ru
Feedback
የሕያ ኢብኑ ኑህ | Yahya Ibnu Nuhe

የሕያ ኢብኑ ኑህ | Yahya Ibnu Nuhe

Открыть в Telegram

﷽ | Muslim | Theology | Comparative Religion | Philosophy | Student | ለንግድ፣ ለህክምና ወይም ለጉብኝት ወደ ቱርክ፣ ዱባይ እና የተለያዩ ሀገራት ለመጓዝ ካሰባችሁ ፈሲሩ ትራቭል የትኬት ጉዳያችሁን በኃላፊነት ያጠናቅቃል። እንግልት የሌለበት ጉዞ ለማድረግ ስትፈልጉ በዋትስአፕ አግኙን፦ https://wa.me/qr/5CWCIMYBZLCJB1

Больше

📈 Аналитический обзор Telegram-канала የሕያ ኢብኑ ኑህ | Yahya Ibnu Nuhe

Канал የሕያ ኢብኑ ኑህ | Yahya Ibnu Nuhe (@yahyanuhe) языкового сегмента Амхарский является активным участником. Сейчас сообщество объединяет 21 276 подписчиков, занимая 3 608 место в категории Религия и духовность и 1 607 место в регионе Эфиопия.

📊 Показатели аудитории и динамика

С момента создания невідомо проект демонстрирует стремительный рост, собрав аудиторию из 21 276 подписчиков.

Согласно последним данным от 28 августа, 2026, канал показывает стабильную активность. За последние 30 дней изменение числа участников составило 4, а за последние 24 часа — -2, при этом общий охват остаётся высоким.

  • Статус верификации: Не верифицирован
  • Уровень вовлечённости (ER): Средний показатель вовлечённости аудитории составляет 20.81%. В первые 24 часа после публикации контент обычно набирает 7.21% реакций от общего числа подписчиков.
  • Охват публикаций: В среднем каждый пост получает 4 428 просмотров. В течение первых суток публикация набирает 1 533 просмотров.
  • Реакции и взаимодействия: Аудитория активно поддерживает контент: среднее количество реакций на один пост — 65.

📝 Описание и контентная политика

Автор описывает ресурс как площадку для выражения субъективного мнения:
﷽ | Muslim | Theology | Comparative Religion | Philosophy | Student | ለንግድ፣ ለህክምና ወይም ለጉብኝት ወደ ቱርክ፣ ዱባይ እና የተለያዩ ሀገራት ለመጓዝ ካሰባችሁ ፈሲሩ ትራቭል የትኬት ጉዳያችሁን በኃላፊነት ያጠናቅቃል። እንግልት የሌለበት ጉዞ ለማድረግ ስትፈልጉ በዋትስአፕ አግኙን፦ https://wa.me/qr/5CWCIMYBZLCJB1

Благодаря высокой частоте обновлений (последние данные получены 29 августа, 2026) канал поддерживает актуальность и высокий уровень охвата публикаций. Аналитика показывает, что аудитория активно взаимодействует с контентом, что делает его важной точкой влияния в категории Религия и духовность.

