uz
Feedback
ግጥም ብቻ 📘

ግጥም ብቻ 📘

Kanalga Telegram’da o‘tish

✔በየቀኑ ምርጥ ምርጥ የጥበብ ስራዎችን ለማግኘት የቻነላችን ተከታይ ስለሆኑ እናመሰግናለን። ✔ @getem @serenity13@wegoch @Words19@seiloch @shiyach_bicha@zefenbicha @leul_mekonnen1

Ko'proq ko'rsatish

📈 Telegram kanali ግጥም ብቻ 📘 analitikasi

ግጥም ብቻ 📘 (@getem) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 63 813 obunachidan iborat bo'lib, Din & Maʼnaviyat toifasida 794-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 494-o'rinni egallagan.

📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika

невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 63 813 obunachiga ega bo‘ldi.

30 Iyun, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni -398 ga, so‘nggi 24 soatda esa 4 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.

  • Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
  • Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 15.55% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 4.21% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
  • Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 9 925 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 2 684 ta ko‘rish yig‘iladi.
  • Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 103 ta reaksiya keladi.

📝 Tavsif va kontent siyosati

Muallif resursni shaxsiy fikrni ifoda etish maydoni sifatida ta’riflaydi:
✔በየቀኑ ምርጥ ምርጥ የጥበብ ስራዎችን ለማግኘት የቻነላችን ተከታይ ስለሆኑ እናመሰግናለን። ✔ @getem @serenity13 ✔ @wegoch @Words19 ✔ @seiloch @shiyach_bicha ✔ @zefenbicha @leul_mekonnen1

Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 01 Iyul, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Din & Maʼnaviyat toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.

63 813
Obunachilar
+424 soatlar
-697 kunlar
-39830 kunlar
Postlar arxiv
እድሜ ለጊዜ! ዘመን ደግ ነው... ጊዜ ደግ ነው አይደለም ክፉ ይኸው ተረስቷል አለንጋ ግፉ! መራቅ ደግ ነው አመት መንጎዱ እኛናእኛችን እንዲዋደዱ [እኛናእኛችን እንዲላመዱ] በጊዜ ፍጥነት... በቀኑ ክንፈት... ያ ሁሉ 'እዬ'ታ፣ ሆነ ትዝታ! [እድሜ ለጊዜ] ሲያልፍ ሲተካ ልብም ቀዝቅዟል፣ እንጂማ ባይሆን.... ያ ሁሉ እሮሮ በምን ይረሳል?! [ያ ሁሉ እምባ በምን ይደርቃል] @alem3_b[ዓለም] @getem @getem @getem

ሀሜት የት ነበረ?? በፊት.... የጎረቤቴ በር በቀን አይዘጋም እኛም ለመፋቀር መሽቶልን አይነጋም 'አቡሽ' ቡና ጥራ...ሲሉን ደስ እያለን አዋቂው ሲታደም  ጓዳ ግባ ሁላ መቼ እናውቃለን??    ልክ እንደ ቡና ቁርስ መሀል ቁልጭ ቁልጭ   ሲያዝኑ እያዘንን ሲስቁም መብለጭለጭ    ውሉን ባንረዳው የጨዋታቸውን    እናውቅ ግን ነበር አንጀት ሆዳቸውን፤   እንከን በየዘመን፣ጥልም በየጊዜው ነበረ አይካድም፣ ግን በኛ ልጅነት እዛው እርቅ ይወርዳል ወዴትም አይሄድም፤ አሁን... ባህል የለሽ ወጉ እኛን አርቆናል በዘመን መዘመን ስራ አቀለለ እንጂ እኛን አቅልሎናል፤    ንግግር በግጥም ወዝ ቸፍ ቢልበት    ለአንዳንዱ ይከብደዋል ለአንዳንዱ ቀሎበት    ከእውነታው አልርቅም መቅረቡ ይጥመኛል    ከማስመሰል በላይ መምሰሉ ከብዶኛል፤ በቀን ሰው ፈርተናል የጨለመው ጥሞን ውሸት ሰፍቶብናል ቀናው መንገድ ጠቦን! እሺ.... ይሄ መፈራራት ፣ይሄ መተማማት ኢትዮጵያን ካስቀረ፣ ያኔ ልጅ እያለን 'ሀሜት' የት ነበረ???? @Weyblann ያቡ @getem @getem

