ar
Feedback
MINSTERY OF EDUCATION ©

MINSTERY OF EDUCATION ©

الذهاب إلى القناة على Telegram

For more information! It’s all about education Official minstry of education telegram channel join and get more info About us ✅የተረጋገጠ የትምህርት ደረጃ Ad:https://telega.io/c/minsterofeducation

إظهار المزيد

📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام MINSTERY OF EDUCATION ©

تُعد قناة MINSTERY OF EDUCATION © (@minster_of_education) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 47 105 مشتركاً، محتلاً المرتبة 3 720 في فئة التعليم والمرتبة 708 في منطقة Ethiopia.

📊 مؤشرات الجمهور والحراك

منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 47 105 مشتركاً.

بحسب آخر البيانات بتاريخ 27 أغسطس, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار 2 134، وفي آخر 24 ساعة بمقدار 28، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.

  • حالة التحقق: غير موثّقة
  • معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 11.05‎%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 7.58‎% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
  • وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 5 203 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 3 568 مشاهدة.
  • التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 7.

📝 الوصف وسياسة المحتوى

يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
For more information! It’s all about education Official minstry of education telegram channel join and get more info About us ✅የተረጋገጠ የትምህርት ደረጃ Ad:https://telega.io/c/minsterofeducation

بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 28 أغسطس, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة التعليم.

47 105
المشتركون
+2824 ساعات
+1 3287 أيام
+2 13430 أيام
أرشيف المشاركات
#ጥቆማ የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ በስሩ በሚገኙ የኢንጂነሪንግ፣ የጤና እና የቢዝነስና ማኅበራዊ ጥናት ኮሌጆች በ2019 የትምህርት ዘመን በመጀመሪያ እና በ2ኛ ዲግሪ ፕሮግራሞች ተማሪዎችን ተቀብ
#ጥቆማ የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ በስሩ በሚገኙ የኢንጂነሪንግ፣ የጤና እና የቢዝነስና ማኅበራዊ ጥናት ኮሌጆች በ2019 የትምህርት ዘመን በመጀመሪያ እና በ2ኛ ዲግሪ ፕሮግራሞች ተማሪዎችን ተቀብሎ በመደበኛው መርሐግብር #በክፍያ ለማስተማር ይፈልጋል። የመግቢያ መስፈርቶች፦ ለመጀመሪያ ዲግሪ አመልካቾች ➻ የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና ከ2016-2018 ዓ.ም. የወሰደ/የወሰደች ➻ ለየዓመቱ የተቀመጠውን የከፍተኛ ትምህርት መግቢያ ነጥብ የሚያሟላ/የምታሟላ ➻ የሪሚዲያል ተፈታኞች ለዓመቱ የተቀመጠውን የከፍተኛ ትምህርት መግቢያ ነጥብ የሚያሟላ/የምታሟላ ➻ በቴክኒክና ሙያ ላጠናቀቁ (የደረጃ 4 የብቃት ማረጋገጫ እና የ2 ዓመት የሥራ ልምድ) ለሁለተኛ ዲግሪ አመልካቾች ➻ የሀገር አቀፍ የ2ኛ ዲግሪ ፕሮግራም መግቢያ (NGAT) ፈተና ያለፈ/ያለፈች ➻ የመጀመሪያ ዲግሪ የተማረ/ችበትን ኦፊሻል ትራንስክሪፕት ማቅረብ የሚችል/የምትችል የምዝገባ ጊዜ እስከ ነሐሴ 29/2018 ዓ.ም (በሥራ ቀናት ጠዋት ከ3፡00–6፡00 እና ከሰዓት ከ8፡00–10፡00) የምዝገባ ቦታ ቢሾፍቱ በሚገኘው የኢትዮጵያ መከለከያ ዩኒቨርሲቲ ዋና መ/ቤት፣ ሬጅስትራርና ምሩቃን ጉዳይ ጽ/ቤት፣ በኢንጂነሪንግ ኮሌጅ ግቢ ውስጥ ተጨማሪ መረጃ ቢያስፈልግዎ በኢሜል አድራሻ registrar@etdu.edu.et መጠየቅ ይችላሉ።

