Ethio Radar|ኢትዮ ራዳር
Welcome to Ethio Radar, a professional news analysis platform brought to you by a dedicated team of experienced journalist. stay informed,stay on radar! እንኳን ወደ ኢትዮ ራዳር ቻናል መጡ,ሀሳብ፣አስተያየት፣ መረጃ ለማጋራት ማስታወቂያ ለማሰራት በ @Ethioradarr01 ያናግሩን
Показати більше📈 Аналітичний огляд Telegram-каналу Ethio Radar|ኢትዮ ራዳር
Канал Ethio Radar|ኢትዮ ራዳር (@ethioradarinfo) у мовному сегменті Амхарська є активним учасником. На даний момент спільнота об'єднує 56 561 підписників, посідаючи 176 місце в категорії Маркетинг і PR та 566 місце у регіоні Ефіопія.
📊 Показники аудиторії та динаміка
З моменту свого створення невідомо, проект продемонстрував стрімке зростання, зібравши аудиторію у 56 561 підписників.
За останніми даними від 29 липня, 2026, канал демонструє стабільну активність. Хоча за останні 30 днів спостерігається зміна кількості учасників на -1 843, а за останні 24 години на -81, загальне охоплення залишається високим.
- Статус верифікації: Не верифікований
- Рівень залученості (ER): Середній показник залученості аудиторії становить 1.48%. Протягом перших 24 годин після публікації контент зазвичай збирає 0.81% реакцій від загальної кількості підписників.
- Охоплення публікацій: В середньому кожен допис отримує 836 переглядів. Протягом першої доби публікація в середньому набирає 459 переглядів.
- Реакції та взаємодія: Аудиторія активно підтримує контент: середня кількість реакцій на один пост – 5.
📝 Опис та контентна політика
Автор описує ресурс як майданчик для висловлення суб'єктивної думки:
“Welcome to Ethio Radar, a professional news analysis platform brought to you by a dedicated team of experienced journalist.
stay informed,stay on radar!
እንኳን ወደ ኢትዮ ራዳር ቻናል መጡ,ሀሳብ፣አስተያየት፣ መረጃ ለማጋራት ማስታወቂያ ለማሰራት በ @Ethioradarr01 ያናግሩን”
Завдяки високій частоті оновлень (останні дані отримано 30 липня, 2026), канал підтримує актуальність та високий рівень охоплення публікацій. Аналітика показує, що аудиторія активно взаємодіє з контентом, що робить його важливою точкою впливу в категорії Маркетинг і PR.
Триває завантаження даних...
| Дата | Залучення підписників | Згадування | Канали | |
| 30 липня | 0 | |||
| 29 липня | 0 | |||
| 28 липня | 0 | |||
