fa
Feedback
PARO EDU

PARO EDU

رفتن به کانال در Telegram

📖 Paro Edu | ትክክለኛና ፈጣን የትምህርት መረጃዎች፣ የፈተና ውጤቶች እና ወቅታዊ ዜናዎች የሚገኙበት ቻናል! 🎓 ዕውቀትዎን ያሳድጉ፤ ከእኛ ጋር ይማሩ! @ParoEdu @Paro_media @ParoLink 🎥 የዩቲዩብ ቻናላችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ 👇 🔗 https://www.youtube.com/@Paroedu

نمایش بیشتر

📈 تحلیل کانال تلگرام PARO EDU

کانال PARO EDU (@paroedu) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 45 858 مشترک است و جایگاه 3 806 را در دسته آموزش و رتبه 736 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 45 858 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 18 سپتامبر, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 236 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر -196 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 11.31% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 5.72% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 5 207 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 2 631 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 7 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاه‌های شخصی توصیف می‌کند:
📖 Paro Edu | ትክክለኛና ፈጣን የትምህርት መረጃዎች፣ የፈተና ውጤቶች እና ወቅታዊ ዜናዎች የሚገኙበት ቻናል! 🎓 ዕውቀትዎን ያሳድጉ፤ ከእኛ ጋር ይማሩ! @ParoEdu @Paro_media @ParoLink 🎥 የዩቲዩብ ቻናላችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ 👇 🔗 https://www.youtube.com/@Paroedu

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 19 سپتامبر, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته آموزش تبدیل کرده‌اند.

45 858
مشترکین
-19624 ساعت
-1 1867 روز
+23630 روز
آرشیو پست ها
PARO EDU
46 027
አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ (AI) ሰዎችን ይተካል ብላችሁ ታስባላችሁ?"
Anonymous voting

PARO EDU
46 027

PARO EDU
46 027
አካል ጉዳተኝነት ከውጤት ያልገደባት ተማሪ ‎ ተማሪ ሶሊያና ማሩ፣ ‎በ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ፈተና ወስደው ከፍተኛ ውጤት ካስመዘገቡ አካል ጉዳተኛ ተማሪዎች መካከል አንዷ ናት። ‎ ‎የማኅበራዊ
አካል ጉዳተኝነት ከውጤት ያልገደባት ተማሪ ‎ ተማሪ ሶሊያና ማሩ፣ ‎በ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ፈተና ወስደው ከፍተኛ ውጤት ካስመዘገቡ አካል ጉዳተኛ ተማሪዎች መካከል አንዷ ናት። ‎ ‎የማኅበራዊ ሳይንስ ተማሪዋ ሶሊያና፣ ከ600 ውስጥ 437 በማምጣት የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ውጤት አሳክታለች። ‎ ‎አካል ጉዳተኛ ብትሆንም፣ አልችልም ብላ ተስፋ ሳትቆርጥ ፈተናዎችን ተሻግራ ከፍተኛ የሚባል ውጤት አስመዝግባለች። 👏👏 ላስመዘገበችው ውጤት የቤተሰቦቿ እና የመምህራን ልዩ ድጋፍ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳረገላት ትገልጻለች። ‎በዩኒቨርሲቲ ቆይታዋ የሕግ ትምህርት ለመቀጠል ፍላጎት እንዳላት የምትገልፀው ተማሪ ሶሊያና፤ በኤሌክትሪክ የሚሠራ ዘመናዊ ዊልቼሮች ድጋፍ እንዲደረግላት ጠይቃለች። #አሚኮ 📣ለትምህርታዊ መረጃዎች ​📚 Join & Share with friends! Help others learn and grow with @ParoEdu. ​👉 Join @ParoEdu

