በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የከተማ ውበትና አረንጓዴ ልማት ቢሮ
Ir al canal en Telegram
Every one comment us about the informations that we are uploading. you are also very wellcommed to give us nominations which helps us to improve our capability with regard to the concerns of the organization.
Mostrar más1 502
Suscriptores
+324 horas
+37 días
+1930 días
Carga de datos en curso...
Canales Similares
Nube de Etiquetas
Sin datos
¿Algún problema? Por favor, actualice la página o contacte a nuestro gerente de soporte.
Menciones Entrantes y Salientes
---
---
---
---
---
---
Atraer Suscriptores
agosto '26
agosto '26
+3
en 0 canales
julio '26
+47
en 0 canales
Get PRO
junio '26
+51
en 0 canales
Get PRO
mayo '26
+38
en 0 canales
Get PRO
abril '26
+33
en 0 canales
Get PRO
marzo '26
+37
en 0 canales
Get PRO
febrero '26
+30
en 0 canales
Get PRO
enero '26
+37
en 0 canales
Get PRO
diciembre '25
+42
en 0 canales
Get PRO
noviembre '25
+64
en 0 canales
Get PRO
octubre '25
+52
en 0 canales
Get PRO
septiembre '25
+44
en 0 canales
Get PRO
agosto '25
+47
en 0 canales
Get PRO
julio '25
+47
en 0 canales
Get PRO
junio '25
+37
en 0 canales
Get PRO
mayo '25
+31
en 0 canales
Get PRO
abril '25
+50
en 0 canales
Get PRO
marzo '25
+52
en 0 canales
Get PRO
febrero '25
+51
en 0 canales
Get PRO
enero '25
+79
en 0 canales
Get PRO
diciembre '24
+134
en 0 canales
Get PRO
noviembre '24
+98
en 0 canales
Get PRO
octubre '24
+95
en 0 canales
Get PRO
septiembre '24
+74
en 0 canales
Get PRO
agosto '24
+111
en 0 canales
Get PRO
julio '24
+32
en 0 canales
Get PRO
junio '24
+32
en 0 canales
Get PRO
mayo '24
+51
en 0 canales
Get PRO
abril '24
+177
en 0 canales
Get PRO
marzo '24
+555
en 0 canales
| Fecha | Crecimiento de Suscriptores | Menciones | Canales | |
| 02 agosto | 0 | |||
| 01 agosto | +3 |
Publicaciones del Canal
ለአንድ ጀምበር የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ቅድመ ዝግጅት ተጠናቋል!
የዘንድሮው የአንድ ጀምበር የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ከባለፉት ዓመታት በላቀ ሁኔታ በታላቅ ዝግጅት ለመተግበር የመጨረሻው ምዕራፍ ላይ ደርሷል። ለመላው የመዲናችን ህዝብ የተላለፈው ጥሪ እና የተደረገው ቅድመ ዝግጅት ኢትዮጵያውያን በነቂስ ወጥተው ታሪክ ለመስራት በጉጉት እንዲጠብቁ አድርጓቸዋል።
የዘመቻውን ስኬታማነት ለማረጋገጥ የሚያስፈልጉ ዋና ዋና የቅድመ ዝግጅት ስራዎች ሙሉ በሙሉ ተጠናቀዋል። ለችግኞቹ የሚሆኑ የጉድጓድ ቁፋሮዎች፣ ጥራት ያላቸው የችግኝ አይነቶች ዝግጅት እንዲሁም የችግኝ ስርጭት ስራዎች ተጠናቀው ወደ መከላው ቦታ ደርሰዋል። ይህ ስራ በሳይንሳዊ መንገድ መከናወኑ የችግኞቹን የመፅደቅ ዕድል በከፍተኛ ደረጃ ያሳድገዋል።
የህብረተሰቡን ተሳትፎ ለማጠናከር ሰፊ የኮሙኒኬሽን ስራዎች ተሰርተዋል። እያንዳንዱ ዜጋ ስለ ተከላው ቦታ፣ ሰዓት እና ስለሚተከሉት የችግኝ አይነቶች (በተለይም ለምግብነትና ለጥላ የሚሆኑ) በቂ መረጃ እንዲያገኝ ተደርጓል። በዚህም ምክንያት አረንጓዴ አሻራውን ለማኖር የማይዘጋጅና የማይጓጓ አንድም ዜጋ የለም ለማለት ይቻላል።
ይህ ብሄራዊ ጥሪ ለነገው ትውልድ የሚተርፍ አረንጓዴ አካባቢን ለመፍጠር፣ የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም እና የሀገራችንን የምግብ ዋስትና ለማረጋገጥ የሚደረግ ታላቅ ዘመቻ ነው። መላው ህዝብ በአንድነት በመነሳት አሻራውን የሚያኖርበትና የሀገር ፍቅሩን በተግባር የሚያሳይበት ታሪካዊ ቀን ይሆናል።
ለምለምና ዉብ ሀገር ሰርተን ለቀጣይ ትዉልድ እናሻግር!
