Dr. Eyob Mamo
📈 تحلیل کانال تلگرام Dr. Eyob Mamo
کانال Dr. Eyob Mamo (@dreyob) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 79 042 مشترک است و جایگاه 1 982 را در دسته آموزش و رتبه 376 را در منطقه أثيوبيا دارد.
📊 شاخصهای مخاطب و پویایی
از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 79 042 مشترک جذب کرده است.
بر اساس آخرین دادهها در تاریخ 09 ژوئن, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر -256 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر 33 بوده و همچنان دسترسی گستردهای حفظ شده است.
- وضعیت تأیید: تأیید نشده
- نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 11.78% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 5.62% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب میکند.
- دسترسی پستها: هر پست به طور میانگین 9 307 بازدید دریافت میکند. در اولین روز معمولاً 4 443 بازدید جمعآوری میشود.
- واکنشها و تعامل: مخاطبان بهطور فعال حمایت میکنند؛ میانگین واکنش به هر پست 71 است.
📝 توضیح و سیاست محتوایی
نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاههای شخصی توصیف میکند:
“Life skill development!
You can contact me
@DrEyobmamo”
به لطف بهروزرسانیهای پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 10 ژوئن, 2026)، کانال همواره بهروز و دارای دسترسی بالاست. تحلیلها نشان میدهد مخاطبان بهطور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته آموزش تبدیل کردهاند.
در حال بارگیری داده...
| تاریخ | رشد مشترکین | اشارات | کانالها | |
| 11 ژوئن | 0 | |||
| 10 ژوئن | +16 | |||
| 09 ژوئن | +44 | |||
| 08 ژوئن | +12 | |||
| 07 ژوئن | +15 | |||
| 06 ژوئن | +7 | |||
| 05 ژوئن | +16 | |||
| 04 ژوئن | +4 | |||
| 03 ژوئن | +5 | |||
| 02 ژوئن | +14 | |||
| 01 ژوئن | +13 |
| 2 | “እውቀትን ወደ ተግባር እንዴት መቀየር ይቻላል?” የሚለውን ትናንትና የጀመርኩትን ተከታይ ሃሳብ ይዤላችሁ ቀርቤአለሁ፡፡
4. መርሆዎችን ወደ ግልጽ ተግባራት መቀየር
አጠቃላይ እውቀት ብዙ ጊዜ ወደ ተግባር አይመራም።
ለምሳሌ፣ “የበለጠ ዲሲፕሊን ማዳበር አለብኝ” ከማለት ይልቅ፣ “በየቀኑ ምሽት ላይ የነገውን ውሎ ለማቀድ 10 ደቂቃ እመድባለሁ” ብንልና ብናደርገው ተመራጭ ነው። “የሰው-ለሰው ግንኙነቶቼን ማሻሻል አለብኝ” ከማለት ይልቅ፣ “በየቀኑ ለአንድ ሰው የሚያበረታታ መልዕክት እልካለሁ” በማለት ተግበር የላቀ ነው።
ግልጽ ተግባራት ግልጽ ውጤቶችን ያስገኛሉ።
5. ለተግባሩ ጊዜ መመደብ (ቀጠሮ መያዝ)
