en
Feedback
ግጥም ብቻ 📘

ግጥም ብቻ 📘

Open in Telegram

✔በየቀኑ ምርጥ ምርጥ የጥበብ ስራዎችን ለማግኘት የቻነላችን ተከታይ ስለሆኑ እናመሰግናለን። ✔ @getem @serenity13@wegoch @Words19@seiloch @shiyach_bicha@zefenbicha @leul_mekonnen1

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel ግጥም ብቻ 📘

Channel ግጥም ብቻ 📘 (@getem) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 64 058 subscribers, ranking 788 in the Religion & Spirituality category and 487 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 64 058 subscribers.

According to the latest data from 09 June, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by -460 over the last 30 days and by -5 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 14.53%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 3.92% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 9 312 views. Within the first day, a publication typically gains 2 510 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 52.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
✔በየቀኑ ምርጥ ምርጥ የጥበብ ስራዎችን ለማግኘት የቻነላችን ተከታይ ስለሆኑ እናመሰግናለን። ✔ @getem @serenity13 ✔ @wegoch @Words19 ✔ @seiloch @shiyach_bicha ✔ @zefenbicha @leul_mekonnen1

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 10 June, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Religion & Spirituality category.

64 058
Subscribers
-524 hours
-1267 days
-46030 days
Posts Archive
( ሞክሼ ... ) ======== ያ ሁሉ እግዚኦ ያ ሁሉ ቢስሚላ ያ ሁሉ ጾም ጸሎት ያ ሁሉ ምህላ ... የት ነው የሚሄደው ስሚኝ እስቲ ሀገሬ ሞክሼ አለሽ ወይ ሌላ ?? By Kiyorna @getem @getem @paappii

ችዬ እንዳይመስልህ! ደክርቼ ሳለሁ ዐለት የመሰልኩ፣ በሃያላን ፊት ደክሜ ያልሰለልኩ፣ ወና ብሆንም ከሌለኝ ያጣው፣ እንደ ምንዱባን ደጅ የማልጠናው ፣ ችዬ እንዳይመስልህ አስችሎኝ ነው። ...አስችሎን አይደል?!... by[ዓለም]  @alem3_b @getem @getem @getem

‎#ዕጣ_ፋንታ ‎ ‎አላውቃትም እና ‎የመኖርን ትርጉም ህይወትን አየኋት ‎ተጣልተን ተዋደን...ሳፈቅራት አጣኋት ‎ ‎ዮኒ ‎     ኣታን @yonatoz @getem @getem @getem

photo content

እንዳበባ~ቅጠል እንደ ክረምት~ጠል እንዳለቀ~ከሰል እንደ ጢሰ~ሰንደል      ክፍተት እያበጁ      በተስፋ እያጃጁ             የካብናቸው ሁሉ             ቀስ ቀስ እያሉ        በዝምታ በደል        ተነጠሉን አይደል?!:፧: By [ዓለም] @getem @getem @paappii

ባንተ እንዳይመስልህ…………… ዉስጤን በምናምን አጥብቄ አላሰርኩት ወ ይ ያልሸፋፈንኩት ታክሜ አልዳንኩት በእድሜ ቁጥር ልኬ የተጠራቀመ በርሜል እምባ አለ መገፋት መከፋት መዋረድ መረሳት መጠላት መወደድ የወረት ዉስጡ ተሰግስጐ ቀዳዳ ሲያገኝ እንደ ዥረት ሚወርድ ያልተተነፈሰ በጊዜ በወቅቱ ያልነገርኩህ እዉነቶች አሉና የበረቱ ትንሽ ስትነካዉ ዝም ብሎ ያፈሳል የነበረኝ ቁስል ደሞ ያመረቅዛል ጥቂት ስለከፋኝ ቢመስል ያካበድኩ እንዳትፈርድብኝ ብዙ ስለሆንኩ ትዝታ ወልዴ✍️ @getem @Tizita21

የነባ አዲስ አለበም ከደቂቃዎች በፊት ተለቋል!!! ENJOY ተhttps://youtube.com/playlist?list=PLCaAHnpIbdyNC0Skx2_ucVEke7T4vaTKm&si=oTCNi45bnXCJlWLs @getem

