cookie

Мы используем файлы cookie для улучшения сервиса. Нажав кнопку «Принять все», вы соглашаетесь с использованием cookies.

avatar

ወሒድ የንጽጽር ማኅደር

ወንድም ወሒድ በኢሥላም እና በክርስትና መካከል ያለውን ልዩነት እና አንድነት በንጽጽር የሚያስቀምጥ ወንድም ነው። ለዚህም የቋንቋ፣ የሰዋስው፣ የዐውድ፣ የተዛማች እና የሥነ አመክንዮ ሙግት በማቅረብ የሚታወቅ ተሟጋች እና ጦማሪ ነው። ለሙግቱ ነጥብ በዋነኝነት የሚጠቀምባቸው ቋንቋ ዐማርኛ፣ ግዕዝ፣ እንግሊዝኛ፣ ዐረቢኛ፣ ዕብራይስጥ እና ግሪክ ናቸው። መልካም የንባብ፣ የጥናት፣ የማነጻጸር ጊዜ ይሁንልዎ!

Больше
Рекламные посты
34 440
Подписчики
+1224 часа
+1047 дней
+65530 дней

Загрузка данных...

Прирост подписчиков

Загрузка данных...

ላብ አደር በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡ 43፥32 ከፊላቸውም ከፊሉን ሠራተኛ አድርጎ ይይዝ ዘንድ ከፊላቸውን ከከፊሉ በላይ በደረጃዎች (በሀብት) አበለጥን፡፡ وَرَفَعْنَا بَعْضَهُمْ فَوْقَ بَعْضٍ دَرَجَاتٍ لِّيَتَّخِذَ بَعْضُهُم بَعْضًا سُخْرِيًّا "አደር" ማለት የዕለት ለዕለት የአኗኗርን ዘይቤን ለማመልከት የሚመጣ ፈሊጣዊ አነጋር እንጂ "አዳር" ከሚለው ቃል የሚሳለጥ አይደለም፥ ለምሳሌ፦ "ሠርቶ አደር" "ወጥቶ አደር" "አርሶ አደር" "አርብቶ አደር" "ወዝ አደር" "ላብ አደር" ሲባል ይህንን ታሳቢ እና ዋቢ ያደረገ ነው። ተወዳጁ ነቢያችን"ﷺ" ስለ ላብ አደር የሠራተኛን ዋጋ ላቡ ሳይደርቅ ክፈሉ" ብለው ነግረውናል፦ ሡነን ኢብኑ ማጃህ መጽሐፍ 16 ቁጥር 8 ዐብደላህ ኢብኑ ዑመር እንደተረከው፦ "የአሏህ መልእክተኛም"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ "የሠራተኛን ዋጋ ላቡ ሳይደርቅ ክፈሉ"። عَنْ عَبْدِ اللَّهِ بْنِ عُمَرَ، قَالَ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم ‏ "‏ أَعْطُوا الأَجِيرَ أَجْرَهُ قَبْلَ أَنْ يَجِفَّ عَرَقُهُ ‏"‏ ‏.‏ አንድ አሠሪ የሠራተኛውን ላብ የማይከፍል ከሆነ አሏህ በትንሣኤ ቀን ከሚጻረራቸው ሦስት ሰዎች አንዱ ይሆናል፦ ሡነን ኢብኑ ማጃህ መጽሐፍ 16 ቁጥር 7 አቢ ሁረይራህ እንደተረከው፦ "የአሏህ መልእክተኛም"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ "አሏህ እንዲህ ይላል፦ "እኔ በትንሣኤ ቀን የሥስት ሰዎች ተጻራሪ ነኝ፥ እኔ የማንም ተጻራሪ ከሆንኩ በትንሣኤ ቀን አሸንፈዋለሁ። በስሜ ቃል የገባ ከዚያም የሚያታልል ሰው፣ ነጻ ሰው ሸጦ ዋጋውን የሚበላ ሰው እና ሠራተኛ የሚቀጥር እና ተጠቅሞበት ከዚያም ደመወዙን የማይሰጥ ሰው ነው"። عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ، قَالَ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم ‏ "‏ ثَلاَثَةٌ أَنَا خَصْمُهُمْ يَوْمَ الْقِيَامَةِ وَمَنْ كُنْتُ خَصْمَهُ خَصَمْتُهُ يَوْمَ الْقِيَامَةِ رَجُلٌ أَعْطَى بِي ثُمَّ غَدَرَ وَرَجُلٌ بَاعَ حُرًّا فَأَكَلَ ثَمَنَهُ وَرَجُلٌ اسْتَأْجَرَ أَجِيرًا فَاسْتَوْفَى مِنْهُ وَلَمْ يُوفِهِ أَجْرَهُ ‏"‏ ‏.‏ አምላካችን አሏህ በቅርቢቱ ሕይወት ኑሯችንን በመካከላችን አከፋሏል፥ ከፊላቸውም ከፊሉን ሠራተኛ አድርጎ ይይዝ ዘንድ ሀብትን ሰጥቶአል፦ 43፥32 እነርሱ የጌታህን ችሮታ ያከፋፍላሉን? እኛ በቅርቢቱ ሕይወት ኑሯቸውን በመካከላቸው አከፋፍለናል፡፡ ከፊላቸውም ከፊሉን ሠራተኛ አድርጎ ይይዝ ዘንድ ከፊላቸውን ከከፊሉ በላይ በደረጃዎች (በሀብት) አበለጥን፡፡ የጌታህም ጸጋ ገነት ከሚሰበስቡት ሀብት በላጭ ናት፡፡ أَهُمْ يَقْسِمُونَ رَحْمَتَ رَبِّكَ ۚ نَحْنُ قَسَمْنَا بَيْنَهُم مَّعِيشَتَهُمْ فِي الْحَيَاةِ الدُّنْيَا ۚ وَرَفَعْنَا بَعْضَهُمْ فَوْقَ بَعْضٍ دَرَجَاتٍ لِّيَتَّخِذَ بَعْضُهُم بَعْضًا سُخْرِيًّا ۗ وَرَحْمَتُ رَبِّكَ خَيْرٌ مِّمَّا يَجْمَعُونَ የአሏህ ገነት ከሚሰበስቡት ሀብት በላጭ ናትና ላብ አደርን በዙልም በመዞለም ጀነት ተነፍጎ አሏህ ከሚጻረረን አሏህን ፈርተን የላብ አደሩን ሐቅ መስጠት ትሩፋት አለው። ዲኒል ኢሥላም የሚያስከብረው ላብ አደርን እንጂ የላብ አደር ቀንን አይደለምና ላብ አደርን እናክብር! አምላካችን አሏህ የሰዎችን ሐቅ ከሚጠብቁ ባሮቹ ያድርገን! አሚን። ✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ https://t.me/Wahidcom ወሠላሙ ዐለይኩም
Показать все...
