es
Feedback
የሕያ ኢብኑ ኑህ | Yahya Ibnu Nuhe

የሕያ ኢብኑ ኑህ | Yahya Ibnu Nuhe

Ir al canal en Telegram

﷽ | Muslim | Theology | Comparative Religion | Philosophy | Student | ለንግድ፣ ለህክምና ወይም ለጉብኝት ወደ ቱርክ፣ ዱባይ እና የተለያዩ ሀገራት ለመጓዝ ካሰባችሁ ፈሲሩ ትራቭል የትኬት ጉዳያችሁን በኃላፊነት ያጠናቅቃል። እንግልት የሌለበት ጉዞ ለማድረግ ስትፈልጉ በዋትስአፕ አግኙን፦ https://wa.me/qr/5CWCIMYBZLCJB1

Mostrar más

📈 Análisis del canal de Telegram የሕያ ኢብኑ ኑህ | Yahya Ibnu Nuhe

El canal የሕያ ኢብኑ ኑህ | Yahya Ibnu Nuhe (@yahyanuhe) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 21 276 suscriptores, ocupando la posición 3 655 en la categoría Religión y espiritualidad y el puesto 1 580 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 21 276 suscriptores.

Según los últimos datos del 28 julio, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de 76, y en las últimas 24 horas de 4, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificación: No verificado
  • Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 22.25%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 7.45% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 4 735 visualizaciones. En el primer día suele acumular 1 585 visualizaciones.
  • Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 88.

📝 Descripción y política de contenido

El autor describe el recurso como un espacio para expresar opiniones subjetivas:
﷽ | Muslim | Theology | Comparative Religion | Philosophy | Student | ለንግድ፣ ለህክምና ወይም ለጉብኝት ወደ ቱርክ፣ ዱባይ እና የተለያዩ ሀገራት ለመጓዝ ካሰባችሁ ፈሲሩ ትራቭል የትኬት ጉዳያችሁን በኃላፊነት ያጠናቅቃል። እንግልት የሌለበት ጉዞ ለማድረግ ስትፈልጉ በዋትስአፕ አግኙን፦ https://wa.me/qr/5CWCIMYBZLCJB1

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 29 julio, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Religión y espiritualidad.

21 276
Suscriptores
+424 horas
+287 días
+7630 días
Archivo de publicaciones
ጹሁፎቹ የሚቀርቡበት የፌስቡክ ፔጅ ፎሎው ለማድረግ ሊንኩን ይጫኑ

ከዚህ በፊት በፔጁ በኩል የማደርሳቸውን ተከታታይ ጽሑፎች (እንደ "የሚሽነሪዎች የ100 ዓመት ጉባኤዎች"፣ "ቁርኣን አይጋጭም"፣ "የቁርኣን አንጸባራቂ ቃላት ወዘተ) በዋናነት በይፋዊ የፌስቡክ ፔጄ ላ
ከዚህ በፊት በፔጁ በኩል የማደርሳቸውን ተከታታይ ጽሑፎች (እንደ "የሚሽነሪዎች የ100 ዓመት ጉባኤዎች"፣ "ቁርኣን አይጋጭም"፣ "የቁርኣን አንጸባራቂ ቃላት ወዘተ) በዋናነት በይፋዊ የፌስቡክ ፔጄ ላይ በቋሚነት እያቀረብኩ እገኛለሁ። ​ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ፌስቡክን የምጠቀመው በፔጅ ማናጀር በኩል ብቻ በመሆኑ፣ ጽሑፎቹን ወደዚህኛው አካውንት ሼር ለማድረግ ዕድሉ እየጠበበኝ መጥቷል። ​ስለዚህ እነዚህ ተከታታይ ጹሁፍችና ሌሎች አዳዲስ የሚጨመሩትን ጨምሮ እንዳያመልጧችህ የምትፈልጉና ጽሑፎቹን በቀላሉ እና በቋሚነት ለማንበብ የምትፈልጉ ዋናውን የፌስቡክ ፔጄን ፎሎው ማድረግ የምትችሉ ሲሆን ቴሌግራምና ዋትስአፕ ለሚቀላችሁ ደግሞ ቻናሎችን ከታች አስቀምጥላችኃለው። እውነትን ለሌሎች ማድረስ የሁላችንም ኃላፊነት ነው። ጽሑፉን በተለያዩ ግሩፖች እና ገጾች ሼር በማድረግ እርስዎም እኩል አጅር ያግኙ! ​"ወደ መልካም ነገር ያመላከተ፣ እንደሠራው ሰው ምንዳ (አጅር) አለው።" ቴሌግራም ዋትስአፕ

ሕዝብ የቤት ካርታ ለማውጣት ወራትና ዓመታት ማዘጋጃ ቤት ደጅ ሲጠና፣ ሰነድ ሲጎድልበት፣ "ሌላ ቀን ተመለስ" ሲባል፣ በየቢሮው ቢሮክራሲና እንግልት ሲገጥመው... ነገሩ ለካ እንዲህ ቀላል ነበረ? ​አ
ሕዝብ የቤት ካርታ ለማውጣት ወራትና ዓመታት ማዘጋጃ ቤት ደጅ ሲጠና፣ ሰነድ ሲጎድልበት፣ "ሌላ ቀን ተመለስ" ሲባል፣ በየቢሮው ቢሮክራሲና እንግልት ሲገጥመው... ነገሩ ለካ እንዲህ ቀላል ነበረ? ​አንድ "ነቢይ" በሳምንታዊ ፕሮግራሙ "የቤት ካርታ እሰጣለሁ" ብሎ ማስታወቂያ ሲለጥፍ፣ መንግሥት የመሬት ካርታ የመስጠት ሥልጣኑን በይፋ ለቸርች አስረክቧል ማለት ነው? ወይስ አዲሱ የአዲስ አበባ መሬት አስተዳደር መመሪያ የሚዲያ አገልግሎቱን በፓስተሮችና በነቢያት በኩል ለማስተላለፍ ወሰነ?በቸርች ማስታወቂያዎች ውስጥ ህግና ስርኣት ምን ይላል የሚለው ተጠንቶ መተግበር መቼም እየቀረ ያለ ይመስላል።

