Ethio Radar|ኢትዮ ራዳር
Welcome to Ethio Radar, a professional news analysis platform brought to you by a dedicated team of experienced journalist. stay informed,stay on radar! እንኳን ወደ ኢትዮ ራዳር ቻናል መጡ,ሀሳብ፣አስተያየት፣ መረጃ ለማጋራት ማስታወቂያ ለማሰራት በ @Ethioradarr01 ያናግሩን
Ko'proq ko'rsatish📈 Telegram kanali Ethio Radar|ኢትዮ ራዳር analitikasi
Ethio Radar|ኢትዮ ራዳር (@ethioradarinfo) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 52 587 obunachidan iborat bo'lib, Marketing toifasida 189-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 630-o'rinni egallagan.
📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika
невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 52 587 obunachiga ega bo‘ldi.
03 Sentabr, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni -3 336 ga, so‘nggi 24 soatda esa -122 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.
- Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
- Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 1.76% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 0.71% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
- Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 924 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 374 ta ko‘rish yig‘iladi.
- Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 3 ta reaksiya keladi.
📝 Tavsif va kontent siyosati
Muallif resursni shaxsiy fikrni ifoda etish maydoni sifatida ta’riflaydi:
“Welcome to Ethio Radar, a professional news analysis platform brought to you by a dedicated team of experienced journalist.
stay informed,stay on radar!
እንኳን ወደ ኢትዮ ራዳር ቻናል መጡ,ሀሳብ፣አስተያየት፣ መረጃ ለማጋራት ማስታወቂያ ለማሰራት በ @Ethioradarr01 ያናግሩን”
Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 04 Sentabr, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Marketing toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.
Ma'lumot yuklanmoqda...
| Sana | Obunachilarni jalb qilish | Esdaliklar | Kanallar | |
| 03 Sentabr | 0 | |||
| 02 Sentabr | 0 | |||
| 01 Sentabr | 0 |
| 2 | ትናንት ይፋ ከተደረገው የ2018 ዓ.ም የሪሚዲያል ፕሮግራም ተማሪዎች ውጤት ጋር በተያያዘ እጅግ በርካታ ተማሪዎች ቅሬታቸውን ለቲክቫህ ዩኒቨርሲቲ ማድረሳቸው ተሰምቷል።
በርካታ ተማሪዎች ውጤታቸው ሙሉ በሙሉ 'Disqualified' የተባለባቸው መሆኑን በመግለፅ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት እንዲሁም ትምህርት ሚኒስቴር ማብራሪያ እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል። ሌላው ቀርቶ የበርካታ ተማሪዎች የሂሳብ ትምህርት ውጤታቸው ብቻ 'Disqualified' ማለቱ አሳሳቢ ሆኗል።
የተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች ተማሪዎች የሆኑት ቅሬታ አቅራቢዎቹ፤ በፈተና ወቅት ምንም አይነት የስነ-ምግባር ግድፈት አለመፈጸማቸውን ገልጸው፣ በእርማት ወቅት ቴክኒካል ችግር ከነበረ እንዲታይላቸው በትህትና ጠይቀዋል።
በዚሁ መሠረት ተማሪዎች ቅሬታቸውን በኦንላይን በ result.ethernet.edu.et ገጽ በመግባት ማቅረብ የሚችሉ ሲሆን፣ አሰራሩም፦ ከውጤቱ ስር መጨረሻ ላይ ያለውን Submit Complaint የሚለውን በመጫን፣ Select a category በሚለው ስር My result disqualified without reason የሚለውን በመምረጥ፣ አጠር ያለ መግለጫና የስልክ ቁጥር ሞልቶ ማስገባት እንደሚቻል ተገልፆል።
በትናንትናው ዕለት ይፋ በሆነው መረጃ መሠረት የሪሚዲያል ፕሮግራም የማለፊያ ነጥብ ለተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች (ከ5 የትምህርት አይነቶች) 250 እንዲሁም ለማኅበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች (ከ4 የትምህርት አይነቶች) 200 መሆኑ ታውቋል።
የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት እንዲሁም ትምህርት ሚኒስቴር በተማሪዎቹ በቀረቡ ቅሬታዎች ላይ የሚሰጡትን ምላሽ ቲክቫህ ዩኒቨርሲቲ እንደሚያደርስ ገልፆል ።
@ethioradarinfo | 280 |
| 3 | የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ከዓለም አቀፍ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን (IFC) ጋር በመተባበር 100 ቢሊዮን ብር ካፒታል ያለው የመጀመሪያውን የቤት መግዣ ብድር መልሶ ማጠናከሪያ ኩባንያ መስርቷል።