ዕቅድ ወጥቶለትና የቀን ገደብ ተቀምጦለት በፕሮግራም የተያዘ ነገር፣ እንዲሁ በምኞት ብቻ ከሚታሰብ ነገር በላይ የመተግበር ዕድሉ ከፍተኛ ነው። ስለሆነም፣ ለመተግበር ያሰብናቸውን ነገሮች በካላንደችን ውስጥ መመዝገብና የጊዜ ገደብ ማስቀመጥ አስፈላጊ ነው፡፡
ለምሳሌ፣ “በዚህ ቀን የአካል ብቃት እንቅስቃሴ እጀምራለሁ”፤ “በዚህ ጊዜ ውስጥ አንድ መጽሐፍ ጀምሬ እጨርሳለሁ” እና የመሳሰሉት ማለት ነው፡፡
ያለ ጊዜ ምደባ የሚኖሩ መልካም ምኞቶች፣ እንዲሁ ምኞት ሆነው የመቅረት ዕድላቸው ሰፊ ነው።
6. ተጠያቂነትን መፍጠር
ማድረግ የፈለግነውን ነገር ከማድረግ ብዙ ከታገልን ምን ለማድረግ እንዳቀድን ለአንድ የቅርብ ሰው መንገርና ተጠያቂነትን ማዳበር ጥሩ ልምምድ ነው። ሰዎች የገቡትን ቃል ሌላ ሰው እንደሚያውቅባቸው ሲረዱ፣ በተግባር የመተርጎም ዕድላቸው ሰፊ ነው።
አማካሪ (Mentor) መፈለግ፣ የአንድ ቡድን አባል መሆን፣ ከጓደኛ ጋር በመጣመር አጋር መሆን፣ እድገታችንን በየጊዜው ሪፖርት የምናደርግለት ሰው መፈለግ፡፡
ተጠያቂነት ምኞትን ወደ ቁርጠኝነት ይቀይራል።
7. ትኩረታችን በድግግሞሹ ላይ እንጂ ፍጹም በመሆን ላይ አለማድረግ
ብዙ ሰዎች አንድን የጀመሩትን ነገር ፍጹም አድርገው ስላልሠሩት ብቻ ማድረጉን ያቆማሉ። ግባችን መሆን ያለበት ግን፣ እንከን የለሽ አፈጻጸም ሳይሆን፣ ደጋግሞ መሥራት ላይ ነው።
ማንኛውም ክህሎት የሚገነባው ፍጹም ባልሆነ አጀማመርና ካለማቋረጥ በሚደረግ ልምምድ ውስጥ ነው። እድገት የድግግሞሽ ውጤት ነው።
ማሳሰቢያ፡-
ኃሙስ ሰኔ 4/2018 ከምሽቱ 3፡00 እስከ 4፡00 ድረስ በዚሁ የቴሌግራም ቻናሌ Live! የሚሰጠው ስልጠና አያምልጣችሁ፡፡
የስልጠናው ርእስ፡- “ከልጅነት (ካለፈ) 'ትራውማ' / 'trauma' መላቀቅ!”
ወዳጆቻችሁ ይህንን channel join በማድረግ ስልጠናው እንዲካፈሉ ጋብዟቸው፡፡
https://t.me/Dreyob
https://m.youtube.com/user/naeleyob623
https://www.facebook.com/Dr-Eyob-Mamo-1050816404958639/ | 1 161 |
| 3 | እውቀትን ወደ ተግባር! (ክፍል አራት) | 1 067 |
| 4 | ነገ ማታ ክ3 እስከ 4 ሰአት
ነጻ የስልጠና እድል!
Mark Your Calendar!
ቀኑ፡- ኃሙስ ሰኔ 4/2018
ሰዓቱ፡- ከምሽቱ 3፡00 እስከ 4፡00
የስልጠናው ርእስ፡- “ከልጅነት (ካለፈ) 'ትራውማ' / 'trauma' መላቀቅ!”
ስልጠናው የሚሰጥበት መንገድ፡- በቴሌግራም Live!
የልጅነታችን “ትራውማ” . . .
💎 በማሕበራዊ ግንኙነታችን ላይ . . .
💎በፍቅር ግንኙነታችን ላይ . . .
💎 ከትዳር አጋራችን ጋር ባለን ግንኙነት ላይ . . .
💎 በስራው ዓለም ውስጥ ባለን የሰው-ለሰው ግንኙነት ላይ . . . ከፍተኛ የሆነ ተጽእኖ አለው፡፡
ይህ ነጻ ስልጠና . . .
1. ለራሳችንም ሆነ ለሰዎች ግራ የሚገባንን የአቀራረብ ልማዶቻችንን ምንጭ ያመለከትናል፣
2. ለአያያዝ አስቸጋሪ የሆኑ ሰዎችን እንደዚያ የሆኑበትን መነሻ እንድንገነዘብ ያስችለናል፡፡
3. ሰዎችን በማማከር ዘርፍ ለተሰማራንና ለመሰማራት ለምንፈልግ ሰዎች ግንዛቤን ይሰጠናል፡፡
ስልጠናው የሚጠው በዋናው የዶ/ር ኢዮብ ማሞ የቴሌግራም ቻናል ላይ Live ይሆናል፡፡
ይህንን ቻናል ጓደኞቻችሁ join እንዲያደርጉ በመጋበዝ ቆዩ!
ስልጠናው የሚሰጠው በዚሁ ቻናል ላይ ሲሆን፣ ይህንን ስልጠናው የሚጥበትን ቻናል ለመቀላቀል እንዲችሉ ለወዳጆቻችሁ
ከዚህ በታች ያለውን ሊንክ ማጋራት ትችላላችሁ፦
https://t.me/Dreyob | 3 235 |
| 5 | የሰኔ ወር የንባብ challenge እንቀጠለ ነው፡፡
በመቶ የሚዎጠሩ አንባቢያን የሰኔ አንድ፣ ሁለትን እና የዛሬውን ክፍል አንበበዋል፡፡
ከዛሬው ንባብ የተቀነጨበ ላጋራችሁ፡-
ቀዩ መስመር ስንል?!
