uz
Feedback
MINSTERY OF EDUCATION ©

MINSTERY OF EDUCATION ©

Kanalga Telegram’da o‘tish

For more information! It’s all about education Official minstry of education telegram channel join and get more info About us ✅የተረጋገጠ የትምህርት ደረጃ ለማግኘት እኛን ይከተሉ!! https://www.youtube.com/@minster_of_education Ad:https://telega.io/c/minsterofeducation

Ko'proq ko'rsatish

📈 Telegram kanali MINSTERY OF EDUCATION © analitikasi

MINSTERY OF EDUCATION © (@minster_of_education) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 43 982 obunachidan iborat bo'lib, Taʼlim toifasida 4 085-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 729-o'rinni egallagan.

📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika

невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 43 982 obunachiga ega bo‘ldi.

07 Iyul, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni 1 172 ga, so‘nggi 24 soatda esa 21 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.

  • Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
  • Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 10.33% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 5.28% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
  • Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 4 544 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 2 322 ta ko‘rish yig‘iladi.
  • Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 7 ta reaksiya keladi.

📝 Tavsif va kontent siyosati

Muallif resursni shaxsiy fikrni ifoda etish maydoni sifatida ta’riflaydi:
For more information! It’s all about education Official minstry of education telegram channel join and get more info About us ✅የተረጋገጠ የትምህርት ደረጃ ለማግኘት እኛን ይከተሉ!! https://www.youtube.com/@minster_of_education Ad:https://telega.io/c/minsterofeduca...

Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 08 Iyul, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Taʼlim toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.

43 982
Obunachilar
+2124 soatlar
+2047 kunlar
+1 17230 kunlar
Postlar arxiv
#ጥቆማ የኢፌዴሪ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት የክረምት አጫጭር ስልጠና ለመስጠት የአመልካቾች ምዝገባ እያደረገ ነው። የስልጠና መስኮች፦ - አዲቲቭ ማኑፋክቸሪንግ (3D Printing) - ማሽ
#ጥቆማ የኢፌዴሪ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት የክረምት አጫጭር ስልጠና ለመስጠት የአመልካቾች ምዝገባ እያደረገ ነው። የስልጠና መስኮች፦ - አዲቲቭ ማኑፋክቸሪንግ (3D Printing) - ማሽን ዲዛይን (SolidWorks & RHINO 8 Design) የ2ኛ ደረጃ ተማሪዎችን ጨምሮ ማንኛውንም በዘርፉ ፍላጎት ያለው የግል ሰልጣኝ መመዝገብ ይችላል ተብሏል። የምዝገባ ጊዜ 👇 ከሐምሌ 01-10/2018 ዓ.ም የምዝገባ አማራጮች፦ በአካል ወይም በኤ-ሜይል epip.et@ftveti.edu.et ስልጠናው ሐምሌ 13/2018 ዓ.ም ይጀምራል። አመልካቾች የዲዛይን ሶፍትዌሮችን በደንብ ማስተናገድ የሚችል የራሳችሁን ላፕቶፕ መያዝ ይጠበቅባችኋል። አድራሻ፦ አዲስ አበባ፣ ወሰን አካባቢ በሚገኘው የቴክኖሎጂና ብየዳ ልህቀት ማዕከል ግቢ ውስጥ ለተጨማሪ መረጃ፦ 0116464455 / 0985112035

ብዙ ጊዜ በኢንተርኔት የሚሰሩ ስራዎች ሲባሉ አብዛኞቹ አያስተማምኑም ወይም አይከፍሉም። ነገር ግን በዚህ ቪዲዮ ላይ ሙሉ በሙሉ እውነተኛ እና በተግባር የሚከፍሉ 3 ምርጥ ድረ-ገጾችን (Websites) ይዤላችሁ መጥቻለሁ! ​📌 በቀን 1 ሰዓት ብቻ የሚጠይቁ ​📌 ያለምንም ቅድመ ክፍያ ወይም ኢንቨስትመንት መጀመር የሚቻሉ ​📌 በስልካችሁ ወይም በኮምፒውተራችሁ መስራት የምትችሏቸው ​አሁኑኑ ቪዲዮውን አይታችሁ መስራት ጀምሩ!👇 🔗 የቪዲዮው ሊንክ: https://youtu.be/1rZZ_d7E1p0?si=0TKETQLawI0ukfOj