| 2 | Sin texto... | 56 |
| 3 | #የአረንጓዴ አሻራችን ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ
አረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ከተጀመረበት ጊዜ አንስቶ የተራቆቱ መሬቶችን መልሶ ከማልማት ባለፈ ችግኝ በማፍላት፣ በመትከልና በመንከባከብ ሂደት ለበርካታ ዜጎች የሥራ ዕድል ተፈጥሯል።
ይህ ንቅናቄ በተለይ ለወጣቶችና ለሴቶች የገቢ ምንጭ በመሆን አረንጓዴ ኢኮኖሚን እውን እያደረገ ይገኛል።
የኢትዮጵያ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ሀገራዊ ገጽታን ከማልማትና የአየር ንብረት ለውጥን ከመከላከል ባሻገር ትልቅ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳን ይዞ መጥቷል።
መርሃ ግብሩ ከተፈጥሮ ጥበቃ ጎን ለጎን የዜጎችን የኑሮ ሁኔታ የሚያሻሽል፣ ሥራ አጥነትን የሚቀንስ እና ዘላቂ የገቢ ምንጭን የሚፈጥር ሆኗል።
በሺህ የሚቆጠሩ የችግኝ ማፍያ ጣቢያዎች በመገንባታቸው ምክንያት በሚሊየኖች የሚቆጠሩ ዜጎች ጊዜያዊና ቋሚ የሥራ ዕድል ተፈጥሮላቸዋል፡፡
ወጣቶችና ሴቶች በጥቃቅንና አነስተኛ ማህበራት ተደራጅተው ችግኝ በማፍላት፣ በማከፋፈልና በመሸጥ ገቢ አግኝተዋል።
እንደ አቮካዶ፣ ማንጎ እና ፓፓያ ያሉ ለምግብ ዋስትና የሚረዱ ፍራፍሬዎችን በማልማት የቤተሰብ ገቢን ማሳደግ ተችሏል።
የተተከሉ ችግኞችን በባለቤትነት በመንከባከብ ሂደት ውስጥ የብዙዎች የዕለት ተዕለት ኑሮ ተደግፏል።
አረንጓዴ አሻራ የደን ሽፋንን ከመጨመርና አካባቢን ከማነቃቃት አልፎ አረንጓዴ ኢኮኖሚን በመገንባት ለበርካታ ዜጎች የስራ ዕድል በመፍጠር የኢኮኖሚ ማነቃቂያ ሆኗል።
ይህንን ህዝባዊ ንቅናቄ አጠናክሮ በመቀጠል የተፈጥሮ ሀብትንና የሰውን ህይወት መቀጠል የሁሉም ኃላፊነት ነው።
#ሰኞ ሐምሌ 27፣2018 ዓ.ም ለሚካሄደው በአንድ ጀምበር የ800 ሚሊየን ችግኞች ተከላ ተዘጋጅተዋል? | 169 |
| 4 | Sin texto... | 150 |
| 5 | የህብረተሰባችን ንቁ ተሳትፎ የአረንጓዴ አሻራችን የጀርባ አጥንት ነዉ!