“ለአንድ ነገር የቀይ መስመር ገደብን ማስቀመጥ ማለት ራሳችንን በሚዛናዊነት ማክበርና መውደድ፣ ያንንም በማድረጋችን ምክንያት ሰዎች ቅር የመሰኘታቸውን አስቸጋሪ ሁኔታ ለመጋፈጥ ዝግጁ መሆን ማለት ነው” - Brené Brown
እስቲ አስበው! አንድ ሃገር ከሌላው የጎረቤት ሃገር ጋር የሚለየው ወሰንና ድንበር ባይኖረው፡፡ በአሁኑ ጊዜ፣ እንኳን በየብስ ላይ ቀርቶ ውኃውና በአየሩ ላይ ሳይቀር “ባለቤት” እና “ወሰን” የሚለይበት ክልልአለው፡፡
እነዚህን ወሰኖች ደግሞ የማስከበሪያ አለም አቀፍ ሕጎች አሉ፡፡ እነዚህን ወሰኖች አለማክበር (ቀዩን መስመር መጣስ)የማሕበራዊና የግንኙነት ቀውስያለውን ያህል ወሰኖቹን አክብረው በሚኖሩ ሕብረተሰቦች መካከል ያለው ሰላምና ብልጽግና ደግሞ ይህ ነው አይባልም፡፡
አሁን ባለንበት ዘመን አንድ ሰው ከሌላው ሰው ጋር፣ አንድ ሕብረተሰብ ከሌላው ሕብረተሰብ ጋር፣ አንድ ድርጅት ከሌላው ድርጅት ጋር . . . በሚያደርገው ግንኙነትና ድርድር የሚቀመጡ ገደቦች “ቀይ መስመር” በመባል ይታወቃሉ፡፡
በዚህ ሃሳብ መሰረት “ቀዩ መስመር” የሚለውን አባባል እንደ አዑዱ ዘርፈ-ብዙ በሆነ መልኩ ልንገልጸው እንችላለን፡፡
· አንድን ግንኙነት የሚገዛ ሕግና መመሪያ፡፡
· በግንኙነት ውስጥ የሚፈቀደውንና የማይፈቀደውን የምንለይበት መንገድ፡፡
· “እሺ” ወይም “እምቢ” የምንላቸውን ነገሮች የሚለየው መስመር፡፡
· የአንድ ግንኙነትና ቅርበት ልክና ገደብ፡፡
· በግንኙነት ውስጥ ለሰዎች የምንሰጠውና ሰዎቹ ለእኛ የሚሰጡን የመብት ገደብ፡፡
· በማንኛውም የግንኙነት አውድ ውስጥ የሚገኝ የስልጣን ገደብ፡፡
· ለግንኙነት ቀውስ ምክንያት የሚሆኑ ልምምዶችን የምናሳውቅበት “ደንብ”፡፡
እነዚህ ከላይ የተጠቀሱትና መሰል ሃሳቦች የሌሉት ግንኙነት አጀማመሩ መልካም ቢመስልም ገና ከጅማሬው ለቀውስ የተወሰነ ግንኙነት ነው፡፡
የብዙ በሕብረተሰባችን መካከል የምናያቸው ንትርኮች፣ ጭቅጭቆችና ክሶች መንስኤው ይኸው የሰውን ቀይ መስመር የመጣስ ሁኔታ ነው፡፡ ይህንን ቀውስ ማስተካከያውና ማረሚያው መንገድ ደግሞ ተገቢውን የቀይ መስመር ወሰንና ገደብ መገንዘብና ያንንም መስመር በሚዛናዊነት ማስመር፣ እንዲሁም ማስከበር ነው፡፡
ንባቡን ለመቀላቀል ከዚህ በታች ባለው link inbox በማድረግ መረጃ ይቀበሉ፡፡
@DrEyobmamo | 4 830 |
| 6 | የሰኔ ወር የንባብ challenge እንቀጠለ ነው፡፡ | 4 016 |
| 7 | እውቀትን ወደ ተግባር! (ክፍል ሶስት)
ትናንትና እና ከትናንት ወዲያ የተመለከትናቸው ሃሳቦች ሊያስከት የሚችሉትን ጥያቄ በማሰብ፣ “እውቀትን ወደ ተግባር እንዴት መቀየር ይቻላል?” የሚል ተከታታይ ሃሳብ ይዤላችሁ ቀርቤአለሁ፡፡
እውቀት በአእምሮ ውስጥ ይከማቻል፤ ተግባር ግን ሕይወትን ይለውጣል፡፡
በቀደሙት ፖቶች እንደተመለከትነው፣ ብዙ ሰዎች የሚቸገሩት በእውቀት ማጣት ሳይሆን በተግባር የመተርጎም (የማስፈጸም) ብቃት በማጣታቸው ነው። ዋናው ቁልፍ በመማር እና በማድረግ መካከል ድልድይ መገንባት ነው።
እውቀትን ወደ ተግባር እንዴት መቀየር ይቻላል?
