታቸው ከጥረታቸው ውጪ እጅግ ዝቅተኛ በመሆኑ ለትምህርት ሚኒስቴር የቅሬታ ጥያቄ አቀረቡ። ተማሪዎቹ ያነሷቸው ዋና ዋና ችግሮች የሚከተሉት ናቸው፡- * በጆግራፊ እና ፊዚክስ የታየ ያልተለመደ ዝቅተኛ ውጤት፡ በማህበራዊ ሳይንስ በጆግራፊ እንዲሁም በተፈጥሮ ሳይንስ በፊዚክስ ትምህርቶች የተመዘገበው ውጤት በብዙዎች ዘንድ እጅግ ዝቅተኛ መሆን በሂደቱ ላይ ጥርጣሬ ፈጥሯል። * የኢንተርኔት መቆራረጥ ችግር፡ ፈተናው በሚሰጥበት ወቅት በተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች አጋጥሞ የነበረው የኢንተርኔት መቆራረጥ ተማሪዎቹ በተረጋጋ ሁኔታ እንዳይፈተኑ አድርጓል። * በሦስት ዙሮች (Seasons) መሰጠት፡ ፈተናው በሦስት ዙር መሰጠቱ በውጤት አሰጣጥ ላይ የውጤት መደባለቅ (Data mismatch) እንዲፈጠር ምክንያት ሆኗል ተብሎ ተሰግቷል። * የ "Disqualified" ሁኔታ፡ አብዛኛዎቹ ተማሪዎች መጀመሪያ "Disqualified" ተብለው ቆይተው፣ ውጤታቸው ሲስተካከል እጅግ ዝቅተኛ ሆኖ መገኘቱ በሲስተሙ ላይ ክፍተት እንዳለ ያሳያል ብለዋል። የተማሪዎቹ ዋና ዋና ጥያቄዎች፡ * የፈተና አሰጣጥ ሲስተም፣ የሦስቱ ዙሮች መረጃ እና የእርማት ሂደቱ በጥብቅ እንዲጣራ። * በተለይ በፊዚክስ እና ጆግራፊ የታዩ ዝቅተኛ ውጤቶች ከ100 በላይ እንዳይቀየሩ ተደርጎ እንዲመረመር። * በፈተናው ውስጥ ትክክለኛ ያልሆኑ ጥያቄዎች ካሉ ታሳቢ ተደርገው ውጤታቸው እንዲስተካከል ጠይቀዋል። @ParoEdu