ch
Feedback
MINSTERY OF EDUCATION ©

MINSTERY OF EDUCATION ©

前往频道在 Telegram

For more information! It’s all about education Official minstry of education telegram channel join and get more info About us ✅የተረጋገጠ የትምህርት ደረጃ Ad:https://telega.io/c/minsterofeducation

显示更多

📈 Telegram 频道 MINSTERY OF EDUCATION © 的分析概览

频道 MINSTERY OF EDUCATION © (@minster_of_education) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 47 093 名订阅者,在 教育 类别中位列第 3 720,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 708

📊 受众指标与增长动态

невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 47 093 名订阅者。

根据 27 八月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 2 134,过去 24 小时变化为 28,整体触达仍然可观。

  • 认证状态: 未认证
  • 互动率 (ER): 平均受众互动率为 11.05%。内容发布后 24 小时内通常能获得 7.58% 的反应,占订阅者总量。
  • 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 5 203 次浏览,首日通常累积 3 568 次浏览。
  • 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 7

📝 描述与内容策略

作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
For more information! It’s all about education Official minstry of education telegram channel join and get more info About us ✅የተረጋገጠ የትምህርት ደረጃ Ad:https://telega.io/c/minsterofeducation

凭借高频更新(最新数据采集于 28 八月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 教育 类别中的关键影响点。

47 093
订阅者
+2824 小时
+1 3287
+2 13430
帖子存档
#Pioneer_College 🔥 አስደሳች ዜና ከፓዩኒዬር ኮሌጅ የዕውቅና ፈቃድ ያለው ፓዩኒዬር ኮሌጅ፤ ለ2019 ዓ.ም ተማሪዎች ብቻ የሚያገለግል የትምህርት ክፍያ ዋጋ ቅናሽ አድርገናል❗️ ከትምህርት
#Pioneer_College 🔥 አስደሳች ዜና ከፓዩኒዬር ኮሌጅ    የዕውቅና ፈቃድ ያለው ፓዩኒዬር ኮሌጅ፤ ለ2019 ዓ.ም ተማሪዎች ብቻ የሚያገለግል የትምህርት ክፍያ ዋጋ ቅናሽ አድርገናል❗️ ከትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን ዕውቅና ባገኘንባቸው የዲግሪ ፕሮግራሞች፦ ► የሕክምና ዶክትሬት ► የጥርስ ሕክምና ዶክትሬት ► ፋርማሲ ► ሜዴካል ላብራቶሪ ሳይንስ 🔔 ምዝገባ ጀምረናል! በጤናው መስክ ተወዳደሪ ሆኖ ለመገኘት ካሰቡ አሁኑኑ ፓዩኒዬር ኮሌጅ ይመዝገቡ! አድራሻ ከጀርመን አደባባይ ወደ ለቡ መብራት በሚሰደው መንገድ ☎️  0902442244 / 0902443344 www.pioneercollege.edu.et

#MoH ነሐሴ 13/2018 ዓ.ም የተሰጠውን የሙያ ፈቃድ የፅሑፍ ፈተና የወሰዳችሁ የአንስቴዥያ ሙያ ተመዛኞች፣ ውጤታችሁን ከነገ ነሐሴ 22/2018 ዓ.ም ጀምሮ መመልከት የምትችሉ መሆኑን ጤና ሚኒስቴ
#MoH ነሐሴ 13/2018 ዓ.ም የተሰጠውን የሙያ ፈቃድ የፅሑፍ ፈተና የወሰዳችሁ የአንስቴዥያ ሙያ ተመዛኞች፣ ውጤታችሁን ከነገ ነሐሴ 22/2018 ዓ.ም ጀምሮ መመልከት የምትችሉ መሆኑን ጤና ሚኒስቴር አሳውቋል። የፅሑፍ ፈተናውን ያለፋችሁ ተመዛኞች የተግባር ፈተና ለመውሰድ ነሐሴ 23 እና 24/2018 ዓ.ም ብቻ ምዝገባ የሚከናወን መሆኑ ተገልጿል። በመሆኑም በተገለፁት ቀናት https://hple.moh.gov.et/ ላይ በመግባት የብሔራዊ መለያ ቁጥር (FAN) እና Password በማስገባት መፈተኛ ጣቢያ በመምረጥ ምዝገባችሁን እንድታከናውኑ ተብሏል። ስትመዘገቡ በመረጣችሁት የፈተና ጣቢያ ሲስተሙ የሚሰጣችሁን QR Code የያዘ ስሊፕ ይዛችሁ በፈተናው ወቅት እንድትገኙ ሚኒስቴሩ አሳስቧል፡፡ @minster_of_education