1. ማጥናትን ቀነስ፣ መተግበርን በዛ ማድረግ!
መጀመሪያ ያወቅነውን ነገር ከመተግበራችን በፊት ተጨማሪ መረጃን ብቻ የመሰብሰብ ፍላጎትን መቆጣጠር አስፈላጊ ነው።
ለተማርነው ለእያንዳንዱ ትምህርት፣ የምንወስደውን አንድ የተግባር እርምጃ ለይተን እንወቅ። “ቀጥሎ ምን መማር አለብኝ?” ብለን ከመጠየቅ ይልቅ፣ “አሁን በማውቀው ነገር ምን ማድረግ አለብኝ?” ብለን እንጠይቅ።
2. በትንሹ መጀመር
ብዙ መልካም ዓላማዎች የሚከሽፉት የመጀመሪያውን እርምጃ በጣም ትልቅ ለማድረግ ስምንሞክር ነው።
ለምሳሌ፣ በየቀኑ ለአንድ ሰዓት ከማንበብ ይልቅ፣ በ10 ደቂቃ መጀመር። ለአንድ ሰዓት የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ከማድረግ ይልቅ፣ በ10 ደቂቃ እንቅስቃሴ መጀመር። ትናንሽ እርምጃዎችን ለመጀመርም ሆነ ደጋግሞ ለመስራት ቀላል ናቸው፡፡
ቀጣይነት (ፅናት) ከአንድ ጊዜ ከፍተኛ ጥረት ይበልጣል።
3. ወዲያውኑ መተግበር
ያወቅነውን እውቀት ለመተግበር በቆየን ቁጥር፣ የማድረግ ዕድላችን እየቀነሰ ይሄዳል። ጠቃሚ ነገር ስንማር፣ ዛሬውኑ እንተግብረው፡፡ ለመለማመድ ከሁሉ የተሻለው ጊዜ ትምህርቱ ገና በአእምሯች ውስጥ ትኩስ እያለ ነው። የተገበርነውን ነገር ደግሞ በቶሎ እንገምግመው፡፡ ባደረግነው ግምገማ መሰረት ደግሞ እርማት ለሚያስፈልገው ነገር እርማት እንስጥ፡፡
በዚህ መልኩ ጥጉ ድረስ ከደረስን በኋላ ሌላ እውቀትንና ሌላ ተግባርን ለመለማመድ ራሳችን ማዘጋጀት እንችላለን፡፡
ይቀጥላል . . .
ማሳሰቢያ፡-
ኃሙስ ሰኔ 4/2018 ከምሽቱ 3፡00 እስከ 4፡00 ድረስ በዚሁ የቴሌግራም ቻናሌ Live! የሚሰጠው ስልጠና አያምልጣችሁ፡፡
የስልጠናው ርእስ፡- “ከልጅነት (ካለፈ) 'ትራውማ' / 'trauma' መላቀቅ!”
ወዳጆቻችሁ ይህንን channel join በማድረግ ስልጠናው እንዲካፈሉ ጋብዟቸው፡፡
https://t.me/Dreyob
https://m.youtube.com/user/naeleyob623
https://www.facebook.com/Dr-Eyob-Mamo-1050816404958639/ | 4 523 |
| 8 | እውቀትን ወደ ተግባር! (ክፍል ሶስት) | 3 736 |
| 9 | "ትናንትና ሰኔ 1 ቀን የተጀመረውን የንባብ challenge ዛሬ መቀላቀል እንችላለን?" ለምትሉ መልሱ አዎን ትችላላችሁ ነው። | 4 564 |
| 10 | ከነገ ወዲያ ማታ ክ3 እስከ 4 ሰአት
ነጻ የስልጠና እድል!
ቀኑ፡- ኃሙስ ሰኔ 4/2018
ሰዓቱ፡- ከምሽቱ 3፡00 እስከ 4፡00
የስልጠናው ርእስ፡- “ከልጅነት (ካለፈ) 'ትራውማ' / 'trauma' መላቀቅ!”
