Dr. Eyob Mamo
📈 تحلیل کانال تلگرام Dr. Eyob Mamo
کانال Dr. Eyob Mamo (@dreyob) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 79 293 مشترک است و جایگاه 1 976 را در دسته آموزش و رتبه 384 را در منطقه أثيوبيا دارد.
📊 شاخصهای مخاطب و پویایی
از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 79 293 مشترک جذب کرده است.
بر اساس آخرین دادهها در تاریخ 24 ژوئیه, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 35 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر 23 بوده و همچنان دسترسی گستردهای حفظ شده است.
- وضعیت تأیید: تأیید نشده
- نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 10.64% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 5.41% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب میکند.
- دسترسی پستها: هر پست به طور میانگین 8 439 بازدید دریافت میکند. در اولین روز معمولاً 4 286 بازدید جمعآوری میشود.
- واکنشها و تعامل: مخاطبان بهطور فعال حمایت میکنند؛ میانگین واکنش به هر پست 59 است.
📝 توضیح و سیاست محتوایی
نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاههای شخصی توصیف میکند:
“Life skill development!
You can contact me
@DrEyobmamo”
به لطف بهروزرسانیهای پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 25 ژوئیه, 2026)، کانال همواره بهروز و دارای دسترسی بالاست. تحلیلها نشان میدهد مخاطبان بهطور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته آموزش تبدیل کردهاند.
در حال بارگیری داده...
| تاریخ | رشد مشترکین | اشارات | کانالها | |
| 25 ژوئیه | +9 | |||
| 24 ژوئیه | +24 | |||
| 23 ژوئیه | +3 | |||
| 22 ژوئیه | +15 | |||
| 21 ژوئیه | +4 | |||
| 20 ژوئیه | +2 | |||
| 19 ژوئیه | +13 | |||
| 18 ژوئیه | +17 | |||
| 17 ژوئیه | +11 | |||
| 16 ژوئیه | +6 | |||
| 15 ژوئیه | +15 | |||
| 14 ژوئیه | +5 | |||
| 13 ژوئیه | +3 | |||
| 12 ژوئیه | +3 | |||
| 11 ژوئیه | +14 | |||
| 10 ژوئیه | 0 | |||
| 09 ژوئیه | +17 | |||
| 08 ژوئیه | +2 | |||
| 07 ژوئیه | 0 | |||
| 06 ژوئیه | +19 | |||
| 05 ژوئیه | +1 | |||
| 04 ژوئیه | 0 | |||
| 03 ژوئیه | +7 | |||
| 02 ژوئیه | +20 | |||
| 01 ژوئیه | +7 |
| 2 | የማያቋርጥ እድገት ልምምዶች! (ክፍል አምስት)
ዓላማ እና ራእይ (Purpose and Vision) – በዓላማ መኖር
እስካሁን የሚከተሉትን ልምምዶች ተመልክተናል፡ “ራስን ማወቅ”፣ “የግል ሃላፊነት”፣ “ቀጣይነት ያለው ትምህርት” እና “ዲሲፕሊን እና ወጥነት”፡፡
ዛሬ ደግሞ፣ “ዓላማ እና ራእይ” የተሰኘውን የመጨረሻ ክፍል አጋራለሁ፡፡
በዓላማ የሚያድጉ ሰዎች ወዴት አእጣጫ እንደሚሄዱ እና ለምን እንደሚሄዱ ጥርት አድርገው ያውቃሉ። ስለሆነም፣ ከመወላወል እና ተስፋ ከመቁረጥ አጉል ልምምዶች ራሳቸው ያላቀቁ ሰዎች ናቸው፡፡ የዓላማ ሰው የመሆንን ወሳኝ ልምምድ ለማዳበር ደግሞ የሚከተሉት መርሆች አስፈላጊ ናቸው፡፡
1. ለሕይወት ግልጽ የሆነ ራእይ መያዝ
2. ትርጉም ያላቸው ግቦችን ማውጣት
3. ድርጊቶችን ከእሴቶቻችን እና ከመርሆቻችን ጋር ማጣጣም
ዛሬን እና ላለፉት አራት ቀናት፣ “የማያቋርጥ እድገት ልምምዶች” በሚል ርእስ ስር እንደተመለከትነው፣ የጀመርነው የእድገት ሂደት ቀጣይነት እንዲኖረው መለማመድ ከሚገቡን ልምምዶች አንጋፋውና የመጨረሻው፣ “ዓላማን እና ራእይን” የማወቅና የመከተል ጉዳይ ነው፡፡
ይህንን ተከታታይ ሃሳብ ስቋጭ፣ ዓላማን እና ራእይን አስመልክቶ የሚከተሉትን ጥያቄዎች ራሳችሁን በመጠየቅ ወደ ፊት እንድትገሰግሱ አበረታታችኋለሁ፡፡
· ለሕይወቴ ማስረዳት የምችላው ግልጽ የሆነ ራእይ አለኝ?
· ዕለታዊ ተግባሮቼ እና ውሳኔዎቼ ከእሴቶቼ፣ ከመርሆቼ እና ከረጅም ጊዜ ዓላማዬ ጋር የተጣጣሙ ናቸው?
· ዓላማዬን ለመፈጸም በዚህ የሕይወት ምዕራፍ ውስጥ የትኞቹን ትርጉም ያላቸው ግቦች መከታተል አለብኝ?
ተጠናቀቀ!
https://m.youtube.com/user/naeleyob623 | 4 583 |
| 3 | ሶስቱ የሚለቀቁ ነገሮች!
ዛሬ ማታ ከመተኛታችሁ በፊት ለራሳችሁ የውስጥ ሰላምና የስሜት ጤንነት ስትሉ . . .
1. ምንም ብታደርጉ ለመለወጥ በማትችሉት ነገር ላይ ያላችሁን ጭንቀት ልቀቁት!
ያንን ካላደረጋችሁ ለነገ ያላችሁን ጉጉት እና ጉልበታችሁን ያሟጥጥባችኋል፡፡
2. ማድረግ የማይገባቸውን ነገር በማድረገ በጎዷችሁ ሰዎች ላይ የያዛችሁትን ቂም ልቀቁት!
ያንን ካላደረጋችሁ በሰዎቹም ተጎድታችሁ እንደገና በታመቀ ቂምም ተጎድታችሁ ድርብ ቁስል ይሆንባችኋል፡፡
3. ምነው ባላደረግኩት ወይም ምነው ባደረኩት በሚል ስሜት ያለባችሁን የውስጥ ጸጸት ልቀቁት!