21 276
Подписчики
-224 часа
-97 дней
+430 день
Архив постов
በ20ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ ላይ በሚሽነሪዎች ዓለም ከተፈጠሩት እጅግ አወዛጋቢና የረቀቁ ስትራቴጂዎች አንዱ "የውስጥ እንቅስቃሴ" (The Insider Movement - IM) የተሰኘው ስልት ነው። የዚህ ስልት ዋነኛ ፍልስፍና "አንድ ሙስሊም ክርስቲያን ለመሆን ዲናዊ የነበረውን አኗኗሩን፣ ማህበረሰቡንና ሃይማኖታዊ መለያውን መተው የለበትም" የሚል ነው። ከዚህ ቀደም ሰዎች እምነታቸውን ሲቀይሩ ስማቸውን ለአብነት ከ'መሀመድ' ወደ 'ጳውሎስ' ይቀይራሉ፣ ከመስጊድ ወጥተው ወደ ቤተክርስቲያን ይሄዳሉ። ይህ ግን በማህበረሰቡ ዘንድ መነጠልንና ከፍተኛ ተቃውሞን ስለፈጠረባቸው፣ አዲሱ ስልት ሰውዬው ራሱን "ሙስሊም" ብሎ እየጠራ፣ ነገር ግን በውስጡ የክርስትናን ዶክትሪን ተሸክሞ በማህበረሰቡ ውስጥ "የውስጥ አርበኛ" ሆኖ እንዲቀጥል የሚያደርግ የረቀቀ የስነ-ልቦና ስልት ነው። ​ይህ ስልት መሬት ላይ እንዴት እንደሚተገበር የሚያሳየውን የመጀመሪያውን ተጨባጭ ምሳሌ እንመልከት፦ "የኢሳ ተከታይ ሙስሊሞች" (Messianic Muslims) የሚባለው አደረጃጀት ነው። በእነዚህ ሚሽነሪዎች የተጠመቀ አንድ ሙስሊም፣ የሙስሊም ስሙን አይቀይርም፣ የቀድሞ አለባበሱን አይተውም፣ አልፎ ተርፎም በቀን አምስት ጊዜ ወደ መስጂድ መሄዱን እና በረመዳን መጾሙን ሁሉ እንዲቀጥል ይደረጋል። ሆኖም መስጂድ ውስጥ ግንባሩን መሬት ላይ አስደግፎ ሱጁድ ሲያደርግ፣ ዱዓውን የሚያደርገው በአዲሱ ሚስጥራዊ እምነቱ መሠረት ለ"ጌታ ዒሳ" (ኢየሱስ) ነው። ሲጠየቅም "እኔ ክርስቲያን አይደለሁም፤ እኔ ዒሳ አል-መሲህን የምከተል ሙስሊም ነኝ" ይላል። ጆን ትራቪስ የተባለው ታዋቂው ሚሽነሪ ባዘጋጀው የስልት መለኪያ (C1-C6 Spectrum) መሠረት፣ ይህ 'C5' የተባለው ከፍተኛው የስውርነት ደረጃ ሲሆን፣ ማህበረሰቡ ሰውዬውን እንደ አንድ ጽኑ ሙስሊም ሲያየው፣ እሱ ግን በውስጡ የክርስትናን አስኳል ተሸክሞ ሌሎችን በድብቅ ይመለምላል። ​ሁለተኛውና እጅግ አስደንጋጩ ምሳሌ ደግሞ በአንዳንድ የእስያና የአፍሪካ ሀገራት የተሞከሩት "መስጊድ-መሰል ማምለኪያ ስፍራዎች" (Contextualized Worship Spaces) ናቸው። በዚህ ስልት መሰረት፣ ሚሽነሪዎቹ የሚተክሉት ቤተክርስቲያን ከውጭ ሲታይ መስቀል የሌለውና ልክ እንደ መስጂድ የተቀረጸ ነው። ውስጥ ሲገባ ምንጣፍ ተነጥፏል፤ ተሳታፊዎቹ ጫማቸውን አውልቀው፣ ወንዶችና ሴቶች ተለያይተው ይቀመጣሉ። አምልኮው የሚመራው "ፓስተር" በማይባል ነገር ግን "ሸይኽ" ወይም "ኢማም" በሚባል መሪ ነው። መጽሐፍ ቅዱስን የሚያነቡት ልክ ቁርዓን እንደሚቀራው በሚስብ የ"ቲላዋ" አይነት ዜማ ነው። መዝሙራቸውም በአካባቢው በሚታወቁ ኢስላማዊ የቃላት አወቃቀር ያለው የዚክር ዓይነት ነው። አንድ ተራ ሙስሊም አጋጣሚ በሩን ከፍቶ ቢገባ መስጊድ ውስጥ ያለ እንጂ ቤተክርስቲያን የገባ አይመስለውም። ይህ የሃይማኖቶች ድንበር ሙሉ በሙሉ የፈረሰበት ስልት፣ እስልምናን በራሱ መለያዎች በመጠቀም ከውስጥ ለመቦርቦር የተነደፈ ነው። ​የዚህ "የውስጥ እንቅስቃሴ" ታላቁ አደጋ ማህበረሰቡን ስነ-ልቦናዊ ግራ መጋባት ውስጥ መክተቱ ነው። ማህበረሰቡ 'ይህ የኛ ነው ወይስ የነሱ?' የሚለውን መለየት እስኪያቅተው ድረስ ድንበሩ ይደበዝዛል። ሚሽነሪዎቹ የሰውን ልጅ መንፈሳዊ ማንነት ልክ እንደ ኮምፒውተር ሶፍትዌር ሃርድዌሩን (የውጪውን ሙስሊም ገጽታ) ሳያስነኩ፣ ሶፍትዌሩን (የውስጡን እምነት) በመቀየር ማህበረሰቡ የራሱን በሽታ መከላከል እንዳይችል ያደርጉታል። ረቢካ ሉዊስ የተባለችው የሚሽነሪ ስትራቴጂስት እንደጻፈችው፣ "ግቡ ሰዎችን ከእስልምና ማውጣት ሳይሆን፣ እስልምናን በክርስቶስ ማጥለቅለቅ ነው" ትላለች። ይህ እጅግ የተራቀቀ የማንነት ጠለፋ፣ ትውልድን ያለ ጦርነት የማተራመስ አላማ በጸጥታ ያነገበ የትሮጃን ፈረስ ነው። ​የመረጃ ምንጮች፦ - ​Rebecca Lewis, "Promoting Movements to Christ within Natural Communities". - ​John Travis, "The C1 to C6 Spectrum: A Practical Tool for Defining Six Types of Christ-Centered Communities Found in the Muslim Context". በቀጣዩ ክፍል በአላህ ፍቃድ የምንዳስሰው አጀንዳ፦ የወጣቱን አእምሮ መቆጣጠር እንዲቻል የተነደፈውን የዘመናዊ ትምህርት ስልትና ዩኒቨርሲቲዎችን እንደ ምልመላ ማዕከል የመጠቀምን ስትራቴጂን (Campus Crusades and Education) በቀጣይ ክፍል - 17 በአላህ ፍቃድ እንመለከተዋለን። ያለፉትን ክፍሎች ለማንበብ

