ወሒድ የዕቅበተ ኢሥላም መጣጥፍት"Wahid Articles of Islamic Apologetics"
ዳዒ ወሒድ በኢሥላም እና በክርስትና መካከል ያለውን ልዩነት እና አንድነት በንጽጽር የሚያስቀምጥ ወንድም ነው። ለዚህም የቋንቋ፣ የሰዋስው፣ የዐውድ፣ የተዛማች እና የሥነ አመክንዮ ሙግት በማቅረብ የሚታወቅ ተሟጋች እና ጦማሪ ነው። ለሙግቱ ነጥብ በዋነኝነት የሚጠቀምባቸው ቋንቋ ዐማርኛ፣ ግዕዝ፣ እንግሊዝኛ፣ ዐረቢኛ፣ ዕብራይስጥ እና ግሪክ ናቸው። መልካም የንባብ፣ የጥናት፣ የማነጻጸር ጊዜ ይሁንልዎ!
显示更多📈 Telegram 频道 ወሒድ የዕቅበተ ኢሥላም መጣጥፍት"Wahid Articles of Islamic Apologetics" 的分析概览
频道 ወሒድ የዕቅበተ ኢሥላም መጣጥፍት"Wahid Articles of Islamic Apologetics" (@wahidcom) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 62 453 名订阅者,在 宗教与灵性 类别中位列第 803,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 533 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 62 453 名订阅者。
根据 25 八月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 15,过去 24 小时变化为 0,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 17.86%。内容发布后 24 小时内通常能获得 7.33% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 11 157 次浏览,首日通常累积 4 579 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 0。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“ዳዒ ወሒድ በኢሥላም እና በክርስትና መካከል ያለውን ልዩነት እና አንድነት በንጽጽር የሚያስቀምጥ ወንድም ነው። ለዚህም የቋንቋ፣ የሰዋስው፣ የዐውድ፣ የተዛማች እና የሥነ አመክንዮ ሙግት በማቅረብ የሚታወቅ ተሟጋች እና ጦማሪ ነው። ለሙግቱ ነጥብ በዋነኝነት የሚጠቀምባቸው ቋንቋ ዐማርኛ፣ ግዕዝ፣ እንግሊዝኛ፣ ዐረቢኛ፣ ዕብራይስጥ እና ግሪክ ናቸው። መልካም የንባብ፣ የጥናት፣ የማነጻጸር ጊዜ ይሁንልዎ...”
凭借高频更新(最新数据采集于 01 九月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 宗教与灵性 类别中的关键影响点。
数据加载中...
| 2 | ቡጢ
በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።
22፥11 ከሰዎች በጫፍ ላይ ሆኖ አሏህን የሚያመልክ ሰው አለ። وَمِنَ النَّاسِ مَن يَعْبُدُ اللَّهَ عَلَىٰ حَرْفٍ
"ቡጢ"Boxing" ማለት "አምስት ጣቶችን በማጠፍ እና በመኮርመት ፊት ላይ ድብደባ ማሳረፍ" ማለት ነው፥ ቡጢ ከሥነ ጥበብ"Art" ቢሆንም ሥረ መሠረቱ ግን ዐረማዊ ልማድ"Pagan Custom" ነው። የሮማዊ የትግል፣ የድብድብ፣ ጦርነት አምላክ "ማርስ"Mārs" ሲባል የእርሱ ሥነ ጥበብ "የማርስ ሥነ ጥበብ"Martial art" ተብሎ ይታወቃል፥ ይህ የዐረማዊ ልማድ ከዛ ጀምሮ ዛሬ ላይ በእያንዳንዱ ሕይወት ውስጥ እንደ ጤናማ ስፓርት መታየቱ ማፈር እና መክሰር ነው። ውጪው የትጉኅ እና የታታሪ ሰው መገለጫ ቢመስልም ውስጡ ግን መብረድ እና መንደድ ያለበት ስሜታዊ ጉዳይ ነው፥ በዲኑል ኢሥላም ሰውን በቡጢ ፊቱን መምታት እና መደብደብ ሐራም ነው፦
ኢማም ቡኻሪይ መጽሐፍ 49 ሐዲስ 41 ቁጥር 2559
አቢ ሁረይራህ"ረ.ዐ." እንደተረከው፦ "ነቢዩ"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ "ከእናንተ አንዱ በሚጋደልበት ጊዜ ፊትን ከመምታት ይቆጠብ"። عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ ـ رضى الله عنه ـ عَنِ النَّبِيِّ صلى الله عليه وسلم قَالَ " إِذَا قَاتَلَ أَحَدُكُمْ فَلْيَجْتَنِبِ الْوَجْهَ ".
ይህ በሆነበት አግባብ ቡጢን ከዲን ጋር አያይዞ ጮቤ መርገጥ ምን ያህል ወጥ የረገረ ነገር መሆኑ ከወዲሁ የታወቀ ነው፥ ፊትን መቶ እና ደብድቦ በሚያስሸልም የሐራም ውድድር ላይ አምላካችን አሏህ ጣልቃ አይገባም። ምንም ነገር የሚከናወነው እና የሚሆነው አሏህ ፈቅዶ ቢሆንም በጉዳዩ ላይ ጣልቃ ይገባል ማለት አይደለም፥ በአሏህ ፈቃድ ዙሪያ ከዚህ ቀደም የጦመርኩትን መጣጥፍ መመልከት ይቻላል፦ https://t.me/Wahidcom/4231
ብጥር እና ንጥር አድርገን ስንመለከተው ቡጢ የግሪክ ወሮም ዐረማዊ ልማድ እና የምዕራባውያን እሴት እና እሳቦት እንዲህ እርዮት አና አብዮት ነው፥ የዐረማዊ ልማድ የሚሰነፍግ እና የሚያጥነገንግ መሆኑ እየታወቀ ግን በዚህ ሂደት ውስጥ ዲንን ቁማር አርጎ ማስያዝ ደግሞ እጅግ ሲበዛ ክፉኛ ነገር ነው፦
22፥11 ከሰዎች በጫፍ ላይ ሆኖ አሏህን የሚያመልክ ሰው አለ። ታዲያ መልካም ነገር ቢያገኘው በእርሱ ይረጋል፥ መከራ ብታገኘው በፊቱ ላይ ይገለበጣል፡፡ የቅርቢቱን ዓለም እና የመጨረሻይቱን ዓለም ከሰረ፡፡ ይህ እርሱ ግልጽ ኪሳራ ነው፡፡ وَمِنَ النَّاسِ مَن يَعْبُدُ اللَّهَ عَلَىٰ حَرْفٍ ۖ فَإِنْ أَصَابَهُ خَيْرٌ اطْمَأَنَّ بِهِ ۖ وَإِنْ أَصَابَتْهُ فِتْنَةٌ انقَلَبَ عَلَىٰ وَجْهِهِ خَسِرَ الدُّنْيَا وَالْآخِرَةَ ۚ ذَٰلِكَ هُوَ الْخُسْرَانُ الْمُبِينُ
ሊክድ ወይም ሊያምን ጫፍ ላይ ሆኖ አሏህን እያመለከ ሲሳካለት ዲኑን አጥብቆ የሚይዝ ሳይሳካለት ከዲን የሚገለበጥ የቅርቢቱን ዓለም እና የመጨረሻይቱን ዓለም ከሰረ፥ ስለዚህ ሐራም የሆነውን ቡጢ ይቅርና ማንኛውን ነገር በፉክክር እና በውድድር የሚደረግ ነፍሥያህ ጉዳይ ውስጥ የአሏህ እጅን አስገብቶ ቁማር መጫወት ግልጽ ኪሳራ ነው። የዓለማቱን ጌታን አሏህን ሁለት ሰዎች በሚያደርጉት ነፍሢያህ"Egocentric" ውድድር እና ፉክክር ውስጥ የአሏህን አሕካም ማስገባት ቂልነት እና ዕብደት ነው፥ ከዘር፣ ከዘውግ፣ ከቀለም፣ ከቋንቋ፣ ከብሔር፣ ከባህል ፉክክር እና ውድድር ወጥተን ሊላሂ በሚደረግ ድርጊት"Theocentric" የዓለማቱን ጌታን አሏህ ያግዘናል እጁም አለበት።
"ዐውራህ" عَوْرَة ማለት "ሐፍረተ ገላ" ማለት ሲሆን ዐውራህ የሚገለጠው በቤት ውስጥ ከፈጅር በፊት፣ በዝሁር እና ከዒሻእ በኋላ ሦስት ጊዜያት ነው፦
24፥58 ለእናንተ የኾኑ ሦስት የሐፍረተ ገላ መገለጫ ጊዜያቶች ናቸውና፡፡ ثَلَاثُ عَوْرَاتٍ لَّكُمْ ۚ لَيْسَ عَلَيْكُمْ
እዚህ አንቀጽ ላይ "ሐፍረተ ገላ" ለሚለው የገባው ቃል "ዐውራት" عَوْرَات ሲሆን "ዐውራህ" عَوْرَة ለሚለው ብዙ ቁጥር ነው፥ ይህም ለባለ ትዳሮች ብቻ ሲሆን ነገር ግን አደባባይ ላይ ሐፍረተ ገላን ከፍቶ ለዛውም ለዓለም ሕዝብ ማሳየት ምን ያህል ሐራም መሆኑን ለመረዳት አያዳግትም። ስለዚህ ቡጢ ሰውን የሚጎዳ፣ ቁማር እና ሐፍረተ ገላ የሚታይበት ስለሆነ ሐራም ነው።
እንደ ጥቅል ለመረዳት በፉክክር እና በውድድር ውስጥ የአሏህ ቀደማይ ፈቃድ"Antecedent Will" የሌለበት ቢሆንም ማንኛውምን ግጥሚያ የሚያሸንፈው ጠንክሮ የተለማመደ፣ ስልት ያለው እና የተሻለ ዝግጅት ያደረገው ሰው መሆኑ የአሏህን ደኃራይ ፈቃድ"Consequent Will" ነው። በቡጢ ሰውን የሚጎዱትን አምላካችን አሏህ ሂዳያህ ይስጣቸው! እኛንም ሰውን ከመጉዳት ይጠብቀን! አሚን።
✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://t.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም | 9 356 |
| 3 | 16ኛው ክፍለ ዘመን በፕሮቴስንታንት አውራ አስረገጥ ተሓድሶ"Magisterial Reformation" የተጀመረው ተቃውሞ አምስት ብቻዎች"Five solae" አዋቅሯል፥ እነዚህ አምስት ብቻዎች የሚባሉት፦
1ኛ. መጽሐፍ ብቻ"Sola Scriptura"
2ኛ. እምነት ብቻ"Sola Fide"
3ኛ. ጸጋ ብቻ"Sola Gratia"
4ኛ. ክርስቶስ ብቻ"Solus Christus"
5ኛ. ክብር ለአምላክ ብቻ"Soli Deo Gloria" ናቸው።
"ክብር ለአምላክ ብቻ"Soli Deo Gloria" በሚል ማዕቀፍ ውስጥ ከአምላክ ውጪ ለሌላ ነገር ስግደት ሆነ ክብር ክልክል መሆን ይካተታል፥ ነገር ግን የቲክ ቶክ ፕሮቴስታንት የሙሥሊም ሙግት ሲያንቆራጥጧቸው ለማምለጥ "ለዳዊት የአክብሮት ስግደት ተሰግዶለታል" ብለው አረፉት። ቆይ "የአክብሮት ስግደት" የሚለው ትምህርታችሁ በአንቀጸ እምነታችሁ ከሌለ ከሙግት ለማምለጥ ለምን መዋሸት አስፈለገ?
✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://t.me/Wahidcom | 10 083 |
| 4 | የበላይነት ስሜት"superiority complex" እና የበታችነት ስሜት"inferiority complex" ሁለቱም በሽታዎች ናቸውና የሥነ ልቡና ህክምና ያስፈልጋቸዋል። ላዕላይ በራስ መተማመን"over confidence" ለንቀት፣ ለትዕቢት እና ለውድቀት ይዳርጋል፥ ታኅታይ በራስ መተማመን"under confidence" ለባዶነት፣ ለብቸኝነት እና ለጥፋተኝነት ስሜት ይዳርጋል።
አምላካችን አሏህ እርሱ ባስቀመጠልን አኽላቅ እና አደብ የምንሰተር ያርገን!
✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://t.me/Wahidcom | 10 493 |
| 5 | ዓመተ ፍዳን ወደ ቅድመ ልደት እንዲሁ ዓመተ ምሕረትን ወደ ድኅረት ልደት በትግላችን ቀይረነዋል። የአጼውን ሥርዓት ላይመለስ ቀብረነዋል። | 11 704 |
| 6 | ይህ የቀደምት ሠለፎች ዐቂዳህ ሆኖ ሳለ የራሳቸው ሥነ መለኮት የማያውቁ የክርስትና ዘለሰኛ ሚሽነሪዎች አምላክ "ፊት" እንዳለው እና አማንያን በፍርድ ቀን ፊቱን እንደሚያዩ በቅጡ አልተረዱም፦
ዘጸአት 33፥20 ደግሞም፦ “ሰው አይቶኝ አይድንምና "ፊቴን" ማየት አይቻልህም፡” አለ። וַיֹּאמֶר, לֹא תוּכַל לִרְאֹת אֶת-פָּנָי: כִּי לֹא-יִרְאַנִי הָאָדָם, וָחָי.
እዚህ አንቀጽ ላይ "ፊት" ለሚለው የገባው ቃል "ፓኒም" פָנִים ሲሆን በግሪክ ሰፕቱአጀንት ደግሞ "ፕሮሶፓን" πρόσωπον ነው፦
ዘጸአት 33፥20 ደግሞም፦ “ሰው አይቶኝ አይድንምና "ፊቴን" ማየት አይቻልህም፡” አለ። καὶ εἶπεν· οὐ δυνήσῃ ἰδεῖν τὸ πρόσωπόν μου· οὐ γὰρ μὴ ἴδῃ ἄνθρωπος τὸ πρόσωπόν μου καὶ ζήσεται.
አምላክ "ፊቴ" እያለ "ፊት የለህም" ብሎ ከእርሱ ጋር ሙግት መግጠም ምን የሚሉት ፈሊጥ ነው? የአምላክ ፊት ማንም በዚህ ዓለም ማየት አይችልም። አምላክ ማንም ሊቀርበው በማይችል ብርሃን ውስጥ ሰለሚኖር እርሱን መቼም ቢሆን ከቶ አንድ ስንኳ ያየ የለም፦
1ኛ ዮሐንስ 4፥12 አምላክን ማንም ከቶ አላየውም። Θεὸν οὐδεὶς πώποτε τεθέαται·
ዮሐንስ 1፥18 መቼም ቢሆን አምላክን ያየው አንድ ስንኳ የለም። Θεὸν οὐδεὶς ἑώρακεν πώποτε·
1ኛ ጢሞቴዎስ 6፥16 ማንም ሊቀርበው በማይችል ብርሃን ይኖራል። አንድ ሰው እንኳ አላየውም ሊያይም አይቻለውም።
1ኛ ጢሞቴዎስ 6፥16 አንድ ሰው እንኳ አላየውም ሊያይም አይቻለውም። ὃν εἶδεν οὐδεὶς ἀνθρώπων οὐδὲ ἰδεῖν δύναται·
የጥንት ሰዎች የአምላክ ፊት ለማየት ይጓጓሉ፦
መዝሙር 42፥3 ነፍሴ ወደ ሕያው አምላክ ተጠማች። መቼ እደርሳለሁ? የአምላክንስ "ፊት" መቼ አያለሁ? צָמְאָ֬ה נַפְשִׁ֨י ׀ לֵאלֹהִים֮ לְאֵ֢ל חָ֥֫י מָתַ֥י אָב֑וֹא וְ֝אֵרָאֶ֗ה פְּנֵ֣י אֱלֹהִֽים׃
እዚህ አንቀጽ ላይ "ፊት" ለሚለው የገባው ቃል "ፓኒም" פָנִים ሲሆን በግሪክ ሰፕቱአጀንት ደግሞ "ፕሮሶፓን" πρόσωπον ነው፥ አምላክን በትንሣኤ አካል ማየት የነቢያቱ እሾት ነው፦
ኢዮብ 19፥26 ይህ ቁርበቴም ከጠፋ በኋላ በዚያን ጊዜ ከሥጋዬ ተለይቼ አምላክን እንዳይ አውቃለሁ። እኔ ራሴ አየዋለሁ፥ ዓይኖቼም ይመለከቱታል።
ራእይ 22፥3 ባሪያዎቹም ያመልኩታል፥ ፊቱንም ያያሉ። καὶ οἱ δοῦλοι αὐτοῦ λατρεύσουσιν αὐτῷ, καὶ ὄψονται τὸ πρόσωπον αὐτοῦ,
እዚህ አንቀጽ ላይ "ፊት" ለሚለው የገባው ቃል "ፕሮሶፓን" πρόσωπον ሲሆን በፍርድ ቀን ትልቁ የቅድስና ደረጃ እና ማዕረግ ነጽሮተ አምላክ ነው፦
ማቴዎስ 5፥8 ልበ ንጹሖች ብፁዓን ናቸው፥ አምላክን ያዩታልና።
ዕብራውያን 12፥14 ትቀደሱም ዘንድ ፈልጉ፥ ያለ እርሱ ጌታን ሊያይ የሚችል የለምና።
አላጋጮሻቹ እነዚህን አናቅጽ ሲመለከቱ ምን ይውጣቸው ይሆን? "መንጦላዕት" ማለት "መጋረጃ" ማለት ነው፥ "ነጽሮተ ሥሉስ ቅዱስ" ማለት አማኞች በቅድስና ከፍ ወዳለ ደረጃ ሲደርሱ በመንጦላዕት ያሉትን ሦስት ፊቶች በንጽሕ ልብ እና በዓይነ ሥጋ የማየት ከፍተኛው ደረጃ እና ማዕረግ ነው። የሚገርመው በእኛ ዐቂዳህ የትንሣኤ ቀን የሚታየው አምላክ አንድ ማንነት ሲሆን በእነርሱ ግን የሥላሴ ሦስት ፊቶች ናቸው፥ አትናቴዎስ ዘእስክንድርያ ስለ ሦስቱ ፊቶች እንዲህ ይናገራል፦
ሃይማኖተ አበው ምዕራፍ 28 ቁጥር 29
"የሥሉስ ቅዱስ የሚሆኑ ሦስት አካላት፣ "ሦስት ገጻት" እና ሦስት መልክአት እንዳሉት ስለ መለኮት የተነገረውን ሁሉ እናምናለን"።
"ሦስት ገጻት" የሚለው ይሰመርበት! በግዕዝ "ገጽ" ማለት "ፊት" ማለት ሲሆን "ገጻት" ማለት "ፊቶች" ማለት ነው፥ ከአንድ በላይ የሆኑ ሦስት ፊቶችን "እንመለከታለን" የሚል ተስፋችሁ አንቀጸ እምነታችሁ ከሆነ እንግዲያውስ ሙሥሊሞች በትንሣኤ ቀን በትንሣኤ አካል የአሏህን ፊት በጀናህ መመልከታችን ሊያስደንቃችሁ አይገባም። አምላካችን አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይወፍቀን! አሚን።
✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://t.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም | 12 033 |
| 7 | የአምላክ ፊት
በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
75፥23 ወደ ጌታቸው ተመልካቾች ናቸው፡፡ إِلَىٰ رَبِّهَا نَاظِرَةٌ
"ሲፋህ" صِفَة ማለት "ባሕሪ"Attribute" ማለት ነው፥ የአሏህ ሲፋህ "ሲፋህ ዛቲያህ" صِفَة ذَاتِيَّة እና "ሲፋህ ፊዕሊያህ" صِفَة فِعْلِيَّة ተብሎ ለሁለት ይመደባል።
"ሲፋህ ዛቲያህ" صِفَة ذَاتِيَّة ማለት "የምንነት ባሕሪ"Passive Attribute" ማለት ሲሆን የአሏህ ሕያውነት፣ ዕውቀት፣ ችሎታ፣ ጥበብ፣ ኃይል፣ ዓይን፣ እጅ፣ እግር፣ ፊት ወዘተ "ሲፋህ ዛቲያህ" صِفَة ذَاتِيَّة ነው።
"ሲፋህ ፊዕሊያህ" صِفَة فِعْلِيَّة ማለት "የድርጊት ባሕሪ"Active Attribute" ማለት ሲሆን የአሏህ ፈጣሪነት፣ ፍርድ፣ ይቅርባይነት፣ ከዐርሽ በላይ የበላይነት ወዘተ "ሲፋህ ፊዕሊያህ" صِفَة فِعْلِيَّة ነው።
"ሲፋህ ዛቲያህ" صِفَة ذَاتِيَّة እራሱ "ሲፋህ መዕነዊያህ" صِفَة مَعْنَوِيَّة እና "ሲፋህ ኸበሪያህ" صِفَة خَبَرِيَّة ተብሎ ለሁለት ይመደባል።
"ሲፋህ መዕነዊያህ" صِفَة مَعْنَوِيَّة ማለት "ትርጉማዊ ባሕሪ"Semantic Attribute" ማለት ሲሆን የአሏህ ሕያውነት፣ ዕውቀት፣ ችሎታ፣ ጥበብ፣ ኃይል ወዘተ በዐቅል የምንረዳቸው "ሲፋህ መዕነዊያህ" صِفَة مَعْنَوِيَّة ወይም "ሲፋህ ዐቅሊያህ" صِفَة عَقْلِيَّة ነው።
"ሲፋህ ኸበሪያህ" صِفَة خَبَرِيَّة ማለት "አዋጃዊ ባሕሪ"Informative Attribute" ማለት ሲሆን የአሏህ ዓይን፣ እጅ፣ እግር፣ ፊት ወዘተ በነቅል የምንረዳቸው "ሲፋህ ኸበሪያህ" صِفَة خَبَرِيَّة ወይም "ሲፋህ ነቅሊያህ" صِفَة نَقْلِيَّة ነው።
ይህንን ከተረዳን ዘንዳ "ወጅህ" وَجْه ማለት "ፊት"Face" ማለት ሲሆን የአሏህ ፊት ሲፋህ ዛቲያህ፣ ሲፋህ ኸበሪያህ፣ ሲፋህ ነቅሊያህ ነው። የአምላካችን የአሏህን ፊት የፍጡራን ዓይኖች አያካብቡትም፥ አሏህ ረቂቅ ነው፦
6፥103 ዓይኖች አያካብቡትም፡፡ እርሱም ዓይኖችን ያካብባል፡፡ እርሱ ረቂቁ ውስጠ ዐዋቂው ነው፡፡ لَّا تُدْرِكُهُ الْأَبْصَارُ وَهُوَ يُدْرِكُ الْأَبْصَارَ ۖ وَهُوَ اللَّطِيفُ الْخَبِيرُ
"አል-ለጢፍ" اللَّطِيف ማለት "ረቂቁ" ማለት ሲሆን የአሏህ ግርዶ ብርሃን ነው፥ ግርዶሹን ቢገልጠው "ፊቱ" ያገኘውን ነገር ሁሉ ያቃጥላል፦
ሡነን ኢብኑ ማጃህ መጽሐፍ 1, ሐዲስ 201
አቡ ሙሣ እንደተረከው፦ "የአሏህ መልእክተኛም”ﷺ” አሉ፦ “አሏህ አይተኛም፥ እርሱ መተኛት አይገባውም። እርሱ ሚዛኖችን ዝቅ ያረጋል ያነሳልም፥ የእርሱ ግርዶ ብርሃን ነው። ግርዶሹን ቢገልጠው "ፊቱ" ያገኘውን ነገር ሁሉ ያቃጥላል"። عَنْ أَبِي مُوسَى، قَالَ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ ـ صلى الله عليه وسلم ـ " إِنَّ اللَّهَ لاَ يَنَامُ وَلاَ يَنْبَغِي لَهُ أَنْ يَنَامَ يَخْفِضُ الْقِسْطَ وَيَرْفَعُهُ حِجَابُهُ النُّورُ لَوْ كَشَفَهَا لأَحْرَقَتْ سُبُحَاتُ وَجْهِهِ كُلَّ شَىْءٍ أَدْرَكَهُ بَصَرُهُ "