PARO EDU
46 027
🔹 ሰላም የፓሮ ሚዲያ ቤተሰቦች! ዛሬ በነፃ (Free) ከምንም በላይ በፈጣን ሁኔታ በ AI ቪዲዮዎችን ማመንጨት የሚያስችሉ ምርጥ ሶፍትዌሮችን ይዘን መጥተናል! ⭕️ ቴክኖሎጂን በመጠቀም የራሶትን ቪ
🔹 ሰላም የፓሮ ሚዲያ ቤተሰቦች! ዛሬ በነፃ (Free) ከምንም በላይ በፈጣን ሁኔታ በ AI ቪዲዮዎችን ማመንጨት የሚያስችሉ ምርጥ ሶፍትዌሮችን ይዘን መጥተናል! ⭕️ ቴክኖሎጂን በመጠቀም የራሶትን ቪዲዮዎች በቀላሉ መስራት ከፈለጉ እነዚህን ነፃ መሣሪያዎች ሊጠቀሙ ይገባል፦ ✅️ 1. InVideo AI ✔️ ለጀማሪዎች በጣም ቀላል እና ምቹ የሆነ ሶፍትዌር ነው። ✔️ የፅሁፍ ትዕዛዝ (Prompt) በመጻፍ ብቻ ሙሉ ቪዲዮ ከድምጽ እና ከቪዲዮ ክሊፖች ጋር አብሮ ያዘጋጅልዎታል። ✅️ 2. Luma Dream Machine ✔️ እጅግ አስደናቂ እና ጥራታቸው የጠበቁ የሲኒማቲክ ቪዲዮዎችን በነፃ ለመፍጠር የሚያስችል ድንቅ AI መሳሪያ ነው። ✅️ 3. Kling AI ✔️ እንቅስቃሴዎችን (Motion) በሚገባ በመረዳት ተጨባጭ እና ሕያው የሆኑ ቪዲዮዎችን ማመንጨት የሚችል ዘመናዊ ሶፍትዌር ነው። ✅️ 4. Leonardo AI ✔️ ለቪዲዮ መነሻ የሚሆኑ ውብ ምስሎችን እና የአኒሜሽን ዲዛይኖችን በነፃ ለማግኘት ይጠቀሙበት። ❇️ ማጠቃለያ፦ እነዚህን ነፃ የ AI መሳሪያዎች በመጠቀም የትኛውንም የቪዲዮ ይዘት ያለ ምንም ወጪ በፍጥነት ማዘጋጀት ይችላሉ። አሁኑኑ ሞክሯቸው! 👇 ተጨማሪ ጠቃሚ የቴክኖሎጂ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉ! 🔗 https://t.me/Paro_media

PARO EDU
46 027
#ጥቆማ ‎የቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሌኒየም ሕክምና ኮሌጅ የነርሲንግ ትምህርት ቤት አዲስ ለሚጀመረው የአጠቃላይ ነርሲንግ የዲግሪ ፕሮግራም (BSc in Comprehensive Nursing) የማመልከቻ
#ጥቆማ ‎የቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሌኒየም ሕክምና ኮሌጅ የነርሲንግ ትምህርት ቤት አዲስ ለሚጀመረው የአጠቃላይ ነርሲንግ የዲግሪ ፕሮግራም (BSc in Comprehensive Nursing) የማመልከቻ ጊዜ እስከ መስከረም 13/2019 ዓ.ም ድረስ አራዝሟል። በፕሮግራሙ የሚታቀፉ ተማሪዎች፦ ➻ የተሟላ የዶርሚተሪ፣ የምግብ እና ሌሎች አገልግሎቶችን ያገኛሉ። ➻ አዳዲስ ኮርሶችን፣ ይዘቶችን እና የስልጠና አካሔዶችን ያካተተ ስልጠና ያገኛሉ። ➻ የተደራጀ ሲሙሌሽን እና ተግባር ተኮር ስልጠና ያገኛሉ። የምዝገባ ጊዜ 👇 እስከ መስከረም 13/2019 ዓ.ም ከቀኑ 11፡00 ድረስ ብቻ ይመዝገቡ 👇 https://portal.sphmmc.edu.et/Web/Announcement ለተጨማሪ መረጃ፦ 0118965125 / 0112756089 ​📚 Join & Share with friends! Help others learn and grow with @ParoEdu. ​👉 Join @ParoEdu