የአንድ ሀገር እድገትና ህልውና የሚረጋገጠው በተፈጥሮ ሀብቷ መበልጸግ እና በህዝቦቿ የተባበረ ክንድ ነው። በሀገራችን ኢትዮጵያ እየተተገበረ ያለው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር የዱር እንስሳትንና እፅዋትን ከመንከባከብ ባለፈ፣ የሀገሪቱን ሁለንተናዊ ገጽታ እየቀየረ ያለ ታላቅ ሀገራዊ ንቅናቄ ነው።
የዚህ ግዙፍ ጉዞ ስኬትና የጀርባ አጥንት ደግሞ ያለ ምንም ጥርጥር የመላው ህብረተሰባችን ንቁና ያልተቆጠበ ተሳትፎ ነው። ይህ ንቅናቄ ተራ የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር ሳይሆን የነገዋን የበለጸገችና የተከበረች ኢትዮጵያን የመገንባት መሰረት ነው።
በአረንጓዴ አሻራ ውስጥ ጤና፣ ምግብ፣ ውበትና ክብር አለ። ዛሬ የምንተክለው እያንዳንዱ ችግኝ ነገ ንጹህ አየርን የሚለግሰን የጤናችን ዋስትና ነው። የአፈር መሸርሸርን በመከላከልና የምግብ ዋስትናን በማረጋገጥ ረገድም የአረንጓዴ አሻራ ፋይዳ ወደር የለውም። ከተሞቻችንና ገጠሮቻችን በለመለመ አረንጓዴ ተሸፍነው ሲያምሩ የአካባቢ ውበትን ከመፍጠር ባለፈ፣ ለትውልድ የሚተርፍ ኩራትንና ክብርን ያጎናጽፉናል።
በአረንጓዴ አሻራ ውስጥ ስራም ህይወትም አለ፤ ምክንያቱም የአካባቢ ጥበቃው በርካታ የስራ እድሎችን ከመፍጠሩም በላይ ለህይወት ቀጣይነት ወሳኙን የአየር ንብረት ሚዛን ይጠብቃል።
ከዚህም በላይ ይህ መርሃ-ግብር ማህበራዊና ፖለቲካዊ እሴቶቻችንን የሚያጠነክር ታላቅ መድረክ ነው። በአረንጓዴ አሻራ ውስጥ አንድነት፣ መቀራረብ፣ ኃይል፣ ተስፋ እና አሸናፊነት አለ። ህዝባችን ልዩነቶቹን ወደ ጎን በመተው ለአንድ አላማ ሲሰለፍ ንጹህ መኖሪያ አካባቢን መፍጠር ብቻ ሳይሆን ጤናማ የውጭ ግንኙነትንም ይገነባል።
አረንጓዴ ልማት አመቺ የአየር ንብረትን ከመፍጠሩም ባሻገር፣ ዘላቂና አስተማማኝ የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚ እንዲሁም የማህበራዊ ቅቡልነትና ተሰሚነትን በዓለም አቀፍ መድረክ ያረጋግጣል። ከሁሉም በላይ ደግሞ ዜጎች በራሳቸው ሀገር እንዲተማመኑና አንገታቸውን ቀና አድርገው እንዲሄዱ ያደርጋል።
የዘንድሮው የ2018/19 ዓ.ም የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር እና በተለይም የአንድ ጀንበር የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር የሀገራችንን የአረንጓዴ አሻራ አድማስ በእጅጉ የሚቀይሩ የትኩረት መስኮች ናቸው። በዚህ ታላቅ መርሃ-ግብር ላይ ከተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች የተውጣጡ ወጣቶች፣ ሴቶች፣ ተማሪዎች፣ የሃይማኖት ተቋማት፣ ሲቪል ማህበራት እና የፀጥታ ተቋማት ይሳተፋሉ።
እንዲሁም ሀገር በቀልና ሀገር በቀል ያልሆኑ ልዩ ልዩ ድርጅቶችና ተቋማት የበኩላቸውን አሻራ ያኖራሉ። ይህ ሰፊ ተሳትፎ የሀገራችን ልማትና ክብር የህዝቦቿ የተባበረ ክንድ መሆኑን በተግባር የሚያረጋግጥ ነው።
በማጠቃለያው መላውን ህብረተሰብ በንቅናቄ በዚህ ታላቅ ሀገራዊ ተልዕኮ ላይ አካል ማድረግ የአንድነታችን መገለጫ ነው። በአንድነታችን ሀገራችንን ማልማትና ማስከበር እንደምንችል ለዓለም የምናሳይበት የብርታታችን ምንጭም ነው። እያንዳንዱ ዜጋ የዘንድሮውን የአንድ ጀንበር የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር የወደፊት ህይወቱን፣ ጤናውንና የሀገሩን ክብር የመገንቢያ ታላቅ አጋጣሚ አድርጎ በመውሰድ የበኩሉን አረንጓዴ አሻራ ሊያኖር ይገባል። | 170 |