"ኢትዮጵያ የክርስቲያን ደሴት ናት!' በደሴትነቷ ግን ሌላ ዘር አታበቅልም አንልም።" . . . ​ይህ አባባል ከመነሻውም የታሪክ እና የማንነት ግድፈት አለበት። በመጀመሪያ ደረጃ፣ ኢትዮጵያ ነቢዩ ሙሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) ገና በመጀመሪያ ሪሳላቸውን ሲጀምሩ (ከመዲናም በፊት) ዲኑን የተቀበለች፣ የነጃሺ ምድር እና የእስልምና የመጀመሪያዋ የሰላም ማዕከል ናት። ሙስሊሙ ማኅበረሰብ በዚህች ምድር ላይ እንደ "ሌላ ዘር" ከውጭ መጥቶ የበቀለ ሳይሆን፣ የዚሁ ምድር ነባር አካል እና ዋነኛ ባለታሪክ ነው። ​"ደሴት" የሚለው ዘይቤ ራሱ ሌላውን ሁሉ እንደ ባዕድ የሚቆጥር አደገኛ አገላለጽ ነው። ጸሐፊው "ሌላ ዘር አታበቅልም አንልም" ሲል፣ ሙስሊሙን እንደ አንድ አጋጣሚ በክርስቲያን ምድር ላይ እንደበቀለ ተጨማሪ ነገር አድርጎ ስሎታል። ይህ ታሪካዊ እውነታን የሚክድ እና የሙስሊሙን ሀገራዊ ሥረ-መሠረት የሚያኮስስ ዲስኩር ነው። ኢትዮጵያ የብዝሃነት አህጉር እንጂ፣ የአንድ ሃይማኖት ብቸኛ ደሴት ሆና አታውቅም። . . . ​"ኦርቶዶክስ የሀገር ባለቤት ናት!' ባለቤትነቷ ግን የጋራ ባለቤትነትን አይነፍግም።" . . . ​እዚህ ላይ ጸሐፊው የፈጠረው ከባድ አመክንዮአዊ ግጭት አለ። "ባለቤት" እና "ተካፋይ" የሚሉ እርከኖችን በአንድ ዜግነት ውስጥ ፈጥሯል። ይህ አስተሳሰብ አንደኛ ደረጃ ዜጋ (ዋና ባለቤት) እና ሁለተኛ ደረጃ ዜጋ (በፈቃድ የተጠለለ/ተከራይ) የሚል መርዛማ ክፍፍልን ይወልዳል። ​በዘመናዊ የሀገር ግንባታ ጽንሰ-ሐሳብ፣ ዜግነት እና የሀገር ባለቤትነት በሊዝ፣ በችሮታ ወይም በሌላው ወገን "እንዳይነፈግ" በመፈቀድ የሚገኝ ሳይሆን የተፈጥሮ መብት ነው። ሀገር የሁሉም ዜጎቿ እኩል ርስት ናት እንጂ፣ አንዱ "ዋና ባለቤት" ሆኖ ሌላውን ተካፋይ እንዲሆን የሚጋብዝበት የግል ጓሮ አይደለችም። ጸሐፊው ይህንን በማለቱ ሳያውቀው (ወይም አውቆ) ሙስሊሙን የዚህች ሀገር እኩል ባለቤት ሳይሆን፣ በዋናው ባለቤት ቸርነት አብሮ የሚኖር "ተከራይ" (Tenant) አድርጎ አቅርቦታል። . . . . ​የጽሑፉ የመክፈቻ ቃላት "አይዟችሁ፤ አትደንግጡ" የሚሉ ናቸው። ይህ አባባል ራሱ የሚመነጨው "እኛ ሥልጣንና ባለቤትነቱን ብንይዝም፣ እናንተን አንጨፈልቃችሁም" ከሚል የትዕቢት ወይም የአሳዳጊነት ሥነ-ልቦና ነው። ​የሙስሊሙ ማኅበረሰብ ጥያቄ ግን ማንም መጥቶ አቅፎ እንዲያኖረው፣ እንዳይነፍገው ወይም እንዲታገሰው አይደለም። ጥያቄው እኩልነት ነው። "እኛ ባለቤት ነን፣ እናንተንም አንከለክልም" የሚለው የችሮታ ቋንቋ፣ በሕገ-መንግሥታዊ እና ተፈጥሯዊ የዜግነት መብቶች ፊት ቦታ የለውም። ​ሲጠቃለል፦ እውነተኛ ሀገራዊ አንድነት ሊገነባ የሚችለው "የእኛ ደሴት ናት፣ ግን እንድትበቅሉ እንፈቅዳለን" በሚል የባለቤትነት ዲስኩር ሳይሆን፣ "ይህች ሀገር በእኩልነት የሁላችንም መሬት ናት" በሚል የዜግነት ክብር ነው። ይህ የጸሐፊው ጽሑፍ ቆንጆ የሚመስሉ ቃላትን ቢጠቀምም፣ በውስጡ ግን የዜጎችን እኩልነት የሚንድ እና የድሮውን የማግለል ፖለቲካ በአዲስ መልክ የሚያቀናቅን እብሪተኛ ገለጻ ነው። © የሕያ ኢብኑ ኑህ