PARO EDU
46 027
#MoE በ2019 ዓ.ም ወደ ፌዴራል ልዩ አዳሪ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለ9ኛ እና 10ኛ ክፍል ለመማር ተመዝግባችሁ ላለፋችሁና እስካሁን ድረስ ምዝገባ ያላደረጋችሁ ተማሪዎች፣ ቀደም ሲል ለምዝገባ
#MoE በ2019 ዓ.ም ወደ ፌዴራል ልዩ አዳሪ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለ9ኛ እና 10ኛ ክፍል ለመማር ተመዝግባችሁ ላለፋችሁና እስካሁን ድረስ ምዝገባ ያላደረጋችሁ ተማሪዎች፣ ቀደም ሲል ለምዝገባ በተጠቀማችሁበት ሊንክ (https://sbs.moe.gov.et/apply) በመግባት እስከ እሑድ መስከረም 10/2019 ዓ.ም ድረስ እንድትመዘገቡ ትምህርት ሚኒስቴር አሳስቧል። ​📚 Join & Share with friends! Help others learn and grow with @ParoEdu. ​👉 Join @ParoEdu

PARO EDU
46 027
#LorcanMedicalCollege ሎርካን ሜዲካል ኮሌጅ ለ2019 ዓ.ም አዲስ ገቢ ተማሪዎቹ የመግቢያ እና የትምህርት መጀመርያ የጊዜ ሰሌዳ ይፋ አድርጓል። ​በወጣው የጊዜ ሰሌዳ መሠረት የመግቢያ ፈ
+3
#LorcanMedicalCollege ሎርካን ሜዲካል ኮሌጅ ለ2019 ዓ.ም አዲስ ገቢ ተማሪዎቹ የመግቢያ እና የትምህርት መጀመርያ የጊዜ ሰሌዳ ይፋ አድርጓል። ​በወጣው የጊዜ ሰሌዳ መሠረት የመግቢያ ፈተና መስከረም 20/2019 ዓ.ም የሚሰጥ ሲሆን፣ የቃል ፈተና መስከረም 21/2019 ዓ.ም ይሰጣል። የዲግሪ ተማሪዎች ኦረንቴሽን መስከረም 22/2019 ዓ.ም እንደሚሰጥ ተገልጿል። የምዝገባ ማጠናቀቂያ ጊዜ 👇 መስከረም 25 እና 26/2019 ዓ.ም መደበኛ ትምህርት የሚጀመረው መስከረም 27/2019 ዓ.ም መሆኑ ተመላክቷል። አዲስ ገቢ ተማሪዎቹ በሕክምና፣ በጥርስ ሕክምና፣ በጥርስ ሳይንስ እንዲሁም በነርሲንግ የትምህርት መስኮች ትምህርታቸውን የሚከታተሉ መሆናቸውን የሎርካን ሜዲካል ኮሌጁ ፕሮቮስት ሔኖክ አለሙ ገልፀዋል። (የመግቢያ ፈተና አወጣጥ ዝርዝር እንዲሁም አካዳሚክ ካላንደሩ ከላይ ተያይዟል።) ​📚 Join & Share with friends! Help others learn and grow with @ParoEdu. ​👉 Join @ParoEdu