ከዚሁ ታሪካዊ የስምምነት እና አዲስ ተቋም መመስረት ጋር ተያይዞ የወጡ ዋና ዋና መረጃዎች፦
📌 የIFC አስተዋፅኦ፦ በዚሁ ስምምነት መሠረት IFC የ200 ሚሊዮን ዶላር አስተዋፅኦ ያደርጋል።
📌 የተቋሙ ፋይዳ፦ ተቋሙ በባንክ ዘርፍ ያለውን የጥሬ ገንዘብ ፍሰት አለመመጣጠን በመቅረፍ በመላ አገሪቱ ተደራሽ የሆነ የቤት ፋይናንስ ስርዓት እንደሚዘረጋ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ አስታውቀዋል።
📌 ግብ፦ ይህ አጋርነት በተመጣጣኝ ዋጋ የሚገነቡና የኢትዮጵያውያንን ክብር የጠበቁ 1 ነጥብ 5 ሚሊዮን ቤቶችን ለማቅረብ ያለውን ግብ ለማሳካት ያለመ ነው።
📌 ተጨማሪ ጥቅሞች፦ በፋይናንስ ሥርዓቱ ውስጥ የግል ዘርፉን ተሳትፎ ለማስፋት ያለውን ግብ እንደሚያሳካና ኢትዮጵያ ፈጣን፣ ጠንካራ እና ሁሉንም ያካተተ ኢኮኖሚ መገንባቷን አጠናክራ እንደምትቀጥልም ጠቅላይ ሚኒስትሩ አጽንኦት ሰጥተዋል።
#አብይአሕመድ #abiyahmed #ethiopia
@ethioaradarinfo | 274 |
| 4 | በአዲስ አበባ ከተማ ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ 1 ልዩ ቦታው «ቻይና ካምፕ» አካባቢ በቤት ሰራተኝነት ተቀጥራ መስራት በጀመረች በ4ኛው ቀን አሰሪዎቿ በተኙበት አጋጣሚ ቻርጅ ላይ የነበረ 85 ሺህ ብር የሚገመት አልትራ S21 ሞባይል እና የተለያዩ አልባሳትን ሰርቃ የተሰወረችው ተከሳሽ መልካም አያልነህ በፍርድ ቤት በጽኑ እስራት ተቀጣች።
የጅማ በር አካባቢ ፖሊስ መምሪያ የምርመራና ክትትል ቡድን በማቋቋም ባደረገው ብርቱ ጥረት ተከሳሿን ከተሰወረችበት ቦታ በአጭር ጊዜ ውስጥ በቁጥጥር ስር በማዋል የተሰረቀውን ሞባይል ማስመለስ ችሏል። በግለሰቧ ላይ አስላጊውን ምርመራ ከተጣራ በኃላም የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ኮልፌ ቀራንዮ ምድብ ፈጣን ወንጀል ችሎት ጥፋተኝነቷን በሰውና በሰነድ ማስረጃዎች በማረጋገጥ፣ ተከሳሿን በ5 አመት ከ7 ወር ፅኑ እስራት እንድትቀጣ ውሳኔ አስተላልፎባታል።
ፖሊስ በቤት ሰራተኝነት ከተቀጠሩ በኋላ መሰል ወንጀሎችን ፈፅመው የሚሰወሩ በመኖራቸው አሰሪዎች የቅርብ ክትትል ከማድረግ ጀምሮ ለንብረታቸው አስፈላጊውን ጥንቃቄ ማድረግ እንዳለባቸው አሳስቧል
@ethioradarinfo | 437 |
| 5 | አባይ ቲቪ
የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለስልጣን በአባይ ቴሌቪዥን ላይ ጠንከር ያለ ማስጠንቀቂያ መስጠቱን አስታወቀ።
ባለስልጣን መሥሪያ ቤቱ ባለፉት ሦስት ወራት ባደረገው የቅርብ ክትትል፣ ጣቢያው በዜናዎቹና በፕሮግራሞቹ ላይ ከባድ የሕግና የሙያ ስነ-ምግባር ጥሰቶችን መፈጸሙን ደርሼበታለሁ ብሏል።
ባለስልጣኑ የዘገባቸው ዋና ዋና የጥሰት ነጥቦች፦
