uk
Feedback
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የከተማ ውበትና አረንጓዴ ልማት ቢሮ

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የከተማ ውበትና አረንጓዴ ልማት ቢሮ

Відкрити в Telegram

Every one comment us about the informations that we are uploading. you are also very wellcommed to give us nominations which helps us to improve our capability with regard to the concerns of the organization.

Показати більше
1 476
Підписники
+224 години
+67 днів
+1330 день

Триває завантаження даних...

Хмара тегів
Немає даних
Виникли проблеми? Будь ласка, оновіть сторінку або зверніться до нашого support-менеджера.
Вхідні та вихідні згадування
---
---
---
---
---
---
Залучення підписників
червень '26
червень '26
+35
в 0 каналах
травень '26
+38
в 0 каналах
Get PRO
квітень '26
+33
в 0 каналах
Get PRO
березень '26
+37
в 0 каналах
Get PRO
лютий '26
+30
в 0 каналах
Get PRO
січень '26
+37
в 0 каналах
Get PRO
грудень '25
+42
в 0 каналах
Get PRO
листопад '25
+64
в 0 каналах
Get PRO
жовтень '25
+52
в 0 каналах
Get PRO
вересень '25
+44
в 0 каналах
Get PRO
серпень '25
+47
в 0 каналах
Get PRO
липень '25
+47
в 0 каналах
Get PRO
червень '25
+37
в 0 каналах
Get PRO
травень '25
+31
в 0 каналах
Get PRO
квітень '25
+50
в 0 каналах
Get PRO
березень '25
+52
в 0 каналах
Get PRO
лютий '25
+51
в 0 каналах
Get PRO
січень '25
+79
в 0 каналах
Get PRO
грудень '24
+134
в 0 каналах
Get PRO
листопад '24
+98
в 0 каналах
Get PRO
жовтень '24
+95
в 0 каналах
Get PRO
вересень '24
+74
в 0 каналах
Get PRO
серпень '24
+111
в 0 каналах
Get PRO
липень '24
+32
в 0 каналах
Get PRO
червень '24
+32
в 0 каналах
Get PRO
травень '24
+51
в 0 каналах
Get PRO
квітень '24
+177
в 0 каналах
Get PRO
березень '24
+555
в 0 каналах
Дата
Залучення підписників
Згадування
Канали
20 червня0
19 червня+3
18 червня+3
17 червня+1
16 червня+5
15 червня0
14 червня+3
13 червня+1
12 червня+1
11 червня+2
10 червня+1
09 червня+4
08 червня+1
07 червня+3
06 червня+2
05 червня+2
04 червня0
03 червня+1
02 червня+2
01 червня0
Дописи каналу