PARO EDU
46 027
አካል ጉዳተኝነት ከውጤት ያልገደባት ተማሪ ‎ ተማሪ ሶሊያና ማሩ፣ ‎በ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ፈተና ወስደው ከፍተኛ ውጤት ካስመዘገቡ አካል ጉዳተኛ ተማሪዎች መካከል አንዷ ናት። ‎ ‎የማኅበራዊ
አካል ጉዳተኝነት ከውጤት ያልገደባት ተማሪ ‎ ተማሪ ሶሊያና ማሩ፣ ‎በ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ፈተና ወስደው ከፍተኛ ውጤት ካስመዘገቡ አካል ጉዳተኛ ተማሪዎች መካከል አንዷ ናት። ‎ ‎የማኅበራዊ ሳይንስ ተማሪዋ ሶሊያና፣ 437 ነጥብ የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ውጤት አሳክታለች። ‎ ‎አካል ጉዳተኛ ብትሆንም፣ አልችልም ብላ ተስፋ ሳትቆርጥ ፈተናዎችን ተሻግራ ከፍተኛ የሚባል ውጤት አስመዝግባለች። 👏👏 ላስመዘገበችው ውጤት የቤተሰቦቿ እና የመምህራን ልዩ ድጋፍ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳረገላት ትገልጻለች። ‎በዩኒቨርሲቲ ቆይታዋ የሕግ ትምህርት ለመቀጠል ፍላጎት እንዳላት የምትገልፀው ተማሪ ሶሊያና፤ በኤሌክትሪክ የሚሠራ ዘመናዊ ዊልቼሮች ድጋፍ እንዲደረግላት ጠይቃለች። #አሚኮ ​📚 Join & Share with friends! Help others learn and grow with @ParoEdu. ​👉 Join @ParoEdu

PARO EDU
46 027
📣 REGISTRATION NOW OPEN!!! Jimma University has brought selected master’s programs right to the capital city, which are tail
📣 REGISTRATION NOW OPEN!!! Jimma University has brought selected master’s programs right to the capital city, which are tailored to the demands of today's dynamic job market, and is now accepting applications! 🎓   𝙒𝙝𝙞𝙘𝙝 𝙥𝙧𝙤𝙜𝙧𝙖𝙢 𝙖𝙧𝙚 𝙮𝙤𝙪 𝙞𝙣𝙩𝙚𝙧𝙚𝙨𝙩𝙚𝙙 𝙞𝙣 𝙚𝙣𝙧𝙤𝙡𝙡𝙞𝙣𝙜 𝙞𝙣? MSc in Artificial Intelligence MA in Project Management and Finance MBA in Business Administration MA in Logistics and Supply Chain Management MA in International Relations and Diplomacy MPH in General Public Health MPH in Epidemiology MSc in Health Monitoring and Evaluation MSc in Health Economics   Ready to Join? Register: https://portal.ju.edu.et/announce/show/6   𝐅𝐨𝐫 𝐌𝐨𝐫𝐞 𝐈𝐧𝐟𝐨𝐫𝐦𝐚𝐭𝐢𝐨𝐧 📞 +251978464748 📍 Kazanchis, Infront of Radisson Blu Hotel (the former HQ of Zemen Bank) 🔗 Telegram   𝙀𝙖𝙧𝙣 𝙖 𝙅𝙞𝙢𝙢𝙖 𝙐𝙣𝙞𝙫𝙚𝙧𝙨𝙞𝙩𝙮 𝘿𝙚𝙜𝙧𝙚𝙚 𝙞𝙣 𝘼𝙙𝙙𝙞𝙨 𝘼𝙗𝙖𝙗𝙖!   #JimmaUniversity #PostgraduateProgram #MastersDegree #HigherEducation #ApplicationOpen #ApplyNow ​📚 Join & Share with friends! Help others learn and grow with @ParoEdu. ​👉 Join @ParoEdu

PARO EDU
46 027
#DebreTaborUniversity ደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ የሁሉም የተቋሙ ነባር የቅድመ እና የድኅረ-ምረቃ ተማሪዎች ምዝገባ የሚካሔደው መስከረም 28 እና 29/2019 ዓ.ም መሆኑን አሳውቋል፡፡ በ2
+1
#DebreTaborUniversity ደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ የሁሉም የተቋሙ ነባር የቅድመ እና የድኅረ-ምረቃ ተማሪዎች ምዝገባ የሚካሔደው መስከረም 28 እና 29/2019 ዓ.ም መሆኑን አሳውቋል፡፡ በ2019 ዓ.ም ደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ አዲስ ገቢ የአንደኛ ዓመት (Freshman) እና የሪሚዲያል ተማሪዎች እንዲሁም በ2018 ዓ.ም በደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ የሪሚዲያል ፕሮግራም ትምህርታችሁን ስትከታተሉ ቆይታችሁ የማለፊያ ውጤት ያመጣችሁ ተማሪዎች የ2019 ዓ.ም ትምህርት ዘመን ምዝገባ በሌላ ማስታወቂያ ጥሪ የሚደረግ መሆኑን ዩኒቨርሲቲው ገልጿል፡፡ ​📚 Join & Share with friends! Help others learn and grow with @ParoEdu. ​👉 Join @ParoEdu