📌 የህግና የስነ-ምግባር ጥሰቶች፦ ከባህላችን ያፈነገጡ ፀያፍ ንግግሮችን ማሰራጨት፣ የሴቶችን ክብር የሚነኩ ይዘቶችን ማቅረብ እና ያልተረጋገጡ የዜና ምንጮችን መጠቀም በጣቢያው ላይ ከተመዘገቡት ዋና ዋና ጥሰቶች መካከል ይጠቀሳሉ።
📌 የጣቢያው ምላሽ፦ የቴሌቪዥን ጣቢያው ኃላፊዎች የተፈጸሙትን ጥፋቶች አምነው ይቅርታ የጠየቁ ሲሆን፣ ችግሮቹን ለማስተካከልና በአፋጣኝ አስፈላጊውን እርምጃ ለመውሰድ ቃል ገብተዋል።
@ethioradarinfo | 406 |
| 6 | ከእስር የሚፈታ ታራሚ አይኖርም ❗️
አዲስ ዓመት በመጣ ቁጥር በርካታ ቤተሰቦች "ዘመዶቻችን በበዓሉ ምክንያት ከእስር ይፈቱልናል" ብለው ተስፋ የሚያደርጉ ቢሆንም፣ የፍትሕ ሚኒስቴር ያሰማው ዜና ግን ለብዙዎች አስደንጋጭ ሆኗል።
ሚኒስቴሩ ለመናኸሪያ ሬዲዮ በሰጠው ማብራሪያ እንደገለጸው፤ በዓላትን ምክንያት በማድረግ ብቻ በይቅርታ የሚፈታ አንድም ታራሚ የለም። "ይቅርታ" የሚደረገው በአዲሱ መመሪያ መሠረት በይቅርታ ቦርድ ተመርምሮ ሲወሰን ብቻ እንደሆነ ተብራርቷል።
ብዙዎቻችን "ምህረት" እና "ይቅርታ" አንድ ይመስለናል። ነገር ግን ምህረት ከፍተኛ የፖለቲካ ውሳኔ ሲሆን፣ ይቅርታ ግን ጥብቅ የሆነ ሕጋዊ አካሄድና መመሪያን የተከተለ አሰራር አለው።በሌላ በኩል፣ ክልሎች በራሳቸው ርዕሳነ-መስተዳድሮች አማካኝነት ታራሚዎችን ሊፈቱ እንደሚችሉ ተጠቁሟል።
@ethioradarinfo | 583 |
| 7 | Matn yo'q... | 512 |
| 8 | ተገቢውን የጉምሩክ ሂደት ያላለፉና በህገ-ወጥ መንገድ ወደ ሀገር ውስጥ የገቡ የተለያዩ ዓይነትና መጠን ያላቸው ከ700 በላይ የሞባይል ቀፎዎች፣ ከሁለት ሺህ በላይ የቻርጀር ገመዶች፣ ልዩ ልዩ የኤሌክትሮኒክስ መለዋወጫዎችና አልበሳት በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ፖሊስ አስታወቀ።
ከዚሁ የኮንትሮባንድ እገታ ጋር ተያይዞ የወጡ ዋና ዋና መረጃዎች፦
📌 የተያዙበት ቦታና ሰዓት፦ በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ፖሊስ ዋና መምሪያ የመሣለሚያ አካባቢ ፖሊስ መምሪያ ነሐሴ 20 ቀን 2018 ዓ.ም በክፍለ ከተማው ወረዳ 8 ልዩ ቦታው «አዲስ አበባ የገበያ ማዕከል» አካባቢ ከምሽቱ 1፡00 ሠዓት ላይ ነው እቃዎቹ የተያዙት።
📌 ተጠርጣሪዎቹና የተጠቀሙበት ተሽከርካሪ፦ አሰፋ ጸጋ እና አማኑኤል ብርሀኑ የተባሉ ሁለት ተጠርጣሪዎች የኮንትሮባንድ ዕቃዎቹን የሠሌዳ ቁጥር B-77746 አ.አ በሆነ «ሱዙኪ» የጭነት ተሽከርካሪ ጭነው ሲንቀሳቀሱ በሥራ ላይ በነበሩ የፖሊስ አባላት በቁጥጥር ስር ውለዋል።
📌 የሕግ ሂደትና የፖሊስ መልዕክት፦ የክፍለ ከተማው ፖሊስ ዋና መምሪያ በተጠርጣሪዎቹ ላይ ተገቢውን የሰውና የሰነድ ማስረጃ በማደራጀት ክስ እንደሚያስመሰርት ገልጻል። ህብረተሰቡም መሰል የወንጀል ድርጊቶች በሀገር ምጣኔ ሀብትና በህጋዊ ነጋዴዎች ላይ የሚያሳድሩትን አሉታዊ ተፅዕኖ በመረዳት መረጃ የመስጠት ባህሉን ሊያጠናክር እንደሚገባ የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ መልዕክቱን አስተላልፏል።
