cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

የሕያ ኢብኑ ኑህ - Yahya Ibnu Nuhe

﷽ | Muslim | Theology | Comparative Religion | Philosophy | Student | Teacher |

Show more
Advertising posts
12 865Subscribers
+2524 hours
+1437 days
+40730 days
Posts Archive
"ከሰዎች መካከል አሉ፣ ይጾማሉ ግን ከጾማቸው ረሀብን እንጅ አያተርፉም" ሱነን ኢብን ማጃህ 1690
Show all...
😢 18👍 10
🥰 21 10👍 1
ቀልድ አይደለም..! እስልምናን የሚተች አንድ የቴሌግራም ቻናል ነው ብለው ወንድሞች ልከውልኝ ሳየው ያገኘሁት ነው። ቁርአን ከአማርኛ ቋንቋ የተዋሳቸው ቃላት አሉ በሚል ሲያቀርብ የተጠቀመው ነው። ሁለቱ ቃላት ማለትም "ፈርስና ፈረስን" በቅጡ መለየት አልቻለም። አፕልኬሽኑ እንኳን ቢያሳሳት ሰው ኮንቴክስት አይቶ እንዴት መረዳት ይሳነዋል? እስልምናን ሲተቹ የምትመለከቷቸው አብዛኛዎቹ ተሳዳቢዎች እውቀት ላይ እንዲህ መናኛ ናቸው። የአማርኛ ቋንቋ በመሠረቱ ለአረብኛ ቃላት ምንጭ መሆን የሚችል አይደለም። እድሜውም ለዚያ አያበቃውም። ባየ ይማም "የአማርኛ ሰዋሰው" በተሰኘ መጽሀፉ መቅድም ላይ አማርኛ ቋንቋ ከተለያዩ ቋንቋዎች ቃላትን በመዋስ የተፈጠረ ድብልቅ ቋንቋ እንደሆነ ይገልጻል። ፈረስ የሚለው ቃልም እንዲሁ የተውሶ ቃል መሆኑን እንዲህ ሲል ይገልጸዋል፦ "አማርኛ የተለያዩ ቋንቋዎችን ይናገር በነበረ ዘማችና አዝማች የተፈጠረ የሠራዊት ቋንቋ ነበር ለማለት ይቻላል፡፡ መሠረታዊ መድበለ ቃላቱ ባብዛኛው ሴማዊ ሲሆኑ፣ በመጠኑ ደግሞ ኩሻዊ ናቸው፡፡ ለዚህ እንደውሻ፣ ካራ፣ ውሃ፣ ሸኮና፣ አኮሌ፣ አሬራ፣ ኮርቻ፣ ቀብድ፣ #ፈረስ፣ ዱላ፣ ወዘተ. ያሉት ቃላት እንደ ምሳሌ መጥቀስ ይቻላል" ባየ ይማም "የአማርኛ ሰዋሰው" መቅድም የአማርኛ ቋንቋ በመሠረቱ ልሳነንጉስ የሆነው በ1272 በአጼ ይኩኖ አምላክ ነበር። ከዚያ በፊት ይታወቅም ይነገር የነበረውም ቋንቋ ግዕዝ ሲሆን አማርኛም ድብልቅ ቋንቋ ሁኖ መነገር ሲጀምር ነገስታቱ ከዛግዌ ለተረከቡት ሰለሞናዊ ስርአት ይፋዊ መነጋገሪያ አደረጉት። እውነታው ይህ ነው፣ ትንሽም ቢሆን ማስተዋልና ማንበብ የታከለበት ሰው መሠል ስህተት ውስጥ አይወድቅም። ___ https://t.me/Yahyanuhe
Show all...