PARO EDU
46 027
#HUCMHS የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ከስር የተዘረዘሩት ትምህርት መስክ ተማሪዎች የ2019 ዓ.ም የመጀመርያ ሴሚስተር ምዝገባ የሚከናወነው መስከረም 14 እና 15/2019 ዓ.
#HUCMHS የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ከስር የተዘረዘሩት ትምህርት መስክ ተማሪዎች የ2019 ዓ.ም የመጀመርያ ሴሚስተር ምዝገባ የሚከናወነው መስከረም 14 እና 15/2019 ዓ.ም መሆኑን አሳውቋል፡፡ 1. ፋርማሲ ➻ ከ2015-2018 ዓ.ም ባቾች 2. ሕክምና ➻ የ2018 ዓ.ም ባች 3. HO, Health Informatics, Nursing, Psychiatry Nursing, Environmental Health, Midwifery, Optometry, MLS, Anesthesia, and MRT ➻ ከ2016-2018 ዓ.ም የገባችሁ ባቾች በ2015 ዓ.ም የገባችሁና በተራ ቁ. 3 ላይ የተዘረዘሩት ፕሮግራም ተማሪዎች ትምህርት የምትቀጥሉበትን ቀን በቀጣይ የሚያሳውቅ መሆኑን ዩኒቨርሲቲው ገልጿል። ​📚 Join & Share with friends! Help others learn and grow with @ParoEdu. ​👉 Join @ParoEdu

PARO EDU
46 027
በግጭት ምክንያት ከትግራይ ክልል የሚወጡ #መምህራን ካሉ በሌሎች የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች እንዲያስተምሩ ይደረጋል፡፡ - ትምህርት ሚኒስቴር በትግራይ ክልል የሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች የሚያስተምሩ መምህራን
በግጭት ምክንያት ከትግራይ ክልል የሚወጡ #መምህራን ካሉ በሌሎች የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች እንዲያስተምሩ ይደረጋል፡፡ - ትምህርት ሚኒስቴር በትግራይ ክልል የሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች የሚያስተምሩ መምህራን በበጸጥታ ችግር ምክንያት ከክልሉ የሚወጡ ከሆነ በሌሎች የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች እንዲያስተምሩ እንደሚደረግ የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) አረጋግጠዋል። በትግራይ ክልል ይማሩ የነበሩ ተማሪዎች በክልሉ ያለው ወቅታዊ ሁኔታ እስኪስተካከል ድረስ በጊዜያዊነት ከትግራይ ክልል ውጪ ወደሚገኙ ሌሎች የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች እንዲመደቡ የሚደረግ መሆኑን ትምህርት ሚኒስቴር መግለፁ ይታወቃል፡፡ ከ5 ሺህ በላይ ነባር ተማሪዎች የዝውውር ማመልከቻ እንዳስገቡ የገለፀው ሚኒስቴሩ፤ ተማሪዎቹ በጊዚያዊነት የሚመደቡበትን ዩኒቨርሲቲ በቅርቡ አሳውቃለሁ ብሏል፡፡   በተያያዘ ትግራይ ክልል በሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች መቀጠል የሚፈልጉ ነባር እና አዲስ ተማሪዎችን በተመለከተ ከዩኒቨርስቲዎቹ ጋር እየተነጋገረ መሆኑን ሚኒስቴሩ ገልጿል፡፡   ​📚 Join & Share with friends! Help others learn and grow with @ParoEdu