@ethioradarinfo | 480 |
| 9 | ያለ አምራችነት ፈቃድ በመንደሮች በሚገኙ ሱቆች እና የንግድ ቦታዎች የሚመረት የለውዝ ቅቤ የጥራት እና የጤና ምርመራ ስለማይደረግለት ለጤና ችግር የመዳረግ እድሉ ከፍተኛ መሆኑን የኢትዮጵያ የለውዝ ቅቤ አምራቾች ማኅበር እና የኢትዮጵያ ደረጃዎች ኢንስቲትዩት አስታውቀዋል።
ከዚሁ አሳሳቢ የጤና እና የጥራት ማስጠንቀቂያ ጋር ተያይዞ የወጡ ዋና ዋና መረጃዎች፦
📌 የጤና ስጋቱ እና «አፍላቶክሲን»፦ የማኅበሩ ተወካይ አቶ ተስፋዬ አስራት ለአሐዱ ሬዲዮ እንደገለጹት፤ ለውዝ «አፍላቶክሲን» በተባለ መርዛማ ሻጋታ የመጠቃት እድሉ ከፍተኛ በመሆኑ ከእርሻ ጀምሮ ጥብቅ ቁጥጥር ይፈልጋል። በየመንደሩ የሚፈጨው ለውዝ ከምርት ስብሰባ ጀምሮ ሲቆላም ሆነ ሲፈጭ ተገቢው ጥንቃቄ ካልተደረገለት ካንሰርን ጨምሮ ለተለያዩ ከባድ የጤና እክሎች ያጋልጣል።
📌 የማኅበራዊ ሚዲያ ማስታወቂያዎች፦ በቲክቶክ እና በሌሎች ማኅበራዊ ትስስር ገጾች በሱቆች የሚጨመቀውን የለውዝ ቂቤ ለማስተዋወቅ ሲባል የሕጋዊ ድርጅቶችን ስም በማጥፋት የንግድ ጉዳት የሚያደርሱ ያልተገቡ ማስታወቂያዎች እየተስፋፉ በመሆኑ ፈጻሚዎች ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ ተጠይቋል።
📌 የኢንስቲትዩቱ አዲስ አሰራር፦ የኢትዮጵያ ደረጃዎች ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ዶክተር መሰረት በቀለ፤ አብዛኛዎቹ ተጠቃሚዎች እና አምራቾች ስለ «አፍላቶክሲን» በቂ ግንዛቤ እንደሌላቸው ገልጸው፣ ችግሩን ለመፍታት ኢንስቲትዩቱ ለአምራቾች የሙያ የብቃት ማረጋገጫ ለመስጠት ዝግጅት ማጠናቀቁን ተናግረዋል።
📌 አስገዳጅ መስፈርቶች፦ ወደፊት ማንኛውም አምራች የንግድ ፈቃድ ከመውጣቱ በፊት የብቃት ማረጋገጫ ማግኘቱ አስገዳጅ እንደሚሆንና፤ ምርቶች ለገበያ ከመቅረባቸው በፊት የመቆያ ጊዜያቸው፣ የአገልግሎት ማብቂያቸው፣ የተሠሩበት አድራሻ እና የአጠቃቀም መመሪያዎች በግልጽ ሊካተቱባቸው እንደሚገባ ታውቋል። | 472 |
| 10 | Matn yo'q... | 507 |
| 11 | ያለ አምራችነት ፈቃድ በመንደሮች በሚገኙ ሱቆች እና የንግድ ቦታዎች የሚመረት የለውዝ ቅቤ የጥራት እና የጤና ምርመራ ስለማይደረግለት ለጤና ችግር የመዳረግ እድሉ ከፍተኛ መሆኑን የኢትዮጵያ የለውዝ ቅቤ አምራቾች ማኅበር እና የኢትዮጵያ ደረጃዎች ኢንስቲትዩት አስታውቀዋል።
ከዚሁ አሳሳቢ የጤና እና የጥራት ማስጠንቀቂያ ጋር ተያይዞ የወጡ ዋና ዋና መረጃዎች፦
📌 የጤና ስጋቱ እና «አፍላቶክሲን»፦ የማኅበሩ ተወካይ አቶ ተስፋዬ አስራት ለአሐዱ ሬዲዮ እንደገለጹት፤ ለውዝ «አፍላቶክሲን» በተባለ መርዛማ ሻጋታ የመጠቃት እድሉ ከፍተኛ በመሆኑ ከእርሻ ጀምሮ ጥብቅ ቁጥጥር ይፈልጋል። በየመንደሩ የሚፈጨው ለውዝ ከምርት ስብሰባ ጀምሮ ሲቆላም ሆነ ሲፈጭ ተገቢው ጥንቃቄ ካልተደረገለት ካንሰርን ጨምሮ ለተለያዩ ከባድ የጤና እክሎች ያጋልጣል።