የዘንድሮው የመዲናዋ የክረምት የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ዝግጅትና ተከላ በቴክኖሎጂ የታገዘ ነው፡፡ አዲስ አበባ በየዓመቱ የሚካሄደው የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር የዘንድሮው የክረምት ወቅት ከቀደሙት ዓመታት በተሻለና በተደራጀ ዝግጅት ተግባራዊ ሊደረግ ሙሉ ዝግጅት ተጠናቋል። ይሄው መርሃ ግብር ውጤታማ እንዲሆን ካለፉት ተሞክሮዎች በመነሳት ሰፊ መሻሻሎች መደረጋቸዉ ተመልክቷል። የዘንድሮው መርሃ ግብር ካለፈው ልዩ ባህሪያት መካከል ዘመናዊ ቴክኖሎጂን በስፋት ጥቅም ላይ ማዋሉ ቀዳሚው ነው። የችግኞችን መገኛ ስፍራ፣ የተከላ ቦታዎችን ዝግጁነት እና አጠቃላይ ሂደቱን በሳተላይትና በዲጂታል መተግበሪያዎች ለመከታተል የሚያስችል አሰራር ተዘርግቷል። ይህ የቴክኖሎጂ አጠቃቀም የትኞቹ አካባቢዎች ምን ዓይነት የችግኝ ዝርያ እንደሚያስፈልጋቸው በትክክል ለመለየትና የእያንዳንዱን አካባቢ የተከላ ሂደት በቅርበት ለመቆጣጠር ከፍተኛ እገዛ ያደርጋል። ሌላው ለየት የሚያደርገው ለአረንጓዴ አሻራ ስኬታማነት ለባለሙያዎች ቀድሞ የተሰጠው ሰፊ ስልጠና ነው። ከተከላው አስቀድሞ በየደረጃው ለሚገኙ የከተማ ዉበትና አረንጓዴ ልማት ባለሙያዎች፣ አስተባባሪዎችና የበጎ ፈቃደኞች መሪዎች ስልጠናዎች ተሰጥተዋል። ይህም ባለሙያዎቹ ህብረተሰቡን በተደራጀና በሳይንሳዊ መንገድ እንዲመሩ፣ የችግኝ አተካከል ስልትን እንዲያስተምሩ እና የተከላ ስራው በዘፈቀደ ሳይሆን ጥናትን መሰረት አድርጎ እንዲከናወን ያደርጋል ተብሏል። በዘንድሮው ዝግጅት ሀገራዊ አቅምን በማሳደግ ረገድ በራስ አቅም ችግኞችን በከፍተኛ ጥራት ማዘጋጀት መቻሉ ትልቅ ስኬት ሆኖ የችግኝ ማፍያ ጣቢያዎች በሚሊዮን የሚቆጠሩ ችግኞች እንዲፈሉ ተደርጓል። ይህም ለምግብነት የሚውሉ የፍራፍሬ ፣ የዉበት ፤ ለመድኃኒትነት አግልግሎት የሚዉሉና ለደን ልማት ተስማሚ የሆኑ የሀገር በቀል ዛፎች ዝርያዎችን በራስ አቅም በበቂ ሁኔታ ማቅረብ መቻሉ ተገልጿል። ባለፉት ዓመታት ከተከናወኑ ተግባራት በተገኘ ልምድ የችግኞች የፅድቀት መጠን በከፍተኛ ደረጃ መሻሻሉ ለዘንድሮው ስራ ትልቅ መነሳሳትን ፈጥሯል። በተጨማሪ መትከል ብቻ ሳይሆን የተተከሉትን ችግኞች የመንከባከብና የማፅደቅ ስራ ላይ ትኩረት በመደረጉ፣ የፅድቀት መጠኑ ካለፉት ዓመታት የላቀ ውጤት አሳይቷል። በዘንድሮው መርሃ ግብርም ከተከላ በኋላ ያለውን ክትትልና እንክብካቤ የሚያረጋግጥ የተደራጀ የባለቤትነት አሰራር በመዘርጋቱ የፅድቀት መጠኑ ይበልጥ እንደሚሻሻል ይጠበቃል።

2
+1
Немає тексту...
196
3
ከሊቅ እስከ ደቂቅ ለአረንጓዴዋ መዲና፤ የአዲስ አበባ የችግኝ ተከላ ስኬትና የዘንድሮው ዝግጅት በኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥ እያስከተለ ያለውን አሉታዊ ተፅዕኖ ለከመላከል፣ የምግብ ዋስትናንና ቀጣይነት ያለው የኢኮኖሚ እድገት ለማረጋገጥ የአረንጓዴ አሻራ መርሐ- ግብር በ2011 ዓ.ም መጀመሩ ይታወሳል፡፡ አዲስ አበባም፣ በ2011 ዓ.ም እንደ ሀገር የተጀመረውን የአረንጓዴ አሻራ መረሐ-ግብር ስትራቴጂ በመከተል እና የላቀ ትኩረት በመስጠት ላለፉት 7 ተከታታይ ዓመታት በብዙ ሚሊዮን የሚቆጠሩ ችግኞችን መትከል ችላለች፡፡ በመዲናዋ ባለፉት ሰባት አመታት 90 ሚሊዮን ችግኞች የተተከሉ ሲሆን፣ ከእነዚህ ውስጥ 86 ነጥብ 82 በመቶ የሚሆኑት ችግኞች ፀድቀዋል፡፡ በእነዚህ የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብሮች በሚሊዮን የሚቆጠሩ የመዲናዋ ነዋሪዎች ከሊቅ እስከ ደቂቅ በሚባል ደረጃ የተሳተፉ ሲሆን፣ መንግስታዊ እና መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች፣ የሀይማኖት ተቋማት፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች እና ሌሎችም በጋራ ስለ መዲናዋ ገጽታ ግንባታ እና ለጋራ ጥቅም በጋራ መቆምን ለዓለም ያሳዩበት አኩሪ ተግባር ሆኗል፡፡ የአረንጓዴ አሻራ መርሐ-ግብር አዲስ አበባ ከተማ ለጀመረችው የዘመናዊ ከተማ ግንባታ ሂደት አንዱ ገጽታ ሆኖ እየተተገበረም ይገኛል፡፡ ይህ ተግባር ከተማዋን አረንጓዴ፣ ውብና ለኑሮ ምቹ እንድትሆን እየተሰራ ከሚገኘው የኮሪደር ልማት ስራ ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት ያለው በመሆኑ በየኮሪደሩ በተዘጋጁ የአረንጓዴ እና የመዝናኛ ስፍራዎች ላይ ለመዲናዋ ውበት እና ድምቀት የሚሰጡ የተለያዩ የእዕዋት አይነቶች በብዛት ተተክለዋል፡፡ በመርሐ-ግብሩ በመዲናዋ የሚገኙ በርካታ የተራቆቱ አካባቢዎችን ማልማት የተቻለ ሲሆን፣ የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም፣ በስራ እድል ፈጠራ እና የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ተሰፋ ሰጪ ውጤቶች ተገኘተውበታል፡፡ በተለይ በመዲናዋ እየተከናወነ በሚገኘው የኮሪደር ልማት እየተተከሉ የሚገኙ ችግኞች የመዲናዋን ውበትና ገጽታ ከማላበስ ባለፈ ጤናማ፣ በአካል የዳበረ እና በመንፈስ የተረጋጋ ትውልድ ለመፍጠር በሚደረገው ጥረት የላቀ ሚና እያበረከቱ ይገኛሉ፡፡ ይህንኑ ስኬት በላቀ ደረጃ ለማስቀጠል፣ በአዲስ አበባ ከተማ በዘንድሮው የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር 6 ሚሊዮን ችግኞችን ለመትከል በከተማዋ ሰፊ የቅድመ-ዝግጅት ሥራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ።
191
4
+1
Немає тексту...
154
5
ሀገር በቀል እጽዋቶች እንዲጠበቁ የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር ጉልህ ሚና እያበረከተ ነው ሀገር በቀል እጽዋቶችና የተፈጥሮ ሀብቶች እንዲጠበቁ የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር ጉልህ ሚና እያበረከተ ይገኛል፡፡ የአየር ንብረት ለውጥ የሚያደርሰውን ዓሉታዊ ተፅዕኖ በመከላከል እጽዋቶችንና የተፈጥሮ ሃብትን መጠበቅና በዘላቂነት መንከባብ አስፈላጊ እንደሆነ ይታመናል፡፡ በዚህም የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር የአየር ንብረት ለውጥን የማስተካከል፣ የአካባቢ ጥበቃን የማስጠበቅ፣ የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥና ሌሎች ዘርፈ ብዙ አላማዎች ማሳካቱን ቀጥሏል፡፡ መርሃ ግብሩ በዓለም እየተከሰተ ያለውን የአየር ንብረት ለውጥ ተፅእኖ ከመቋቋም ባለፈ ሀገር በቀል እጽዋቶችንና ሀብቶች እንዲጠበቁ ጉልህ ሚና እየተጫወተ ነው፡፡ ኢትዮጵያ በብዝኃ ሕይወት ኃብታቸው ከሚታወቁ ሀገራት መካከል በግንባር ቀደምትነት የምትጠቀስ ሲሆን፣ በአየር ንብረት ለውጥ የሀገር በቀል እጽዋቶችን ጨምሮ ለብዝኃ ሕይወት ኃብቶች መመናመን ምክንያት እንዳይሆን የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር የራሱን ሚና ይጫወታል፡፡ እንደ ሀገር በ2011 ዓ.ም የተጀመረው የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር ኢትዮጵያውያን በላቀ ትጋት ሀገር በቀል እጽዋቶችን ጨምሮ ለምግብነት የሚያገለግሉ ችግኞችን እየተከሉ ይገኛሉ። በተለይ ሀገር በቀል እጽዋቶች፣ ለመድኃኒትነትና ለተለያዩ ግልጋሎቶች የሚውሉ በመሆናቸው የጥበቃ እንክብካቤ ስራው ይበልጥ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበትም ይታመናል፡፡ የአረንጓዴ አሻራ የአካባቢን ተፈጥሯዊ ገፅታ በመጠበቅና በመንከባከብ የደን መመናመንና የአፈር መሸርሸርን ከመከላከል ባሻገር የሀገሪቱን የደንና የአረንጓዴ ሽፋን በማሳደግ ንፁህ አየርና ውሃ እንዲኖር አድርጓል፡፡ መረጃዎች እንደሚያሳዩት ኢትዮጵያ በአንድ ወቅት ከ40 በመቶ በላይ የደን ሽፋን የነበራት ቢሆንም በወቅቱ በነበረው ዘላቂ ያልሆነ የተፈጥሮ ሀብትና የመሬት አጠቃቀም ምክንያት የደን ሽፋኗ ወደ 3 በመቶ ወርዶ እንደነበር የሚታወስ ነው፡፡ በ2017 ዓ.ም 8 ቢሊየን ችግኞች የተተከሉ ሲሆን፣ በ2018 ዓ.ም ከ8 ቢሊየን በላይ ችግኝ ለመትከል መታቀዱንም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በቅርቡ በይፋ ማስጀመራቸው የሚታወስ ነው፡፡ ይህ ተግባር የኢትዮጵያ የደን ሽፋን መጠንን ወደ 23.6 በመቶ እና ከዛ በላይ እድገት እንዲመዘገብ ለማድረግ ትልቅ አቅም ይፈጥራል፡፡ ለዚህም ለሀገር በቀል እጽዋቶችና ለተፈጥሮ ሀብቶች ጥበቃ ሁሉም የሚጠበቅበትን ድርሻ መወጣት አለበት፡፡
182
6
Немає тексту...