በምስራቅ ጎህ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የሳይንስ ልህቀት ማዕከል ለመማር የተመዘገባችሁና ፈተና የወሰዳችሁ ተማሪዎች ከዛሬ ነሐሴ 22/2018 ዓ.ም ጀምሮ በተመዘገባችሁበት ሊንክ እየገባችሁ ውጤታችሁን
በምስራቅ ጎህ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የሳይንስ ልህቀት ማዕከል ለመማር የተመዘገባችሁና ፈተና የወሰዳችሁ ተማሪዎች ከዛሬ ነሐሴ 22/2018 ዓ.ም ጀምሮ በተመዘገባችሁበት ሊንክ እየገባችሁ ውጤታችሁን ማየት የምትችሉ መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ አሳውቋል። የተመረጣችሁ ተማሪዎች የፊታችን ረቡዕ ነሐሴ 27/2018 ዓ.ም በምስራቅ ጎህ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የሳይንስ ልህቀት ማዕከል በመገኘት እንድትመዘገቡ ተብሏል።

የመጀመሪያ ዓመት ተማሪዎችን አስቀድሞ ከተመደቡበት ዩኒቨርሲቲ ማዛወር፣ ተቀብሎ ማስተማር በጥብቅ የተከለከለ ነው፡፡ - ትምህርት ሚኒስቴር በትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) በቀን 06/11/2
+1
የመጀመሪያ ዓመት ተማሪዎችን አስቀድሞ ከተመደቡበት ዩኒቨርሲቲ ማዛወር፣ ተቀብሎ ማስተማር በጥብቅ የተከለከለ ነው፡፡ - ትምህርት ሚኒስቴር በትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) በቀን 06/11/2018 ዓ.ም ተፈርሞ ለሁሉም የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች የተላከ ሰርኩላር፤ የ2ኛ ደረጃ ትምህርት ማጠቃለያ ፈተና ተፈትነው የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ውጤት ያመጡ ተማሪዎች በሚኒስቴር መ/ቤቱ በመደበኛ እና በሪሚዲያል ፕሮግራም ለዩኒቨርሲቲዎች የሚመደብ መሆኑን አስታውሷል፡፡ ይሁን እንጂ በሚኒስቴር መ/ቤቱ የተመደቡ ተማሪዎች በየተመደቡበት ዩኒቨርሲቲ እየተማሩ ያሉ መሆናቸውን ለማረጋገጥ በተደረገ ጥናት፣ ከሚኒስቴር መ/ቤቱ ዕውቅና ውጪ ዩኒቨርሲቲዎች ባልተሰጣቸው ስልጣንና አግባብነት በሌለው ሁኔታ ተማሪዎችን ከተመደቡበት ውጭ የመቀያየር ሥራ እነደሚሠሩ አረጋግጧል፡፡ ይህም ህብረ-ብሄራዊነትን የሚጉዳና የእኩልነት መብትንና ፍትሃዊ አሠራርን የሚፃረር ሆኖ እንደተገኘ ሚኒስቴሩ ገልጿል፡፡ በመሆኑም በትምህርት ሚኒስቴር ምደባ የተሰጣቸውን የመጀመሪያ ዓመት ተማሪዎች ከሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ዕውቅና ውጪ በምንም አይነት ሁኔታ አስቀድሞ ከተመደቡበት ማዛወርም ሆነ በማንኛውም ሁኔታ ተቀብሎ ማስተማር በጥብቅ የተከለከለ መሆኑን አሳስቧል፡፡ ይህን ውሳኔ ጥሶ የተገኘ የዩኒቨርሲቲ አመራር ተጠያቂ እንደሚሆኑም ሚኒሰቴሩ አስገንዝቧል፡፡

ጅማ ዩኒቨርሲቲ ከሰላም ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ሲያሰለጥናቸው የነበሩ ከአንድ ሺህ በላይ ወጣቶችን አስመርቋል። የብሔራዊ የሰላም በጎ ፈቃድ አገልግሎት ሰልጣኝ ወጣቶቹ በሕይወት ክህሎት፣ በብቁ ዜጋ
ጅማ ዩኒቨርሲቲ ከሰላም ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ሲያሰለጥናቸው የነበሩ ከአንድ ሺህ በላይ ወጣቶችን አስመርቋል። የብሔራዊ የሰላም በጎ ፈቃድ አገልግሎት ሰልጣኝ ወጣቶቹ በሕይወት ክህሎት፣ በብቁ ዜጋ እና በሀገር ግንባታ ጭብጦች ላይ ስልጠናቸውን ሲከታተሉ ቆይተዋል።

የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የሳይንስ ኢንኩቤሽን ማዕከል በ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ያስፈተናቸው ተማሪዎች በሙሉ (100%) ማለፋቸውን ገልጿል። ብቃት ተኮር የተማሪዎች ቅበላ፣ ተማሪ ተኮ
የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የሳይንስ ኢንኩቤሽን ማዕከል በ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ያስፈተናቸው ተማሪዎች በሙሉ (100%) ማለፋቸውን ገልጿል። ብቃት ተኮር የተማሪዎች ቅበላ፣ ተማሪ ተኮር የማስተማር ስልት እና ጠንካራ የምዘና ስርዓት መተግበሩ ማዕከሉ በተከታታይ ዓመታት ያስፈተናቸውን የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ሙሉ በሙሉ እንዲያልፉ እንዳስቻለው የማዕከሉ ዳይሬክተር ዓለሙ ተስፋዬ (ዶ/ር) ለአሚኮ ዲጂታል ተናግረዋል። የማዕከሉ የተማሪዎች ቅበላ አቅምን ለማሳደግ ከባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ጋር እየተወያየ እንደሚገኝ ገልፀዋል።

#ሎርካን_ሜዲካል_ኮሌጅ የበርካታ ዓመታት ልምድ ባላቸው ሐኪሞችና ምሁራን ባለቤትነት የሚመራው ሎርካን ሜዲካል ኮሌጅ ምዝገባ ላይ ነው❗️ BSc Fields of Study: → Doctor of Medici
#ሎርካን_ሜዲካል_ኮሌጅ የበርካታ ዓመታት ልምድ ባላቸው ሐኪሞችና ምሁራን ባለቤትነት የሚመራው ሎርካን ሜዲካል ኮሌጅ ምዝገባ ላይ ነው❗️ BSc Fields of Study: → Doctor of Medicine → Doctor of Dental Medicine → Bachelor of Dental Science → Nursing TVET Programs: → Dental Therapy → Nursing → Medical Laboratory → Pharmacy → Radiography ⭐️ CPD ማዕከል አገልግሎት! ☎️ 0913398780 / 0911596059 አድራሻ፦ CMC አደባባይ ከፀሐይ ሪል እስቴት ጀርባ ከ ICMC ጠቅላላ ሆስፒታል አጠገብ 📍 Addis Ababa, CMC Square, Behind Tsehay Real Estate, next to ICMC General Hospital Facebook: https://www.facebook.com/Lorcanmedicalcollege Tiktok: https://www.tiktok.com/@lorcan.medical.co

#KiburCollege ክቡር ኮሌጅ የአፍሪካ የቢዝነስ ስኩል ማኅበር አባል ተቋም ሲሆን ክህሎትን መሠረት ያደረገ ተግባራዊ የትምህርት አሰጣጥን የሚከተል ከፍተኛ የትምህርት ተቋም ነው። ✅ በመጀመሪያ
#KiburCollege ክቡር ኮሌጅ የአፍሪካ የቢዝነስ ስኩል ማኅበር አባል ተቋም ሲሆን ክህሎትን መሠረት ያደረገ ተግባራዊ የትምህርት አሰጣጥን የሚከተል ከፍተኛ የትምህርት ተቋም ነው። ✅ በመጀመሪያ ዲግሪ ✅ ቴክኒክና ሙያ (TVET) ✅ በ Remedial Program ✅ አጫጭር ስልጠናዎች በዳግም ምዝገባ ፍቃድ ባገኘንባቸው የትምህርት ዘርፎች ተማሪዎችን ለመቀበል በምዝገባ ላይ ነን!! Website: https://kibur.net አድራሻ፦ ጀሞ ሚካኤል ከአፍሪካ ህንፃ አጠገብ ☎️ 0113854042 / 0904848586 Telegram: https://t.me/kiburcollege Facebook:  https://www.facebook.com/kiburcollege