photo content

በቅርቡ የምክክር ኮሚሽኑ በሀገራችን የዘመን አቆጣጠር ላይ ሲውል የነበረውን እና ሃይማኖታዊ አንድምታ ያለውን "ዓ.ም." (ዓመተ ምህረት) በመተው፣ ሁሉንም አቃፊና ገለልተኛ እንደሚሆን በተስማሙበት "ዓ.ል." (ዓመተ ልደት) ወይም "እ.ኢ.አ." (እንደ ኢትዮጵያ አቆጣጠር) እንሸጋገር የሚል ሀሳብ አቅርቧል። ይህን ተከትሎ ግን በአንዳንድ የኦርቶዶክስ እምነት አክቲቪስቶች ዘንድ ሰማይ ምድሩን የሚያቀልጥ ጩኸት እየሰማን ነው። አንዳንዶችም "ለምን የኛን ተውት ትላላችሁ? ሂጅራስ ለምን ሆነ?" እያሉ እያማረሩ ነው። ​እዚህ ላይ ግን በግልጽ መነጋገር ያለብን እጅግ አስገራሚ ደብል ስታንደርድ አለ። ​በመጀመሪያ ደረጃ፣ ሙስሊሙ የራሱ የሆነ የ"ሂጅራ" ዘመን አቆጣጠር አለው። ሂጅራ የሚያመለክተው የነብዩ ሙሐመድን (ሰ.ዐ.ወ) ከጥቃት ለመሸሽ ያደረጉትን ታሪካዊ ስደት እንጂ፣ በማንም እምነት ላይ ጣልቃ የሚገባ (ቲዮሎጂያዊ) ትርክት የለውም። ይህን የሂጅራ አቆጣጠር "የኛን አይወክልም" በማለት እንዳንጠቀምበት ሲያወግዙ የነበሩ ወገኖች፣ ዛሬ ላይ ደግሞ ተመልሰው "ሙስሊሙን ጨምሮ ሁሉም ሰው 'ዓመተ ምህረት' ብሎ ካልጠራ ሞቼ እገኛለሁ" ማለታቸው የግብዝነት ጥግ ነው። የራስህን ሃይማኖታዊ መለኪያ በሌላው ላይ መጫን መብት አይደለም! ፈልገህ "ዓ.ም" ብለህ መጠቀም መብትህ እንደሆነው ሁሉ፣ የሌላውን አለመጠቀምም ማክበር ግዴታህ ነው። ​እኛ ሙስሊሞች "ዓ.ም" (ዓመተ ምህረት) የሚለውን ለምን አንቀበለውም? ይህ ጉዳይ ከእልህ ወይም ከፖለቲካ ሳይሆን፣ ቀጥታ ከእስልምና ዐቂዳ ጋር የሚያያዝ ነው። እስልምና የነብዩላህ ዒሳን ድንቅ አፈጣጠር ይቀበላል። ነገር ግን "ዓመተ ምህረት" ሲባል ከጀርባው ያለው ሃይማኖታዊ እሳቤ በእስልምና ፍጹም ተቀባይነት የለውም። ለምን የሚለውን በአጭሩ እንመልከት፦ በክርስትና አስተምህሮ "ዓመተ ምህረት" ማለት የሰው ልጅ በአዳም ኃጢአት ምክንያት እርግማን ላይ ወድቆ ስለነበር፣ ኢየሱስ ተወልዶና በመስቀል ላይ ሞቶ የሰውን ልጅ ኃጢአት ተሸክሞ "ምህረት አወረደ" ከሚል እሳቤ የመነጨ ነው። ​እስልምና "የአዳም ኃጢአት ለትውልድ ይተላለፋል (Original Sin)" የሚለውን ጽንሰ-ሀሳብ ሙሉ በሙሉ ውድቅ ያደርጋል። ቁርኣን በግልጽ "ማንም ነፍስ የሌላዋን ነፍስ ኃጢአት አትሸከምም" ይላል። እያንዳንዱ ሰው ንጹሕ ሆኖ ነው የሚወለደው። ​በእስልምና ምህረት (መግፊራ) የሚገኘው በቀጥታ ወደ አላህ በመጸጸት እንጂ፣ በማንም ነብይ መሰቀልም ሆነ ደም መፍሰስ አይደለም። ዒሳ (ዐ.ሰ) ታላቅ ነብይ እንጂ፣ ተሰቅሎ የሰውን ልጅ ኃጢአት የተሸከመ አዳኝ አይደለም። ​ስለዚህ አንድ ሙስሊም "ዓመተ ምህረት" ብሎ በሚጽፍበት ወይም በሚናገርበት ጊዜ፣ ይህንን የክርስትናን ሥነ-መለኮት እንደተቀበለ ይቆጠራል። ለዚህ ነው ሙስሊሙ ይህን ቃል መጠቀም በሸሪዓ የማይፈቀድለት። ​መፍትሔው ምንድን ነው? ሀገር የጋራ ናት። ሀገራዊ አሰራሮችም የሁሉንም ዜጋ እምነት የማያጋጩና ገለልተኛ መሆን አለባቸው። "ዓ.ል" (ዓመተ ልደት) ብንል፦ ዒሳ (ዐ.ሰ) መወለዱን ስለሚያመለክት፣ የቀኑ ጉዳይ ላይ ዝርዝር ሀተታውን ባንቀበልም በጥቅሉ ግን ሙስሊሙም ልደቱን ስለሚያምንበት ከማንም እምነት ጋር አይጋጭም። "እ.ኢ.አ" (እንደ ኢትዮጵያ አቆጣጠር) ብንል፦ አቆጣጠሩን ሃይማኖታዊ ከመሆን አውጥቶ ሀገራዊ እና የጋራ ያደርገዋል። ​የምክር ኮሚሽኑ ያቀረበው ሀሳብ ይህንን ልዩነት ያከበረ፣ ብዝሃነትን ያማከለ እና ማንም በሌላው እምነት ውስጥ ገብቶ እምነቱን እንዳያጎድል የሚጠብቅ የሰለጠነ ሀሳብ ነው። ክርስቲያን ወገኖቻችን በግላቸው፣ በቤተክርስቲያናቸውና በሰነዳቸው "ዓ.ም" ማለታቸውን ማንም አልከለከላቸውም። ነገር ግን በጋራ ሀገራዊ ሰነዶች ላይ የኔን እምነት ትርክት ሙስሊሙም ይጋራው ብሎ ማስገደድ፣ ከፍትህም ሆነ ከአብሮነት ያፈነገጠ ፅንፈኝነት ነው! ፌስቡክ | ዋትስአፕ

photo content

እፎይ የተሰኘው የካራ እምነት ተከታይ በሰሒሕ ሙስሊም ላይ የሰፈረውን ይህንን ሐዲስ አንስቶ ያቀረበው ትችት፣ የአላህን መሐሪነትና የሰውን ተፈጥሮ በቅጡ ካለመረዳት የመነጨ ነው። ሐዲሱ እኮ ሰዎችን ለኃጢአት የሚያነሳሳ ሳይሆን፣ በተቃራኒው ተስፋ መቁረጥን የሚያክም ታላቅ ነብያዊ መድኃኒት ነው። የሰው ልጅ እንደ መላእክት ኃጢአት የማይሠራ ፍጹም ፍጡር ሆኖ አልተፈጠረም፤ ስህተት ሰርቶ መመለስ የሚችል ነጻ ፍቃድ የተሰጠው ፍጡር ነው። አላህ እጅግ መሐሪ በመሆኑ፣ ይህ መለኮታዊ ባሕሪው ይቅርታ ጠያቂዎችን በምህረት የሚመለከትበት ማንነቱ ነው። ሰዎች ፈጽሞ የማይሳሳቱ ቢሆኑ ኖሮ፣ የመላእክትን ባህሪ ይላበሱ ነበር እንጂ የሰው ልጅ የመፈጠሩ ዓላማ በተግባር ባልታየ ነበር። ስለዚህ ሐዲሱ "ኃጢአት ሥሩ" እያለ ሳይሆን፣ "ብትሳሳቱም የአላህ እዝነት ከኃጢአታችሁ ይሰፋልና በተስፋ ወደ እርሱ ተመለሱ" የሚል የጠለቀ የውዴታና የተስፋ ቋንቋ ነው። [1] ​ይህ ግለሰብ ይህንን መለኮታዊ የእዝነት ቋንቋ ከማጣጣሉ በፊት፣ እስኪ የራሱን መጽሐፍ ቅዱስ ቢያስተውለው ኖሮ ልክ እንደ ሐዲሱ ዓይነት ተመሳሳይ ትምህርት ባገኘበት ነበር። ኢየሱስ በሉቃስ ወንጌል ላይ፦ "ንስሐ ከማያስፈልጋቸው ከዘጠና ዘጠኝ ጻድቃን ይልቅ ንስሐ በሚገባ በአንድ ኃጢአተኛ በሰማይ ደስታ ይሆናል" በማለት ያስተምራል። [2] ታዲያ መጽሐፍ ቅዱስ "ከጻድቃን ይልቅ በኃጢአተኛው ንስሐ በሰማይ ትልቅ ደስታ ይሆናል" ሲል፣ አምላክ ሰዎች ጻድቅ ከመሆን ይልቅ ኃጢአት እንዲሠሩ ይፈልጋል ማለት ነውን? ብለን ብንጠይቀው አይደለም እንደሚል ግልጽ ነው፤ የንስሐን እና የምህረትን ታላቅነት ማሳየቱ እንደሆነ ማብራራቱ አይቀርም። ​ታዲያ ለራሱ መጽሐፍ ሲሆን "የፈጣሪ ጸጋ መገለጫ ነው" ብሎ የሚያስተምረውን ሎጂክ፣ በእስልምና አስተምህሮ ላይ ሲያገኘው ለምን ጠማማ ትርጉም ይሰጠዋል? ይህ ጥላቻ የፈጠረው ግልጽ የሚዛን መሳት ነው። እስልምና የሰው ልጅን ደካማ ተፈጥሮ በሚገባ ስለሚያውቅ፣ ኃጢአት ቢሠራ እንኳ በጸጸት ርቆ እንዳይቀር የይቅርታን በር ወለል አድርጎ ይከፍትለታል። ይህንን ታላቅ የአላህ እዝነት በማጣመም ከሚሳለቅ፣ "ኃጢአት ሰርተን ንስሐ ከገባን፣ ንስሐ ከማያስፈልጋቸው ዘጠና ዘጠኝ ጻድቃን በላይ በሰማይ ትልቅ ደስታ እንፈጥራለን" የሚለውን የራሱን መጽሐፍ ቅዱስ ቃል እኩል ቢተቸው ኖሮ ቢያንስ ለሎጂኩ ታማኝ መሆኑን ባሳየ ነበር። ​የግርጌ ማስታወሻዎች፦ [1] ሰሒሕ ሙስሊም፣ ሐዲስ ቁጥር 2749። [2] መጽሐፍ ቅዱስ፣ የሉቃስ ወንጌል፣ ምዕራፍ 15፣ ቁጥር 7 ፌስቡክ | ዋትስአፕ