👍 30 4🥰 1
ሸይጧን በረመዷን ታስሯል ካላችሁ ለምን ኃጥያት ላይ ትወድቃላችሁ?ሸይጧን ከታሰረ እንዴት ወንጀል አልጠፋም? ጥሩ ጥያቄ ነው፣ እስኪ በአጭሩ እንደሚከተለው እናብራራው፥ የሰውን ልጅ ወደ መጥፎ ተግባራት የሚመሩት ሁለት አካላት ናቸው። እነሱም፦ 1- የሰይጣን ጉትጎታ (شَرِّ الشَّيْطَانِ) 2- የነፍስ ጉትጎታ (شَرِّ نَفْسِي) ናቸው። የሰው ልጅ ከሸይጧን ጉትጎታ በተጨማሪ የነፍስያው ጉትጎታም ሀራም ተግባራት ላይ ይጥሉታል። ስለዚህም ሸይጧን መታሰሩ ብቻ የሰው ልጅ መጥፎ ከመስራት አያቅቡትም፣ ነፍሱንም ጭምር መግራት ካልቻለ በቀር..!በመሠረቱ የሸይጧን ጉትጎታም ደካማ ተብሎ በቁርአን ተጠቅሷል። ነፍስ በዚህ በኩል የምትፈጥረው ጉትጎታ ቀላል አይደለም። ለዚህ ምንድን ማስረጃው ከተባለ የሚከተሉት የቁርአን አንቀጾችና ሀዲሳት ይጠቀሳሉ፦ ◾️ ማስረጃዎች፡- 1- ቁርኣን እንዲህ ይላል፦ إِنَّ النَّفْسَ لَأَمَّارَةٌ بِالسُّوءِ إِلَّا مَا رَحِمَ رَبِّي "...ነፍስ ሁሉ ጌታዬ የጠበቃት ካልሆነች በስተቀር በመጥፎ ነገር በእርግጥ አዛዥ ናትና፡፡.." (ቁርኣን 12፡53)። 2- ቁርኣንም ደግሞ እንዲህ ይላል፦ وَلَقَدْ خَلَقْنَا الْإِنْسَانَ وَنَعْلَمُ مَا تُوَسْوِسُ بِهِ نَفْسُهُ وَنَحْنُ أَقْرَبُ إِلَّيْبِينَ "ሰውንም ነፍሱ (በሐሳቡ) የምታጫውተውን የምናውቅ ስንኾን በእርግጥ ፈጠርነው፤ እኛም ከደም ጋኑ ጅማት ይበልጥ ወደርሱ ቅርብ ነን፡፡" (ቁርኣን 50፡16)። 3- ነቢዩ "ﷺ" ይህንን ዱዓ አስተምረውናል፦ أَعُوذُ بِكَ مِنْ شَرِّ نَفْسِي وَمِنْ شَرِّ الشَّيْطَانِ "ከነፍሴ ክፋት ከሰይጣንም ክፋት በአንተ እጠበቃለሁ" ["አቡ ዳውድ"፣ 5067 - صحيح]። 4- ነቢዩ "ﷺ" እንዲህ ብለዋል፦ الْمُجَاهِدُ مَنْ جَاهَدَ نَفْسَهُ "ሙጃሂድ (ታጋይ ማለት) ነፍሱን የሚታገል ነው።" ["ቲርሚዚ", 1621 - صحيح]. 5- ቁርኣንም እንዲህ ይላል። وَأَمَّا مَنْ خَافَ مَقَامَ رَبِّهِ وَنَهَى النَّفْسَ عَنِ الْهَوَى فَإِنَّ الْجَنَّةَ هِيَ الْمَأْوَى "በጌታው ፊት መቆምን የፈራ ሰውማ ነፍሱንም ከዝንባሌዋ የከለከለ፥ ገነት እርሷ በእርግጥ መኖሪያው ናት፡፡ (ቁርአን 79፡40-41)። ወሏሁ አዕለም..! © አቡ ሐይሰም (Yahya) ___ https://t.me/Yahyanuhe
Show all...
👍 42 5👏 4
የኢዩ ጩፋ ስሁት ፍረጃ | ምላሽ -17 https://vm.tiktok.com/ZMMU8MN9b/
Show all...
👍 18
"ሳራ ነኝ ሰለምቴዋ" በሚል አካውንት የምናውቃት እህታችን በኦንላይን ሾፒንግ የሚከተሉትን አልባሳት የመሸጥ ስራ ጀምራለች። የወደዳችሁትን ልብስ በመግዛት አበረታታቷት፦ ስልክ ቁጥር፦ +96654 798 4638 📞
Show all...