ወደ አዲስ ኪዳን ስንመጣ የሰው ሥጋ መብላት እና ደም መጠጣት ሐላል ሆኗል፦ ዮሐንስ 6፥53-54 ስለዚህ ኢየሱስ እንዲህ አላቸው፦ “እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ የሰውን ልጅ ሥጋ ካልበላችሁ ደሙንም ካልጠጣችሁ በራሳችሁ ሕይወት የላችሁም። ሥጋዬን የሚበላ ደሜንም የሚጠጣ የዘላለም ሕይወት አለው፥ እኔም በመጨረሻው ቀን አስነሣዋለሁ። ሥጋዬ እውነተኛ መብል፡ ደሜም እውነተኛ መጠጥ፡ ነውና። የክርስቶስ ሥጋ እና ደም ምሳሌአዊ ሳይሆን እውነተኛ መብል እና መጠጥ ነው፥ የጌታ እራት የሚባለው "እንጀራው ወደ ሥጋ እዲሁ ወይኑ ወደ ደም ይለወጣል" የሚል እምነት በካቶሊክ እና በኦርቶዶክስ ትምህርት ውስጥ አለ፦ ማቴዎስ 26፥26-27 ሲበሉም ኢየሱስ እንጀራን አንሥቶ ባረከ ቈርሶም ለደቀ መዛሙርቱ ሰጠና፦ “እንካችሁ፥ ብሉ ይህ ሥጋዬ ነው፡” አለ። ጽዋንም አንሥቶ አመስግኖም ሰጣቸው እንዲህም አለ፦ “ሁላችሁ ከእርሱ ጠጡ፤ 28: ስለ ብዙዎች ለኃጢአት ይቅርታ የሚፈስ የአዲስ ኪዳን ደሜ ይህ ነው። ካቶሊክ "እንጀራው ወደ ሥጋ እዲሁ ወይኑ ወደ ደም በኑባሬ ደረጃ ይለወጣል" የሚል ትምህርታቸው "ትራንስ ሰብስታንቴሽን"transubstantiation" ሲባል በኦርቶዶክስ ደግሞ "እንጀራው ወደ ሥጋ እዲሁ ወይኑ ወደ ደም በተማልሎአዊ ይለወጣል" ሲባል ተማልሎአዊ ለውጥ"mystical change" ነው፥ በሁለቱም እምነት "የበቃ ሰው በከለር፣ በጣዕም፣ በይዘት ተቀይሮ ያየዋል" የሚል እምነት አላቸው። በፕሮቴስታንት ደግሞ "ኅብስቱ ከሥጋው ጋር እንዲሁ ወይኑ ከደሙ ጋር ኅብረት ብቻ አለው እንጂ አይለወጥም" የሚል ትምህርት "ኮን ሰብስታንቴሽን"Consubstantiation" ይባላል። ይህ ውስብስብ ትምህርት የሰው ሥጋ መብላት እና ደም መጠላት ሐላል ነው" የሚል ትምህርት ነው፥ ቅሉ ግን የሰውን ሥጋ መሥዋዕት መሠዋት ሐራም ነው። 1ኛ ነገሥት 13፥1-2 2ኛ ነገሥት 23:20 ዘዳግም 18፥9-12 ተመልከት!  የሰው መሥዋት መሰዋት የዐረማዊ አሕዛብ የሚያደርጉት ርኵሰት ነው።                                                                     አምላካችን አሏህ የሰውን ልጅ ያከበረው ፍጡር ነው፥ ሐላል ምግብ ከየብስ እና ከባሕር እንዲመገቡት የአደምን ልጆች አሏህ በየብስ እና በባሕር አሳፈራቸው። ከፈጠርናቸውም ፍጡሮች ከማዕድናት፣ ከዕጽዋት፣ ከእንስሳት በብዙዎቹ ላይ ማብለጥን አበለጣቸው፦ 7፥70 የአደምንም ልጆች በእርግጥ አከበርናቸው፡፡ وَلَقَدْ كَرَّمْنَا بَنِي آدَمَ 7፥70 በየብስ እና በባሕር አሳፈርናቸው፥ ከመልካሞች ሲሳዮች ሰጠናቸው፡፡ وَحَمَلْنَاهُمْ فِي الْبَرِّ وَالْبَحْرِ وَرَزَقْنَاهُم مِّنَ الطَّيِّبَاتِ 7፥70 ከፈጠርናቸውም ፍጡሮች በብዙዎቹ ላይ ማብለጥን አበለጥናቸው፡፡ وَفَضَّلْنَاهُمْ عَلَىٰ كَثِيرٍ مِّمَّنْ خَلَقْنَا تَفْضِيلًا አምላካችን አሏህ ሰው እርስ በእርስ ሥጋውን እንዲበላላ ሐላል አላደረግም፥ ከዚያ በተቃራኒ የሰው ሥጋ መብላት ሐራም ነው፦ 49፥12 ከፊላችሁም ከፊሉን አይማ! አንደኛችሁ የወንድሙን ሥጋ የሞተ ኾኖ ሊበላው ይወዳልን? መብላቱን ጠላችሁት ሐሜቱንም ጥሉት፡፡ አሏህን ፍሩ! አሏህ ጸጸትን ተቀባይ አዛኝ ነውና፡፡ وَلَا يَغْتَب بَّعْضُكُم بَعْضًا ۚ أَيُحِبُّ أَحَدُكُمْ أَن يَأْكُلَ لَحْمَ أَخِيهِ مَيْتًا فَكَرِهْتُمُوهُ ۚ وَاتَّقُوا اللَّهَ ۚ إِنَّ اللَّهَ تَوَّابٌ رَّحِيمٌ ሡነን አቢ ዳውድ መጽሐፍ 43, ሐዲስ 106 አነሥ ኢብኑ-ማሊክ እንደተረከው፦ "የአሏህ መልእክተኛ"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ "ወደ ሰማይ በተወሰድኩኝ ጊዜ ከነሐስ የሆነ ጥፍር ኖሯቸው ፊቶቻቸውን እና ደረቶቻቸውን የሚቧጥጡ በሆኑ ሰዎች በኩል አለፍኩ። እኔም፡- "ጂብሪል ሆይ! እነማናቸው እነዚህ? ስለው፥ እርሱም፦ "እነዚህ የሰዎችን ሥጋ የሚበሉ እና ክብራቸውን የሚነኩ ናቸው" አለኝ"። عَنْ أَنَسِ بْنِ مَالِكٍ، قَالَ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم ‏ "‏ لَمَّا عُرِجَ بِي مَرَرْتُ بِقَوْمٍ لَهُمْ أَظْفَارٌ مِنْ نُحَاسٍ يَخْمِشُونَ وُجُوهَهُمْ وَصُدُورَهُمْ فَقُلْتُ مَنْ هَؤُلاَءِ يَا جِبْرِيلُ قَالَ هَؤُلاَءِ الَّذِينَ يَأْكُلُونَ لُحُومَ النَّاسِ وَيَقَعُونَ فِي أَعْرَاضِهِمْ ‏"‏ አምላካችን አሏህ ሡናን ከሚተገብሩ ሙእሚን ያድርገን! አሚን።    ✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ https://t.me/Wahidcom ወሠላሙ ዐለይኩም
Показать все...
የሰው ሥጋ በባይብል በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኛ በሆነው፡፡ 7፥70 የአደምንም ልጆች በእርግጥ አከበርናቸው፡፡ وَلَقَدْ كَرَّمْنَا بَنِي آدَمَ እስራኤላውያን በሚያጠፉት ጥፋት አምላክ ቅጣቱ የወንዶች ልጆቻቸውን እና የሴቶች ልጆቻቸውን ሥጋ እንደሚበሉ ማድረግ ነበር፦ ዘሌዋውያን 26፥29 የወንዶች ልጆቻችሁንም ሥጋ ትበላላችሁ፥ የሴቶች ልጆቻችሁንም ሥጋ ትበላላችሁ። "ትበላላችሁ" የሚለው ይሰመርበት! እስራኤላውያንን ጠላቶቻቸው ባስጨነቋቸው እና መከራ ባሳይዋቸው ጊዜ የሆዳቸውን ፍሬ የሆኑትን የወንዶች እና የሴቶች ልጆቻቸውን ሥጋ እንደሚበሉ ነግሯቸዋል፦ ዘዳግም 28፥53 ጠላቶችህም ከብበው ባስጨነቁህ እና መከራ ባሳዩህ ጊዜ አምላክህ እግዚአብሔር የሚሰጥህን የሆድህን ፍሬ የወንዶች እና የሴቶች ልጆችህን ሥጋ ትበላለህ። ለእስራኤላውያን የወንዶች እና የሴቶች ልጆቻቸውን ሥጋ የሚያበላው እራሱ አምላክ እንደሆነ ይናገራል፦ ኤርምያስ 19፥9 የወንዶች እና የሴቶች ልጆቻቸውንም ሥጋ "አበላቸዋለሁ"። "አበላቸዋለሁ" የሚለው