PARO EDU
46 027
#ጥቆማ: በጋዜጠኝነት ሞያ አዲስ ለተመረቃችሁና በሞያው መስራት ለምትፈልጉ የተዘጋጀ ነፃ ስልጠና በአሁን ወቅት ​በሚዲያ ዘርፍ በጋዜጠኝነት፣ በሪፓርተርነት ለመስራት ተወዳዳሪ ለመሆን ከአዲስ ተመራቂዎ
#ጥቆማ: በጋዜጠኝነት ሞያ አዲስ ለተመረቃችሁና በሞያው መስራት ለምትፈልጉ የተዘጋጀ ነፃ ስልጠና በአሁን ወቅት ​በሚዲያ ዘርፍ በጋዜጠኝነት፣ በሪፓርተርነት ለመስራት ተወዳዳሪ ለመሆን ከአዲስ ተመራቂዎች ወይም በቅርብ ከሚመረቁ የመጨረሻ አመት ተማሪዎቾ ምን ይጠበቃል ?በተግባር የተደገፈ የሦስት ሰዓታት የሥልጠና በነጻ ተዘጋጅቷል። ሥልጠናው በነገው ዕለት ቅዳሜ መስከረም 9 ቀን 2019 በመገናኛ ስለሺ ሕንጻ 10ኛ ፎቅ በሚገኘው ዘ third ስፔስ (The Third Space) ሞያው ላይ እየሰሩ ባሉ ባለሞያዎች ይሰጣል። መርሃ-ግብሩ ሙሉ በሙሉ ነፃ ቢሆንም የቦታው መጠን የተወሰነ በመሆኑ ፍላጎት ያላቸው ተሳታፊዎች 👉 https://forms.gle/ph5TSRS9crgHJUMJ9 በሚለው ማስፈንጠሪያ አስቀድመው መመዝገብ ይኖርባቸዋል። #ConceptHub ​📚 Join & Share with friends! Help others learn and grow with @ParoEdu. ​👉 Join @ParoEdu

PARO EDU
46 027
"በቀጣይ ከኛ ምን ዓይነት ትምህርታዊ ወይም ቴክኖሎጅያዊ መረጃዎችን ማየት ትፈልጋላችሁ?"
Anonymous voting

PARO EDU
46 027
የሪሚዲያል ተማሪዎች የውጤት ቅሬታ እና የቀረበው ጥያቄ በ2018 ዓ.ም. የሪሚዲያል (Remedial) ፕሮግራም ተከታትለው የነበሩ ተማሪዎች የፈተና ውጤታቸው ከጥረታቸው ውጪ እጅግ ዝቅተኛ በመሆኑ ለት
የሪሚዲያል ተማሪዎች የውጤት ቅሬታ እና የቀረበው ጥያቄ በ2018 ዓ.ም. የሪሚዲያል (Remedial) ፕሮግራም ተከታትለው የነበሩ ተማሪዎች የፈተና ውጤታቸው ከጥረታቸው ውጪ እጅግ ዝቅተኛ በመሆኑ ለትምህርት ሚኒስቴር የቅሬታ ጥያቄ አቀረቡ። ተማሪዎቹ ያነሷቸው ዋና ዋና ችግሮች የሚከተሉት ናቸው፡- * በጆግራፊ እና ፊዚክስ የታየ ያልተለመደ ዝቅተኛ ውጤት፡ በማህበራዊ ሳይንስ በጆግራፊ እንዲሁም በተፈጥሮ ሳይንስ በፊዚክስ ትምህርቶች የተመዘገበው ውጤት በብዙዎች ዘንድ እጅግ ዝቅተኛ መሆን በሂደቱ ላይ ጥርጣሬ ፈጥሯል። * የኢንተርኔት መቆራረጥ ችግር፡ ፈተናው በሚሰጥበት ወቅት በተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች አጋጥሞ የነበረው የኢንተርኔት መቆራረጥ ተማሪዎቹ በተረጋጋ ሁኔታ እንዳይፈተኑ አድርጓል። * በሦስት ዙሮች (Seasons) መሰጠት፡ ፈተናው በሦስት ዙር መሰጠቱ በውጤት አሰጣጥ ላይ የውጤት መደባለቅ (Data mismatch) እንዲፈጠር ምክንያት ሆኗል ተብሎ ተሰግቷል። * የ "Disqualified" ሁኔታ፡ አብዛኛዎቹ ተማሪዎች መጀመሪያ "Disqualified" ተብለው ቆይተው፣ ውጤታቸው ሲስተካከል እጅግ ዝቅተኛ ሆኖ መገኘቱ በሲስተሙ ላይ ክፍተት እንዳለ ያሳያል ብለዋል። የተማሪዎቹ ዋና ዋና ጥያቄዎች፡ * የፈተና አሰጣጥ ሲስተም፣ የሦስቱ ዙሮች መረጃ እና የእርማት ሂደቱ በጥብቅ እንዲጣራ። * በተለይ በፊዚክስ እና ጆግራፊ የታዩ ዝቅተኛ ውጤቶች ከ100 በላይ እንዳይቀየሩ ተደርጎ እንዲመረመር። * በፈተናው ውስጥ ትክክለኛ ያልሆኑ ጥያቄዎች ካሉ ታሳቢ ተደርገው ውጤታቸው እንዲስተካከል ጠይቀዋል። @ParoEdu