ለምን አይባልም ------------------- አንዱ ዘመኑን በሙሉ ፤ ያለምንም እረፍት ተግቶ ያስቀድሳል ሌላው.... "ባንድ ቀን ንሰሀ ፤ ከፃድቁ እኩል፥ ገነትን ይወርሳል ። ይህንን እያየ ... ልባችን አስካክቶ ጥያቄ ቢጥልም እግዜር አዋቂ ነው ለምን? አይባልም። By kirubel @getem @getem @paappii

የውድቀቴን መንገድ ሸርሽራ በመውደድ ያቀናችኝ ንግስት ... የሰጠችኝ ክብር አቤት አቤት ሲያምር {ልክ እንዳንቺ ማርያም} መኖር እንድጠላ መንፈሴን አድክሞ ማጣት አንቆኝ ሲዞር ክንዱን አፈርጥሞ የምሆነው ጠፍቶኝ ተንበርክኬ ሳዝን ሳትለኝ ደካማ ቀና አረገችኝ ቀንበሬን ተሸክማ! እምቅ የእንባ ጠል ጉንጬን ሲንጠለጠል ኅዘን በደቆሰው ልስልስ ስስ አንጀቷ ዕንባዬን ያበሰው አቤት ሲያምር ጣቷ {ልክ እንዳንቺ ማርያም} እኔነት እስካጣ ፍቅር ሸሽቶኝ በሮ ብቸኝነት ሚስማር ሲያደማኝ ቸንክሮ የማረገው ጠፍቶኝ ሞቴን እየናፈቅኩ ሳዘጋጅ መስቀሌን ትንፋሽ ለገሰችኝ ዳብሳ ሰንበር ቁስሌን የጅራፍ ሹል ትርትራት የልቤ ስውር ስብራት አድቅቆ ሲጥለኝ ... እንዲሆን ለነፍሷ ስሞ ሳቅ ያሳየኝ አቤት ሲያምር ጥርሷ {ልክ እንዳንቺ ማርያም} ስትችልበት ማዘን ስታውቅበት ማቀፍ ብሶት አስዘርግፎ በሰላም ማሳረፍ {ልክ እንዳንቺ ማርያም} ስትችልበት ጸሎት ስታውቅበት ማውራት ጨለማን ገርስሶ በፈገግታ ማብራት {ልክ እንዳንቺ ማርያም} ስትችልበት ማከም ስታውቅበት ማዳን ፍቅር በልብ ሰጥቶ መለገስ ማር ኪዳን #ኤልዳን @eldan29 @getem @getem @paappii

የራስ ገድል! ^^   ^^   ^^   ^^  ^^   ^^   ^^   ^^  ^^ ደፈጣ ነው ውጊያ ብቻ፥ መገዳደር  ያለ መርቻ፣ ላለመርገፍ ተቀርጥፎ፥ ላለመውደቅ ተዝለፍልፎ! የማልጣል ተንጠልጥዬ፥ የማልወድቀው ተፈንቅዬ፥ ይሄው  ምርኮ ከ'ግሬ በታች፣ በረሃዬን በእምባ ሸማች።! ቀራንዮ በኮረብታ፣ የብቻዬን ጎለጎታ፣  ...  ...  .. ችንካር አለው ደግሞ ስቅል፣... የራስ ምርኮ የራስ ገድል።፨! @alem3_b [ዓለም] @getem @getem @getem