የ2018 ዓ.ም 3ኛ ዙር የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ የመልቀቂያ ፈተና በዛሬው ዕለት መሠጠት ጀምሯል። በዚህ ዙር የተፈጥሮ ሳይንስ ተፈታኞች በወረቀት እና በኦንላይን ፈተናቸውን ከዛሬ ሐምሌ 01/201
+5
የ2018 ዓ.ም 3ኛ ዙር የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ የመልቀቂያ ፈተና በዛሬው ዕለት መሠጠት ጀምሯል። በዚህ ዙር የተፈጥሮ ሳይንስ ተፈታኞች በወረቀት እና በኦንላይን ፈተናቸውን ከዛሬ ሐምሌ 01/2018 ዓ.ም ጀምሮ ለሦስት ተከታታይ ቀናት ይወስዳሉ።

#ETA የትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን በትምህርት ማስረጃ ማረጋገጫ እና የአቻ ግመታ መመሪያ 990/2016 አንቀጽ 5 ንኡስ አንቀጽ 5 ላይ ብቻ ሀ፣ ለ እና ሐ ተብሎ ተጨምሮ በተዘጋጀው ማሻሻያ ረቂ
#ETA የትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን በትምህርት ማስረጃ ማረጋገጫ እና የአቻ ግመታ መመሪያ 990/2016 አንቀጽ 5 ንኡስ አንቀጽ 5 ላይ ብቻ ሀ፣ ለ እና ሐ ተብሎ ተጨምሮ በተዘጋጀው ማሻሻያ ረቂቅ ላይ የትምህርት ማኅበረሰቡ እና ባለድርሻ አካላት እስከ ሐምሌ 13/2018 ዓ.ም ከዚህ በታች በተቀመጡት አማራጮች አስተያየታቸውን እንዲሰጡ ጠይቋል። https://forms.gle/ndRhodE2yoHSn2P5A ሊንክን በመጫን አስተያየት መስጫውን ማግኘት ትችላላችሁ፤ አስተያየታችሁን ሞልታችሁ ስትጨርሱ (Submit) የሚለውን በመጫን አስተያየታችሁን መላክ የምትችሉ መሆኑ ተገልጿል። ማሻሻያ የተደረገበትን ረቂቅ አዋጅ በባለሥልጣኑ ድረ-ገፅ www.neta.gov.et ላይ ማግኘት ይቻላል። ለሚኖራችሁ ማንኛውም አስተያየት በባለሥልጣኑ ኢ-ሚይል አድራሻ Info@eta.et ላይ አስተያየታችሁን ሞልታችሁ መላክ ትችላላችሁ ተብሏል። በአካል ቀርባችሁ መረጃዎችንና አስተያየታችሁን መስጠት ለምትፈልጉ የፊት ለፊት የመወያያ መድረክ በቅርቡ እንደሚያዘጋጅ ባለሥልጣኑ ገልጿል።