ይሰመርበት! አምላክ የሰውን ሥጋ ለዛውም የገዛ የአብራክ ክፋል ልጅ መብላት ከመፍቀዱ አልፎ ማስበላቱ ምን ዓይነት ቅጣት ይሆን? አስበይው አምላክ በይው እስራኤላውያንን ናቸው። በዚህ ምክንያት አባቶች ልጆቻቸውን ይበላሉ ልጆችም አባቶቻቸውን ይበላሉ፦ ሕዝቅኤል 5፥10 ስለዚህ በመካከልሽ አባቶች ልጆቻቸውን "ይበላሉ" ልጆችም አባቶቻቸውን "ይበላሉ"። ምቾት ላይ የነበረ ሰው ረሃብ ላይ የምግብ እጦት ስለሚኖር በወንድሙ፣ አቅፋውም በምትተኛ በሚስቱ እና በቀሩትም ልጆች ይቀናል፥ ከመሰሰቱ የተነሳ ከሚበላው ከልጆቹ ሥጋ ለአንዱ አይሰጥም፦ ዘዳግም 28፥54 በአንተ ዘንድ የተለሳለሰ እና በቅምጥልነት ሁልጊዜ ይኖር የነበረ ሰው በወንድሙ፣ አቅፋውም በምትተኛ በሚስቱ እና በቀሩትም ልጆች ይቀናል። ዘዳግም 28፥55 በደጆችህ ሁሉ ውስጥ ጠላቶችህ ከብበው ባስጨነቁህ እና መከራ ባሳዩህ ጊዜ ሌላ ነገር የቀረው የለምና ከሚበላው ከልጆቹ ሥጋ ለአንዱ አይሰጥም። የሆዳቸውን ፍሬ የሆኑትን የወንዶች እና የሴቶች ልጆቻቸውን ሥጋ ከማጣትም አልፈው ሴት በእግርዋ መካከል በሚወጣው በእንግዴ ልጅ ትቀናለች፦ ዘዳግም 28፥57 በወንድ እና በሴት ልጅዋም፥ በእግርዋ መካከል በሚወጣው በእንግዴ ልጅ፥ በምትወልዳቸውም ልጆች ትቀናለች። በተግባር ልጅን ቀቅሎ መብላት የተለመደ ነገር ነበር፥ ይህንን ተግባር ኤርሚያስ በሰቆቃ ነግሮናል፦ 2ኛ ነገሥት 6፥28-29 ንጉሡም፦ ምን ሆነሻል? አላት፥ እርስዋም፦ ይህች ሴት፦ "ዛሬ እንድንበላው ልጅሽን አምጪ! ነገም ልጄን እንበላለን" አለችኝ። ልጄንም ቀቅለን በላነው፥ በማግሥቱም፦ "እንድንበላው ልጅሽን አምጪ" አልኋት፤ ልጅዋንም ሸሸገችው" ብላ መለሰችለት። ሰቆ ኤርምያስ 4፥10 ዮድ። የርኅሩኆች ሴቶች እጆች ልጆቻችውን ቀቅለዋል፥ የወገኔ ሴት ልጅ በመቀጥቀጥዋ መብል ሆኑአቸው። ሰቆ ኤርምያስ 2፥20 ሬስ።አቤቱ፥ እይ፤ በማን ላይ እንደዚህ እንዳደረግህ ተመልከት። በውኑ ሴቶች ፍሬያቸውን፥ ያቀማጠሉአቸውን ሕፃናት ይበላሉን?
Показать все...
يَخْمِشُونَ وُجُوهَهُمْ وَصُدُورَهُمْ فَقُلْتُ مَنْ هَؤُلاَءِ يَا جِبْرِيلُ قَالَ هَؤُلاَءِ الَّذِينَ يَأْكُلُونَ لُحُومَ النَّاسِ وَيَقَعُونَ فِي أَعْرَاضِهِمْ ‏"‏ አምላካችን አሏህ ሡናን ከሚተገብሩ ሙእሚን ያድርገን! አሚን። ✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ https://t.me/Wahidcom ወሠላሙ ዐለይኩም
Показать все...
ወሒድ የንጽጽር ማኅደር

ወንድም ወሒድ በኢሥላም እና በክርስትና መካከል ያለውን ልዩነት እና አንድነት በንጽጽር የሚያስቀምጥ ወንድም ነው። ለዚህም የቋንቋ፣ የሰዋስው፣ የዐውድ፣ የተዛማች እና የሥነ አመክንዮ ሙግት በማቅረብ የሚታወቅ ተሟጋች እና ጦማሪ ነው። ለሙግቱ ነጥብ በዋነኝነት የሚጠቀምባቸው ቋንቋ ዐማርኛ፣ ግዕዝ፣ እንግሊዝኛ፣ ዐረቢኛ፣ ዕብራይስጥ እና ግሪክ ናቸው። መልካም የንባብ፣ የጥናት፣ የማነጻጸር ጊዜ ይሁንልዎ!

