شـبـاب السـلــفـــيـــيــن
👉«ሰለፍያ ቀጥተኛ የሀቅ መንገድ ብሎም አይነኬ ፅኑ ተራራ ነው።» ለአስተያዬትና እርማት
إظهار المزيد📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام شـبـاب السـلــفـــيـــيــن
تُعد قناة شـبـاب السـلــفـــيـــيــن (@nuredinal_arebi) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 28 719 مشتركاً، محتلاً المرتبة 2 501 في فئة الدين والقيم الروحية والمرتبة 1 191 في منطقة Ethiopia.
📊 مؤشرات الجمهور والحراك
منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 28 719 مشتركاً.
بحسب آخر البيانات بتاريخ 01 أغسطس, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار -341، وفي آخر 24 ساعة بمقدار -22، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.
- حالة التحقق: غير موثّقة
- معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 14.56%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 7.42% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
- وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 4 183 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 2 131 مشاهدة.
- التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 42.
📝 الوصف وسياسة المحتوى
يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
“👉«ሰለፍያ ቀጥተኛ የሀቅ መንገድ ብሎም አይነኬ ፅኑ ተራራ ነው።»
ለአስተያዬትና እርማት”
بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 02 أغسطس, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة الدين والقيم الروحية.
جاري تحميل البيانات...
| التاريخ | نمو المشتركين | الإشارات | القنوات | |
| 02 أغسطس | 0 | |||
| 01 أغسطس | 0 |
| 2 | ክረምት እንደት ይዟችኋል ቤተሰብ⁉️
t.me/nuredinal_arebi
t.me/nuredinal_arebi | 662 |
| 3 | 🏷ጀግናዬ...‼️
ለሁሉም እሽ ማለት ሲበዛ ደግነት ሳይሆን ከሞኝነትና ከጂልነት ስለሚቆጠር እምቢ ማለትን ተማር...!!
ጀግናዬ የተነገረ ሁሉ እውነት እንዳልሆነ ሁሉ ያልተነገረ ሁሉ ደግሞ ስህተት አይደለም።
..ወዳጅና ጠላትህን ለይ...ልንገርህ ወዳጅና ጠላት ማለት አብረው የሚፈጠሩ እና ጎን ለጎን የሚያድጉ እንክርዳድና ስንደዎች ናቸው።
..🏷ዝምታህን ስበር..
ዝም ያለ ሁሉ አጥፊ የለፈለፈ ሁሉ ተበዳይ የሚመስላቸው አሉ እና አስፈላጊውን ጊዜና ቦታው ስታገኝ ዝምታህን አበረው።
ለላከህ ሁሉ አትላክ
ክፉ ክፉ ነው ወዳጅ መስሎ ወደ ገደል ይገፋሀል ተጠንቀቅ‼️
..ስማ‼️
አብዝተህ ተቀናቃኝ..ተባዝተህ ደግ ሁን
«ቀናወችና ደጎች ዋጋቸው የሚታወቀው ከስሜት ወጥተህ ተረጋግተህ ስታስብ ቦታቸው ላይ ስታገኛቸው ነው።
....ኑር...✍️
t.me/nuredinal_arebi
t.me/nuredinal_arebi | 963 |
| 4 | https://t.me/UstazKedirAhmed?livestream | 879 |
| 5 | በትዝታ ቅኝት በሀሳብ ተጉዘን፡
ያው እዚህ ደርሰናል ሁሉን ነገር ይዘን፡
ብዙ ሚስጥራትን በምፀት አርግዘን፡
ሁሉንም ሸፍነን በፈገግታ ደርዘን፡
ነገን የተሻለ ለማድረግ አስበን፡
መግዘፍ ሲኖርብን እንደ እባብ ተስበን፡
የትውስታን ባህር የናፍቆት ዳገቱን፡
ትዝታን ስንቅ አርገን ተሻገርነው ስንቱን፡
.....አልሃምዱሊላህ በስ...✍️
....ኑር...✍️
t.me/nuredinal_arebi
t.me/nuredinal_arebi | 1 757 |
| 6 | ....ለሁላችንም ይድረስ አንብቧትማ...‼️
…እንድህ ነን ሁላችን…
------------------------
ሁሉም የራሱን አይብ አርቆ ይቀብራል፡
የሌሎችን ነውር ደፍሮ ይናገራል፡
ወንዱ ወንድነቱን አራግፎ ጨርሷል፡
ወኔው ላሽቆ ወድቆ ብዙ ነገር ፈርሷል፡
ሴቱ በሴትነት መከበር አልቻለም፡
ሁሉም ተቃራኒ ሆኗል በዚህች አለም፡
ሁሉም አስመሳይ ነው አያውቅም ሀቂቃ፡
ከሊቅ እስከ ደቂቅ እንደዚህ ነን በቃ!!