ነገር ግን በፍርድ ቀን አማንያን አምላካችን አሏህን ተመልካቾች ናቸው፥ በተቃራኒው ከሓዲያን አሏህን ከማየት ተጋራጆች ናቸው፦
75፥23 ወደ ጌታቸው ተመልካቾች ናቸው፡፡ إِلَىٰ رَبِّهَا نَاظِرَةٌ
84፥15 ይከልከሉ! እነርሱ በዚያ ቀን ከጌታቸው ማየት ተጋራጆች ናቸው፡፡ كَلَّا إِنَّهُمْ عَن رَّبِّهِمْ يَوْمَئِذٍ لَّمَحْجُوبُونَ
የአሏህ ግርዶ ብርሃን ነው፥ አማንያን በጀናህ ውስጥ ተጨማሪ የሚያገኙት መንፈሳዊ ጸጋ የአሏህ ፊት መመልከት ነው፦
ኢማም ሙስሊም መጽሐፍ 1 ሐዲስ 354
ሱሐይብ እንደተረከው፦ "ነቢዩም"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ "እነዚያ የጀናህ ባለቤቶች ጀነናህ በሚገቡ ጊዜ የተከበረው እና ከፍ ያለው አሏህ፦ “ጭማሪ እንድሰጣችሁ ትፍልጋላችሁን? ብሎ ይጠይቃቸዋል፥ እነርሱም፦ ፊታችንን አላበራህምን? ወደ ጀናህ አላስገባከንምን? ከእሳትስ አላዳንከንምን? ይላሉ፥ ከዚያ እርሱ ግርዶሹን ያነሳል፥ እርሱ ለእነርሱ የወደደው አሸናፊው እና ክብራማ የሆነውን ከጌታቸውን "ፊት" በስተቀር ለእነርሱ ምንም ነገር በእነርሱ ዘንድ የለም"። عَنْ صُهَيْبٍ، عَنِ النَّبِيِّ صلى الله عليه وسلم قَالَ " إِذَا دَخَلَ أَهْلُ الْجَنَّةِ الْجَنَّةَ - قَالَ - يَقُولُ اللَّهُ تَبَارَكَ وَتَعَالَى تُرِيدُونَ شَيْئًا أَزِيدُكُمْ فَيَقُولُونَ أَلَمْ تُبَيِّضْ وُجُوهَنَا أَلَمْ تُدْخِلْنَا الْجَنَّةَ وَتُنَجِّنَا مِنَ النَّارِ - قَالَ - فَيَكْشِفُ الْحِجَابَ فَمَا أُعْطُوا شَيْئًا أَحَبَّ إِلَيْهِمْ مِنَ النَّظَرِ إِلَى رَبِّهِمْ عَزَّ وَجَلَّ " | 9 178 |
| 8 | የእንጨት አምልኮ
በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
11፥2 እንዲህ በላቸው፡- «አሏህን እንጂ ሌላን አታምልኩ! እኔ ለእናንተ ከእርሱ የተላክሁ አስጠንቃቂ እና አብሳሪ ነኝ»። أَلَّا تَعْبُدُوا إِلَّا اللَّهَ ۚ إِنَّنِي لَكُم مِّنْهُ نَذِيرٌ وَبَشِيرٌ
በኦርቶዶክስ እና በካቶሊክ ክርስትና "ዕፀ መስቀል" የሚባል ስግደት እና አምልኮ የሚቀበል ግዑዝ ነገር አለ፥ "ዕፅ" ማለት "እንጨት" ማለት ሲሆን "ዕፀ መስቀል" ማለት "የእንጨት መስቀል" ማለት ነው። በግሪክ ኮይኔ "ስታውሮስ ክይሎን" σταυρός ξύλον ሲባል ይህ የእንጨት መስቀል የማይሰማ እና የማይለማ እንዲሁ የማይናገር እና የማይጋገር ግዑዝ ነገር ሆኖ ሳለ በኦርቶዶክስ ይሰገድለታል፦
የዘወትር ፀሎት ቁጥር 8
"ዓለምን ለማዳን ሲል ኢየሱስ ክርስቶስ “ለ”-ተሰቀለበት መስቀል እሰግዳለው"
ለእንጨት መስቀል መስገድ አግባብ ነውን? ዘርዓ ያዕቆብ ከደረሳቸው መጻሕፍት አንዱ "መስተብቁዕ ዘመስቀል" ነው፥ "መስተብቁዕ" ማለት "ልመና" "ጸሎት" ማለት ሲሆን "መስተብቁዕ ዘመስቀል" ማለት "የመስቀል ልመና" ማለት ነው። መስተብቁዕ ዘመስቀል ላይ መስቀል እና ማርያም ከፈጣሪ ጋር ተካክለው ምስጋና እንደሚቀርብላቸው ይናገራል፦
መስተብቁዕ ዘመስቀል ቁጥር 8
"ለእሉ ክልኤቱ ፍጡራን ስብሐተ ፈጣሪ ይደልዎሙ እስመ ተዐረዩ በክብሮሙ"
"ለእነዚህ ሁለት ፍጥረታት የፈጣሪ ምስጋና ይገባቸዋል፥ በክብር ተካክለዋልና"
"ሁለቱ" የተባሉት "መስቀል እና ማርያም" ሲሆኑ እነዚህ ሁለት ፍጡራን ከፈጣሪ ጋር "በክብር ተካክለዋል" ይለናል፥ ኢየሱስን፦ "ዘዕሩይ ምስለ አብ በመለኮቱ(በባሕይርው ከአብ ጋር የሚተካከል)" ሲሉት ሲገርመን ማርያም እና መስቀልን "እስመ ተዐረዩ በክብሮሙ(በክብር ተካክለዋል)" ሲሏቸው አስደመመን። ስለተስተካከሉ ለፈጣሪ የሚገባው የፈጣሪ ምስጋና "ይገባቸዋል" ብለው አረፉት፥ ይህ እልም ያለ ሺርክ ነው። ስብሐት(ምስጋና) ለሦስቱ ማለትም ለእግዚአብሔር፣ ለድንግል እና ለመስቀል እንደሚገባ የዘወትር ጸሎት ላይ ተገልጿል፦
የዘወትር ጸሎት ቁጥር 9
"ስብሐት ለእግዚአብሔር ወወላዲቱ ድንግል ወለመስቀሉ ክቡር"
ትርጉም፦ "ለእግዚአብሔር፣ ለወለደችው ለድንግል እና ለክቡር መስቀሉ ምስጋና ይገባል"
እንደ ሥላሴ አስተምሮት አብ፣ ወልድ እና መንፈስ ቅዱስ ፈጽመው ሳይለያዩ እንደሚስተካከሉ ሁሉ እግዚአብሔር፣ ድንግል ማርያም እና መስቀል በክብር ይተካከላሉ፦
ድርሳነ መድኃኔ ዓለም ዘሰኑይ ምዕራፍ 10 ቁጥር 19
"ይህ መስቀል እንደ እግዚአብሔር የከበረ እንደ ድንግል ማርያም ከፍ ያለ ነው፥ ሦስትነታቸው ትክክል የሚሆን እንደ አብ፣ እንደ ወልድ፣ እንደ መንፈስ ቅዱስ ፈጽሞ የማይለይ ነው። እንዲሁም መድኃኒታችን ከእናቱ እና ከመስቀል ጋር ሦስትነታቸው ትክክል ነው፥ እንዲህ እናምናለን እንዲህ እናመልካለን"።
"እንዲህ እናምናለን እንዲህ እናመልካለን" የሚለው ይሰመርበት! "መድኃኒታችን ከእናቱ እና ከመስቀል ጋር ሦስትነታቸው ትክክል ነው" ካለ ሌላ ሥላሴ ሆኑ ማለት ነው፥ በተጨማሪ ማርያምን እና መስቀልን ከእግዚአብሔር ጋር "እናመልካለን" ካሉ ዓይን ያስፈጠጠ እና ጥርስ ያስገጠጠ ባዕድ አምልኮ ነው። "የማናቸውንም ምሳሌ፥ የተቀረጸውንም ምስል ለአንተ አታድርግ፣ አትስገድላቸው፣ አታምልካቸውም" እየተባለ ለማይሰማ እና ለማይለማ፥ ለማይናገር እና ለማይጋገር ለግዑዝ እንጨት ስግደት መስገድ እና አስተካክሎ ማምለክ አግባብ አይደለም፥ ይህ ድርጊት አሳፋሪ እንደሆነም ተገልጿል፦
መዝሙር 97፥7 "ለተቀረጸ ምስል የሚሰግዱ" ሁሉ እና በጣዖቶቻቸው የሚመኩ ይፈሩ።
ዘጸአት 20፥4 የማናቸውንም ምሳሌ፥ የተቀረጸውንም ምስል ለአንተ አታድርግ! አትስገድላቸው፥ አታምልካቸውምም።
"ለተቀረጸ ምስል የሚሰግዱ ሁሉ ይፈሩ" የሚለው ይሰመርበት! ለተቀረጸ ምስል መስገድ"Icon veneration" በኦርቶዶክስ እና በካቶሊክ ክርስትና እሙን እና ቅቡል የሆነ ትምህርት ነው። እኛም ሙሥሊሞች ደግሞ ለእናንተ የምንለው ትልቅ ቁም ነገር "የፈጠራችሁን "እኔን ብቻ አምልኩኝ" ያለውን አሏህን ብቻ በብቸኝነት አምልኩ" ማለትን ነው፦
29፥56 እናንተ ያመናችሁ ባሮቼ ሆይ! ምድሬ በእርግጥ ሰፊ ናት፥ ብትቸገሩ ተሰደዱ። "እኔን ብቻ አምልኩኝ"፡፡ يَا عِبَادِيَ الَّذِينَ آمَنُوا إِنَّ أَرْضِي وَاسِعَةٌ فَإِيَّايَ فَاعْبُدُونِ
11፥2 እንዲህ በላቸው፡- «አሏህን እንጂ ሌላን አታምልኩ! እኔ ለእናንተ ከእርሱ የተላክሁ አስጠንቃቂ እና አብሳሪ ነኝ»። أَلَّا تَعْبُدُوا إِلَّا اللَّهَ ۚ إِنَّنِي لَكُم مِّنْهُ نَذِيرٌ وَبَشِيرٌ
የፈጠረንን አንዱን አምላክ ብቻ ማምለክ ምንኛ መታደል ነው? አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይስጠን! አሚን።
✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://t.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም | 15 110 |
| 9 | ፍዝዝ እና ድንዝዝ ብላችሁ መውቀሱን እና መክሰሱን ትታችሁ በእናንተም መጽሐፍ አምላክ ሰዎች ሁሉ እንዲድኑ እና እውነቱን ወደ ማወቅ እንዲደርሱ ይፈልጋል፦
1ኛ ጢሞቴዎስ 2፥4 እርሱ ሰዎች ሁሉ እንዲድኑ እና እውነቱን ወደ ማወቅ እንዲደርሱ "ይፈልጋል"። ὃς πάντας ἀνθρώπους θέλει σωθῆναι καὶ εἰς ἐπίγνωσιν ἀληθείας ἐλθεῖν.
