en
Feedback
ግጥም ብቻ 📘

ግጥም ብቻ 📘

Open in Telegram

✔በየቀኑ ምርጥ ምርጥ የጥበብ ስራዎችን ለማግኘት የቻነላችን ተከታይ ስለሆኑ እናመሰግናለን። ✔ @getem @serenity13@wegoch @Words19@seiloch @shiyach_bicha@zefenbicha @leul_mekonnen1

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel ግጥም ብቻ 📘

Channel ግጥም ብቻ 📘 (@getem) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 63 695 subscribers, ranking 786 in the Religion & Spirituality category and 498 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 63 695 subscribers.

According to the latest data from 21 July, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by -215 over the last 30 days and by 14 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 11.86%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 4.27% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 7 553 views. Within the first day, a publication typically gains 2 722 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 56.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
✔በየቀኑ ምርጥ ምርጥ የጥበብ ስራዎችን ለማግኘት የቻነላችን ተከታይ ስለሆኑ እናመሰግናለን። ✔ @getem @serenity13 ✔ @wegoch @Words19 ✔ @seiloch @shiyach_bicha ✔ @zefenbicha @leul_mekonnen1

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 22 July, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Religion & Spirituality category.

63 695
Subscribers
+1424 hours
-177 days
-21530 days
Posts Archive
ደህና...... እንዴት አደርክ?     (ደህና!) እንዴት ዋልክ?    (ደህና!) እንዴት አመሸክ?    ( ደህና!)፤ ደህና ሚለው ቃሌን     ከጅምሩ አውቀው በሁሌ ሰላምታ      ጠየቁኝ አጥብቀው፤ ህ! ሰላምታው ቢበዛ   አንድም ላይሰጥ ተስፋ (አሁን ግን ደህና ነህ?)     የሚል እንዴት ይጥፋ!??? @Weyblann @getem @getem

አገር ንቆ..ሰው አይጸድቅም! @myPoems396 @getem @getem @getem
አገር ንቆ..ሰው አይጸድቅም! @myPoems396 @getem @getem @getem

~  ~  ~  ~  ~  ~  ~  ~  ~  ~  ~  ~ ~  ~ ° ብሸፍተም ሰው ስገድል.. ስትጠራኝ ሳትሸነግል.. ቀስቴን ጥዬ ተሸነፍኩኝ አንተን ሳይህ 'ረገፍኩኝ፨ ድንገት ራደ ሰዉነቴ፣ ተፈታልኝ ሰንሰለቴ፨ ° ለካ እንዲ ነህ ሰው ስትለውጥ ለካ እንዲ ነህ ሰው ስትጠራ፣ ጨካኙን ልብ ደግ ያልሰራ፣ ታኖራለህ ስታራራ፨፨ ° ለካ እንዲ ነህ ስታንኳኳ፣ ጻዲቅ ሆነ ገዳዩ እንኳ፨! By @alem3_b[ዓለም] @getem @getem @getem

እንዳትረሺኝ  ብዬሽ፤ አትርሳኝ ብለሽኝ ፤ በቃል ክር አስሬሽ፤ በቃል ክር አስረሽኝ፤ በደልሽኝ በደልኩሽ፤ በደልኩሽ በደልሽኝ ፤ ቃልሽን አከበርሽ ቃሌን አከበርኩኝ ፤ ይሄ በደላችን... እንኳን  በ'ዚህ ሕይወት በመቃብርም ውስጥ ችሎ አያረሳሳም፤ ደግሞ እንደምታውቂው የወዳጅ ፍቅሩ እንጅ በደሉ አይረሳም ። By Tewodros kassa @topazionnn @topazionnn

እውነትም ሰገነት! ውሸት አልነበረም ያ ሁሉ ሙገሳ፥ ሰማይ ታህል ነበር ጨረቃ አንችን ለብሳ። አድማስና ማማ ማጋነን ቢመስል፥ ወንዝ እንኳ ሚረጋው ሲቃኝ ባንቺ ምስል፤ እውነት? ያባይ ጅረት ሳቅሽን ይበልጣል? የጢሱ ርግብታ? ከርጋታሽ ይሰክናል? እስቲ ጽጌሬዳ?ይመ--ስልሻል ወይ፣ ይቅርና በበጋ እርሙንስ በጸደይ?! ንግግርሽ ሃገር አርምሞሽ አሃጉር አንቺ ላይ ከረመ ውበት ሲያንጎራጉር!። ሃሳብሽ ገራገር መርኅሽ ዝምታ፣፨                     .                     .                     . እውነትም ሰገነትእውነትም ከፍታ!።🙌🏿 By @alem3_b [ዓለም] @getem @getem @getem

ድሮ አንቺን ለማየት ሰፈርሽ ስመጣ አንዲት ዝርግ ድንጋይ አየሁ ተቀምጣ ፤ ቁጭ አልኩኝ በድንገት እንዲህ እንደ ዘበት… ያፈቀረሸ ልቤ ፣ ሳሉ ሲነሳበት ማስታገሻ ነበር ፣ ሰፈርሽ መገኘት። ዛሬስ አትይኝም? እዛው ተቀምጬ አትመጣም ወይ? እያልሁ አንቺ ብትቀሪ… : ዲግሪ ጭኖ መጣ ሀይስኩል ተማሪ። እዛው ትናንትና እዛው አንቺ ሰፈር ከጠፍጣፉ ድንጋይ ሳልነሳ ቀንቶኝ… : ያምና ብላቴና ያልፈኛል ገላምጦኝ። አትገረሚም ወይ? ሳልነሳ ከዛ ቤተ መቅደስ ታዛ ከስር የማይጠፋ የወንጌል ሰባኪ ቅስናውን ገድፎ በየመሸታ ቤት ሲያወርድ ያድራል ውስኪ። እዛው ትናንትና አንቺን ከማይበት ከጠፍጣፉ ድንጋይ ተቀምጬ እያለሁ አንዱ አብሮ አደጌ በመኺና ባየው- እጆቼን ዘረጋሁ ለናፍቆት ሰላምታ መስታወቱን ሳበ በእንዴት ነህ? ፈንታ ያን ጊዜ ተከፋሁ ውስጤን ቦረቦረኝ- ምናል እንደ ድሮው አቅፎ ሰላም ቢለኝ? (ጎስቁያለሁ በቃ?🤔) አትገረሚም ወይ? ሰዎች አሉኝ ከንቱ መንገድ ቀየሩብኝ ቀፍፎ ፣ ጎርብጧቸው ዘባተሎ ጨርቄ… ያካሌ ቡትቱ። (ጎስቁያለሁ ለካ !) እዛው ቁጭ ብዬ ተዓምር ደረሰ ሰፈሩ ተዳሰ ቅጥሩ ፈራረሰ የግቢያችሁ በሩ ይከብድ የነበረው በአባትሽ ትከሻ… : የማንም ወመኔ አጨሰበት ሺሻ። እዛችው ከትናንት ከግቢያችሁ ማዶ እስክሰማ ድረስ ቀጭን ክፉ መርዶ : እየጫኑ ዲግሪ፣ እየናቀኝ ውሪ፣ ሰክሮ እየሳተ… የ’ግዜአብሔር አዳሪ እብድ ነው እያሉኝ እነ ቲቲ ፣ ሜሪ እየተቃመበት የአባትሽ ገዳም እየተጨሰበት የእናትሽ በዓት ትዝታችን ሲናድ በከተማ ልማት ፤ አንዱም ድል ሳይመታኝ ስንቱን ዘመን ሽሬ እልፍ ዘመን ኖሬ ሁሉን እየረታሁ … ሁሉን እየነሳሁ… “አግብታለች” ቢሉኝ በድንገት ተነሳሁ። (ታስታውሽኝ ይሆን?) አታውቂኝም ለካ🥹 ሚካኤል .አ @getem @getem @paappii

ለፀሐይ ፍካት ማን ይፈግጋል? ለሰማይ ንጣት ማን ይደግሳል? ማን ግድ ብሎት ማን ስሜት ሰጥቶት? ከምድር አልፎ ሰማዩን አይቶት?¡ ዘልቋል ከውስጥኽ?ገብቶሃል ቅኔው? ምን ብትነጠፍ ሰማይ ብትሆነው የያዘው እክል እስካልለቀቀው፧ ከኑሮ አሻግሮ ግትር አንገቱን እስካላዞረው፧ መቼም አያይህ ያልቀናለት ሰው! By @alem3_b[ዓለም] @getem @getem @getem

ይቅር በላቸው[ፀሎት] የሞገቱኝን ሽራፊ ቀኖች ያስጀነኑኝን ጎዶሎ ሀብቶች... _  _  _ ሸንበቆ ድግፍ እፍኝ ትምክህቶች መውደቂያ ያጡ ድፍን ተምኔቶች! ይቅር በላቸው... የተጣደፉ ፈራጅ ከንፈሮች ያልተማከሩ ልብና አፎች! ያልደነገጡ ድንድን ስሜቶች ያልተረጋጉ ሰንካላ እምነቶች! ይቅር በላቸው! ይበልጥም...
የሞገቱኝን ሽራፊ ቀኖች! ያስጀነኑኝን ጎዶሎ ሃብቶች!
_  _  _ ያስመከቱኝን ውዥቅ ቀለማት ያስፎከሩኝን ግንጥል ድምቀታት! ይቅር በላቸው! አልደበቁኝም ልሽሽው ካልኩት አላስጣሉኝም ከተሯሯጥኩት አላወጡኝም ከሰው ትከሻ ወይ አልሰጡኝም ዝና ሙገሳ፨ ይቅር በላቸው! ማራቸው ያለህ ልቤ አስታኮ፧ አብረህ አስበኝ ሊልህ ነው እኮ፧፧ By @alem3_b [ዓለም] @getem @getem @getem

እንዳትመለሺ ፣ መምጪያ መንገድሽ ላይ እሾህ ብዘራበት ... ልቤ ሳቅ ታየበት ... የጨለመው ዓይኔ – ብርሃን ዘነበበት ኃጢያትም አንዳንዴ – የእግዜር እጅ አለበት By Thomas Atsede @getem @getem @paappii

የቁም ፍቅር ስደክም ብውል አዳር ብለፋም፤ አስታውሳለሁ ከውስጤ አይጠፋም፤ የዛ ቀን ግለት የዛች ቀኑ ፍም፤ ያገኘሁሽ ቀን በዛች ካፌ ፍክት ብለሽ፣ ያየሁሽ ለታ እዚያ ጥግ ላይ ስልክሽን ይዘሽ፤ 'ሰው አለው' ብዬ ወንበሩን ልስብ፣ ገና ሳልለው እንዲሁ ባሳብ፤ ሳወጣ ሳወርድ ቃላት ስመርጥ፣ አይንሽን ስቃኝ ከንፈሬን ስመጥ፤ እንዲሁ ቆሜ እንዲሁ እንዳለሁ፤ ለካ ሳላውቀው እረዥም ሰአት ተገትሬያለሁ፤ አሁን ስመለስ ራሴን ሳገኘው፤ ዙሪያ ገባውን ባይኔ ብቃኘው፤ አልለማ አልሰማ አልጠፋ አልበራ፤ እንዲሁ ብቻ ግትር ብዬ እንደጅብራ፤ 'እብድ ነው?' በሚል አስተያየትሽ ብትገረምሚኝ፤ አቅፌው ሄድኩኝ ያንድ ደቂቃ ፍቅሬን ሳትሰሚኝ፤ By @Lawyerly1 @getem @getem @getem

