Dr. Eyob Mamo
📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام Dr. Eyob Mamo
تُعد قناة Dr. Eyob Mamo (@dreyob) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 79 194 مشتركاً، محتلاً المرتبة 1 969 في فئة التعليم والمرتبة 377 في منطقة Ethiopia.
📊 مؤشرات الجمهور والحراك
منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 79 194 مشتركاً.
بحسب آخر البيانات بتاريخ 14 يونيو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار -94، وفي آخر 24 ساعة بمقدار -3، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.
- حالة التحقق: غير موثّقة
- معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 11.21%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 6.00% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
- وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 8 877 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 4 753 مشاهدة.
- التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 73.
📝 الوصف وسياسة المحتوى
يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
“Life skill development!
You can contact me
@DrEyobmamo”
بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 15 يونيو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة التعليم.
جاري تحميل البيانات...
| التاريخ | نمو المشتركين | الإشارات | القنوات | |
| 15 يونيو | +2 | |||
| 14 يونيو | +8 | |||
| 13 يونيو | +2 | |||
| 12 يونيو | +20 | |||
| 11 يونيو | +149 | |||
| 10 يونيو | +16 | |||
| 09 يونيو | +44 | |||
| 08 يونيو | +12 | |||
| 07 يونيو | +15 | |||
| 06 يونيو | +7 | |||
| 05 يونيو | +16 | |||
| 04 يونيو | +4 | |||
| 03 يونيو | +5 | |||
| 02 يونيو | +14 | |||
| 01 يونيو | +13 |
| 2 | “የሕይወታችን ጥራት የሚወሰነው በውሳኔዎቻችን ጥራት ነው” ይባላል! | 1 791 |
| 3 | “ቀዩ መስመር” የተሰኘውን የሰኔ ወር የንባብ መጽሐፍ አሁንም መቀላቀል ይቻላል ወይ? ብላችሁ ዛሬም የምትጠይቁ አላችሁ፡፡
የመጀመሪው ሳምንት ንባብ፣ ማለትም የ7 ቀን ንባብ ተነቧል፡፡
አሁንም ሰዎች እተቀላቀሉና ያመለጣቸውን በማንበብ ከሚቀጥለው ቀን ጀምሮ እየቀጠሉ ነው፡፡
ዛሬ ከተቀላቀላችሁ፣ ያለፋችሁን መለስ ብላችሁ በማንበብ ነገ ከሌሎቹ ጋር የ8ኛ ቀን ንባብን ተቀጥላላችሁ፡፡
ንባብ የተመረጠው መጽሐፍ - “ቀዩ መስመር”
ንባቡ የጀመረበት ቀን - ሰኔ 1 / 2018
ንባቡ የሚጠናቀቅበት ቀን - ሰኔ 30 / 2018
ይህንን Book Club ለመቀላቀል፡- በዚህ 👉 @DrEyobmamo የቴሌግራም አድራሻ (user name) inbox በማድረግ ፍላጎታችሁን ስትገልጹ ሙሉ መረጃ ይላክላችኋል፡፡
Join now!!! | 3 559 |
| 4 | ጊዜ ነጻ ነው፣ ግን ውድ ነው!
“ጊዜ በነፃ የሚገኝ ቢሆንም፣ ዋጋው ግን በገንዘብ አይተመንም”
ጊዜ “በነፃ የሚገኝ” ነው የሚባለው፣ የማኅበራዊ ደረጃ፣ ሀብት ወይም መልክና ቁመና ሳይለይ ለሁሉም ሰው እኩል የሚሰጥ በመሆኑ ነው።
እያንዳንዱ ሰው በየቀኑ እኩል 24 ሰዓታትን ያገኛል። ጊዜን ማከማቸት ወይም መውረስ አይቻልም። ሆኖም ግን “ዋጋው በገንዘብ የማይተመን” ነው፤ ምክንያቱም አንዴ ካለፈ በኋላ መልሶ ማግኘት፣ መተካት ወይም ለጥቂት ጊዜ ማቆም አይቻልም።
እንደ ገንዘብ ወይም ንብረት ሳይሆን፣ ጊዜ ያለፈውን ነገር እንደገና ለመመለስ ሁለተኛ ዕድል አይሰጥም።
ይህም ጊዜን በሕይወት ውስጥ ካሉ እጅግ ውድ ሀብቶች አንዱ ያደርገዋል። እያንዳንዱ ቅጽበት የራሱ የሆነ አቅም (ዕድል) አለው—ይህም ለማደግ፣ ለወዳጅነት፣ ለመማር እና ለግል ብስለት የሚሆን ዕድል ነው።
ጊዜ በከንቱ ሲባክን፣ ከእሱ ጋር የተያያዘው ዕድልም ለዘላለም አብሮ ይጠፋል።
በመወላወል፣ በጭንቀት፣ በሰዎች በመገደድና እንዲሁ ቁጭ ብሎ በማሳለፍ ጊዜያችሁ አይባክን፡፡
ዛሬ ነቃ በሉና ለነገ እቅድ አውጡ! ነገ ደግሞ ተነሱና ያቀዳችሁትን ተግብሩ!