ሁሌ በመሰለኝ ሰው የምንወነጂል፡
የራሳችን ሳያልቅ የሌላ እምንከጂል፡
ስም የምናወጣ ለአዛኝ ብለን ጨካኝ፡
አዋቂ እምንንቅ ባለ ራዕይ አምካኝ፡
......እንደዚህ ነን እኛ....
ስንቱን የጥበብ ሰው ደጋግመን በደልነው፡
ስንቱን በሌለበት ቀጥቅጠን ገደልነው፡
ሁሉም አውቃለሁ ባይ ሁሉም ተናጋሪ፡
ከፈረሱ በፊት የሚቀድም ጋሪ፡
ሁላችንም ዘፋኝ ሁላችን ዘማሪ፡
ሁላችንም ሌባ ሁላችን አዝማሪ፡
ሁላችንም አጫሽ ሁላችን ሰካሪ፡
ሁላችን ዘረኛ በውሸት መስካሪ፡
ቃላችን ተግባር ጋር በቃ አልተጣጣመም፡
ዛሬም እንደ ትናንት ግፋችን አልቆመም፡
አክባሪ ተንቆ ጋጠ-ወጥ ደምቆ፡
አንባ-ገነን ጎልቶ ፍትህ ተሸምቆ፡
መመስገን ሲናፍቅ ግፈኛው በሙሉ፡
ታጋይ መባል ሲመርጥ አጭበርባሪው ሁሉ፡
ከሚመኝ ኗሪ ጋር፤
በሔድናቸው መንገድ ባለፍናቸው ቀናት፡
ለካ ሁላችንም፤
ልባችን ቀጣፊ ነፍስም ዱርዬ ናት፡
.....አዎ....‼️
ሁላችንም አዳኝ ሁላችን ታማሚ
ሁላችንም ዶክተር መዳኒት ቀማሚ፡
ሁላችንም ደጋሽ ሁላችን ታዳሚ፡
ሁላችንም ችግር ሁላችን አውዳሚ፡
ሁላችን ባላገር ሁላችን እንግዳ፡
ሁላችንም ዘመድ ሁላችንም ባዳ፡
ሁላችን እንቅልፋም ሁላችንም ንቁ፡
ሁላችንም ድንጋይ ሁላችንም እንቁ፡
ሁላችንም ሳቂ ሁላችን አኩራፊ፡
ሁላችንም ሌባ ሁላችን ዘራፊ፡
ሁላችን ዝመኞች ሁላችን ለፍላፊ፡
ሁላችንም ክፉ ሁላችን ጠላፊ፡
ሁላችንም ተራ ሁላችን ዝነኛ፡
ሁላችንም ደጎች ሁላችን ምቀኛ፡
አስተውሎ ላየን እንደዚህ ነን እኛ፡
ሁላችን ፀበኛ ሁላችን ገላጋይ፡
ሁላችን ሴረኛ ሁላችንም ሸምጋይ፡
ሁላችን የበታች ሁላችን የበላይ፡
አንድነት ያቃተን ተናበን አንድ ላይ፡
ሁላችንም ተጓዥ ሁላችንም መጪ፡
ሁላችንም ቀሚ ሁላችንም ሰጪ፡
ሁላችን ከሳሽ ሁላችንም ቀጪ፡
ሁላችንም ጠላት ሆነን ለሁላችን፡
የጠላት መሳቂያ ሆኗል መኖራችን፡
መጨቆን መሰደድ በሀይማኖታችን፡
ሰበር ዜና ሆኗል ሁሌም መሞታችን፡
አሁን ያለንበት እንድህ ነው ሁላችን፡
🔸...ኑረዲን አል-ዓረብ..✍️
t.me/nuredinal_arebi
t.me/nuredinal_arebi | 2 138 |
| 7 | አለማወቅ ደፋር ያደርጋል
------------------------
አንዳንድ ጊዜ ሰው ለምን ያለ ፍርሃት ወደ አደጋ እንደሚገባ ይገርመኝ ነበር።
ለምን በድፍረት ሳያስብ ውሳኔ እንደሚሰጥ፣
ለምን የማያውቀውን ነገር እንደሚያሳንስ፣
ለምን ሁሉን እንደሚያውቅ ሆኖ ያለ ጥርጥር እንደሚናገር አገርም ነበር።
መልሱ ግን ከምናስበው በተቃራኒ ነው።