| 6 | Sin texto... | 145 |
| 7 | Sin texto... | 230 |
| 8 | አዲስ አበባ በአንድ ጀምበር 1 ሚሊዮን ችግኞችን ለመትከል ተሰናድታለች፤
አዲስ አበባ ከተማ በዘንድሮው የ2018/19 የክረምት ወቅት የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ታሪካዊ ሊባል የሚችል የአንድ ጀምበር የችግኝ ተከላ ለማካሄድ የመጨረሻ ዝግጅቷን አጠናቃለች። ለዚህ የአንድ ጀንበር ክንዉን በ248 ሄክታር መሬት ላይ 176 የተከላ ቦታዎች መዘጋጀታቸዉን ማወቅ ተችሏል፡፡
መዲናዋ በመጪው ሐምሌ 27 ቀን 2018 ዓ.ም በሚካሄደው በዚህ ደማቅ መርሃ ግብር ላይ በአንድ ጀምበር ብቻ 1 ሚሊዮን ችግኞችን ለመትከል አቅዳ እየሰራች ትገኛለች። ይህ ታላቅ ህዝባዊ ንቅናቄ የአካባቢ ጥበቃን ከማረጋገጥ ባለፈ የከተማዋን ውበትና የአየር ንብረት ሚዛን ለመጠበቅ ታላቅ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ተብሏል።
በዕለቱ በሚካሄደው ሰፊ የልማት ዘመቻ ላይ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች፣ የመንግስት ሰራተኞች፣ ወጣቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎችና የዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ አባላት በነቂስ ወጥተው እንደሚሳተፉ ይጠበቃል።
ዘንድሮ የሚተከሉት ችግኞች በጥንቃቄ የተመረጡ ሲሆን ትኩረታቸውም በምግብ ዋስትና ላይ አወንታዊ ተፅዕኖ በሚፈጥሩ የፍራፍሬ ተክሎች እና የአካባቢውን ስነ-ምህዳር በሚያድሱ ሀገር በቀል ዛፎች ላይ የተመሰረተ ነው። ይህ የዝግጅት ምዕራፍ የተከላ ቦታዎችን የመለየትና ጉድጓድ የመቆፈር ስራዎችን ያካተተ ሲሆን ለችግኞቹ ቀጣይ እንክብካቤና መፅደቅ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶታል።
ይህ በዋና ከተማዋ የሚከናወነው ታላቅ መርሃ ግብር በሀገር አቀፍ ደረጃ በአንድ ጀምበር 800 ሚሊዮን ችግኞችን ለመትከል ከተያዘው ታላቅ ብሄራዊ እቅድ ጋር የተቆራኘ አካል ነው። ኢትዮጵያ በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር አማካኝነት በአለም አቀፍ መድረክ በበጎ ተፅዕኖ ፈጣሪነቷ እየተገነባች ሲሆን ይህ ንቅናቄ የቀጠናውን የአየር ንብረት ወደ ማመጣጠን ለመሸጋገር እንደ ትልቅ ድልድይ ያገለግላል።
ከዚህም ባለፈ የአረንጓዴ ዲፕሎማሲ የበላይነትን ለመያዝ የሀገርን ሉዓላዊነት በተግባር ለማስከበር እና ብሄራዊ ፍላጎቶቻችንን በስኬት ለማሳካት እንደ ዋነኛ መሳሪያ ተወስዷል።
በመጨረሻም ይህ የክረምት የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር የኢትዮጵያውያንን አንድነት ይበልጥ የሚያጠናክርበት መድረክ መሆኑ ተገልጿል።
ዜጎች ልዩነቶቻቸውን ወደ ጎን በመተው ለሀገራዊ ልማት በጋራ የሚቆሙበት እና ዘላቂ ሰላምን በተግባር የሚገነቡበት ታላቅ የሰላም መድረክ ሆኖ ያገለግላል።
መላው የአዲስ አበባ ነዋሪዎች በሐምሌ 27ቱ የአንድ ጀምበር ታሪካዊ ተከላ ላይ በመሳተፍ አረንጓዴ አሻራቸውን እንዲያሳርፉ ጥሪ ቀርቧል። | 222 |
| 9 | Sin texto... | 202 |
| 10 | በአንድ ጀምበር 800 ሚሊየን ችግኞችን በመትከል ታሪክ ልንሰራ 3 ቀን ብቻ ቀረን!