መልካም የእረፍት ቀን የምወዳችሁ የሃገሬ ሰዎች! | 4 844 |
| 5 | የሰኔ ወርን የንባብ challenge አዳዲስ አንባቢያን አሁንም እየተቀላቀሉ እንደሆነ ታውቃላችሁ?
ለመቀላቀል አልረፈደም!!!
ለንባብ የተመረጠው መጽሐፍ - “ቀዩ መስመር”
ንባቡ የጀመረበት ቀን - ሰኔ 1 / 2018
ንባቡ የሚጠናቀቅበት ቀን - ሰኔ 30 / 2018
ይህንን Book Club ለመቀላቀል፡- በዚህ 👉 @DrEyobmamo የቴሌግራም አድራሻ (user name) inbox በማድረግ ፍላጎታችሁን ስትገልጹ ሙሉ መረጃ ይላክላችኋል፡፡
Join now!!! | 5 962 |
| 6 | ጥያቄ፡
የሰኔን ወር የንባብ challenge ሳንቀላቀል ያለፈን ሰዎች ምን ማድረግ እንችላለን?
መልስ፡
የሰኔን ወር የንባብ challenge ወደ 500 የሚጠጉ ሰዎች ተቀላቅለው በማንበብ ላይ ናቸው፡፡
ዛሬ አምሰተኛው ቀን ተለቆ በመነበብ ላይ ነው፡፡
ዛሬውኑ በመቀላቀል ያለፋችሁን በአንዴ በማንበብ ከሌሎች አንባቢያን ጋር ከነገ ጀምሮ አስተካክላችሁ መቀጠል ትችላላችሁ፡፡
ንባብ የተመረጠው መጽሐፍ - “ቀዩ መስመር”
ንባቡ የጀመረበት ቀን - ሰኔ 1 / 2018
ንባቡ የሚጠናቀቅበት ቀን - ሰኔ 30 / 2018
ይህንን Book Club ለመቀላቀል፡- በዚህ 👉 @DrEyobmamo የቴሌግራም አድራሻ (user name) inbox በማድረግ ፍላጎታችሁን ስትገልጹ ሙሉ መረጃ ይላክላችኋል፡፡
Join now!!! | 6 937 |
| 7 | እውቀትን ወደ ተግባር! (ክፍል አምስት)
“እውቀትን ወደ ተግባር እንዴት መቀየር ይቻላል?” የሚለውን ትናንትና እና ከትናንትና ወዲያ ያቀረብኩትን መመሪያ የመጨረሻ ሃሳብ ይዤላችሁ ቀርቤአለሁ፡፡
8. የምንተገብረውን ነገር መገምገም
መገምገም ያለበት ያለን መነቃቃትና ምኞት ሳይሆን በተደጋጋሚ የተገበርናቸው ነገሮችና ያመጡት ውጤት ነው፡፡
ለምሳሌ፣ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ውጤታችን፣ ለመጻፍ አቅደን የተጻፉ ገጾች፣ ለመሸጥ አስበን የተከናወኑ የሽያጭ መጠኖች፣ ጀምረን የጨረስናቸው ነገሮች እና የመሳሰሉት፡፡
መዝነን የማንለካው ነገር ስኬታማነቱን ማወቅና መምራት ያስቸግራል፡፡
9. የተማርውን ማስተማር
እውቀታችንን በፍጥነት ወደ ተግባር ለመቀየር ከሁሉ ፈጣኑ መንገድ ሌሎችን ማስተማር ነው። ስናስተምር፣ ግንዛቤያችንን እናጣራለን፣ በእውቀታችን ውስጥ ያሉትን ክፍተቶች እንለያለን፣ ያስተማርነውን የመኖር የኃላፊነት ስሜት ይሰማናል።
ሌሎች ማስተንማር ብዙ ጊዜ መረጃን ወደ ጽኑ ፍጎትና ወደ ተግባራዊነት ይቀይረዋል።
ማሳሰቢያ፡-
ኃሙስ ሰኔ 4/2018 ከምሽቱ 3፡00 እስከ 4፡00 ድረስ በዚሁ የቴሌግራም ቻናሌ Live! የሚሰጠው ስልጠና አያምልጣችሁ፡፡
የስልጠናው ርእስ፡- “ከልጅነት (ካለፈ) 'ትራውማ' / 'trauma' መላቀቅ!”
ወዳጆቻችሁ ይህንን channel join በማድረግ ስልጠናው እንዲካፈሉ ጋብዟቸው፡፡
https://t.me/Dreyob
https://m.youtube.com/user/naeleyob623
https://www.facebook.com/Dr-Eyob-Mamo-1050816404958639/ | 6 163 |
| 8 | የዛሬው ነጻ ስልጠና የቴሌግራም ቅጂ ቀርቦላችኋል።
እናመሰግናለን! | 5 749 |
| 9 | record.ogg | 6 048 |
| 10 | ስልጠናው ከገማሽ ሰዓት በኋላ ይጀምራል!!! | 7 783 |
| 11 | ከ3 ሰዓት እስከ 4 ሰዓት የሚቆየው የነጻ ስልጠናችን ከ አንድ ሰዓት በኋላ ይጀምራል!!! | 7 413 |
| 12 | የዛሬው የነጻ ስልጠኛ ልክ ከምሽቱ 3 ሰዓት ላይ ይጀምራል፡፡
ስልጠናው የሚሰጠው በዚሁ channel ነው፡፡ ቻናሉን join ያላደረጉ ጓደኞቻችሁን join እንዲያደርጉ እየጋበዛችሁ ቆዩ፡፡
የስልጠናው ርእስ፡- “ከልጅነት (ካለፈ) 'ትራውማ' / 'trauma' መላቀቅ!”
የልጅነታችን “ትራውማ” . . .
💎 በማሕበራዊ ግንኙነታችን ላይ . . .
💎በፍቅር ግንኙነታችን ላይ . . .
💎 ከትዳር አጋራችን ጋር ባለን ግንኙነት ላይ . . .
💎 በስራው ዓለም ውስጥ ባለን የሰው-ለሰው ግንኙነት ላይ . . . ከፍተኛ የሆነ ተጽእኖ አለው፡፡
ይህ ነጻ ስልጠና . . .
1. ለራሳችንም ሆነ ለሰዎች ግራ የሚገባንን የአቀራረብ ልማዶቻችንን ምንጭ ያመለከትናል፣
2. ለአያያዝ አስቸጋሪ የሆኑ ሰዎችን እንደዚያ የሆኑበትን መነሻ እንድንገነዘብ ያስችለናል፡፡
3. ሰዎችን በማማከር ዘርፍ ለተሰማራንና ለመሰማራት ለምንፈልግ ሰዎች ግንዛቤን ይሰጠናል፡፡
በ3 ሰአት እንገናኛለን!!! | 7 129 |
| 13 | ዛሬ ማታ ከ3 ሰዓት እስከ 4 ሰዓት ላለን ስልጠና ራሳችሁን ለማዘጋጀት፣ ይህንን የልጅነት trauma ን የመለየት መጠይቅ ሰርታችሁ እንድትቆዩ ይሁን፡፡ | 7 231 |
| 14 | የዛሬው ምሽት ነጻ ስልጠና አያምልጣችሁ!