#MoE ትምህርት ሚኒስቴር በ2019 ዓ.ም በዘጠኝ የፌዴራል ልዩ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የ9ኛ እና የ10ኛ ክፍል ተማሪዎችን በኦንላይን መዝግቦ በማወዳደር ለማስተማር ይፈልጋል። ሚኒስቴሩ
#MoE ትምህርት ሚኒስቴር በ2019 ዓ.ም በዘጠኝ የፌዴራል ልዩ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የ9ኛ እና የ10ኛ ክፍል ተማሪዎችን በኦንላይን መዝግቦ በማወዳደር ለማስተማር ይፈልጋል። ሚኒስቴሩ ለ2019 የትምህርት ዘመን በ2018 ዓ.ም ትምህርት በጀመረባቸው አምስት የፌዴራል ልዩ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች እንዲሁም በአራት አዲስ በሚጀምሩ የፌዴራል ልዩ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የ9ኛ እና 10ኛ ክፍል ተማሪዎችን አወዳድሮ ለማስተማር ይፈልጋል። በመሆኑም በእነዚህ ዘጠኝ የፌዴራል ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤቶች ተመዝግባችሁ ለመማር የምትፈልጉ ተማሪዎች የመግቢያ ፈተና ስለሚኖር ቅድመ ዝግጅት እንድታደርጉ ሚኒስቴሩ አሳስቧል። የምዝገባ ጊዜው በቀጣይ የሚገለፅ መሆኑን ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል።

#AAU #GAT በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሚሰጠውን የድኅረ-ምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (GAT) ለመውሰድ ይመዝገቡ! የ GAT ማመልከቻ ጊዜ የሚያበቃው👇 ነሐሴ 05/2018 ዓ.ም ➫ https
#AAU #GAT   በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሚሰጠውን የድኅረ-ምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (GAT) ለመውሰድ ይመዝገቡ! የ GAT ማመልከቻ ጊዜ የሚያበቃው👇 ነሐሴ 05/2018 ዓ.ም   https://portal.aau.edu.et ይግቡ። 'Online Exams' የሚለውን ይጫኑ። Quick Links ከሚለው ስር 'Apply for GAT' የሚለውን ይጫኑ። 'Test Taker Registration' የሚለውን ቅፅ ይሙሉ። የፓስፖርት መጠን ያለው ፎቶ ያስገቡ። 'Submit' የሚለውን ይጫኑ። ሲስተሙ የሚሰጥዎን የመለያ ቁጥር ይያዙ። ቴሌብር በመጠቀም የምዝገባ ክፍያ ይፈፅሙ። አድሚሽን ቲኬትዎን በማውረድ ፕሪንት ብለው፡፡   የ GAT ፈተና በሁለት ዞሮች እንደሚሰጥ የዩኒቨርሲቲው መርሐግብር ያሳያል👇 ከሐምሌ 20-24/2018 ዓ.ም እና ከነሐሴ 07-08/2018 ዓ.ም

#ጥቆማ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ለ2019 የትምህርት ዘመን የመጀመሪያ ሴሚስተር የድኅረ-ምረቃ ፕሮግራሞች አመልካቾችን በመቀበል ላይ ይገኛል፡፡ ዩኒቨርሲቲው ለ Masters ፕሮግራም በመደበኛ እና በኤ
#ጥቆማ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ለ2019 የትምህርት ዘመን የመጀመሪያ ሴሚስተር የድኅረ-ምረቃ ፕሮግራሞች አመልካቾችን በመቀበል ላይ ይገኛል፡፡   ዩኒቨርሲቲው ለ Masters ፕሮግራም በመደበኛ እና በኤክስቴንሽን መርሐግብሮች እንዲሁም ለ PhD ፕሮግራም በመደበኛ እና በኤክስቴንሽን መርሐግብሮች አመልካቾችን ይቀበላል፡፡ የድኅረ-ምረቃ ፕሮግራሞቹን ዝርዝር በ https://admission.aau.edu.et/GraduatePrograms መመልከት ይችላሉ፡፡ አመልካቾች በቅድሚያ በዩኒቨርሲቲው የሚሰጠውን የድኅረ-ምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (GAT) መውሰድና ማለፍ ይጠበቅባቸዋል፡፡ የ GAT ማመልከቻ ጊዜ የሚያበቃው 👇 ነሐሴ 05/2018 ዓ.ም