👍 64 13🎉 1
ከጎኑ የሚሰግደውን ሰው የለቅሶ ሲቃ በመጠኑም ሰምቶ ነበርና ሲጨርሱ ወደሱ ዘወር ብሎ "ምን ያክል ትርጉሙ ቢገባህ ነው እንዲህ ያስለቀሰህ?" አለው ሰውየውም በትካዜ "የቁርአኑ ትርጉሙ አልገባኝም፤ ያስለቀሰኝም እሱ ነው" አለው። ለስንቱ የዱንያ ሀጃ በርካታ ስራዎችንና ሳይንሶችን ለብዙ አመታት ያጠናው ጭንቅላታችን የአሏህን ቃል ግን ትርጉሙን እንኳን አለማወቁን ማሰብ እንዴት ሀዘን ይፈጥራል?
Show all...
😢 119👍 19 8
ከፈትዋ ውጭ ላሉ የንጽጽራዊ ጥያቄዎች ብቻ፦ t.me/Yahyanuhe1
Show all...
👍 39 2
ቲክቶክ እንደገባሁ ፕላትፎርሙ ለአጫጭር ቪዲዮዎች የተገነባ በመሆኑ ምን መስራት እንዳለብኝ ጊዜ ሰጥቸ ማሰብ ጀመርኩ። ከመጡልኝ ሀሳቦች መካከል "ስቲሮት - ከ100 በላይ የመጽሀፍ ቅዱስ ግጭቶች" የተሰኘውን መጽሀፌን ሙሉውን በአጫጭር ቪዲዮ በማቅረብ መጽሀፉን ላላነበቡ ሰዎች አሰልቺ ባልሆነ መንገድ ማቅረብ ነበር። ሀሳቡን ካመጣሁ በኃላ በምን መቅረብ እንዳለበትም የራሴን ምልከታ ይዠ ሁሌም ወደሚተባበረኝ ግራፊክስ ዲዛይነር ወንድሜ ሄድኩ። ከዚህ በፊት እንደነበረው ነጻ ትብብር እንዲያደርግ ሳይሆን ቋሚ ስራ ስለሚሆን የማክዮቶም ቢሆን የሆነ ነገር ለአንድ ቪዲዮ እያሰብኩለት እንዲሰራልኝ ነገርኩት፥ ብዙም አላሳሰበውም፣ ሁሉኑም የዳዕዋ ስራዎቼን ከመጽሀፎቼ ኢዲት ጀምሮ ስለሚሰራልኝ አጅሩ ላይ ብቻ ትኩረት እንደሚያደርግ አቃለሁና እምቢ እንደማይለኝ በመገመት ነበር የሄድኩት፣ ተስማምተን ስራውን ጀመረው፥ ቪዲዮዎቹ በተጀመሩ ሰሞን ጥቂት ሰዎች ቪዲዮዎቹ በተለያዩ አጋጣሚዎች ከወዳጅ ዘመድ እየተላከላቸው ማግኘታቸውን እየገለጹ ቴሌግራሜን አፋላልገው እስልምና ላይ ያሉ ጥያቄዎቻቸውን ይጠይቁኝ ጀመር። ብዙዎቹ ጋ ደስ የሚል ተግባቦት ፈጠርን። ከብዙ ቀናት በኃላ ሀገራችን ካፈራቻቸው ታላላቅ ዓሊሞች መካከል አንዱ የሆኑት ሸይኽ ትምህርቶቹን በብዙ ቦታዎች እንደሚያሰራጯቸውና እንደወደዷቸው ብዙ ፍሬም እንዳመጡ ነገሩኝ። ለካ ቪዲዮዎቹ ከተሰሩ የትም ቦታ መድረስ ይችላሉ በሚል ትልቅ ሞራል ነበርና ስራውን ማስፋት እንዳለብኝ አመንኩ። ወንድማችን ጋር በመነጋገር ግጭቶቹ 100ዎቹም በአሏህ ፍቃድ ለመዳሰስ ተስማማን። በተጨማሪም የመጽሀፍ ቅዱስ የንባብ ልዩነቶችን/Textual Variants/ አስመልክቶ "የመጽሀፍ ቅዱስ መበረዝ ማሳያዎች" በሚል የተጀመረው ፕሮግራምም ይደርሳል። - የመጽሀፍ ቅዱስ ግጭቶች 35 ክፍል የደረሱ ሲሆን በቲክቶክ፣ በፌስቡክ በቴሌግራምና በዩቲዩብ ይለቀቃል - የመጽሀፍ ቅዱስ መበረዝ ማሳያዎች እስካሁን 4 ክፍል የተለቀቀ ሲሆን ከረመዷን በኃላ በአሏህ ፍቃድ በሰፊው መድረስ ይጀምራል - መጽሀፍ ቅዱስና ጥያቄዎቼ እስካሁን 5 ክፍሎች የተለቀቀ ሲሆን እንደሁኔታው እሱም በአሏህ ፍቃድ ይቀጥላል። ትምህርቶቹን ባገኛችሁት አጋጣሚ በቀናነት ለወገኖቻችን ሼር ማድረግ አትርሱ፤ የትኛው ትምህርት ለሒዳያ ሰበብ እንደሚሆናቸው አናውቅም። የኛ ኃላፊነት በታዘዝነው መልኩ ማድረስ ብቻ ነው፥ በኒያችን ልክ እንመነዳለን። አሏህ ከፈቀደ ደግሞ በዚህች ትንሽ ስራ በርካታ ሰዎችን ወደ ሒዳያ ሊመራልንም ይችላል። አሏህ ይገዘን..! 📌 ቲክቶክ https://www.tiktok.com/@yahyaibnunuhe?_t=8ktCFn5kjJt&_r=1 📌 ቴሌግራም https://t.me/Yahyanuhe 📌 ፌስቡክ https://www.facebook.com/share/LUWjmvQRLtVVzsSX/?mibextid=qi2Omg 📌 ዩቲዩብ https://youtube.com/@YahyaIbnuNuhe?si=-ffuMuU8R4Dp7w85
Show all...
👍 34 6
ስምህ በሰዎች ዘንድ መታወቁ አልያም ስራዎችህ ሰዎች ዘንድ አጀንዳ መሆናቸው ለአኼራ ስኬትህ ያን ያህል አስፈላጊ አይደለም። وَرُسُلًا لَّمْ نَقْصُصْهُمْ عَلَيْكَ “...ባንተ ላይም ያልተረክናቸውን መልክተኞች (እንደላክን ላክንህ)..” ቁርአን 4፥164 በሰዎች ዘንድ የማይታወቁ አሏህ ﷻ ዘንድ ግን የሚታወቁ በርካታ ነብያት አሉ። አሏህ ዘንድ ለመታወቅ በርትቶ መስራት ትልቁ ስኬት ነው። የፍጡራን ሙገሳና እውቅና እዚህው ምድር ላይ የሚቀር ትርጉም አልባ ቅጽበት ነው። በምድር ባይታወቁም በሰማይ ከሚታወቁት አሏህ ያድርገን..! مجهولون في الأرض معروفون في السماء،!
Show all...
👍 51 18🥰 10
👍 26🥰 7
👍 23 7👏 4
◾️ ኢየሱስ የተከበረ መባሉ ፈጣሪ ያሰኘዋል? | ምላሽ - 13 🎙ኡስታዝ አቡ ሐይደር ___ https://t.me/Yahyanuhe
Show all...
◾️ኢየሱስ የአሏህ ቅርብ መሆኑ አምላክ ያደርገዋል? 🎙 ኡስታዝ አቡ ሐይደር ___ https://t.me/Yahyanuhe
Show all...
2👍 1
ከአሏህ ዘንድ መሆኑ ፈጣሪ ያደርገዋልን? https://vm.tiktok.com/ZMMBnvmt6/
Show all...
👍 20
የመጽሀፍ ቅዱስ ግጭቶች - 34 https://vm.tiktok.com/ZMMB6LoDB/
Show all...
