MINSTERY OF EDUCATION ©
📚 ትክክለኛና ፈጣን የትምህርት መረጃዎች፣ የፈተና ውጤቶችና ወቅታዊ ዜናዎች የሚያገኙበት ቻናል! 📩 ለማስታወቂያ እና ለፕሮሞሽን (For Promotion/Ads)፦ 👉 @Minofedu 🌐 በTelega.io ለማዘዝ፦ https://telega.io/c/minsterofeducation
Show more📈 Analytical overview of Telegram channel MINSTERY OF EDUCATION ©
Channel MINSTERY OF EDUCATION © (@minster_of_education) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 47 157 subscribers, ranking 3 725 in the Education category and 718 in the Ethiopia region.
📊 Audience metrics and dynamics
Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 47 157 subscribers.
According to the latest data from 06 September, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 1 451 over the last 30 days and by -7 over the last 24 hours, overall reach remains high.
- Verification status: Not verified
- Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 14.00%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 7.38% reactions from the total number of subscribers.
- Post reach: On average, each post receives 6 602 views. Within the first day, a publication typically gains 3 481 views.
- Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 11.
📝 Description and content policy
The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
“📚 ትክክለኛና ፈጣን የትምህርት መረጃዎች፣ የፈተና ውጤቶችና ወቅታዊ ዜናዎች የሚያገኙበት ቻናል!
📩 ለማስታወቂያ እና ለፕሮሞሽን (For Promotion/Ads)፦
👉 @Minofedu
🌐 በTelega.io ለማዘዝ፦ https://telega.io/c/minsterofeducation”
Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 07 September, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Education category.
Data loading in progress...
| Date | Subscriber Growth | Mentions | Channels | |
| 06 September | +10 | |||
| 05 September | +24 | |||
| 04 September | +18 | |||
| 03 September | +1 | |||
| 02 September | +28 | |||
| 01 September | +25 |
| 2 | https://t.me/EasyGift67bot?start=_tgr_IlcqeOI2YzQ0 | 177 |
| 3 | 🎁በፓሮ ሚዲያ የቴሌግራም ቻናል ላይ የሚደረግ የሞባይል ካርድ ጊቭአዌ (Giveaway) ሽልማት። ነገ ምሽት 2:00 ሰዓት።
🎁የአሳታፊነት መስፈርቶች፡
✔️የቴሌግራም ቻናሉን (@Paro_Media) አባል መሆን (Join ማድረግ)።
✔️መልእክቱን ለሌሎች ሰዎች ማጋራት (Share ማድረግ)።
👇👇👇
https://t.me/Paro_media
https://t.me/Paro_media | 231 |
| 4 | የኤሌክትሪክ (መብራት) ኃይልን ለመጀመሪያ ጊዜ የፈጠረው/ያገኘው ሰው ማን ይባላል?