PARO EDU
46 027
🔥 የቲክቶክ Coin በቅናሽ ለመግዛት! 🔥 በአስተማማኝ እና ፈጣን አገልግሎት የቲክቶክ coin መግዛት ይፈልጋሉ? ለመግዛት አሁኑኑ ያግኙን: @teketel_dawit የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ
🔥 የቲክቶክ Coin በቅናሽ ለመግዛት! 🔥 በአስተማማኝ እና ፈጣን አገልግሎት የቲክቶክ coin መግዛት ይፈልጋሉ? ለመግዛት አሁኑኑ ያግኙን: @teketel_dawit የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ: @Paro_Media ✅Payment Proof 👇👇👇👇 @ParoTiktokCoin @ParoTiktokCoin

PARO EDU
46 027
#MoE የሪሚዲያል ፕሮግራም ለመከታተል የሚያስችል ውጤት ያመጣችሁ ተማሪዎች የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ምርጫ አድርጉ ተብሏል፡፡ በ2018 ዓ.ም የ2ኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ሀገር አቀፍ ፈተና ወ
#MoE   የሪሚዲያል ፕሮግራም ለመከታተል የሚያስችል ውጤት ያመጣችሁ ተማሪዎች የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ምርጫ አድርጉ ተብሏል፡፡   በ2018 ዓ.ም የ2ኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ሀገር አቀፍ ፈተና ወስዳችሁ የሪሚዲያል ፕሮግራም ለመከታተል የሚያስችል ውጤት ያመጣችሁ ተማሪዎች የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የምደባ ምርጫችሁን ከመስከረም 7-11/2019 ዓ.ም ድረስ እንድታደርጉ ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል፡፡   የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ለመምረጥ 👇 https://student.ethernet.edu.et/preferences   ​🔹───────────────🔹 🎯 አብረውን ይሁኑ! 🔗👉 @ParoEdu 👈 🔹───────────────🔹