የሰው ሥጋ በባይብል በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኛ በሆነው፡፡ 7፥70 የአደምንም ልጆች በእርግጥ አከበርናቸው፡፡ وَلَقَدْ كَرَّمْنَا بَنِي آدَمَ እስራኤላውያን በሚያጠፉት ጥፋት አምላክ ቅጣቱ የወንዶች ልጆቻቸውን እና የሴቶች ልጆቻቸውን ሥጋ እንደሚበሉ ማድረግ ነበር፦ ዘሌዋውያን 26፥29 የወንዶች ልጆቻችሁንም ሥጋ ትበላላችሁ፥ የሴቶች ልጆቻችሁንም ሥጋ ትበላላችሁ። "ትበላላችሁ" የሚለው ይሰመርበት! እስራኤላውያንን ጠላቶቻቸው ባስጨነቋቸው እና መከራ ባሳይዋቸው ጊዜ የሆዳቸውን ፍሬ የሆኑትን የወንዶች እና የሴቶች ልጆቻቸውን ሥጋ እንደሚበሉ ነግሯቸዋል፦ ዘዳግም 28፥53 ጠላቶችህም ከብበው ባስጨነቁህ እና መከራ ባሳዩህ ጊዜ አምላክህ እግዚአብሔር የሚሰጥህን የሆድህን ፍሬ የወንዶች እና የሴቶች ልጆችህን ሥጋ ትበላለህ። ለእስራኤላውያን የወንዶች እና የሴቶች ልጆቻቸውን ሥጋ የሚያበላው እራሱ አምላክ እንደሆነ ይናገራል፦ ኤርምያስ 19፥9 የወንዶች እና የሴቶች ልጆቻቸውንም ሥጋ "አበላቸዋለሁ"። "አበላቸዋለሁ" የሚለው ይሰመርበት! አምላክ የሰውን ሥጋ ለዛውም የገዛ የአብራክ ክፋል ልጅ መብላት ከመፍቀዱ አልፎ ማስበላቱ ምን ዓይነት ቅጣት ይሆን? አስበይው አምላክ በይው እስራኤላውያንን ናቸው። በዚህ ምክንያት አባቶች ልጆቻቸውን ይበላሉ ልጆችም አባቶቻቸውን ይበላሉ፦ ሕዝቅኤል 5፥10 ስለዚህ በመካከልሽ አባቶች ልጆቻቸውን "ይበላሉ" ልጆችም አባቶቻቸውን "ይበላሉ"። ምቾት ላይ የነበረ ሰው ረሃብ ላይ የምግብ እጦት ስለሚኖር በወንድሙ፣ አቅፋውም በምትተኛ በሚስቱ እና በቀሩትም ልጆች ይቀናል፥ ከመሰሰቱ የተነሳ ከሚበላው ከልጆቹ ሥጋ ለአንዱ አይሰጥም፦ ዘዳግም 28፥54 በአንተ ዘንድ የተለሳለሰ እና በቅምጥልነት ሁልጊዜ ይኖር የነበረ ሰው በወንድሙ፣ አቅፋውም በምትተኛ በሚስቱ እና በቀሩትም ልጆች ይቀናል። ዘዳግም 28፥55 በደጆችህ ሁሉ ውስጥ ጠላቶችህ ከብበው ባስጨነቁህ እና መከራ ባሳዩህ ጊዜ ሌላ ነገር የቀረው የለምና ከሚበላው ከልጆቹ ሥጋ ለአንዱ አይሰጥም። የሆዳቸውን ፍሬ የሆኑትን የወንዶች እና የሴቶች ልጆቻቸውን ሥጋ ከማጣትም አልፈው ሴት በእግርዋ መካከል በሚወጣው በእንግዴ ልጅ ትቀናለች፦ ዘዳግም 28፥57 በወንድ እና በሴት ልጅዋም፥ በእግርዋ መካከል በሚወጣው በእንግዴ ልጅ፥ በምትወልዳቸውም ልጆች ትቀናለች። በተግባር ልጅን ቀቅሎ መብላት የተለመደ ነገር ነበር፥ ይህንን ተግባር ኤርሚያስ በሰቆቃ ነግሮናል፦ 2ኛ ነገሥት 6፥28-29 ንጉሡም፦ ምን ሆነሻል? አላት፥ እርስዋም፦ ይህች ሴት፦ "ዛሬ እንድንበላው ልጅሽን አምጪ! ነገም ልጄን እንበላለን" አለችኝ። ልጄንም ቀቅለን በላነው፥ በማግሥቱም፦ "እንድንበላው ልጅሽን አምጪ" አልኋት፤ ልጅዋንም ሸሸገችው" ብላ መለሰችለት። ሰቆ ኤርምያስ 4፥10 ዮድ። የርኅሩኆች ሴቶች እጆች ልጆቻችውን ቀቅለዋል፥ የወገኔ ሴት ልጅ በመቀጥቀጥዋ መብል ሆኑአቸው። ሰቆ ኤርምያስ 2፥20 ሬስ።አቤቱ፥ እይ፤ በማን ላይ እንደዚህ እንዳደረግህ ተመልከት። በውኑ ሴቶች ፍሬያቸውን፥ ያቀማጠሉአቸውን ሕፃናት ይበላሉን? ወደ አዲስ ኪዳን ስንመጣ የሰው ሥጋ መብላት እና ደም መጠጣት ሐላል ሆኗል፦ ዮሐንስ 6፥53-54 ስለዚህ ኢየሱስ እንዲህ አላቸው፦ “እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ የሰውን ልጅ ሥጋ ካልበላችሁ ደሙንም ካልጠጣችሁ በራሳችሁ ሕይወት የላችሁም። ሥጋዬን የሚበላ ደሜንም የሚጠጣ የዘላለም ሕይወት አለው፥ እኔም በመጨረሻው ቀን አስነሣዋለሁ። ሥጋዬ እውነተኛ መብል፡ ደሜም እውነተኛ መጠጥ፡ ነውና። የክርስቶስ ሥጋ እና ደም ምሳሌአዊ ሳይሆን እውነተኛ መብል እና መጠጥ ነው፥ የጌታ እራት የሚባለው "እንጀራው ወደ ሥጋ እዲሁ ወይኑ ወደ ደም ይለወጣል" የሚል እምነት በካቶሊክ እና በኦርቶዶክስ ትምህርት ውስጥ አለ፦ ማቴዎስ 26፥26-27 ሲበሉም ኢየሱስ እንጀራን አንሥቶ ባረከ ቈርሶም ለደቀ መዛሙርቱ ሰጠና፦ “እንካችሁ፥ ብሉ ይህ ሥጋዬ ነው፡” አለ። ጽዋንም አንሥቶ አመስግኖም ሰጣቸው እንዲህም አለ፦ “ሁላችሁ ከእርሱ ጠጡ፤ 28: ስለ ብዙዎች ለኃጢአት ይቅርታ የሚፈስ የአዲስ ኪዳን ደሜ ይህ ነው። ካቶሊክ "እንጀራው ወደ ሥጋ እዲሁ ወይኑ ወደ ደም በኑባሬ ደረጃ ይለወጣል" የሚል ትምህርታቸው "ትራንስ ሰብስታንቴሽን"transubstantiation" ሲባል በኦርቶዶክስ ደግሞ "እንጀራው ወደ ሥጋ እዲሁ ወይኑ ወደ ደም በተማልሎአዊ ይለወጣል" ሲባል ተማልሎአዊ ለውጥ"mystical change" ነው፥ በሁለቱም እምነት "የበቃ ሰው በከለር፣ በጣዕም፣ በይዘት ተቀይሮ ያየዋል" የሚል እምነት አላቸው። በፕሮቴስታንት ደግሞ "ኅብስቱ ከሥጋው ጋር እንዲሁ ወይኑ ከደሙ ጋር ኅብረት ብቻ አለው እንጂ አይለወጥም" የሚል ትምህርት "ኮን ሰብስታንቴሽን"Consubstantiation" ይባላል። ይህ ውስብስብ ትምህርት የሰው ሥጋ መብላት እና ደም መጠላት ሐላል ነው" የሚል ትምህርት ነው፥ ቅሉ ግን የሰውን ሥጋ መሥዋዕት መሠዋት ሐራም ነው። 1ኛ ነገሥት 13፥1-2 2ኛ ነገሥት 23:20 ዘዳግም 18፥9-12 ተመልከት! የሰው መሥዋት መሰዋት የዐረማዊ አሕዛብ የሚያደርጉት ርኵሰት ነው። አምላካችን አሏህ የሰውን ልጅ ያከበረው ፍጡር ነው፥ ሐላል ምግብ ከየብስ እና ከባሕር እንዲመገቡት የአደምን ልጆች አሏህ በየብስ እና በባሕር አሳፈራቸው። ከፈጠርናቸውም ፍጡሮች ከማዕድናት፣ ከዕጽዋት፣ ከእንስሳት በብዙዎቹ ላይ ማብለጥን አበለጣቸው፦ 7፥70 የአደምንም ልጆች በእርግጥ አከበርናቸው፡፡ وَلَقَدْ كَرَّمْنَا بَنِي آدَمَ 7፥70 በየብስ እና በባሕር አሳፈርናቸው፥ ከመልካሞች ሲሳዮች ሰጠናቸው፡፡ وَحَمَلْنَاهُمْ فِي الْبَرِّ وَالْبَحْرِ وَرَزَقْنَاهُم مِّنَ الطَّيِّبَاتِ 7፥70 ከፈጠርናቸውም ፍጡሮች በብዙዎቹ ላይ ማብለጥን አበለጥናቸው፡፡ وَفَضَّلْنَاهُمْ عَلَىٰ كَثِيرٍ مِّمَّنْ خَلَقْنَا تَفْضِيلًا አምላካችን አሏህ ሰው እርስ በእርስ ሥጋውን እንዲበላላ ሐላል አላደረግም፥ ከዚያ በተቃራኒ የሰው ሥጋ መብላት ሐራም ነው፦ 49፥12 ከፊላችሁም ከፊሉን አይማ! አንደኛችሁ የወንድሙን ሥጋ የሞተ ኾኖ ሊበላው ይወዳልን? መብላቱን ጠላችሁት ሐሜቱንም ጥሉት፡፡ አሏህን ፍሩ! አሏህ ጸጸትን ተቀባይ አዛኝ ነውና፡፡ وَلَا يَغْتَب بَّعْضُكُم بَعْضًا ۚ أَيُحِبُّ أَحَدُكُمْ أَن يَأْكُلَ لَحْمَ أَخِيهِ مَيْتًا فَكَرِهْتُمُوهُ ۚ وَاتَّقُوا اللَّهَ ۚ إِنَّ اللَّهَ تَوَّابٌ رَّحِيمٌ ሡነን አቢ ዳውድ መጽሐፍ 43, ሐዲስ 106 አነሥ ኢብኑ-ማሊክ እንደተረከው፦ "የአሏህ መልእክተኛ"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ "ወደ ሰማይ በተወሰድኩኝ ጊዜ ከነሐስ የሆነ ጥፍር ኖሯቸው ፊቶቻቸውን እና ደረቶቻቸውን የሚቧጥጡ በሆኑ ሰዎች በኩል አለፍኩ። እኔም፡- "ጂብሪል ሆይ! እነማናቸው እነዚህ? ስለው፥ እርሱም፦ "እነዚህ የሰዎችን ሥጋ የሚበሉ እና ክብራቸውን የሚነኩ ናቸው" አለኝ"። عَنْ أَنَسِ بْنِ مَالِكٍ، قَالَ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم ‏ "‏ لَمَّا عُرِجَ بِي مَرَرْتُ بِقَوْمٍ لَهُمْ أَظْفَارٌ مِنْ نُحَاسٍ
Показать все...
"የስላሴ እሳቤ" እና "የተደበቀው እውነት" መጽሀፍ ከአ/አበባ በተጨማሪ አዳማ እና ደሴ ይገኛሉ። አዳማ መጽሀፉን የምትፈልጉ call +251966640370 ደሴ :-አረብገንዳ ሸህ አብዱ መክተባ          ሸርፍተራ ፋጡማ መክተባ እንዲሁም አህመድ መክተባ ይገኛል አ/አበባ call 0920781016
Показать все...