¹ አለሽ የሆነ ነገር...... አለሽ የሆነ መስህብ .... አለሽ የሆነ ግርማ....... (እንዲያ ባይሆንማ.....) ወደ ላይ.... ወደ ላይ...... (ወደ ጥጥ ደመና)  ሽቅብ መንጠራራት (መኩራራት) ሳያንሰው ፣ ዝቅ ሊል ወዳንቺ —··· ዋርካን እንደ ሐረግ ምን አልፈሰፈሰው? ያልለመደበትን (ያ'ላፈጣጠሩ) ስለምን ይቸገር? አለሽ የሆነ ነገር....! ² (እኔማ በእኔ ቤት......) ከሆዱ በልጦበት.... ገበሬ ለውበት —···· እርሻውን አይለቅም ፣ ወፍ ያለ አይመስለኝም.... ዝማሬ የማያውቅ —··· ስንጥር የማይለቅም ፣ ሰው ገላ ላይ ሆኖም —···መንደፍ የጠፋበት — ንብ አይቼ አላውቅም ። እንዲህ ያለ ጥበብ — እንዲህ ያለ መላ ፣ ባንቺ አየሁ ፡ ባንቺ አየሁ — የታለ በሌላ?! ³ አለሽ የሆነ ነገር.... አለሽ....! ከጥንት መንፈስ የተዋረሰሽ .... እንደ ደሊላ — የጀግናውን ልብ ያስበረገገ (ሳምሶንን ድኩም ያረገ ) ። እሷስ በአንዲት መቀስ — በፀጉር መላጫ ፤ ይበልጣል ያንቺ ሳቅ — የጥሜ መቁረጫ ። ⁴ አለሽ የሆነ ነገር..... ያቺ “ሔለን” ሚሏት የግሪክ ሀገር ውብ የትሮይ ምርኮኛ ፤ የጠፋች እንደሆን እሷን ለማስመለስ...... በሺህ መርከብ ፈረስ — ዘምቶ አየን ጦረኛ ። ሰውማ አመሉ ነው ይዋጋል ይሞታል ፤ አይበቃም ላንቺ ግን  ባህሩም ይዘምታል። ⁵ አለሽ የሆነ ነገር..... አዳም የጥንቱ — ቀልብ የሳተበት ሕግ የሻረበት (የሔዋን ፍቅር) የተቀጣበት ። (የእሱን አየን....) ገነት ሲቀር (ሞት ሲመጣ) በአንዲት ፍሬ — ትንሽ በለስ ፣ እኔስ ባንቺ የገባሁት —··· ሃጢያቴ በምን ይመለስ? አለሽ የሆነ ነገር.... __ By Bekalu shumye Inspired by Cole Porter's: “You've got that thing ” @getem @getem @paappii

ይቅናት . . ልጂት ተላላ አይኗም ቀልቃላ በሺ ሰው ትኩረት ልቧ ማይሞላ ሁሉንም መያዝ ሁሉንም ማግኘት ሰላሳ ነገር ባንዴ መመኘት የማያደክማት እረፍት የማታውቅ ገና ጅምር ናት ተፈጥራ ማታልቅ ደሞ ታምራለች እግዚኦ መልኳ አይደርስባትም ሉሲፈርንኳ አይኗም እንደ ልጅ አንጀት ያባባል ጉድፍ ገብቶበት ውበት ያነባል ልኬት የላትም ማነፃፀሪያ ንጉስ ቢጠጋት ይመስላል ባሪያ ኧረ'ዲያ....! እኔ ግን ልቤን ልኬን ስለማውቅ ቅዠት ህልሜ ላይ ከምደባልቅ ምንም ብወዳት ምንም ብታምርም መ'ላክ ጠልፌ ከቤቴ አላስርም የራሴን ቀብር በጄ አልቆፍርም ትሂድ ትንሳፈፍ ክንፏን ታማታ እድል የቀናው የማታ ማታ ላባዋ ሲረግፍ ዳዴ ስትጀምር ያግኛትና መንገዷን ያስምር... እያልኩ ለሰው ቸር እመኛለሁ አልችላትማ... ምን አደርጋለሁ? By Tadios Alemayehu @getem @getem @paappii

ላ'ባቴ ሰው ብቻ አይደለህም፣ ካፈር ወጥተህ ላፈር መላክ ነህ ሉሲፈር... ክብርህ ማንነትህ፣ ባመፅ የሚታፈር የማትንበረከክ የማትርመጠመጥ፣ ከባለጌ ዙፋን በርጩማ የምትመርጥ። ያለ ባህር ሰርጓጅ ያለ ሙሴ በትር፣ በመታገስ ብቻ ባህር የምትመትር። ካዘልከኝ ጀምሮ በእንኮኮ ጫንቃህ ላይ፣ ከፍታውን እንጂ፣ ዝቅታውን ሳላይ። እንደ ንሥር መጠቅሁ፣ እንደ ኮከብ በራሁ፣ የገዛ ክንፎቼን እንደ ዳንቴል ሰራሁ። በርግጥ ደሀ ነበርክ... ከሰላምታ በቀር የማታበረክት፣ ነጠላህ መናኛ፣ ሰውነትህ የክት። በርግጥ ደሀ ነበርክ፣ የነጣህ የጠራህ፣ ከጦር ሜዳ ይልቅ፣ ገበያ ሚያስፈራህ። ቤሳ ባታወርሰኝ፣ አወረስከኝ ትግል፣ የትም እንዳይጥለኝ ህይወት እንደ ፈንግል። አባዬ ብርሃን አባ የምስራቅ በር፣ ገመና ሸሻጊ እንደ ካባ ገበር፣ አባቴ ባትሆን፣ ምን ይውጠኝ ነበር። By ብዕውቀቱ ስዩም @getem @getem @paappii