በጠንካራ የሙስሊም ማህበረሰብ ውስጥ አደባባይ ላይ ቤተክርስቲያን መትከል፣ መስቀል ማቆምና በድምጽ ማጉያ መስበክ አፋጣኝ ማህበራዊ ተቃውሞ እንደሚያመጣ ሚሽነሪዎች በረጅም ጊዜ ልምዳቸው ተረድተዋል። ለዚህ በጥናት ያመጡት መፍትሄ "ህንጻ-አልባው እንቅስቃሴ" ወይም የቤት ውስጥ አብያተ ክርስቲያናት የተሰኘውን ስውር አደረጃጀት ነው። ይህ ስልት ሃይማኖትን ከ'ተቋምነት' ወደ 'ጓዳዊ የአኗኗር ዘይቤ' የሚቀይር ነው። ሰዎች ከውጭ ሲታዩ የነበሩበትን ኢስላማዊ ባህል፣ የአለባበስ ዘይቤና ማህበራዊ መስተጋብር ሳይለቁ፣ በቤታቸው ግድግዳ ውስጥ ግን አዲስ ሃይማኖታዊ ማንነት እንዲገነቡ ይደረጋል። ​ይህ ስልት መሬት ላይ እንዴት እንደሚተገበር የመጀመሪያውን ተጨባጭ ምሳሌ እንመልከት፦ በመካከለኛው እስያ እና በአፍሪካ ቀንድ (በተለይም በኢትዮጵያና ጎረቤት ሀገራት) በስፋት የተሞከረው "የቡና እና የሻይ ጓዳ" ስልት ነው። አንድ ለዚህ የሰለጠነ ግለሰብ (እነሱ ቸርች ፕላንተር ይሉታል) በሰፈሩ ውስጥ ከ5 እስከ 6 የሚሆኑ ጎረቤቶችን ለቡና ወይም ለሻይ ይጋብዛል። ውይይቱ የሚጀምረው ስለ ኑሮ ውድነት፣ ስለ ልጆች አስተዳደግ ወይም ስለ ሰላም ነው። ቀስ ብሎ አስተናጋጁ "እስኪ ዛሬ ስለ ነብዩ አዩብ (ኢዮብ) ትዕግስት ከቁርዓን እና ከመጽሐፍ ቅዱስ እያመሳከርን እንወያይ" ይላል። ይህ ስብስብ 'ቤተክርስቲያን' አይባልም፤ 'የቡና ስብስብ' ወይም 'የወዳጆች ምሽት' የሚል ስም ይሰጠዋል። ተሳታፊዎቹ ወደ መስጅድ መሄዳቸውን ሳያቋርጡ፣ በየሳምንቱ በጓዳ በሚደረገው በዚህ ስውር የሃሳብ ማጋራት ውስጥ ማንነታቸው ቀስ በቀስ ይቀየራል። ​ሁለተኛው አስገራሚ ምሳሌ ደግሞ "የክህሎት ማሰልጠኛ ሴሎች" የሚባሉት ወይንም በእንግሊዝኛው Vocational Cell Groups ናቸው። ለምሳሌ በወጣቶች ዘንድ ያለውን የእንግሊዝኛ ቋንቋ የመናገር ጉጉት ወይም በሴቶች ዘንድ ያለውን የሙያ ስልጠና ፍላጎት እንደ መግቢያ በር ይጠቀሙበታል። በአንድ መኖሪያ ቤት ሳሎን ውስጥ "ነጻ የእንግሊዝኛ የንግግር ክበብ" (English Speaking Club) ይከፈታል። መጀመሪያ ላይ መደበኛ የእንግሊዝኛ ቃላት ይነበባሉ፤ ከጥቂት ሳምንታት በኋላ ግን የንባብ ልምምድ ማድረጊያ መጽሐፉ 'የዮሐንስ ወንጌል' ወይም በሚሽነሪዎች የተዘጋጁ ስነ-ጽሁፎች ይሆናሉ። ተማሪው ቋንቋ እየተማረ መሆኑን እያሰበ፣ ሳያውቀው አእምሮውን ለባዕድ ዶክትሪን አሳልፎ ይሰጣል። የሰፈሩ ማህበረሰብ ወጣቶቹ እውቀት እየፈለጉ መሆኑን ሲያስብ፣ በጓዳ ውስጥ ግን ጸጥተኛ የሃይማኖት ሽግግር ይከናወናል። ​የዚህ 'የቤት ውስጥ አደረጃጀት' ታላቁ አደጋ ከመሬት በታች እንደሚራባ ፈንገስ መሆኑ ነው። መደበኛ ቤተክርስቲያን ቢሆን ኖሮ ህዝቡ አውቆ ሊያወግዘው፣ የሚመለከተው የመንግስት አካልም ህንጻውን ከአላማው ውጭ በማስተማሩ በህገ ወጥነት ፈርጆ ሊያሽገው ይችል ነበር። የጓዳ ውስጥ ስብስብ ግን በህግም ሆነ በማህበራዊ ቁጥጥር ስር አይወድቅም። አንዱ ሳሎን ውስጥ የሰለጠነው ሰው፣ የራሱን ሳሎን ከፍቶ ሌላ 5 ሰዎችን ይመለምላል። ዴቪድ ጋሪሰን የተባለው የሚሽነሪ ስትራቴጂስት "Church Planting Movements" በተሰኘው መጽሐፉ ላይ እንዳሰፈረው፣ “የሙስሊሙ ማህበረሰብ የሃይማኖት መሪዎች አደጋውን ተረድተው መንቃት ሲጀምሩ፣ እንቅስቃሴው ቀድሞውኑ ከቁጥጥራቸው ውጭ በሆኑ መቶዎች በሚቆጠሩ ሳሎኖች ውስጥ ተሰራጭቶ ያበቃል” ይላል። ይህ ያለምንም ጩኸት ማህበረሰብን ከስሩ የመመዝበር የተራቀቀ መሬት ላይ የሚዘረጋ ስልት ነው። ​በቀጣዩ ክፍል የምንዳስሰው አጀንዳ፡ ራሱን "ሙስሊም" ብሎ የሚጠራው፣ ነገር ግን በውስጡ ክርስቲያን የሆነው አዲሱ በሚሽነሪ የተጠመቀ ትውልድ ስውር ማንነት (The Insider Movement) የተሰኘውን እጅግ አወዛጋቢ ስልት በቀጣይ ክፍል - 16 በአላህ ፍቃድ እንመለከተዋለን። ​የመረጃ ምንጮች፦ • ​David Garrison, "Church Planting Movements: How God Is Redeeming a Lost World". • ​Evangelizing Muslims - Helps for beginning house churches (Guidelines for Clandestine Work), pp. 50-52. ያለፈውን ክፍል ለማንበብ