በጋራ ተስፋን እንትከል! | 217 |
| 11 | #የዛሬዉ አረንጓዴ አሻራችን ለነገው ትውልድ መድህን ነው
የመዲናችንን የአንድ ጀምበር የክረምት አረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ከአራት ቀናት በኋላ ሐምሌ 27 ቀን 2018 ዓ.ም ይከናወናል። ይህ ታላቅ ብሄራዊ ጥሪ የከተማችንን ውበትና የአየር ንብረት በአስተማማኝ ደረጃ ላይ ለማድረስ የምናደርገው የጋራ ዘመቻ ነው።
ይህ ዘመቻ ለከተማችን ውበት፣ ለሀገራችን ሁለንተናዊ እድገት እንዲሁም ቀጣናዊ አህጉራዊና ዓለም አቀፋዊ ተፅዕኖ ፈጣሪነታችንን ለማሳደግ የሚደረግ ታሪካዊ እርምጃ በመሆኑ ሁላችንም በጋራ ልንቆምለት ይገባል።
ለከተማችን ብሎም ለሀገራችን የምናበረክተው ይህ አረንጓዴ አሻራ ዛሬን አሳምረን ነገን የምንገነባበትና ታሪክን ወደ ሚቀጥለው ትውልድ በክብር የምናሸጋግርበት ድልድይ ነው።
ለዚህ ታላቅ ሀገራዊ ክንውን ቀዳሚው ተግባራችን በስነ-ልቦና መዘጋጀት ነው። በጋራና በአንድነት መስራት ያለውን ትልቅ አቅም በመገንዘብ የነገውን አዲሱን ትውልድ መልካም የስራ ባህል ትብብርና ፍቅር በተግባር ልናስተምረው ይገባል።
አንድነት ኃይል በመሆኑ በስምምነትና በጋራ የሚሰራ ስራ ውጤቱ ሁልጊዜም ታላቅና አመርቂ ነው። በዚህ ዘመቻ የምናሳየው ትጋት የከተማችንን ገጽታ ከመቀየር ባለፈ በመካከላችን ያለውን አብሮነትና የስራ ባህል የሚያሻሽል ይሆናል።
የምንፈልገውን ለውጥ ማምጣትና የአረንጓዴ ሌጋሲ ለሀገራችን የሚያስገኘውን ታላቅ ክብርና ሽልማት በጋራ ማረጋገጥ እንችላለን።
የችግኝ ተከላው ስኬታማ እንዲሆን የቴክኒክና የእንክብካቤ ዝግጅቶች እኩል መከናወን አለባቸው። የሚተከሉትን ችግኞች ከመሬት ማረፋቸው በፊት በአግባቡ መያዝና እንደየዘርፋቸው ተስማሚ በሆነው ቦታ ላይ መትከል ያስፈልጋል።
በተከላው ሂደት ላይ ማንኛውም አይነት ችግር ወይም ጥያቄ ካጋጠመን የባለሙያ እርዳታ መጠየቅ ተገቢ ነው።
ከሁሉ በላይ ደግሞ የተከልንባቸውን ቦታዎች ለይተን በመያዝ ወቅቱ ሲደርስ ተመልሰን ተገቢውን ክትትልና እንክብካቤ በማድረግ ችግኞቹ እንዲጸድቁ የበኩላችንን መወጣት ይኖርብናል። ለሐምሌ 27 በጋራ እንዘጋጅ! | 407 |
| 12 | Sin texto... | 415 |
| 13 | የመዲናዋ ወንዞች ንፅህና እንዲረጋገጥ በተከናወነው ሥራ የማህበረሰቡ ቆሻሻ የማስወገድ ባህልና አቅም አድጓል
የአዲስ አበባ ወንዞች ንፅህና እንዲረጋገጥ በተከናወነው ሥራ የማህበረሰቡ ቆሻሻ የማስወገድ ባህልና አቅም ማደጉን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የከተማ ውበትና አረንጓዴ ልማት ቢሮ ገለፀ።
የቢሮው ምክትል ሃላፊ ኢንጂነር እንዳሻው ከተማ ከአዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ በከተማዋ በ2018 ዓ.ም በርካታ የአረንጓዴ ቦታዎችን ማልማት ተችሏል ብለዋል።
በአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር በበጀት ዓመቱ 5 ነጥብ 6 ሚሊየን ችግኞችን ተክለናል ያሉት ምክትል ሃላፊው ዜጎችን በማሳተፍ የሚከናወነው የተፋሰስ ሥራ ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ መሆኑንም አንስተዋል፡፡