👋አዲስ መረጃና ዕውቀት ለምትፈልጉ ሁሉ! በየቀኑ የምንጠቀምበት ቴክኖሎጂ፣ የመስመር ላይ (Online) ስራዎች እና የዩቲዩብ ሚስጥሮች ምን ያህል ይገቧችኋል? ራሳችሁን በዕውቀት ማሳደግና ተጨማሪ ገቢ መፍጠር ትፈልጋላችሁ? እንግዲያውስ Paro Media የተሰኘውን የዩቲዩብ Channel ሰብስክራይብ በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ! በቻናላችን ላይ፦ ✅የኦለይን ስራዎች (Online Work Tips): ከቤትዎ ሳይወጡ በስልክዎ ወይም በኮምፒውተርዎ ብቻ ገቢ የሚያገኙባቸው መንገዶች። ✅ የቴክኖሎጂ መረጃዎች (Tech Info): ወቅታዊ እና ጠቃሚ የቴክኖሎጂ መረጃዎችና መተግበሪያዎች። ✅የዩቲዩብ ስኬት (YouTube Tips): የዩቲዩብ ቻናል እንዴት እንደሚከፈት፣ ተከታይ (Subscribers) እና እይታ (Views) እንዴት በቀላሉ ማሳደግ እንደሚቻል የሚጠቁሙ ድንቅ ምክሮች። 👉 አሁኑኑ ሊንኩን በመንካት ሰብስክራይብ ያድርጉና ይማሩበት: 👇👇👇 https://www.youtube.com/@paro_media ​📢 ማስታወቂያ ማስመዝገብ ለምትፈልጉ፦ @Minofedu ያናግሩን

የትግራይ ክልል መምህራን ማኅበር በትግራይ ክልል የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ መልቀቂያ ፈተና የወረቀት ተፈታኞች የሚሰጥበት ጊዜ በትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ወደ ሐምሌ 22-24/2018 ዓ.ም መ
+1
የትግራይ ክልል መምህራን ማኅበር በትግራይ ክልል የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ መልቀቂያ ፈተና የወረቀት ተፈታኞች የሚሰጥበት ጊዜ በትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ወደ ሐምሌ 22-24/2018 ዓ.ም መራዘሙ ተገቢ አይደለም ሲል ወቅሷል። ማኅበሩ ዛሬ ባወጣው መግለጫ፣ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ቀድሞ ባወጣው መርሐግብር መሠረት የትግራይ ክልል ተማሪዎች ለፈተናው ተዘጋጅተው እንደነበር አስታውሷል። "ለትግራይ ተፈታኝ ተማሪዎች ብቻ መርሐግብሩ እንዲራዘም መደረጉ ተገቢ አይደለም" ያለው ማኅበሩ፤ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ቀድሞ ባወጣው መርሐግብር መሠረት ፈተናው እንዲሰጥ ጠይቋል። (የማኅበሩ መግለጫ ከላይ ተያይዟል።)

የጤና ባለሙያዎች የሙያ ፈቃድ ፈተና በነሐሴ ወር 2018 ዓ.ም ይሰጣል። - ጤና ሚኒስቴር ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በመጀመሪያ ዲግሪ ለተመረቃችሁ የጤና ባለሙያዎች የሙያ ፈቃድ ፈተና በነሐሴ ወር 2
የጤና ባለሙያዎች የሙያ ፈቃድ ፈተና በነሐሴ ወር 2018 ዓ.ም ይሰጣል። - ጤና ሚኒስቴር ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በመጀመሪያ ዲግሪ ለተመረቃችሁ የጤና ባለሙያዎች የሙያ ፈቃድ ፈተና በነሐሴ ወር 2018 ዓ.ም ለመስጠት ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የጤና ሚኒስቴር ገልጿል። በመሆኑም መረጃችሁን ወደ ሲስተም ያላስገባችሁ ነባር እና አዲስ ተመዛኞች ከሰኔ 30 እስከ ሐምሌ 17/2018 ዓ.ም ድረስ ብቻ https://hple.moh.gov.et/ ላይ በመግባት የብሔራዊ መታወቂያ መለያ ቁጥር (FAN 16 Digit) በማስገባት አስፈላጊ መረጃዎችን በማሟላት ለምዝገባ እንድትዘጋጁ ሚኒስቴሩ አሳስቧል፡፡ መረጃ የማስተሳሰር ሂደት እንዳለቀ የፈተና ጣቢያ መረጣ ሂደት እንደሚቀጥል ተገልጿል፡፡ 🔔 በሰኔ 2018 ዓ.ም የመውጫ ፈተና ተፈትናችሁ ያለፉችሁ ተመዛኞች የስም ዝርዝራችሁን በተማራችሁበት ተቋም አማካኝነት ወደ ሲስተም ማስጫን ይጠበቅባችኋል ተብሏል። @minster_of_education

የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ የሁለተኛ ዙር ፈተና እየሠጠ ነው። ሰኔ 26/2018 ዓ.ም መሠጠት የጀመረው የሁለተኛ ዙር የኦንላይን ተፈታኝ የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች ፈተና ነገ ይጠናቀቃል። የሦስተኛ ዙር
+3
የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ የሁለተኛ ዙር ፈተና እየሠጠ ነው። ሰኔ 26/2018 ዓ.ም መሠጠት የጀመረው የሁለተኛ ዙር የኦንላይን ተፈታኝ የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች ፈተና ነገ ይጠናቀቃል። የሦስተኛ ዙር የተፈጥሮ ሳይንስ ተፈታኞች የወረቀት እና የኦንላይን ፈተና ከረቡዕ ሐምሌ 01/2018 ዓ.ም ጀምሮ ለሦስት ተከታታይ ቀናት ይሰጣል። ተፈታኞች ፈተናውን ወደሚወስዱበት ተቋማት መግባት ጀምረዋል።

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ6ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና ካስፈተኑ 768 ትምህርት ቤቶች፥ 543ቱ ተማሪዎቻቸውን ሙሉ በሙሉ ማሳለፋቸው ተገለፀ። የአዲስ አበባ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የ2018
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ6ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና ካስፈተኑ 768 ትምህርት ቤቶች፥ 543ቱ ተማሪዎቻቸውን ሙሉ በሙሉ ማሳለፋቸው ተገለፀ። የአዲስ አበባ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የ2018 ዓ.ም የ6ኛ ክፍል ፈተና ውጤት ይፋ አድርጓል። በከተማ አስተዳደሩ በ2018 ዓ.ም የ6ኛ ክፍል ፈተና ከወሰዱ ተማሪዎች 97.48% የሚሆኑት 50% እና በላይ በማስመዝገብ ወደ 7ኛ ክፍል መዘዋወራቸውን ቢሮው አሳውቋል። በመዲናዋ ፈተናውን ከወሰዱ 84,257 የ6ኛ ክፍል ተማሪዎች መካከል 82,137 ተማሪዎች የማለፊያ ነጥብ ሆኖ የተቆረጠውን 50 በመቶ እና በላይ አስመዝግበዋል። ተማሪዎች ውጤት ለማየት 👇 https://aa6.ministry.et/#/result

በትግራይ ክልል በወረቀት ለመፈተን ለተመዘገቡ 15,325 የ12ኛ ክፍል ተፈታኞች ፈተናው ከሐምሌ 22-24/2018 ዓ.ም እንደሚሰጥ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቋል። ተፈታኞቹ በተገለ
በትግራይ ክልል በወረቀት ለመፈተን ለተመዘገቡ 15,325 የ12ኛ ክፍል ተፈታኞች ፈተናው ከሐምሌ 22-24/2018 ዓ.ም እንደሚሰጥ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቋል። ተፈታኞቹ በተገለፁት ቀናት በመቐለ እና በአክሱም ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ በወረቀት እንደሚፈተኑ አገልግሎቱ ገልጿል። ተፈታኞች ወደተገለፁት ዩኒቨርሲቲዎች ሐምሌ 20/2018 ዓ.ም በመግባት እና ሐምሌ 21/2018 ዓ.ም ላይ ኦሬንቴሽን በመውሰድ መፈተን የሚችሉ መሆኑን አገልግሎቱ አብራርቷል። በተያያዘ በትግራይ ክልል በበይነ መረብ ለመፈተን የተመዘገቡ 14,755 ተፈታኞች በስድስቱ ዙር ከሰኔ 23/2018 ዓ.ም ጀምሮ ፈተናው እየተሰጠ መሆኑ ተመልክቷል።