| 27 липня | 0 | |||
| 26 липня | 0 | |||
| 25 липня | 0 | |||
| 24 липня | 0 | |||
| 23 липня | 0 | |||
| 22 липня | 0 | |||
| 21 липня | 0 | |||
| 20 липня | 0 | |||
| 19 липня | 0 |
| 2 | አደገኛው አዘዋዋሪ በቁጥጥር ስር ዋለ
የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ከኢንተርፖል እና ከማላዊ ፖሊስ ጋር ባደረገው የተቀናጀ አደገኛ ወንጀለኞችን የማደን ዘመቻ፣ በበርካታ ወጣቶች ላይ ከባድ ኢሰብአዊ ድርጊት ሲፈጽም የቆየውን አደገኛ ሕገ-ወጥ የሰዎች አዘዋዋሪ አድነው ባሻው ውዳሞን በማላዊ በቁጥጥር ሥር ውሎ ወደ ሀገር እንዲመጣ መደረጉን አስታወቀ።
በፖሊስ መግለጫ መሠረት የተጠርጣሪው ዘግናኝ ድርጊቶች እና የቁጥጥር ስራ ሂደቶች የሚከተሉት ናቸው፦
📌 የማታለያ ዘዴው፦ ተጠርጣሪው ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል (ከሀድያ እና ከንባታ አከባቢዎች) ወጣቶችን ወደ ደቡብ አፍሪካ ለማሻገር በሚል እስከ 800 ሺህ ብር እየጠየቀ ሲያታልል ቆይቷል።
📌 የፈጸመው ኢሰብአዊ ድርጊት፦ ተጓዦችን በኬንያና ታንዛኒያ በኩል በኮንቴነር አጭቆ በመጫን፣ በየጫካው ጥሎ በመጥፋት፣ በረሃብና በኤሌክትሪክ ንዝረት በማሰቃየት እንዲሁም ከቤተሰቦቻቸው ገንዘብ በማስፈራራት ሲቀበል እንደነበር ተገልጿል።
📌 ለሀገር አሳልፎ መሰጠት፦ ከ2015 ዓ.ም ጀምሮ ሲደረግ በቆየ ጥብቅ ክትትል ማላዊ ውስጥ በቁጥጥር ሥር የዋለው ተጠርጣሪው፣ ሐምሌ 22 ቀን 2018 ዓ.ም ለኢትዮጵያ አሳልፎ ተሰጥቷል።
የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ መሰል አደገኛ ሕገ-ወጥ የሰው አዘዋዋሪዎችንና ወንጀለኞችን የማደኑን ተግባር አጠናክሮ እንደሚቀጥል በመግለጽ፣ ህብረተሰቡ መሰል ድርጊቶችን ሲመለከት በነፃ ስልክ መስመር 991 ወይም በ EFPApp ጥቆማ እንዲሰጥ ጥሪ አቅርቧል።
#ethioradae | 85 |
| 3 | Немає тексту... | 1 |
| 4 | የግብር ጭማሪ የነጋዴዎችን እንባ አሰማ
በአዲስ አበባ እና በተለያዩ የክልል ከተሞች የሚገኙ የቁርጥ ግብር ከፋዮች፣ ለ2018 ግብር ዘመን የተጣለባቸው የክፍያ መጠን ከሚችሉት በላይ እንደሆነባቸው በመግለጽ ጥብቅ ቅሬታቸውን በማቅረብ ላይ ይገኛሉ።
በርካታ ነጋዴዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል፣ የተቆረጠባቸው ግብር ከአምናው ጋር ሲነጻጸር የሰማይና ምድር ያህል መራራቁን አጋልጠዋል፦
📌 የአንድ ጀምበር ጭማሪ፦ ከዚህ ቀደም ከ15 እስከ 25 ሺህ ብር ይከፍሉ የነበሩ ነጋዴዎች አሁን ላይ እስከ 180 ሺህ ብር፣ እንዲሁም ከ12 ሺህ ብር የነበረው ወደ 110 ሺህ ብር እንዲከፍሉ መታዘዛቸውን በምሬት ተናግረዋል።
📌 "በዘፈቀደ የተደረገ ግምገማ"፦ ነጋዴዎቹ እንደሚያስረዱት ከሆነ ግብሩ የተወሰነው በቦታው ላይ በተደረገ ተጨባጭ የንግድ እንቅስቃሴ ወይም የገቢ እድገት ጥናት ሳይሆን በዘፈቀደና በደፈናው ነው።
📌 የመታሸግ ስጋትና የእንግልት አሰራር፦ የተጣለባቸውን ከፍተኛ ገንዘብ ወዲያውኑ ካልከፈሉ የንግድ ሱቆቻቸው እንደሚታሸጉ እንደተነገራቸው የጠቀሱት አቤቱታ አቅራቢዎቹ፣ ቅሬታቸውን ለማስመዝገብ የሚሄዱበት የአቤቱታ ሂደትም በራሱ ሌላው ትልቅ እንግልት እንደሆነባቸው ገልጸዋል።
ይህ ያልተመጣጠነ የግብር ጭማሪ ከንግድ ውጭ እንደሚያደርጋቸውና ሰርቶ ለማደር ከፍተኛ ፈተና እንደደቀነባቸው የሚናገሩት ነጋዴዎቹ፤ የሚመለከተው የመንግሥት አካል የንግድ አቅማቸውን ባገናዘበ መልኩ በአስቸኳይ ውሳኔውን እንዲያስተካክልላቸውና መፍትሔ እንዲሰጣቸው ተማፅነዋል።
#ethioradar | 285 |
| 5 | ነገ በበርካታ አካባቢዎች የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት ይቋረጣል!