አላህ የፍጥረታትን መጨረሻ አስቀድሞ ያውቃል። ይህ መለኮታዊ ዕውቀቱ ፍጹም መሆኑን ያሳያል። ነገር ግን "አስቀድሞ አወቀ" ማለት "አስገድዶ አሠራ" ማለት አይደለም። ለምሳሌ፣ አንድ ብቁ መምህር የትኛው ተማሪው እንደሚያልፍና የትኛው በስንፍናው ምክንያት እንደሚወድቅ አስቀድሞ ሊያውቅ ይችላል፤ ወረቀት ላይም ሊጽፈው ይችላል። ተማሪው ሲወድቅ ግን የወደቀው መምህሩ አስቀድሞ ስላወቀና ስለጻፈው ሳይሆን፣ የራሱ ምርጫና ስንፍና ስላመጣበት ነው። አላህም ሰዎች በነጻ ምርጫቸው ምን እንደሚሠሩ አስቀድሞ ያውቃል፤ አዋቂነቱ ግን የሰዎችን ነጻ ምርጫ አይነጥቅም። አስተያየት ሰጪው ያነሳው ጥያቄ አዲስ አይደለም፤ ከ1400 ዓመታት በፊት ታላላቆቹ ሰሐባዎች ልክ እንደዚሁ ነብዩን (ﷺ) ጠይቀዋቸው ነበር። "የአላህ መልእክተኛ ሆይ! መጨረሻችን አስቀድሞ የታወቀ ከሆነ፣ ለምን ሥራን ትተን በውሳኔያችን ላይ ብቻ አንደገፍም?" አሏቸው። የነብዩ (ﷺ) ምላሽ እጅግ ድንቅ እና ሎጂካዊ ነበር፦ "ሥሩ! (መልካም ተግባርን ፈጽሙ)፤ ሁሉም ሰው ለተፈጠረለት (ለተዘጋጀለት) ነገር ይገራል (ይመቻችለታል)።" [1] ​ይህ ማለት፣ አንተ የጀነት ሰዎች ከሚሠሩት መልካም ተግባር ጋር ራስህን ካገኘኸው፣ አላህ ለጀነት እያገራህ መሆኑን ታውቃለህ ማለት ነው። የገሀነም ሰዎች መጨረሻቸው የማይታወቀው እኮ፣ በምርጫቸው የገሀነምን ተግባር (ክህደትንና አመጽን) ስለፈጸሙ ነው። ስለዚህ አንድ ሙስሊም "ለገሀነም አለመወሰኔን በምን አወቅኩ?" ብሎ ተስፋ አይቆርጥም፤ ይልቁንም በአላህ እዝነት ተስፋ እያደረገ ወደ ጀነት የሚያደርሰውን ተግባር ይፈጽማል። ​ይህ አስተያየት ሰጪ የራሱን መጽሐፍ ቅዱስ በቅጡ ቢያነብ ኖሮ፣ ይህንን የ"ቀደር" ጽንሰ-ሀሳብ ነቅፎ ባልተሳለቀ ነበር። መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ጳውሎስ፣ እግዚአብሔር አንዳንዶችን አስቀድሞ ለጥፋት እንዳዘጋጃቸው በግልጽ ጽፏል። ​ወደ ሮሜ ሰዎች በተጻፈው መልእክት ላይ እንዲህ ይላል፦ "ሸክላ ሠሪ ከአንዱ ጭቃ ክፍል አንዱን ዕቃ ለክብር አንዱንም ለውርደት ሊሠራ በጭቃ ላይ ሥልጣን የለውምን?... እግዚአብሔር ቁጣውን ሊያሳይ ኃይሉንም ሊገልጥ ወዶ፥ ለጥፋት የተዘጋጁትን የቁጣ ዕቃዎች በብዙ ትዕግሥት ከቻለ... እንግዲህ ምን እንላለን?" [2] ​እንግዲህ አስተውሉ! መጽሐፍ ቅዱስ ራሱ ፈጣሪ "ለጥፋት (ለገሀነም) የተዘጋጁ የቁጣ ዕቃዎች (ሰዎች)" እንዳሉ እየተናገረ፣ ተቺው ግን ሶሒሕ ሙስሊምን ጠቅሶ እስልምናን ይተቻል። ታዲያ በእሱ ሎጂክ መሠረት አጸፋዊ ጥያቄ እናንሳለት፦ "መጽሐፍ ቅዱስህ ለጥፋት የተዘጋጁ ዕቃዎች አሉ ካለ፣ አንተ ራስህ ለጥፋት ከተዘጋጁት የቁጣ ዕቃዎች መካከል አለመሆንህን በምን አወቅክ?" ማጠቃለያ የአላህን ዘላለማዊ ዕውቀትና የሰውን ልጅ ነጻ ምርጫ ማመዛዘን የጠለቀ ዲናዊ እውቀትን ይጠይቃል። እስልምና የሰው ልጅ በተስፋና በፍርሃት መካከል ሆኖ የጌታውን እዝነት እንዲሻ ሲያስተምር፣ ተቺዎች ግን የራሳቸውን መጽሐፍ ድንጋጌ ዘንግተው እንዲህ በከንቱ ትችት ይወድቃሉ። ​የግርጌ ማስታወሻዎች፦ [1] ሶሒሕ አል-ቡኻሪ፣ ሐዲስ ቁጥር 6605፤ እንዲሁም ሶሒሕ ሙስሊም 2647 [2] መጽሐፍ ቅዱስ፣ ወደ ሮሜ ሰዎች፣ ምዕራፍ 9፣ ከቁጥር 21-22 ፌስቡክ | ዋትስአፕ