#Pioneer_College 🔥 አስደሳች ዜና ከፓዩኒዬር ኮሌጅ የዕውቅና ፈቃድ ያለው ፓዩኒዬር ኮሌጅ፤ ለ2019 ዓ.ም ተማሪዎች ብቻ የሚያገለግል የትምህርት ክፍያ ዋጋ ቅናሽ አድርገናል❗️ ከትምህርት
#Pioneer_College 🔥 አስደሳች ዜና ከፓዩኒዬር ኮሌጅ    የዕውቅና ፈቃድ ያለው ፓዩኒዬር ኮሌጅ፤ ለ2019 ዓ.ም ተማሪዎች ብቻ የሚያገለግል የትምህርት ክፍያ ዋጋ ቅናሽ አድርገናል❗️ ከትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን ዕውቅና ባገኘንባቸው የዲግሪ ፕሮግራሞች፦ ► የሕክምና ዶክትሬት ► የጥርስ ሕክምና ዶክትሬት ► ፋርማሲ ► ሜዴካል ላብራቶሪ ሳይንስ 🔔 ምዝገባ ጀምረናል! በጤናው መስክ ተወዳደሪ ሆኖ ለመገኘት ካሰቡ አሁኑኑ ፓዩኒዬር ኮሌጅ ይመዝገቡ! አድራሻ ከጀርመን አደባባይ ወደ ለቡ መብራት በሚሰደው መንገድ ☎️  0902442244 / 0902443344 www.pioneercollege.edu.et

#MoH ነሐሴ 13/2018 ዓ.ም የተሰጠውን የሙያ ፈቃድ የፅሑፍ ፈተና የወሰዳችሁ የአንስቴዥያ ሙያ ተመዛኞች፣ ውጤታችሁን ከነገ ነሐሴ 22/2018 ዓ.ም ጀምሮ መመልከት የምትችሉ መሆኑን ጤና ሚኒስቴ
#MoH ነሐሴ 13/2018 ዓ.ም የተሰጠውን የሙያ ፈቃድ የፅሑፍ ፈተና የወሰዳችሁ የአንስቴዥያ ሙያ ተመዛኞች፣ ውጤታችሁን ከነገ ነሐሴ 22/2018 ዓ.ም ጀምሮ መመልከት የምትችሉ መሆኑን ጤና ሚኒስቴር አሳውቋል። የፅሑፍ ፈተናውን ያለፋችሁ ተመዛኞች የተግባር ፈተና ለመውሰድ ነሐሴ 23 እና 24/2018 ዓ.ም ብቻ ምዝገባ የሚከናወን መሆኑ ተገልጿል። በመሆኑም በተገለፁት ቀናት https://hple.moh.gov.et/ ላይ በመግባት የብሔራዊ መለያ ቁጥር (FAN) እና Password በማስገባት መፈተኛ ጣቢያ በመምረጥ ምዝገባችሁን እንድታከናውኑ ተብሏል። ስትመዘገቡ በመረጣችሁት የፈተና ጣቢያ ሲስተሙ የሚሰጣችሁን QR Code የያዘ ስሊፕ ይዛችሁ በፈተናው ወቅት እንድትገኙ ሚኒስቴሩ አሳስቧል፡፡ @minster_of_education

የሐዲስ ዓለማየሁ ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት ያስፈተናቸውን የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች በሙሉ (100%) ማሳለፉን ገልጿል። በ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ፈተና ከወሰዱ 37 የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች ውስጥ
የሐዲስ ዓለማየሁ ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት ያስፈተናቸውን የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች በሙሉ (100%) ማሳለፉን ገልጿል። በ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ፈተና ከወሰዱ 37 የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች ውስጥ 28ቱ500 በላይ ውጤት ማስመዝገባቸው ተገልጿል። በትምህርት ቤቱ የተመዘገበው ከፍተኛ ውጤት 569 መሆኑን የትምህርት ቤቱ ርዕሰ መምህር ደረጀ ከፈለኝ ለአሚኮ ተናግረዋል። ትምህርት ቤቱ ላለፉት አራት ተከታታይ ዓመታት ያስፈተናቸውን የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች በሙሉ ማሳለፍ መቻሉን ገልፀዋል። @minster_of_education

የአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ልዩ አዳሪ ያልሆነ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ያስፈተናቸው ተማሪዎች በሙሉ (100%) ማለፋቸውን ገልጿል። በትምህርት
የአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ልዩ አዳሪ ያልሆነ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ያስፈተናቸው ተማሪዎች በሙሉ (100%) ማለፋቸውን ገልጿል። በትምህርት ቤቱ የተመዘገበ ከፍተኛ ውጤት 567 መሆኑ ተገልጿል።   @minster_of_education