እንዳትረሺኝ ብዬሽ፤ አትርሳኝ ብለሽኝ ፤ በቃል ክር አስሬሽ፤ በቃል ክር አስረሽኝ፤ በደልሽኝ በደልኩሽ፤ በደልኩሽ በደልሽኝ ፤ ቃልሽን አከበርሽ ቃሌን አከበርኩኝ ፤ ይሄ በደላችን... እንኳን በ'ዚህ ሕይወት በመቃብርም ውስጥ ችሎ አያረሳሳም፤ ደግሞ እንደምታውቂው የወዳጅ ፍቅሩ እንጅ በደሉ አይረሳም ። By Tewodros kassa @getem @getem @paappii

📢 የሰላም ድምፆች | Voices for Peace የግጥም ስብስብ (Anthology) — የሕትመት ጥሪ ዓለም አቀፉ የፀሐፊያን ማኅበር PEN International አባል የሆነው PEN Eritrea፣ ‘የሰላም ድምፆች’ በሚል ርዕስ ለኢትዮጵያውያን እና ኤርትራውያን ገጣሚያን የሚሆን ድንቅ የጋራ መድብል የሕትመት ዕድል አዘጋጅቷል። 📌 መሥፈርቶች ✍️ ከዚህ ቀደም ያልታተሙ እስከ 3 ግጥሞች (በአጠቃላይ ከ5 ገጽ ያልበለጠ) 🕊️ ጭብጥ፦ ሰላም፣ ግጭት፣ ተስፋ፣ ስደት፣ መትረፍ (Survival) ወይም ተያያዥ ማኅበራዊ ጉዳዮች 🌍 በየትኛውም ቋንቋ የተጻፉ ግጥሞችን ማቅረብ ይቻላል 🎁 የተመረጡ ግጥሞች፦ 📖 በጋራ መድበል ተሰብስበው ይታተማሉ ✍️ ከገጣሚያኑ ጋር በመመካከርና ባለቤትነታቸው ተጠብቆ ወደ እንግሊዘኛ ቋንቋ ይተረጎማሉ 👉🏾 የተመረጡ ገጣሚያን የ $200 ዶላር (ሁለት መቶ ዶላር) ክፍያ ያገኛሉ። 📅 ማብቂያ ቀን፦ ሰኔ 22 ቀን 2018 ዓ.ም. (June 29, 2026) 🔗 ዝርዝር መረጃና ማመልከቻ ሊንክ፦ አማርኛ፦ https://peneritrea.com/blog/%e1%8b%a8%e1%88%b0%e1%88%8b%e1%88%9d-%e1%8b%b5%e1%88%9d%e1%8d%86%e1%89%bd-voices-for-peace-%e1%8b%a8%e1%8c%8d%e1%8c%a5%e1%88%9d-%e1%88%b5%e1%89%a5%e1%88%b5%e1%89%a5 English: https://peneritrea.com/blog/%e1%8b%a8%e1%88%b0%e1%88%8b%e1%88%9d

‎ሰራተኛ እያፈላለኩ በደላላ አንዲት  ልጅ አገኘው ‎ ‎አንገቷን እንደደፋች "ጋሽዬ እኔ የስራ ሆነ የሙያ ችግር የለብኝም ብቻ ‎ስራ እንዳልቆይ ተደግሞብኛል ፤ ሰርቼ እንዳልለወጥ አሰርተውብኛል" ምናምን ብላ ዘበዘበች ‎ ‎ ‎"ብሎ ነገር የለም እኔ ተረት ተረት አልወድም ድግምት ምናምን የለም " ብዬ ካለችው አምስት መቶ ብር ጨምሬ ቀጠርኳት ‎ ‎21 ቀን እንደሰራች ‎አንዴ ‎ ‎ጠረጴዛዬ ላይ አንገቴን ደፍቼ እየፃፍኩ አንድ ሶስቴ ስጠራኝ አልሰማ ብያታለሁ መሰለኝ ‎"ምን አባህ ይዘጋሃል ብላ" ‎ይዛው በነበረው ፔርሙዝ  አናቴን አለቺኝ ‎ ‎ተጮኸ። I think እኔ ነኝ የጮህኩት ‎ጎረቤት ተሰበሰበ ‎መቼ ፣ ማን እንደመታኝ በደንብ ያወቅኩት ከሁለት ቀን በኋላ ነው ‎ ‎መንፈስ ፣ ድግምት ፣ ተተብትቦብኛል የሚለኝ ሰው ሲገጥመኝ የጀመረውን አረፍተነገር ሳይጨረሰው ነው የማመልጠው ‎ ‎የሻሼን ፍንክት የቀመሰ ሰው በዚህ ነገር አይፈላሰፍም 😁 By Adhanom Mitiku @wegoch @wegoch @paappii