👉አለማወቅ ደፋር ያደርጋል።
ሰው አደጋውን ካላወቀ አይፈራውም።
የጉዞውን መንገድ ካላወቀ ግንባሩን ሳይደፋ ይጓዛል።
ጥልቀቱን የማያውቅ ሰው ወደ ውሃው ያለ ማመንታት ሊዘል ይችላል።
ከፊቱ ያለውን ገደል የማያውቅ ሰው በፍጥነት ሊሮጥ ይችላል።
ምክንያቱም ፍርሃት ብዙ ጊዜ ከእውቀት ይመጣል።
አደጋውን የምታውቅ ከሆነ ትጠነቀቃለህ።
ውጤቱን የምታውቅ ከሆነ ታስባለህ።
አማራጩን የምታውቅ ከሆነ ትመርጣለህ።
እውቀት ፍርሃትን ብቻ አይፈጥርም፤ ጥንቃቄንም ይፈጥራል።
አለማወቅ ግን ሰውን ከእውነታው ይለያል።
የማያውቀውን ነገር ቀላል ያደርገዋል።
የማይችለውን እንደሚችል ያሳምነዋል።
የማይገባውን እንደገባው ያስመስላል።
የሚያስፈራውን እንደማያስፈራ ያሳየዋል።
ከዚህ የተነሳ አንዳንድ ሰዎች የማያውቁትን ነገር ለመናገር በጣም ደፋሮች ናቸው።
ስለማያውቁት ጉዳይ ይፈርዳሉ።
ስለማያውቁት ሰው ይወስናሉ።
ስለማያውቁት ነገር በእርግጠኝነት ይከራከራሉ።
እውቀት ያለው ሰው ግን አንዳንድ ጊዜ ይቆማል።
👉"ምናልባት አላውቅም።"
👉"ምናልባት ተሳስቻለሁ።"
👉"በቂ መረጃ የለኝም።"
👉"በመጀመሪያ ልመርምር።"
ይላል።
ይህ ድክመት አይደለም።
ይህ የእውቀት ትልቁ ምልክት ነው።
እውነተኛ ብልህነት ሁሉን እንደምታውቅ መናገር አይደለም፤ የማታውቀውን መለየት መቻል ነው።
ሰው የማያውቀውን ሲያውቅ የሚጀምረው እውነተኛ ጥንቃቄ ነው።
እናም አንድ ነገር ልብ በል።
አለማወቅ ደፋር ያደርጋል፤ እውቀት ግን ያስተውላል።
የማያውቅ ሰው ወደ አደጋ ሊሮጥ ይችላል።
የሚያውቅ ሰው ግን ከመሮጡ በፊት መንገዱን ይመረምራል።
የማያውቅ ሰው በቀላሉ ይፈርዳል።
የሚያውቅ ሰው ግን ጥያቄ ይጠይቃል።
የማያውቅ ሰው በእርግጠኝነት ይናገራል።
የሚያውቅ ሰው ግን እርግጠኛ ባልሆነበት ጊዜ ዝም ማለትን ያውቃል።
ስለዚህ ከማናውቀው ነገር ጋር በድፍረት ከመጋፈጣችን በፊት እንጠይቅ።
"ምን አላውቅም?"
ይህንን ጥያቄ መጠየቅ ከፍርሃት የበለጠ የጥበብ መጀመሪያ ነው።
እውቀት አንዳንድ ጊዜ ያስፈራል፤ ምክንያቱም የምናምንባቸውን ነገሮች እንድንመረምር ያስገድደናል።
ነገር ግን ያ ፍርሃት የሚጠቅመን ፍርሃት ነው።
ምክንያቱም እውቀት ወደ ጥንቃቄ ይመራል፤ ጥንቃቄ ደግሞ ከብዙ ስህተቶች ያድናል።
ስለዚህ ሁሉን እንደምታውቅ አትቸኩል።
ስለማታውቀው ጉዳይ ድምፅህን ከፍ ከማድረግ በፊት እውቀትህን አሳድግ።
👉ስለማታውቀው ሰው ከመፍረድህ በፊት ሁኔታውን ተረዳ።
ወደማታውቀው መንገድ ከመግባትህ በፊት መንገዱን ጠይቅ።
ምክንያቱም...