በሀገር አቀፍ ደረጃ በሴቶች ከፍተኛ የሆነውን የ12ኛ ክፍል ውጤት (583) ያስመዘገበችው ተማሪ ሕዳሴ ዘመኑ ሽልማት ተበረከተላት። የአዊ ብሔረሰብ አስተዳደር ምክር ቤት ከእንጅባራ ከተማ አስተዳደር
በሀገር አቀፍ ደረጃ በሴቶች ከፍተኛ የሆነውን የ12ኛ ክፍል ውጤት (583) ያስመዘገበችው ተማሪ ሕዳሴ ዘመኑ ሽልማት ተበረከተላት። የአዊ ብሔረሰብ አስተዳደር ምክር ቤት ከእንጅባራ ከተማ አስተዳደር ጋር በመተባበር ባዘጋጀው የዕውቅና መርሐግብር፤ ተማሪ ሕዳሴ ላፕቶፕ እና ዘመናዊ ስልክ ተሸልማለች። ተማሪ ሕዳሴ ዘመኑን ለላቀ ውጤት ያበቁ ወላጆቿ እና የትምህርት ቤቱ ርዕሰ መምህርም ዕውቅና ተሰጥቷቸዋል። የተማረችበት አገው ምድር 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ደግሞ የ100 ሺህ ብር ሽልማት ተበርክቶለታል። @minster_of_education

በደብረ ብርሃን ከተማ የሚገኘው ኃይሌ ማናስ አካዳሚ በ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ያስፈተናቸው ተማሪዎች በሙሉ (100%) ማለፋቸውን ገልጿል። አካዳሚው ዘንድሮ 43 ተማሪዎች የ12ኛ ክ
በደብረ ብርሃን ከተማ የሚገኘው ኃይሌ ማናስ አካዳሚ በ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ያስፈተናቸው ተማሪዎች በሙሉ (100%) ማለፋቸውን ገልጿል። አካዳሚው ዘንድሮ 43 ተማሪዎች የ12ኛ ክፍል ፈተና ያስፈተነ ሲሆን፣ ሁሉም የማለፊያ ውጤት አሳክተዋል። 30 ተማሪዎች ደግሞ ከ500 በላይ ነጥብ አስመዝግበዋል። ተማሪ ናትናኤል ክንደዓለም የአካዳሚውን ከፍተኛ ውጤት 570.25 አስመዝግቧል። ዘንድሮ በአካዳሚው የ12ኛ ክፍል ፈተና ከወሰዱ ተማሪዎች መካከል 38 ተማሪዎች በውጭ አገራት ዩኒቨርሲቲዎች ነጻ የትምህርት ዕድል ማግኘታቸውን የአካዳሚው ምክትል ዳይሬክተር ተስፋዬ ክፍሌ ለአሚኮ ተናግረዋል። @minster_of_education

በትግራይ ክልል የሚገኘው ቓላሚኖ ልዩ አዳሪ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቀቂያ ፈተና ያስፈተናቸው 58 ተማሪዎች በሙሉ ከ500 በላይ ነጥብ በማምጣት ማለፋቸውን ትምህ
በትግራይ ክልል የሚገኘው ቓላሚኖ ልዩ አዳሪ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቀቂያ ፈተና ያስፈተናቸው 58 ተማሪዎች በሙሉ ከ500 በላይ ነጥብ በማምጣት ማለፋቸውን ትምህርት ቤቱ ገልጿል፡፡   46 ተማሪዎች ከ550 በላይ ነጥብ ሲያመጡ፣ 12 ተማሪዎች ደግሞ ከ500-549 ውጤት ማምጣታቸው ታውቋል፡፡   587.92 በትምህርት ቤቱ የተመዘገበ ከፍተኛ ውጤት ሲሆን፣ በሴት ተማሪ የተመዘገበው ከፍተኛ ውጤት ደግሞ 581.33 መሆኑ ተገልጿል፡፡    @minster_of_education