ስልጠናው የሚሰጠው በዚሁ ቻናል ላይ ነው፡፡
ዛሬ ማታ ክ3 እስከ 4 ሰአት
የስልጠናው ርእስ፡- “ከልጅነት (ካለፈ) 'ትራውማ' / 'trauma' መላቀቅ!”
ስልጠናው የሚሰጥበት መንገድ፡- በቴሌግራም Live!
የልጅነታችን “ትራውማ” . . .
💎 በማሕበራዊ ግንኙነታችን ላይ . . .
💎በፍቅር ግንኙነታችን ላይ . . .
💎 ከትዳር አጋራችን ጋር ባለን ግንኙነት ላይ . . .
💎 በስራው ዓለም ውስጥ ባለን የሰው-ለሰው ግንኙነት ላይ . . . ከፍተኛ የሆነ ተጽእኖ አለው፡፡
ይህ ነጻ ስልጠና . . .
1. ለራሳችንም ሆነ ለሰዎች ግራ የሚገባንን የአቀራረብ ልማዶቻችንን ምንጭ ያመለከትናል፣
2. ለአያያዝ አስቸጋሪ የሆኑ ሰዎችን እንደዚያ የሆኑበትን መነሻ እንድንገነዘብ ያስችለናል፡፡
3. ሰዎችን በማማከር ዘርፍ ለተሰማራንና ለመሰማራት ለምንፈልግ ሰዎች ግንዛቤን ይሰጠናል፡፡
ስልጠናው የሚጠው በዋናው የዶ/ር ኢዮብ ማሞ የቴሌግራም ቻናል ላይ Live ይሆናል፡፡
ይህንን ቻናል ጓደኞቻችሁ join እንዲያደርጉ በመጋበዝ ቆዩ!
ስልጠናው የሚሰጠው በዚሁ ቻናል ላይ ሲሆን፣ ይህንን ስልጠናው የሚጥበትን ቻናል ለመቀላቀል እንዲችሉ ለወዳጆቻችሁ
ከዚህ በታች ያለውን ሊንክ ማጋራት ትችላላችሁ፦
https://t.me/Dreyob | 7 337 |
| 15 | ዛሬ ማታ ክ3 እስከ 4 ሰአት
ነጻ የስልጠና እድል!
ቀኑ:- ዛሬ ኃሙስ ሰኔ 4/2018
ሰዓቱ፡- ከምሽቱ 3፡00 እስከ 4፡00
የስልጠናው ርእስ፡- “ከልጅነት (ካለፈ) 'ትራውማ' / 'trauma' መላቀቅ!”
ስልጠናው የሚሰጥበት መንገድ፡- በቴሌግራም Live!
የልጅነታችን “ትራውማ” . . .
💎 በማሕበራዊ ግንኙነታችን ላይ . . .
💎በፍቅር ግንኙነታችን ላይ . . .
💎 ከትዳር አጋራችን ጋር ባለን ግንኙነት ላይ . . .
💎 በስራው ዓለም ውስጥ ባለን የሰው-ለሰው ግንኙነት ላይ . . . ከፍተኛ የሆነ ተጽእኖ አለው፡፡
ይህ ነጻ ስልጠና . . .
1. ለራሳችንም ሆነ ለሰዎች ግራ የሚገባንን የአቀራረብ ልማዶቻችንን ምንጭ ያመለከትናል፣
2. ለአያያዝ አስቸጋሪ የሆኑ ሰዎችን እንደዚያ የሆኑበትን መነሻ እንድንገነዘብ ያስችለናል፡፡
3. ሰዎችን በማማከር ዘርፍ ለተሰማራንና ለመሰማራት ለምንፈልግ ሰዎች ግንዛቤን ይሰጠናል፡፡
ስልጠናው የሚጠው በዋናው የዶ/ር ኢዮብ ማሞ የቴሌግራም ቻናል ላይ Live ይሆናል፡፡
ይህንን ቻናል ጓደኞቻችሁ join እንዲያደርጉ በመጋበዝ ቆዩ!