እስኪ ንገሪኝ የኔ ቀረርቶ ፥ የኔማ ዛቻ መቁረጥ አያውቅም ፥ መገዝገዝ ብቻ፡፡ የኔም ስንብት ፥ የመለየቴ ጫፍ ቢቆይ እስከ ምሽት ፥ ቢርቅ እስከ ደጃፍ! "ቻው" ስልሽ ሰምቶ ከጭፍሮቹ ጋር ፥ መንገዴን ዘግቶ ናፍቆትሽ በሌት ፥ ይጠብቀኛል ፥ "አይኗስ?" ፥ ይለኛል "ሳቋስ?" ፥ ይለኛል "ጥርሷስ?" ፥ ይለኛል የማልችለውን ይጠይቀኛል፡፡ እስኪ ንገሪኝ … ስንቴ 'ቻው' ብልሽ ፥ ይቆርጥልኛል? By Habtamu Hadera @getem @getem @paappii

...... ቀንም ለኛ ሲፈርድ   ነገር ሲደላደል ክፋት ደግ ይሆናል   ልክነት ነው በደል፤ አሻጋሪን ጊዜ ምኞት ቢያስጠብቀን ያለ ፈራጁ ግን ብዙ ነው ሚርቀን ብንፈጥን አንደርስም ብንዘገይም እዛው አምላኩን ለማያውቅ እድል ነው ሚገዛው፤ 'ስማኝ ጃል!' ጊዜን መጠበቁ ያለ ዳኛ አይሆንም 'ራሱም ባበጀው' ፈጣሪ አይኮነንም!!! ጊዜን ሳይሆን እግዜርን ነው መጠበቅ!      ያቡ✍️ @Weyblann @getem @getem @getem

የዘውትር ፀሎት አቤቱ... በሰው ጉልበቴ የምችላት ሴት አይኗ ሁሉንም የማያሳስት ልቧ በተንኮል ያልተነካካ እራሷን ከሰው ሳታለካካ በቁመቴ ልክ በጎጆው መጠን የማይቸግራት እግሯን መመጠን ለኔና ቤቴ እሷኑ ስጠን አቤቱ... ምጥ ላስተምርሽ የማልላትን ዋጋዋ ቀልሎ የማልደፍራትን ጠንካራ ጊደር ቀንዷ ማይከብዳት ቅናት መንገዷን የማይጋርዳት አቅጣጫ ብስት ሳትስት አብራኝ እንዳልቀላውጥ ድምጿ ሚገራኝ እሷን ጀባበል ወደሷ ምራኝ አቤቱ... የዘመን ግርዶሽ አይኗን ያልያዘው እልኳን ፍቅር ያደበዘዘው የሰው ምርቃት የሰው በረካ አንተው አድለኝ አንተው በል እንካ ላልበላው ነገር ሁሉን አልንካ By Tadios Alemayehu @getem @getem @paappii

( ሞክሼ ... ) ======== ያ ሁሉ እግዚኦ ያ ሁሉ ቢስሚላ ያ ሁሉ ጾም ጸሎት ያ ሁሉ ምህላ ... የት ነው የሚሄደው ስሚኝ እስቲ ሀገሬ ሞክሼ አለሽ ወይ ሌላ ?? By Kiyorna @getem @getem @paappii

ችዬ እንዳይመስልህ! ደክርቼ ሳለሁ ዐለት የመሰልኩ፣ በሃያላን ፊት ደክሜ ያልሰለልኩ፣ ወና ብሆንም ከሌለኝ ያጣው፣ እንደ ምንዱባን ደጅ የማልጠናው ፣ ችዬ እንዳይመስልህ አስችሎኝ ነው። ...አስችሎን አይደል?!... by[ዓለም]  @alem3_b @getem @getem @getem

‎#ዕጣ_ፋንታ ‎ ‎አላውቃትም እና ‎የመኖርን ትርጉም ህይወትን አየኋት ‎ተጣልተን ተዋደን...ሳፈቅራት አጣኋት ‎ ‎ዮኒ ‎     ኣታን @yonatoz @getem @getem @getem

photo content