"ትምህርት ቢሮው የራሱን ፈተና አዘጋጅቶ ላልተፈተኑ ተማሪዎች በአጭር ጊዜ ውስጥ ይሰጣል።" - የትግራይ ክልል ትምህርት ቢሮ "ማንኛውም ክልል የሀገር አቀፍ ፈተና የማውጣት እና የመፈተን ስልጣን የለውም" - የፌዴራል መንግሥት የወረቀት ፈተናውን ከሐምሌ 22-24/2018 ዓ.ም ለመስጠት ታቅዷል። - የፌዴራል መንግሥት "ትምህርት ሚኒስቴር በወረቀት ለሚፈተኑ የትግራይ ተማሪዎች የፈተና ወረቀት አላከም" ያለው የትግራይ ክልል ትምህርት ቢሮ፤ በአጭር ጊዜ ውስጥ የራሱን ፈተና አዘጋጅቶ ላልተፈተኑ ተማሪዎች ፈተናውን እንደሚሰጥ አሳውቋል። ሰኔ 29/2018 ዓ.ም ዩኒቨርሲቲ ገብተው ከሐምሌ 01/2018 ዓ.ም ጀምሮ በወረቀት ሊፈተኑ የነበሩ 15,349 ተማሪዎች ፈተናው ከፌደራል መንግሥት ስላልተላከ ወደ ዩኒቨርሲቲ እንዳይጓዙ መደረጉን የቢሮው ኃላፊ ኪሮስ ጉዕሽ (ዶ/ር) ተናግረዋል። "ፈተናው በአውሮፕላን የሚመጣና በፌዴራል ፖሊስ የሚጠበቅ በመሆኑ፣ ወደ ትግራይ እንዳይላክ የሚያደርግ ምንም ዓይነት ምክንያት የለም" ያሉት ኃላፊው፤ "ውሳኔ ፖለቲካዊ ነው" ሲሉ ገልፀዋል። "የክልል ካቢኔ የፈተና ወረቀቱ በወቅቱ እንዲላክ ለፌዴራል መንግሥት ደብዳቤ አስተላልፏል። እስካሁን አውንታዊ ምላሽ አላገኘም" ብለዋል። በዚህም ትምህርት ቢሮው የራሱን ፈተና አዘጋጅቶ ላልተፈተኑ ተማሪዎች ፈተናውን በአጭር ጊዜ ውስጥ እንደሚሰጥ አመልክተዋል። የትግራይ ክልል ትምህርት ቢሮ "በራሴ ፈተና አዘጋጅቼ እፈትናለሁ" ማለቱን ተከትሎ፣ ስማቸው እንዲጠቀስ ያልፈለጉ የፌዴራል መንግሥት የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ታማኝ የመረጃ ምንጭ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ምላሽ ሰጥተዋል። እኚሁ ምንጭ "ይህን ፈተና የማዘጋጀት ስልጣን የፌዴራል መንግሥት የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ብቻ ነው " ያሉ ሲሆን፤ ማንኛውም ክልል የሀገር አቀፍ ፈተና የማውጣት እና የመፈተን ህጋዊ ስልጣን እንደሌለው ገልፀዋል። የትግራይ ክልል "እራሴ ፈተና አውጥቼ እፈትናለሁ" የሚለው አካሄድ ፍፁም ቅቡልነት የሌለው መሆኑን የገለፁት አመራሩ፤ "እንፈትናለን ብለው ከወሰኑና ፈተናውን ከሰጡ የፈተናው ውጤት ተቀባይነት ስለማይኖረው የተማሪዎችን ቀጣይ የህይወት ጉዞ ነው የሚያበላሹት" ሲሉ አስጠንቅቀዋል። ቀደም ብሎ በትግራይ ክልል በተካሄደው የኦንላይን ፈተና ወቅት የነበረውን ሁኔታ ያነሱት አመራሩ ፤ የፌዴራል ፀጥታ አካላትና ፈታኞች በአግባቡ ስራቸውን እንዳይወጡ ጫና ተደርጎባቸው እንደነበር ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልፀዋል። ለአብነትም ለጸጥታ ማስከበር ስራ የተሰማሩ አካላት እንኳን መሳሪያ እንዳይዙ የማድረግ ጫና እንደነበረባቸው ጠቅሰው፣ በወቅቱ የተማሪዎች ቀጣይ ህይወት ጉዞ እንዳይበላሽ ሲባል ብቻ ትምህርት ሚኒስቴር ፈተናው በጫና ውስጥም ቢሆን ታግሶ እንዲሰጥ ማድረጉን አስታውሰዋል። የአሁኑ የወረቀት ፈተና አግባብ ባለው የፈተና አካሄድና ስርዓት ከሐምሌ 22-24/2018 ዓ.ም ድረስ እንዲሰጥ መታቀዱን እኚሁ አካል ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልፀዋል።