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የጥገና ሥራ ለማከናወን ነገ ሐምሌ 23 ቀን 2018 ዓ.ም በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች የኃይል አቅርቦት ለተወሰነ ሰዓት እንደሚቋረጥ አስታውቋል።
በዚህም መሠረት የኃይል መቋረጡ የሚካሄድባቸው ሰዓታት እና አካባቢዎች የሚከተሉት ናቸው፦
ከጠዋቱ 4፡00 – 10፡00
• ኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት፣ ችሎት አደባባይ፣ ዘበኛ ሰፈር፣ ሾላ፣ ሰሜን ሆቴል ጫፍ፣ ቀለመወርቅ ት/ቤት፣ ዶሮ ተራ፣ ራስ ደስታ፣ አርበኞች ት/ቤት እና አካባቢያቸው።
• ዕንቁላል ፋብሪካ፣ ሀግቤስ አራት መንታ፣ ጎጃም በረንዳ፣ ጅንአድ፣ አበበች ጎበና፣ ቄጤማ ተራ፣ ፓስተር አደባባይ፣ አቤት ሆስፒታል፣ ቅዱስ ዮሐንስ ቤተክርስቲያን፣ ዳትሰን ሰፈር፣ ሰን ሆቴል እና አካባቢያቸው።
• 3ኛ ፖሊስ ጣቢያ፣ አዲስ አበባ ሜዲካል ኮሌጅ፣ ተክለሃይማኖት ቤተክርስቲያን፣ አትክልት ተራ፣ ጣሊያን ሰፈር፣ ፒያሳ (በከፊል)፣ ማዘጋጃ ቤት፣ አውቶብስ ተራ እና አካባቢያቸው።
• ማርቆስ መጋዘን፣ ቀጨኔ 8 ቁጥር ማዞሪያ፣ ቀጨኔ 1ኛ፣ 2ኛ እና 3ኛ መንገድ፣ ይመር ውኃ፣ መቀጠያ፣ 19 ታቦት ማደሪያ፣ መታፈሪ ሰፈር፣ ጴጥሮስ ሆስፒታል፣ ሽሮ ሜዳ እና አካባቢያቸው።
ከጠዋቱ 2፡00 – 10፡00
• አያት ለገጣፎ ሰብስቴሽን ፊትለፊት ያሉ ኮንዶሚኒየሞች፣ ክቡርደመና፣ ሰላም ቪሌጅ፣ ጣፎ ገብርኤል፣ ጋሪ ተራ፣ ባጃጅ ተራ እና አካባቢያቸው።
ከጠዋቱ 3፡00 – 10፡30
• ገላን፣ አራብሳ፣ እንጀራ ማምረቻ ፋብሪካ፣ ፕሮጀክት 13 አራብሳ ወታደር ሰፈር፣ ነጋ ቦንገር፣ ጀሶ ፋብሪካ፣ ብሔረፅጌ ቆዳ ፋብሪካ፣ ፓስታና መኮረኒ ፋብሪካ እና አካባቢያቸው።
• አባ ሳሙኤል፣ አቡሴራ፣ ሉግና፣ ዱፍና፣ ደበራ ጢኖ፣ ሻሸመኔ፣ ዱከም፣ በላይነህ ክንዴ፣ በስተቀኝ ያሉ ኢንዱስትሪዎች፣ ካፍ ማደያ እና አካባቢያቸው።
ከጠዋቱ 4፡30 – 11፡00
• መቐለ (ላቺ በከፊል)፣ ሀምዲያ ኢንዱስትሪ ዞን፣ ቀበሌ 03፣ ባህርዳር (አዲስ ዓለም)፣ ኦቪድ፣ ሰማኤታ፣ ሚሊኒየም ት/ቤት እና አካባቢያቸው።
ከጠዋቱ 1፡00 – 6፡00
• ወልዲያ፣ ይምርሃነ ክርስቶስ፣ ቢልባላ፣ ቂርቆስ፣ ሳሬዜና፣ ሶርባ፣ ላሊበላ፣ ገነተ ማርያም፣ ዘሃ፣ ሙቅ ውኃ፣ ተከዜ ገዳሜ፣ ኢርፋ ገለሶቴ እና አካባቢያቸው።
• ቅዱስ አርቢ፣ ዳቦ ከተማ፣ ቡርኮ፣ አይና ሚካኤል፣ ጭሮ፣ ሜኤሶ፣ አሰቦት እና አካባቢያቸው።
በመሆኑም በተጠቀሱት አካባቢዎች የምትገኙ ደንበኞች የጥገና ሥራው እስኪጠናቀቅ እና የኃይል አቅርቦቱ ወደ መደበኛ ሁኔታው እስኪመለስ ድረስ በትዕግስት እንዲጠብቁ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ጠይቋል። | 426 |
| 6 | ተበዳሪዎች ላይ ቅጣት ሊጣል ነው
ዳሸን ባንክ እና ኢትዮ ቴሌኮም በቴሌብር መተግበሪያ አማካኝነት የወሰዱትን የዲጂታል ፋይናንሲንግ ብድር በተቀመጠው የጊዜ ገደብ ያልከፈሉ ተበዳሪዎች ላይ ህጋዊ እርምጃ መውሰድ መጀመራቸውን እና በተለያዩ ፍርድ ቤቶች ክስ እየመሰረቱ እንደሚገኙ አስታወቁ።
ባንኩ ባወጣው መግለጫ እንዳመለከተው፦
📌 ተበዳሪዎች ያለባቸውን ውዝፍ ዕዳ እንዲከፍሉ በተደጋጋሚ ማስጠንቀቂያ ሲሰጥ የቆየ ቢሆንም፣ ከዚህ ቀደም የተደረገውን የቅጣት ክፍያ ምሕረት ተጠቅመው ዕዳቸውን ባልከፈሉ አካላት ላይ የሕግ አካሄድ ተጀምሯል።