👍 13
ማሪባ - ተምሳሌታዊ መንደር በአውስትራሊያ ጠራፋማ አካባቢዎች የምትገኝ ብዙም የማትታወቅ ማሪባ የምትባል ትንሽየ መንደር አለች። ዶክመንትሪው የሚያትተው በመንደሯ የሚኖሩ ሙስሊሞች ያሳለፉትን ታሪክ ነው። በፈገግታ ጀምሮኝ በእንባ እያጀበኝ ጨረስኩት። ከ100 አመት በፊት ከአልባኒያ ተሰደው የመጡ ሙስሊሞች እስካሁን ዲናቸውን አቆይተው ለልጅ ልጆቻቸው እንዴት እንዳስተላለፉት የሚዘግብ ዶክመንትሪ ነበር። በዚህ ሒደት ውስጥ ወንድሞቻቸው ከፍረውባቸዋል፣ ከቤተሰባቸው ጥቂት የማይባለውን በሚሽነሪ ተነጥቀዋል። ብዙ ድንግዝግዝ ገጥሟቸዋል። ... ጥቂቶች ግን በጽናት ዲኑን ይዘው ከነሱም አልፈው ለበርካቶች መስለም ምክንያት ሁነዋል። ከቤተሰባቸው ውስጥ የከፈሩባቸውን አስበው ሲያለቅሱ ውስጥን ይፈታተናል። ከዚያ ሁሉ መከራ በኃላ ግን በፍጹም አልተሰበሩም። እንደገና ተባብረው መነሳት ቻሉ። የከፈሉት መስዋዕትነት በጥቂት ደቂቃ ዶክመንትሪ ሲታይ ቀላል ይመስላል። የኖሩት ስቃይ ግን ሲያወሩት ከፊታቸው ይነበባል። ምን አስታወሰኝ?በየአካባቢያችን ይህንን ዲን ለኛ ለማስተላለፍ በአባቶቻችን የተከፈለው መስዋዕትነት እንዲሁ ቀላል አይደለም። በየቦታው ይዘገብ ቢባል ብዙ የኢማንና የትግል ትምህርቶችን የሚሰጡ ታሪኮችን መስማታችን አይቀርም። የሚያስጨንቀው ግን እኛስ ለልጆቻቸችን ይህንን ዲን ለማስተላለፍ እያደረግን ያለነው አስተዋፅኦ ምን ያክል ነው የሚለው ነው?ሰዎች አምነው እንዲድኑና ጀነትን እንዲያገኙ በመጨነቅ ለሌላው ህዝብ ያደረግነው ጥሪስ ምን ያክል ነው?መርሳት የሌለብን ግን በባከነችዋ እያንዳንዷ ጊዜያችን ልክ የምንቆጭበት ጊዜ እንደሚመጣ ነው። አሏህ ያሳውቀን፥ አሏህ ይገዘን..! ___ https://t.me/Yahyanuhe
Show all...
👍 66 11
በዚህ ረመዷን በእናንተ እና በጌታችሁ መካከል የሚቀር ሚስጥራዊ ስራን አስቀሩ፥ አሏህ ዘንድ እንጅ ማንም የማያውቀው መልካም ስራ..!
Show all...
64👍 19
የመጽሀፍ ቅዱስ ግጭቶች - 33 https://vm.tiktok.com/ZMMh5buyX/
Show all...
👍 17
በሚሴንጀር መልዕክትም ሆነ ቲክቶክ ንጽጽር ለማስተማር ላይቭ ስንገባ አንዳንድ ሰዎች ፈትዋ ይጠይቁናል። ብዙ ሰው የንጽጽር ተማሪ በቀላሉ ፈትዋ መስጠት የሚችል ይመስለዋል። ፈትዋ እውቀትና ጥንቃቄ የሚፈልግ ባለቤትም ያለው መስክ ነው። ፈትዋ የሚሰጠው ዑለማ ብቻ ነው፣ እኛ እስልምና ላይ በሚነሱ ሹበሀዎች ላይ መልስ የምንሰጥ የንጽጽር ተማሪዎች ብቻ ነን። አጋጣሚ ትላንትናም ቲክቶክ ላይቭ ላይ አንድ ሰው ሲጠይቀኝ እሱም ሆነ ሌላ ሰው ጥያቄያቸውን ለሸይኽ ሙሐመድ ዘይን ዘህረዲን እንዲጠይቁ ተናገርኩ፤ እንዴት እንደሚያገኟቸው ግን አልተናገርኩም ነበር። ይህንን ፍቃድ ለመጠየቅ በማሰብ ላይቭ ሲገቡ ድንገት ስላየሁ ጠየቅኳቸው። ስልካቸውን ለፈለገ ሰው ሁሉ እንድሰጥ ነገሩኝ፥ እንዲያ ከሆነ እንደሚቸገሩ ሀሳብ ባነሳም "በፍጹም" አሉኝ። ሰዎች ፈትዋ ፈልገው የሚደውሉት ያስጨነቃቸው ጉዳይ በመኖሩ መሆኑን ጠቅሰው እንደፈለጉ ደውለው ወይንም በዋትስአፕ በኩል መጠየቅ እንደሚችሉ ገለጹ። ባይሆን እኩለ ሌሊት የሚደውሉ ሰዎች ስላሉ ሰአቱን ቀይረው ቀን ቢያደርጉላቸው እንደሚሻላቸው አነሱ። የሚገርመው ግን እኩለ ሌሊት ቢደወል እራሱ ከእንቅልፋቸው ተነስተው ፈትዋ እንደሚሰጡ ጠቅሰዋል። ይህንን ስናወራ እራሱ ፊታቸው ላይ ከፍተኛ ድካም ይታያል። አሏህ እድሜያቸውን ያርዝምልን። ይኸው ስልካቸው፣ በዋትስአፕም መጠየቅ ትችላላችሁ፦ +251932232390
Show all...