📌 የማኅበራዊ ሚዲያ ማስታወቂያዎች፦ በቲክቶክ እና በሌሎች ማኅበራዊ ትስስር ገጾች በሱቆች የሚጨመቀውን የለውዝ ቂቤ ለማስተዋወቅ ሲባል የሕጋዊ ድርጅቶችን ስም በማጥፋት የንግድ ጉዳት የሚያደርሱ ያልተገቡ ማስታወቂያዎች እየተስፋፉ በመሆኑ ፈጻሚዎች ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ ተጠይቋል።
📌 የኢንስቲትዩቱ አዲስ አሰራር፦ የኢትዮጵያ ደረጃዎች ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ዶክተር መሰረት በቀለ፤ አብዛኛዎቹ ተጠቃሚዎች እና አምራቾች ስለ «አፍላቶክሲን» በቂ ግንዛቤ እንደሌላቸው ገልጸው፣ ችግሩን ለመፍታት ኢንስቲትዩቱ ለአምራቾች የሙያ የብቃት ማረጋገጫ ለመስጠት ዝግጅት ማጠናቀቁን ተናግረዋል።
📌 አስገዳጅ መስፈርቶች፦ ወደፊት ማንኛውም አምራች የንግድ ፈቃድ ከመውጣቱ በፊት የብቃት ማረጋገጫ ማግኘቱ አስገዳጅ እንደሚሆንና፤ ምርቶች ለገበያ ከመቅረባቸው በፊት የመቆያ ጊዜያቸው፣ የአገልግሎት ማብቂያቸው፣ የተሠሩበት አድራሻ እና የአጠቃቀም መመሪያዎች በግልጽ ሊካተቱባቸው እንደሚገባ ታውቋል። | 1 |
| 12 | ''አለሁ''
ከሰሞኑ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አሕመድ ከመገናኛ ብዙኃን ራቅ ማለታቸውን ተከትሎ የተለያዩ የሐሰት ዜናዎች ሲሰራጭ ሰንብቷል። በዛሬው እለት ብልጽግና ፓርቲ በይፋዊ የቲክቶክ ገጹ ለሰሞንኛው አጀንዳ መልስ የሚመስል ቪዲዮ ለቋል። በቪዲው ላይም ጠቅላይ ሚኒስትሩ! "አለሁ እግዚአብሔር ይመስገን" በማለት ሲናገሩ ተሰምተዋል።
@ethioradarinfo | 778 |
| 13 | የምሽቱ ትልቁን ፍልሚያ ጆኒ አሸነፈ
በዓድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም በታላቅ ድምቀት ሲካሄድ የሰነበተው የኢቲኤፍሲ 2 (ETFC 2) ኮከቦች ምሽት በጉጉት በተጠበቀውና በዋናው የዋንጫ ፍልሚያ (Main Event) በይፋ ፍጻሜ አግኝቷል!
በሚድል ዌይት (Middleweight MMA Bout) ዘርፍ በጆኒ እና በሴዶ መካከል የተደረገው ይህ አስደናቂና አቃጣጣኝ ፍልሚያ የመላው ተመልካች ቀልብ የሳበ ነበር።
በከፍተኛ የኤምኤምኤ (MMA) ቴክኒክ፣ የላቀ ብቃትና ፍጹም የድል ወኔ ተጋጣሚውን ሴዶን ያሸነፈው ጆኒ፡ የምሽቱን ትልቅ ድል በመቀዳጀት አዲሱ የ ETFC 2 ቻምፒዮን (Champion) በመሆን ዘውዱን ደፍቷል!
#ዳጉ_ጆርናል | 990 |
| 14 | በጆኒ አሸናፊነት ተጠናቀቀ‼ | 719 |
| 15 | 10ኛው ፍልሚያ በኢድሪስ አሸናፊነት ተጠናቀቀ!
በዓድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም እየተካሄደ በሚገኘው የኢቲኤፍሲ 2 (ETFC 2) ምሽት፣ በዕለቱ አሥረኛው ፍልሚያ በኤምኤምኤ (MMA Bout) ዘርፍ በኢድሪስ እና በቦይካ መካከል የተደረገው አቃጣጣኝ ፍልሚያ በይፋ ፍጻሜ አግኝቷል።
ብቃትና ወኔ በተሞላው በዚህ ግጥሚያ ኢድሪስ ተጋጣሚውን ቦይካን በማሸነፍ ሌላኛውን ደማቅ ድል አስመዝግቧል!