photo content

ክርስቲያን ወገኖች "ጅን"ን በተመለከተ ባለው የእስልምና አስተምህሮት ዙሪያ የሚሳለቁት፣ ቃሉን ከራሳቸው የ"ጋኔን" (እርኩስ መንፈስ) ትርጓሜ ጋር በማምታታት ነው። በክርስትና አስተምህሮ ጋኔን ማለት ወደ ንስሐ የማይመለስና የወደቀ እርኩስ መንፈስ ነው። "ታዲያ ከእርኩስ መንፈስ ጋር እንዴት ወንድማማችነት ይፈጠራል?" ብለው መገረማቸው የዚሁ የተሳሳተ መነጽር ውጤት ነው። ​እውነታው ግን እጅግ የተለየ ነው። በእስልምና ጅን ማለት ልክ እንደ ሰው ልጅ ነጻ ፍቃድ የተሰጠው፣ የሚያስብ እና የራሱ ምርጫ ያለው ፍጡር ነው። በመሆኑም ከነሱ ውስጥ አላህን የሚያመልኩ ደጋጎች እንዳሉ ሁሉ፣ የሚያምፁ እርኩሳንም (ሰይጣናት) አሉ። እስልምና በእምነት "ወንድሞቻችን" የሚለው እነዚያን ፈጣሪያቸውን አውቀው በጎ መንገድን የመረጡትን አማኝ ጅኖችን እንጂ፣ አጥፊዎቹን አጋንንት አይደለም። ወንድማማችነት የሚገነባው በአምልኮ አንድነት እንጂ፣ በፍጡርነት የዘር ሐረግ አይደለም። ​ይህንን ሀሳብ የሚያጣጥሉ ወገኖች፣ ራሳቸውን መጽሐፍ ቅዱስ ላይ ቢመዝኑት ተመሳሳይ ሎጂክ ያገኛሉ። በራእይ ዮሐንስ ምዕራፍ 22 ቁጥር 9 ላይ፣ ዮሐንስ ላናገረው መልአክ ሊሰግድለት ሲል፣ መልአኩ እንዲህ ብሎ ገሰጸው፦ "እንዳታደርገው ተጠንቀቅ፤ ከአንተ ጋር ከወንድሞችህም ከነቢያት ጋር... አብሬ ባሪያ ነኝ፤ ለእግዚአብሔር ስገድ።" ​እዚህ ላይ መሠረታዊ ጥያቄ እናንሳ፤ መጽሐፍ ቅዱስ በአይን የማይታይ መንፈሳዊ ፍጡር የሆነውን "መልአክ" የሰው ልጆች "ወንድምና አብሮ ባሪያ" መሆኑን ካረጋገጠ፣ እስልምና ነጻ ፍቃድ ኖሯቸው አላህን የሚያመልኩ መንፈሳዊ ፍጡራንን (አማኝ ጅኖችን) "የእምነት ወንድሞቻችን ናቸው" ሲል ለምን እንግዳ ይሆንባቸዋል? ትምህርቱ እጅግ ግልጽ ነው፤ በፈጣሪ ፊት የየትኛውም ፍጡር ክብርና ዝምድና የሚለካው፣ ለጌታው ባለው ፍጹም ታዛዥነት እንጂ በተፈጠረበት አካል አይደለም! ተውሒድ (አምላክን በብቸኝነት ማምለክ) በሰዎችና በጅኖች መካከል ያለውን ልዩነት አፍርሶ የሚያስተሳስር ታላቅ የወንድማማችነት ዘለበት ነው! ፌስቡክ | ዋትስአፕ