መልስዎን ከታች ባሉት ኢሞጂዎች ብቻ ይምረጡ፡
❤️ ቶማስ ኤዲሰን (Thomas Edison)
👍 ቤንጃሚን ፍራንክሊን (Benjamin Franklin)
🔥 ኒኮላ ቴስላ (Nikola Tesla)
👏 አልበርት አንስታይን (Albert Einstein) | 3 403 |
| 5 | #ተጨማሪ
ጳጉሜን 02 እና 03/2018 ዓ.ም የሚሰጠውን የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የቅድመ-ምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (UAT) ለመውሰድ የመፈተኛ ማዕከላችሁን አምቦ ዩኒቨርሲቲ የመረጣችሁ ፈተናው የሚሰጥበት ማዕከል በሀጫሉ ሁንዴሳ ካምፓስ መሆኑ ተገልጿል።
በተመሳሳይ ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲን በፈተና ማዕከልነት የመረጣችሁ፣ ፈተናው በፖሊ ካምፓስ የሚሰጥ መሆኑ ተመላክቷል።
@minster_of_education | 3 215 |
| 6 | https://youtu.be/rNqQgwZHZhE?si=2RmMCC3uSj6wc0XM | 3 557 |
| 7 | #AAU #UAT
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በ2019 ዓ.ም በመደበኛ መርሐግብር የቅድመ-ምረቃ ትምህርት ለመከታተል ላመለከታችሁ የቅድመ-ምረቃ የመግቢያ ፈተና (UAT) ጳጉሜን 02 እና 03/2018 ዓ.ም ይሰጣል።
ፈተናው በተጠቀሱት ቀናት በሦስት ፈረቃ ማለትም ፈረቃ 1: ጠዋት ከ2:30-5:00 ፈረቃ 2: ረፋድ ከ5:30-8:00 ፈረቃ 3: ከሰዓት ከ8:30-11:00 የሚሰጥ መሆኑ ተገልጿል።
መርሐግብሩን እዚህ በጥንቃቄ ይመልከቱ። የመፈተኛ ማዕከልዎን የመፈተኛ ሰዓትዎን በደንብ ይመልከቱ።
🔔 ቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሌኒየም ሕክምና ኮሌጅ፣ የኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ እና ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲን ለፈተና ማዕከልነት የመረጣችሁ አመልካቾች ወደ አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ የፈተና ማዕከል የተዘዋወራችሁ መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል።
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲን ለፈተና ማዕከል የመረጡ ማየት የተሳናቸው አመልካቾችች በሙሉ ዋናው ግቢ በሚገኘው የአካል ጉዳተኞች ማዕከል ላብ 1 ማክሰኞ ጳጉሜን 03/2018 ዓ.ም በፈረቃ 3 ፈተናቸውን የሚወስዱ መሆኑ ተገልጿል፡፡
@minster_of_education | 3 082 |
| 8 | የካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ በተለያዩ የጤና ሙያ መስኮች ያሰለጠናቸውን 252 የጤና ባለሙያዎች አስመርቋል።
ተመራቂዎቹ በሕክምና ዶክትሬት፣ በነርሲንግ፣ በሕክምና ላቦራቶሪ ሳይንስ፣ በስፔሻሊቲ፣ በሰብ-ስፔሻሊቲ እና በማኅበረሰበ ጤና ማስተርስ ፕሮግራሞች ትምህርታቸውን ተከታትለው ያጠናቀቁ ናቸው።
ኮሌጁ በዛሬው 9ኛ ዙር የምርቃት ስነ-ስርዓት፣ በነርሲንግ እና በሕክምና ላቦራቶሪ ሳይንስ የመጀመሪያ ዲግሪ ተመራቂዎችን ለመጀመሪያ ጊዜ አስመርቋል።
ኮሌጁ በአኔስቴዢያ እና በክሪቲካል ኬር ሜዲሲን ስፔሻሊቲ እንዲሁም በዩሮጋይኔኮሎጂ ሰብ-ስፔሻሊቲ ለመጀመሪያ ጊዜ ተማራዎችን አስመርቋል።
በሕክምና ዶክትሬት ትምህርት CGPA 3.90 ውጤት ያስመዘገበው ዶ/ር ይርጋለም መሐመድ የወርቅ ሜዳሊያ ተሸላሚ ሆኗል።
ኮሌጁ የቅድመ-ምረቃ የሕክምና ዶክትሬት ስልጠና፣ ስፔሻሊቲ እና ሰብስፔሻሊቲን ጨምሮ በ21 ፕሮግራሞች የሕክምና ትምህርት በመስጠት ላይ ይገኛል።
@minster_of_education | 3 056 |
| 9 | #NGATResult
ነሐሴ 20 እና 21/2018 ዓ.ም የተሰጠው የ2018 ዓ.ም የድኅረ-ምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (NGAT) ውጤት ተለቋል።
ውጤትዎን ለማየት 👇
https://result.ethernet.edu.et
ሊንኩን ከተጫኑ በኋላ 'NGAT Results' ላይ 'View Results' የሚለውን በመጫንና Username በማስገባት ውጤትዎን ይመልከቱ።
@minster_of_education | 3 620 |
| 10 | የሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲዎች የ2019 ዓ.ም ቅበላ የመግቢያ ፈተና ጳጉሜን 04/2018 ዓ.ም እንደሚሰጥ መገለፁ ይታወቃል።
ወደ አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ለመሔድ ከላይ በምስሉ የተገለፁትን አራት የትራንስፖርት አቅጣጫ አማራጭ መንገዶች ይጠቀሙ። | 3 277 |
| 11 | 🔔 የህክምና ትምህርትዎን በሀገር ውስጥ እና በዓለም አቀፍ ተቋማት ዕውቅና ባለው ሚዮንግሰንግ ሜዲካል ኮሌጅ ይማሩ!