የሰካራሙ ፍልስፍና ✍️ እዚያ ሰማይ ከማደሪያው ከመቅደሱ፣ ሱራፌል ተጋርዶ ፊቶቹን ይሰጋል እዚህ ምድር አንድ ሰካራም ሰው፣ ለእግዚያር ምክር ይዞ በድፍረት ያወጋል እንደዚህ ይለዋል በሰካራም ድምጡ በደልና መፅድቅ  እንዲለዋወጡ... እንዲህ ተናገረ... " ሰማያት ያለኸው፣ እግዚያር ሆይ ጌታዬ   ሃሳብ  ቢጤ ላንተ፣ በፊትህ ከታዬ   ምን መሰለህ እግዚያር...     በዚህኛው አለም በምንኖርባት፣                      ሰዎች በተቃርኖ መርህ ይኖራሉ   ተው!...ስትል ጥሰው፣                  አድርግ ያልካቸውን መቼ ያደርጋሉ? እኔንም ተመልከት... አትስከር ያልከውን፣ ትዛዝህን ልጥስ ዘውትር እየጠጣው፣ ዘውትር ለምን ላልቅስ? ስለዚህ እግዝያር ለዚህ ተቃርኖ ዛር አንድ መፍትሔ አለኝ... አታድርግን ጓግተን ከምንላወሰው ህግጋት ቀልብሰህ ብትቃረን ከሰው እጥር ምጥን ያለች፣ ፈጥረህ ሰማይ ድግስ አድርግን አታድርግ፣ እንዲያ ብታደርግስ?... (ቤተ መቅደስ እንዳትመጡ የወይን ጠጅ ሂዱ ጠጡ ቅድስናን እንዳትኖሩ በደል ብቻ ሂዱ ዝሩ)... በዛች ትንሽ ድግስ አድርግን አታድርግ፣ እንዲያ ብታደርግስ? እኔንም ተመልከት... እዚህኛው ዓለም ላይ፣ ሰው ተቃርኖን ተግቶ ይከውናል እንዳትመጡ ስላልክ ፍቃድህን ልጥስ፣ ምናልባት መቅደስህ እመጣ ይሆናል።" " እዚያ ሰማይ ከማደሪያው ከመቅደሱ፣ ሱራፌል ተጋርዶ ፊቶቹን ይሰጋል እዚህ ምድር አንድ ሰካራም ሰው፣ ለእግዚያር ምክር ይዞ በድፍረት ያወጋል። ፈጥረህ ትንሽ ድግስ አድርግን አታደርግ፣ እንዲያ ብታደርግስ ¶ በደል አቅፎ እየኖረ፣ እንዲያ ያመካኛል ሐጥያት መፅደቅ ቢሆን፣ እያለ ይመኛል። ፈጥረህ ሰማይ ድግስ እንዲያ ብታደርግስ። By ሰምረ የሽዋስ @getem @getem @getem

"ቃል ያለ ቃል" ስንን ያለ ኮሳሳ ባለ ማወቅ የከሳ ስልል ያለ ስናና ተካድኖት ኦና ይቆማል አይቆምም ይገጥማል አይገጥምም ይጠራል አይጠራም ይጮኻል አይሰማም እንዲህ ነው... ቃል ያለ ቃል ነፍስ ያደርቃል። በአጀባ ያንቃል በሁካታ ይደቃል ለሞት ያነቃል ኮታ ይነጥቃል። ቃል ያለ ቃል ነፍስ ያደርቃል። By Natnael Abebe @getem @getem @paappii

ሀገር እንደ ጭድ ኮስኩሳኝ ሳስታውሳት ስትረሳኝ ኢትዬጵያ ወባ ሆናብኝ ራሴ...ለአንገት ከብዳብኝ ሀገር ጀርባዋን ስታሳየኝ ስተን እንደ ሽታ ወገን ሚባል ጠፋኝ ረግፎ በበሽታ ሀገርማ ጫንቃዋማ ቆስሏል እንደ ንፍሮ ሀገርማ ፊቷማ ተቀባብቷል በፊልትሮ ህዝብ ሚሉት እየሰመጠ ጉድጓድ ደርሷል የግል ኑሮ ሀገር እንደ ጭድ ኮስኩሳኝ ሳስታውሳት ስትረሳኝ እያደርኩ እየሞትኩኝ ጥንብ አንሳ ላያነሳኝ ሰው መሆንጥሎኝ  አውሬ ነው የሚያነሳኝ ብቻ ጭዱ ያለቦታዋ እኔን ማቀፍ ለምን ሻተች ሀገር ታጥባ ወታ በእኔ እቅፍ እየሸተተች ለመሽተቴ አትፍረዱ እንባዬ ነው የሚያወዛኝ ሳቅ ባክህ አይባልም ሀገር ሞቶበት ላለ ሀዛኝ ሀገር ወባ ሆና ስታንቀጠቅጠኝ በትኩሳት መቼም ህመሜ ናት አንዳንዴ አይነግሩትም ህመምን ጠልተው አይጠሉትም እያንቀጠቀጠችኝ እያብረከረከችኝድ በጭድ ቤቷ እየኮሰኮሰችኝ ወባ ሆና እያመመችኝ ትታ የማተወኝ ትቼ የማልተዋት ሀገር አለችኝ By @geez_mulat @getem @getem @getem