አለማወቅ ደፋር ያደርጋል፤ እውቀት ግን ደፋርነትህን ከጥበብ ጋር ያጣምረዋል።
በሕይወት ውስጥ የሚያስፈልገን ያለ ማሰብ የምንሮጥበት ድፍረት ሳይሆን፣ መቼ መሮጥ፣ መቼ መቆም፣ መቼ መጠየቅና መቼ መጠንቀቅ እንዳለብን የምናውቅበት ጥበብ ነው።
ስለዚህ እውቀትን ፈልጉ፤ የማታውቁትን ጠይቁ። ምክንያቱም የማያውቅ ሰው ምንም ነገር አይፈራም፤
የሚያውቅ ሰው ግን ምን መፍራት እንዳለበት ያውቃል።
አሏህ ልቦና ይስጠን አሚን
t.me/nuredinal_arebi
t.me/nuredinal_arebi | 2 762 |
| 8 | هذا اليوتيوبر ( الجاهِل ) كَـفَّــر الحافِظ السيوطي !!
__
🖋️ قال شيخ الإسلام ابن تيمية : فإنَّ تسليط الجُهَّال على تَكفير علماء المسلمين مِن أعظَم المنكرات، وإنما أصلُ هذا مِن الخوارج والروافض الذين يُكفّرون أئمة المسلمين؛ لِما يَعتقدون أنهم أخطئوا فيه مِن الدين ،
وقد اتفق أهل السُّنة والجماعة على أن علماء المسلمين لا يَجوز تَكفيرهم بمجرد الخطأ المحض؛ بل كل أحدٍ يُؤخذ مِن قوله و يُترك إلا رسول الله صلى الله عليه وسلم ،
وليس كل مَن يُترك بعض كلامه لخطأٍ أخطأه يُكفّر ولا يُفسَّق بل ولا يُأثَّم؛ فإنَّ الله تعالى قال في دعاء المؤمنين : {ربنا لا تؤاخذنا إن نسينا أو أخطأنا} وفي الصحيح عن النبي صلى الله عليه وسلم «أن اللهَ تعالى قال : قد فَعلت».
[مجموع الفتاوى - ١٠٠/٣٥]
__
🖋️ قال شيخ الإسلام ابن تيمية : دَفعُ التكفير عن علماء المسلمين وإن أخطئوا هو من أحقِّ الأغراض الشرعية.
[مجموع الفتاوى - ١٠٣/٣٥]
t.me/nuredinal_arebi
t.me/nuredinal_arebi | 2 455 |
| 9 | አወቀብንና ለዱንያ እንደወጣን፡
ጭራሽ የያዝነውን አሶስደን መጣን ።
«ዱንያ ህልማችን ላይ አኸይራን እንጨምር» | 2 253 |
| 10 | الدُنيا صَعبةٌ جدًا على الإنسَانِ الَّذي يَتأثر قَلبُهُ بِسهُولة. | 2 502 |
| 11 | «ያኔ የተከተበ ግን ሁሌ የሚነበብ»
👉ቀጣይ ዓመት ራሴ ላነበው
..... .. ለራሴ የጻፍኩት መፅናኛ!!