ስልጠናው የሚሰጥበት መንገድ፡- በቴሌግራም Live!
የልጅነታችን “ትራውማ” . . .
💎 በማሕበራዊ ግንኙነታችን ላይ . . .
💎በፍቅር ግንኙነታችን ላይ . . .
💎 ከትዳር አጋራችን ጋር ባለን ግንኙነት ላይ . . .
💎 በስራው ዓለም ውስጥ ባለን የሰው-ለሰው ግንኙነት ላይ . . . ከፍተኛ የሆነ ተጽእኖ አለው፡፡
ይህ ነጻ ስልጠና . . .
1. ለራሳችንም ሆነ ለሰዎች ግራ የሚገባንን የአቀራረብ ልማዶቻችንን ምንጭ ያመለከትናል፣
2. ለአያያዝ አስቸጋሪ የሆኑ ሰዎችን እንደዚያ የሆኑበትን መነሻ እንድንገነዘብ ያስችለናል፡፡
3. ሰዎችን በማማከር ዘርፍ ለተሰማራንና ለመሰማራት ለምንፈልግ ሰዎች ግንዛቤን ይሰጠናል፡፡
ስልጠናው የሚጠው በዋናው የዶ/ር ኢዮብ ማሞ የቴሌግራም ቻናል ላይ Live ይሆናል፡፡
ይህንን ቻናል ጓደኞቻችሁ join እንዲያደርጉ በመጋበዝ ቆዩ!
ስልጠናው የሚሰጠው በዚሁ ቻናል ላይ ሲሆን፣ ይህንን ስልጠናው የሚጥበትን ቻናል ለመቀላቀል እንዲችሉ ለወዳጆቻችሁ
ከዚህ በታች ያለውን ሊንክ ማጋራት ትችላላችሁ፦
https://t.me/Dreyob | 5 315 |
| 11 | ነጻ የስልጠና እድል!
Mark Your Calendar!
ቀኑ፡- ኃሙስ ሰኔ 4/2018
ሰዓቱ፡- ከምሽቱ 3፡00 እስከ 4፡00
የስልጠናው ርእስ፡- “ከልጅነት (ካለፈ) 'ትራውማ' / 'trauma' መላቀቅ!”
ስልጠናው የሚሰጥበት መንገድ፡- በቴሌግራም Live!
የልጅነታችን “ትራውማ” . . .
💎 በማሕበራዊ ግንኙነታችን ላይ . . .
💎በፍቅር ግንኙነታችን ላይ . . .
💎 ከትዳር አጋራችን ጋር ባለን ግንኙነት ላይ . . .
💎 በስራው ዓለም ውስጥ ባለን የሰው-ለሰው ግንኙነት ላይ . . . ከፍተኛ የሆነ ተጽእኖ አለው፡፡
ይህ ነጻ ስልጠና . . .
1. ለራሳችንም ሆነ ለሰዎች ግራ የሚገባንን የአቀራረብ ልማዶቻችንን ምንጭ ያመለከትናል፣
2. ለአያያዝ አስቸጋሪ የሆኑ ሰዎችን እንደዚያ የሆኑበትን መነሻ እንድንገነዘብ ያስችለናል፡፡
3. ሰዎችን በማማከር ዘርፍ ለተሰማራንና ለመሰማራት ለምንፈልግ ሰዎች ግንዛቤን ይሰጠናል፡፡
ስልጠናው የሚጠው በዋናው የዶ/ር ኢዮብ ማሞ የቴሌግራም ቻናል ላይ Live ይሆናል፡፡
ይህንን ቻናል ጓደኞቻችሁ join እንዲያደርጉ በመጋበዝ ቆዩ!
ስልጠናው የሚጥበትን ቻናል ለመቀላቀል ከዚህ በታች ያለውን ሊንክ ይጫኑ
https://t.me/Dreyob | 6 326 |
| 12 | እውቀትን ወደ ተግባር! (ክፍል ሁለት)
ትናንትና የጀመርነውን ሃሳብ በመቀጠል የሚቀጥሉትን ተጨማሪ ሃሳቦች አቀርባለሁ . . .