የሐዲስ ዓለማየሁ ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት ያስፈተናቸውን የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች በሙሉ (100%) ማሳለፉን ገልጿል። በ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ፈተና ከወሰዱ 37 የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች ውስጥ
የሐዲስ ዓለማየሁ ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት ያስፈተናቸውን የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች በሙሉ (100%) ማሳለፉን ገልጿል። በ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ፈተና ከወሰዱ 37 የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች ውስጥ 28ቱ500 በላይ ውጤት ማስመዝገባቸው ተገልጿል። በትምህርት ቤቱ የተመዘገበው ከፍተኛ ውጤት 569 መሆኑን የትምህርት ቤቱ ርዕሰ መምህር ደረጀ ከፈለኝ ለአሚኮ ተናግረዋል። ትምህርት ቤቱ ላለፉት አራት ተከታታይ ዓመታት ያስፈተናቸውን የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች በሙሉ ማሳለፍ መቻሉን ገልፀዋል። @minster_of_education

የአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ልዩ አዳሪ ያልሆነ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ያስፈተናቸው ተማሪዎች በሙሉ (100%) ማለፋቸውን ገልጿል። በትምህርት
የአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ልዩ አዳሪ ያልሆነ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ያስፈተናቸው ተማሪዎች በሙሉ (100%) ማለፋቸውን ገልጿል። በትምህርት ቤቱ የተመዘገበ ከፍተኛ ውጤት 567 መሆኑ ተገልጿል።   @minster_of_education

በሀገር አቀፍ ደረጃ በሴቶች ከፍተኛ የሆነውን የ12ኛ ክፍል ውጤት (583) ያስመዘገበችው ተማሪ ሕዳሴ ዘመኑ ሽልማት ተበረከተላት። የአዊ ብሔረሰብ አስተዳደር ምክር ቤት ከእንጅባራ ከተማ አስተዳደር
በሀገር አቀፍ ደረጃ በሴቶች ከፍተኛ የሆነውን የ12ኛ ክፍል ውጤት (583) ያስመዘገበችው ተማሪ ሕዳሴ ዘመኑ ሽልማት ተበረከተላት። የአዊ ብሔረሰብ አስተዳደር ምክር ቤት ከእንጅባራ ከተማ አስተዳደር ጋር በመተባበር ባዘጋጀው የዕውቅና መርሐግብር፤ ተማሪ ሕዳሴ ላፕቶፕ እና ዘመናዊ ስልክ ተሸልማለች። ተማሪ ሕዳሴ ዘመኑን ለላቀ ውጤት ያበቁ ወላጆቿ እና የትምህርት ቤቱ ርዕሰ መምህርም ዕውቅና ተሰጥቷቸዋል። የተማረችበት አገው ምድር 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ደግሞ የ100 ሺህ ብር ሽልማት ተበርክቶለታል። @minster_of_education

በደብረ ብርሃን ከተማ የሚገኘው ኃይሌ ማናስ አካዳሚ በ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ያስፈተናቸው ተማሪዎች በሙሉ (100%) ማለፋቸውን ገልጿል። አካዳሚው ዘንድሮ 43 ተማሪዎች የ12ኛ ክ
በደብረ ብርሃን ከተማ የሚገኘው ኃይሌ ማናስ አካዳሚ በ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ያስፈተናቸው ተማሪዎች በሙሉ (100%) ማለፋቸውን ገልጿል። አካዳሚው ዘንድሮ 43 ተማሪዎች የ12ኛ ክፍል ፈተና ያስፈተነ ሲሆን፣ ሁሉም የማለፊያ ውጤት አሳክተዋል። 30 ተማሪዎች ደግሞ ከ500 በላይ ነጥብ አስመዝግበዋል። ተማሪ ናትናኤል ክንደዓለም የአካዳሚውን ከፍተኛ ውጤት 570.25 አስመዝግቧል። ዘንድሮ በአካዳሚው የ12ኛ ክፍል ፈተና ከወሰዱ ተማሪዎች መካከል 38 ተማሪዎች በውጭ አገራት ዩኒቨርሲቲዎች ነጻ የትምህርት ዕድል ማግኘታቸውን የአካዳሚው ምክትል ዳይሬክተር ተስፋዬ ክፍሌ ለአሚኮ ተናግረዋል። @minster_of_education