ስልጠናው የሚሰጠው በዚሁ ቻናል ላይ ሲሆን፣ ይህንን ስልጠናው የሚጥበትን ቻናል ለመቀላቀል እንዲችሉ ለወዳጆቻችሁ
ከዚህ በታች ያለውን ሊንክ ማጋራት ትችላላችሁ፦
https://t.me/Dreyob | 6 197 |
| 16 | የብዙዎች ጥያቄ
የሰኔውን ወር የንባብ አሁን ብንቀላቀልስ?
መልስ፡-
የሰኔ ወር ንባብ ዛሬ አራተኛ ቀኑን ይዟል፡፡
ዛሬ በመቀላቀልና ያለፋችሁን በማንበብ ከነገ ጀምሮ በየጠዋቱ የሚለቀቀውን ወሩን ሙሉ በማንበብ መቀጠል ትችላላችሁ፡፡
ንባብ የተመረጠው መጽሐፍ - “ቀዩ መስመር”
ንባቡ የጀመረበት ቀን - ሰኔ 1 / 2018
ንባቡ የሚጠናቀቅበት ቀን - ሰኔ 30 / 2018
ይህንን Book Club ለመቀላቀል፡- በዚህ 👉 @DrEyobmamo የቴሌግራም አድራሻ (user name) inbox በማድረግ ፍላጎታችሁን ስትገልጹ ሙሉ መረጃ ይላክላችኋል፡፡
Join now!!! | 5 953 |
| 17 | “እውቀትን ወደ ተግባር እንዴት መቀየር ይቻላል?” የሚለውን ትናንትና የጀመርኩትን ተከታይ ሃሳብ ይዤላችሁ ቀርቤአለሁ፡፡
4. መርሆዎችን ወደ ግልጽ ተግባራት መቀየር
አጠቃላይ እውቀት ብዙ ጊዜ ወደ ተግባር አይመራም።
ለምሳሌ፣ “የበለጠ ዲሲፕሊን ማዳበር አለብኝ” ከማለት ይልቅ፣ “በየቀኑ ምሽት ላይ የነገውን ውሎ ለማቀድ 10 ደቂቃ እመድባለሁ” ብንልና ብናደርገው ተመራጭ ነው። “የሰው-ለሰው ግንኙነቶቼን ማሻሻል አለብኝ” ከማለት ይልቅ፣ “በየቀኑ ለአንድ ሰው የሚያበረታታ መልዕክት እልካለሁ” በማለት ተግበር የላቀ ነው።
ግልጽ ተግባራት ግልጽ ውጤቶችን ያስገኛሉ።
5. ለተግባሩ ጊዜ መመደብ (ቀጠሮ መያዝ)
ዕቅድ ወጥቶለትና የቀን ገደብ ተቀምጦለት በፕሮግራም የተያዘ ነገር፣ እንዲሁ በምኞት ብቻ ከሚታሰብ ነገር በላይ የመተግበር ዕድሉ ከፍተኛ ነው። ስለሆነም፣ ለመተግበር ያሰብናቸውን ነገሮች በካላንደችን ውስጥ መመዝገብና የጊዜ ገደብ ማስቀመጥ አስፈላጊ ነው፡፡
ለምሳሌ፣ “በዚህ ቀን የአካል ብቃት እንቅስቃሴ እጀምራለሁ”፤ “በዚህ ጊዜ ውስጥ አንድ መጽሐፍ ጀምሬ እጨርሳለሁ” እና የመሳሰሉት ማለት ነው፡፡
ያለ ጊዜ ምደባ የሚኖሩ መልካም ምኞቶች፣ እንዲሁ ምኞት ሆነው የመቅረት ዕድላቸው ሰፊ ነው።
6. ተጠያቂነትን መፍጠር
ማድረግ የፈለግነውን ነገር ከማድረግ ብዙ ከታገልን ምን ለማድረግ እንዳቀድን ለአንድ የቅርብ ሰው መንገርና ተጠያቂነትን ማዳበር ጥሩ ልምምድ ነው። ሰዎች የገቡትን ቃል ሌላ ሰው እንደሚያውቅባቸው ሲረዱ፣ በተግባር የመተርጎም ዕድላቸው ሰፊ ነው።
አማካሪ (Mentor) መፈለግ፣ የአንድ ቡድን አባል መሆን፣ ከጓደኛ ጋር በመጣመር አጋር መሆን፣ እድገታችንን በየጊዜው ሪፖርት የምናደርግለት ሰው መፈለግ፡፡
ተጠያቂነት ምኞትን ወደ ቁርጠኝነት ይቀይራል።