4. ተግባር የሌለው እውቀት ወደ ኩራት ሊመራ ይችላል
አንዳንድ ጊዜ ሰዎች ራሳቸውን የሚመዝኑት ባከናወኑት ነገር ሳይሆን በሚያውቁት ነገር ልክ ነው። ሳይመሩ ስለ አመራር ጥበብ ሊወያዩ፣ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ሳያደርጉ ስለ ጤና ሊያወሩ፣ ወይም ራሳቸው የማይከተሉትን መርሆዎች ሊያስተምሩ ይችላሉ።
እውቀት፣ አንድ ሰው ምንም ዓይነት እውነተኛ ስኬት ሳያስመዘግብ አስቀድሞ ስኬታማ እንደሆነ እንዲሰማው ሊያደርግ ይችላል። መረጃ ሰውን ሳያሳድግና ባህሪውን ሳይለውጥ፣ ኩራቱን ብቻ ሊያሳብጥበት ይችላል።
5. ተግባር እውነተኛ እውቀታችንን ያሳያል
ብዙ ነገሮች በተግባር ለመሥራት እስክንሞክራቸው ድረስ ቀላል ይመስላሉ። ለምሳሌ፣ አመራርን በንግግር ማስረዳት ቀላል ነው፤ ነገር ግን በተግባር መምራት ከባድ ነው። ይቅርታን መስበክ ቀላል ነው፤ ነገር ግን በተግባር ይቅር ማለት ከባድ ነው።
ትዕግስተኛን ሰው ማድነቅ ቀላል ነው፤ ነገር ግን በተግባር ማሳየት ከባድ ነው። ተግባር በንድፈ-ሀሳብ ግንዛቤ እና በእውነተኛ ክህሎት መካከል ያለውን ልዩነት ቁልጭ አድርጎ ያሳያል። አንድን ነገር በተግባር እስካልኖርነው ድረስ በእውነት አናውቀውም።
6. በእውቀትና በተግባር መካከል ያለው ክፍተት ብስጭትን ይፈጥራል
ሰዎች ሁል ጊዜ እየተማሩ ነገር ግን ምንም ዓይነት ለውጥ ስለማያዩ ተስፋ ሊቆርጡ ይችላሉ። ችግሩ አብዛኛውን ጊዜ የመረጃ እጥረት ሳይሆን የመተግበር እጥረት ነው።
አንድ ሰው፣ ገንዘብን እንዴት ማስተዳደር እንዳለበት፣ ግንኙነቶችን እንዴት ማሻሻል እንደሚቻል፣ ጤናን እንዴት መጠበቅ እንደሚችል ሊያው ይችላል፣ ሆኖም ግን፣ ተግባር እውቀትን ተከትሎ ስላልመጣ ህይወት በነበረችበት ትቀጥላለች። እውነተኛ ለውጥ የሚመጣው በመማር እና በማድረግ መካከል ባለው ክፍተት ውስጥ ነው።
7. ጥቂት ተግባር ከብዙ መረጃ ይበልጣል
በተግባር የዋለ አንድ መርህ፣ እያወቅን ችላ ካልናቸው መቶ ትምህርቶች የበለጠ ዋጋ አለው። አንድ ምዕራፍ አንብቦ በተግባር ማዋል፣ ሙሉ ቤተ-መጽሐፍትን አንብቦ ምንም ነገር ከመለወጥ የበለጠ ጠቃሚ ሊሆን ይችላል፡፡
ስኬት የሚለካው በምናውቀው መጠን ሳይሆን በተገበርነው መጠን ነው።
ማሳሰቢያ፡-
ኃሙስ ሰኔ 4/2018 ከምሽቱ 3፡00 እስከ 4፡00 ድረስ በዚሁ የቴሌግራም ቻናሌ Live! የሚሰጠው ስልጠና አያምልጣችሁ፡፡
የስልጠናው ርእስ፡- “ከልጅነት (ካለፈ) 'ትራውማ' / 'trauma' መላቀቅ!”
ወዳጆቻችሁ ይህንን channel join በማድረግ ስልጠናው እንዲካፈሉ ጋብዟቸው፡፡
https://t.me/Dreyob
https://m.youtube.com/user/naeleyob623
https://www.facebook.com/Dr-Eyob-Mamo-1050816404958639/ | 5 841 |
| 13 | እውቀትን ወደ ተግባር! (ክፍል ሁለት) | 5 003 |
| 14 | የሰኔ ወር ንባብ ዛሬ ጀምሯል፡፡
በተለያየ ምክንያት አምልጧችሁ ከሆነ ዛሬውኑ መቀላቀል ትችላላችሁ!
በመቶ የሚቆጠሩ አንባቢያን ተቀላቅለዋል፡፡ እርስዎም ዛሬ ይቀላቀሉ ነገ ማንበብን ይጀምሩ!