.... ማንም እንዳያነበው እሽ⁉️
ሁሌም በፈገግታ አልሀምዱ ሊላህ በል
#ኑር...አሏህ ዕድሜ ሠጥቶህ ይህን እንድታነብ ከፈቀደልህ፣ እንደ #ለህድ የጨለመውንና የጠበበውን መንገድ ማለፍህን እንደማትረሳ ተስፋ አደርጋለሁ፡፡
ተስፋ መቁረጥ ጥርሱን አግጥጦ የገፋህን ቅጽበት፣ ቀናት ሁሉ በማይገለጥ ሸንኮፍ ተጋርደው አልነጋ ሲሉ፤በአኬልዳማ ተደልድለው መራመጃ የነፈጉህ መንገዶች፤ አቅም ባጣም በሹክሹክታ ‹‹ያልፋሉ!›› ስልህ ከመጣህበት በላይ የምትደርስበትን ጸዳል ጉብታ በከሲታ ተስፋ ውስጥ. . .ተስፋ አድርጌ ነው። #አልሃምዱሊላህ ፡፡
የዛሬ ዓመት በዚህ ሰዓት ደክሞህ ነበር፡፡ የአሏህ ውሳኔ ሆኖብህ በሕይወትህ ረግጠህ የማታውቃቸው አዚማም ሥፍራዎች ላይ ቆመሃል፡፡
ትዝ ይልሀል ጨለማን ተጋፍጠህ ነበር
ሐኪም ቤት በፍርሀት እየተንቀጠቀጥክ ቆመሀል።
ከሰው ፊት በጭንቀት ቆመሀል፡፡
..ያኔ ከጎንህ አብሮ አደረሰ አልነበረም፣
..የረጂም ጊዜ ጓደኛህ አልነበረም፣
..በችግሬ ይደርሳል ያልከው ሰውን አልነበረም።
የውስጥ ስሜትህን ለመናገር የሚረዳህ ጠፍቶ አይንህ ሰውን ፍለጋ ወዳና ወዲህ ሲያማትር ከጀሊሉ ብሎም ከአንድ ሰው ውጭ አብሮህ ማን ነበር!?
ሐያሉ ጌታህ ፊት ወንጀሎችህን ረስተህ አይንህን በጨው አጥበህ የእንባ ዘለላ እያፈሰስክ #የዛሬን ብለህ ቆመሀል።
(አዛኙ ጌታ ግን አላሳፈረህም)
በሀሳብና በጭንቀት ሰውነትህ እያየኸው ይቀንስ ነበር ከእለት ወደ እለት ባዶነት እየተሰማህ ከሰው እየተደበቅክ ያለቀስክበትን ቅፅበት ትረሳዋለህ!?
ህመምህን ደብቀህ ደህና ነኝ ብለህ ስራ የወጣህበትን አጋጣሚስ....
ምን ይህ ብቻ አፈር ልሰህ ወደ ሕልምህ እንዲያቀናህ ያበቀልከውን ፍሬ ሌባ ያለ ኀፍረት ወስዶብሃል፡፡
...በአሏህ ከተመካህ ድፍረትና ጭስን ተመስለህ በመርፌ ቀዳዳ እንደምትወጣ ፍርሃት በዋጠው ለሆሳስ ነግሬህ ነበር፣ አላሳፈርከኝም…ዛሬ እዚህ ደርሰሃል፡፡#አልሃምዱሊላህ
የዛሬ ዓመት በዚህ ሰዓት ዓለም ተገልብጦብህ ነበር፡፡በደም፣ በሥጋ በመንፈስ የተዛመዱህ በቅርበት ያሉ ወዳጆች ጀርባቸውን እንጂ ፊት አልሠጡህም፡፡
የሩቆቹ እንጂ የቅርቦቹ ከመቅረብ ይልቅ በጀርባ ማውራትን መርጠው ነበር..በዛ ስሜት ንግግራቸውን ሰምተህ.. ፈገግታህስ..ትዝ ይልሀል⁉️
የኋላ ታሪክህንና የሚደርስልህ ነገህን ረስተው በቆምክበት ሥፍራ መዝነው አቅልለውሃል፡፡
ይጎትቱኛል ያልካቸው መዳፎች ገፍተው ወደ መቀመቅ እንድትወርድ በይነውብሃል፡፡
...የታመመ የማይድን
የተሰበረ የማይጠግን
የወደቀ የማይነሳ
የተዋረደ ወደ ክብር የማይመለስ የሚመስላቸው ብዙዎች እንደሆኑ አስተውል ብዬ..ፍርሃት ባደበዘዘው ለሆሳስ ነግሬህ ነበር…..‹‹ያልፋል!›› ተብዬ ይሔው አለፈ፡፡
.....አልሃምዱሊላህ ‼️
«በመታመምህ ማዘናቸው ቀርቶ መታመሙን በምን እናረጋግጥ ይጣራ ሲሉ አልሰማህም!?ግን አለፈ አልሃምዱሊላህ ሊላህ»
«ግን በደል ስለማይረሳ እንጂ እንደ ውሀ ሙላት አብሽር እያለ በሚችለው ሁሉ ከጎኔ የቆመ ተራራ የሆነ እጂግ አዛኝ #ወገን እንደነበረኝ በዛ ቅፅበት ሞት ቢመጣ ራሱን የምደሰትበት ለሰላምም ነበረው...