በሱረቱ አል-ከህፍ (18፥12) ላይ "ከዚያም ከሁለቱ ክፍሎች ለቆዩት ጊዜ ልክ ያረጋገጠው ማንኛው መሆኑን ልናውቅ አስነሳናቸው" በሚለው አንቀጽ ዙሪያ፣ በተለይም "ልናውቅ" በሚለው ቃል ላይ የሚነሳው ጥያቄ፣ በእስልምና አስተምህሮ፣ በአረብኛ የቋንቋ ህግ ሰፊ ማብራሪያ ያለው ጽንሰ-ሀሳብ ነው። አላህ የነገሮችን መጀመሪያና መጨረሻ ቀድሞ የሚያውቅ ሆኖ ሳለ፣ ለምን "ልናውቅ" የሚለውን ቃል ተጠቀመ? ይህ አገላለጽ የአላህን ቅድመ-ዕውቀት የሚጻረር ነውን? ይህንን ጭብጥ ከስረ-መሰረቱ እንደሚከተለው እናብራራዋለን። ​በእስልምና አስተምህሮ መሠረት የአላህ ዕውቀት ፍጹምና ማለቂያ የሌለው ነው። ሆኖም የቁርኣን የቋንቋ ሊቃውንት ይህንን አንቀጽ ሲያብራሩ፣ "ዕውቀት" በሁለት መሠረታዊ ዘርፎች እንደሚከፈል ያስረዳሉ፦ • ​ዒልም አል-አዘሊ (የቅድመ-ዕውቀት)፦ አላህ አንድ ነገር ከመፈጠሩ ወይም ከመከሰቱ በፊት በዘላለማዊ ዕውቀቱ የሚያውቀው እውቀት ነው። አላህ የዋሻው ሰዎች ምን ያህል ጊዜ እንደተኙ፣ መቼም እንደሚነሱ አስቀድሞ ያውቃል። • ​ዒልም አል-ዉቁዕ (የማረጋገጥና የተጨባጭ ዕውቀት)፦ ይህ ደግሞ አንድ ነገር በተጨባጭ ዓለም ሲከሰት፣ ያንን የተከሰተ ነገር በድርጊት ዓለም ማወቅና ማሳየት ነው። ​በቁርኣን ውስጥ "ልናውቅ" የሚለው ቃል ሲመጣ የሚያመለክተው የመጀመሪያውን (አለመኖርን አጥፍቶ ማወቅን) ሳይሆን፣ ሁለተኛውን (በገሃድ የተከሰተውን ማረጋገጥን) ነው። ይኸውም በዘላለማዊ ዕውቀቱ የሚያውቀውን ነገር፣ ወደ ተጨባጭ ዓለም አምጥቶ በገሃድ መከሰቱን ልናሳይ ወይም ለሰዎች ልናሳውቅ ማለት ነው። አላህ የገለጸውም፣ በውስጥ የሚያውቀውን እውቀት ለሰዎች በገሃድ አውጥቶ ለማሳየት ነው። ​ታላላቅ የቁርኣን ሙፈሲሮች ይህንን ጥልቅ የቋንቋ አገላለጽ ጉዳይ በሚገባ ዳስሰውታል፦ • ​ኢማም አጥ-ጦበሪ፦ በታዋቂው የቁርኣን ማብራሪያ መጽሐፋቸው ላይ፣ ይህንን አንቀጽ ሲተነትኑ እንዲህ ይላሉ፦ "አላህ 'ልናውቅ' ማለቱ፣ ለሰዎች ልናሳውቅና በተጨባጭ ልናሳያቸው ማለት ነው። አላህማ እነርሱ ከመተኛታቸውም ሆነ ከመነሳታቸው በፊት የቆዩበትን ጊዜ አስቀድሞ ያውቃል። ነገር ግን የቃሉ ትርጉም 'በተግባር ዓለም ሲከሰት ልናየውና ለፍጡራን ልናረጋግጠው' ማለት ነው።" [1] • ​ኢማም አል-ቁርጡቢ፦ በታላቁ የተፍሲር መጽሐፋቸው እንዲህ ብለዋል፦ "በዚህ አንቀጽ ላይ 'ልናውቅ' ማለት፣ በድብቅ የነበረውን እውቀት ወደ እይታ ዓለም ልናወጣው ማለት ነው። አላህ ቀድሞ የሚያውቀው ቢሆንም፣ በድርጊት መከሰቱን ማወቅና ሰዎችን ማስመስከር የቃሉ ዋነኛ መልእክት ነው።" [2] ​መጽሀፍ ቅዱስ በዚህ ዙሪያ ምን ይላል? ​ይህንን የቁርኣን ቃል የነቀፉ ክርስቲያን ወገኖች ይህን ጥያቄ ከማንሳታቸው በፊት የራሳቸውን መጽሐፍ ቅዱስ በጥልቀት ቢመረምሩ ኖሮ፣ ጥያቄውን ለማንሳት ብዙ ርቀት መሄድ አይጠበቅባቸውም ነበር። ​ማስረጃ አንድ፦ የአብርሃም ፈተና በኦሪት ዘፍጥረት ላይ እግዚአብሔር አብርሃምን ልጁን ይስሐቅን እንዲሠዋው አዘዘው። አብርሃም ልጁን ሊሠዋ ቢላዋውን ሲያነሳ፣ የእግዚአብሔር መልአክ ጠርቶት እንዲህ አለው፦ " በብላቴናው ላይ እጅህን አትዘርጋ፥ አንዳችም አታድርግበት፤ አንድ ልጅህን ለእኔ አልከለከልህምና እግዚአብሔርን የምትፈራ እንደ ሆንህ አሁን ዐውቄያለሁ አለ።" [3] ​እዚህ ላይ ጥያቄ ይነሳል፦ እግዚአብሔር ሁሉን አዋቂ ሆኖ ሳለ፣ አብርሃም እንደሚታዘዘው አስቀድሞ አያውቅም ነበርን? "አሁን አውቄአለሁ" (Now I know) ማለቱስ ከዚህ በፊት አላውቅም ነበር ማለቱ ነውን? በፍጹም! የክርስቲያን ሥነ-መለኮት ሊቃውንት ይህንን ሲያብራሩ "አሁን በተግባር አረጋገጥኩ፣ እምነትህ በገሃድ ተገለጠ" ማለት ነው ይላሉ። ታዲያ ለመጽሐፍ ቅዱስ የሰራው ይህ የቋንቋና የሥነ-መለኮት ሚዛን፣ ለቁርኣኑ "ልናውቅ" ወይም "ልናረጋግጥ" ለሚለው ቃል ሲደርስ ለምን ይሰናከላል? ይህ ግልፅ የሆነ ሚዛን መሳት ነው። ​ማስረጃ ሁለት፡ የእስራኤላውያን የምድረ በዳ ጉዞ በኦሪት ዘዳግም ላይ እግዚአብሔር እስራኤላውያንን በምድረ በዳ ስላንከራተተበት ምክንያት ሲገልጽ እንዲህ ይላል፦ "አምላክህ እግዚአብሔር ይፈትንህ ዘንድ፥ በልብህም ያለውን ትእዛዙን ትጠብቅ ወይም አትጠብቅ እንደ ሆነ ያውቅ ዘንድ፥ ሊያስጨንቅህ በእነዚህ በአርባ ዓመታት በምድረ በዳ የመራህን መንገድ ሁሉ ዐስብ። ኦሪት ዘዳግም 8፥2" [4] ​እግዚአብሔር በሰዎቹ ልብ ውስጥ ያለውን አስቀድሞ አያውቅም እንዴ? "ያውቅ ዘንድ" ሲል የተደበቀበትን እውቀት ለመፈለግ ነውን? የክርስቲያን ምሁራንም የሚሰጡት ምላሽ አንድ ነው፤ "ይህ አገላለጽ የሰዎቹ ተግባር ከውስጥ ወደ ውጭ ወጥቶ በገሃድ እንዲረጋገጥ ማድረጉን የሚያሳይ ነው።" ​የሙግቱ ማጠቃለያ፡- በቁርኣንም "ልናውቅ" የተባለው ልክ በመጽሐፍ ቅዱስ "ያውቅ ዘንድ" እና "አሁን አውቄአለሁ" እንደተባለው ዓይነት የተለመደ እና መለኮታዊ የቋንቋ ዘይቤ እንጂ፣ የአላህን ሁሉን አዋቂነት የሚሸራርፍ አንዳችም ጉድለት የለበትም። ​ማጠቃለያ ​በቁርኣን ሱረቱ አል-ከህፍ ላይ የገባው "ልናውቅ አስነሳናቸው" የሚለው ቃል፣ አላህ የዋሻው ሰዎች የተኙበትን ዘመን አላውቅም ብሎ ሳይሆን፣ ቀድሞ በዘላለማዊ ዕውቀቱ የሚያውቀውን ታላቅ እውነት አሁን ደግሞ ፍጡራን በሚረዱት የድርጊት ዓለም ለማረጋገጥ እና ምስክር ለማቆም የተጠቀመበት የቋንቋ ዘይቤ ነው። ይህም እውቀትን ከተሰወረበት አውጥቶ በገሃድ የማሳየት ጥበብ ነው። ​የግርጌ ማስታወሻዎች፦ [1] ኢማም ሙሐመድ ኢብኑ ጀሪር አጥ-ጦበሪ፣ ጃሚዕ አል-በያን አን ተእዊል አያል ቁርኣን፣ ሱረቱ አል-ከህፍ፣ አንቀጽ 12 ማብራሪያ፣ ቅጽ 15፣ ገጽ 158። [2] ኢማም ሙሐመድ ኢብኑ አህመድ አል-ቁርጡቢ፣ አል-ጃሚዕ ሊአሕካም አል-ቁርኣን፣ ሱረቱ አል-ከህፍ፣ ቅጽ 10፣ ገጽ 366-367። [3] መጽሐፍ ቅዱስ፣ ኦሪት ዘፍጥረት፣ ምዕራፍ 22 ቁጥር 12። [4] መጽሐፍ ቅዱስ፣ ኦሪት ዘዳግም፣ ምዕራፍ 8 ቁጥር 2። ምልክት በማስቀመጥ በፌስቡክ ኮሜንት የሚደረገውን ውይይት ለመከታተል የሚከተለውን ሊንክ መጠቀም ይችላሉ።