► በዘመናዊ መልክ የተደራጀ
► የራሱ የሆነ ምቹ የተማሪዎች መኖሪያ ያለው
► የኮሪያ ሆስፒታል እህት ኩባንያ
15ኛ ዙር የህክምና ትምህርት ምዝገባ ላይ ነን!
🎓 ኮሌጃችን ያስተማራቸውን ተማሪዎች በሙሉ የብቃት ምዘና ፈተና ማሳለፍ ችሏል!
ለማመልከት 👇
https://maps.app.goo.gl/oxRezU99L2DqnngD6
አድራሻ፦
አዲስ አባባ፣ ገርጂ ኮሪያ ሆስፒታል ቅጥር ግቢ ሬጅስትራር ቢሮ
የምዝገባ ጊዜ 👇
እስከ ጳጉሜን 02/2018 ዓ.ም ድረስ። አሁኑኑ ይመዝገቡ!
☎️ 0116395020
ድረ-ገጽ፦ www.mmc-edu.net
Facebook: https://web.facebook.com/MMCmedcollege/
#MyungsungMedicalCollege | 3 003 |
| 12 | 🌻 የአዲስ ዓመት 25% ቅናሽ ከነሐሴ 27/2018 ዓ.ም እስከ መስከረም 21/2019 ዓ.ም🌻
12ኛ ዙር የኢንቴሪየር ዲዛይን (Interior Design) ስልጠና ምዝገባ ላይ ነን!
👉 AutoCAD, Revit, እና 3D Max ሶፍትዌሮችን በአንድ ላይ
👉 በተጨማሪ በተግባር በወርክሾፕ የሚሰጥ
የበለጠ ይጠብቁ ...
💥 ሴጅ ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት 💥
☎️ 0906777799 / 0906777755
አድራሻ፦ ቁ.1: ፒያሣ ቸርችል ጎዳና ኤልያና ሆቴል 2ኛ ፎቅ፣ ቁ.2: መገናኛ ደራርቱ ህንፃ 5ኛ ፎቅ እና ቁ.3: አዳማ ራስ ሆቴል 2ኛ ፎቅ
ለመመዝገብ ድረ-ገጽ 👇 www.sageethiopia.com
Telegram: https://t.me/sagetraininginstitute
Tiktok: https://www.tiktok.com/@sage_training_institute | 2 470 |
| 13 | የሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲዎች የ2019 ዓ.ም ቅበላ የመግቢያ ፈተና ጳጉሜን 04/2018 ዓ.ም ይሰጣል።
በ2019 ዓ.ም በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ እና በአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ በአፕላይድ ሳይንስ እና በኢንጂነሪንግ የትምህርት ዘርፎች የመግቢያ ፈተና ለመፈተን በኦንላይን የተመዘገባችሁ አመልካቾች የመግቢያ ፈተና ጳጉሜን 04/2018 ዓ.ም እንደሚሰጥ ተገልጿል።
በመሆኑም ያመለከታችሁ በሙሉ በመረጣችሁት የፈተና ጣቢያ በአካል በመቅረብ መፈተን የምትችሉ መሆኑን ዩኒቨርሲቲዎቹ አሳውቀዋል።
ተፈታኞች በዕለቱ ከጠዋቱ 1፡00 ሰዓት በመፈተኛ ጣቢያዎች መገኘት ይጠበቅባችኋል። የሞባይል ስልክ እንዲሁም ማንኛውም ኤሌክትሮኒክስ መሳሪያዎችን ይዞ ወደ ፈተና ጣቢያ መግባት የተከለከለ መሆኑ ተገልጿል፡፡
አመልካቾች ለፈተና ስትቀርቡ የ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና ውጤት፣ የአድሚሽን ካርድ እና የምዝገባ ማረጋገጫ ኮፒ መያዝ ይጠበቅባችኋል፡፡
የመግቢያ ፈተናውን የሚያልፉ አመልካቾች በትምህርት ሚኒስቴር በኩል በሚደረገው የዩኒቨርሲቲ ምደባ ውስጥ አይካተቱም፡፡