ግርዶ በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው። 42፥51 ለሰውም አሏህ በራእይ ወይም ከግርዶ ወዲያ ወይም መልእክተኛን መልአክን የሚልክ እና በፈቃዱ የሚሻውን ነገር የሚያወርድለት ቢኾን እንጅ በገሃድ ሊያናግረው ተገቢው አይደለም፡፡ እርሱ የበላይ ጥበበኛ ነውና፡፡ وَمَا كَانَ لِبَشَرٍ أَن يُكَلِّمَهُ اللَّهُ إِلَّا وَحْيًا أَوْ مِن وَرَاءِ حِجَابٍ أَوْ يُرْسِلَ رَسُولًا فَيُوحِيَ بِإِذْنِهِ مَا يَشَاءُ ۚ إِنَّهُ عَلِيٌّ حَكِيمٌ ጭሮ አዳሪ ከመሆን ይልቅ ጸብ አጫሪ መሆንን ምርጫቸው ያረጉ ክርስቲያን ሚሽነሪዎች "ጸብ በደላላ ካልሆነልን" ብለው ለገላይ በማያመች "ያዙኝ ልቀቁኝ ደግፉኝ ጣሉኝ" በማለት መፎለሉን፣ ማቅራራቱን፣ መሸለሉን፣ መፎከሩን ተያይዘውታል። "አሏህ እንደ እንስት ሒጃብ ይለብሳል" በማለት የሌለ አሻሚ ሕፀፅ"Fallacy of equivocation" ያፅፃሉ። ምሁራን "ውኃን ከጥሩ ነገርን ከሥሩ" እንደሚሉ ስለ ሒጃብ ከሥር መሠረቱ ኢንሻላህ እንመልከት! "ሒጃብ" حِجَاب የሚለው ቃል "ሐጀበ" حَجَبَ ማለትም "ሸፈነ" "ጋረደ" ከሚል ሥርወ ቃል የመጣ ሲሆን "መሸፈኛ"cover" "መጋረጃ"curtain" "ግርዶ"screen" ማለት ነው፥ ለምሳሌ፦ መርየም ያደረገችው መጋረጃ "ሒጃብ" حِجَاب ተብሏል፦ 19፥17 ከእነርሱም "መጋረጃን" አደረገች፡፡ فَاتَّخَذَتْ مِن دُونِهِمْ حِجَابًا እዚህ አንቀጽ ላይ "መጋረጃ" ለሚለው የገባው ቃል "ሒጃብ" حِجَاب እንደሆነ ልብ አድርግ! በተጨማሪ የጀነት ሰዎች እና የእሳት ሰዎች እንዳይገናኙ በመካከል ያለው አዕራፍ "ሒጃብ" حِجَاب ተብሏል፦ 7፥46 በመካከላቸውም ግርዶሽ አለ፡፡ وَبَيْنَهُمَا حِجَابٌ ስለዚህ "ሒጃብ" حِجَاب የሚለው ቃል እንደ ዐውዱ የተለያየ ትርጉም አለው። ለተጨማሪ ግንዛቤ እነዚህ አናቅጽ ተመልከት፦ 17፥45 38፥32 41፥5 ሌላው ሴት ልጅ የምትሰተርበት ጉፍታ "ሒጃብ" حِجَاب ተብሏል፦ 33፥59 አንተ ነቢዩ ሆይ! ለሚስቶቸህ፣ ለሴቶች ልጆችህ እና ለምእምናን ሚስቶች ከመከናነቢያዎቻቸው በላያቸው ላይ እንዲለቁ ንገራቸው፡፡ يَا أَيُّهَا النَّبِيُّ قُل لِّأَزْوَاجِكَ وَبَنَاتِكَ وَنِسَاءِ الْمُؤْمِنِينَ يُدْنِينَ عَلَيْهِنَّ مِن جَلَابِيبِهِنَّ ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 65 ሐዲስ 312 ዑመር"ረ.ዐ." እንደተናገረው፦ "እኔ የአሏህ መልእክተኛ ሆይ! ሰናይ እና እኩይ ሰዎች ወደ እርሶ ይገባሉ፥ ለምእመናን እናቶች በሒጃብ እንድታሰትራቸው አስጤናለው" አልኩኝ፥ ከዚያም አሏህ የሒጃብ አንቀጽ አወረደ"። قَالَ قَالَ عُمَرُ ـ رضى الله عنه ـ قُلْتُ يَا رَسُولَ اللَّهِ، يَدْخُلُ عَلَيْكَ الْبَرُّ وَالْفَاجِرُ، فَلَوْ أَمَرْتَ أُمَّهَاتِ الْمُؤْمِنِينَ بِالْحِجَابِ، فَأَنْزَلَ اللَّهُ آيَةَ الْحِجَابِ‏.‏ እዚህ ድረስ ከተግባባን አምላካችን አሏህ አንድን ሰው ነቢይ አርድጎ ለማስነሳት በግልጠት ከሚያናግርበት መንገድ አንዱ ከግርዶ ወዲያ ነው፦ 42፥51 ለሰውም አሏህ በራእይ ወይም ከግርዶ ወዲያ ወይም መልእክተኛን መልአክን የሚልክ እና በፈቃዱ የሚሻውን ነገር የሚያወርድለት ቢኾን እንጅ በገሃድ ሊያናግረው ተገቢው አይደለም፡፡ እርሱ የበላይ ጥበበኛ ነውና፡፡ وَمَا كَانَ لِبَشَرٍ أَن يُكَلِّمَهُ اللَّهُ إِلَّا وَحْيًا أَوْ مِن وَرَاءِ حِجَابٍ أَوْ يُرْسِلَ رَسُولًا فَيُوحِيَ بِإِذْنِهِ مَا يَشَاءُ ۚ إِنَّهُ عَلِيٌّ حَكِيمٌ እዚህ አንቀጽ ላይ "ግርዶ" ለሚለው የገባው ቃል "ሒጃብ" حِجَاب ሲሆን አሏህን