Osoo abdii hin qabaatin hawwii hin qabnu turre ‎Wagoota booda Har'a milkaa'e ‎Amma Waancaa qabane ‎Amma Diinni badeera ‎በሀያ ሁለት አመት ታሪክ ስለሰራ ‎ ‎Arsenal🔥🔥🔥 ‎ ‎ ‎ዮኒ ‎    ኣታን @yonatoz ‎ ‎@getem @getem @getem

.... አይበገሬው እኔ    አንቺን በማጣቴ      ለ'ሲቃ' ብደርስም፣ _____ ወንድ ልጅ ነኝና   ተለየሽኝ ብዬ     ለአንቺስ አላለቅስም! ✍️ @Weyblann @getem @getem

አጃኢብ ሰው መዉደድ አጃኢብ ትዝታ........ እንደምን ይቻላል..... ......ናፍቆትን መላመድ የተለዩ ለታ.......... ✍✍ [ ዔደን ታደሰ ] @Edi2_4 @getem @getem

Repost from Sunset Hiking
🌄 We’re Back And We’re Hiking Again Hey Sunset community 🌄 Life happened. The city got louder. And for a while, the sunsets
🌄 We’re Back And We’re Hiking Again Hey Sunset community 🌄 Life happened. The city got louder. And for a while, the sunsets were quieter without us. Sunset Hiking is officially back with a stronger team, clearer plan, and a growing 4,000+ hiking community ready to move again. Over the next weeks, we’ll be sharing: 🥾 Upcoming sunset hikes 🌅 Community moments 🧭 Safe, well-organized experiences If you’re still here, it means you love nature as much as we do. Let’s start again one sunset at a time. 🌄👣

(እናት ትዝታ ናት!) ።።።።።።።።።። ይጨልማል ያልኩት በድምፅሽ ይነጋል ሊወጋኝ የመጣው ባይኖችሽ ይወጋል። ሊገርፈኝ ያሴረ ልቡናሽ ሲገርፈው ይረግፋል ከጥፍሬ የሚያስረኝን ሁሉ አስሬ አስቀመጥኩት በስምሽ ጠፍሬ። ፉንጋውን ዩኒቨርስ ውብ ብለሽ ጠራሽው ዓለም አምሮ አያውቅም አንቺ ካልሠራሽው። ከፍ ብዬ ብታይ ከሊባኖስ ዝግባ ጎጆሽን አልፌ ከእልፍኝ ብገባ ቢቆለል እድሜዬ ቢመጥቅ ሀሳቤ እልፍ ቢያተርፍ እጄ ቆመሽ ብጠብቂኝ አልሆንም አባትሽ አትሆኚም ልጄ። ፣ አረሙን ነቃቅላ በሞገስ የታየች ነፍሴ በፍቅር ወዝታ ዜማዋ ሆነሽ ነው የትናንት የዛሬ የነገ ትዝታ! ፣ ህልው ነኝ ለማለት ልቤ ሲያንሰራራ አንቺ ቅኝት ላይ ነው ዜማዬ ሚሰራ! By Yadel Tizazu @getem @getem @paappii

ከልቤ ላይ አንተን ማዉጣት ማለት…… ገቢዎች ሰምተዉኝ ያላመንኩበትን ጉዳዬን  መቀልበስ ቀበሌ ገብቼ በደስታ መመለስ መርጌታ ከሚል ቻናሎች ላይ መዉጣት የተበደርኩትን ስመልስ በብቃት ከ crash ኤ ጋራ እራት እንደመዉጣት ለእናቴ በአደራ ሚስጢር እንደማዉራት አንተን መርሳት ለኔ…… አለቃዬን መዉደድ እብድ ሰዉ ማሳበድ ዛፍና ፓል መግጨት ተምሬ በድፍረት ያልፍልኛል ማለት እርሺኝ ብሎ ማሰብ……… ወፍ በእግሯ ስትሳብ ተኩላ በዉበት ሲሳብ ቴሌ በትክክል ሲያመጣልኝ ሂሳብ እኒህ ሁሉ ተቀይረዉ ምድር ቀዉጢ እስካልሆነች- አንተን መርሳት ዉዴ የሚቻል አደለም። ትዝታ ወልዴ✍️ @getem @Tizita21