📌 አስቀድሞ ለቀረበላቸው ጥሪ ምላሽ ያልሰጡ ተበዳሪዎች ላይ በፍርድ ቤት ክስ ተመስርቶ ከዋናው ዕዳ በተጨማሪ ባንኩ ለክስ ያወጣቸውን ልዩ ልዩ ወጪዎች እንዲሸፍኑ ውሳኔ እየተሰጠ ይገኛል።
ዳሸን ባንክ አክሲዮን ማህበር የሕዝብ ገንዘብ ለማስመለስ የጀመረውን ህጋዊ እርምጃ አጠናክሮ እንደሚቀጥል በመጠቆም፣ እስካሁን የክስ መጥሪያ ያልደረሳቸው ተበዳሪዎች ጉዳዩ ወደ ፍርድ ቤት ከመሄዱ እና ተጨማሪ አላስፈላጊ እንግልት እንዲሁም ወጪ ሳይደርስባቸው ያለባቸውን ዕዳ በአስቸኳይ እንዲከፍሉ ጥብቅ ማሳሰቢያ አስተላልፏል።
#ethioradar | 454 |
| 7 | በሀገራዊ የምክክር ጉባኤ የሀገር ግንባታ አጀንዳ ላይ በተደረገው ውይይት፣ የሀገሪቱን የቋንቋ አጠቃቀም በተመለከተ በርካታ ዋና ዋና ምክረ ሀሳቦች ቀርበዋል።
በቀረበው ምክረ ሀሳብ መሠረት፦
📌 የፌዴራል የሥራ ቋንቋዎች፦ አማርኛ፣ ኦሮምኛ፣ ትግርኛ፣ አፋርኛ እና ሶማሊኛ የፌዴራል የሥራ ቋንቋዎች እንዲሆኑ ተጠቅሷል።
📌 ብሔራዊ ቋንቋ፦ አማርኛ ብሔራዊ ቋንቋ ሆኖ እንዲቀጥል የሚል ሀሳብ የተነሳ ሲሆን፣
📌 የውጭ ቋንቋዎች፦ እንግሊዝኛ፣ አረብኛ፣ ፈረንሳይኛ እና ቻይንኛን የመሳሰሉ የውጭ ቋንቋዎች በሥርዓተ ትምህርት እንዲካተቱ ወይም የሥራ ቋንቋ እንዲሆኑ የቀረበው ሀሳብ "የሀገር ውስጥ ቋንቋዎችን ያጠፋል" በሚል ስጋት ከፍተኛ ክርክር አስነስቷል።
በአሁኑ ወቅት እነዚህ የቀረቡት ምክረ ሀሳቦች በ4 ሺህ የጉባኤው ተሳታፊዎች ሰፊ ውይይት እየተደረገባቸው የሚገኝ ሲሆን፣ በመጨረሻም ውሳኔ የሚሰጥባቸው መሆኑ ተገልጿል።
#ethioradar | 484 |
| 8 | ቴምር ፕሮፐርቲስ #Temir_Properties
💥 አዲስ የቤት ባለቤት የሚሆኑበት ወርቃማ ዕድል በሳርቤት አደባባይ!
#09-90-22-09-02
በከተማዋ እምብርት ሳርቤት አደባባይ ላይ እጅግ ዘመናዊና ምቹ የሆኑ የመኖሪያ አፓርትመንቶችን ለሽያጭ አቅርቧል።
✨ 3B + G + 23
👉 100% ሙሉ ክፍያ =30% ልዩ ቅናሽ
👉20% ቅድመ ክፍያ — ቀሪውን በሒደት የሚከፍሉበት ምቹ ሁኔታ።
✅ የካሬ አማራጮች:
🔥ባለ 1 መኝታ: 73 ካሬ
👍ጠቅላላ ዋጋ=8,760,000
👍ቅ/ክፍያ(20%) =1,752,000
✅ሙሉ ለሚከፍል =6,132,000
➡️: 93 ካሬ
👍ጠቅላላ ዋጋ=11,160,000
👍ቅ/ክፍያ(20%) =2,232,000
✅ሙሉ ለሚከፍል =7,812,000
🔥ባለ 2 መኝታ: 102 ካሬ
👍ጠቅላላ ዋጋ=12,240,000
👍ቅ/ክፍያ(20%) =2,448,000
✅ሙሉ ለሚከፍል =8,568,000
➡️: 112 ካሬ
👍ጠቅላላ ዋጋ=13,450,000
👍ቅ/ክፍያ(20%) =2,688,000
✅ሙሉ ለሚከፍል =9,408,000
🔥ባለ 3 መኝታ: 134
👍ጠቅላላ ዋጋ=16,080,000
👍ቅ/ክፍያ(20%) =3,216,000
✅ሙሉ ለሚከፍል=11,256,000
➡️: 151 ካሬ
👍ጠቅላላ ዋጋ=18,120,000
👍ቅ/ክፍያ(20%) =3,624,000
✅ሙሉ ለሚከፍል=12,684,000
➡️: 175ካሬ
👍ጠቅላላ ዋጋ=21,000,000
👍ቅ/ክፍያ(20%) =4,200,000
✅ሙሉ ለሚከፍል=14,700,000
➡️ ከ30% በላይ ሲከፍሉ ከ15-20% ቅናሽ እናደርጋለን።
🔑 በ3 ዓመት ውስጥ የሚረከቡት
⏩ ማሳሰቢያ: ምንም አይነት የዋጋ ጭማሪ አናደርግም!