ለንባብ የተመረጠው መጽሐፍ - “ቀዩ መስመር”
ንባቡ የሚጀመርበት ቀን - ሰኔ 1 / 2018
ንባቡ የሚጠናቀቅበት ቀን - ሰኔ 30 / 2018
ይህንን Book Club ለመቀላቀል፡- በዚህ 👉 @DrEyobmamo የቴሌግራም አድራሻ (user name) inbox በማድረግ ፍላጎታችሁን ስትገልጹ ሙሉ መረጃ ይላክላችኋል፡፡
Join now!!! | 5 879 |
| 15 | የማይካድ ሀቅ!!!
• ለራሳችሁ ፕሮግራም ካላወጣችሁ፣ ሰዎች ፕሮግራም ያወጡላችኋል፡፡
• የራሳችሁን ሕይወት ካልመራችሁ፣ ሰዎች ወደፈለጉበት ይመሯችኋል፡፡
• ሕይወታችሁን በመልክ በመልኩ ካላደረጃችሁት፣ የመጣውን ሁኔታ ሁሉ እየተቀበላችሁ ለመኖር ትገደዳላችሁ፡፡
• እቅድ አውጥታችሁ የምትከተሉት ነገር ከሌላችሁ፣ ከሁኔታዎች እንደሸሻችሁ ትኖራላችሁ፡፡
• ብዙ እምቅ ብቃት ኖሯችሁ ካለምንም እቅድ እና አደረጃጀት ከኖራችሁ፣ ምንም እውቀት የሌላቸውና የተደራጁት እንደነዷችሁ ትኖላችሁ፡፡
አስቡበት | 6 237 |
| 16 | የሰኔ ወር ንባብ ዛሬ ጀምሯል፡፡
በተለያየ ምክንያት አምልቷችሁ ከሆነ ዛሬውኑ መቀላቀል ትችላላችሁ!
በመቶ የሚቆጠሩ አንባቢያን ተቀላቅለዋል፡፡ እርስዎም ዛሬ ይቀላቀሉ ነገ ማንበብን ይጀምሩ!
ለንባብ የተመረጠው መጽሐፍ - “ቀዩ መስመር”
ንባቡ የሚጀመርበት ቀን - ሰኔ 1 / 2018
ንባቡ የሚጠናቀቅበት ቀን - ሰኔ 30 / 2018
ይህንን Book Club ለመቀላቀል፡- በዚህ 👉 @DrEyobmamo የቴሌግራም አድራሻ (user name) inbox በማድረግ ፍላጎታችሁን ስትገልጹ ሙሉ መረጃ ይላክላችኋል፡፡
Join now!!! | 6 691 |
| 17 | እውቀትን ወደ ተግባር! (ክፍል አንድ)
ሰላም ተከታታዮቼ! ዛሬን ጨምሮ ለአምስት ቀናት፣ “እውቀትን ወደ ተግባር!” በሚል ርእስ ስር ለሕይወታችሁ ጠቃሚ መመሪያዎችን አጋራችኋለሁ፡፡
በማንበብ፣ በስልጠናም ሆነ በመደበኛ ትምህርት አንድን እውቀት ካገኛችሁ በኋላ የሚቀጥለው የቤት ስራችሁ ያንን እውቀት ተግባራዊ ማድረግ ነው፡፡
ያንን ካላደረጋችሁ ሁል ጊዜ ባላችሁበት የምትረግጡና ቀስ በቀስ ወደ ኋላ የምትቀሩ ትሆናላችሁ፡፡
“እውቀት መንገዱን ያሳያል፤ ተግባር ግን እግርን ያንቀሳቅሳል” የሚባለው ለዚህ ነው፡፡
“የምናውቀው ነገር ሌሎችን ያስደንቃል፤ የምንተገብረው ነገር ግን እኛን ወደ ፊት ያራምዳል” የሚባለውም ለዚህ ነው፡፡
1. ተግባር የሌለው እውቀት የሐሰት በራስ መተማመንን ይፈጥራል
አንድ ሰው ምን ማድረግ እንዳለበት እያወቀ ሊወድቅ ይችላል፤ ምክንያቱም ማወቅና ማድረግ አንድ አይደሉም። ለምሳሌ፣ ስለ ውኃ ዋና መጽሐፍትን ያነበበ፣ ነገር ግን ፈጽሞ ውሃ ውስጥ የማይገባ ሰው መዋኘት አይችልም።
ብቃት የሚመጣው ከተግባር እንጂ ከመረጃ አይደለም።ማወቅ ብቻ በቂ አይደለም፤ በተግባር ማዋል አለብን። መመኘት ብቻ በቂ አይደለም፤ ማድረግ አለብን!!!