ለሚቀጥለው ወር በተዘጋጀው የኡምራ ፓኬጅ ከወንድሜ አብዱረሕማን አሚን ጋር በአላህ ፍቃድ አብረን እንጓዛለን። በነዚህ ቀናት ኡምራ ለማድረግ የነያችሁ ጉዟችሁን ከአንደሉስ ትራቭል ጋር ማድረግ ትችላላች
ለሚቀጥለው ወር በተዘጋጀው የኡምራ ፓኬጅ ከወንድሜ አብዱረሕማን አሚን ጋር በአላህ ፍቃድ አብረን እንጓዛለን። በነዚህ ቀናት ኡምራ ለማድረግ የነያችሁ ጉዟችሁን ከአንደሉስ ትራቭል ጋር ማድረግ ትችላላችሁ። ​የጉዟችን ዝርዝር መረጃዎች፦ • ​የጉዞ ጊዜ፡ ከነሐሴ 20 እስከ ነሐሴ 30 • ​ምዝገባ የሚያበቃው፡ ነሐሴ 15 • የቆይታ ጊዜ፡ 7 ቀናት በመካ እና 3 ቀናት በመዲና ​በአንደሉስ ትራቭል ልዩ የጉዞ ጥቅል ውስጥ የተካተቱት፦ • ​የአየር ትኬት • ​የዑምራ ቪዛ • ​ ምቹ የውስጥ ትራንስፖርት • ​ደረጃውን የጠበቀ የሆቴል ማረፊያ • ​የሁለቱንም ከተሞች ታሪካዊ ቦታዎች ጉብኝት ​ለበለጠ መረጃ እና ምዝገባ፦ 📞 09 11 27 40 33 📞 09 92 04 79 20 📍 አድራሻ፡ ጀሞ 3፣ ሰኢድ ያሲን ሕንፃ፣ 2ኛ ፎቅ ​አንደሉስ ትራቭል - ታማኝ የጉዞ አጋርዎ! ✈️

ከሰሞኑ የቡርኪናፋሶው መሪ ኢብራሂም ትራውሬ የወሰናቸውን ውሳኔዎች አስመልክቶ ዓለም አቀፍ ሚዲያዎች ያወጡትን ዘገባ ብዙዎቻችን ተመልክተናል። በርግጥም ፖለቲካ ምን ያህል አስመሳይና መልክ አልባ እንደሆነ ፍንትው አድርጎ የሚያሳይ አሳዛኝ ክስተት ነው። ​ኢብራሂም ትራውሬ ወደ ስልጣን ሲመጣ፣ አፍሪካን ከምዕራባውያን የኒዮ-ኮሎኒያሊዝም ቀንበር ነፃ እንደሚያወጣ ቆራጥ መሪ ተደርጎ ነበር የተሳለው። በዚህም ጉዞው የሀገሪቱ ሙስሊም ማህበረሰብና ታዋቂ ዑለሞች ትልቅ የፖለቲካና የሞራል ስንቅ በመሆን ከጎኑ ቆመው ነበር። ዛሬ ግን ስልጣኑ ሲደላደል፣ ያንኑ መሰረቱን በጠላትነት ፈርጆ ማጥቃት ጀምሯል። ​"አክራሪነትን እዋጋለሁ" የሚለው ያረጀና ያፈጀ የአምባገነኖች ፖለቲካዊ ሰበብ፣ ዛሬ በቡርኪናፋሶ መሬት ላይ በግልጽ እየተተገበረ ነው። ንፁሀንና ሰላማዊ የሆኑ ታዋቂ ሊቃውንትን (እንደ ኢማም መሀመድ ኢስሀቅ ኪንዶ እና ኢማም ማህሙድ ባሮ) በእስር ማሰቃየት፣ በዋጋዱጉ የሚገኘውን ትልቁን መስጊድ መዝጋት፣ እንዲሁም ተቃውሞ ያሰሙትን ወጣቶች "ለስነ-ዜጋ ስልጠና" በሚል ሰበብ ወደ ወታደራዊ ካምፕ ማጋዝ፤ ይህ ሁሉ በስልጣኔ ስም የተሸፈነ የመንግስት ሽብር ነው። ከዚህም አልፎ፣ በአረብ ሀገራት ዲናቸውን የሚማሩ ከ800,000 በላይ ተማሪዎችን "ዜግነት እንነጥቃለን" ብሎ ማስፈራራት፣ መንግስት በእስልምና ላይ የከፈተውን ጦርነት ጥልቀት ያሳያል። ​ከሁሉ በላይ ልብ የሚሰብረው ደግሞ፣ "የፀረ-ኢምፔሪያሊዝም" አርማ አንግቤያለሁ የሚለው ይህ መሪ፣ ፊቱን አዙሮ ከእስራኤል ጋር እጅና ጓንት መሆኑ ነው። የፍልስጤም ንፁሃን ደም እየፈሰሰ ባለበት በዚህ ከባድ ጊዜ፣ አዲሱን የእስራኤል አምባሳደር በክብር ተቀብሎ የፀጥታ ትብብር መጀመሩ፣ የትራውሬን እውነተኛ ማንነት እና በሙስሊሙ ማህበረሰብ ላይ የፈጸመውን ከባድ ክህደት ያረጋግጣል። ​ታላቁ ጌታችን አላህ በቅዱስ ቁርኣን ላይ፣ የአላህን ቤት ከሚዘጉና ዲንን ከሚያፍኑ አመራሮች በላይ በደለኛ እንደሌለ እንዲህ በማለት ያስጠነቅቃል፡- ​«የአላህንም ስም በውስጣቸው እንዳይወሳ ከአላህ መስጊዶች ከከለከለና እርስዋንም በማበላሸት (በማፍረስ) ከሚጥር ሰው ይበልጥ በደለኛ ማነው?» (አል-በቀራህ 2፥114) ​እውነትን የያዙ ዑለሞች በአምባገነን መሪዎች ፊት ፈተና ቢበዛባቸውም፣ እውነትን ከመናገር ወደ ኋላ አይሉም። ነቢዩ ሙሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) ይህንን የታላላቅ ሰዎችን የጀግንነት ሚና እንዲህ በማለት አብራርተውታል፡- ​"ከጂሃድ ሁሉ በላጩ፣ በአምባገነን (ጨቋኝ) መሪ ፊት እውነተኛ ቃል መናገር ነው።" (ሱነን አቢ ዳውድ 4344) ​የቡርኪናፋሶ ሙስሊሞች ዛሬ እየገጠማቸው ያለው ፈተና የሁላችንም ህመም ነው። ከህመሙ በላይ ግን ትምህርትም ነው። ፖለቲከኞች ዛሬ ጣዖት ሆነው ይመለካሉ፤ ስልጣን ሲይዙ ግን የመጀመሪያ ሰለባ የሚያደርጉት ደጋፊዎቻቸውን ነው። እውነተኛ ተስፋችንና መመኪያችን በምድር ላይ ባሉ የፖለቲካ "አዳኞች" ላይ ሳይሆን፣ ፍትህን በማያንጓድደው አሸናፊው ጌታችን ላይ ብቻ መሆን አለበት። ትዕግስትና ዱዓ መሳሪያችን ናቸው! © የሕያ ኢብኑ ኑህ