PARO EDU
46 027
በትግራይ ክልል በሚገኙ የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች አዲስ ለተመደቡ እንዲሁም ለነባር ተማሪዎች በጊዚያዊነት የምትመደቡበትን ዩኒቨርሲቲ በቅርቡ ይገለጻል፡፡ - ትምህርት ሚኒስቴር በትግራይ ክልል ይማሩ የ
በትግራይ ክልል በሚገኙ የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች አዲስ ለተመደቡ እንዲሁም ለነባር ተማሪዎች በጊዚያዊነት የምትመደቡበትን ዩኒቨርሲቲ በቅርቡ ይገለጻል፡፡ - ትምህርት ሚኒስቴር በትግራይ ክልል ይማሩ የነበሩ ተማሪዎች በጠየቁት መሠረት፣ በክልሉ ያለው ወቅታዊ ሁኔታ እስኪስተካከል ድረስ በጊዜያዊነት ከትግራይ ክልል ውጪ ወደሚገኙ ሌሎች የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች እንድትመደቡ የሚደረግ መሆኑን ትምህርት ሚኒስቴር መግለፁ ይታወቃል፡፡ "በዚህ ጉዳይ ላይ ቅሬታ ያላችሁ ተማሪዎች ወደ ትምህርት ሚኒስቴር በአካል መሔድ ሳይጠበቅባችሁ፣ የትምህርት ሒደታችሁ እንዳይስተጓጎል እና ደኅንነታችሁ ተጠብቆ ትምህርታችሁን በመደበኛነት እንድትቀጥሉ ለማስቻል በጊዜያዊነት የምትመደቡበትን ዩኒቨርሲቲ በቅርቡ ይፋ እንደሚያደርግ" ሚኒስቴሩ ገልጿል፡፡ "ያለው ነባራዊ ሁኔታ ሲስተካከል፣ መጀመሪያ በተመደባችሁባቸው ዩኒቨርሲቲዎች ተመልሳችሁ ትምህርታችሁን የምትቀጥሉ መሆኑን ከወዲሁ እናሳውቃለን" ብሏል ሚኒስቴሩ ባጋራው አጭር መልዕክት፡፡ በተለያየ ምክንያት ትግራይ ክልል በሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች መቀጠል የሚፈልጉ #ነባር እና #አዲስ ተማሪዎችን በተመለከተ ከዩኒቨርስቲዎቹ ጋር እየተነጋገረ መሆኑን የጠቆመው ትምህርት ሚኒስቴር፤ ተማሪዎቹ በትዕግስት እንዲጠብቁ ጠይቋል፡፡ ​🔹───────────────🔹 🎯 አብረውን ይሁኑ! 🔗👉 @ParoEdu 👈 🔹───────────────🔹

PARO EDU
46 027
#EthiopianDefenceUniversity የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ የ2019 ዓ.ም የፍሬሽማን ተማሪዎች ወደ ግቢ የቅበላ ጊዜ መስከረም 11 እና 12/2019 ዓ.ም መሆኑን ገልጿል፡፡ ተማራቂ
#EthiopianDefenceUniversity የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ የ2019 ዓ.ም የፍሬሽማን ተማሪዎች ወደ ግቢ የቅበላ ጊዜ መስከረም 11 እና 12/2019 ዓ.ም መሆኑን ገልጿል፡፡ ተማራቂ ያልሆኑ ነባር ተማሪዎች የምዝገባ ጊዜ መስከረም 14 እና 15/2019 ዓ.ም እንደሆነ ዩኒቨርሲቲው ያወጣው የ2019 ትምህርት ዘመን ካሌንደር ያሳያል፡፡ https://t.me/ParoEdu

PARO EDU
46 027
#ጥቆማ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመደበኛው መርሐግብር በ2019 ትምህርት ዘመን ለመማር አመልክታችሁና ተወዳድራችሁ ቅበላ ያላገኛችሁ አመልካቾች፣ የዩኒቨርሲቲውን መግቢያ ፈተና (UAT) 50 እና ከዚ
#ጥቆማ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመደበኛው መርሐግብር በ2019 ትምህርት ዘመን ለመማር አመልክታችሁና ተወዳድራችሁ ቅበላ ያላገኛችሁ አመልካቾች፣ የዩኒቨርሲቲውን መግቢያ ፈተና (UAT) 50 እና ከዚያ በላይ ካላችሁ በተከታታይ ትምህርት ፕሮግራም (Extension) ማመልከት የምትችሉ መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል፡፡ https://t.me/ParoEdu