«መልካሞች ሆይ ውለታችሁን ለመክፈል ባልችልም በልቤ ውስጥ ግን ሁሌም ትልቅ ቦታ አላችሁ»
የዛሬ ዓመት በዚህ ሰዓት…..ደርሶብህ የማያውቀው የመከራ ፍላጻ ተወርውሮ ቤትህ ገብቶ ገርበብ ያለ በርህን ዘግቶ፣ ክፍት መስኮትህን ደፍኖ ከሁሉ አራርቆህ፣ የጨበጥከውን ነጥቆ፣ የጎረስከውን አስተፍቶህ ብዙ ቀናትና ወራት ሳይነጉልህ…በድቅድቅ ውስጥ ማንም ሳያይህ ከራስህ ጋር ስትታገል፣ ባልተዘጋጀ ትከሻ ላይ ሲህር ሌላ ሸክም ኾኖ ሲያጎብጥህ፤ ከገጠመህ ይልቅ የሚመጣውን ተዓምር አስቤ ፍርሃት ባደበዘዘው ለሆሳስ ‹‹አይዞህ! ይህም ያልፋል!›› ብዬህ ነበር፡፡(ይኸው! አለፍከው አይደል?)አልሃምዱሊላህ ሊላህ በላ...አልሃምዱሊላህ
‹‹ንገረኝ!›› ሲሉህ እንዴት እንደምትገልፀው ተቸግረህ፣ የምትወደውን ብዕር ጨለማ ውስጥ ጥለህ መናገር ከብዶህ….በዝምታ ከዝምታ ጋር ታግለሃል፡፡
ግን ያኔም በመሆን የምትተነፍስበትን ብዕር እንጂ ፈገግታህን እና ጨዋታህን አልጣልክም፡፡ያንኳኳሃቸው በሮች ወቅታቸው ስላልደረሰ እንጂ መከፈታቸው እንደ ቂያማ የማይቀር ቀጠሮ መሆኑን ከሕመሞችህ ልቀው ባይሰ´ሙህም ነግሬህ ነበር፣አላመንከኝም ነበር፡፡
ዛሬ እዚህ ስለደረስክ እኮራብሃለሁ፡፡
«ሁሉም የሆነው በአሏህ እዝነት ከዚያም በወገንህ እገዛ ነው።»
✅ስማ ኑር...‼️
አደራ እነዚያን እንደ ሻማ🕯 የቀለጡልህን የጨለማህ ቀን መብራቶች እንዳትረሳቸው»
🏷በተለይ ሦስት ነገር አትርሳ….‼️
👉ትንሽ ሻማ ይዘው ጨለማህ ድረስ መጥተው ብርሃናቸውን ያካፈሉህን፣
👉የተፈጠረው ሳይገባህ፣ የተናገርከው ሳይገባቸው ጆሮ የሠጡህን!
👉ደግሞም ችለው ያልቻሉትን፣ መንገድ መጠቆም ሲችሉ መንገድህን የዘጉትን፣ ጥሩ ቃል እንኳ እንደ ሰማይ የራቃቸውንና ወደቀ ብለው በደስታ በሌለህበት መርጠህ ባልተሰጠኸው ችግር የተሳለቁብህን... እንደማትፈፅመው እያወቁ በክፉ እንድትታይ ያደረጉህን፣ አምነሀቸው ጓደኛ አድርገሀቸው፣ የመከራ ቀን የውስጥ ክፋታቸውን ያሳዩህን #እንዳትረሳቸው... ግን እነሱ አንተ ላይ የሰሩትን ለመስራት ተፈፅሞ እንዳታስብ እነሱም ማንነታቸውን አስተዋወቁህ እንጂ ምንም ማድረግ አልቻሉም፡፡
👉ሦስተኛ. . .ማን እንደኾንክ አትርሳ፡፡
አሁን ያለህበት ብሩህ ቀን ሲያዘናጋህ ይህን ጽሑፍ አንብብ፡፡
ያለ መሣሪያ ጦርነት ውስጥ ገብተህ የወጣህ፣ ያለ ምሽግ ከፈንጂ ጋር የተጋፈጥክ፣ ራስህን አጥተህ ራስህን ያገኘህ ልበ-ብረት ነህ፡፡
#እኮራብሃለሁ! እራስህን ከማንም በላይ ታውቀዋለህ አይዞህ አዛኝ እንደሆንክ፣ናፋቂ እንደሆንክ፣ተጫዋች እንደሆንክ፣የዋህ እንደሆንክ ቀጥል....... ክፋት፣ምቀኝነት፣ቂምና ጥላቻ ለማንም እንደማይጠቅም አውቀህ ደግነትን ሆነህ ስበከው.. እልሀለሁ... ይህ ቀን አልፎ የሆነ ስዓት በሙሉ ጤንነትህ ታነበዋለህ መንሻ አሏህ አይዞህ እሽ ኑር...«አሏህ ክፉ አይሰራም ትል የለ...አብሽር»
«በፈገግታ ሁሉን ማለፍና ማስተናገድ ትችላለህ አልሃምዱሊላህ
ሁሉም አለፈና አሁን አነበብኩት፡
ተማሩበት ብዬ ወደናንተ ላኩት፡
t.me/nuredinal_arebi
t.me/nuredinal_arebi | 2 741 |
| 12 | በርቱ አሏህ ይጠብቃችሁ
«ለአሏህ ስል እወዳችኋለሁ የሆነ ትዝታ መጣብኝና አስታወስኳችሁ ደግሞ ናፍቃችሁኛል እሽ‼️ | 2 926 |
| 13 | لا يوجد نص... | 3 799 |
| 14 | ወዳጅ እንደሌለህ!