በአዲሱ መደበኛ ትርጉም "ይፈልጋል" ለሚለው የገባው ቃል "ቴሌይ" θέλει ሲሆን ሥርወ ቃሉ "ቴሎ" θέλω ነው፥ "ቴሌማ" θέλημά ማለት "ፈቃድ"will" ማለት ሲሆን ቴሌማ እራሱ "ቴሌማ አፖዶሲስ" θέλημά ἀπόδοσις እና "ቴሌማ ፕሮታሲስ" θέλημά πρότᾰσῐς ተብሎ ለሁለት ይከፈላል። "ቴሌማ አፖዶሲስ" θέλημά ἀπόδοσις ማለት "ቀዳማይ ፈቃድ" ማለት ሲሆን ሰዎች ሁሉ እንዲድኑ እና እውነቱን ወደ ማወቅ እንዲደርሱ የአምላክ ቀዳማይ ፈቃድ ነው፥ "ቴሌማ ፕሮታሲስ" θέλημά πρότᾰσῐς ማለት "ደኃራይ ፈቃድ" ማለት ሲሆን ሰዎች ካመፁ ለገሃነም መሆናቸው የአምላክ ደኃራይ ፈቃድ ነው። ዮሐንስ ዘደማስቆ"John of Damascus" ይህንን ነጥብ አፋፍቶ እና አዳብሮ አስቀምጦታል፦
"እንዲሁም የአምላክ የመጀመሪያ ፍላጎት ሁሉም ሰው እንዲድን እና ወደ መንግሥቱ እንዲመጣ መሆኑን ማስታወስ አለብን! 1ኛ ጢሞቴዎስ 2፥4 እርሱ ቸር አምላክ ስለሆነ ከቸርነቱ እንድንካፈል እንጂ ለቅጣት አላዘጋጀንም፥ ነገር ግን እርሱ ፍትሓዊ አምላክ ስለሆነ ኃጢአተኞች ቅጣት እንዲደርስባቸው ፈቃዱ ነው። የመጀመሪያው የአምላክ ቀዳማይ ፈቃድ እና ደስታ፣ ከእርሱ የመነጨ፣ ተብሎ ይጠራል፥ ሁለተኛው ደግሞ የአምላክ ደኃራይ ፈቃድ እና ፍላጎት፣ መነሻው በእኛ ውስጥ ተብሎ ይጠራል"።
Exposition of the Orthodox Faith (John of Damascus) Book II(2) chapter 29
ዮሐንስ ዘደማስቆ ይህንን ያብራራው 1ኛ ጢሞቴዎስ 2፥4 ያለውን ዐውድ በተናገረበት ነው። ዮሐንስ አፈ ወርቅ"John Chrysostom" ይህንን ነጥብ ፊት የማያስመልስ አገንት የማያስቀልስ አድርጎ አስቀምጦታል፦
"ይህ ማለት ግን እርሱ ከምሩ ስለፈቀደ ነው፥ ይህ አንድ ኃያል እንደሚለው የእርሱ ምራዊ ፍላጎት ነው። መልካም ደስታ የሚለው ቃል በሁሉም ቦታ ማለት ቀዳማይ ፈቃድ ማለት ነው፥ ምክንያቱም ሌላ ፈቃድም አለ። ለምሳሌ፦ የመጀመሪያው ፈቃድ ኃጢአተኞች እንዳይጠፉ ነው፥ ሁለተኛው ፈቃድ ሰዎች ክፉ ከሆኑ እንዲጠፉ ነው"።
Homilies on Ephesians (Chrysostom) Homily 1 Ephesians 1፥5
እንግዲህ እነዚህ አበው ከተቀበላችሁ በቁርኣን የተቀመጠውን የአሏህን ፈቃድ ውልግድ እና ውልብድ፣ ወለም እና ዘለም፣ ውልፍጥ እና ዝልፍጥ ሳትሉ በቅጡ እና በአግባብ መረዳት ትችላላችሁ። አምላካችን አሏህ ሂዳያህ ይወፍቃችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይወፍቀን! አሚን።
✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://t.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም | 11 402 |
| 10 | የአሏህ ፈቃድ
በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።
81፥29 የዓለማቱ ጌታ አሏህ ካልፈቀደ አትፈቅዱም፡፡ وَمَا تَشَاءُونَ إِلَّا أَن يَشَاءَ اللَّهُ رَبُّ الْعَالَمِينَ
"መሺኣህ" مَشِئَة የሚለው ቃል "ሻአ" شَاءَ ማለትም "ፈቀደ" ከሚለው ሥርወ ቃል የመጣ ሲሆን "ፈቃድ"Will" ማለት ነው፥ የአሏህ ፈቃድ "መሺኣህ ሙቀደማህ" مَشِئَة مُقَدِّمَة እና "መሺኣህ ነቲጃህ" مَشِئَة نَتِيجَة ተብሎ ለሁለት ይከፈላል።
፨ "ሙቀደማህ" مُقَدِّمَة ማለት "ቀዳማይ"Antecedent" ማለት ሲሆን "መሺኣህ ሙቀደማህ" مَشِئَة مُقَدِّمَة ማለት "ቀደማይ ፈቃድ"Antecedent Will" ማለት ነው፥ አምላካችን አሏህ ለዓለማት በደልን የሚሻ አይደለም፡፡ ለባሪያዎቹ ከህደትን አይወድም፦
3፥108 አሏህ ለዓለማት በደልን የሚሻ አይደለም፡፡ وَمَا اللَّهُ يُرِيدُ ظُلْمًا لِّلْعَالَمِينَ
23፥31 አሏህ ለባሮቹ በደልን የሚሻ አይደለም፡፡ وَمَا اللَّهُ يُرِيدُ ظُلْمًا لِّلْعِبَادِ
ሰዎች ቢክዱ አሏህ ከከሓዲዎች የተብቃቃ ነው፥ ለባሪያዎቹም ከህደትን አይወድም። ብናምን ግን እርሱን ይወድልናል፦
39፥7 ብትክዱ አሏህ ከእናንተ የተብቃቃ ነው፥ ለባሪያዎቹም ከህደትን አይወድም። ብታመሰግኑ እርሱን ይወድላችኋል፡፡ إِن تَكْفُرُوا فَإِنَّ اللَّهَ غَنِيٌّ عَنكُمْ ۖ وَلَا يَرْضَىٰ لِعِبَادِهِ الْكُفْرَ ۖ وَإِن تَشْكُرُوا يَرْضَهُ لَكُمْ
አሏህ በሰዎች ገሩን ነገር መሻቱ እና በሰዎች ችግሩን አለመሻቱ የእርሱ ቀደማይ ፈቃድ ነው፦
2፥185 አሏህ በእናንተ ገሩን ነገር ይሻል፥ በእናንተም ችግሩን አይሻም፡፡ يُرِيدُ اللَّهُ بِكُمُ الْيُسْرَ وَلَا يُرِيدُ بِكُمُ الْعُسْرَ
፨ "ነቲጃህ" نَتِيجَة ማለት "ደኃራይ"Consequent" ማለት ሲሆን "መሺኣህ ነቲጃህ" مَشِئَة نَتِيجَة ማለት "ደኃራይ ፈቃድ"Consequent Will" ማለት ነው፥ አምላካችን አሏህ ለሰው የሰጠውን ፈቃድ በአሏህ ደኃራይ ፈቃድ ሥር ነው፦
81፥29 የዓለማቱ ጌታ አሏህ ካልፈቀደ አትፈቅዱም፡፡ وَمَا تَشَاءُونَ إِلَّا أَن يَشَاءَ اللَّهُ رَبُّ الْعَالَمِينَ
አሏህ በደኃራይ ፈቃዱ ለሰው ነጻ ፈቃድ ስለሰጠው ሰው የማመን እና የመካድ ፈቃድ አለው፦
18፥29 «እውነቱም ከጌታችሁ ነው፡፡ የፈቀደ ሰው ይመን፤ የፈቀደ ሰው ይካድ» በላቸው፡፡ وَقُلِ الْحَقُّ مِن رَّبِّكُمْ ۖ فَمَن شَاءَ فَلْيُؤْمِن وَمَن شَاءَ فَلْيَكْفُر
"የፈቀደ" ለሚለው የግሥ መደብ የገባው ቃል "ሻአ" شَاءَ ሲሆን ሰው ኸይር እና ሸር የሆኑ ሁለት አማራጭ መምረጥ የሚችል ፍጡር መሆኑን በቂ ማሳያ ነው፦
72፥14 የሠለሙ ሰዎች እነዚያ ቅንን መንገድ መረጡ፡፡ فَمَنْ أَسْلَمَ فَأُولَـٰئِكَ تَحَرَّوْا رَشَدًا
41፥17 ሰሙዶችማ መራናቸው ዕውርነትንም በቅንነት ላይ መረጡ፡፡ وَأَمَّا ثَمُودُ فَهَدَيْنَاهُمْ فَاسْتَحَبُّوا الْعَمَىٰ عَلَى الْهُدَىٰ
አሏህ ቢሻ ኖሮ በምድር ያሉት ሰዎች ሁሉ አማኝ ያረግ ነበር፥ በተቃራኒው አሏህ ቢሻ ኖሮ ከሓድያንን ባላጋሩ ነበር፦
10፥99 ጌታህም ቢሻ ኖሮ በምድር ያሉት ሰዎች ሁሉም የተሰበሰቡ ሆነው ባመኑ ነበር፡፡ ታዲያ አንተ ሰዎችን አማኞች እንዲኾኑ ታስገድዳለህን?። وَلَوْ شَآءَ رَبُّكَ لَـَٔامَنَ مَن فِى ٱلْأَرْضِ كُلُّهُمْ جَمِيعًا ۚ أَفَأَنتَ تُكْرِهُ ٱلنَّاسَ حَتَّىٰ يَكُونُوا۟ مُؤْمِنِينَ
6፥107 አሏህ ቢሻ ኖሮ ባላጋሩ ነበር፥ በእነርሱ ላይ ጠባቂ አላደረግንህም፡፡ አንተ በእነርሱ ላይ ኃላፊ አይደለህም፡፡ وَلَوْ شَاءَ اللَّهُ مَا أَشْرَكُوا ۗ وَمَا جَعَلْنَاكَ عَلَيْهِمْ حَفِيظًا ۖ وَمَا أَنتَ عَلَيْهِم بِوَكِيلٍ
አሏህ በቀዳማይ ፈቃዱ ሁሉንም አማኝ ቢያደርግ ማስገደድ ስለሆነ ከነጻ ፈቃድ ጋር ይጻረር ነበር፥ በተቃራኒው በቀዳማይ ፈቃዱ ከሓዲያን እንዳይክዱ ቢያደርግ ማስገደድ ስለሆነ ከግብረገባዊ ተጠያቂነት ጋር ይጻረር ነበር። ሰዎች በነጻ ፈቃዳቸው እንዲያምኑ መፍቀዱ እና በነጻ ፈቃዳቸው እንዲክዱ መፈቀዱ ደኃራይ ፈቃዱ ነው፥ አማንያን ወደ ጀነት የሚገቡት በእምነታቸው ምክንያት እና ይሠሩት በነበሩት ምክንያት ነው፦
10፥9 እነዚያ ያመኑ እና መልካም ሥራዎችን የሠሩ ጌታቸው "በእምነታቸው ምክንያት" የገነትን መንገድ ይመራቸዋል፥ ከሥራቸው ወንዞች ይፈስሳሉ፡፡ በመጠቀሚያ ገነቶች ውስጥ ይኖራሉ፡፡ إِنَّ الَّذِينَ آمَنُوا وَعَمِلُوا الصَّالِحَاتِ يَهْدِيهِمْ رَبُّهُم بِإِيمَانِهِمْ ۖ تَجْرِي مِن تَحْتِهِمُ الْأَنْهَارُ فِي جَنَّاتِ النَّعِيمِ
46፥14 እነዚያ የገነት ጓዶች ናቸው፡፡ በእርሷ ውስጥ ዘውታሪዎች ሲኾኑ፡፡ በዚያ "ይሠሩት በነበሩት ምክንያት" ታላቅን ምንዳ ይመነዳሉ፡፡ أُولَـٰئِكَ أَصْحَابُ الْجَنَّةِ خَالِدِينَ فِيهَا جَزَاءً بِمَا كَانُوا يَعْمَلُونَ
"በእምነታቸው ምክንያት" "ይሠሩት በነበሩት ምክንያት" የሚለው ይሰመርበት! በተቃራኒው ከሓዲያን ወደ ጀሀነም የሚገቡት በክህደታቸው ምክንያት እና ይሠሩት በነበሩት ምክንያት ነው፦
6፥30 «ትክዱት በነበራችሁት "ምክንያት" ቅጣቱን ቅመሱ» ይላቸዋል፡፡ قَالَ فَذُوقُوا الْعَذَابَ بِمَا كُنتُمْ تَكْفُرُونَ
10፥8 እነዚያ "ይሠሩት በነበሩት "ምክንያት" መኖሪያቸው በእሳት ውስጥ ነው፡፡ أُولَـٰئِكَ مَأْوَاهُمُ النَّارُ بِمَا كَانُوا يَكْسِبُونَ
"ትክዱት በነበራችሁት ምክንያት" "ይሠሩት በነበሩት ምክንያት" የሚለው ይሰመርበት! ስለዚህ የአሏህ ቀደማይ ፈቃድ ሰው ከጀሀነም እንዲድን ነው፥ ነገር ግን ሰው በምርጫው የጀሀነም መሆን ከፈለገ አሏህ ይህንን ጉዳይ መፍቀዱ የአሏህ ደኃራይ ፈቃዱ ነው። | 8 631 |
| 11 | ኢየሱስ መንገድ ነው!
በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።
5፥75 የመርየም ልጅ አልመሢሕ ከበፊቱ መልክተኞች በእርግጥ ያለፉ የኾነ መልክተኛ እንጅ ሌላ አይደለም፡፡ مَّا الْمَسِيحُ ابْنُ مَرْيَمَ إِلَّا رَسُولٌ قَدْ خَلَتْ مِن قَبْلِهِ الرُّسُلُ
ኢየሱስ ወደ ጌታ አምላክ የሚያደርስ መንገድ ስለሆነ ለፊልጶስ፦ "የእውነት እና የሕይወት መንገድ እኔ ነኝ" አለው፦
ዮሐንስ 14፥6 ኢየሱስም እንዲህ አለው፦ "የእውነት እና የሕይወት መንገድ እኔ ነኝ፥ በእኔ በኩል ካልሆነ በቀር ወደ አብ የሚመጣ የለም"።(የ 2000 ዕትም 80 አሓዱ)
ግዕዙም በተመሳሳይ፦ "አነ ውእቱ ፍኖተ ጽድቅ ወሕይወት" እንደሚለው ተመልከት! "መንገድ" ማለት በመነሻ እና በመዳረሻ መካከል ያለ "መካከለኛ"Mediator" ነው፥ ካለ መካከለኛ መልእክተኛ በኩል ወደ ጌታ አምላክ መድረስ አይቻልም፦
1 ጢሞቴዎስ 1፥5 አንድ አምላክ አለና፥ በአምላክ እና በሰዎች መካከል ያለው "መካከለኛው" ደግሞ አንድ አለ፥ እርሱም ሰው የሆነ ክርስቶስ ኢየሱስ ነው። εἷς γὰρ Θεός, εἷς καὶ μεσίτης Θεοῦ καὶ ἀνθρώπων, ἄνθρωπος Χριστὸς Ἰησοῦς,
ይህ ጥቅስ በግልጽ እና በማያሻማ መልኩ "መካከለኛ" የተባለው ከአንዱ አምላክ ውጪ "ሰው" እንደሆነ ይናገራል፥ እዚህ አንቀጽ ላይ "መካከለኛ" ለሚለው የገባው ቃል "ሜሲተስ" μεσίτης ነው። ሙሴ ከኢየሱስ መላክ በፊት በብሉይ ኪዳን በአምላክ እና በሕዝቡ መካከል ሆኖ መልእክት ሲያስተላልፍ የነበረ መካከለኛ ነበረ፦
ዘዳግም 5፥5 እኔ የያህዌህን ቃል እነግራችሁ ዘንድ በዚያን ጊዜ በያህዌህ እና በእናንተ መካከል ቆሜ ነበር።
"በያህዌህ እና በእናንተ መካከል" የሚለው ኃይለ ቃል ይሰመርበት! ሙሴ ተስፋው የተሰጠው ዘር መሢሑ እስኪመጣ "መካከለኛ" ነበረ፦
ገላትያ 3፥19 ሕጉ የመጣው በመላእክት በኩል በአንድ "መካከለኛ እጅ" ነበር።(አዲሱ መደበኛ ትርጉም) διαταγεὶς δι’ ἀγγέλων ἐν χειρὶ μεσίτου.
ሕግ የመጣው በመላእክት በኩል ነው፥ በተለይ "በስተ ቀኙም የእሳት ሕግ ነበረላቸው" የሚለውን ስንረዳ የእሳት ሕግ የተባለው ቶራህ ሲሆን ቅዱሳኑ የተባሉት መላእክት ናቸው።
ዘዳግም 33፥2 የሐዋርያት ሥራ 7፥53 ዕብራውያን 2፥2 ተመልከት!
ገላትያ 3፥19 "መካከለኛ" ለሚለው የገባው ቃል "ሜሲቶዩ" μεσίτου ሲሆን "እጅ" የሚለውን ለማገናዘብ የመጣ አገናዛቢ ነው፥ ይህም "መካከለኛ" የሚለው ቃል "ሙሴ" የሚለውን ስም ተክቶ የመጣ ነው። ዘኍልቍ 4፥37 ነህምያ 9፥14 ነህምያ 10፥29 ነህምያ 8፥15 ተመልከት!
"በመካከለኛ እጅ" የሚለው "በሙሴ እጅ" የሚለውን ለመተካት የመጣ እንደሆነ ካየን ዘንዳ ሙሴ "መካከለኛ" መባሉ አስረግጠን እና ረግጠን መናገር እንችላለን። መካከለኛው ሙሴ መካከለኛነቱ ለአንድ ማንነት ሳይሆን ለአዛዥ አምላክ እና ለታዛዥ ሕዝቡ ሲሆን አምላክ ግን አንድ ማንነት ነው፦
ገላትያ 3፥20 መካከለኛውም ለአንድ ብቻ አይደለም፥ አምላክ ግን አንድ ነው። ὁ δὲ μεσίτης ἑνὸς οὐκ ἔστιν, ὁ δὲ Θεὸς εἷς ἐστιν.
ኢዮብ 9፥32 እጁን በሁለታችን ላይ የሚያኖር "መካከለኛ" በመካከላችን ምነው በተገኘ። εἴθε ἦν ὁ μεσίτης ἡμῶν καὶ ἐλέγχων καὶ διακούων ἀνὰ μέσον ἀμφοτέρων·
ኢዮብ ከሙሴ በፊት በእርሱ እና በአምላኩ መካከል "መካከለኛ" እንዲኖር ተመኝቶ ከ 400 ዓመት በኃላ ሙሴ መካከለኛ ሆኖ ተነስቷል። ታዲያ ሙሴ ምን ነበር? ሰው እና ነቢይ ወይስ የአምላክ እና የሰው ውሕደት? "መካከለኛ" ማለት "የአምላክ እና የሰው ውሕደት" ነው" ብለው የሚቀጥፉ ሰዎች ሙሴ "መካከለኛ" መባሉን ሲረዱ ምን ይውጣቸው ይሆን? ኢየሱስም በአዲስ ኪዳን "መካከለኛ" የተባለው ሙሴ በተባለበት ቀመር እና ሒሣብ ነው፥ ይህም ሰው በአምላክ እና በሕዝቡ መካከል በሥራ እና በቃል ብርቱ ነቢይ የነበረው የናዝሬቱ ኢየሱስ ነው። የናዝሬቱ ኢየሱስ ከአምላክ እየሰማ ለሕዝቡ የሚናገር መካከለኛ ሰው ነበር፦
ሉቃስ 24፥19 በአምላክ እና በሕዝቡ ሁሉ ፊት በሥራ እና በቃል ብርቱ ነቢይ ስለ ነበረው ስለ ናዝሬቱ ስለ ኢየሱስ።
ዮሐንስ 8፥40 ነገር ግን አሁን ከአምላክ የሰማሁትን እውነት የነገርኋችሁን ሰው ልትገድሉኝ ትፈልጋላችሁ?።
አምላክ ባለቤት ሲሆን ሰው ተሳቢ ነው፥ በባለቤት እና በተሳቢ መካከል "የሰማሁት" የሚል አጫፋሪ ግሥ አለ። ይህ ቁልጭ እና ፍንትው አድርጎ የሚያሳየው በላከው አምላክ እና በተላከው መካከለኛ ሰው ያለውን የማንነት እና የምንነት ልዩነት ነው። እርግጥ ነው! ኢየሱስ ከበፊቱ መልክተኞች በእርግጥ ያለፉ የኾነ መልክተኛ እንጅ ሌላ አይደለም፦
5፥75 የመርየም ልጅ አልመሢሕ ከበፊቱ መልክተኞች በእርግጥ ያለፉ የኾነ መልክተኛ እንጅ ሌላ አይደለም፡፡ مَّا الْمَسِيحُ ابْنُ مَرْيَمَ إِلَّا رَسُولٌ قَدْ خَلَتْ مِن قَبْلِهِ الرُّسُلُ
አምላካችን አሏህ በእርሱ መንገድ ከሚጓዙ ባሮቹ ያርገን! ከጥመት መንገድ ይጠብቀን! አሚን።
✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://t.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም | 9 389 |
| 12 | የአምልኮ መገዛት
በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
3፥51 «አሏህ ጌታዬ እና ጌታችሁ ነው፥ ስለዚህ አምልኩት! ይህ ቀጥተኛ መንገድ ነው» አላቸው፡፡ إِنَّ اللَّهَ رَبِّي وَرَبُّكُمْ فَاعْبُدُوهُ ۗ هَـٰذَا صِرَاطٌ مُّسْتَقِيمٌ
"የባሕርይ መገዛዛት"Ontological subordination" ማለት በባሕርይ የማይመሳሰሉ ሆነው ነገር ግን በባሕርይ አንዱ ከሌላው ስለሚበልጥ በመካከላቸው ገዥ እና ተገዥ አለ። ለምሳሌ፦ ሰው እና እንስሳ በምንነት የተለያዩ "ባሕርይ"Essence" ስላላቸው ሰው ገዥ እንስሳ ተገዥ ነው፦
መዝሙር 8፥6 ሁሉን ከእግሮቹ በታች አስገዛህለት። πάντα ὑπέταξας ὑποκάτω τῶν ποδῶν αὐτοῦ,
እዚህ አንቀጽ ላይ ለመገዛት የገባው ሥርወ ቃል "ሃይፖታሶ" ὑποτάσσω ሲሆን ገዥው ሰው ተገዥው በጎችን፣ ላሞችን፣ ሁሉ ደግሞም የምድረ በዳውን እንስሶች፣ የሰማይንም ወፎች፣ የባሕርን ዓሦች፣ በባሕር መንገድ የሚሄደውንም ሁሉ ነው፦
ዘፍጥረት 1፥28 የባሕርን ዓሦችና የሰማይን ወፎች በምድር ላይ የሚንቀሳቀሱትንም ሁሉ "ግዙአቸው"።
መዝሙር 8፥8 በጎችን፣ ላሞችን፣ ሁሉ ደግሞም የምድረ በዳውን እንስሶች፣ የሰማይንም ወፎች፣ የባሕርን ዓሦች፣ በባሕር መንገድ የሚሄደውንም ሁሉ።
እንስሳ ሰውን የሚገዛው የባሕርይ ቢሆንም የአክብሮት መገዛት እንጂ የአምልኮ መገዛት አይደለም። ነገር ግን ኢየሱስ ፍጡር ስለሆነ ለአምላክ የሚገዛበትን ለማሳየት የገባው ሥርወ ቃል "ሃይፖታሶ" ὑποτάσσω ነው፦
1ኛ ቆሮንቶስ 15፥28 ሁሉ ከተገዛለት በኋላ ግን "አምላክ" ሁሉ በሁሉ ይሆን ዘንድ በዚያን ጊዜ ልጁ ራሱ ደግሞ ሁሉን ላስገዛለት "ይገዛል"። ὅταν δὲ ὑποταγῇ αὐτῷ τὰ πάντα, τότε καὶ αὐτὸς ὁ Υἱὸς ὑποταγήσεται τῷ ὑποτάξαντι αὐτῷ τὰ πάντα, ἵνα ᾖ ὁ Θεὸς πάντα ἐν πᾶσιν.
"ሆ ቴዎስ" ማለት "አምላክ" ማለት ሲሆን ኢየሱስ ሁሉን ላስገዛለት አምላክ ይገዛል፥ ለአምክ የሚደረግ መገዛት የባሕርይ መገዛት ሲሆን የአምልኮ መገዛት ነው፦
ያዕቆብ 4፥7 እንግዲህ ለአምላክ "ተገዙ"! ዲያብሎስን ግን ተቃወሙ ከእናንተም ይሸሻል። ὑποτάγητε οὖν τῷ Θεῷ· ἀντίστητε δὲ τῷ διαβόλῳ, καὶ φεύξεται ἀφ’ ὑμῶν·
እዚህ አንቀጽ ላይ "ተገዙ" ለሚለው የገባው ቃል በተመሳሳይ "ሃይፖታሶ" ὑποτάσσω ነው፥ ስለዚህ ኢየሱስ በምንነት ሰው፣ የሰው ልጅ፣ ፍጡር በማንነቱ ነቢይ፣ መልእክተኛ እና መሢሕ ስለሆነ ለአምላኩ የሚገዛው መገዛት የአምልኮ መገዛት ነው። ኢየሱስ በምድራዊ ቆይታው አምላኩን ሲለምን፣ ሲጸልይ፣ ሲሰግድለት፣ ሲጦም እና ሲፈራው ከማየት ባሻገር አሁን ላይ ሰማይ የአምላኩ አገልጋይ ነው፦
ዕብራውያን 8፥2 እርሱ በመቅደስ "አገልጋይ" ነው። τῶν ἁγίων λειτουργὸς
እዚህ አንቀጽ ላይ "ሌይቶሬዎርጎስ" λειτουργός ሲሆን የግሥ መደቡ "ላትሬኦ" λατρεύω ነው፥ "ላትሬያ" λατρεία ማለት "አምልኮ" ማለት ሲሆን ኢየሱስ በሰማይ ባለው መቅደስ "አምላኪ"(አገልጋይ) ሰለሆነ ሰማይ ላይ "አምላካችን" እያለ የሚናገርለት አምላክ አለው፦
ራእይ 19፥5 ድምፅም እንዲህ ሲል ከዙፋኑ ወጣ፦ “ባሪያዎቹ ሁሉ እርሱንም የምትፈሩት ታናናሾችና ታላላቆች ሆይ! "አምላካችንን" አመስግኑ”። καὶ φωνὴ ἀπὸ τοῦ θρόνου ἐξῆλθεν λέγουσα Αἰνεῖτε τῷ Θεῷ ἡμῶν, πάντες οἱ δοῦλοι αὐτοῦ, οἱ φοβούμενοι αὐτόν, οἱ μικροὶ καὶ οἱ μεγάλοι.