እህታችን መሠረትን ፎሎ አድርጓት የ500 ቻሌንጅ ተጀምሯል ። https://www.tiktok.com/@aziza654321?_r=1&_t=ZS-98Fe3XZdbSW
እህታችን መሠረትን ፎሎ አድርጓት የ500 ቻሌንጅ ተጀምሯል ። https://www.tiktok.com/@aziza654321?_r=1&_t=ZS-98Fe3XZdbSW

ክርስቲያን ሚስዮናውያን እና አፖሎጂስቶች ኢየሱስ (ዐ.ሰ) በጲላጦስ ትዕዛዝ በመስቀል ላይ መሞቱ ሊካድ የማይችልና እና ሙሉ በሙሉ የተረጋገጠ የታሪክ እውነታ አድርገው በከፍተኛ የራስ መተማመን ያቀርቡታል። ነገር ግን ይህንን ትርክት ከታሪክ፣ ከህክምና ሳይንስ እና በራሳቸው ከመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ካሉ መረጃዎች አንፃር በሰፊው ስንመዝነው፣ አጠያያቂ የሆኑ በርካታ ክፍተቶችን እናገኛለን። ፩/ ​ከህክምናው እንጀምር ​በሮማውያን ሥርዓት በመስቀል ላይ የሚፈፀም የሞት ቅጣት ዋነኛ አላማው ሰውን በፍጥነት መግደል ሳይሆን፣ በከፍተኛ ስቃይ ውስጥ ለቀናት እያሰቃዩ በማቆየት መግደል ነው። ታላቁ የብሪታንያ ብዙሀን መገናኛ (BBC) በመቶ ሺዎች የሚቆጠር ፓውንድ አውጥቶ ባዘጋጀው እና ታዋቂ የነገረ-መለኮት ምሁራንን ባካተተው ዘጋቢ ፊልም ላይ ይህንን የህክምና እውነታ በግልፅ አስቀምጦታል። ​በመስቀል ላይ የተሰቀለ ሰው የሚሞተው ደም በመፍሰስ ወይም የውስጥ አካላቱ ስለሚጎዱ አይደለም። ይልቁንም፣ የሰውነት ክብደት ወደ ታች በሚጎትትበት ጊዜ በደረት ላይ ከፍተኛ ጫና ስለሚፈጠር፣ ትንፋሽ ለማስገባት እና ለማስወጣት እጅግ አስቸጋሪ ይሆናል። ስለዚህ የተሰቀለው ሰው ለመተንፈስ ሲል እግሮቹን ተጠቅሞ ሰውነቱን ወደ ላይ መግፋት ግድ ይለዋል። ይህ ሂደት ሰውየው አቅም አጥቶ እስኪዝል ድረስ ለቀናት የሚቀጥል እጅግ አዝጋሚ ስቃይ ነው። ሞቱን ለማፋጠን ሲፈለግ ብቻ፣ የተሰቃዩን እግሮች በመስበር የሰውነቱን ክብደት መሸከም እንዳይችል እና በፍጥነት ትንፋሽ እንዲያጥረው ይደረጋል። ይሁን እንጂ መጽሐፍ ቅዱስ እንደሚያስረዳው፣ የኢየሱስ እግሮች አልተሰበሩም። ፪/ ​የጲላጦስ ጥርጣሬን ጠቅሰን እንለፍ ​ታዲያ ኢየሱስ እግሮቹ ሳይሰበሩ፣ እንደ ታሪክ ምሁራኑ ቀናትን መውሰድ ሲገባው፣ እንዴት በሶስት ወይም በስድስት ሰዓታት ውስጥ ሊሞት ቻለ? ይህ እንቆቅልሽ በዘመኑ የነበረውን የሮማውያን ገዥ ጲላጦስን ሳይቀር ክፉኛ አጠራጥሮት ነበር። ማርቆስ 15፡44 ላይ እውነታው እንዲህ ሰፍሯል፦ ​"ጲላጦስም አሁኑኑ እንዴት ሞተ ብሎ ተደነቀ፥ የመቶ አለቃውንም ጠርቶ ከሞተ ቆይቶአልን? ብሎ ጠየቀው፤" ​በመደበኛ ሁኔታ ከሶስት ቀናት በላይ የሚፈጅ የሞት ቅጣት፣ እግሮቹ ባልተሰበሩ ሰው ላይ እንዴት ከግማሽ ቀን ባነሰ ጊዜ ውስጥ ተጠናቀቀ? ይህ ጥያቄ የታሪክ ተመራማሪዎችን ዛሬም ድረስ የሚያስጨንቅ እንቆቅልሽ ነው። ፫/ ​የታሪክ ምሁራን ጥርጣሬ እና የጆሴፈስ መዝገብ ​በኦክስፎርድ ዩኒቨርሲቲ የታሪክ ምሁር የሆኑት ጌዛ ቨርሜስ "ዘ ሪዘረክሽን: ሂስትሪ ኤንድ ሚዝ" በተሰኘው መጽሐፋቸው ገጽ 145 ላይ ይህንን ጉዳይ በሰፊው ዳስሰውታል። በመስቀል ላይ የተሰቀለ ሰው ከሞት ሊተርፍ እንደሚችል ለማሳየትም፣ የታሪክ ተመራማሪው ፍላቪየስ ጆሴፈስ በራሱ የህይወት ታሪክ ላይ የፃፈውን አስገራሚ ክስተት በማስረጃነት ያቀርባሉ። ጆሴፈስ በመንገድ ላይ ሲጓዝ ሶስት ጓደኞቹ በመስቀል ላይ ተሰቅለው ይመለከታል፤ ወዲያውኑ ለሮማውያን አዛዥ ተማፅኖ ከመስቀል ላይ እንዲወርዱ ያደርጋል፤ በህክምና እርዳታም ከሶስቱ አንዱ በህይወት ሊተርፍ ችሏል። ​ቨርሜስ አክለውም፣ በዮሐንስ ወንጌል ላይ የተጠቀሰው "ጎኑን በጦር ወጋው" የሚለው ትርክት፣ ኢየሱስ በፍጥነት መሞቱን የተጠራጠሩ ሰዎችን ጥያቄ ለማዳፈን ሆን ተብሎ ቆየት ብሎ የተጨመረ የፈጠራ ታሪክ ሊሆን እንደሚችል በጠንካራ ሁኔታ ይሞግታሉ። ፬/ ​የመድሃኒት እፅዋቱ እንቆቅልሽ ​ወደ መጽሐፍ ቅዱስ ስንመለስ፣ ሞቷል ከሚለው ድምዳሜ ይልቅ ለጥርጣሬ የሚያጋልጡ ሌሎች ከባድ ክፍተቶችን እናገኛለን። ዮሐንስ 19፡39 ላይ እንዲህ የሚል ቃል ሰፍሯል፦ ​"ደግሞም አስቀድሞ በሌሊት ወደ ኢየሱስ መጥቶ የነበረ ኒቆዲሞስ መቶ ንጥር የሚያህል የከርቤና የእሬት ቅልቅል ይዞ መጣ።" ​እነዚህ እፅዋት በዘመኑ ለህክምና እና ቁስልን ለማዳን የሚያገለግሉ ጠቃሚ መድኃኒቶች ነበሩ። "መቶ ንጥር" ደግሞ እጅግ በጣም ብዙ መጠን ያለው ነው። አእምሮን የሚሞግተው ትልቁ ጥያቄ፦ በእርግጥ ለሞተ ሰው ይህ ሁሉ የህክምና እፅዋት ለምን አስፈለገ? ነው ወይስ ኒቆዲሞስ ኢየሱስ በህይወት እንዳለ ስለሚያውቅ ነበር ቁስሉን ሊያክመው የመጣው? ፭/ ​ጥልቁ የቁርኣን መፍትሄ ​ይህ ሁሉ የታሪክ፣ የህክምና እና የሎጂክ እንቆቅልሽ፣ ፍፁም እና በማያሻማ ሁኔታ ምላሽ የሚያገኘው በታላቁ ቁርኣን ውስጥ ነው። አላህ አይሁዶች ኢየሱስን ሰቀልነው ብለው የሚያቀርቡትን የሐሰት ሙግት ሲያፈርስ፣ እውነታውን በተጨበጠ ቃሉ እንዲህ ያስቀምጠዋል፦ ​"የአላህን መልክተኛ የመርየምን ልጅ አልመሲሕ ዒሳን እኛ ገደልን በማለታቸውም (ረገምናቸው)፡፡ አልገደሉትም አልሰቀሉትምም፡፡ ግን ለእነርሱ (የተገደለው ሰው በዒሳ) ተመሰለባቸው፡፡ እነዚያም በርሱ ነገር የተለያዩት ከርሱ በመጠራጠር ውስጥ ናቸው፡፡ ጥርጣሬን ከመከተል በስተቀር በርሱ ነገር ምንም እውቀት የላቸውም፡፡ በእርግጥም አልገደሉትም፡፡" (ሱረቱ አን-ኒሳእ 4፡157) ​ታላቁ የቁርኣን ሊቅ ኢማም ኢብኑ ከሲር ይህንን አንቀፅ ሲያብራሩ፣ አላህ ነቢዩን ዒሳን ከጠላቶቹ ሴራ በማዳን ወደ እርሱ እንዳነሳው እና ሌላ ሰው በመስቀል ላይ እንደዋለ በዝርዝር ያስረዳሉ። ​ማጠቃለያ፦ እስልምና ስለ ነቢዩ ዒሳ (ዐ.ሰ) የሚያስተምረው እውነት ከሎጂክ፣ ከታሪክ ግኝቶች እና ከጤናማ አእምሮ ጋር ሙሉ በሙሉ የሚስማማ ነው። ጲላጦስ የተጠራጠረው እና የታሪክ ምሁራን እንቆቅልሽ የሆነባቸው ፈጣን "ሞት"፣ የቁርኣንን መለኮታዊ እውነት በተጨባጭ የሚያረጋግጥ ማስረጃ ነው። በመስቀል ላይ የተፈፀመው ሌላ ክስተት እንጂ፣ የሁሉም ቻይ አምላኩ መልዕክተኛና ነቢይ እዚያ ላይ አልነበረም! በኮሜንት የሚደረየሚደረገውን ውይይት ለመከታተል ይህንን ይጫኑ

ከአንድ ሚሊዮን በላይ ህዝብ የስፔንን የዓለም ዋንጫ ድል ለማክበር በማድሪድ ከተማ አደባባዮች በወጣበት ወቅት፣ ደጋፊዎች የእስራኤልን ባንዲራ መሬት ላይ ጥለው ሲረግጡትና የሚያልፉ መኪናዎችም እንዲረግ
ከአንድ ሚሊዮን በላይ ህዝብ የስፔንን የዓለም ዋንጫ ድል ለማክበር በማድሪድ ከተማ አደባባዮች በወጣበት ወቅት፣ ደጋፊዎች የእስራኤልን ባንዲራ መሬት ላይ ጥለው ሲረግጡትና የሚያልፉ መኪናዎችም እንዲረግጡት ሲያደርጉ የሚያሳይ ተንቀሳቃሽ ምስል ዓለምን አዳርሷል። ​ይህ ድርጊት የሚያሳየን ትልቅ የህሊና ሀቅ አለ፤ የሰው ልጅ የቱንም ያህል በደስታ ቢዋጥም፣ በዓለም ላይ የሚፈጸመው የንጹሃን ደም እና የጭቆና በደል ህሊናውን አይለቀውም። እውነተኛ የሰው ልጅነት ስሜት የሚንጸባረቀው የራሳችንን ደስታ ስናከብርም የሌሎችን ስቃይ አለመዘንጋት ላይ ነው። ማህበረሰቡ ለፍትህ ያለው ጥማትና ለጭቆና ያለው ጥላቻ በማንኛውም አጋጣሚ ብቅ ማለቱ አይቀርም። ​የትም እንሁን ምን፣ የቱንም ያህል የደስታ ማዕበል ውስጥ እንዋጥ፤ የተበደሉትን ማስታወስና ለጭቆና ስርዓት እምቢ ማለት የህያው ህሊና ምልክት ነው። © ግፍን በቻልነው አቅም መታገል የሚያሰለች መሆን የለበትም!