169
7
ለአዲስ አበባ የችግኞች ፅድቀት ስኬት የህብረተሰቡ ሚና ከፍተኛ መሆኑ ተገለፀ፡፡ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ባለፉት ዓመታት የአረንጓዴ አሻራ የተተከሉ ችግኞች የፅድቀት መጠን ከጊዜ ወደ ጊዜ በከ+4
ለአዲስ አበባ የችግኞች ፅድቀት ስኬት የህብረተሰቡ ሚና ከፍተኛ መሆኑ ተገለፀ፡፡ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ባለፉት ዓመታት  የአረንጓዴ አሻራ የተተከሉ ችግኞች የፅድቀት መጠን ከጊዜ ወደ ጊዜ በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ መምጣቱ ተረጋግጧል። ይህ ስኬት ዋና ከተማዋን ወደ ስነ-ምህዳራዊ ሚዛን የመመለስ ጉዞን እያፋጠነው የሚገኝ ሲሆን፣ የከተማዋን ውበት ከመጨመር ባለፈ የአየር ብክለትን በመቀነስ፣ የከርሰ ምድር ውሃን በማበልጸግ እና ነዋሪዎች ንጹህ አየር እንዲያገኙ በማድረግ ረገድ የሚጫወተው ሚና የላቀ ነዉ ተብሏል ። ለችግኞቹ መፅደቅ በዋናነት የተጠቀሰው ምክንያት ችግኝ ከመትከል ባለፈ የተከናወነው የተቀናጀ የእንክብካቤ ስራ መሆኑ ተገልጿል። ተከታታይነት ያለው ውሃ የማጠጣት፣ አረም የማጽዳት እና ችግኞቹን ከእንስሳትና ከሰዎች ንክኪ የመጠበቅ ስራዎች በትኩረት በመሰራታቸው ለውጤቱ መገኘት ትልቅ መሰረት እንደሆነ ተመላክቷል። የተለያዩ የመንግስት እና የግል ተቋማት በየራሳቸው ቅጥር ግቢ እና በ20/50 ሜትር ራዲየስ ዙሪያቸው የተተከሉ ችግኞችን በባለቤትነት ስሜት እንዲንከባከቡ የተደረገው አሰራር ለፅድቀት መጠኑ ማደግ ከፍተኛውን አስተዋጽኦ አበርክቷል። ይህ የተቋማት ተሳትፎ የችግኞችን የመሞት ዕድል በከፍተኛ ደረጃ መቀነሱም ተነግሯል። በቀጣይም ይህንን የተገኘ ስኬት ይበልጥ ለማስቀጠል ማህበረሰቡን በስፋት ባለቤት ያደረገ የቅንጅት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተገልጿል።
198
8
Немає тексту...