@minster_of_education | 2 977 |
| 14 | የ Anesthesia ሙያ የመጀመሪያ ዲግሪ ተመራቂዎች የተግባር ፈተና ጳጉሜን 03/2018 ዓ.ም ይሰጣል፡፡
ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በ Anesthesia ሙያ በመጀመሪያ ዲግሪ ተመርቃችሁ በነሐሴ 2018 ዓ.ም የፅሑፍ ፈተና ያለፋችሁና የተግባር ፈተና (OSCE) ለመውሰድ ምዝገባ ያጠናቀቃችሁ፤ ፈተናው ጳጉሜን 03/2018 ዓ.ም እንደሚሰጥ ጤና ሚኒስቴር አሳውቋል፡፡
ተፈታኝ ጳጉሜን 02/2018 ዓ.ም ከሰዓት 8፡00 ሰዓት በመፈተኛ ጣቢያ በመገኘት ስለፈተናው አሰጣጥ ቅድመ ገለጻ መከታተል ይኖርባቸዋል ተብሏል።
ተፈታኞች በፈተናው ዕለት ማንነታቸውን የሚገልፅ ብሔራዊ መታወቂያ መያዝ ይኖርባቸዋል የተባለ ሲሆን፣ ምንም አይነት የኤሌክትሮኒክስ መሳሪያ (ስልክ፣ የእጅ ሰዓት፣ መነጽር (የተረጋገጠ የዕይታ ችግር ከሌለ በስተቀር) ይዞ መግባት አይፈቀድም፡፡
ማንኛውም ተመዛኝ ወደ ፈተና ጣቢያ ሲሔድ ሲስተሙ የሚሰጠውን QR Code ያለው የፈተና መግቢያ ስሊፕ መያዝ ይጠበቅበታል፡፡
(ተመዛኞች የመረጣችሁትን የፈተና ጣቢያ እዚህ ይመልከቱ፡፡)
@minster_of_education | 4 341 |
| 15 | ደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ የሰባት የሪሚዲያል ፕሮግራም ተማሪዎች ውጤታቸው በስህተት Disqualified እንደተባለባቸው በመግለፅ፣ የዩኒቨርሲቲው ሬጅስትራር ጽ/ቤት ለትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ማሳወቁን ገልጿል።
ሰባቱም ተማሪዎች ለአገልግሎቱ ማመልከት ስለሚገባቸው፣ ተማሪዎቹ ቅሬታቸውን እንዲያቀርቡ መረጃው እንዲደርሳቸው ጠይቋል፡፡
ተማሪዎቹ (3 የማኅበራዊ ሳይንስ እና 4 የተፈጥሮ ሳይንስ) ፈተናቸውን በደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ የፈተና ማዕከል የወሰዱ ናቸው።
(ጥር 11, 2022 የተከፈተና 18,853 ተከታዮች ያሉት የደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ ሬጅስትራር የቴሌግራም ገጽ ትናንት ነሐሴ 28/2018 ዓ.ም ያጋራው መረጃ ከላይ ተያይዟል።)
በተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች ፈተናቸውን የወሰዱና ውጤታቸው Disqualified የተባለባቸው እጅግ በርካታ ተማሪዎች ቅሬታቸውን እያቀረቡ ይገኛሉ። በደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ የተገለፀው አይነት መሠል ግድፈት ሊኖር ስለሚችል ዩኒቨርሲቲዎች በድጋሜ የሪሚዲያል ተፈታኞችን ውጤት እንዲያዩ ይጠየቃሉ። | 4 488 |
| 16 | #ጥናት
በሀገር አቀፍ ደረጃ የተካሔደ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የእርካታ ዳሰሳ ጥናት የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በዩኒቨርሲቲው ውስጥ በሚያገኙት አገልግሎት የሚሰማቸው እርካታ ዝቅተኛ መሆኑን አሳየ፡፡