☎️09-38-04-99-22 | 591 |
| 9 | Немає тексту... | 476 |
| 10 | በትግራይ ክልል የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተናን በወረቀት የሚወስዱ ተማሪዎች ወደ መቐለ ዩኒቨርሲቲ ግቢዎች መግባት መጀመራቸውን የዩኒቨርሲቲው ምንጮች አስታውቀዋል።
ወደ ተመደቡበት ግቢ ለሚገቡት ተፈታኞች እስከ ነገ ድረስ አቀባበል የሚደረግላቸው ሲሆን፣ ስለ ፈተናው ሂደት አስፈላጊው ገለፃና ማብራሪያ ከተሰጣቸው በኋላ ከሐምሌ 22 እስከ 24 ቀን 2018 ዓ.ም ባሉት ቀናት ውስጥ ፈተናውን እንደሚወስዱ ተገልጿል።
ሕወሓት ከሳምንታት በፊት የ12ኛ ክፍል ተማሪዎችን በራሴ ፈተና አውጥቼ እፈትናለሁ፣ እንዲሁም ዩኒቨርሲቲ እመድባለሁ ሲል የነበረ ቢሆንም፣ አሁን ላይ ተማሪዎቹ በሀገር አቀፍ ደረጃ በሚሰጠው ብሔራዊ ፈተና ለመካፈል ወደ ዩኒቨርሲቲው መግባት ጀምረዋል።
#ethioradar | 490 |
| 11 | የወንጀል ድርጊቱ የተፈፀመው በጅማ ከተማ በሚገኘው ሔርማታ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግቢ ውስጥ ሲሆን፣ ተማሪ ሙአዝ ቢላል የተባለው ተከሳሽ የሚማርበትን ክፍል ሲረብሽ ቆይቶ በመስኮት በኩል ዘሎ ወደ ውጭ ይወጣል።
ይህን የተመለከተው የክፍሉ አለቃ ተማሪ ሙሳብ መሀመድ ድርጊቱ ትክክል እንዳልሆነ በመንገርና በመቆጣት የተሰጠውን ኃላፊነት ይወጣል። በዚህ ምክንያት በተማሪዎቹ መካከል ግጭት የተፈጠረ ሲሆን፣ "ልትናገረኝ አይገባም" በማለት የተበሳጨው ተማሪ ሙአዝ ቢላል፣ አስቀድሞ ደብቆ ይዞት የገባውን ጩቤ በመመዘዝ የክፍል አለቃውን ተማሪ ሙሳብ መሀመድን በያዘው ስለት ወግቶ ሕይወቱ እንዲያልፍ አድርጓል።
ወንጀሉን የፈጸመው ተማሪ በፖሊስ በቁጥጥር ሥር ውሎ ምርመራ ሲጣራበት የቆየ ሲሆን፣ ጉዳዩን ሲከታተል የቆየው የጅማ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሐምሌ 19 ቀን 2018 ዓ.ም በዋለው ችሎት ተማሪ ሙአዝ ቢላል ጥፋተኛ መሆኑን በማረጋገጥ በ15 ዓመት ጽኑ እስራት እንዲቀጣ ወስኖበታል።
#ethioradar | 485 |
| 12 | ፍቅርና ይቅርባይነት
ዛሬ በሰይፉ ሾው ላይ የቀረበው የሀብታሙ እና የቤተልሔም ታሪክ፣ በብዙዎች ልብ ውስጥ ትልቅ ትምህርት እና ተስፋን ያጫረ እውነተኛ የፍቅር ምስክርነት ሆኖ አልፏል።
በተለይም ቤተልሔም ልጅ በሚወለድበትና የእናትነትን ፈተና በምትወጣበት ያንን ሁሉ መከራና ስቃይ ብቻዋን አልፋ፣ ዛሬ ላይ በልቧ ምንም ዓይነት ቅሬታ ሳይያዝ ይቅርታን መታደሏ ምን ያህል ታላቅና የሰፋ ደግ ልብ እንዳላት ያሳየበት አጋጣሚ ነበር።«ለዓይን አያሳየኝ» በሚባልበት በዚህ ዘመን፣ እንዲህ ዓይነት አርቆ አሳቢነት፣ አስተዋይነት እና የይቅር ባይነት መንፈስ ማሳየት የእውነተኛ ፍቅር መገለጫ መሆኑ ተገልጿል።