250
9
ከመካነ መቃብር ወደ አረንጓዴ ገነት አዲስ አበባ በአሁኑ ወቅት ታላቅ የከተማ መልክ ለውጥ ውስጥ ትገኛለች። ከኮሪደር ልማቱ ጎን ለጎን፣ እስካሁን ድረስ "የፍርሃት ቀጠና" ተደርገው ይታዩ የነበሩ የመካነ መቃብር ስፍራዎች ፣ አሁን ግን የከተማዋ አረንጓዴ ሳንባዎች እና የነዋሪው ማረፊያ ወደ መሆን እየተቀየሩ ነው። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የጀመረው ይህ የመልሶ ማልማት ስራ፣ የቀብር ስፍራዎችን ከሀዘንና ከጭንቀት ድባብ አውጥቶ፣ ለከተማዋ ተጨማሪ ውበት እና ለነዋሪዎች ደግሞ ሰላማዊ የእረፍት ቦታ እንዲሆኑ ለማድረግ ያለመ ነው። የከተማ ውበትና አረንጓዴ ልማት ቢሮ መረጃ እንደሚያመላከተው ፣ በከተማዋ የሚገኙ የዘላቂ ማረፊያዎች (መካነ መቃብሮች) የቀብር አገልግሎት ከመስጠት ባለፈ የከተማዋ የአረንጓዴ ማዕከላት እንዲሆኑ እየተደረገ ነው። በቢሮው የተቀናጀ የዘላቂ ማረፊያ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር የሆኑት አቶ አጃይብ ኩምሳ እንደገለጹት፣ ቀደም ሲል የቆሸሹና ለአራዊት መናኸሪያ የነበሩ ስፍራዎች አሁን ላይ ዘመናዊ የመሰረተ ልማት ግንባታ ተደርጎላቸው የከተማዋን ውበት የሚመጥኑ እየሆኑ ነው። ለዚህ ለውጥ እንደ ማሳያ የሚጠቀሰው የቅዱስ ጴጥሮስ ወ ጳውሎስ መካነ መቃብር ሲሆን ፣ ስፍራው በዘመናዊ መልኩ ተገንብቶ ለአገልግሎት ዝግጁ ሆኗል። በዚህ ማረፊያ የውስጥ ለውስጥ የድንጋይ ንጣፍ መንገዶች፣ ሌሊት የሚያበሩ የጌጥ መብራቶች፣ ንፁህ መጸዳጃ ቤቶች፣ የአገልግሎት መስጫ ቢሮዎች እና ለጎብኚዎች ምቹ የሆኑ መቀመጫ ወንበሮች ተሟልተውለታል። ይህ ዘመናዊ ማረፊያ በአሁኑ ወቅት ለካቶሊክ ፣ ለወንጌላውያን እና ለእስልምና እምነት ተከታዮች በጋራ አገልግሎት እየሰጠ የሚገኝ ሁለገብ ስፍራ ነው። በተመሳሳይ መልኩ የቀጨኔ ዘላቂ ማረፊያም በልማቱ ምክንያት እጅግ ተመራጭ እየሆነ መምጣቱን ዳይሬክተሩ ገልጸዋል። ስፍራው ካለው ልዩ ውበት የተነሳ ለቀብር ሥነ-ስርዓት ብቻ ሳይሆን፣ ለፊልም ቀረጻና ለተለያዩ የጉብኝት አገልግሎቶች ጭምር መዋል መጀመሩ የለውጡ ትልቅ ማሳያ ነው። ኢትዮጵያ የዘላቂ ማረፊያዎችን አያያዝ ከዓለም አቀፍ ተሞክሮዎች ጋር እያቀናጀች መሆኑን አቶ አጃይብ ጠቁመዋል። እንደ አሜሪካ፣ ጣሊያን እና ቱርክ ባሉ ሀገራት መካነ መቃብሮች የሠርግ ሥነ-ስርዓት ጭምር የሚካሄድባቸው እና ሰዎች መንፈሳቸውን የሚያረጋጉባቸው ስፍራዎች እንደሆኑ ይታወቃል። የአዲስ አበባው ተሞክሮም እነዚህን ዓለም አቀፍ ተሞክሮዎች መነሻ በማድረግ የቀብር ስፍራዎችን ወደ ታሪካዊና መዝናኛ ቦታነት የመቀየር ዓላማ አለው። በዓለም ዙሪያ ያሉ ታላላቅ ከተሞች መካነ መቃብሮቻቸውን ለቱሪስት መዳረሻነት ሲጠቀሙባቸው ቆይተዋል። ለምሳሌ በፈረንሳይ የሚገኘው ፔርላሼዝ (Père Lachaise) በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ቱሪስቶች የሚጎበኙት መናፈሻ ሲሆን፣ በእንግሊዝ የሚገኘው ሃይጌት (Highgate) ደግሞ ለከተማዋ ነዋሪዎች እንደ ትልቅ የአየር መተንፈሻ ያገለግላል። በጃፓን የሚገኘው ኣኦያማ (Aoyama) መካነ መቃብርም በ"ቼሪ ብሎሰም" ወቅት በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች የተፈጥሮ ውበትን ለመመልከት የሚሰባሰቡበት ማራኪ ስፍራ ነው። ይህ ዓይነቱ የመልሶ ማልማት ሥራ የቀብር ስፍራዎችን ደረጃ ከማሻሻል ባለፈ ለከተማዋ በርካታ ጥቅሞች ይሰጣል። ነዋሪዎች ዘመዶቻቸውን ለመዘከር በሚመጡበት ወቅት በሰላማዊና በፅዱ አካባቢ እንዲቆዩ ከማድረጉም በላይ፣ የከተማዋን የአየር ንብረት ሚዛን ለመጠበቅና ተጨማሪ አረንጓዴ ቦታዎችን ለመፍጠር ከፍተኛ እገዛ ያደርጋል። ይህም አዲስ አበባን እንደ ስሟ "አዲስ አበባ" ለማድረግ የሚደረገውን ትልቅ ጥረት በእጅጉ ያግዛል። በአሁኑ ወቅት በከተማ አስተዳደሩ ስር የሚተዳደሩ 11 ያህል የዘላቂ ማረፊያዎችን ወደዚህ ደረጃ ለማሸጋገር ሰፊ ሥራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ። ህብረተሰቡም በልማቱ ላይ ያለው የግንዛቤ ደረጃ እየጨመረ መምጣቱ ተመልክቷል። በአጠቃላይ የአዲስ አበባ መካነ መቃብሮች ከሀዘን ስፍራነት ወደ "ህያው መናፈሻነት" እያደረገች ያለው ሽግግር፣ ከተማዋ ለነዋሪዎቿ ያላትን ምቾትና ውበት ለማሻሻል የምታደርገው ጥረት አንዱ ትልቅ ማሳያ ነው።
229
10
Немає тексту...