#NGAT ሀገር አቀፍ የድኅረ-ምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (NGAT) ዛሬ ይጠናቀቃል፡፡ ትናንት ነሐሴ 20/2018 ዓ.ም መሠጠት የጀመረው የNGAT ፈተ፤ ዛሬ ጠዋት እየተሰጡ በሚገኙ ፈተናዎች
+3
#NGAT ሀገር አቀፍ የድኅረ-ምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (NGAT) ዛሬ ይጠናቀቃል፡፡ ትናንት ነሐሴ 20/2018 ዓ.ም መሠጠት የጀመረው የNGAT ፈተ፤ ዛሬ ጠዋት እየተሰጡ በሚገኙ ፈተናዎች እንደሚጠናቀቅ ይጠበቃል፡፡ የተወሰኑ ዩኒቨርሲቲዎች ፈተናውን ትናንት ሰጥተው አጠናቀዋል፡፡ ምስል፦ እንጅባራ፣ ዋቸሞ፣ ወራቤ እና ጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲዎች

#UoG የጎንደር ዩኒቨርሲቲ የቅድመ-ምረቃ የሕክምናና ጤና ሳይንስ ነባር ተማሪዎች የ2019 ትምህርት ዘመን የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ቀናት መስከረም 04 እና 05/2019 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው ገልጿ
+1
#UoG የጎንደር ዩኒቨርሲቲ የቅድመ-ምረቃ የሕክምናና ጤና ሳይንስ ነባር ተማሪዎች የ2019 ትምህርት ዘመን የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ቀናት መስከረም 04 እና 05/2019 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው ገልጿል፡፡ ትምህርት መስከረም 06/2019 ዓ.ም የሚጀምር መሆኑ ተገልጿል፡፡

በአዲስ አበባ ከተማ አስተደደር የሚገኙት የእቴጌ መነን የልጃገረዶች መካከለኛና 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት እንዲሁም የገላን የወንዶች መካከለኛና 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ያስፈተኗቸውን የ12ኛ ክፍል ተ
በአዲስ አበባ ከተማ አስተደደር የሚገኙት የእቴጌ መነን የልጃገረዶች መካከለኛና 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት እንዲሁም የገላን የወንዶች መካከለኛና 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ያስፈተኗቸውን የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ሙሉ በሙሉ (100%) ማሳለፍ ችለዋል፡፡ በአዲስ አበባ ከተማ አስተደደር 24 ትምህርት ቤቶች ያስፈተኗቸውን የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ሙሉ በሙሉ (100%) ማሳለፉ በትምህርት ሚኒስቴር መገለፁ ይታወቃል፡፡ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሚገኘው የሱፕር ሆሊ ሴቪየር ትምህርት ቤት ተማሪ የሆነችው ተማሪ መቅደላዊት ሱራፌል በሀገር አቀፍ ደረጃ በማኅበራዊ ሳይንስ መስክ ከሴት ተማሪዎች ከፍተኛውን ውጤት (569.17) አስመዝግባለች፡፡ የከተማ አስተዳደሩ በ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቀቂያ ፈተና ካስፈተናቸው ተማሪዎች መካከል 32.3 በመቶ የሚሆኑትን ማሳለፍ መቻሉ መገለፁ ይታወሳል፡፡ በ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ውጤት ላይ የተገኘውን መሻሻል የበለጠ ለማጠናከር ተግቶ እየሠራ እንደሚገኝ የከተማ አስተዳደሩ ትምህርት ቢሮ ገልጿል፡፡

በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሞዴል ማኅበረሰብ ትምህርት ቤት (AAU-MCS) በ2019 ትምህርት ዘመን ልጆቻችሁን ለማስተማር ያመለከታችሁና ተቀባይነት ያገኛችሁ፣ የምዝገባ ጊዜ ከነሐሴ 27-29/2018 ዓ
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሞዴል ማኅበረሰብ ትምህርት ቤት (AAU-MCS) በ2019 ትምህርት ዘመን ልጆቻችሁን ለማስተማር ያመለከታችሁና ተቀባይነት ያገኛችሁ፣ የምዝገባ ጊዜ ከነሐሴ 27-29/2018 ዓ.ም መሆኑን ትምህርት ቤቱ አሳውቋል፡፡ የምዝገባ ቦታ 5 ኪሎ (በቀድሞው የድኅረ ምረቃ/ፋርማሲ ትምህርት ቤት ግቢ) የምዝገባ ክፍያ መጠንና አከፋፈል መረጃ እንዲሁም የተማሪዎች የደንብ ልብስ ናሙና መረጃ ከምዝገባ ቦታ የምታገኙ መሆኑ ተገልጿል፡፡