"አምላካችን" የሚለው ቃል ይሰመርበት! ከዙፋኑ የወጣው "አምላካችን" የሚል ድምፅ በዙፋኑ መካከል ካለው ከኢየሱስ የወጣ ድምፅ ነው፥ "በዚያን ጊዜ" ማለት በሚመጣበት ጊዜ ለአምላኩ የአምላኮ መገዛት በግልጽ እና በይፋ ይገዛል። የእርሱ አስተምሮት «አሏህ ጌታዬ እና ጌታችሁ ነው፥ ስለዚህ አምልኩት! ይህ ቀጥተኛ መንገድ ነው» የሚል ነው፦
3፥51 «አሏህ ጌታዬ እና ጌታችሁ ነው፥ ስለዚህ አምልኩት! ይህ ቀጥተኛ መንገድ ነው» አላቸው፡፡ إِنَّ اللَّهَ رَبِّي وَرَبُّكُمْ فَاعْبُدُوهُ ۗ هَـٰذَا صِرَاطٌ مُّسْتَقِيمٌ
ክርስቲያኖች ሆይ! ኢየሱስ ያመለከውን አምላክ እንድታመልኩ ጥሪያችን ነው። አምላካችን አሏህ ሂዳያህ ይወፍቃችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይወፍቀን! አሚን።
✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://t.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም | 11 179 |
| 13 | "አባቴ ከሁሉ ይበልጣል" ሲል አብ ሁሉንም የሚበልጠው በባሕርይ ከሆነ ከኢየሱስም የሚበልጠው በባሕርይ ነው፥ "ከእኔ አብ ይበልጣል" ሲል በሰውነቱ ከሆነ አምላክ ሰውን የሚበልጠው በባሕርይ እንጂ በግብር አይደለም። "ክርስቶስ" ማለት "የተቀባ" ማለት ሲሆን የተቀባውን ሰው የቀባው አምላክ በባሕርይ ስለሚበልጠው "የክርስቶስም ራስ አምላክ ነው" ተብሏል።
በእርግጥ መሢሑ ለአሏህ ባሪያ ከመኾን ፈጽሞ አይጠየፍም፥ ቀራቢዎች የኾኑት መላእክትም አይጠየፉም፡፡ እርሱን ከመገዛት የሚጠየፍ እና የሚኮራም ሰው አሏህ ሁሉንም ወደ እርሱ በእርግጥ ይሰበስባቸዋል፦
፥172 መሢሑ ለአሏህ ባሪያ ከመኾን ፈጽሞ አይጠየፍም፥ ቀራቢዎች የኾኑት መላእክትም አይጠየፉም፡፡ እርሱን ከመገዛት የሚጠየፍ እና የሚኮራም ሰው አሏህ ሁሉንም ወደ እርሱ በእርግጥ ይሰበስባቸዋል፡፡ لَّن يَسْتَنكِفَ الْمَسِيحُ أَن يَكُونَ عَبْدًا لِّلَّهِ وَلَا الْمَلَائِكَةُ الْمُقَرَّبُونَ ۚ وَمَن يَسْتَنكِفْ عَنْ عِبَادَتِهِ وَيَسْتَكْبِرْ فَسَيَحْشُرُهُمْ إِلَيْهِ جَمِيعًا
ሳታመቻምቹ እና ሳታመናፍሱ አንዱን አምላክ አሏህን በብቸኝነት እንድታመልኩ ጥሪያችን ነው። አምላካችን አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይስጠን! አሚን።
✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://t.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም | 1 |
| 14 | የአምልኮ መገዛት
በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
3፥51 «አሏህ ጌታዬ እና ጌታችሁ ነው፥ ስለዚህ አምልኩት! ይህ ቀጥተኛ መንገድ ነው» አላቸው፡፡ إِنَّ اللَّهَ رَبِّي وَرَبُّكُمْ فَاعْبُدُوهُ ۗ هَـٰذَا صِرَاطٌ مُّسْتَقِيمٌ
"የባሕርይ መገዛዛት"Ontological subordination" ማለት በባሕርይ የማይመሳሰሉ ሆነው ነገር ግን በባሕርይ አንዱ ከሌላው ስለሚበልጥ በመካከላቸው ገዥ እና ተገዥ አለ። ለምሳሌ፦ ሰው እና እንስሳ በምንነት የተለያዩ "ባሕርይ"Essence" ስላላቸው ሰው ገዥ እንስሳ ተገዥ ነው፦
መዝሙር 8፥6 ሁሉን ከእግሮቹ በታች አስገዛህለት። πάντα ὑπέταξας ὑποκάτω τῶν ποδῶν αὐτοῦ,
እዚህ አንቀጽ ላይ ለመገዛት የገባው ሥርወ ቃል "ሃይፖታሶ" ὑποτάσσω ሲሆን ገዥው ሰው ተገዥው በጎችን፣ ላሞችን፣ ሁሉ ደግሞም የምድረ በዳውን እንስሶች፣ የሰማይንም ወፎች፣ የባሕርን ዓሦች፣ በባሕር መንገድ የሚሄደውንም ሁሉ ነው፦
ዘፍጥረት 1፥28 የባሕርን ዓሦችና የሰማይን ወፎች በምድር ላይ የሚንቀሳቀሱትንም ሁሉ "ግዙአቸው"።
መዝሙር 8፥8 በጎችን፣ ላሞችን፣ ሁሉ ደግሞም የምድረ በዳውን እንስሶች፣ የሰማይንም ወፎች፣ የባሕርን ዓሦች፣ በባሕር መንገድ የሚሄደውንም ሁሉ።
እንስሳ ሰውን የሚገዛው የባሕርይ ቢሆንም የአክብሮት መገዛት እንጂ የአምልኮ መገዛት አይደለም። ነገር ግን ኢየሱስ ፍጡር ስለሆነ ለአምላክ የሚገዛበትን ለማሳየት የገባው ሥርወ ቃል "ሃይፖታሶ" ὑποτάσσω ነው፦
1ኛ ቆሮንቶስ 15፥28 ሁሉ ከተገዛለት በኋላ ግን "አምላክ" ሁሉ በሁሉ ይሆን ዘንድ በዚያን ጊዜ ልጁ ራሱ ደግሞ ሁሉን ላስገዛለት "ይገዛል"። ὅταν δὲ ὑποταγῇ αὐτῷ τὰ πάντα, τότε καὶ αὐτὸς ὁ Υἱὸς ὑποταγήσεται τῷ ὑποτάξαντι αὐτῷ τὰ πάντα, ἵνα ᾖ ὁ Θεὸς πάντα ἐν πᾶσιν.
"ሆ ቴዎስ" ማለት "አምላክ" ማለት ሲሆን ኢየሱስ ሁሉን ላስገዛለት አምላክ ይገዛል፥ ለአምክ የሚደረግ መገዛት የባሕርይ መገዛት ሲሆን የአምልኮ መገዛት ነው፦
ያዕቆብ 4፥7 እንግዲህ ለአምላክ "ተገዙ"! ዲያብሎስን ግን ተቃወሙ ከእናንተም ይሸሻል። ὑποτάγητε οὖν τῷ Θεῷ· ἀντίστητε δὲ τῷ διαβόλῳ, καὶ φεύξεται ἀφ’ ὑμῶν·
እዚህ አንቀጽ ላይ "ተገዙ" ለሚለው የገባው ቃል በተመሳሳይ "ሃይፖታሶ" ὑποτάσσω ነው፥ ስለዚህ ኢየሱስ በምንነት ሰው፣ የሰው ልጅ፣ ፍጡር በማንነቱ ነቢይ፣ መልእክተኛ እና መሢሕ ስለሆነ ለአምላኩ የሚገዛው መገዛት የአምልኮ መገዛት ነው። ኢየሱስ በምድራዊ ቆይታው አምላኩን ሲለምን፣ ሲጸልይ፣ ሲሰግድለት፣ ሲጦም እና ሲፈራው ከማየት ባሻገር አሁን ላይ ሰማይ የአምላኩ አገልጋይ ነው፦
ዕብራውያን 8፥2 እርሱ በመቅደስ "አገልጋይ" ነው። τῶν ἁγίων λειτουργὸς
እዚህ አንቀጽ ላይ "ሌይቶሬዎርጎስ" λειτουργός ሲሆን የግሥ መደቡ "ላትሬኦ" λατρεύω ነው፥ "ላትሬያ" λατρεία ማለት "አምልኮ" ማለት ሲሆን ኢየሱስ በሰማይ ባለው መቅደስ "አምላኪ"(አገልጋይ) ሰለሆነ ሰማይ ላይ "አምላካችን" እያለ የሚናገርለት አምላክ አለው፦
ራእይ 19፥5 ድምፅም እንዲህ ሲል ከዙፋኑ ወጣ፦ “ባሪያዎቹ ሁሉ እርሱንም የምትፈሩት ታናናሾችና ታላላቆች ሆይ! "አምላካችንን" አመስግኑ”። καὶ φωνὴ ἀπὸ τοῦ θρόνου ἐξῆλθεν λέγουσα Αἰνεῖτε τῷ Θεῷ ἡμῶν, πάντες οἱ δοῦλοι αὐτοῦ, οἱ φοβούμενοι αὐτόν, οἱ μικροὶ καὶ οἱ μεγάλοι.
"አምላካችን" የሚለው ቃል ይሰመርበት! ከዙፋኑ የወጣው "አምላካችን" የሚል ድምፅ በዙፋኑ መካከል ካለው ከኢየሱስ የወጣ ድምፅ ነው፥ "በዚያን ጊዜ" ማለት በሚመጣበት ጊዜ ለአምላኩ የአምላኮ መገዛት በግልጽ እና በይፋ ይገዛል። የእርሱ አስተምሮት «አሏህ ጌታዬ እና ጌታችሁ ነው፥ ስለዚህ አምልኩት! ይህ ቀጥተኛ መንገድ ነው» የሚል ነው፦
3፥51 «አሏህ ጌታዬ እና ጌታችሁ ነው፥ ስለዚህ አምልኩት! ይህ ቀጥተኛ መንገድ ነው» አላቸው፡፡ إِنَّ اللَّهَ رَبِّي وَرَبُّكُمْ فَاعْبُدُوهُ ۗ هَـٰذَا صِرَاطٌ مُّسْتَقِيمٌ
ክርስቲያኖች ሆይ! ኢየሱስ ያመለከውን አምላክ እንድታመልኩ ጥሪያችን ነው። አምላካችን አሏህ ሂዳያህ ይወፍቃችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይወፍቀን! አሚን።
✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://t.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም
አንዱን አምላክነቱ ለሰዎች የባሕርይ ሲሆን ኢየሱስ እራሱን ከሰዎች ጋር አካቶ "አምላካችን" ማለቱ በራሱ ኢየሱስ ለአንዱ አምላክ የሚገዛው የባሕርይ መገዛዛት ነው፦
ኢሳይያስ 61፥2 የተወደደችውን የያህዌን ዓመት "አምላካችን" የሚበቀልበትን ቀን እናገር ዘንድ እና የሚያለቅሱትን ሁሉ አጽናና ዘንድ ልኮኛል። לִקְרֹ֤א שְׁנַת־רָצֹון֙ לַֽיהוָ֔ה וְיֹ֥ום נָקָ֖ם לֵאלֹהֵ֑ינוּ לְנַחֵ֖ם כָּל־אֲבֵלִֽים׃
ራእይ 19፥5 ድምፅም እንዲህ ሲል ከዙፋኑ ወጣ፦ “ባሪያዎቹ ሁሉ እርሱንም የምትፈሩት ታናናሾችና ታላላቆች ሆይ! "አምላካችንን" አመስግኑ”። καὶ φωνὴ ἀπὸ τοῦ θρόνου ἐξῆλθεν λέγουσα Αἰνεῖτε τῷ Θεῷ ἡμῶν, πάντες οἱ δοῦλοι αὐτοῦ, οἱ φοβούμενοι αὐτόν, οἱ μικροὶ καὶ οἱ μεγάλοι.