1
11
Немає тексту...
232
12
“የዘንድሮ የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር የኮፕ 32 ጉባኤን በሚመጥን ደረጃ ዝግጅት እየተደረገ ነዉ “። ክቡር አቶ ግርማ ሰይፉ የከተማ ዉበትና አረንጓዴ ልማት ቢሮ ኃላፊ የዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ኢትዮጵያ እ.ኤ.አ በ2027 ለምታስተናግደው 32ኛው የተባበሩት መንግስታት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (COP32) የሚመጥን ታላቅ ዝግጅት እየተደረገበት መሆኑን የከተማ ውበትና አረንጓዴ ልማት ቢሮ ኃላፊ ክቡር አቶ ግርማ ሰይፉ ተናገሩ። በአሁኑ ወቅት በአዲስ አበባና በተለያዩ ከተሞች የተጀመሩት የኮሪደር ልማት ስራዎች እና የወንዝ ዳርቻ ፕሮጀክቶች ከዲፕሎማሲ፣ ከአየር ንብረት፣ ከምግብ ዋስትና፣ ከከተማ ውበት፣ ከስራ ፈጠራ እንዲሁም ከመዝናኛ አንጻር ዘርፈ-ብዙና ግዙፍ ጠቀሜታዎች እንዳላቸው ቢሮ ኃላፊው በዝርዝር አስረድተዋል ። ኢትዮጵያ በታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ ከሰሃራ በታች ባሉ የአፍሪካ ሀገራት ስም የተሰጣትን የCOP32 የአየር ንብረት ጉባኤ የማስተናገድ ታላቅ ዕድል ማግኘቷን ተከትሎ የዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ ዘመቻ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶታል። የዘንድሮው መርሃ ግብር ዝግጅት ይህንን ዓለም አቀፍ ጉባኤ በሚመጥን መልኩ በከፍተኛ የሕዝብ ንቅናቄና በዘመናዊ አደረጃጀት እየተከናወነ መሆኑን የገለፁት አቶ ግርማ ሰይፉ ሀገሪቱ በክረምቱ ወቅት የምታከናውነው የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ለዓለም እንግዶች ማሳያ የሚሆንና የኢትዮጵያን የአረንጓዴ ዲፕሎማሲ መሪነት ይበልጥ የሚያጎላ መሆኑን አስምረዉበታል። የተጀመሩት የኮሪደር ልማቶችና የወንዝ ዳርቻዎችን ማልማት በዋናነት የሀገሪቱን ገፅታ በመቀየር ረገድ ከፍተኛ የዲፕሎማሲ አቅም እንደሚፈጥሩ ታምኖበታል ፡፡ አዲስ አበባ የአፍሪካ መዲና እና የዓለም አቀፍ ዲፕሎማቶች መቀመጫ እንደመሆኗ መጠን፣ እነዚህ አረንጓዴ ስራዎች ከተማዋን ለኑሮና ለስራ ምቹ በማድረግ የሀገርን ገጽታ ይገነባሉ ተብሏል። ከአየር ንብረት አንጻር ደግሞ የካርቦን ልቀትን በመቀነስ፣ የከተማ ሙቀትን በመከላከል፣ የአፈር መሸርሸርን በማስቀረትና የብዝሃ ሕይወትን መልሶ በማደስ ረገድ የማይተካ ሚና የሚያበረክት ሲሆን ከተማችንን ስማርት ሲቲ በማድረግ ዉስጥ ድርሻዉ ከፍተኛ እንደሚሆን ሲገለፅ መቆየቱ ይታወሳል ።
253
13
በከተማዋ ባለፉት ሰባት ዓመታት በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የተተከሉ 90 ሚሊዮን ችግኞች የከተማዋን አለም አቀፍ ደረጃ ያሻሻሉ እና የነዋሪዎችን ችግር የፈቱ ናቸዉ - ለተጨማሪ መረጃ ፦ 👇👇👇