በትግራይ ክልል የሚገኘው ቓላሚኖ ልዩ አዳሪ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቀቂያ ፈተና ያስፈተናቸው 58 ተማሪዎች በሙሉ ከ500 በላይ ነጥብ በማምጣት ማለፋቸውን ትምህ
በትግራይ ክልል የሚገኘው ቓላሚኖ ልዩ አዳሪ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቀቂያ ፈተና ያስፈተናቸው 58 ተማሪዎች በሙሉ ከ500 በላይ ነጥብ በማምጣት ማለፋቸውን ትምህርት ቤቱ ገልጿል፡፡   46 ተማሪዎች ከ550 በላይ ነጥብ ሲያመጡ፣ 12 ተማሪዎች ደግሞ ከ500-549 ውጤት ማምጣታቸው ታውቋል፡፡   587.92 በትምህርት ቤቱ የተመዘገበ ከፍተኛ ውጤት ሲሆን፣ በሴት ተማሪ የተመዘገበው ከፍተኛ ውጤት ደግሞ 581.33 መሆኑ ተገልጿል፡፡    @minster_of_education

#NGAT ሀገር አቀፍ የድኅረ-ምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (NGAT) ዛሬ ይጠናቀቃል፡፡ ትናንት ነሐሴ 20/2018 ዓ.ም መሠጠት የጀመረው የNGAT ፈተ፤ ዛሬ ጠዋት እየተሰጡ በሚገኙ ፈተናዎች
+3
#NGAT ሀገር አቀፍ የድኅረ-ምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (NGAT) ዛሬ ይጠናቀቃል፡፡ ትናንት ነሐሴ 20/2018 ዓ.ም መሠጠት የጀመረው የNGAT ፈተ፤ ዛሬ ጠዋት እየተሰጡ በሚገኙ ፈተናዎች እንደሚጠናቀቅ ይጠበቃል፡፡ የተወሰኑ ዩኒቨርሲቲዎች ፈተናውን ትናንት ሰጥተው አጠናቀዋል፡፡ ምስል፦ እንጅባራ፣ ዋቸሞ፣ ወራቤ እና ጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲዎች

#UoG የጎንደር ዩኒቨርሲቲ የቅድመ-ምረቃ የሕክምናና ጤና ሳይንስ ነባር ተማሪዎች የ2019 ትምህርት ዘመን የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ቀናት መስከረም 04 እና 05/2019 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው ገልጿ
+1
#UoG የጎንደር ዩኒቨርሲቲ የቅድመ-ምረቃ የሕክምናና ጤና ሳይንስ ነባር ተማሪዎች የ2019 ትምህርት ዘመን የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ቀናት መስከረም 04 እና 05/2019 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው ገልጿል፡፡ ትምህርት መስከረም 06/2019 ዓ.ም የሚጀምር መሆኑ ተገልጿል፡፡

በአዲስ አበባ ከተማ አስተደደር የሚገኙት የእቴጌ መነን የልጃገረዶች መካከለኛና 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት እንዲሁም የገላን የወንዶች መካከለኛና 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ያስፈተኗቸውን የ12ኛ ክፍል ተ
በአዲስ አበባ ከተማ አስተደደር የሚገኙት የእቴጌ መነን የልጃገረዶች መካከለኛና 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት እንዲሁም የገላን የወንዶች መካከለኛና 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ያስፈተኗቸውን የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ሙሉ በሙሉ (100%) ማሳለፍ ችለዋል፡፡ በአዲስ አበባ ከተማ አስተደደር 24 ትምህርት ቤቶች ያስፈተኗቸውን የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ሙሉ በሙሉ (100%) ማሳለፉ በትምህርት ሚኒስቴር መገለፁ ይታወቃል፡፡ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሚገኘው የሱፕር ሆሊ ሴቪየር ትምህርት ቤት ተማሪ የሆነችው ተማሪ መቅደላዊት ሱራፌል በሀገር አቀፍ ደረጃ በማኅበራዊ ሳይንስ መስክ ከሴት ተማሪዎች ከፍተኛውን ውጤት (569.17) አስመዝግባለች፡፡ የከተማ አስተዳደሩ በ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቀቂያ ፈተና ካስፈተናቸው ተማሪዎች መካከል 32.3 በመቶ የሚሆኑትን ማሳለፍ መቻሉ መገለፁ ይታወሳል፡፡ በ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ውጤት ላይ የተገኘውን መሻሻል የበለጠ ለማጠናከር ተግቶ እየሠራ እንደሚገኝ የከተማ አስተዳደሩ ትምህርት ቢሮ ገልጿል፡፡

በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሞዴል ማኅበረሰብ ትምህርት ቤት (AAU-MCS) በ2019 ትምህርት ዘመን ልጆቻችሁን ለማስተማር ያመለከታችሁና ተቀባይነት ያገኛችሁ፣ የምዝገባ ጊዜ ከነሐሴ 27-29/2018 ዓ
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሞዴል ማኅበረሰብ ትምህርት ቤት (AAU-MCS) በ2019 ትምህርት ዘመን ልጆቻችሁን ለማስተማር ያመለከታችሁና ተቀባይነት ያገኛችሁ፣ የምዝገባ ጊዜ ከነሐሴ 27-29/2018 ዓ.ም መሆኑን ትምህርት ቤቱ አሳውቋል፡፡ የምዝገባ ቦታ 5 ኪሎ (በቀድሞው የድኅረ ምረቃ/ፋርማሲ ትምህርት ቤት ግቢ) የምዝገባ ክፍያ መጠንና አከፋፈል መረጃ እንዲሁም የተማሪዎች የደንብ ልብስ ናሙና መረጃ ከምዝገባ ቦታ የምታገኙ መሆኑ ተገልጿል፡፡

👋አዲስ መረጃና ዕውቀት ለምትፈልጉ ሁሉ! በየቀኑ የምንጠቀምበት ቴክኖሎጂ፣ የመስመር ላይ (Online) ስራዎች እና የዩቲዩብ ሚስጥሮች ምን ያህል ይገቧችኋል? ራሳችሁን በዕውቀት ማሳደግና ተጨማሪ ገቢ መፍጠር ትፈልጋላችሁ? እንግዲያውስ Paro Media የተሰኘውን የዩቲዩብ Channel ሰብስክራይብ በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ! በቻናላችን ላይ፦ ✅የኦለይን ስራዎች (Online Work Tips): ከቤትዎ ሳይወጡ በስልክዎ ወይም በኮምፒውተርዎ ብቻ ገቢ የሚያገኙባቸው መንገዶች። ✅ የቴክኖሎጂ መረጃዎች (Tech Info): ወቅታዊ እና ጠቃሚ የቴክኖሎጂ መረጃዎችና መተግበሪያዎች። ✅የዩቲዩብ ስኬት (YouTube Tips): የዩቲዩብ ቻናል እንዴት እንደሚከፈት፣ ተከታይ (Subscribers) እና እይታ (Views) እንዴት በቀላሉ ማሳደግ እንደሚቻል የሚጠቁሙ ድንቅ ምክሮች። 👉 አሁኑኑ ሊንኩን በመንካት ሰብስክራይብ ያድርጉና ይማሩበት: 👇👇👇 https://www.youtube.com/@paro_media ​📢 ማስታወቂያ ማስመዝገብ ለምትፈልጉ፦ @Minofedu ያናግሩን

የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ሞዴል 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት እና የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ማኅበረሰብ ትምህርት ቤት የ12ኛ ክፍል ፈተና ያስፈተኗቸው ተማሪዎች ሙሉ በሙሉ (100%) የማለፊያ ነጥብ አስመዝግበዋል።
+1
የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ሞዴል 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት እና የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ማኅበረሰብ ትምህርት ቤት የ12ኛ ክፍል ፈተና ያስፈተኗቸው ተማሪዎች ሙሉ በሙሉ (100%) የማለፊያ ነጥብ አስመዝግበዋል። ከጎንደር ዩኒቨርሲቲ ሞዴል 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪ ረድኤት ሳሙኤል 574.4 እንዲሁም ከጎንደር ዩኒቨርሲቲ ማኅበረሰብ ትምህርት ቤት ተማሪ ናትናኤል ሙላት 570.16 በማምጣት የየትምህርት ቤታቸውን ከፍተኛ ውጤት ማስመዝገባቸውን ዩኒቨርሲቲው ገልጿል። @minster_of_education