"አምላካችን" የሚለው ቃል ይሰመርበት! ከዙፋኑ የወጣው "አምላካችን" የሚል ድምፅ በዙፋኑ መካከል ካለው ከኢየሱስ የወጣ ድምፅ ነው። የሥነ መለኮት ምሁር እና ተንታኝ ዮሐንስ ጊል "አምላካችን" የሚለው ኢየሱስ ስለመሆኑ ባብራሩበት የትርጓሜ መጽሐፍ እንዲህ ብለዋል፦
ራእይ 7፥17 "በዙፋኑ መካከል ያለው" በጉ እረኛቸው ይሆናልና። ὅτι τὸ Ἀρνίον τὸ ἀνὰ μέσον τοῦ θρόνου ποιμανεῖ αὐτούς
"ድምፅም እንዲህ ሲል ከዙፋኑ ወጣ" የሚለው በዙፋኑ ላይ ከተቀመጠው ከእግዚአብሔር አብ አይደለም፥ "አምላካችንን አመስግኑ" የሚለው ሐረግ በትክክለኛነት እና በአግባብነት በአብ ሊነገር አይችልም። ይልቁንም መካከለኛ ሆኖ ስለ አብ ለሕዝቡ፦ "አምላኬ እና አምላካችሁ፥ እና አባቴ እና አባታችሁ" ያለው በዙፋኑ መካከል ካለው በግ ከክርስቶስ ነው። Gill's Exposition of the Whole Bible Commentary, Revelation 19:5
ኢየሱስ ወደ አንዱ አምላክ ከሰገደ፣ ከጦመ፣ ከጸለየ እንዲሁ እርሱ ከፈራው እና ካመለከው ለአንድ አምላክ የሚገዛው መገዛት የባሕርይ መገዛዛት ነው። አንዱ አምላክ ከሁሉ ይበልጣል፥ "ሁሉ" በሚል ቃል ውስጥ ኢየሱስ ስለሚካተት ከእርሱ አብ በባሕርይ የሚበልጠው የበላይ ነው፦
ዮሐንስ 10፥29 የሰጠኝ አባቴ ከሁሉ ይበልጣል። ὁ Πατήρ μου ὃ δέδωκέν μοι πάντων μεῖζόν ἐστιν
ዮሐንስ 14፥28 "ከ"እኔ" አብ ይበልጣልና። ὁ Πατὴρ μείζων μού ἐστιν.
1ኛ ቆሮንቶስ 11፥3 የክርስቶስም ራስ አምላክ ነው። κεφαλὴ δὲ τοῦ Χριστοῦ ὁ Θεός. | 1 |
| 15 | በባይብል የገደለ ብቻ ሳይሆን አባቱን ወይም እናቱን የሚሰድብ ፈጽሞ ይገደላል፦
ዘሌዋውያን 27፥17 ሰውንም እስኪሞት ድረስ የሚመታ ፈጽሞ ይገደል።
ዘጸአት 21፥17 አባቱን ወይም እናቱን የሚሰድብ ፈጽሞ ይገደል።
ኢየሱስ ሲመጣ ደግሞ ሕጉ ጠብቆ እና አጥብቆ የሞት ፍርድ የሚገባው የገደለ ብቻ ሳይሆን በወንድሙ ላይ የሚቆጣ ሁሉ የሞት ፍርድ እንደሚገባው አበክሮ እና አዘክሮ ተናግሯል፦
ማቴዎስ 5፥21-22 ለቀደሙት፦ አትግደል እንደ ተባለ ሰምታችኋል፤ የገደለም ሁሉ ፍርድ ይገባዋል። እኔ ግን እላችኋለሁ፥ በወንድሙ ላይ የሚቆጣ ሁሉ ፍርድ ይገባዋል።
"የገደለም ሁሉ ፍርድ ይገባዋል" ማለት በዘሌዋውያን 27፥17 "ፈጽሞ ይገደል" የሚለው ከሆነ "በወንድሙ ላይ የሚቆጣ ሁሉ ፍርድ ይገባዋል" ማለት "ፈጽሞ ይገደላል" ማለት ነው። እንደውም ኢየሱስ እንቅጩን ፍርጥ አርጎ፦ "በሰይፍ የሚገድል ማንም ቢኖር ራሱ በሰይፍ እንዲገደል ይገባዋል" ብሏል፦
ራእይ 13፥10 "በሰይፍ የሚገድል ማንም ቢኖር ራሱ በሰይፍ እንዲገደል ይገባዋል"።
በተጨማሪ ሬካብ እና ወንድሙ በዓና ወደ ኢያቡስቴ ቤት ገብተው ኢያቡስቴን ገድለዉት እራሱን ቆረጡት፥ ዳዊትም ሬካብን እና ወንድሙ በዓናን አስገድሎ እጃቸውን እና እግራቸውን እንዲቆረጥ አድርጓል፦
2 ሳሙኤል 4፥7 ወደ ቤትም በገቡ ጊዜ እርሱ በእልፍኙ በምንጣፉ ላይ ተኝቶ ሳለ መቱት፥ ገደሉትም፤ ራሱንም ቈርጠው ወሰዱት።
ሳሙኤል 4፥12 ዳዊትም ጕልማሶቹን አዘዘ፥ ገደሉአቸውም፤ እጃቸውን እና እግራቸውን ቈርጠው በኬብሮን በውኃ መቆሚያ አጠገብ አንጠለጠሉአቸው።
ኢዮአብ እና ሠራዊቱ በአሞን ከከተማ ይኖሩ የነበሩትን የአሞን ልጆች አውጥተው በመጋዝ ተረተሩአቸው፤ በመጥረቢያም ቈራረጡአቸው። ዳዊትም በአሞን ልጆች ከተሞች ሁሉ እንዲሁ አደረገ፦
1ኛ ዜና መዋዕል 20፥3 በውስጥዋም የነበሩትን ሕዝብ አውጥተው በመጋዝ ተረተሩአቸው፤ በመጥረቢያም ቈራረጡአቸው። ዳዊትም በአሞን ልጆች ከተሞች ሁሉ እንዲሁ አደረገ። ዳዊትም ሕዝቡም ሁሉ ወደ ኢየሩሳሌም ተመለሱ። καὶ τὸν λαὸν τὸν ἐν αὐτῇ ἐξήγαγε καὶ διέπρισε πρίοσι καὶ ἐν σκεπάρνοις σιδηροῖς καὶ ἐν διασχίζουσι· καὶ οὕτως ἐποίησε Δαυὶδ τοῖς πᾶσιν υἱοῖς ᾿Αμμών. καὶ ἀνέστρεψε Δαυὶδ καὶ πᾶς ὁ λαὸς αὐτοῦ εἰς ῾Ιερουσαλήμ.
"ዳዊትም በአሞን ልጆች ከተሞች ሁሉ እንዲሁ አደረገ" በማለት ዳዊት ልክ እንደ ኢዮአብ የአሞን ልጆችን በመጋዝ ተረተሩአቸው፤ በመጥረቢያም ቈራረጡአቸው፥ ግሪክ ሰፕቱአጀንት በዚህ ልክ ያስቀመጡት ሲሆን የ 2 ሺህ የኦርቶዶክስ ባይብል እና King James Version በዚህ አግባብ ተርጉመውታል፦
1 Chronicles 20፥3 KJV And he brought out the people that were in it, and cut them with saws, and with harrows of iron, and with axes. Even so dealt David with all the cities of the children of Ammon. And David and all the people returned to Jerusalem.
ነቢያችን"ﷺ" በቂሷስ ፍርድ እና ቅጣት ማድረጋቸው ነቢይ ላለመሆናቸው መስፈርት ከሆነ እንግዲያውስ በነካ አፋችሁን "ሙሴ፣ ኢየሱስ፣ ዳዊት የፈጣሪ ነቢይ አይደሉም" በሉና! ምን ይሻላችኃል ግን? ባይብል ሲጠቀስ እንቡር እና ፒርር እንዲሁ ቡፍ እና ኩፍ ከምትሉ ቁርኣንን እና ሐዲስን ለማሳጣት፣ ለማጭሸማቀቅ እና ለማሳቀቅ ፊጥ እና ቁጢጥ የምትሉትን ተዉ! አምላካችን አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይስጠን! አሚን።
✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://t.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም | 11 168 |
| 16 | የነቢያችን"ﷺ" ቅጣት
በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
42፥40 የመጥፎም ነገረ ዋጋ ብጤዋ መጥፎ ናት፡፡ وَجَزَاءُ سَيِّئَةٍ سَيِّئَةٌ مِّثْلُهَا
"ቂሷስ" قِصَاص የሚለው ቃል "ቋሶ" قَاصَّ ማለትም "አመሳሰለ" ከሚል ሥርወ ቃል የመጣ ሲሆን "ማመሳሰል" ማለት ነው፦
2፥179 ባለ አእምሮዎች ሆይ! ለእናንተም በማመሳሰል ሕግ ውስጥ ሕይወት አለላችሁ፡፡ ትጠነቀቁ ዘንድ ገዳይን መግደል ተደነገገላችሁ፡፡ وَلَكُمْ فِي الْقِصَاصِ حَيَاةٌ يَا أُولِي الْأَلْبَابِ لَعَلَّكُمْ تَتَّقُونَ
እዚህ አንቀጽ ላይ "ማመሳሰል" ለሚለው ቃል የገባው "ቂሷስ" قِصَاص መሆኑ ልብ አድርግ! ሰው ጤናማ ሕይወት ይኖር ዘንድ አምላካችን አሏህ ቂሷስን ደንግጓል፥ በቂሷስ ነፍስ ያጠፋ ነፍሱ ይጠፋል፣ ዓይን ያጠፋ ዓይኑ ይጠፋል፣ አፍንጫም ያጠፋ አፍንጫው ይጠፋል፣ ጆሮም ያጠፋ ጆሮው ይጠፋል፣ ጥርስ የሰበረ ጥርሱ ይሰበራል። እነዚህ ቁስሎችን በቂሷስ ይፈታሉ፦
5፥45 በእነርሱም ላይ በውስጧ፦ «ነፍስ በነፍስ ዓይንም በዓይን አፍንጫም በአፍንጫ ጆሮም በጆሮ ጥርስም በጥርስ ይያዛል፥ ቁስሎችንም "ማመሳሰል" አለባቸው» ማለትን ጻፍን፡፡ وَكَتَبْنَا عَلَيْهِمْ فِيهَا أَنَّ النَّفْسَ بِالنَّفْسِ وَالْعَيْنَ بِالْعَيْنِ وَالْأَنفَ بِالْأَنفِ وَالْأُذُنَ بِالْأُذُنِ وَالسِّنَّ بِالسِّنِّ وَالْجُرُوحَ قِصَاصٌ
አሁንም እዚህ አንቀጽ ላይ "ማመሳሰል" ለሚለው ቃል የገባው "ቂሷስ" قِصَاص መሆኑ አንባቢ ልብ ይለዋል። መጥፎ ለሠሩ ሠዎች መጥፎ ቅጣት መቅጣት ቂሷስ ነው፥ የአሏህ መጽሐፍ ጭብጡ ቂሷስ ነው፦
42፥40 የመጥፎም ነገረ ዋጋ ብጤዋ መጥፎ ናት፡፡ وَجَزَاءُ سَيِّئَةٍ سَيِّئَةٌ مِّثْلُهَا
ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 65, ሐዲስ 26
አነሥ እንደተረከው፦ “ነቢዩም"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ "የአሏህ መጽሐፍ ቂሷስ ነው"። أَنَّ أَنَسًا، حَدَّثَهُمْ عَنِ النَّبِيِّ صلى الله عليه وسلم قَالَ “ كِتَابُ اللَّهِ الْقِصَاصُ ”.