#ጥቆማ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት በ34 አጫጭር የስልጠና ፕሮግራሞች በቅርቡ ስልጠና መስጠት እንደሚጀምር አሳውቋል። ኢንስቲትዩቱ ከደረጃ 6 እስከ ደረጃ 8 (ከመጀመሪያ ዲግሪ እስከ ፒኤችዲ
#ጥቆማ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት በ34 አጫጭር የስልጠና ፕሮግራሞች በቅርቡ ስልጠና መስጠት እንደሚጀምር አሳውቋል። ኢንስቲትዩቱ ከደረጃ 6 እስከ ደረጃ 8 (ከመጀመሪያ ዲግሪ እስከ ፒኤችዲ) እያሰለጠነ ሲሆን፤ የገበያ ፍላጎት በማጥናት በ34 የስልጠና ዘርፎች አጫጭር ስልጠናዎች በቅርቡ መስጠት እንደሚጀምር ገልጿል። @minster_of_education

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ2018 ዓ.ም የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ከተማ አቀፍ ፈተና ውጤት ነገ ይፋ እንደሚደረግ የከተማ አስተዳደሩ ትምህርት ቢሮ ገልጿል። በመዲናዋ የ6ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተ
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ2018 ዓ.ም የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ከተማ አቀፍ ፈተና ውጤት ነገ ይፋ እንደሚደረግ የከተማ አስተዳደሩ ትምህርት ቢሮ ገልጿል። በመዲናዋ የ6ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና ከሰኔ 8 -10/2018 ዓ.ም በ199 የመፈተኛ ጣቢያዎች ለሦስት ቀናት መሰጠቱ ይታወሳል፡፡ @minster_of_education

ብርቱዎቹ የ12ኛ ክፍል ተፈታኝ እናቶች እንዚህ እናቶች የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ለመፈተን ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ የተገኙ ተማሪዎች ናቸው፡፡ የእናትነት ኃላፊነትን እየተወጡ በተመሳሳይ ጊዜ የ
+1
ብርቱዎቹ የ12ኛ ክፍል ተፈታኝ እናቶች እንዚህ እናቶች የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ለመፈተን ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ የተገኙ ተማሪዎች ናቸው፡፡ የእናትነት ኃላፊነትን እየተወጡ በተመሳሳይ ጊዜ የትምህርት ህልማቸውን ለማሳካት ያሳዩት ጥንካሬና ትጋት ከፍተኛ አድናቆት የሚቸረው ነው። 👏👏