ያንን ካላደረጋችሁት የራስ መተማመናችሁን ስለሚነካው ቀና ብላችሁ ለመኖር ስቸግራችኋል፡፡
መልካም አዳር! | 5 171 |
| 4 | የማያቋርጥ እድገት ልምምዶች! (ክፍል አራት)
ዲሲፕሊን እና ወጥነት (Discipline and Consistency) – ዕለታዊ ልማዶችን መለማመድ
በሕይወታችን የማያቋርጥ እድገት ውስጥ ለመግባት ከፈለግን ልናዳብር ከሚገቡን ልምምዶች አምስቶቹን ላጋራችሁ ብዬ፣ ባለፉት ሶስት ቀናት “ራስን ማወቅ”፣ “የግል ሃላፊነት” እና “ቀጣይነት ያለው ትምህርት” የተሰኙ ሃሳቦች አጋርቻለሁ፡፡
ዛሬ ደግሞ፣ “ዲሲፕሊን እና ወጥነት” የተሰኘውን አጋራለሁ፡፡
ሕይወታችን በቀጣይነት እንዲያድግ ከፈለግን ዲሲፕሊን እና ወጥነት ችላ ሊባሉ የማገባቸው ልምምዶች ናቸው፡፡ ዲሲፕሊን ከሌለን የተለያዩ ነገሮችን እንጀምራለን፣ ነገር ግን አንቀጥላቸውም፡፡ ይህንን ወሳኝ ልምምድ ለማዳበር ደግሞ የሚከተሉት መርሆች አስፈላጊ ናቸው፡፡
1. ከዓላማችን አንጻር ጠቃሚ የሆኑ ልማዶችን ማዳበር
2. ጊዜያችንን በጥበብ መጠቀም
3. በትናንሽ ነገሮች ላይ ታማኝ መሆን
የጀመርነው የእድገት ከአንዱ ደረጃ ወደ ሌላኛው ደረጃ እደገ እንዲሄድ ከፈለግን የጸና ዲሲፕሊን እና ወጥነት ያለው ልምምድ ያስፈልገናል፡፡ ነገሮችን እየጀመርን የምናቆምና በምኞት ብቻ የምንኖር ከሆነ እድገታችን ይገታል፡፡
በነገው ፖስቴ ክፍል አምስትን ይዤ እመለሳለሁ፡፡ እሰከዚያው ድረስ የሚከተሉትን ጥያቄዎች ራሳችሁን በመጠየቅ ሃላፊነትን የመውሰድ ልምምድን ለማዳበር ሞክሩ፡፡
· እያደግኩ እንድሄድ የሚረዱኝና አድገቴን የሚከለክሉ ዕለታዊ ልማዶቼ ምንድን ናቸው?
· ጊዜዬን በታቀደ መንገድ እየተጠቀምኩ ነው ወይስ ትኩረትን በሚከፋፍሉ ነገሮች እየተወሰድኩኝ ነው?
· ጀመርኳቸው እንጂ መጨረስ ያልቻልኳቸው አስፈላጊ ነገሮች ምንድን ናቸው?
ይቀጥላል . . . | 6 462 |
| 5 | የጸጸታችን ምንጮች ብዙ ናቸው!
• አንድን ውሳኔ በመወሰናችን ወይም ባለመወሰናችን ምክንያት ያመለጠንን እድል በማሰብ እንጸጸታለን፡፡ “ምነው በቶሎ በወሰንኩኝ ኖሮ … ምነው ከውሳኔ በዘገየሁ ኖሮ” …
• አንድን የምንወደውን ሰው ከዛሬ ነገ እንጠይቃለን በማለት ስንወላውል በድንገት ሳናገኘው በመሞቱ እንጸጸታለን፡፡ “ምነው ጠይቄው በሆነ ኖሮ … ምነው አግዤው በሆነ ኖሮ” …
• የማይሆን የፍቅር ሕይወት ውስጥ በመግባታችን ምክንያት በደረሰብን ጉዳት እንጸጸታለን፡፡ “ምነው ከዚህ ሰው ጓደኝነት ባልጀመርኩኝ ኖሮ … ምነው ምርጫዬን ባስተካከልኩ ኖሮ” …
• ሰውን አምነን ከእጃችን ገንዘብ በማውጣታችን ምክንያት በደረሰብን የክህደት ሁኔታ እንጸጸታለን፡፡ “ምነው እምቢ ባልኩኝ ኖሮ … ምነው ባላመንኩት ኖሮ” …
• በማይረባ ምክንያት ከወዳጆቻችን ጋር በመጣላታችን ምክንያት እንጸጸታለን፡፡ “ምነው በታገስኩት ኖሮ … ምነው ነገሩን ቀለል አድርጌ በያዝኩት ኖሮ” …
• በሰዎች የግል ውሳኔ ገብተንናሰዎቹን ለአንድ ተግባር ገፋፍተናቸው በሰዎቹ ላይ በደረሰው አስከፊ ሁኔታ ምክንያት እንጸጸታለን፡፡ “ምነው አርፌ በተቀመትኩኝ ኖሮ … ምነው ሰውየው የራሱን ውሳኔ እንዲወስን በተውኩት ኖሮ” …
የነሃሴ ወር የንባብ challenge በዚህ ወሳኝ ስሜት ዙሪያ ሰፊ ግንዛቤ ይሰጣችኋልና ከአሁኑ ተመዝገቡ፡፡
የንባብ ወር - ነሃሴ / 2018
ለንባብ የተመረጠው መጽሐፍ - “የሕይወት ጸጸቶች”
ንባቡ የሚጀመርበት ቀን - ነሃሴ 1 / 2018
ንባቡ የሚጠናቀቅበት ቀን - ነሃሴ 30 / 2018
ይህንን Book Club ለመቀላቀል፡- በዚህ 👉 @DrEyobmamo የቴሌግራም አድራሻ (user name) inbox በማድረግ ፍላጎታችሁን ስትገልጹ ሙሉ መረጃ ይላክላችኋል፡፡
Join now!!! | 6 687 |
| 6 | የማያቋርጥ እድገት ልምምዶች! (ክፍል ሶስት)
ቀጣይነት ያለው ትምህርት (Continuous Learning) – ለማደግ መወሰን
በሕይወታችን የማያቋርጥ እድገት ውስጥ ለመግባት ከፈለግን ልናዳብር ከሚገቡን ልምምዶች አምስቶቹን ላጋራችሁ ብዬ፣ ባለፉት ሁለት ቀናት “ራስን ማወቅ” እና “የግል ሃላፊነት” የተሰኙ ሃሳቦችን አጋርቻለሁ፡፡
ዛሬ ደግሞ፣ “ቀጣይነት ያለው ትምህርት” የተሰኘውን አጋራለሁ፡፡
ሕወታችን በቀጣይነት እንዲያድግ የግድ ቀጣይ የሆነ ትምህርት የምንማር ሰዎች መሆን አስፈላጊ ነው፡፡ ትምህርት ደግሞ እድሜ ልካችንን የሚቀጥል ሊሆን ይገባዋል፡፡ ይህንን ወሳኝ ልምምድ ለማዳበር ደግሞ የሚከተሉት መርሆች አስፈላጊ ናቸው፡፡
1. ያለማቋረጥ ማንበብ፣ መማር እና መሰልጠን
2. አማካሪዎችን መፈለግ እና የእነሱን ግብረ-መልስ (feedback) መስማት
3. በየጊዜው የሚገጥሙንን ውድቀቶች ወደ ትምህርት መቀየር
የጀመርነው የእድገት ጉዞ እስከመጨረሻው እንዲዘልቅ ከፈለግን በየእለቱ የምንማር ሰዎች መሆን አስፈላጊ ነው፡፡ መማር ያቆመ ሰው ማደግ ያቆመ ሰው እንደሆነ በማስታወስ ከሁሉም ነገር፣ ሁል ጊዜ እንማር፡፡
በነገው ፖስቴ ክፍል አራትን ይዤ እመለሳለሁ፡፡ እሰከዚያው ድረስ የሚከተሉትን ጥያቄዎች ራሳችሁን በመጠየቅ ሃላፊነትን የመውሰድ ልምምድን ለማዳበር ሞክሩ፡፡
· የተሻለ ሰው እንድሆን የሚረዱኝ ነገሮች ምንድን ናቸው?
· በሽንፈት ጊዜ ተስፋ እቆርጣለሁ ወይስ እንደ መማሪያ እና ማደጊያ እድል እጠቀመዋለሁ?