ሳያዩ በድምፅ ብቻ መስማት ሲሆን ተወዳጁ ነቢያችን"ﷺ" በለይለቱል ኢሥራእ ወል ሚራጅ ጊዜ አምስት ወቅት ሶላትን ሲቀበሉ ያዩት ይህ ሒጃብ ብርሃን ነው፦ ኢማም ሙሥሊም መጽሐፍ 1, ሐዲስ 350 አቢ ዘር እንደተረከው፦ “የአሏህ መልእክተኛን”ﷺ” ጌታህን አይተከዋልን? ብዬ ጠየኳቸው። እርሳቸው፦ "ያየሁት ብርሃን ነው፥ እንዴት እርሱን ማየት እችላለው? አሉ። عَنْ أَبِي ذَرٍّ، قَالَ سَأَلْتُ رَسُولَ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم هَلْ رَأَيْتَ رَبَّكَ قَالَ ‏ “‏ نُورٌ أَنَّى أَرَاهُ ‏”‏ ‏.‏ ሡነን ኢብኑ ማጃህ መጽሐፍ 1, ሐዲስ 201 አቡ ሙሣ እንደተረከው፦ "የአሏህ መልእክተኛም”ﷺ” አሉ፦ “አሏህ አይተኛም፥ እርሱ መተኛት አይገባውም። እርሱ ሚዛኖችን ዝቅ ያረጋል ያነሳልም፥ የእርሱ ግርዶ ብርሃን ነው። أَبِي مُوسَى، قَالَ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ ـ صلى الله عليه وسلم ـ ‏”‏ إِنَّ اللَّهَ لاَ يَنَامُ وَلاَ يَنْبَغِي لَهُ أَنْ يَنَامَ يَخْفِضُ الْقِسْطَ وَيَرْفَعُهُ حِجَابُهُ النُّورُ "መንጦላዕት" የሚለው የግዕዙ ቃል "አንጦልዐ" ማለትም "ጋረደ" "ሸፈነ" ከሚል ሥረወ ቃል የመጣ ሲሆን "መጋረጃ" ማለት ነው። የፈጣሪ መጋረጃ ብርሃን ነው፥ ማንም ሊቀርበው በማይችል በብርሃን መጋረጃ ይኖራል፦ መዝሙር 31፥20 በፊትህ "መጋረጃ" ከሰው ክርክር ትጋርዳቸዋለህ። תסתירם בסתר פניך מרכסי איש መዝሙር 4፥6 በጎውን ማን ያሳየናል? የሚሉ ብዙ ናቸው። ያህዌህ ሆይ! የፊትህ "ብርሃን" በላያችን ታወቀ። רַבִּ֥ים אֹמְרִים֮ מִֽי־יַרְאֵ֪נוּ֫ טֹ֥וב נְֽסָה־עָ֭לֵינוּ אֹ֨ור פָּנֶ֬יךָ יְהוָֽה׃ 1ኛ ጢሞቴዎስ 6፥16 እርሱ ብቻ የማይሞት ነው፥ ማንም ሊቀርበው በማይችል ብርሃን ይኖራል። አንድ ሰው እንኳ አላየውም ሊያይም አይቻለውም። አንድ ሰው እንኳ ያለየው እና ሊያየው የማይቻለው በብርሃን መጋረጃ ስለሚኖር ነው። ከመስማት እና ከመስማማት ይልቅ የመደናቆር እና የመጻረር አባዜ ስለተጠናወታቸው እንጂ በትውፊት እና በአዋልድ መጻሕፍት ውስጥ "ሰባቱ መንጦላይት" የሚባሉት "ሰባቱ የእሳት መጋረጃ" ሲሆኑ አምላክ በእነዚህ ሰባት የእሳት መጋረጃ የተሰወረ ነው፦ ሰይፈ ሥላሴ ዘዓርብ ቁጥር 14 "ሥላሴ "በእሳት መጋረጃ" ውስጥ የተሰወረ ነው"። መዓዛ ቅዳሴ ምዕራፍ 1 ቁጥር 51 "በሱራፌል መካከል "የእሳት መጋረጃ" በፊቱ ጋረደ፥ አሳቡን የሚያውቅ የለም። አኳኃኑን የሚረዳ የለም፥ ስውር በሆነ መሰወሪያው እራሱን ሰወረ"። እንግዲህ ቅንፍጥፍ በማለት ከማዛግ ይልቅ ቅልጥፍጥፍ ብላችሁ በአርምሞ እና በጥሞና ብትመረምሩ እና ብትመራመሩ የአሏህ ምሪት ለማግኘት መደንርደሪያ ነው። አምላካችን አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይስጠን! አሚን። ✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ https://t.me/Wahidcom ወሠላሙ ዐለይኩም
Показать все...
1. ጥያቄ ካላችሁ፣ 2. መረጃ ከፈለጋችሁ፣ 3. መሥለም ከፈለጋችሁ በዚህ አድራሻ አግኙኝ፦ https://m.me/Wahidapologist
Показать все...
"የተደበቀዉ እዉነት" የሚል መጽሐፍ Abdu Book Delivery እኛም ጋር ያገኙታል። አድራሻችን፦ አዲስ አበባ ፒያሳ ለበለጠ መረጃ በ 0929574133 ይደዉሉልን! በዚሁ ስልክ ቁጥር በቴሌ ግራም፣ በዋትሳፕ እና በኢሞ ያነጋግሩን! ክፍለ አገር እና ባሕር ማዶ ላላችሁ የመጻሕፍት ወዳጆች በተመጣጣኝ ዋጋ እና በታማኝነት በያላችሁበት በፍጥነት እንልክላችኋለን። በቴሌግራም👇👇👇 https://t.me/Abdubook በtiktok፦👇??👇👇👇 https://vm.tiktok.com/ZMjLMx7X9
Показать все...