photo content

የሰው ልጅ በተፈጥሮው ስሜታዊ ፍጡር ነው። በዘመናዊው የሥነ-ልቦና እና የፊዚዮሎጂ ሳይንስ እንደተረጋገጠው፣ በአካል መነካካት በሰውነታችን ውስጥ እንደ "ኦክሲቶሲን" እና "ዶፓሚን" ያሉ የቅርበት እና የስሜት መነሳሳትን የሚፈጥሩ ሆርሞኖች እንዲመረቱ ያደርጋል። ንክኪ በሁለት ሰዎች መካከል ያለውን ሥነ-ልቦናዊ የርቀት ግድግዳ የማፍረስ ከፍተኛ ኃይል አለው። ​እስልምና ይህንን የሰው ልጅ ተፈጥሯዊ ዝንባሌ (ፍትወተ-ሥጋ) በሚገባ ያውቃል። በመሆኑም ሎጂኩ እጅግ ግልጽ ነው፦ "አንድን አደጋ ለመከላከል፣ ወደ አደጋው የሚያደርሱትን መንገዶች በሙሉ መዝጋት ያስፈልጋል።" አንድ ሰው በሚያዳልጥ ጭቃ ላይ እየተንሸራተተ "አልወድቅም" ብሎ ማሰብ እንደማይችለው ሁሉ፣ የሰውን ልጅ ከተፈጥሯዊ ስሜቱ ጋር እያጋጩ "በንጹህ ልብ ከተደረገ ችግር የለውም" ማለት ምክንያታዊነት የጎደለው የዋህነት ነው። ለዚህም ነው እስልምና መጨባበጥን እንደ አንድ የዝሙት መግቢያ በመቁጠር አስቀድሞ በር የሚዘጋው። መጽሀፍ ቅዱስ በማቴዎስ ወንጌል፣ ምዕራፍ 5፣ ቁጥር 28 ፦ "ወደ ሴት ያየ ሁሉ የተመኛትም ያን ጊዜ በልቡ ከእርስዋ ጋር አመንዝሮአል"። ይላል። ​እዚህ ላይ አንድ መሠረታዊ ጥያቄ እናንሳ፤ መጽሐፍ ቅዱስ "ማየት" ብቻውን የልብን ንጽህና አጉድፎ ወደ "ልብ ዝሙት" ያደርሳል ብሎ ካመነ፣ ከእይታ በበለጠ እጅግ ጠንካራ ስሜትን የሚቀሰቅሰው "አካላዊ ንክኪ (መጨባበጥ)" እንዴት "በንጹህ ልብ" በሚል ሰበብ ችላ ሊባል ይችላል? እይታ ኃጢአት ከሆነ፣ መነካካት በሎጂክ ደረጃ የከፋ ነው። አላህ የሰው ልጅን የፈጠረ ጌታ እንደመሆኑ፣ ለሰው ልጅ የቱ እንደሚበጀው አስቀድሞ በማወቅ መከላከያ አጥርን አበጅቶለታል። እስልምና እጅግ ተግባራዊ (Practical) የሆነ ዲን ነው። በሽታው ከመጣ በኋላ መድኃኒት ከመፈለግ፣ በሽታው የሚመጣበትን መንገድ አስቀድሞ ማድረቅን የሚመርጥ መለኮታዊ ሀይማኖት ነው። ፌስቡክ | ዋትስአፕ

photo content

በአሜሪካ ሚቺጋን ግዛት የሪፐብሊካን ፓርቲ የፕራይመሪ ምርጫ ላይ የተከሰተው ታሪክ፣ ማንነቱን ለሚክድና ሃይማኖቱን ለዱንያ ጥቅም ለሚሸጥ ሁሉ ትልቅ ማስተማሪያ ነው። ​አሚር ሀሰን የተባለው ግለሰብ፣ ቀድሞ ሙስሊም የነበረና በኋላ ግን ሃይማኖቱን ቀይሮ ክርስቲያን መሆኑን ያወጀ ሰው ነው። ይህ ሰው በጽንፈኛ ፖለቲከኞች ዘንድ ተቀባይነትን ለማግኘት ሲል፣ እጅግ አክራሪ፣ ፀረ-ሙስሊምና ፀረ-ስደተኛ አቋሞችን ማንጸባረቅ ጀመረ። በዚህ የክህደት መንገዱም ከቀድሞው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ፣ ከኮንግረስ አፈ-ጉባኤ ማይክ ጆንሰን እና ከሴናተር ቲም ስኮት ሳይቀር ሙሉ ድጋፍን (Endorsement) አገኘ። በገንዘብም በኩል ከፍተኛ ዶላር በማሰባሰብ፣ "አሁንማ ማንም አያቆመኝም" ብሎ የተመካበት ጊዜ ነበር። ​ነገር ግን የአላህ (ሱ.ወ) ጥበብና ፍትህ አስገራሚ ነው። የቱንም ያህል ማንነትህን ብትክድና ሙስሊሞችን ብትጠላም፣ ፀረ-ሙስሊም የሆኑ ዘረኞች መቼም ቢሆን በሙሉ ልብ አይቀበሉህም። አሚር ክርስቲያን ነኝ ብሎ ቢምልም፣ ዘረኞቹ መራጮች ስሙ "አረብኛ/ሙስሊም" ስለሚመስል ብቻ አላመኑትም፤ ድምፃቸውንም ነፈጉት። ከዚህም በላይ አላህ ይህንን ግለሰብ ያዋረደውና መሳለቂያ ያደረገው በጠንካራ ተፎካካሪ እጅ አይደለም! ​አሚር የተሸነፈው ቶም ስሚዝ ለተባለ ግለሰብ ሲሆን፣ ይህ አሸናፊ ሰው፦ ⛳️ ​በፌስቡክ ገጹ 95 ብቻ ተከታዮች ፎሎወሮች ያሉት፣ ⛳️ ​ለምርጫው ከ2,000 ዶላር በታች ያወጣ፣ ⛳️ ​እና ከሁሉ በላይ ደግሞ "ከምርጫው ራሴን አግልያለሁ" ብሎ ላሳወቀና "ለሌላ እጩ ድምፃችሁን ስጡ" በማለት ቅስቀሳውን ላቆመ ሰው ነበር! ​ከምርጫው ራሱን ባገለለና ምንም ዓይነት የፖለቲካ ክብደት በሌለው ሰው መሸነፍ፣ ተራ ሽንፈት ሳይሆን ታሪክ የማይረሳው መለኮታዊ ውርደት ነው። እምነትን ሸጦ ክብርን ከሰው ልጆች መፈለግ መጨረሻው ኪሳራ ነው። ታላቁ ጌታችን አላህ በቅዱስ ቁርኣን ላይ፣ እውነተኛ ክብር ከማን ዘንድ እንደሚገኝ እንዲህ በማለት ያስጠነቅቃል፡- “እነዚያ ከምእምናን ሌላ ከሓዲዎችን ወዳጆች አድርገው የሚይዙ እነሱ ዘንድ ልቅናን ይፈልጋሉን ልቅናውም ሁሉ ለአላህ ብቻ ነው፡፡” — አን-ኒሳዕ (4:139) ​የሰዎችን ውዴታ ለማግኘት ሲባል የአላህን መንገድ መተው የሚያስከትለውን አሳፋሪ ውድቀት፣ ነቢዩ ሙሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) በሚከተለው ሐዲሳቸው እንደሚከተለው ገልጸውታል፡- ​"አላህን በማስቆጣት የሰዎችን ውዴታ የፈለገ ሰው፣ አላህም በእርሱ ላይ ይቆጣል፤ ሰዎችንም በእርሱ ላይ ያስቆጣበታል።" (ሱነን አል-ቲርሚዚ 2414) ​ሃይማኖቱን ሸጦ ዱንያን ለማግኘት የሞከረ፣ አላህ በዱንያም እንዲህ መሳለቂያ ያደርገዋል፤ የአኼራውም ዕጣ ፈንታ የከፋ ይሆናል። አላህ መጨረሻችንን ያሳምርልን፤ ማንነታችንንና እምነታችንን ጠብቀን፣ ለፈጣሪያችን ብቻ አድረን በክብር የምንኖር ያድርገን! ፌስቡክ | ዋትስአፕ