....ታውቃለህ...!?
ማንም ሰው አይልህም ምን ሆኖ ተከፋ፡
ሰው አይጠይቅህም ዘመናት ብትጠፋ፡
አይደለም እንባና ደምክን ብታፈሰው፡
ማንም ሰው አይልህም ምን ሆኖ ሆድ ባሰውን!!
መሳቅ ስትጀምር ግን ይበዛል ጥያቄ፡
ለምን እንደሆነ እኔ ምን አውቄ!!
🕯ይገርመኛል!!
ባጋጠመህ ጊዜ የመክሸፍ አደጋ፡
ምን ጨለማ ቢሆን ሀምሌ ቢሆን በጋ፡
ከየትም ይመጣል ለነገር ፍለጋ፡
ከች ይላል ከቤትህ ሌሊቱ አይነጋ፡
...አይ ሰው..!!
ትንሽ ሲያነቅፍህ የህይወትህ ስንጥር፡
ጠያቂህ ይበዛል ባለቀስክ ቁጥር፡
ግን ደግሞ ከአንጀቱ ምንም አያደርግም፡
ምን ሞልቶ የተረፈው መርዳት አይፈልግም፡
ስታለቅስ ደግሞ ለእንባህ ማድመቂያ፡
ሀዘን ስብራትህ እንዳይኖረው ማብቂያ፡
ባነር ይሰራሉ ትልቅ ማስታወቂያ፡
......ይገርማል....!!!
ሀዘንህ ሲሰማ ሁሉም ይታደማል፡
አስተናጋጅ ሆኖ ጠላትህ ይቆማል፡
ወዳጅ የምትለው አንተን ይጠቁማል፡
በሀዘንህ ቀን እንኳን አንተነት ይታማል፡
አስተውለህ ካየህ ሁሉም ነገር ያማል፡
ማስመሰል ማታለል እጂጉን ያደክማል፡
.....ባለቤት ይሰማል...!?
በጣም እንዲታለቅስ ይነካሉ ቁስል፡
አብሽር በርታ ጠንክር ማለትን ይመስል፡
በጣም እንድታለቅስ ይጫናሉ ቁስል፡
ለእንባህ ማድመቂያ ይለብሳሉ ካኪ፡
ከወደቅክ ይላሉ ዘረፋና አካኪ፡
ደስተኛ ሁንና ሞክራቸው እስኪ...!?
👉....ሰምተሀል...ደስተኛ ሁን ማንም ስላንተ አይጨነቅም።
...ኑር....✍️
t.me/nuredinal_arebi
t.me/nuredinal_arebi | 1 |
| 15 | ....ስማ....
በሆነ አጋጣሚ ሲጠፋ ከደጂህ፡
ከጎኑ ባትቆምም አቅም አጥሮት እጂህ፡
ክፉ አንዳታወራ ስለዛ ወዳጅህ፡
.....Nur.....✍️
t.me/nuredinal_arebi
t.me/nuredinal_arebi | 3 158 |
| 16 | .....ፅኑዎች ሆይ አብሽሩ
-----------------------
የዉስጥን ስቃይ ባለቤቱ ብቻ ያዉቀዋል....