የ ሥዓሊ እና መምህር ኃይሉ ክፍሌ "ተገማች፡ ዋዜማ" የሥዕል አውደርዕይ እዚህ ትርዒት ላይ ተገኝቼ፣ በከተማ ዝመና ውስጥ የማንነትንና የትዝታን ትርጉም የሚፈትሹ ስራዎችን ተመልክቻለሁ። የጥበብ ስራዎ
+9
የ ሥዓሊ እና መምህር ኃይሉ ክፍሌ "ተገማች፡ ዋዜማ" የሥዕል አውደርዕይ እዚህ ትርዒት ላይ ተገኝቼ፣ በከተማ ዝመና ውስጥ የማንነትንና የትዝታን ትርጉም የሚፈትሹ ስራዎችን ተመልክቻለሁ። የጥበብ ስራዎቹ የሚጠቀሟቸው ቁሶችና የሚያነሷቸው ሰብአዊ ጥያቄዎች ቆም ብሎ ለማሰብ ትልቅ እድል ይሰጣሉ። የለውጥ ሂደቱ ወዴት እየወሰደን ነው? የጋራ ትዝታችንን እያካተትን ነው ወይስ እየረሳን? እነዚህንና መሰል ጥያቄዎችን የሚመልስ ድንቅ ትርዒት ነው። እድሉ ያላችሁ እንዳያመልጣችሁ! 📍 እስከ ግንቦት 24 ድረስ ክፍት ነው @Seiloch #Hailukifle #artExhibition.

አብጄ ከሆነ ወስደሽ አስጠምቂኝ፥ አብደሽ ከሆነ ግን፣ በስተርጅና አያምርም ሀገሬ አታስቂኝ፥ By Dessu Fikriel @getem @getem @paappii

@ɢᴇᴛᴇᴍ ʙʏ ʏᴇᴀʙsɪʀᴀ Astawesegn regasa

‎ያልኩላትን ቃላት አንዱንም ሳታውቀው ‎          ትኖራለች በግፍ ‎ዘነጋችው እንጂ እንኳን እሷ ለኔ ‎       ጆሮም አለው ደግፍ ‎ተረሳስታኝ ኖራ ‎የነገርኳትን ሆድ እሷ እንደምታውቀው ‎ሰርክ እመኝኝ ማለት ልቤን አወለቀው ‎ ‎ዙሮ ላይመለስ እንጨት ሆኖ ከሰል ‎እኔ አንዴ ዝም ብል ተነጣጠልን መሰል። ‎ ‎ዮኒ ‎     ኣታን @yonatoz ‎ ‎@getem @getem @getem

ቁር ያቆረፈደዉ ሽብሽቡ ቆዳዬ፤ በእንባ ሞጭሙጮ የደከመው አይኔ፤ በዘመናት ንጉደት ፀጉሬ ቢሸብትም፤ መንጋጋዬ ረግፎ በድዴ ብቀርም፤ ጉልበቴ ተዳክሞ ወገቤ ቢጎብጥም፤ አንተን የሚያልመዉ ልቤ አላረጀም።
ቁር ያቆረፈደዉ ሽብሽቡ ቆዳዬ፤ በእንባ ሞጭሙጮ የደከመው አይኔ፤ በዘመናት ንጉደት ፀጉሬ ቢሸብትም፤ መንጋጋዬ ረግፎ በድዴ ብቀርም፤ ጉልበቴ ተዳክሞ ወገቤ ቢጎብጥም፤ አንተን የሚያልመዉ ልቤ አላረጀም። ድንገት ባጋጣሚ ልትመጣ ካሰብክ፤ ከበራፉ አለሁ ጥለኸኝ እንደሄድክ። [ ዔደን ታደሰ ] @topazionnn @getem @getem

በቁጣ ጅራፍ በዓይን ሽርደዳ ተስፋው እስኪላጥ ልቤ ቢጎዳ (አላመነታም) ሳቄን አልገታም ኮስታራ ገጽሽ ግልምጫን አዝሎ ሊያሸሸኝ ቢጥር መውደዴን ሰቅሎ (አላማርርም) ሳቄን አልቀብርም ሺ ማጣት ጎርፎ ቢያንደረድረኝ ወስዶ እንዴትም ሳቄን እንዲነጥቅ አልፈቅድለትም #ኤልዳን @eldan29 @getem @getem @getem