· ሊያሳድጉኝ የሚችሉ አማካሪዎች፣ መምህራን ወይም ሰዎች እነማን ናቸው?
ነገ ይቀጥላል . . .
https://m.youtube.com/user/naeleyob623
https://www.facebook.com/Dr-Eyob-Mamo-1050816404958639/ | 6 597 |
| 7 | Book Reading Challenge with Dr. Eyob
ለነሃሴ ወር reading challenge የተመረጠው መጽሐፍ፣ “የሕይወት ጸጸቶች” የተሰኘው ነው፡፡
"ካለፈው መማር፣ ዛሬን ማጣጣምና ለነገ ማቀድ!"
ከአሁኑ በመመዝገብ ራሳችሁን አዘጋጁ!
በእያንዳንዱ የሕይወት ምእራፋችን ውስጥ የምናደርጋቸው ምርጫና ውሳኔዎች ውስጥ ነገ የምንጸጸትባቸው ሁኔታዎች አሉ፡፡
ይህ ሁኔታ የማይቀር የሕይወት ሂደት ነው፡፡
ጸጸትን በትክክለኛው መንገድ ከተጠቀምንበት ለእድገት ይሆንልናል፡፡ ካልተጠቀምንበት ግን እድገታችንን ይገታዋል፡፡
በሕይወታችን የምንደብቃቸው ነገሮችና የምንጸጸትባቸው ሁኔታዎች በበዙ ቁጥር የውስጥ ስቃያችን እየጨመረ እንደሚሄድ አንዘንጋ፡፡
ይህ መጽሐፍ፡-
📖 የጸጸትን ትርጉም በትኖ ያሳየናል፡፡
📖 በየእድሜው የሚመጡ የጸጸት አይነቶችን ያብራራልናል፡፡
📖 ከጸጸት የመውጫውንም መንገድ ይጠቁመናል፡፡
📖 ከብዙ ሰዎችም የግል ልምምድ በመነሳት ተግባራዊ መመሪያዎችን ያካፍለናል፡፡
መጽሐፉን ለማንበብ ከአሁኑ በመመዝገብ ራሳችሁን አዘጋጁ፡፡
የንባብ ወር - ነሃሴ / 2018
ለንባብ የተመረጠው መጽሐፍ - “የሕይወት ጸጸቶች”
ንባቡ የሚጀመርበት ቀን - ነሃሴ 1 / 2018
ንባቡ የሚጠናቀቅበት ቀን - ነሃሴ 30 / 2018
ይህንን Book Club ለመቀላቀል፡- በዚህ 👉 @DrEyobmamo የቴሌግራም አድራሻ (user name) inbox በማድረግ ፍላጎታችሁን ስትገልጹ ሙሉ መረጃ ይላክላችኋል፡፡
Join now!!! | 6 821 |
| 8 | የማያቋርጥ እድገት ልምምዶች! (ክፍል ሁለት)
የግል ኃላፊነት (Personal Responsibility) – ኃላፊነትን መውሰድ
በሕይወታችን የማያቋርጥ እድገት ውስጥ ለመግባት ከፈለግን ልናዳብር ከሚገቡን ልምምዶች አምስቶቹን ላጋራችሁ ብዬ፣ ባለፈው ፖስቴ “ራስን ማወቅ” የሚለውን ሃሳብ አጋርቻለሁ፡፡ ዛሬ ደግሞ፣ “የግል ኃላፊነት” የተሰኘውን አጋራለሁ፡፡
እድገታችን ቀጣይነት የሚኖረው በሁኔታዎች ላይ ማማረርን ስናቆም እና ለምርጫዎቻችን፣ ለስሜቶቻችን እና ለድርጊቶቻችን ሙሉ ኃላፊነት ስንወስድ ነው። ይህንን ወሳኝ ልምምድ ለማዳበር ደግሞ የሚከተሉት መርሆች አስፈላጊ ናቸው፡፡
1. ለስህተቶቻችን ሙሉ ኃላፊነትን መውሰድና መቀበል
2. ለማንኛውም ተግባራችንም ሆነ ባህሪያችን ተጠያቂ መሆን
3. መቆጣጠር በማንችላቸው ነገሮች ላይ ሳይሆን መቆጣጠር በምንችላቸው ነገሮች ላይ ማተኮር
የጀመርነው የእድገት ጉዞ ቀጣይነት እንዲኖረው ከፈለግን በሕወታችን ለሚከናወኑት ነገሮች በሙሉ የሚወቀስ ሰው ከመፈለግ ይልቅ ሙሉውን ሃላፊነት እኛው ስንወስድ ነው፡፡
በነገው ፖስቴ ክፍል ሶስትን ይዤ እመለሳለሁ፡፡ እሰከዚያው ድረስ የሚከተሉትን ጥያቄዎች ራሳችሁን በመጠየቅ ሃላፊነትን የመውሰድ ልምምድን ለማዳበር ሞክሩ፡፡
· በሕይወቴ በየትኞቹ ዘርፎች ነው ኃላፊነቱን እኔ ከመውሰድ ይልቅ ሁኔታዎችን ወይም ሌሎችን ሰዎችን የምወቅሰው?
· ሊታወቁ እና ሆን ተብሎ ሊለወጡ የሚገባቸው ምን ዓይነት ስህተቶች ወይም ጤናማ ያልሆኑ ባህሪያት አሉብኝ?
· እየተጠቀምኩ ያለሁት ጉልበት ልቆጣጠራቸው በማልችላቸው ነገሮች ላይ በመጨነቅ ነው፣ ወይስ ተጽዕኖ መፍጠር እና ማሻሻል በምችላቸው ነገሮች ላይ ነው?
ነገ ይቀጥላል . . . | 6 444 |
| 9 | የማያቋርጥ እድገት ልምምዶች! (ክፍል አንድ)
በሕይወታችን የማያቋርጥ እድገት ውስጥ ለመግባት ከፈለግን ልናዳብር ከሚገቡን ልምምዶች አምስቶቹን ላጋራችሁ፡፡
ራስን ማወቅ (Self-Awareness) – ራስን መረዳት
የማያቋርት እድገት የሚጀምረው የራስን ጥንካሬዎች፣ ድክመቶች፣ እሴቶች፣ ስሜቶች እና መነሳሳቶች በመረዳት ነው። እነዚህን ነገሮች ለመረዳት ደግሞ የሚከተሉት ልምምዶች የግድ ናቸው፡፡
1. የሕይወታችንን ዓላማ መለየት እና እሱ ላይ መቆየት
2. ሁል ጊዜ ራሳችንን መፈተሽ (Self-reflection)
3. መሻሻል ያለባቸውን ክፍተቶች በመለየት ማሻሻል
እድገት የሚጀምረው በጽኑ ፍላጎትና በውሳኔ ቢሆንም፣ የሚቀጥለውና ዘላቂ የሚሆነው ግን በዓላማችን ላይ በመቆየት፣ ራስን በመፈተሽ እና የማያቋርጥ መሻሻል በማድረግ ነው፡፡
በነገው ፖስቴ ክፍል ሁለትን ይዤ እመለሳለሁ፡፡ እሰከዚያው ድረስ የሚከተሉትን ጥያቄዎች ራሳችሁን በመጠየቅ ራስን የማወቅ ልምምድን ለማዳበር ሞክሩ፡፡
· በዓላማ እየኖርኩ ነው ወይስ ሕይወት በሚያመጣው ሁኔታ እየተገፋሁ ብቻ ነው የምኖረው?
· ቅን የሆነ ራስን መመርመር ስላስወገድኩ ብቻ ሳይለወጡ የቀሩ የሕይወቴ ክፍሎች የትኞቹ ናቸው?