"ይድነቅሽ ድንቄ" ይለቀማል ጥጥ ፣ ይለቀማል ወርቁ ግዮን መፍሰሻሽስ ፣ እግዚያር ነው ስንቁ ላለማለቁ! እንደወንዝሽ ያለ ፣ ሌላ ወንዝ አውቄ ጅረቱ ከእሳት ፣ መፍሰሱ ለጽድቄ ገረመኝ ደነቀኝ ፣ ይድነቅሽ ድንቄ ጠጥቼው መጣሁ ፣ ልነግርሽ ፈልጌ ከምንጩ ስጠጣ ፣ታወቀኝ መፍለቄ እስከመጨረሻ ፣ ላይጠማኝ መጽደቄ By Natnael Abeba @getem @getem @getem

በለጋ አዕምሯችን፣ ‎የገባንን ፅፈን፤ ‎ልክ ነው በማለት፣ ‎ልክነትን አልፈን፤ ‎ወራዜነት ቀጥፈን፤ ‎እኛነትን ጥለን፣ ‎እኔነትን ታቅፈን፤ ‎ ‎በተናጠል ኖረን፤ ‎አይገርምም? ‎ዛሬም ትክክል ነን፤ ‎ ‎ወዶ አይተርቱ ‎"ሆድ ከሀገር ይሰፋል" ‎ለሆዱ ያደረም፣ ‎ትውልድን ያጠፋል፤ ‎ ‎ማንነት ለማወቅ፣ ‎"ጠይቁ" የሚሉን፤ ‎በኛ ሊከብሩ ነው፣ ‎የሚነጣጥሉን፤ ‎ ‎እነሱ ‎ሁሉም በፊናቸው፣ ‎የሚሰብኩን እውነት፤ ‎ ‎(ያው እውነት ከተባለ!) ‎ ‎የኔ ጥያቄ ግን፣ ‎ምንድነው ማንነት? ‎ ‎እህት፣ ወንድምህ ላይ፣ ‎መቀሰር ጣትህን? ‎ ‎(እንደዛ ከሆነ) ‎ ‎የዛሬ ስላቅህ ‎ነገ ተመልሶ፣ ‎ይነካል ቤትህን፤ ‎ ‎ሕመሜ ካስደሳ፣ ‎ከበሮ ካስነሳ፣ ‎ጎሽ፣ እሰይ፣ ለማለት፤ ‎ ‎ከደጅህ ካራቀኝ፣ ‎ክንድህ ካልጠበቀኝ፣ ‎የቱ ጋር ነው እውነት? ‎ ‎ምንድነው ነው ልክነት? ‎ ‎የልጅነታችን፤ ‎በሙሉ ልባችን፤ ‎ ‎አድጎብን ማመኑ፣ ‎ትተን መመርመሩን፤ ‎ዛሬም ትክክል ነው፣ ‎ሌሎች የሚነግሩን። ‎ 🖋ON @getem @getem @getem

አለመምረጥን መምረጥ ፣ …ቢቻል ----------------------------------------- ከጠዋት ጣይና ፥ ከጨረቃ ብርሃን? በፊያሜታና ፥ ከሸገሯ ሮማን? እንዲህ ያለው ምርጫ ፥ ጽድቅ ነው እርግማን? በረሃብ አይደለም ፥ በሲኦል አይደለም ፈጣሪ 'ሚቀጣህ ፥ ምርጫ እየሰጠ ነው ፥ ደስታ የሚያሳጣህ። By Habtamu Hadera @getem @getem @paappii

( ስንትና ስንት ዓመት ) ================ ከከፍታዬ ላይ ከፍቅሬ ሳልወርድ ሌላ እቅፍ ሳያምረኝ ሌላ አካል ሳል''ለምድ ... ጨዋታሽን ሳልጠግብ ሳቅሽ ሳይሰለቸኝ ከአንቺ በቀር ያለው ዓለም ሳይመቸኝ .... ፍቅርን ከጀመርነው እንዲያ እንደ ዘበት ይኸው ተቆጠረ ስንትና ስንት ዓመት ! አንቺ ውብ ጸሐዬ ... " ወረት ይዞህ እንጂ በጠዋቷ ሙቀት ከርማ ስታቃጥል አትደርስም ከቤቷ .. " : ሲሉ ያደከሙኝን ምላሶች ታግሼ በልቤ ዙፋን ላይ አንቺን ብቻ አንግሼ .... እጆችሽን ሳልለቅ ከሰመረ ህይወት ይኸው እንደዋዛ ስንትና ስንት ዓመት ! @Kiyorna @getem @getem @getem