በሌላ በኩል ሀብታሙ ከአቅም በላይ በሆነ ምክንያት በዚያ አስቸጋሪ ወቅት አጠገቧ ባይኖርም፣ ዛሬ ላይ ስህተቱን አምኖ ይቅርታ ለመጠየቅ መደፈሩ እና በቤተልሔም ይቅር ባይነት የተከናወነው እርቅ እውነተኛ ፍቅር በፈተናዎች ውስጥ አልፎ እንደሚጸና አስመስክሯል።
ለዚህ ውብ አጋጣሚ እና እርቅ መሳካት፣ ሁለት በፍቅር የተሳሰሩ ልቦችን በማገናኘትና ውብ ቤተሰብን መልሶ በመገንባት በኩል ትልቁን አስተዋጽኦ ላደረገው ለሰይፉ ፋንታሁን ከፍተኛ ምስጋናና ክብር ተቸሮታል።ሁለቱም ጠንክረው፣ እጅ ለእጅ ተያይዘው ልጃቸውን በፍቅርና በደስታ የሚያሳድጉበት መልካም ጊዜ እንዲሆንላቸው አድናቂዎቻቸውና ተከታታዮቻቸው መልካም ምኞታቸውን ገልጸውላቸዋል።
#ethioradar | 528 |
| 13 | አዲስሳይት
👉Studio 32ካሬ
✅1 መኝታ 60ካሬ ጀምሮ
✅2 መኝታ 90ካሬ ጀምሮ እና
✅3 መኝታ ከ 112ካሬ ጀምሮ
👉40% ለምትከፍሉ 10% ቅናሽ ቀሪውን 60% ቤቱን ስትረከቡ የምትከፍሉት
👉100% ለሚከፍሉ እስከ 35% ቅናሽ
👉4B+4SB+18 የሆነ ዘመናዊ የመኖሪያ አፓርትመንት
👉 በመገናኛ ጫካ ፕሮጀክት ከቴምር ሪልስቴት
💥 የንግድ ሱቆች
⨳ #ቡልጋሪያ ላይ ከ900ሺህ ብር ቅድመ ክፍያ ጀምሮ፣
⨳ #ፒያሳ ላይ ከ1.4ሚሊዮን ብር ቅድመ ክፍያ ጀምሮ፣
⨳ #ቃሊቲገላን ላይ ከ500ሺህ ብር ቅድመ ክፍያ ጀምሮ።
#ቴምርሪልስቴት #ቴምርፕሮፐርቲስ
ለበለጠ መረጃ ይደውሉ
👇👇👇👇👇👇
☎️09-38-04-99-22
☎️09-90-22-09-02 | 540 |
| 14 | በሀገራዊ የምክክር መድረክ ላይ የተሳተፉ ንዑሳን ቡድኖች የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ፣ አርማ እና መዝሙር እንዲሁም የክልሎች ምልክቶችን በተመለከተ በርካታ አማራጭ ሃሳቦችን አቅርበዋል።
በፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ተወካይ አቶ ፈይሰል አብዱላዚዝ እንደገለጹት፣ በአረንጓዴ፣ ቢጫና ቀይ ቀለማት ላይ አጠቃላይ ስምምነት ቢኖርም በአርማውና ተያያዥ ጉዳዮች ላይ ግን የሚከተሉት ዋና ዋና ሃሳቦች ተነስተዋል፦
የአርማ አማራጮች፦ አሁን ያለው የኮከብ አርማ ተነስቶ እንደ አሜሪካ ባንዲራ የሁሉም ብሔረሰቦች አርማ እንዲቀመጥ፣ ወይም የሰላም ምልክት የሆነችው «እርግብ» እንድትሆን፣ አሊያም ሁሉንም ክልሎች ሊወክል የሚችል አዲስ አርማ እንዲዘጋጅ ሀሳብ ቀርቧል።
የክልል ባንዲራ፦ ከሀገሪቱ አንድ ሰንደቅ ዓላማ ውጭ ሌላ መኖር የለበትም የሚል ሀሳብ የተነሳ ሲሆን፣ ክልሎችም ተመሳሳይ የሶስቱን ቀለማት ባንዲራ በመጠቀም የየራሳቸውን አርማ ብቻ እንዲጨምሩበት ተመክሯል።
ብሔራዊ መዝሙር፦ የአሁኑ ሀገራዊ መዝሙር እንዲቀጥል እና የክልሎች መዝሙር ደግሞ ይዘቱ «ጠብ አጫሪ» እንዳይሆን መደረግ እንዳለበት ስምምነት ላይ ተደርሷል።