photo content

ክርስትናን በርግጥ የመሰረተው ማነው? ​ዛሬ በስፋት የሚታወቀው የክርስትና ሃይማኖት ክርስቲያኖች እንደሚያምኑት በቀጥታ በኢየሱስ ክርስቶስ የተመሰረተ ሳይሆን፣ በጠርሴሱ ጳውሎስ የተቀረጸ መሆኑን የሚከ
ክርስትናን በርግጥ የመሰረተው ማነው? ​ዛሬ በስፋት የሚታወቀው የክርስትና ሃይማኖት ክርስቲያኖች እንደሚያምኑት በቀጥታ በኢየሱስ ክርስቶስ የተመሰረተ ሳይሆን፣ በጠርሴሱ ጳውሎስ የተቀረጸ መሆኑን የሚከራከሩ የታሪክና የነገረ-መለኮት ምሁራን አሉ። ጳውሎስ በሥጋ አይቶትም ሆነ አግኝቶት የማያውቀውን የኢየሱስን ታሪካዊ ህይወት ወስዶ፣ ኢየሱስም ሆነ የመጀመሪያዎቹ ደቀመዛሙርት ወደማያውቁት አዲስ የድነት ርዕዮተ-ዓለም ቀይሮታል። ከእርሱ በፊት ከነበሩት የኢየሱስ የቅርብ ተከታዮች ትምህርት የተለየ እና የሙሴን ህግጋት የሚሽር አዲስ ወንጌል ይዞ ብቅ ማለቱ፣ ከመጀመሪያዋ የኢየሩሳሌም አማኝ አባላት እና ከኢየሱስ ተከታዮች ጋር ከፍተኛ የሥነ-መለኮትና የስልጣን ሽኩቻ ውስጥ ከትቶት ነበር። ​ይህንን ሃሳብ ታዋቂው የታሪክ ምሁር ሃያም ማኮቢ በመጽሐፋቸው በሰፊው ዳስሰውታል። ማኮቢ እንዳብራሩት፣ የጳውሎስ ትምህርት ከንጹሑ የኢየሱስ አስተምህሮ የተገኘ ሳይሆን፣ በዘመኑ ከነበሩት የግሪክ ጣዖት አምልኮዎች የተቀዳና የኢየሱስን ትክክለኛ መሲህነት ያዛባ አዲስ ሃይማኖት ነው። በመሆኑም ዛሬ የምናየው ክርስትና የኢየሱስን ቀጥተኛ አስተምህሮ ሳይሆን፣ ጳውሎስ የራሱን ራእዮች እና አመለካከቶች ተጠቅሞ የፈጠረውን እምነት መሆኑን መገንዘብ እንችላለን። • Hyam Maccoby, The Mythmaker: Paul and The Invention of Christianity, Chapter 1: The Problem of Paul. . . ⛳️ በዚህ ጉዳይ እንቀጥላለን! ፌስቡክ | ዋትስአፕ

በአሜሪካ ሚቺጋን ግዛት የተመዘገበው የአብዱልረህማን አል-ሰይድ አስደናቂ ድል፣ በዲሞክራቶችም ሆነ በሪፐብሊካኖች ፓርቲ ውስጥ ከፍተኛ ድንጋጤን ከመፍጠሩም በላይ፣ የአሜሪካን የፖለቲካ ታሪክ አቅጣጫ በከፍተኛ ሁኔታ እየቀየረ ይገኛል። ​በአሜሪካ የጽዮናውያን ዋነኛ የፖለቲካ ደጋፊ እና ሎቢስት የሆነው "አይፓክ" እና አጋሮቹ፣ የአብዱልረህማንን ተቀናቃኝ ለማሳለፍ ብቻ 65 ሚሊዮን ዶላር አፍስሰው ነበር። ​ይህን ያህል የገንዘብ ጎርፍ ለምን አስፈለገ? ከተባለ መልሱ ግልጽ ነው፤ የአሜሪካን ግብር ከፋይ ገንዘብ፣ የጦር መሳሪያ እና በዓለም አቀፍ መድረክ ያላትን የ"ድምጽን በድምጽ የመሻር" መብት በመጠቀም በፍልስጤም ህዝብ ላይ እየፈጸሙ ያለውን የዘር ማጥፋት ያለከልካይ ለማስቀጠል ስለፈለጉ ነው። ​በደንብ አስቡት፣ አይፓክ በአንድ የሴኔት ወንበር ምርጫ ላይ የራሱን ተላላኪ ዕጩ ለማሳለፍ ብቻ 65 ሚሊዮን ዶላር አፈሰሰ። በመጨረሻ ግን... በሕዝብ ድምጽ ተሸነፈ! ​ይህ የምርጫ ውጤት ከአንድ ግለሰብ ማሸነፍ ባለፈ እጅግ ትልቅ ትርጉም አለው። ላለፉት ዓመታት የተፈጸመውን ጭ*ፍጨ*ፋ በቅርበት የተከታተለው ተራው አሜሪካዊ መራጭ፤ የሀገሩ ፖለቲካ በገንዘብ በሚገዙ የውጭ ሎቢስቶች ሳይሆን፣ በሕዝቡ ፍላጎት፣ እሴትና ህሊና እንዲመራ ያለውን ጽኑ አቋም አሳይቷል። ቀድሞ በጽዮናውያን ሎቢ (አይፓክ) መደገፍ ለአንድ ፖለቲከኛ ትልቅ የድል ካርድ ተደርጎ ይወሰድ ነበር። ዛሬ ግን በአብዛኛው የአሜሪካ ክፍል የነሱ ድጋፍ ማግኘት እንደ ትልቅ የፖለቲካ ኪሳራና ውርደት መቆጠር ጀምሯል። የትኛውም የውጭም ሆነ የሀገር ውስጥ የሎቢስቶች ጥረት ከተራው ዜጋ ድምጽ ሊበልጥ አይችልም። የሕዝብ ገንዘብም ንጹሃንን ለመጨፍጨፍ መዋል የለበትም። ​የአሜሪካ ሕዝብ ግብሩ እና ሀብቱ የውጭ ሀገር ጦርነቶችንና ጭፍጨፋዎችን የገንዘብ ድጋፍ ለማድረግ ሳይሆን፣ ለፍትህ እና ለራሱ ሕዝብ የተሻለ አገልግሎት ለመስጠት እንዲውል አጥብቆ እየጠየቀ መሆኑን የሚቺጋኑ ድል በግልጽ አሳይቷል። ገንዘብ የሕዝብን ድምጽ መግዛት ያቃተው ታሪካዊ አጋጣሚ! ፌስቡክ | ዋትስአፕ