· ከሌሎች ሰዎች በተደጋጋሚ እንዳርም የምቀበለው አስተያየት ምንድን ነው?
ነገ ይቀጥላል . . .
https://t.me/Dreyob
https://m.youtube.com/user/naeleyob623
https://www.facebook.com/Dr-Eyob-Mamo-1050816404958639/ | 8 458 |
| 10 | የዶ/ር ኢዮብን መጽሐፍት የቴሌግራም የንባባ challenge በመቀላቀል ማንበብ እንደምትችሉ ታውቃላችሁ?
እስካሁን የተነበቡ መጽሐፍት ዝርዝር ከዚህ በታች ተጠቅሰዋል፡፡
ከተጠቀሱት መካከል ያላነበባችሁትን መጽሐፍ በመምረጥና መስፈርቱን በማሟላት ግሩፑን መቀላቀልና በሚመቻችሁ ጊዜ ማንበብ ትችላላችሁ፡፡
በዚህ 👉 @DrEyobmamo የቴሌግራም አድራሻ (user name) inbox በማድረግ ፍላጎታችሁን ስትገልጹ ሙሉ መረጃ ይላክላችኋል፡፡
==========
1. “አመራር A to Z”፡- በሕይወትህ የአመራርን ጥበብ ካላዳበርክ የትም አትደርስም፡፡ ራስህን፣ ቤተሰብህን፣ ስራህንና ንግድህን ለመምራትም ሆነ ሕይወትህን በተዋቀረ መልክ ወደፊት ለማራመድ መሰረታዊ የአመራር ግንዛቤ ያስፈልግሃል፡፡ ይህ መጽሐፍ ከአመራር መሰረታዊ ትርጉም በመነሳት የተለያዩ የአመራር ጥበቦችን ማንም ሊገነዘበው በሚችለው መንገድ ያስተምርሃል፡፡
2. “የጊዜ አጠቃቀም ጥበብ”፡- ምንም ነገር ብትከስር መጨረሻ ላይ የምትከፍለው በጊዜህ ነው፡፡ የስልጣኔ ሁሉ ስልጣኔ ጊዜን በተገቢው መንገድ የመጠቀም ስልጣኔ ነው፡፡ በሕይወትህ እቅድ የሞላው ኑሮ ለመኖርም ሆነ ማንኛውንም ተግባርህን በወቅቱና በተዋጣለት ሁኔታ ለማከናወን ከፈለክ የጊዜ አጠቃቀምን መሰረታዊ እውነታዎች ከዚህ መጽሐፍ የማግኘት ምርጫ አለህ፡፡
3. “የስሜት ብልህነት”፡- በሕይወትህ ምንም አይነት የአእምሮ እውቀት ቢኖርህም በስሜት ብልህነትና ብቃት እስክትበስል ድረስ 80 በመቶውን የስኬት ምንጭ እንዳጣህ አትዘንጋ፡፡ የብዙ ስኬቶቻችን ምንጭ መነሻው ከጤናማ ስሜት ነው፡፡ የብዙ ውድቀታችን ምክንያትም ቢሆን መንስኤው ስሜትን በተገቢው ቦታ፣ መንገድና መጠን አለመግለጥ ነው፡፡ ይህንን ምስጢር በሚገባ ለማወቅ መጽሐፉ የግድ ነው፡፡
4. “የአለማችን አስቸጋሪ ሰዎች”፡- በሕይወትህ ከአስቸጋሪ ሰዎች በፍጹም ማምለጥ አትችልም፡፡ እኔና አንተም ብንሆን ለሌላው ሰው የሚያስቸግር ባህሪይ እንደሚኖረን አይካድም፡፡ ሰዎችን አያያዝ ሁኔታዊ ስለሆነ፣ እንዳለህ የቅርበት ሁኔታ ጥበብን ማዳበርን ይጠይቃል፡፡ በዚህ መጽሐፍ ውስጥ በጣም የተለመዱ የአስቸጋሪ ሰዎች ባህሪይና እንዴት በጥበብ ልትይዛቸው እንደምትችል በሚገባ ትማራለህ፡፡
5. “ምርጫና ውሳኔ”፡- የትናንት ምርጫህን ዛሬ እየኖርክ ነው፡፡ የዛሬ ምርጫህን ደግሞ ነገ ትኖረዋለህ፡፡ ሆኖም፣ አንዳንድ ጊዜ የሌሎች ምርጫዎች ወደ አንተ አልፈው የሚመጡበትም ጊዜ አለ፡፡ ለዚያም ቢሆን የምትሰጠውን ምላሽ የመለየትና የመምረጥ አቅሙ አለህ፡፡ ስለምርጫና ውሳኔ ትርጉም፣ ተጽእኖና ስለ ትክክለኛ ምርጫ ምስጢር ለመገንዘብ ወደ መጽሐፉ ጎራ በልና አንብበው፡፡
6. “ጀምሮ መጨረስ”፡- ሕይወት ጀምሮ የመጨረስ ሂደት ነች፡፡ የዚህች ሕይወት ጥራትና ስኬት የሚለካው ደግሞ በየጊዜው ጀምረን በብቃት በምንጨርሳቸው ነገሮች ነው፡፡ በትምህርት ዓለም፣ በፍቅርና በቤተሰብ ዓለም፣ በስራው ዓለምና በአጠቃላይ በራእያችንና በግቦቻችን ሂደት ውስጥ አንድን ነገር የመጀመር፣ የመቀጠልና በብቃት የመጨረስ ተግባራዊ መመሪያዎች ጥርት ባለ መልኩ ቀርበዋል፡፡
7. “ቀዩ መስመር”፡- በማንኛውም ማሕበራዊ ዘርፍ በሚኖረን የሰው-ለሰው ግንኙነት ውስጥ ሰዎቹ በእኛ ሕይወት የሚፈቀድላቸውንና የማይፈቀድላቸውን ነገር የመለየትና የቀይ መስመር (Boundary) ማስመር ወሳኝ ነው፡፡ የቀይ መስመራችንን ማስመርና ማስከበር ለጤናማ ማሕበራዊ ሕይወት ወሳኝ በመሆኑ፣ ብልሃቱንና አቅሙን የምናሳድግበትን መመሪያዎች በዚህ መጽሐፍ ገጾች ውስጥ እናገኛለን፡፡
8. “ራእይን ማወቅና መኖር”፡- የስኬት መስመር ውስጥ ለመግባት የፈለገ ማንኛውም ሰው ሕይወትን ከትናንትና ታሪኩ ወይም ከወቅቱ ሁኔታው በመነሳት ከተረጎማት ቀስ በቀስ ጊዜውን ማባከኑ፣ ስኬተ-ቢስ መሆኑና ተስፋ መቁረጡ ጥርጥር የለውም፡፡ ሕይወት ግን መጀመር ያለባት ከነገው ራእይ ነው፡፡ የራእይን ትርጉም፣ እንዴት ራእያችንን እንደምናውቅና እንደምንኖር በዚህ መጽሐፍ ገጾች ውስጥ እናገኛለን፡፡
9. “የመኖር አቅም”፡- በሕወታችን የሚገጥሙን የመኖር አቅምን የሚያሳጡ አስቸጋሪ ሁኔታዎች፣ በአንድ በኩል ከራሳችን ጋር ያለንን ግንኙነት ሲነኩ፣ በሌላ በኩል ደግሞ ከሰዎች ጋር ካለንን ግንኙነት ጋር ይነካካሉ፡፡ ይህ መጽሐፍ ባሉን የራስ-በራስ እና የሰው-ለሰው የግንኙነት ዘርፎች ዙሪያ አቅም አሳጪ ሁኔታዎች እንድንለይ አቅጣጫ ያሳየናል፡፡ በተጨማሪም፣ ተገቢውን ምላሽ በመስጠት በብርታት ለማለፍ እንድንችል ዘመን-ዘለል መመሪያዎች እናገኛለን፡፡ | 9 546 |
| 11 | አታምታቱ!
1. ይቅርታ እና አብሮነት
አንድ ሰው ሆን ብሎ እና ደጋግሞ የሚያጠፋችሁ ከሆነና ይቅርታ የሚጠይቃችሁ ከሆነ፣ ይቅርታውን ተቀበሉና ይቅር በሉት፡፡ ነገር ግን ይቅርታን እና አብሮነትን አታምታቱ፡፡ ሰዎችን ይቅር ብላችሁ በአብሮነት ግን ያለመቀጠልን ጥበብ ማዳበር ትችላላችሁ፡፡ ሁለቱ የተለያዩ ነገሮች ናቸው፡፡
ሰዎች ምንም ያህል ሆን ብለው ደጋግመው ቢያጠፉኝም ይቅር ብዬ አብሮነቴን መቀጠል እፈልጋለሁ ካላችሁ ደግሞ ደጋግማችሁ ለመጎዳት ራሳችሁን ማዘጋጀት የግድ ነው፡፡
2. አጋርነት እና ወዳጅነት
አጋርነትን እና ወዳጅነትን አታምታቱ፡፡ ከሰዎች ጋር በአጋርነት እየሰራችሁ የግድ ወዳጅ መሆን የለባችሁም፡፡ ሁለቱ የተለያዩ ነገሮች ናቸው፡፡
ከአንድ ሰው የስራ አጋር ሆናችሁ ጓደኛ ላትሆኑ ትችላላችሁ፡፡ በተመሳሳይ ሁኔታ ከአንድ ሰው ጋር የቅርብ ጓደኛ ሆናችሁ በምንም አይነት የስራ ዘርፍ አጋር ያለመሆንን ነጻነት ልትጠብቁ ትችላላችሁ፡፡ ያንንም በማድረጋችሁ ምንም ጥፋተኝነት ሊሰማችሁ አገባም፡፡
ከወዳጆቼ ሁሉ ጋር የስራ አጋር መሆን እፈልጋለሁ ካላችሁ ደግሞ በስራ አጋርነት ምክንያት ወዳጅነታችሁን የመሰዋት ሁኔታ ሲከሰት ለዚያ ሁኔታ ራሳችሁን አዘጋጁ፡፡
3. መግባባትን እና የቀይ መስመር
መግባባትን እና ቀይ መስመርን አታምታቱ፡፡ ከአንድ ሰው ጋር በጣም ተግባባችሁ ማለት መከበር ያለበት የቀይ መስመር የላችሁም ማለት አይደለም፡፡ ሁለቱ የተለያዩ ነገሮች ናቸው፡፡
ከሰዎች ጋር እጅግ ተግባብታችሁ ሳለ፣ እንዲከበርላችሁ የምትፈልጉት ወሰን ሊኖራችሁ ይችላል፡፡ መግባባት አንደኛችን ለሌላኛው ያለን አመለካከት ጉዳይ ነው፡፡ የቀይ መስመር ወሰን ግን የሚፈቀደውና የማይፈቀደው የሚለይበት ገደብ ነው። አንድ ሰው ከቀረበኝ ምንም አይነት የቀይ መስመር ማስመር አልፈልግም ካላችሁ ደግሞ፣ የስሜት፣ የጊዜ፣ የቁሳቁስና የመሳሰሉት ክስረቶችን ለማስተናግድ ተዘጋጁ፡፡
የመርህ ሰው መሆን ማለት ክፉ መሆን ማለት አይደለም!
ይህንን እውነት ስትለማመዱ በማንም ሰው ሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ ሰላምና ውስጥ መረጋጋት ታገኛላችሁ፡፡
https://t.me/Dreyob
https://m.youtube.com/user/naeleyob623
https://www.facebook.com/Dr-Eyob-Mamo-1050816404958639/ | 9 214 |
| 12 | አታምታቱ! | 8 294 |
| 13 | ጥያቄ፡-
ዶ/ር ብዙ ጊዜ ኢጎ (Ego) ሲባል እሰማለሁ፣ ትርጉሙ ግን አይገባኝም፡፡ እባክህ በአጭሩ አስረዳኝ፡፡
መልስ፡-
ኢጎ (Ego) ማለት በቀላሉ ሲተረጎም የ"እኔነት" ስሜት ነው። ራሳችንን እንዴት እንደምንመለከት እና ከሌሎች ጋር ያለንን ግንኙነት እንዴት እንደምንመራ ይወስናል።
ኢጎ ብዙውን ጊዜ ከመጠን ያለፈ የራስን አስፈላጊነት ወይም ትዕቢትን ያመለክታል።
ምሳሌ፦ "እሱ ትልቅ ኢጎ አለው" ሲባል ስለ ራሱ በጣም ከፍ ያለ ግምት አለው ማለት ነው።
ይህንን በቀላል መንገድ ለመረዳት፦
♦️ ጤናማ ኢጎ፦ በራስ የመተማመን ስሜትን፣ ለራስ ክብር መስጠትን እና የተረጋጋ ማንነትን ይሰጠናል።
♦️ ጤናማ ያልሆነ ኢጎ፦ ሁልጊዜ ማረጋገጫ (validation) እንድንፈልግ፣ ራሳችንን ከሌሎች ጋር እንድናወዳድር ወይም ትችት ሲቀርብብን አጸፋውን ሳንመልስ እንዳናርፍ ያደርገናል፡፡
ለምሳሌ፣ አንድ ሰው ስራችንን ቢተች፦
♦️ ጤናማ ኢጎ ካለን፦ "ምናልባት ከዚህ ትምህርት ልወስድ እችላለሁ" ብለን እናስባለን።
♦️ ጤናማ ያልሆነ ኢጎ ካለን፦ "እንዴት ቢደፍረን ነው እኔን የሚተቸው!" ብለን እናስባለን።
በማጠቃለያም፣ ኢጎ ራሱ "መጥፎ" አይደለም። በዚህ ዓለም ውስጥ ለመንቀሳቀስ የራስ ስሜት ያስፈልገናል።
ችግሮች የሚፈጠሩት ኢጎአችን የተጋነነ ሲሆን ወይም ሁልጊዜ ትክክል ለመሆን፣ የበላይ ለመሆን ወይም ነገሮችን ለመቆጣጠር ባለን ፍላጎት ከመጠን በላይ ስንጠመድ ነው።
https://t.me/Dreyob
https://m.youtube.com/user/naeleyob623
https://www.facebook.com/Dr-Eyob-Mamo-1050816404958639/ | 12 490 |
| 14 | ስልታዊ ማፈግፈግ (Strategic Retreat)
ስልታዊ ማፈግፈግ (Strategic Retreat) ማለት አንድን የጀመርነውን ነገር ርግፍ አድርጎ መተው ማለት አይደለም። ለወደፊት በብቃት ለመንቀሳቀስ ሲባል ለተወሰነ ጊዜ በብልሃት ወደ ኋላ ማፈግፈግ ማለት ነው።
በህይወት ውስጥ አንዳንዴ ለማሸነፍ ምርጡ መንገድ ወደ ፊት መግፋቱን መቀጠል ሳይሆን፤ ቆም ብሎ ማሰብ፣ ሁኔታዎችን መገምገም፣ ከተጎዳንበት ነገር ማገገም እና እራስን እንደገና ማዘጋጀት ነው።
ስልታዊ ማፈግፈግ ማለት ጥንካሬን ለመጠበቅ፣ ግልጽነት ለማግኘት እና ለወደፊት ለተሻለ ውጤታማነት ለመዘጋጀት ሆን ተብሎ የሚወሰን ጊዜያዊ ዝምታ፣ ከነገሮች ዘወር የማለት፣ የመውጣት፣ የመቆም ወይም አቅጣጫን የመቀየር ውሳኔ ነው።
ይህ ማለት፦
☑️ ማቋረጥ ሳይሆን፣ መስተካከል (recalibrating) ነው።
☑️ ፍርሃት ሳይሆን፣ ጥበብ ነው።
☑️ መሸነፍ ሳይሆን፣ ለተሻለ የላቀ ግስጋሴ መዘጋጀት ነው።
"አንዳንዴ ትልቁን ስእል ለማየት ወደ ኋላ ማፈግፈግ ያስፈልጋል" እንደሚባለው ማለት ነው፡፡
መቼ ነው ስልታዊ ማፈግፈግን ማሰብ ያለብን?