በከተማዋ ባለፉት ሰባት ዓመታት በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የተተከሉ 90 ሚሊዮን ችግኞች የከተማዋን አለም አቀፍ ደረጃ ያሻሻሉ እና የነዋሪዎችን ችግር የፈቱ ናቸዉ - ለተጨማሪ መረጃ ፦ 👇👇👇👇 https://www.facebook.com/aaurbanbeutification Telgram:- 👇👇👇👇 https://t.me/addisabebagreenarea Twitter:- 👇👇👇👇 https://twitter.com/urbanbeauty1 YouTube:- 👇👇👇👇 https://www.youtube.com/channel/UC3jdcm6b4ib7WIAfVAsmgcA Tiktok 👇👇👇👇 https://www.tiktok.com/@urbanbeautificatic Website 👇👇👇👇 https://www.aaubgdb.go
248
14
አዲስ አበባ በዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር 6 ሚሊዮን ችግኞችን ትተክላለች፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በዘንድሮዉ የ2018/19 የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር 6 ሚሊዮ+1
አዲስ አበባ በዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር 6 ሚሊዮን ችግኞችን ትተክላለች፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በዘንድሮዉ የ2018/19 የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር 6 ሚሊዮን ዘርፈ ብዙ ጥቅም የሚሰጡ ችግኞችን ለመትከል ሙሉ ዝግጅቷን አጠናቃለች፡፡ በዘንድሮው መርሃ ግብር በተለይም ለሀገር በቀል እፅዋት እና ለፍራፍሬ ችግኞች ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ የሚሰራ ሲሆን፥ በተለያዩ አካባቢዎች ሰፊ ተከላ ይከናወናል፡፡ ከተማ አስተዳደሩ በዘንድሮው ዓመት በአዳዲስ ስፍራዎች ላይ ችግኝ ከመትከል ባለፈ፥ ቀደም ሲል ተተክለዉ በተለያዩ ምክንያቶች በደረቁ ችግኞች ምትክ አዳዲስ ተከላዎችን በማካሄድ እንክብካቤ እንደሚያደርግ አስታውቋል፡፡ ከተማዋ ካላት የችግኝ ተከላ ልምድ አንፃር ባለፉት ሰባት ዓመታት ዉስጥ በመዲናዋ የተተከሉ ችግኞች ቁጥር 90 ሚሊዮን የደረሰ ሲሆን፥ እስካሁን የተተከሉት ችግኞች የፅድቀት መጠንም 86.82 በመቶ መድረሱ ተገልጿል፡፡
268
15
የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ-ግብር ንቅናቄውን ተቀላቅለው ለመጭው ትውልድ አረንጓዴ ዐሻራዎን ያኑሩ! - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ-ግብር ንቅናቄውን ተቀላቅለው ለመጭው ትውልድ አረንጓዴ ዐሻራዎን ያኑሩ! - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
301
16
በዚህ ዓመት 8 ቢሊዮን ችግኞችን ለመትከል ግብ አስቀምጠን፣ ከፍ ወደ አደረግነው 65 ቢሊዮን ችግኞች ግብ የመድረስ ትልማችንን ለማሳካት በጽናት እየገሰገስን እንገኛለን። ‎ ‎ንቅናቄውን ተቀላቅለው ለ
በዚህ ዓመት 8 ቢሊዮን ችግኞችን ለመትከል ግብ አስቀምጠን፣ ከፍ ወደ አደረግነው 65 ቢሊዮን ችግኞች ግብ የመድረስ ትልማችንን ለማሳካት በጽናት እየገሰገስን እንገኛለን። ‎ ‎ንቅናቄውን ተቀላቅለው ለመጭው ትውልድ አረንጓዴ ዐሻራዎን ያኑሩ! ጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ
309
17
+4
Немає тексту...