የይሁኔ ወልዱ መታሰቢያ ደሴ ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት በ2018 ዓ.ም ካስፈተናቸው 84 የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች፣ 80 ተማሪዎች ከ500 በላይ ውጤት ሲያስመዘግቡ፤ ሦስት ተማሪዎች ከ450 እስከ 499
+1
የይሁኔ ወልዱ መታሰቢያ ደሴ ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት በ2018 ዓ.ም ካስፈተናቸው 84 የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች፣ 80 ተማሪዎች ከ500 በላይ ውጤት ሲያስመዘግቡ፤ ሦስት ተማሪዎች ከ450 እስከ 499 ውጤት አስመዝግበዋል። በትምህርት ቤቱ በወንዶች 587.17 ከፍተኛ ውጤት ሆኖ መመዝገቡን የትምህርት ቤቱ ርዕሰ መምህር ሳሊም አህመድ ለአሚኮ ተናግረዋል። @minster_of_education

በ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና የወሰዱ የመቐለ ዩኒቨርሲቲ ሳይንስ ሼርድ ካምፓስ ተማሪዎች በሙሉ (100%) የማለፊያ ነጥብ ማምጣታቸውን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል፡፡ ተማሪ ሰምሃል መሃሪ
በ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና የወሰዱ የመቐለ ዩኒቨርሲቲ ሳይንስ ሼርድ ካምፓስ ተማሪዎች በሙሉ (100%) የማለፊያ ነጥብ ማምጣታቸውን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል፡፡ ተማሪ ሰምሃል መሃሪ የትምህርት ቤቱን ከፍተኛ ውጤት 550.76 ማስመዝገቧ ተገልጿል፡፡ @minster_of_education

በደምቢ ዶሎ ዩኒቨርሲቲ የነጋሶ ጊዳዳ ልዩ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ያስፈተናቸው ሁሉም ተማሪዎች የማለፊያ ነጥብ ማምጣታቸውን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል፡፡
በደምቢ ዶሎ ዩኒቨርሲቲ የነጋሶ ጊዳዳ ልዩ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ያስፈተናቸው ሁሉም ተማሪዎች የማለፊያ ነጥብ ማምጣታቸውን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል፡፡ ትምህርት ቤቱ ለሦስተኛ ተከታታይ ዓመት ያስፈተናቸው ተማሪዎች በሙሉ (100%) ማለፊያ ውጤት ማምጣታቸው ተገልጿል፡፡ @minster_of_education

የዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ STEM ማዕከል በ2018 ዓ.ም ያስፈተናቸው የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች በሙሉ (100%) ማለፋቸውን ዩኒቨርሲቲው ገልጿል። በአገር አቀፍ ደረጃ ያስፈተኗቸውን ተማሪዎች ሙሉ በሙሉ (
የዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ STEM ማዕከል በ2018 ዓ.ም ያስፈተናቸው የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች በሙሉ (100%) ማለፋቸውን ዩኒቨርሲቲው ገልጿል። በአገር አቀፍ ደረጃ ያስፈተኗቸውን ተማሪዎች ሙሉ በሙሉ (100%) ካሳለፉ 88 ትምህርት ቤቶች መካከል፣ አራት ትምህርት ቤቶች በትግራይ ክልል የሚገኙ መሆናቸውን ትምህርት ሚኒስቴር መግለፁ ይታወቃል።

የጋሞ ባይራ አዳሪ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በ2018 ዓ.ም ያስፈተናቸውን የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች በሙሉ (100%) አሳልፏል። በ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ መልቀቂያ ፈተና የተፈተኑ 17
የጋሞ ባይራ አዳሪ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በ2018 ዓ.ም ያስፈተናቸውን የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች በሙሉ (100%) አሳልፏል። በ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ መልቀቂያ ፈተና የተፈተኑ 172 ተማሪዎቹ በሙሉ (100%) ማለፋቸውን የትምህርት ቤቱ አስተዳደር አሳውቋል።