በቁም እስር ላይ ያሉን የሰው ልጆች በአውሬዎች አስከብቦ ማስፈራራትና ማሰቃየት... ይህ በዚህ ዘመን የምንሰማው ሳይሆን በጨለማው ዘመን የነበሩ ጨካኝ ነገሥታት እንኳ ለማድረግ የሚከብዳቸው ተግባር ነው። ነገር ግን፣ ይሄ በ21ኛው ክፍለ ዘመን በእስራኤል ምድር ሊተገበር የታሰበ እውነታ ነበር። ​የእስራኤል የብሔራዊ ደህንነት ሚኒስትር የሆነው ኢታማር ቤን-ግቪር፣ ፍልስጤማውያን የፖለቲካ እስረኞች በሚገኙበት የኬትዚኦት እስር ቤት ዙሪያ፣ "አዞዎችን" በማስቀመጥ እስረኞቹን በከፍተኛ ፍርሃትና ሥነ-ልቦናዊ ስቃይ ውስጥ ለማኖር አውዛጋቢ እቅድ አውጥቶ ነበር። ታዲያ እቅዱ ለምን ተገታ? ​የእስራኤል ፍርድ ቤት እቅዱን በጊዜያዊነት ያገደው ግን፣ የታሳሪዎቹ መብት ተገፎ፣ የሰው ልጅ በአውሬ ሊበላ ይችላል በሚል ስጋት ወይንም "ሰብዓዊ መብት" ተሟጋቾች በፈጠሩት ጫና አይደለም። ​ይልቁንም፣ 'ሌት ዘ ኤኒማልስ ሊቭ' የተሰኘ የእንስሳት መብት ተሟጋች ቡድን ያቀረበውን አቤቱታ ተከትሎ ነው። ፍርድ ቤቱ እግዱን የጣለው፦ "ይህ አሰራር በአዞዎቹ (በእንስሳቱ) ላይ ጉዳት ሊያደርስ ይችላል" በሚል ስጋት ነው። ልብ የሚሰብረው እውነታ እዚህ ላይ ነው! ​ዓለም ለሰዎች ሰብዓዊ መብት መቆሙ ቀርቶ፣ ለእስራኤል ፍርድ ቤትም ሆነ ለመብት ተሟጋቾች፣ ከፍልስጤማውያን እስረኞች ሕይወትና ሥነ-ልቦናዊ ደህንነት ይልቅ፣ የአዞዎቹ ደህንነት በለጠባቸው! ​ሰውየው በመቶዎች የሚቆጠሩ የሰው ልጆችን ከቀን በቀን በአዞዎች አፍ ፊት ለማኖር ሲያቅድ፣ የዓለም ፍርድ ቤቶች የሚያስቡት ስለ እንስሳቱ እንጂ ስለ ፍልስጤማውያኑ አይደለም። ይህ በእውነት የእስራኤላውያንን ጭካኔ ብቻ ሳይሆን፣ ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ለፍልስጤማውያን ያለውን ግድየለሽነትና ደብል ስታንዳርድ ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ ነው። ይህ ግፍ ግን እንዲህ አይቀጥልም፣ በአላህ ፍቃድ ፍልስጤማውያን ይህንን ሰው* በ*ላ ስርኣት ገርስሰው በነጻነት የሚኖሩበት ቀን ሩቅ አይደለም! ፌስቡክ | ዋትስአፕ

photo content

የዘመኑ ምርጥ የዲፕሎማሲ ቀልድ! 🤣 ​የእስራኤሉ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጊዲዮን ሳዓር ሰሞኑን ቀልድ አምሮታል መሰል ለሚዲያ ቀርቦ እንዲህ ይላል፦ ​"ሰዎች እስራኤል በዓለም አቀፍ ደረጃ ተገልላለች
የዘመኑ ምርጥ የዲፕሎማሲ ቀልድ! 🤣 ​የእስራኤሉ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጊዲዮን ሳዓር ሰሞኑን ቀልድ አምሮታል መሰል ለሚዲያ ቀርቦ እንዲህ ይላል፦ ​"ሰዎች እስራኤል በዓለም አቀፍ ደረጃ ተገልላለች ይላሉ... ይሄ እኮ ፈጽሞ የማይረባ ውሸት ነው! ብዙ ሀገራት ወደ እኛ እየመጡ ግንኙነታቸውን ማጠናከር እንደሚፈልጉ እየነገሩን ነው። ለማስረጃ ያህል... ልብ በሉ... በዚህ ሳምንት የኮንጎ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እኛ ጋር መጥቶ ነበር!" ​እውነትም ታላቅ ዓለም አቀፋዊ የዲፕሎማሲ ድል! 👏😂 ​አይ የዓለም ልዕለ ኃያልነት! የዓለም መንግሥታት ሁሉ በተግባራቸው አፍረውና ህዝባቸውን ሰግተው ጀርባቸውን ቢሰጡም፣ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት እና ዓለም አቀፍ ፍርድ ቤቶች ውግዘት ቢያዘንቡም፣ አውሮፓውያን ቢሸሹም... ዋናው ነገር ኮንጎ ከእስራኤል ጎን ናት! ​ከ190 በላይ የዓለም ሀገራት ቢያገሉን ምን ይገርማል? ኮንጎ መጥታ ከጎበኘችንማ እንዴት "ተገልለናል" እንላለን? ​የእስራኤል መንግሥት የደረሰበትን የዲፕሎማሲ ኪሳራና የብቸኝነት ጥግ ከዚህ በላይ የሚያስረዳ ፖለቲካዊ ኮሜዲ ከየትም አይገኝም! ​እስኪ ኮንጎን አምጡልን! 🇨🇩🤝🇮🇱 😅 ቪዲዮው ፌስቡክ ኮሜንት ላይ አለ።