በ2018 ዓ.ም 8 ወንዞች ላይ የወንዝና ወንዝ ዳርቻ የልማት ሥራዎች እንደተከናወኑ ገልጸው ከእነዚህ መካከል በአጭር ጊዜ ውስጥ ተገንብቶ በቅርቡ ተመርቆ አገልግሎት መስጠት የጀመረው የቀበና ወንዝን ጨምሮ የቀጨኔ ወንዝ ዳርቻ፣ የአርሴማ የወንዝ ዳርቻ ተጠቃሽ መሆናቸው ተናግረዋል፡፡
ይሄም የወንዝ ዳርቻዎች የቱሪስት መዳረሻ እንዲሆኑ አዋቂዎች እና ህጻናት በነጻነት እንዲንቀሳቀሱ፣ እንዲዝናኑ ከማድረግ ባለፈ አካባቢዎችም የስጋት ስፍራ እንዳይሆኑ አድርጓል፡፡
በአረንጓዴ ልማት ላይ ያለው የማህበረሰቡ ግንዛቤ ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ መምጣቱንም በመጥቀስ አረንጓዴ ቦታዎችን ለመጠበቅ መንግስት ብቻ ሳይሆን ሁሉም ዜጋ ሃላፊነት አንዳለበት አመላክተዋል።
ዜጎች አካባቢያቸውን ከብክለት እንዲጠብቁ፤ የከተማዋ ወንዞች ንጽህና እንዲረጋገጥ የፍሳሽ ማስወገጃ መስመር መዘርጋቱንም ምክትል ሃላፊው አንስተዋል።
እንዲሁም የወንዞች ንፅህና እንዲረጋገጥ በተከናወነ ሥራ የማህበረሰቡ ቆሻሻ የማስወገድ አቅም ማደጉን በመግለፅ ደረቅ ቆሻሻም ይሁን ፍሳሽ ወደ ወንዝ እንዳይለቀቅ ስራዎች ሲከናወኑ እንደነበር አስታውሰዋል።
የከተማዋ ነዋሪዎች አካባቢያቸውን ጠባቂ እንዲሆኑ ፣ በከተማዋ የንጽህና መጠበቂያ ቤቶችንም በማስፋፋት ለህብረተሰቡ አገልግሎት እንዲሰጡ አድርገናል ብለዋል።
ኢንጂነር እንዳሻው ከተማ እንደገለፁት ፤ በከተማዋ በአረንጓዴ ልማት ላይ መረጃ ለመለዋወጥ የሚያስችሉ አሰራሮችም ተዘርግተዋል። | 262 |
| 14 | Sin texto... | 227 |
| 15 | Sin texto... | 217 |
| 16 | Sin texto... | 291 |
| 17 | የመዲናዋ የአንድ ጀንበር የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር ቅድመ ዝግጅት ስራ ከወዲሁ መጠናቀቁ ተገለፀ፡፡
የከተማ ዉበትና አረንጓዴ ልማት ቢሮ የዘንድሮ 2018/19 የመዲናዋን የአንድ ጀምበር የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር ቅድመ ዝግጅት ስራ ማጠናቀቁን ገልጿል፡፡
በዛሬዉ ዕለት በአንድ ጀምበር የሚተከሉ ችግኞችን በተከላዉ ቦታ ተገኝተዉ መረጃን ቴክኖሎጂ በመጠቀም በለማዉ ሶፍት ዌር ወደ መረጃ ቋት ለሚያስገቡ ከየወረዳዉ ለተዉጣጡ የከተማ ዉበትና አረንጓዴ ልማት ቢሮ ባለሙያዎች ቴክንካል በሆኑ ጉዳዮች ዙሪያ አስፈላጊዉ ገለፃ ተደርጓል፡፡
በገለፃዉ ወቅት የመረጃ አያያዝ፤የተተከሉ ችግኞችን ሪፖርት ማድረጊያ መንገድ፤መልካም አጋጣሚዎች እና በሂደቱ ሊከሰቱ በሚችሉ ተግዳሮቶች እና መፍትሄዎቻቸዉ ዙሪያ ሰፊ ማብራሪዎች የተሰጡ ሲሆን የተተከሉ ችግኞች ሪፖርት በሚደረጉበት ጊዜ ከፍተኛ ጥንቃቄ ማድረግ እንደሚገባ አፅንኦት ተሰጥቶታል፡፡