በሕይወት ጎዳና ላይ ስንጓዝ ሁላችንም የራሳችን የሆነ ከባድ
ደመና ከራሳችን በላይ ያንዣብባል ብዙ የሀሳብና የህፀፅ አበባወችም የሲቃ እንባ ጠጥቶ ያፈራል።
....ግና በዙሪያችን ያሉ ሰዎች
የዝናቡን መዉረድ እንጂ... ያ ዝናብ በዉስጣችን የሚፈጥረውን
ቅዝቃዜና የሚቀሰቅሰዉን ትዝታ ፊጽሞ ሊረዱት አይችሉም።
ብዙ ጊዜ ሰዎችን የምንፈርደዉ በምናየው ዉጫዊ ገጽታቸው
ብቻ ነው።
"እሱ/እሷ ምን ይጎድላቸዋል!?" እንላለን።
.......ነገር ግን ከጥሩ ልብሶች፣
ከሚያምሩ ፈገግታዎች እና ከቀን ተቀን
እንቅስቃሴዎች ጀርባ የሚደበቁ ስንት የተሰበሩ ልቦች አሉ⁉️
ስንት የሚደሙ ነፍሳትስ አሉ⁉️
👉ሕመም የምሰማው ለቆሰለዉ ሰው ብቻ ነው።
ሌላው ሰው ሊያዝንልህ፣
ሊያጽናናህ ወይም ሊራራልህ ይችላል፤
ነገር ግን
በጨለማ ክፍል ዉስጥ ብቻህን የምታፈሰዉን የእንባ ዘለላ ትክክለኛ ክብደት ሊሰማው አይችልም።
ያንተን ጫማ ተጭቶ
ያልተጓዘ ሰው፣ መንገድህ ምን ያህል አሰቃቂ እንደነበረ ሊረዳ አይችልም።
የሚያስለቅስህ ነገር ለሌላው ሰው ቀላል መስሎ ሊተይ
ይችላል። "ለዚህ ነገር ነው የምታለቅሰው?" ሊሉህ ይችላሉ።
ምክንያቱም እነሱ የሚያዩት የወደቀውን ጃንጥላና የራሰዉን መሬት
ብቻ ነው፤ በልብህ ዉስጥ የፈረሰውን ዓለም አያዩትም።
.....ነገር ግን ማስታወስ ያለብህ አንድ ታላቅ እዉነት አለ፦
ይህ በእንባ የራሰ መንገድ፣
ይሄ ብቻህን የተሸከምከዉ ከባድ
ደመና ለዘላለም አይኖርም።
አሁን የምታሳልፈው ስቃይ
ጥንካሬህን የምትገነባበት፣
የነገ ማንነትህን የምታንጽበት ነበልባል እሳት ነው።
👉ማንም ባይረዳህ እንኳ፣ የራስህን ሕመም በራስህ ጽናት አክመህ እንደምትነሳ እመን።
"የቁስሉ ሕመም የሚያዉቀዉ ባለቤቱ ብቻ ቢሆንም፣ ከሕመሙ
በኋላ የሚመጣውን ብርሃንና ጥንካሬ የሚያጣጥመዉም ያው
የጸናው ልብ ብቻ ነዉ።"
«አሏህ ሆይ በመከራ ለፀኑ ልቦች ፈረጃውን አቅርቦላቸው አሚን።»
....ኑር....✍️
t.me/nuredinal_arebi
t.me/nuredinal_arebi | 3 890 |
| 17 | خَصائِصُ_الْمَرأَةِ_السَّلَفِيَّةِ.mp3 | 4 157 |
| 18 | لو أنَّ أحدَكم همَّ بإزالةِ جبلٍ، وهو واثقٌ باللهِ لأزالَه.
ከእናንተ መካከል አንዱ ተራራን ለማንቀሳቀስ ቢያስብና በአሏህ ላይ ሙሉ እምነት ቢኖረው ያንቀሳቅሰዋል።
➛ሒማ ይኑረን..!!
- ابن القيّم.
t.me/nuredinal_arebi
t.me/nuredinal_arebi | 3 798 |
| 19 | የቀብር ስነስርአት ነገ ጊንባ ቱላውሊያ ነው | 5 208 |
| 20 | انا لله وانا اليه راجعون
አባቴ በዱንያ ላይመለስ ሞተብኝ ቅርብ የላችሁ እዲሰግዱበት ሩቅ ያላችሁ በዱአችሁ | 4 154 |