#ዳጉ_ጆርናል | 675 |
| 16 | ንቃተ ህሊና ፍልሚያ አሸነፏል
በዓድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም እየተካሄደ በሚገኘው የኢቲኤፍሲ 2 (ETFC 2) ምሽት፣ በዕለቱ ዘጠነኛው ፍልሚያ በኤምኤምኤ (MMA Bout) ዘርፍ በሮቤል እና በንቃተ ህሊና መካከል የተደረገው አቃጣጣኝ ፍልሚያ በይፋ ፍጻሜ አግኝቷል።
በከፍተኛ ቴክኒክ፣ ብቃትና ወኔ በተሞላው በዚህ ግጥሚያ ንቃተ ህሊና ተጋጣሚውን ሮቤልን በማሸነፍ ሌላኛውን ደማቅ ድል አስመዝግቧል!
@ethioradarinfo | 511 |
| 17 | ስምንተኛው ፍልሚያ በኤሌዘር (Elezar) አሸናፊነት ተጠናቀቀ!
በዓድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም እየተካሄደ በሚገኘው የኢቲኤፍሲ 2 (ETFC 2) ምሽት፣ በዕለቱ ስምንተኛ ፍልሚያ በ 75 ኪሎ ግራም የኤምኤምኤ (MMA Bout) ዘርፍ በኤሌዘር እና በቃላብ መካከል የተደረገው አቃጣጣኝ ፍልሚያ በይፋ ፍጻሜ አግኝቷል።
በከፍተኛ ቴክኒክ፣ ብቃትና ወኔ በተሞላው በዚህ ግጥሚያ ኤሌዘር ተጋጣሚውን ቃላብን በማሸነፍ ሌላኛውን ደማቅ ድል አስመዝግቧል!
#ዳጉ_ጆርናል | 436 |
| 18 | ረቢቅ 🏆
በዓድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም እየተካሄደ በሚገኘው የ ኢቲኤፍሲ 2 (ETFC 2) ምሽት፣ በዕለቱ ሰባተኛ ፍልሚያ በሙአይ ታይ (Muay Thai Match) ዘርፍ በኢትዮጵያዊው ተዋጊ በረቢቂ (Rebik) እና በደቡብ ሱዳናዊው ተዋጊ ስቲፈን (Stephen) መካከል የተደረገው ዓለም አቀፋዊ ፍልሚያ በይፋ ፍጻሜ አግኝቷል።
በከፍተኛ ቴክኒክ፣ ብቃትና ወኔ በተሞላው በዚህ ግጥሚያ ተዋጊ ረቢክ ተጋጣሚውን ስቲፈንን በማሸነፍ ለሀገሩ ኢትዮጵያ ሌላኛውን ደማቅ ድል አስመዝግቧል!
@ethioradarinfo | 696 |
| 19 | አምስተኛው ፍልሚያ በመስፍን አሸናፊነት ተጠናቀቀ
በዓድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም እየተካሄደ በሚገኘው የ ኢቲኤፍሲ 2 (ETFC 2) ምሽት፣ በ 71 ኪሎ ግራም የቦክስ ዘርፍ በመስፍን እና በአቤኔዘር መካከል የተደረገው አምስተኛው የዕለቱ ፍልሚያ በይፋ ፍጻሜ አግኝቷል።
በከፍተኛ ቴክኒክ፣ ብቃትና ጥንካሬ በተሞላው በዚህ ፍልሚያ ተዋጊ መስፍን ብሩ ተጋጣሚውን አቤኔዘርን በማሸነፍ የምሽቱን ታላቅ ድል ተቀዳጅቷል!
#ዳጉ_ጆርናል | 544 |
| 20 | ዛሬ ተጠባቂው የኤምኤምኤ (MMA) ፋይት ይደረጋል። በዚህ ውድድር ላይ ሴዶ እና ጆኒ ተጠባቂ ናቸው።ማን ሊያሸንፍ ይችላል? በኢሞጅዎቹ ግምትዎን ያስቀምጡ።
ጆኒ ❤️ ሴዶ 👏 | 547 |