1. ወደ ፊት መቀጠል አላስፈላጊ ጉዳት ሲያስከትል
አንዳንድ ጊዜ ሁኔታው ውስጥ መቆየት የስሜትን ወይም የአካልን ጥንካሬን ሲያሟጥጥ መለስ ማለት ጥሩ ነው።
2. ግልጽነት እና አቅጣጫ ሲፈልጉ
አንዳንድ ጊዜ ህይወት ግራ ሲያጋባን፣ “ትክክለኛ አቅጣጫ ላይ ነኝ? ብሎ ለመጠየቅ ማፈግፈግ አስፈላጊ ነው፡፡
3. ዝለት (Burnout) ሲሰማን
አንዳንድ ጊዜ ብዙ ለፍተን ጥቂት ስናገኝ፣ ከመሯሯጣችን የተነሳ ውስታችን ሲደክም መረጋጋት ያስፈልጋል፡፡
4. መርዛማ (Toxic) ሰዎች ሲበዙብን
አንዳንድ ጊዜ በዙሪያችን ያሉ ሰዎች ከትቅማቸው ጉዳታቸው ሲበዛና ጤና-ቢስ የሆነ ሃሳብና ተግባራቸው ሲበዛ ዘወር ማለት የግድ ነው፡፡
5. ለታላቅ እድል ለመዘጋጀት
አንዳንድ ጊዜ እስካሁን በሰራነው ስራ፣ በሄድንበት መንገድና በድግግሞሹ የሕወት ለውጥና እድገት ካላገኘት ራሳችን ለማሻሻል የትኩረት ለውጥ ማድረግ ወሳኝ ነው፡፡
በስልታዊ ማፈግፈግ ወቅት ምን ማድረግ አለብን?
ስልታዊ ማፈግፈግ ስናደርግ ከከባድ ሁኔታዎች በማምለጥ ዝም ብለን ገለል ማለት ሳይሆን የሚከተሉትን ልምምዶች ማዳበር ማለት ነው፡፡
ማሰላሰል (Reflect): ምን ትምህርት ተምሬያለሁ?
ማገገም (Recover): አካላዊ፣ ስሜታዊ እና መንፈሳዊ ጥንካሬን መመለስ።
እንደገና መገምገም (Reevaluate): ምን መቀጠል አለበት? ምን ማቆም አለበት?
ቦታ መቀየር (Reposition): ቀጣዩ ስራዬ ወይም እድሌ የት ነው?
እንደገና መገንባት (Rebuild): አዳዲስ ልማዶችን፣ ስርዓቶችን እና አመለካከቶችን ማዳበር።
አንዳንዴ ጥንካሬ የሚገኘው ዝም ብሎ ወደ ፊት በመገስገስ ሳይሆን መቼ ወደ ኋላ ማፈግፈግ እንዳለብን በማወቅ፣ መረጋጋት፣ ጸሎት ማድረግ፣ አመለካከትን በማስተካከል እና ለቀጣዩ የህይወት ምዕራፍ በመዘጋጀት ነው።
https://t.me/Dreyob
https://m.youtube.com/user/naeleyob623
https://www.facebook.com/Dr-Eyob-Mamo-1050816404958639/ | 11 583 |
| 15 | ስልታዊ ማፈግፈግ (Strategic Retreat) | 9 699 |
| 16 | ሕይወት ይቀጥላል!
እንኳን አሁን ከምታልፉበት አስቸጋሪ ሁኔታ አይደለም፤ ከሞት በኋላ እንኳን ሕይወት አለ።
አንዳንድ ጊዜ ያለንበት ሁኔታ ሁሉም ነገር ያበቃ ያስመስለናል። ነገር ግን ሕይወት እጅግ ከዚያ የበለጠ ነው። ዛሬ የሚያስለቅሰን ነገር ነገ የምንማርበት ትምህርት ሊሆን ይችላል፤ ዛሬ የተዘጋ የሚመስለው በር ነገ ወደ ተሻለ እድል የሚመራ መንገድ ሊሆን ይችላል።
ከክስረት በኋላ ሕይወት አለ።
የገንዘብ ኪሳራ፣ የንግድ መውደቅ ወይም የእቅድ መፈራረስ የሕይወት መጨረሻ አይደለም። ብዙ ሰዎች ከከባድ ኪሳራ በኋላ እንደገና ተነስተው ተሻለ ሕይወት ገንብተዋል። ክስረት መጨረሻ ሳይሆን አዲስ ጅማሮ ሊሆን ይችላል።
ከፍቅረኛ መለየት በኋላ ሕይወት አለ።
አንድ ግንኙነት ሲያበቃ ልብ በጣም ሊሰበር ይችላል። የወደድነውን ሰው ማጣት እንደ ዓለም መፍረስ ሊሰማን ይችላል። ነገር ግን ሕይወት አይቆምም። እንደገና መሳቅ፣ መውደድ እና ተስፋ ማግኘት ይቻላል።
ስራ ከማጣት በኋላ ሕይወት አለ።
ስራችን የማንነታችን አንድ ክፍል ቢሆንም ሙሉ ማንነታችን አይደለም። ስራ ማጣት ከባድ ሊሆን ይችላል፣ ግን አዲስ አቅጣጫ፣ አዲስ ክህሎት እና አዲስ እድል የሚጀምርበት ጊዜም ሊሆን ይችላል።
ከውድቀት በኋላ ሕይወት አለ።
ማንም ሰው ሳይወድቅ አይማርም፤ ሳይሳሳትም አይበስልም። ውድቀት የሕይወት መጨረሻ ሳይሆን የሚያስተምረን እና የሚያጠናክረን ሂደት ነው። ዛሬ የወደቃችሁበት ቦታ ነገ የምትነሱበት ቦታ ሊሆን ይችላል። ታላላቅ ሰዎች ብዙ ጊዜ ከብዙ ውድቀቶች በኋላ ነው ወደ ስኬት የደረሱት። ስለዚህ ውድቀትን እንደ መጨረሻ ሳይሆን እንደ አዲስ ትምህርት እዩት።
ስለዚህ አሁን የምታልፉበት ሁኔታ የመጨረሻው ምዕራፍ አይደለም።
የዛሬው ሕመም የነገውን ታሪክ እየጻፈ ሊሆን ይችላል። ሕይወት ሁልጊዜ ከመጨረሻ በኋላ አዲስ ጅማሮ አላት። ዛሬ የምታልፉበትን ሁኔታ እንደ ሕይወታችሁ መጨረሻ አትቁጠሩት።
https://t.me/Dreyob
https://m.youtube.com/user/naeleyob623
https://www.facebook.com/Dr-Eyob-Mamo-1050816404958639/ | 11 829 |
| 17 | ሕይወት ይቀጥላል! | 9 732 |
| 18 | ለምን አንዳንድ ሰዎች በፍጥነት ወደፊት ይጓዛሉ?