7. ትኩረታችን በድግግሞሹ ላይ እንጂ ፍጹም በመሆን ላይ አለማድረግ
ብዙ ሰዎች አንድን የጀመሩትን ነገር ፍጹም አድርገው ስላልሠሩት ብቻ ማድረጉን ያቆማሉ። ግባችን መሆን ያለበት ግን፣ እንከን የለሽ አፈጻጸም ሳይሆን፣ ደጋግሞ መሥራት ላይ ነው።
ማንኛውም ክህሎት የሚገነባው ፍጹም ባልሆነ አጀማመርና ካለማቋረጥ በሚደረግ ልምምድ ውስጥ ነው። እድገት የድግግሞሽ ውጤት ነው።
ማሳሰቢያ፡-
ኃሙስ ሰኔ 4/2018 ከምሽቱ 3፡00 እስከ 4፡00 ድረስ በዚሁ የቴሌግራም ቻናሌ Live! የሚሰጠው ስልጠና አያምልጣችሁ፡፡
የስልጠናው ርእስ፡- “ከልጅነት (ካለፈ) 'ትራውማ' / 'trauma' መላቀቅ!”
ወዳጆቻችሁ ይህንን channel join በማድረግ ስልጠናው እንዲካፈሉ ጋብዟቸው፡፡
https://t.me/Dreyob
https://m.youtube.com/user/naeleyob623
https://www.facebook.com/Dr-Eyob-Mamo-1050816404958639/ | 6 143 |
| 18 | እውቀትን ወደ ተግባር! (ክፍል አራት) | 5 213 |
| 19 | ነገ ማታ ክ3 እስከ 4 ሰአት
ነጻ የስልጠና እድል!
Mark Your Calendar!
ቀኑ፡- ኃሙስ ሰኔ 4/2018
ሰዓቱ፡- ከምሽቱ 3፡00 እስከ 4፡00
የስልጠናው ርእስ፡- “ከልጅነት (ካለፈ) 'ትራውማ' / 'trauma' መላቀቅ!”
ስልጠናው የሚሰጥበት መንገድ፡- በቴሌግራም Live!
የልጅነታችን “ትራውማ” . . .
💎 በማሕበራዊ ግንኙነታችን ላይ . . .
💎በፍቅር ግንኙነታችን ላይ . . .
💎 ከትዳር አጋራችን ጋር ባለን ግንኙነት ላይ . . .
💎 በስራው ዓለም ውስጥ ባለን የሰው-ለሰው ግንኙነት ላይ . . . ከፍተኛ የሆነ ተጽእኖ አለው፡፡
ይህ ነጻ ስልጠና . . .
1. ለራሳችንም ሆነ ለሰዎች ግራ የሚገባንን የአቀራረብ ልማዶቻችንን ምንጭ ያመለከትናል፣
2. ለአያያዝ አስቸጋሪ የሆኑ ሰዎችን እንደዚያ የሆኑበትን መነሻ እንድንገነዘብ ያስችለናል፡፡
3. ሰዎችን በማማከር ዘርፍ ለተሰማራንና ለመሰማራት ለምንፈልግ ሰዎች ግንዛቤን ይሰጠናል፡፡
ስልጠናው የሚጠው በዋናው የዶ/ር ኢዮብ ማሞ የቴሌግራም ቻናል ላይ Live ይሆናል፡፡
ይህንን ቻናል ጓደኞቻችሁ join እንዲያደርጉ በመጋበዝ ቆዩ!
ስልጠናው የሚሰጠው በዚሁ ቻናል ላይ ሲሆን፣ ይህንን ስልጠናው የሚጥበትን ቻናል ለመቀላቀል እንዲችሉ ለወዳጆቻችሁ
ከዚህ በታች ያለውን ሊንክ ማጋራት ትችላላችሁ፦
https://t.me/Dreyob | 6 917 |
| 20 | የሰኔ ወር የንባብ challenge እንቀጠለ ነው፡፡
በመቶ የሚዎጠሩ አንባቢያን የሰኔ አንድ፣ ሁለትን እና የዛሬውን ክፍል አንበበዋል፡፡
ከዛሬው ንባብ የተቀነጨበ ላጋራችሁ፡-
ቀዩ መስመር ስንል?!