እነዚህ በንዑሳን ቡድኖች የጸደቁ አጀንዳዎች በመቀጠል 250 አባላት ወዳሉት አጠቃላይ የውይይት ቡድን ተሸጋግረው ተጨማሪ ውይይት እንደሚደረግባቸው ታውቋል።
#ethioradar | 613 |
| 15 | በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ሥርዓት (ELMIS) ፕሮጀክት ኃላፊ እና የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት ዋና ሥራ ፈጻሚን ጨምሮ በርካታ ከፍተኛ አመራሮች በፌደራል ፖሊስ በቁጥጥር ሥር መዋላቸው ተገለጸ።
ተጠርጣሪዎቹ በቁጥጥር ሥር የዋሉት፦
📌 በውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት እና በ ELMIS ሲስተም ላይ የመረጃ ማጥፋት ወንጀል፤
📌 በከባድ ሙስና እና በሕገ-ወጥ የሰው ዝውውር መሳተፍ፤
📌 የመንግሥትን የውጭ ምንዛሬ ለግል ጥቅም በማዋል ወንጀሎች ተጠርጥረው መሆኑ ታውቋል።
በአሁኑ ወቅት በፌደራል ፖሊስ አማካኝነት በሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ እና በጥፋቱ ተጠራጣሪዎች ላይ ከፍተኛ የምርመራ ሂደት እየተካሄደ ይገኛል።
#ethioradar | 531 |
| 16 | የፌደራል ሲቪል ሠርቪስ ኮሚሽን ሁሉም የሲቪል ሠርቪስ መስሪያ ቤቶች የሠራተኞቻቸውን ማስረጃዎች በተቀመጠው የጊዜ ገደብ ውስጥ አረጋግጠው እንዲያጠናቅቁ አሳሰበ።
ኮሚሽኑ ዛሬ በጉዳዩ ዙሪያ ባካሄደው የውይይት መድረክ ላይ እንዳስታወቀው፤ እስከ አሁን ያሉ "የተሳሳቱ" የመንግሥት ሠራተኞች መረጃዎች መንግሥት አስተማማኝ የሆነ የሠራተኛ መረጃ እንዳይኖረው ማድረጋቸው አልፎ፣ ለትክክለኛ ሠራተኞች ብቻ ደሞዝ የመክፈል ሂደቱን እንቅፋት ሆኖበታል።
ይህንን አሰራር ሙሉ በሙሉ ዘመናዊና ግልጽ ለማድረግ ሲባል፣ ኮሚሽኑ በዘረጋው አዲስ ዲጂታል ሥርዓት መሠረት ለእያንዳንዱ የመንግሥት ሠራተኛ ልዩ የመለያ ቁጥር የሚሰጥ ይሆናል።
የሲቪል ሠርቪስ ኮሚሽን ኮሚሽነር መኩሪያ ኃይሌ በመድረኩ ላይ እንደገለጹት፣ ማንኛውም የመንግሥት መሥሪያ ቤት የሠራተኞቹን መረጃዎችና ማስረጃዎች በፍጥነት ወደ ዲጂታል ሥርዓት በማስገባት የተቋሙን የመረጃ ጥራት እንዲያረጋግጥ አጥብቀው አሳስበዋል።
#ethioradar | 581 |
| 17 | አዲስሳይት
👉Studio 32ካሬ
✅1 መኝታ 60ካሬ ጀምሮ
✅2 መኝታ 90ካሬ ጀምሮ እና
✅3 መኝታ ከ 112ካሬ ጀምሮ
👉40% ለምትከፍሉ 10% ቅናሽ ቀሪውን 60% ቤቱን ስትረከቡ የምትከፍሉት
👉100% ለሚከፍሉ እስከ 35% ቅናሽ
👉4B+4SB+18 የሆነ ዘመናዊ የመኖሪያ አፓርትመንት
👉 በመገናኛ ጫካ ፕሮጀክት ከቴምር ሪልስቴት
💥 የንግድ ሱቆች
⨳ #ቡልጋሪያ ላይ ከ900ሺህ ብር ቅድመ ክፍያ ጀምሮ፣
⨳ #ፒያሳ ላይ ከ1.4ሚሊዮን ብር ቅድመ ክፍያ ጀምሮ፣
⨳ #ቃሊቲገላን ላይ ከ500ሺህ ብር ቅድመ ክፍያ ጀምሮ።
#ቴምርሪልስቴት #ቴምርፕሮፐርቲስ
ለበለጠ መረጃ ይደውሉ
👇👇👇👇👇👇