ሴት እና ኑሮ በሌት አትምጪ እንደ ዘራፊ፤ እስኪነጋልን ልረፍ እረፊ፤ ቀኑን እንዳሻሽ ከቻልሽ ምጪ፤ ከኑሮ በላይ ለጆሮ ልቀሽ ብትደመጪ! By @Lawyerly1 @getem @getem @paappii

ጥሞና ግሮሰሪ ተከሳሽ እገሌ፣  በቀደመው ወር ጥር አራት ሳት' ገደማ፣ ላምስት' ሲቆጥር ከላዩ ደርቦ የቻይና፣ ሌዘር ኮት ተሸፋፍኖ ከሰው፣ ጥሶ ከመለኮት እየተገላበጠ ተራምዶ በእንክብል ጥቁር ተከናንቦ አርጎ የፊት ጭምብል (የማይታይ መስሎት!) ግራጫ ቀለም፣ አርጎ የክት ሱሪ ደርድሮ ሲጠጣ፣ ገነት ግሮሰሪ ባይን አማኝ ምስክር በባዶ ክርክር ከዛሬ ጀምሮ፣ ከመቅደስ ተባሯል ለጥሞና ጊዜ፣ ለስድስት ወር ታስሯል። * (ተከሳሽ መልስ አለህ?) : እርግጥ ነው አልክድም ክሳቹን፣ ቅዳሜ አመሻሽ ለውስኪ ስገባ የኔ ጥያቄ ግን፣ ታማኙ ምዕመን ፣ ያይን ምስክሩ ምን ሊሰራ ገባ? : : (ከስድስት ወር በኋላ) : : የመሰከረበት ያ ታማኝ አገልጋይ ጥሞና ተብሎ ከታሰረው ታጋይ የነደደ እሳት፣ በስካር ቆስቁሰው ከሸንጎ ቆመዋል፣ ክፉኛ ተቧቅሰው * ሸንጎ ተጀምሮ ክሱ ሲዘረዘር * ለካ! ለጥሞና ጊዜ፣ የታሰረው ወጣት ገነት ግሮሰሪን፣ ለልማት ስላጣት ሆዱና አድማሱን፣ እስከ ጥግ አስፍቷል በጥሞና ጊዜው፣ ግሮሰሪ ከፍቷል። (ጥሞና ግሮሰሪ) አይን አማኙም ከዚሁ፣  ሰባት ጠጥቶ ሳይከፍል በጉራ፣ ጥሶ ሄዷል ወጥቶ። ይልቅ በቢሉ ውስጥ እንዲህ ፅፎለታል ክርስቶስ እዳዬን፣ ጠቅልሎ ከፍሎታል። ¶ ¶ በጥሞና ጊዜ ከምዕመን ለማሸሽ፣ ልክ አግባብ ቢኖርምኀ በግ ከበግ ጋር እንጂ፣ ተኩላ ጋር አይኖርም። ለስድስት ወር ባለም'፣ የከረመች ነፍስ ወደ ውጭ እንጂ፣ ወደቤቱ አትነፍስ። By @Bati232333 @getem @getem @getem

እድሜ ለጊዜ! ዘመን ደግ ነው... ጊዜ ደግ ነው አይደለም ክፉ ይኸው ተረስቷል አለንጋ ግፉ! መራቅ ደግ ነው አመት መንጎዱ እኛናእኛችን እንዲዋደዱ [እኛናእኛችን እንዲላመዱ] በጊዜ ፍጥነት... በቀኑ ክንፈት... ያ ሁሉ 'እዬ'ታ፣ ሆነ ትዝታ! [እድሜ ለጊዜ] ሲያልፍ ሲተካ ልብም ቀዝቅዟል፣ እንጂማ ባይሆን.... ያ ሁሉ እሮሮ በምን ይረሳል?! [ያ ሁሉ እምባ በምን ይደርቃል] @alem3_b[ዓለም] @getem @getem @getem