“ለአንድ ነገር የቀይ መስመር ገደብን ማስቀመጥ ማለት ራሳችንን በሚዛናዊነት ማክበርና መውደድ፣ ያንንም በማድረጋችን ምክንያት ሰዎች ቅር የመሰኘታቸውን አስቸጋሪ ሁኔታ ለመጋፈጥ ዝግጁ መሆን ማለት ነው” - Brené Brown
እስቲ አስበው! አንድ ሃገር ከሌላው የጎረቤት ሃገር ጋር የሚለየው ወሰንና ድንበር ባይኖረው፡፡ በአሁኑ ጊዜ፣ እንኳን በየብስ ላይ ቀርቶ ውኃውና በአየሩ ላይ ሳይቀር “ባለቤት” እና “ወሰን” የሚለይበት ክልልአለው፡፡
እነዚህን ወሰኖች ደግሞ የማስከበሪያ አለም አቀፍ ሕጎች አሉ፡፡ እነዚህን ወሰኖች አለማክበር (ቀዩን መስመር መጣስ)የማሕበራዊና የግንኙነት ቀውስያለውን ያህል ወሰኖቹን አክብረው በሚኖሩ ሕብረተሰቦች መካከል ያለው ሰላምና ብልጽግና ደግሞ ይህ ነው አይባልም፡፡
አሁን ባለንበት ዘመን አንድ ሰው ከሌላው ሰው ጋር፣ አንድ ሕብረተሰብ ከሌላው ሕብረተሰብ ጋር፣ አንድ ድርጅት ከሌላው ድርጅት ጋር . . . በሚያደርገው ግንኙነትና ድርድር የሚቀመጡ ገደቦች “ቀይ መስመር” በመባል ይታወቃሉ፡፡
በዚህ ሃሳብ መሰረት “ቀዩ መስመር” የሚለውን አባባል እንደ አዑዱ ዘርፈ-ብዙ በሆነ መልኩ ልንገልጸው እንችላለን፡፡
· አንድን ግንኙነት የሚገዛ ሕግና መመሪያ፡፡
· በግንኙነት ውስጥ የሚፈቀደውንና የማይፈቀደውን የምንለይበት መንገድ፡፡
· “እሺ” ወይም “እምቢ” የምንላቸውን ነገሮች የሚለየው መስመር፡፡
· የአንድ ግንኙነትና ቅርበት ልክና ገደብ፡፡
· በግንኙነት ውስጥ ለሰዎች የምንሰጠውና ሰዎቹ ለእኛ የሚሰጡን የመብት ገደብ፡፡
· በማንኛውም የግንኙነት አውድ ውስጥ የሚገኝ የስልጣን ገደብ፡፡
· ለግንኙነት ቀውስ ምክንያት የሚሆኑ ልምምዶችን የምናሳውቅበት “ደንብ”፡፡
እነዚህ ከላይ የተጠቀሱትና መሰል ሃሳቦች የሌሉት ግንኙነት አጀማመሩ መልካም ቢመስልም ገና ከጅማሬው ለቀውስ የተወሰነ ግንኙነት ነው፡፡
የብዙ በሕብረተሰባችን መካከል የምናያቸው ንትርኮች፣ ጭቅጭቆችና ክሶች መንስኤው ይኸው የሰውን ቀይ መስመር የመጣስ ሁኔታ ነው፡፡ ይህንን ቀውስ ማስተካከያውና ማረሚያው መንገድ ደግሞ ተገቢውን የቀይ መስመር ወሰንና ገደብ መገንዘብና ያንንም መስመር በሚዛናዊነት ማስመር፣ እንዲሁም ማስከበር ነው፡፡
ንባቡን ለመቀላቀል ከዚህ በታች ባለው link inbox በማድረግ መረጃ ይቀበሉ፡፡
@DrEyobmamo | 7 092 |
متاح الآن! بحث تيليغرام 2025 — أهم رؤى العام 