አንዳንድ ሰዎች አንድ ሰው ከእነሱ ጋር ፈጽሞ እንደማይሄድ እያወቁት እንኳን ያንን ሰው መርሳትና ወደ ፊት መራመድ ያስቸግራቸዋል፡፡
ከአንድ ግንኙነት አልፎ ወደ ፊት መጓዝ የሚያስቸግራቸው ሰዎች የሚከተሉት ምልክቶች ይታዩባቸዋል፡-
⏭️ ሁል ጊዜ ስለዚያ ሰው ማሰብ፣
⏭️ ማሕበራዊ ሚዲ እንቅስቃሴውን መከታተል
⏭️ስለእነሱ ሌላን ሰው መጠየቅ
⏭️ ቴክስት ማድረግና መልስ ሲጠብቁ መዋል
⏭️ ሰዎችን አንዴ block አንድ ደግሞ unblock ማድረግ ይታይባቸዋል፡፡
እንደዚህ አይነት ሰዎች ያለፉ ትዝታዎችን ለወራት አልፎ ተርፎም ለዓመታት ደግመው ደጋግመው ያስባሉ።
አንዳንድ ሰዎች ግን በዚህ ጉዳይ ጎበዞች ናቸው፡፡ የአንድ ሰው ሁኔታ እንደማያስኬዳቸው ሲገባቸው በቅድሚያ ግንኑነቱን ለማስተካከል የሚችሉትን ካደረጉ በኋላ ወደ ፊት ለመሄድ ይወስናሉ፡፡
ከእነዚህ አይነት ሰዎች የምንማራቸውን ነገሮች እንመልከትና ፈለጋቸውን እንከተል፡-
⏭️ ስሜታቸውን በፍጥነት process ካደረጉ በኋላ ውሳኔን ያስተላልፋሉ፤
⏭️ ሞዛናዊና ጤናማ የሆነ የመተሳሰር (attachment) ስሜት ስላላቸው መላቀቅ ሲገባቸው ይላቀቃሉ፣
⏭️ አንድ ሰው የእነሱ ያለመሆኑን እውነታውን በፍጥነት ተቀብለው ከራሳቸው ጋር ሰላም ይፈጥራሉ፣
⏭️ ትኩረታቸውን ሆን ብለው ወደ ዓላማቸውና ወደ ሌሎች ነገሮች ያዞራሉ።
ከአስቸጋሪ ሰዎች ተላቀን ወደፊት መራመድ አማራጭ የሌለው መንገድ ነው!
https://t.me/Dreyob
https://m.youtube.com/user/naeleyob623
https://www.facebook.com/Dr-Eyob-Mamo-1050816404958639/ | 12 229 |
| 19 | ራስን የመግዛት (ዲሲፕሊን) ያላቸው እና የሌላቸው
የግል ዕድገት (Personal Growth)
ራስን የመግዛት ችሎታ ያላቸው ሰዎች፦
ከስህተቶቻቸው ይማራሉ፣ ኃላፊነትን ይቀበላሉ፣ እና እራሳቸውን ለማሻሻል ለውጦችን ያደርጋሉ።
ራስን የመግዛት ችሎታ የሌላቸው ሰዎች፦
ብዙውን ጊዜ ሁኔታዎችን ወይም ሌሎችን ይወቅሳሉ፣ ያኑኑ ስህተትም በተደጋጋሚ መፈጸማቸውን ሊቀጥሉ ይችላሉ።
በዚህ ጉዳይ ላይ እናንተ እንዴት ናችሁ!
መልካም ምሽት ይሁላችሁ የምወዳችሁ የሃገሬ ሰዎች! | 11 059 |
| 20 | 16. “ግንኙነትና አለመግባባትን መፍታት”፡- ሰዎች የምንናገረውንና የምንተገብረውን ነገር በእንዴት አይነት የተሳሳተ ሁኔታ እንደሚገነዘቡን ብናውቅ መናገርና ምንም ነገር ማድረግ እናቆማለን የሚባል አባባል አለ፡፡ ለማንኛውም ማሕበራዊ ሕይወት ጤንነት የትክክለኛ ግንኙነትን መመሪያዎች ማወቅ አስፈላጊ ነው፡፡ ይህ መጽሐፍ በቃልና ቃል-አልባ በሆኑ መንገዶች ስለምናደርጋቸው ግንኙነቶች ትልቅ ሃሳብ ይዟል፡፡
[7/6/2026 7:54 PM] Dr. Eyob Mamo: 17. “የጥበብ መንገድ”፡- እውቀት የተወሰነ መንገድ ይወስድሃል፣ ጥበብ ግን እስከወዲያኛው ያዘልቅሃል፡፡ አንዳንድ ሰዎች በብዙ እውቀት ተሞልተው እንኳን ብልሹ ሕይወት ሲኖሩ ማየት የተለመደ ነው፡፡ ይህ እንዳይሆን ከእውቀት የላቀውን የጥበብን መንገድ ማስተናገድ አስፈላጊ ነው፡፡ ይህ መጽሐፍ ጥበብ ምን እንደሆነ፣ ከእውቀት በምን እንደሚለይና ጥበብን እንዴት ማግኘት እንደሚቻል ያመላክትሃል፡፡
18. “ሁለቱ ክህሎቶች”፡- ሁለት አይነት ክህሎቶች አሉ፡- አንደኛው የሞያ ክህሎት ሲሆነ፣ ሌላኛው ግን ማሕበራዊ ክህሎት ነው፡፡ የመጀመሪያው ስራን በስኬታማነት እንድንሰራ ሲያደርገን፣ ሁለተኛው ግን ማሕበራዊ ግንኙነታችን የሰመረ እንዲሆን ያግዘናል፡፡ ማንኛውም የሞያ ክህሎት ከማሕበራዊ ክህሎት ውጪ ብዙ ርቀት አያስኬደንም፡፡ ለማብራሪያውና ለግንዛቤው መጽሐፉን ማንበብ ጠቃሚ ነው፡፡
19. “አመኔታ”፡- አንዳንድ ሰዎች ሁሉንም ሰው በጭፍንነት የማመን ዝንባሌ ስላላቸው ሁል ጊዜ እየተጎዱ ይኖራሉ፡፡ ሌሎች ደግሞ ማንንም ባለማመንና በጥርጣሬ ድንበራቸውን አጥረው ብቻቸውን ይንገላታሉ፡፡ ይህ መጽሐፍ ከጭፍን ጥርጣሬና ከጭፍን አመኔታ ጠርዞች ወጥተን ወደ ንቁ አመኔታ እንዴት ማደግ እንደምንችል በግልጽ ያሳያል፡፡ “እመን፣ ነገር ግን አጣራ!” የሚለውን እውነታ ተግባራዊ ያደርግልናል!