በትምህርት ሚኒስቴር አስተባባሪነት ከተለያዩ ተቋማት በተውጣጡ አጥኚዎች የተሠራው ጥናቱ፤ በ2017 እና በ2018 ዓ.ም በዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ በሚሰጡ አገልግሎቶች መምህራን፣ ተማሪዎች፣ የአስተዳደር ሠራተኞች እና ማህበረሰቡ ምን ያህል ደስተኛ ናቸው የሚለውን ለማወቅ ነው፡፡
በጥናቱ በ2017 ዓ..ም የተሻለ ደረጃ ላይ የነበሩ፣ በ2018 ዝቅ ማለታቸው የታየ ሲሆን፣ በተቃራኒው ባለፈው ዓመት ዝቅተኛ ደረጃ ላይ የነበሩት በዚህ ዓመት መሻሻል ማሳየታቸውን ጥናቱ ጠቁሟል፡፡
በጥናቱ 47ቱም የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች የተካተቱ ሲሆን፣ ከ16 ሺህ በላይ ተማሪዎች፣ ከ16 ሺህ በላይ መምህራን፣ ከ4 ሺህ በላይ የዩኒቨርሲቲ አስተዳደር ሠራተኞች እና 4 ሺህ የሚሆኑ የማኅበረሰብ ክፍሎች (በአጠቃላይ 61,431 ሰዎች) በጥናቱ ውስጥ ተሳታፊ ሆነዋል፡፡
የጥናቱ ዋና ዋና ትኩረቶች
● የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የአገልግሎት እርካታ
● የዩኒቨርሲቲ መምህራን አገልግሎት አሰጣጥ
● በዩኒቨርሲቲዎች የአስተዳደር ሠራተኞች እርካታ
● ዩኒቨርሲቲዎች በአካባቢው ማኅበረሰብ ዘንድ በሚሰጡት አገልግሎት እርካታ
ከ47ቱ ዩኒቨርሲቲዎች በተማሪዎች የአገልግሎት እርካታ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ቀዳሚውን ስፍራ ሲይዝ፣ ኦዳ ቡልቱም እና ወልድያ ዩኒቨርሲቲዎች ተከታዮቹን ደረጃዎች አጊኝተዋል፡፡
በተቃራኒው አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በተማሪዎች አገልግሎት ደስተኛ አለመሆን ቀዳሚ ሲሆን፣ መቐለ እና ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲዎች ተከታዮቹን ደረጃዎች ይዘዋል፡፡
ሸገር ኤፍኤም የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተ/ፕሬዝዳንትን ስለጥናቱ ግኝት የጠየቀ ሲሆን፣ "ለጊዜው መልስ መስጠት እንደማይችሉ" ነግረውታል፡፡
ከ47ቱ ዩኒቨርሲቲዎች መካከል በመምህራን "የተሻለ አገልግሎት ይሰጣል" ተብሎ በጥናቱ በቀዳሚነት የተለየው ኦዳ ቡልቱም ዩኒቨርሲቲ ቀዳሚው ሲሆን፣ ቀብሪደሃር እና ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲዎች ተከታዮቹን ደረጃዎች ይዘዋል፡፡
በእነዚህ ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ የሚያስተምሩ መምህራን ለመምህራን በሚሰጠው አገልግሎት ጥሩ እርካታ እንዳላቸው ጥናቱ ጠቅሷል፡፡
መቐለ ዩኒቨርሲቲ ዝቅተኛ የመምህራን እርካታ ያለበት ዩኒቨርሲቲ መሆኑን ጥናቱ ያሳየ ሲሆን፣ ዋቸሞ እና ሐዋሳ ዩኒቨርሲቲዎች ተከታዮቹን ደረጃዎች ይይዛሉ፡፡