👍 81 21
እውን እስልምና የመዳን ዋስትና የለውም? https://vm.tiktok.com/ZMMrTVJkR/
Show all...
👍 18
በብዛት የምትጠቀሙትና ለንጽጽር ስራዎች ቅርባችሁ እንደሆነ የምታምኑት አፕልኬሽን የቱ ነው? ትምህርቶችስ በዋናነት በየትኛው የማኅበራዊ ሚዲያ አፕ በኩል ቢለቀቅ ትመርጣላችሁ?በተጨማሪም በጹሁፍ ማንበብ ወይንስ በቪዲዮ መመልከት ይቀላችኃል?Anonymous voting
  • ፌስቡክ
  • ቴሌግራም
  • ቲክቶክ
  • በጹሁፍ ማንበብ እመርጣለሁ
  • ቪዲዮ መመልከት ይሻለኛል
0 votes
👍 36
እዚህ ውስጥ ብዙ ወንጀሎች አሉ። ዳሩ ግን የጴንጤ ባለስልጣናት ላይ እየሄዱ መጸለይ ግለሰቡን ከህግ በላይ ያደረገው ይመስላል..! https://vm.tiktok.com/ZMMrFmXVA/
Show all...
😱 13👍 9
በዛውያ ቲቪ የሚተላለፈውን የሀሩን ሚዲያ "ጀዛከሏህ" የተሰኘ ፕሮግራም ኢፍጣር ሰአት ላይ ከቤተሰብ ጋር እተመለከትን ነበር። ከመላው ኢትዮጵያ የተሰባሰቡ 400 ደረሳዎችን ስለሚያቀሩ ወጣት ሸይኽና ዓሊም አስመልክቶ የተዘጋጀ መሰናዶ ነው። ሸይኽ ሙሐመድ ጁድ የዓሊም ልጅ ዓሊም ናቸው። ከምንም በላይ ግን መድረሳው እንዳይበተን በመጨነቅ ከማስተማር አልፈው ለተማሪዎች ምግብ ፍለጋ የሚያደርጉት ድካም እንዴት ልብ ይሰብራል?የነገ 400 ዓሊሞችን ምግብ መመገብ የሚቸግር አቅም ማጣት እንዴት ውስጥን ይረብሻል..?! ኡስታዝ አብዱረሕማን ሱልጣንን ጨምሮ የሀሩን ሚዲያ ባልደረቦች ከሸይኹ ጋር በመነጋር መድረሳውን በአቅማችን እንደ ሙስሊም የምንረዳበትን መንገድ ማመቻቸት ቢቻል እጅግ በጣም ትልቅ እመርታ ነበር። ኢንሻአላህ ስራው ከተጀመረና ከተፈለግኩ ለማስተባበርና በተፈለግኩበት ለማገዝ ሙሉ ፍቃደኛ ነኝ። #ረመዷን_2
Show all...
👍 85 6
የመጽሀፍ ቅዱስ ግጭቶች #32 https://vm.tiktok.com/ZMMM9wNWs/
Show all...
👍 13
Sign in and get access to detailed information

We will reveal these treasures to you after authorization. We promise, it's fast!