በመድረኩ የተገኙት የቢሮዉ ም/ኃላፊ ኢንጂነር እንዳሻዉ ከተማ ችግኞችን በስታንዳርድ መትከል እና መረጃ አያያዛችን ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተሻሻለ መጥቷል ያሉ ሲሆን የችግኝ ተከላ ጉዳይ ከሀገር አልፎ አለም አቀፍ አጀንዳ እየሆነ በመምጣቱ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ መትከልና ሪፖርት ማድረግ ይገባል ብለዋል፡፡
በሌላ በኩል የቢሮው ም/ኃላፊ ወ/ሮ ፀሐይ ጌታሁን በበኩላቸው በእያንዳንዱ የተከላ ቦታ የተመደበውን የችግኝ መጠን በትክክል ለይቶ ማወቅና ትክክለኛውን የተተከለ ችግኝ ሪፖርት ማድረግ ወሳኝ መሆኑን ገልጸው ጉዳዩ አገራዊ አጀንዳ በመሆኑ ሁላችንም በትኩረትና ወጥ በሆነ አሰራር ልንተገብረው ይገባል ብለዋል።
ከባለሙያዎቹም የተለያዩ ጥያቄዎችና አስተያየቶች የተነሱ ሲሆን ከመድረክ እና በቢሮዉ የተፋሰስና አረንጓዴ ልማት ዳይሬክተር ወ/ሮ ስንታየሁ መንግስቱ ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዉበታል፡፡
በመጨረሻም ይህን ትልቅ አጀንዳ የሆነዉ የአንድ ጀምበር የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር በተቀናጀና በታቀደዉ መሰረት በስኬት ማጠናቀቅ እንደሚገባ ጥብቅ አቅጣጫ ተቀምጧል፡፡ | 259 |
| 18 | Sin texto... | 236 |
| 19 | Sin texto... | 407 |
| 20 | የኢትዮጵያውያን ክንድ ተባብሮ፣ በአንድ ጀምበር 800 ሚሊዮን ችግኞችን በመትከል ሌላ ታሪክ ለመስራት 5 ቀናት ብቻ ቀርተዋል! ውድ የሀገሬ ልጆች፤ በእነዚህ ቀናት አስፈላጊውን ዝግጅት እንድታደርጉ፣ በቁርጠኝነት እንድትነሱ እና በአንድነታችን የምናስመዘግበውን ድል እውን እንድናደርግ ጥሪዬን አቀርባለሁ።
በጋራ ተስፋን እንትከል!
Irreen Itoophiyaanotaa walta'insaan guyyaa tokkotti biqiltuuwwan miliyoona 800 dhaabuudhaan seenaa kanbiraa hojjechuuf guyyoota 5 qofaatu hafe! Ijoollee biyyakoo jaalatamoo, guyyoota kanneenitti qophii barbaachisaa akka gootan, kutannoodhaan akka kaataniifi injifannoo tokkummaa keenyaan galmeessifnu akka dhugoomsitanin waamichakoo dhiyeessa.
Waliin abdii haadhaabnu!
Only 5 days remain to make history through the united arm of all Ethiopians by planting 800 million seedlings in a single day! In these remaining days, I call upon my beloved fellow citizens to make the necessary preparations, rise with determination, and ensure the victory we will achieve in our unity.
Together, let us plant hope!
#GreenLegacy | 300 |