👋አዲስ መረጃና ዕውቀት ለምትፈልጉ ሁሉ! በየቀኑ የምንጠቀምበት ቴክኖሎጂ፣ የመስመር ላይ (Online) ስራዎች እና የዩቲዩብ ሚስጥሮች ምን ያህል ይገቧችኋል? ራሳችሁን በዕውቀት ማሳደግና ተጨማሪ ገቢ መፍጠር ትፈልጋላችሁ? እንግዲያውስ Paro Media የተሰኘውን የዩቲዩብ Channel ሰብስክራይብ በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ! በቻናላችን ላይ፦ ✅የኦለይን ስራዎች (Online Work Tips): ከቤትዎ ሳይወጡ በስልክዎ ወይም በኮምፒውተርዎ ብቻ ገቢ የሚያገኙባቸው መንገዶች። ✅ የቴክኖሎጂ መረጃዎች (Tech Info): ወቅታዊ እና ጠቃሚ የቴክኖሎጂ መረጃዎችና መተግበሪያዎች። ✅የዩቲዩብ ስኬት (YouTube Tips): የዩቲዩብ ቻናል እንዴት እንደሚከፈት፣ ተከታይ (Subscribers) እና እይታ (Views) እንዴት በቀላሉ ማሳደግ እንደሚቻል የሚጠቁሙ ድንቅ ምክሮች። 👉 አሁኑኑ ሊንኩን በመንካት ሰብስክራይብ ያድርጉና ይማሩበት: 👇👇👇 https://www.youtube.com/@paro_media ​📢 ማስታወቂያ ማስመዝገብ ለምትፈልጉ፦ @Minofedu ያናግሩን

#AAEB የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የ2019 ትምህርት ዘመን ዓመታዊ የጊዜ ሰሌዳ ለሁሉም ክ/ከተሞች ትምህርት ጽ/ቤቶች እና በከተማ አስተዳደር ስር ለሚገኙ ሦስት አዳሪ ትምህርት
+5
#AAEB የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የ2019 ትምህርት ዘመን ዓመታዊ የጊዜ ሰሌዳ ለሁሉም ክ/ከተሞች ትምህርት ጽ/ቤቶች እና በከተማ አስተዳደር ስር ለሚገኙ ሦስት አዳሪ ትምህርት ቤቶች ልኳል። በዚህም፦ ከሐምሌ 19 እስከ ነሐሴ 22/2018 ዓ.ም የነባር እና አዲስ ተማሪዎች ምዝገባ ይከናወናል። ከነሐሴ 26 እስከ ጳጉሜን 5/2018 ዓ.ም የአዲስ ገቢ የ7ኛ እና የ9ኛ ክፍል ተማሪዎች ምዝገባ ይከናወናል። መስከረም 05/2019 ዓ.ም የመጀመሪያ ቀን የመጀመሪያ መደበኛ ትምህርት ክፍለ ጊዜ ይጀመራል። (የከተማ አስተዳደሩ ትምህርት ቢሮ ለሁሉም ክ/ከተሞች ትምህርት ጽ/ቤቶች እና በከተማ አስተዳደር ስር ለሚገኙ ሦስት አዳሪ ት/ቤቶች የላከው ሙሉ የ2019 ዓ.ም የትምህርት ካሌንደር ከላይ ተያይዟል።)

#SamaraUniversity ሠመራ ዩኒቨርሲቲ 'የአፋር ጥናት ኢንስቲትዩት' / Institute of Afar Studies ሊያቋቁም ነው። የሚቋቋመው ኢንስቲትዩት በአሊ አሪፍ ቡርሃን ስም የሚሰየም መሆ
#SamaraUniversity ሠመራ ዩኒቨርሲቲ 'የአፋር ጥናት ኢንስቲትዩት' / Institute of Afar Studies ሊያቋቁም ነው። የሚቋቋመው ኢንስቲትዩት በአሊ አሪፍ ቡርሃን ስም የሚሰየም መሆኑንም የዩኒቨርሲቲው ሴኔት ወስኗል። በሌላ በኩል የዩኒቨርሲቲው ሴኔት በፓሊዎአንትሮፖሎጂ የትምህርት መስክ የሁለተኛ ዲግሪ ፕሮግራም (MA in Paleoanthropology) እንዲከፈቱ አፅድቋል፡፡ @minster_of_education