በዩኒቨርሲቲ አስተዳደር ሠራተኞች እርካታ ኦዳ ቡልቱም፣ ቀብሪደሃር እና ሰላሌ ዩኒቨርሲቲዎች ከፍተኛ እርካታ የተመዘገበባቸው ሲሆኑ፤ መቐለ፣ ደብረ ማርቆስ እና መቅደላ አምባ ዩኒቨርሲቲዎች ደግሞ ዝቅተኛ የአስተዳደር ሠራተኞች እርካታ የተጠቀሰባቸው ናቸው፡፡
ሐራማያ፣ ዓዲግራት እና ወልድያ ዩኒቨርሲቲዎች በአካባቢው ማኅበረሰብ ዘንድ በሚሰጡት አገልግሎት ከፍተኛ እርካታ ከተመዘገበባቸው መካከል ሲሆኑ፤ ዲላ፣ ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ እና ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ደግሞ በአካባቢው ማኅበረሰብ ዝቅተኛ የእርካታ ደረጃ ከተመዘገበባቸው መካከል ቀዳሚዎቹ መሆናቸውን ጥናቱ ጠቅሷል፡፡
ተማሪዎች በማደሪያ እና በመመገቢያ ስፍራዎች ላይ ከፍተኛ ቅሬታ እንዳላቸው የሚገልፀው ጥናቱ፤ የዩኒቨርሲቲ መምህራንም በደሞዝና ጥቅማ ጥቅም ደስተኛ እንዳልሆኑ ጥናቱ አመላክቷል፡፡ #ShegerFM | 4 227 |
| 17 | የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የራስ ገዝነት ሽግግር በመጠናቀቁ አዲስ ፕሬዝዳንት ለመሾም የውድድር ማስታወቂያ በቅርቡ ይወጣል፡፡ - ትምህርት ሚኒስቴር
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የራስ ገዝነት ሽግግር ጊዜው በማብቃቱ አዲስ ፕሬዝዳንት ለመሾም የሚያስችለውን የውድድር ማስታወቂያ ለማውጣት የመጨረሻ ዝግጅት ላይ እንደሚገኝ የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ኮራ ጡሽኔ ለሸገር ኤፍኤም ተናግረዋል፡፡
የውድድር ማስታወቂያው በቅርብ ቀናት እንደሚወጣ ሚኒስትር ዴኤታው ገልፀዋል።
ሳሙኤል ክፍሌ (ዶ/ር) ከነሐሴ 24/2015 ዓ.ም ጀምሮ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተጠባባቂ ፕሬዝዳንት በመሆን እያገለገሉ ይገኛሉ፡፡
በሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ ውሳኔ፣ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የመጀመሪያው ራስ ገዝ ዩኒቨርሲቲ የሆነው ሐምሌ 28/ 2015 ዓ.ም እንደነበር አይዘነጋም፡፡
@minster_of_education | 4 365 |
| 18 | በሁለት ሳምንታት ጊዜ ውስጥ ለአስር ዩኒቨርሲቲዎች አዲስ አመራር ለመመደብ የሚያስችል የውድድር ማስታወቂያ ይፋ እንደሚሆን ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል፡፡
የአስሩ ዩኒቨርሲቲዎች አመራር ምደባ ከተጠናቀቀ በኋላ ደግሞ ለ17 ዩኒቨርሲቲዎች አዲስ አመራር ለመመደብ የውድድር ማስታወቂያ እንደሚወጣ የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ኮራ ጡሽኔ ለሸገር ኤፍኤም ተናግረዋል።
ከዚህ በኋላ የዩኒቨርሲቲ አመራሮች የሚመደቡት በውድድር ብቻ መሆኑን የጠቆሙት ሚኒስትር ዴኤታው፤ ውድድሩ ብቃትና ስብዕና ላይ መሰረት ያደረገ ትክክለኛ ውድድር እንደሚሆን ገልፀዋል።
የዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ለመሆን ከዚህ በኋላ ግዴታ ሦስተኛ ዲግሪ የማይጠየቅ ሲሆን፣ ኢንዱስትሪዎችን ጨምሮ በየትኛውም ተቋም የሚገኙ ባለሙያዎች ለኃላፊነቱ መወዳደር ይችላሉ ብለዋል።
@minster_of_education | 3 845 |
| 19 | ትምህርት ሚኒስቴር የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ምደባን ለማዘመን ከቀጣዩ የትምህርት ዘመን ጀምሮ በቴክኖሎጂ የታገዘ አዲስ የአሰራር ስርዓት ሊዘረጋ ነው፡፡
የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) ከመንግሥት ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንቶች ጋር ባደረጉት የምክክር መድረክ እንደገለፁት፣ የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ስብጥር ብዝሃነትን ባካተተ፣ መቻቻልንና ሀገራዊ አንድነትን በሚያጠናክር መልኩ ሊሆን ይገባል።
ከዚሁ ጋር በተያያዘ በዩኒቨርሲቲዎች ከተማሪዎች ምደባና ዝውውር ጋር ተያይዘው የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመፍታት ከቀጣዩ የትምህርት ዘመን ጀምሮ በቴክኖሎጂ የታገዘ አዲስ የአሰራር ስርዓት በትምህርት ሚኒስቴር እንደሚዘረጋ ገልፀዋል።
ከበጀት አጠቃቀም ጋር በተያያዘ ዩኒቨርሲቲዎች የተመደበላቸውን በጀት ለታቀደለት ዓላማ ብቻ በቁጠባና በተጠያቂነት መንፈስ መጠቀም እንዳለባቸው አሳስበዋል።
የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ክንደያ ገብረህይወት (ፕ/ር) በበኩላቸው ዩኒቨርስቲዎቹ በስምምነት ተማሪዎችን ሲያዘዋውሩ ለትምህርት ሚኒስቴር ማሳወቅ እንዳለባቸው አስገንዝበዋል።
@minster_of_education | 3 212 |
| 20 | #ሎርካን_ሜዲካል_ኮሌጅ
የበርካታ ዓመታት ልምድ ባላቸው ሐኪሞችና ምሁራን ባለቤትነት የሚመራው ሎርካን ሜዲካል ኮሌጅ ምዝገባ ላይ ነው❗️
BSc Fields of Study:
→ Doctor of Medicine
→ Doctor of Dental Medicine
→ Bachelor of Dental Science
→ Nursing
TVET Programs:
→ Dental Therapy
→ Nursing
→ Medical Laboratory
→ Pharmacy
→ Radiography
⭐️ የ CPD ማዕከል አገልግሎት!
☎️ 0913398780 / 0911596059
አድራሻ፦
CMC አደባባይ ከፀሐይ ሪል እስቴት ጀርባ ከ ICMC ጠቅላላ ሆስፒታል አጠገብ
📍 Addis Ababa, CMC Square, Behind Tsehay Real Estate, next to ICMC General Hospital
Facebook: https://www.facebook.com/Lorcanmedicalcollege
Tiktok: https://www.tiktok.com/@lorcan.medical.co | 3 737 |