327
18
የዚህን ዓመት የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ-ግብር ዛሬ በይፋ አስጀምረናል። በዚህ ዓመት 8 ቢሊዮን ችግኞችን ለመትከል ግብ አስቀምጠን፣ ከፍ ወደ አደረግነው 65 ቢሊዮን ችግኞች ግብ የመድረስ ትልማችንን ለ+9
የዚህን ዓመት የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ-ግብር ዛሬ በይፋ አስጀምረናል። በዚህ ዓመት 8 ቢሊዮን ችግኞችን ለመትከል ግብ አስቀምጠን፣ ከፍ ወደ አደረግነው 65 ቢሊዮን ችግኞች ግብ የመድረስ ትልማችንን ለማሳካት በጽናት እየገሰገስን እንገኛለን። ‎ ‎ንቅናቄውን ተቀላቅለው ለመጭው ትውልድ አረንጓዴ ዐሻራዎን ያኑሩ! Today, we officially launched this year’s Green Legacy Initiative. With a target of planting 8 billion seedlings this year, we are steadily advancing toward our larger set goal of 65 billion trees. Join the movement and leave your green legacy for future generations! #GreenLegacy
297
19
የአዲስ አበባን ገፅታ የቀየረውና ለኑሮ ምቹ ያደረገው አረንጓዴ አሻራ ተፈጥሮ ንጹህ አየርን፣ ዝናብንና ለምለም መሬትን በመለገስ የሰውን ልጅ ህልው ስትደግፍ፣ ሰው ደግሞ እሷን በመንከባከብና በመጠበቅ ኃላፊነቱን ሊወጣ ይገባል። ይህንኑ የተፈጥሮ ሚዛን ለመጠበቅ በ2011 ዓ.ም የተጀመረው የአረንጓዴ አሻራ አገራዊ ንቅናቄ፤ በማኅበራዊ፣ በኢኮኖሚያዊና በአካባቢያዊ ገጽታ ላይ ዘርፈ-ብዙ ፋይዳዎችን እያስገኘ ይገኛል። ባለፉት ሰባት ዓመታት በመዲናዋ 90 ሚሊዮን ችግኞች የተተከሉ ሲሆን፣ ከተተከሉት ውስጥ 86 ነጥብ 82 በመቶ የሚሆኑት ፅድቀዋል። ከተተከሉት መካከልም ለምግብ የሚሆኑ የፍራፍሬ ዛፎች እንዲሁም ለባህላዊና ዘመናዊ ሕክምና የሚያገለግሉ ዕፅዋት እንደሚገኙበት ዳይሬክቶሬቱ አክሎ ገልጿል። ይህ ታላቅ ንቅናቄ የከተማዋን ሥነ-ምህዳር ከማደስ ባለፈ፣ የአካባቢ ብክለትን በመከላከልና የአየር ንብረት መዛባትን በመቋቋም ረገድ የጎላ ሚና እየተጫወተ ይገኛል። ከተማዋን ውብና ለኑሮ ተስማሚ ከማድረግ ባሻገር፣ ለነዋሪዎች ምቹ የሆኑ በርካታ አረንጓዴ የመዝናኛ ቦታዎችን ለመፍጠርም አስችሏል። በተጨማሪም ለአካባቢው ዜጎች ሰፊ የሥራ ዕድል የፈጠረ ሲሆን፥ ለሀገሪቱ የዲፕሎማሲ ገፅታ ግንባታም ትልቅ አዎንታዊ አስተዋጽኦ አበርክቷል። ይህንኑ ስኬት በላቀ ደረጃ ለማስቀጠል፣ በዘንድሮው የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር 5 ሚሊዮን ችግኞችን ለመትከል በከተማዋ ሰፊ የቅድመ-ዝግጅት ሥራዎች እየተከናወኑ ናቸው። የዘንድሮውን ዕቅድ ስኬታማ ለማድረግ በአሁኑ ወቅት የችግኝ ማፍላትና ማጓጓዝ፣ የጉድጓድ ቁፋሮ፣ ሰፊ የሕዝብ ንቅናቄ መፍጠርና ለዘርፉ ባለሙያዎች ሥልጠና የመስጠት ሥራዎች በተሟላ ሁኔታ መከናወናቸውን ዳይሬክቶሬቱ አስታውቋል። ይህ ታላቅ አገራዊ ንቅናቄ መዲናዋ ነዋሪዎቿን ባሳተፈ መልኩ አረንጓዴና ለኑሮ ተስማሚ የሆነች ከተማ ለመፍጠር እየተደረገ ያለውን ዘላቂ ጥረት ይበልጥ የሚያጠናክረው መሆኑ ተገልጿል።
245
20
Немає тексту...
237