☎️09-38-04-99-22
☎️09-90-22-09-02 | 745 |
| 18 | አንጋፋዋ አርቲስት ከዚህ አለም በሞት ተለይታለች
አንጋፋዋ ድምጻዊት፣ የግጥምና ዜማ ደራሲ ሳጅን አልማዝ ተፈራ ባደረባት ሕመም በሕክምና ስትረዳ ቆይታ ሐምሌ 16 ቀን 2018 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይታለች።
የሕይወት ታሪክ እና የሙዚቃ ጉዞ፦
ድምጻዊት አልማዝ ተፈራ በነገሌ ቦረና ተወልዳ ያደገች ሲሆን፣ ትምህርቷን በይርጋለም ከተማ ተከታትላለች። በመቀጠልም በጅማ ፖሊስ ኦኬስትራ ባንድ ከምስረታው ጀምሮ ለበርካታ ዓመታት በድምጻዊነት፣ በግጥምና ዜማ ደራሲነት እንዲሁም በጃዝ ሙዚቃ ተጫዋችነት ከፍተኛ አገልግሎት አበርክታለች።
በሙዚቃ ዘመኗ ሶስት አልበሞችን ለአድማጭ ያደረሰች ሲሆን፦
የመጀመሪያ አልበም (1978 ዓ.ም)፦ በጅማው መንዝ ሙዚቃ ቤት የታተመና ‘ጅማ ላይ ነው ቤቱ’፣ ‘አካል መውደድ’ እና ‘የፍቅር ጽገሬዳ’ የመሳሰሉ ተወዳጅ ዜማዎችን ያካተተ ነበር።
ሁለተኛ አልበም (1982 ዓ.ም)፦ በዚሁ መንዝ ሙዚቃ ቤት ታትሞ ለአድማጭ ደርሷል።
ሦስተኛ አልበም (1993 ዓ.ም)፦ ወደ አዲስ አበባ በመዛወር በፖሊስ ኦኬስትራ ውስጥ ማገልገል በጀመረችበት ወቅት በአፍሪካ ኤሌክትሮኒክስ አሳታሚነት የቀረበ ነው።
ከራሷ አልበሞችና ነጠላ ዜማዎች በተጨማሪ፣ በድርሰት ብቃቷ ለሌሎች ድምጻውያንም ተወዳጅ ሥራዎችን አበርክታለች።
ከእነዚህም መካከል የአንጋፋዋ ድምጻዊት ሒሩት በቀለን ‘እንደ ንጋት ጮራ’፣ ‘የባቄላ አበባ’ እና ‘ቃልኪዳን አክባሪ’ የተሰኙ ዘፈኖችን ግጥምና ዜማ ደርሳለች።
የሁለት ሴት ልጆች እናት የነበረችው የአርቲስት ሳጅን አልማዝ ተፈራ ሥርዓተ ቀብር፣ ዛሬ ቀን 10:00 ሰዓት ላይ በቅዱስ ዮሴፍ መካነ መቃብር እንደሚፈጸም ከቤተሰቦቿ የተገኘው መረጃ ያመላክታል።
#ethioradar | 839 |
| 19 | አስቸኳይ የአፋልጉኝ ጥሪ ❗️❗️❗️
በጀሞ 3 የ11 ዓመት ህፃን በጎርፍ ተወሰደ!
ሼር❗️ ሼር ❗️ | 846 |
| 20 | ኢትዮቴሌኮም ስጦታ አበርክቷል
የሀገራችን የቴሌኮም ግዙፍ ተቋም የሆነው ኢትዮ ቴሌኮም በያዝነው በጀት ዓመት 215.8 ቢሊየን ብር ገቢ መሰብሰቡን አበሰረ። ተቋሙ ያስመዘገበውን ከፍተኛ የገቢ እድገት እና ትርፋማነት አስመልክቶ፣ የስኬቱ ዋና አካል ለሆኑት ከ90 ሚሊዮን በላይ ደንበኞቹ ነፃ የስጦታ ፓኬጅ ማዘጋጀቱን ገልጿል።
የተዘጋጀው የቴሌ ስጦታ፦
📌 1.5 ጊጋ ባይት (GB) የኢንተርኔት ዳታ፤
📌 15 ደቂቃ የሀገር ውስጥ ጥሪ፤
📌 30 የጽሑፍ መልዕክቶች (SMS) ናቸው።
የስጦታው መጠቀሚያ ጊዜ እና ደንብ፦
የሚቆይበት ቀን፦ ከዛሬ ጀምሮ እስከ ሐምሌ 19/2018 ዓ.ም ድረስ ብቻ፤
የአገልግሎት ሰዓት፦ በየቀኑ ከሌሊቱ 6:00 እስከ ምሽቱ 12:00 ሰዓት ባለው ጊዜ ውስጥ አገልግሎት ላይ የሚውል ይሆናል።
#ethioradar | 798 |