20. “የመገፋት ሕመም”፡- በራሳችን ላይ ባለን አመለካከትም ሆነ ከሌሎች ጋር በሚኖረንን ማሕበራዊ ግንኙነት ላይ ታላቅ ተጽእኖ ከሚያስከትሉ ልምምዶችና የስነ-ልቦና ቀውሶች መካከል የመገፋት ሁኔታ (Rejection) አንጋፋው ነው፡፡ የመገፋት ልምምድ ከማሕጸን ጀምሮ እስከ ሽምግልና እድሜያችን ድረስ ሲከተለን የሚኖር ሁኔታ በመሆኑ ስለጉዳዩ በቂ እውቀት ማዳበር ወሳኝ ነው፡፡
21. “የፍቅር ሕይወት”፡- ከምንለማመዳቸው የየእለት ስሜቶች መካከል የፍቅር ስሜት ጠንካራው ነው፡፡ በዚህ መጽሐፍ ውስጥ በወጣትነት ጊዜ ራሳችንን ለትክክለኛ የፍቅር ሕይወት፣ አልፎም እስከመጨረሻው ለሚዘልቅ የትዳር ሕይወት እንዴት ማዘጋጀት እንደሚቻል የሚጠቁሙንን ተግባራዊ ትምህርቶች ማንም ሰው በቀላሉ ሊገነዘበው በሚችለው መልኩ ተገልጸዋል፡፡
22. “ጀምሮ መጨረስ”፡- ሕይወት ጀምሮ የመጨረስ ሂደት ነች፡፡ የዚህች ሕይወት ጥራትና ስኬት የሚለካው ደግሞ በየጊዜው ጀምረን በብቃት በምንጨርሳቸው ነገሮች ነው፡፡ በትምህርት ዓለም፣ በፍቅርና በቤተሰብ ዓለም፣ በስራው ዓለምና በአጠቃላይ በራእያችንና በግቦቻችን ሂደት ውስጥ አንድን ነገር የመጀመር፣ የመቀጠልና በብቃት የመጨረስ ተግባራዊ መመሪያዎች ጥርት ባለ መልኩ ቀርበዋል፡፡
23. “የትዳር ሕይወት”፡- የተቃራኒ ጾታ ግንኙነት ከፍቅር ግንኙነትና ከእጮኝነት አልፎ ወደ ትዳር ሲዘልቅ ይዞት የሚመጣው ደስታና ፈተና በሚገባና በሚዛናዊነት ሊያዝ ይገባዋል፡፡ በሁሉም ነገር የተለያዩ ተቃራኒ ጾታዎች ወደ አንድነት ሲመጡ ይህንን፣ የ“አንድነት በሁለትነት” አዲስ ጎዳና በተሳካለት ሁኔታ የሚመሩበት መርሆች በዚህ መጽሐፍ ውስጥ በቀላሉ ሊተገበሩ በሚችል መልኩ ተብራርተውልናል፡፡
24. “ቀዩ መስመር”፡- በማንኛውም ማሕበራዊ ዘርፍ በሚኖረን የሰው-ለሰው ግንኙነት ውስጥ ሰዎቹ በእኛ ሕይወት የሚፈቀድላቸውንና የማይፈቀድላቸውን ነገር የመለየትና የቀይ መስመር (Boundary) ማስመር ወሳኝ ነው፡፡ የቀይ መስመራችንን ማስመርና ማስከበር ለጤናማ ማሕበራዊ ሕይወት ወሳኝ በመሆኑ፣ ብልሃቱንና አቅሙን የምናሳድግበትን መመሪያዎች በዚህ መጽሐፍ ገጾች ውስጥ እናገኛለን፡፡
25. “ራእይን ማወቅና መኖር”፡- የስኬት መስመር ውስጥ ለመግባት የፈለገ ማንኛውም ሰው ሕይወትን ከትናንትና ታሪኩ ወይም ከወቅቱ ሁኔታው በመነሳት ከተረጎማት ቀስ በቀስ ጊዜውን ማባከኑ፣ ስኬተ-ቢስ መሆኑና ተስፋ መቁረጡ ጥርጥር የለውም፡፡ ሕይወት ግን መጀመር ያለባት ከነገው ራእይ ነው፡፡ የራእይን ትርጉም፣ እንዴት ራእያችንን እንደምናውቅና እንደምንኖር በዚህ መጽሐፍ ገጾች ውስጥ እናገኛለን፡፡
26. “ራስን ማወቅና መምራት”፡- ራሳችንን በሚገባ በማወቅ ካልመራን የመጣው ሰውና ሁኔታ ሁሉ ይመራናል፡፡ የሕይወታችንን ራእይ በመለየት ካልተከተልን፣ የሰው ራእይ እንደተከተልን ኖረን እናልፋለን፡፡ ለራሳችን በሚገባ በማወቅና ፍላጎታችንን በመለየት ለሕይወታችን ግብ ካላወጣን የመጣውንና ያጋጠመንን ነገር ሁሉ እንደግብ በመቁጠር እድሜያችንን እናባክናለን፡፡ ይህ መጽሐፍ ራሳችንን በሚገባ ከማወቅ የሚመጣውን ራስን የመምራት እውነታዎች በግልጽ ያሳየናል፡፡
27. “የልጆች አስተዳደግ”፡- ለአንድ ሃገርም ሆነ ሕብረተሰብ ጤናማነትና የወደፊት ስኬታማነት ትልቅ መዋጮ ከሚያበረክቱ ሁኔታዎች መካከል የልጆች አስተዳደግ ጉዳይ ቀንደኛው ነው፡፡ ይህ መጽሐፍ፣ “ልጆችን በምን መልኩ ብናሳድጋቸው፣ ምን ብናስተምራቸው፣ በምን መልኩ ብንከታተላቸውና እንዴት ምሳሌ ብንሆንላቸው ጤናማ የወደፊት ይኖራቸዋል?” ለሚሉትና ለሌሎች ወሳኝ ጥያቄዎች ሰፊ መልስ፣ መመሪያና ማብራሪያ የሚሰጥ መጽሐፍ ነው፡፡
28. “የተደራጀ ሕይወት”፡- ማንኛውን በሕይወታችን ያገኘነው ስኬት ቀጣይነት እንዲኖረው ካስፈለገ ማዳበር ከሚገቡን ክህሎቶች መካከል የአደረጃጀት ክህሎት አንዱና ቀንደኛው ነው፡፡ አንድን ነገር በእጃችን ማስገባት አንድ ጉዳይ ሲሆን፣ ያንን በእጃችን ያስገባነውን ነገር በተዋጣለት ሁኔታ ማስቀጠል “የአደረጃጀት ክህሎት” የሚፈልግ ጉዳይ ነው፡፡ ይህ መጽሐፍ ይህንን ክህሎት አስመልክቶ አስፈላጊና ተግባራዊ ገለጻ የሚያደርግ መጽሐፍ ነው፡፡
29. “የመኖር አቅም”፡- በሕወታችን የሚገጥሙን የመኖር አቅምን የሚያሳጡ አስቸጋሪ ሁኔታዎች፣ በአንድ በኩል ከራሳችን ጋር ያለንን ግንኙነት ሲነኩ፣ በሌላ በኩል ደግሞ ከሰዎች ጋር ካለንን ግንኙነት ጋር ይነካካሉ፡፡ ይህ መጽሐፍ ባሉን የራስ-በራስ እና የሰው-ለሰው የግንኙነት ዘርፎች ዙሪያ አቅም አሳጪ ሁኔታዎች እንድንለይ አቅጣጫ ያሳየናል፡፡ በተጨማሪም፣ ተገቢውን ምላሽ በመስጠት በብርታት ለማለፍ እንድንችል ዘመን-ዘለል መመሪያዎች እናገኛለን፡፡ | 9 918 |