እዚህ ጋር ያልመረጣችሁ ካላችሁ አሁንም መምረጥና የዳታው አካል መሆን ትችላላችሁ። ምርጫችሁ ጥቅም አለው።

በፍልስጤማውያን ላይ የሚፈጸመውን ግፍ አውግዘን ስንጽፍ መጥተው የሚዘልፉን አንዳንድ ሰዎች የሚያሳዩት ግብዝነት ይገርማል። እነዚህ ወገኖች ትላንት በአካባቢያቸው አብረዋቸው ይኖሩ የነበሩትን ቤተ እስራኤላውያን በተለያዩ አግላይ ስሞች (እንደ 'ፈላሻ' እና 'ቡዳ') ሲያሸማቅቁና ቁምስቅላቸውን ሲያሳዩ የኖሩ ናቸው። ዛሬ ላይ ይህንን ዓለም አቀፍ ግፍ የምትከላከሉት ለግፍ ፈጻሚው አካል የተለየ ፍቅር ኖሯችሁ ሳይሆን፣ ጥቃቱ እየደረሰ ያለው በሙስሊሙ ላይ ነው በሚል እሳቤ ብቻ እንደሆነ ግልጽ ነው። ቨዲዮውን ለመመልከት

ምዕራቡ ዓለም በሙስሊሙ ላይ የሽብርተኝነት ታርጋ ከለጠፈባቸው ተግባራት መካከል፣ እነሱ ራሳቸው ያልፈጸሙት አንድ እንኳ ተግባር ካለ ጥቀሱልኝ! ኮሜንት በዚህ ማድረግ ይችላሉ።

የቁርኣን ብርሃን ወደ ቤትዎ ያምጡ! — ከአንደሉስ የቁርኣን አካዳሚ ጋር! ​ጊዜና ቦታ ሳይገድብዎ፣ በሥራ ውጥረትም ሆነ በቤተሰብ ኃላፊነት መካከል ሆነው የጌታዎን ቃል (ቁርኣንን) መማር ይፈልጋሉ? ​"አንደሉስ የቁርኣን አካዳሚ" ዘመኑ ያፈራውን ቴክኖሎጂ በመጠቀም፣ ርቀትን አቅርቦና ጊዜን ቆጥቦ የቁርኣን ትምህርትን እጅግ ማራኪ በሆነ መልኩ በደጅዎ አቅርቧል! ​ኦንላይን (በበይነ-መረብ) መቅራትዎ የሚያስገኝልዎት ልዩ ጥቅሞች፦ • ​ምቹ የሰዓት ምርጫ፦ በሥራ፣ በትምህርት ወይም በሌሎች ማኅበራዊ ኃላፊነቶች ቢጠመዱም፣ የትምህርት ሰዓትዎን 100% ለእርስዎ በሚመች የትረፍ ሰዓት ማስተካከል ይችላሉ። • ​የትራንስፖርት ድካምና ወጪ የሌለበት፦ ከትራፊክ መጨናነቅ፣ ከታክሲ ሰልፍ እና ከተጨማሪ ወጪ ነጻ በሆነ መልኩ፤ የቤትዎ ሙቀትና ምቾት ሳይለይዎት ቁርኣንን ይቀራሉ። • ​የግል ትኩረት (One-on-One Session)፦ በክፍል ውስጥ ከብዙ ተማሪዎች ጋር ከመማር ይልቅ፣ መምህሩ ሙሉ ጊዜውንና ትኩረቱን ለእርስዎ ብቻ ይሰጣል። ይህ ደግሞ የንባብ ስህተቶችዎን በፍጥነት ለማረምና ተጅዊድዎን በአጭር ጊዜ ለማስተካከል እጅግ ይረዳል። • ​ ብቁ መምህራን ከየትኛውም ቦታ፦ አካባቢዎ ላይ ብቁ የቁርኣን መምህራን ባይኖሩም እንኳ አያስቡ፤ አንደሉስ አካዳሚ የትም ሀገር ቢሆኑ በቂ ልምድና ዕውቀት ካላቸው ምርጥ መምህራን ጋር በቀጥታ ያገናኝዎታል። • ​ለልጆች ደኅንነት እና ለወላጅ የልብ ዕረፍት፦ ልጆችዎ ከዓይንዎ ሳይርቁ፣ በቤትዎ ውስጥ ሆነው ትምህርታቸውን በደስታ ሲከታተሉ ማየት ለእርስዎ ትልቅ የልብ ዕረፍት ይሰጥዎታል። ቴክኖሎጂን ለበጎ ነገር እንዲጠቀሙበትም ያደርጋቸዋል። ​በአንደሉስ አካዳሚ ምን ምን ይማራሉ? • ​ለጀማሪዎች፦ ፊደላትን ከመለየት ጀምሮ መሠረታዊ የቃዒዳ ትምህርት • ​ለአንባቢዎች፦ ቁርኣንን ከነ ሕጉ (በተጅዊድ) የማንበብ ልምምድ • ​ለሐፊዞች፦ የቁርኣን ሂፍዝ (ማፈዝ) እና የሙራጀዓ (ክለሳ) ፕሮግራም ​ለእርስዎም ሆነ ለልጆችዎ የሚሆን ጥራት ያለው ትምህርት አዘጋጅተን እንጠብቅዎታለን። ቁርኣን የልብ ብርሃን፣ የኑሮ በረከት ነው፤ ይህንን በረከት ዛሬውኑ ወደ ሕይወትዎ ያስገቡ! ​ምዝገባ ጀምረናል! ​ለበለጠ መረጃ እና ለመመዝገብ፦ • ​ዋትስአፕ (WhatsApp)፦ [0941415977] • ​ቴሌግራም፦ [0941415977] ​አንደሉስ የቁርኣን አካዳሚ — ቁርኣንን በየትኛውም ቦታ፣ በማንኛውም ሰዓት!