2. ጥቅም ላይ ያልዋለ እውቀት ቀስ በቀስ ኃይሉን ያጣል
እውቀት ልክ እንደ ጡንቻ ነው። ካልተንቀሳቀሰና ካልተሠራበት ይደክማል። ብዙ ሰዎች በመደበኛ ትምህርት ላይ ይሳተፋሉ፣ መጽሐፍትን ያነባሉ፣ ስልጠናዎችን ይወስዳሉ፤ ነገር ግን የተማሩትን ነገር ፈጽሞ በተግባር አይተረጉሙትም።
ጊዜ እያለፈ ሲሄድ ትምህርቶቹ የራቁ ትውስታዎች ብቻ ሆነው ይቀራሉ። በተግባር ያልተገለጠ ነገር ውሎ አድሮ መረሳቱ አይቀሬ ነው።
3. እውቀት ኃላፊነትን ይጨምራል
ባወቅን ቁጥር፣ ላለመንቀሳቀስ የምንሰጠው ሰበብ እየቀነሰ ይሄዳል። የታማኝነትን፣ የዲሲፕሊንን፣ የአካል ጤና መመሪያዎችን ወይም የዓላማን አስፈላጊነት እያወቀ ነገር ግን ችላ የሚል ሰው በእውቀቱና በተግባሩ መካከል ላለው ክፍተት ተጠያቂ ነው።
እውቀት ስጦታ የመሆኑን ያህል ኃላፊነትም ነው። በአንድ ነገር ላይ ካወቅን በኋላ ማንንም መውቀስ አንችልም፡፡ ሃላፊነቱ የእኛው ነው፡፡
በነገው ፖስቴ አራት ነጥብ የያዘውን ክፍል ሁለት ይዤ እመለሳሁ፡፡
ማሳሰቢያ፡-
ኃሙስ ሰኔ 4/2018 ከምሽቱ 3፡00 እስከ 4፡00 ድረስ በዚሁ የቴሌግራም ቻናሌ Live! የሚሰጠው ስልጠና አያምልጣችሁ፡፡
የስልጠናው ርእስ፡- “ከልጅነት (ካለፈ) 'ትራውማ' / 'trauma' መላቀቅ!”
ወዳጆቻችሁ ይህንን channel join በማድረግ ስልጠናው እንዲካፈሉ ጋብዟቸው፡፡
https://t.me/Dreyob
https://m.youtube.com/user/naeleyob623
https://www.facebook.com/Dr-Eyob-Mamo-1050816404958639/ | 6 310 |
| 18 | እውቀትን ወደ ተግባር! (ክፍል አንድ) | 5 434 |
| 19 | ነገ ሰኔ አንድ ነው!!!
የወሩ reading challenge ነገ ማለዳ ይጀምራል፡፡
በመቶ የሚቆጠሩ አንባቢያን ተቀላቅለዋል፡፡ እርስዎም ዛሬ ይቀላቀሉ ነገ ማንበብን ይጀምሩ!
ለንባብ የተመረጠው መጽሐፍ - “ቀዩ መስመር”
ንባቡ የሚጀመርበት ቀን - ሰኔ 1 / 2018
ንባቡ የሚጠናቀቅበት ቀን - ሰኔ 30 / 2018
ይህንን Book Club ለመቀላቀል፡- በዚህ 👉 @DrEyobmamo የቴሌግራም አድራሻ (user name) inbox በማድረግ ፍላጎታችሁን ስትገልጹ ሙሉ መረጃ ይላክላችኋል፡፡
Join now!!! | 6 779 |
| 20 | ስህተት እና ስኬት!
▶️ የሰዎችን ስህተትና ውድቀት ለትምህርት ተጠቀሙበት እንጂ ለትችት አታውሉት፡፡
▶️ የሰዎችን ስኬት ለመነሳሳት ተጠቀሙበት እንጂ ቅንአት መንፈስ አታስቡት፡፡
▶️ የራሳችሁን ስህተትና እንደ አንድ ክስተት ተመልከቱት እንጂ ከማንነታችሁ ጋር አታነካኩት፡፡
▶️ የራሳችሁን ስኬት ለሚቀጥለው ደረጃ እንደ መሻገሪያ ተጠቀሙበት እንጂ አትኩራሩበት፡፡
መልካም ምሽት!!! | 6 179 |
اکنون در دسترس! پژوهش تلگرام ۲۰۲۵ — مهمترین بینشهای سال 