የመጥፎም ነገረ ዋጋ ብጤዋ መጥፎ ስለሆነ በአንድ ወቅት ነቢያችን"ﷺ" እረኛቸውን ለዑረይናህ ሰዎች እንዲንከባከባቸው ሰተዋቸው ሳሉ የዑረይናህ ሰዎች ግን በተቃራኒው የነቢያችንን"ﷺ" እረኛ እጅና እግር ቆርጠው እና ዓይን አጥፍተው በመግደላቸው ቂሷስ ተደርጎ እጃቸውንና እግራቸውንም እንዲቆረጥ እና ዓይኖቻቸውም እንዲጠፋ ተደርጓል፦
ሡነን ነሣኢይ መጽሐፍ 37, ሐዲስ 62
አነሥ እንደተረከው፦ "ሰዎች ከዑክል ወይም ከዑረይናህ ወደ ነቢዩ"ﷺ" መጡ፥ የመዲናህ አየር ንብረት ተጨናንቋል። ነቢዩም"ﷺ" ለእነርሱ፦ "ወደ ግመሎች ሂዱና ወተታቸውን ጠጡ እንዲሁ ሽንታቸውን ለመድኃኒት ተጠቀሙ" ብለው አዘዟቸው፥ እነርሱ ግን እረኛውን ገድለው ግመሎቹን ሰረቁ። ነቢዩም"ﷺ" ከኃላቸው ሰው ልከው እጃቸውን እና እግራቸውንም ቈረጡ፥ ዓይኖቻቸውም አጠፉ"። عَنْ أَنَسٍ، قَالَ أَتَى النَّبِيَّ صلى الله عليه وسلم نَفَرٌ مِنْ عُكْلٍ أَوْ عُرَيْنَةَ فَأَمَرَ لَهُمْ - وَاجْتَوَوُا الْمَدِينَةَ - بِذَوْدٍ أَوْ لِقَاحٍ يَشْرَبُونَ أَلْبَانَهَا وَأَبْوَالَهَا فَقَتَلُوا الرَّاعِيَ وَاسْتَاقُوا الإِبِلَ فَبَعَثَ فِي طَلَبِهِمْ فَقَطَّعَ أَيْدِيَهُمْ وَأَرْجُلَهُمْ وَسَمَلَ أَعْيُنَهُمْ .
"ሠመለ" سَمَلَ ማለት "አጠፋ" ማለት ነው። አምላካችን አሏህ፦ "ዓይንም በዓይን ይያዛል፥ ቁስሎችንም "ማመሳሰል" አለባቸው" ስላለ እነዚህ ሰዎች የእረኛውን ዓይን ስላጠፉ ዓይናቸው እንዲጠፋ ተደርጓል፦
ሡነን ነሣኢይ መጽሐፍ 37, ሐዲስ 78
አነሥ እንደተረከው፦ "ነቢዩ"ﷺ" የእረኛውን ዓይኖች በማጥፋታቸው ምክንያት የእነዚያን ሰዎች ዓይኖች ብቻ አጥፍተው ነበር"። عَنْ أَنَسٍ، قَالَ إِنَّمَا سَمَلَ النَّبِيُّ صلى الله عليه وسلم أَعْيُنَ أُولَئِكَ لأَنَّهُمْ سَمَلُوا أَعْيُنَ الرُّعَاةِ .
በኪታቡ አት-ተሕሪሙ አድ-ደም ዐውድ ውስጥ "እነዚያ" የተባሉት የዑረይናህ ሰዎች እንደሆኑ አንባቢ ልብ ይለዋል። በባይብልም ቢሆን ዓይን ያጠፋ ዓይኑ እንዲጠፋ ትእዛዝ አለ፦
ዘጸአት 21፥23-25 ጕዳት ግን ቢያገኛት ሕይወት በሕይወት፣ ዓይን በዓይን፣ ጥርስ በጥርስ፣ እጅ በእጅ፣ እግር በእግር፣ መቃጠል በመቃጠል፣ ቍስል በቍስል፣ ግርፋት በግርፋት ይከፈል። | 9 502 |
| 17 | "ዳዊትም በአሞን ልጆች ከተሞች ሁሉ እንዲሁ አደረገ" በማለት ዳዊት ልክ እንደ ኢዮአብ የአሞን ልጆችን በመጋዝ ተረተሩአቸው፤ በመጥረቢያም ቈራረጡአቸው፥ ግሪክ ሰፕቱአጀንት በዚህ ልክ ያስቀመጡት ሲሆን የ 2 ሺህ የኦርቶዶክስ ባይብል እና King James Version በዚህ አግባብ ተርጉመውታል፦
1 Chronicles 20፥3 KJV And he brought out the people that were in it, and cut them with saws, and with harrows of iron, and with axes. Even so dealt David with all the cities of the children of Ammon. And David and all the people returned to Jerusalem.
ነቢያችን"ﷺ" በቂሷስ ፍርድ እና ቅጣት ማድረጋቸው ነቢይ ላለመሆናቸው መስፈርት ከሆነ እንግዲያውስ በነካ አፋችሁን "ሙሴ፣ ኢየሱስ፣ ዳዊት የፈጣሪ ነቢይ አይደሉም" በሉና! ምን ይሻላችኃል ግን? ባይብል ሲጠቀስ እንቡር እና ፒርር እንዲሁ ቡፍ እና ኩፍ ከምትሉ ቁርኣንን እና ሐዲስን ለማሳጣት፣ ለማጭሸማቀቅ እና ለማሳቀቅ ፊጥ እና ቁጢጥ የምትሉትን ተዉ! አምላካችን አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይስጠን! አሚን።
✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://t.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም | 1 |
| 18 | የነቢያችን"ﷺ" ቅጣት
በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
42፥40 የመጥፎም ነገረ ዋጋ ብጤዋ መጥፎ ናት፡፡ وَجَزَاءُ سَيِّئَةٍ سَيِّئَةٌ مِّثْلُهَا
"ቂሷስ" قِصَاص የሚለው ቃል "ቋሶ" قَاصَّ ማለትም "አመሳሰለ" ከሚል ሥርወ ቃል የመጣ ሲሆን "ማመሳሰል" ማለት ነው፦
2፥179 ባለ አእምሮዎች ሆይ! ለእናንተም በማመሳሰል ሕግ ውስጥ ሕይወት አለላችሁ፡፡ ትጠነቀቁ ዘንድ ገዳይን መግደል ተደነገገላችሁ፡፡ وَلَكُمْ فِي الْقِصَاصِ حَيَاةٌ يَا أُولِي الْأَلْبَابِ لَعَلَّكُمْ تَتَّقُونَ
እዚህ አንቀጽ ላይ "ማመሳሰል" ለሚለው ቃል የገባው "ቂሷስ" قِصَاص መሆኑ ልብ አድርግ! ሰው ጤናማ ሕይወት ይኖር ዘንድ አምላካችን አሏህ ቂሷስን ደንግጓል፥ በቂሷስ ነፍስ ያጠፋ ነፍሱ ይጠፋል፣ ዓይን ያጠፋ ዓይኑ ይጠፋል፣ አፍንጫም ያጠፋ አፍንጫው ይጠፋል፣ ጆሮም ያጠፋ ጆሮው ይጠፋል፣ ጥርስ የሰበረ ጥርሱ ይሰበራል። እነዚህ ቁስሎችን በቂሷስ ይፈታሉ፦
5፥45 በእነርሱም ላይ በውስጧ፦ «ነፍስ በነፍስ ዓይንም በዓይን አፍንጫም በአፍንጫ ጆሮም በጆሮ ጥርስም በጥርስ ይያዛል፥ ቁስሎችንም "ማመሳሰል" አለባቸው» ማለትን ጻፍን፡፡ وَكَتَبْنَا عَلَيْهِمْ فِيهَا أَنَّ النَّفْسَ بِالنَّفْسِ وَالْعَيْنَ بِالْعَيْنِ وَالْأَنفَ بِالْأَنفِ وَالْأُذُنَ بِالْأُذُنِ وَالسِّنَّ بِالسِّنِّ وَالْجُرُوحَ قِصَاصٌ
አሁንም እዚህ አንቀጽ ላይ "ማመሳሰል" ለሚለው ቃል የገባው "ቂሷስ" قِصَاص መሆኑ አንባቢ ልብ ይለዋል። መጥፎ ለሠሩ ሠዎች መጥፎ ቅጣት መቅጣት ቂሷስ ነው፥ የአሏህ መጽሐፍ ጭብጡ ቂሷስ ነው፦
42፥40 የመጥፎም ነገረ ዋጋ ብጤዋ መጥፎ ናት፡፡ وَجَزَاءُ سَيِّئَةٍ سَيِّئَةٌ مِّثْلُهَا
ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 65, ሐዲስ 26
አነሥ እንደተረከው፦ “ነቢዩም"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ "የአሏህ መጽሐፍ ቂሷስ ነው"። أَنَّ أَنَسًا، حَدَّثَهُمْ عَنِ النَّبِيِّ صلى الله عليه وسلم قَالَ “ كِتَابُ اللَّهِ الْقِصَاصُ ”.
የመጥፎም ነገረ ዋጋ ብጤዋ መጥፎ ስለሆነ በአንድ ወቅት ነቢያችን"ﷺ" እረኛቸውን ለዑረይናህ ሰዎች እንዲንከባከባቸው ሰተዋቸው ሳሉ የዑረይናህ ሰዎች ግን በተቃራኒው የነቢያችንን"ﷺ" እረኛ እጅና እግር ቆርጠው እና ዓይን አጥፍተው በመግደላቸው ቂሷስ ተደርጎ እጃቸውንና እግራቸውንም እንዲቆረጥ እና ዓይኖቻቸውም እንዲጠፋ ተደርጓል፦
ሡነን ነሣኢይ መጽሐፍ 37, ሐዲስ 62
አነሥ እንደተረከው፦ "ሰዎች ከዑክል ወይም ከዑረይናህ ወደ ነቢዩ"ﷺ" መጡ፥ የመዲናህ አየር ንብረት ተጨናንቋል። ነቢዩም"ﷺ" ለእነርሱ፦ "ወደ ግመሎች ሂዱና ወተታቸውን ጠጡ እንዲሁ ሽንታቸውን ለመድኃኒት ተጠቀሙ" ብለው አዘዟቸው፥ እነርሱ ግን እረኛውን ገድለው ግመሎቹን ሰረቁ። ነቢዩም"ﷺ" ከኃላቸው ሰው ልከው እጃቸውን እና እግራቸውንም ቈረጡ፥ ዓይኖቻቸውም አጠፉ"። عَنْ أَنَسٍ، قَالَ أَتَى النَّبِيَّ صلى الله عليه وسلم نَفَرٌ مِنْ عُكْلٍ أَوْ عُرَيْنَةَ فَأَمَرَ لَهُمْ - وَاجْتَوَوُا الْمَدِينَةَ - بِذَوْدٍ أَوْ لِقَاحٍ يَشْرَبُونَ أَلْبَانَهَا وَأَبْوَالَهَا فَقَتَلُوا الرَّاعِيَ وَاسْتَاقُوا الإِبِلَ فَبَعَثَ فِي طَلَبِهِمْ فَقَطَّعَ أَيْدِيَهُمْ وَأَرْجُلَهُمْ وَسَمَلَ أَعْيُنَهُمْ .
"ሠመለ" سَمَلَ ማለት "አጠፋ" ማለት ነው። አምላካችን አሏህ፦ "ዓይንም በዓይን ይያዛል፥ ቁስሎችንም "ማመሳሰል" አለባቸው" ስላለ እነዚህ ሰዎች የእረኛውን ዓይን ስላጠፉ ዓይናቸው እንዲጠፋ ተደርጓል፦
ሡነን ነሣኢይ መጽሐፍ 37, ሐዲስ 78
አነሥ እንደተረከው፦ "ነቢዩ"ﷺ" የእረኛውን ዓይኖች በማጥፋታቸው ምክንያት የእነዚያን ሰዎች ዓይኖች ብቻ አጥፍተው ነበር"። عَنْ أَنَسٍ، قَالَ إِنَّمَا سَمَلَ النَّبِيُّ صلى الله عليه وسلم أَعْيُنَ أُولَئِكَ لأَنَّهُمْ سَمَلُوا أَعْيُنَ الرُّعَاةِ .
በኪታቡ አት-ተሕሪሙ አድ-ደም ዐውድ ውስጥ "እነዚያ" የተባሉት የዑረይናህ ሰዎች እንደሆኑ አንባቢ ልብ ይለዋል። በባይብልም ቢሆን ዓይን ያጠፋ ዓይኑ እንዲጠፋ ትእዛዝ አለ፦
ዘጸአት 21፥23-25 ጕዳት ግን ቢያገኛት ሕይወት በሕይወት፣ ዓይን በዓይን፣ ጥርስ በጥርስ፣ እጅ በእጅ፣ እግር በእግር፣ መቃጠል በመቃጠል፣ ቍስል በቍስል፣ ግርፋት በግርፋት ይከፈል።
በባይብል የገደለ ብቻ ሳይሆን አባቱን ወይም እናቱን የሚሰድብ ፈጽሞ ይገደላል፦
ዘሌዋውያን 27፥17 ሰውንም እስኪሞት ድረስ የሚመታ ፈጽሞ ይገደል።
ዘጸአት 21፥17 አባቱን ወይም እናቱን የሚሰድብ ፈጽሞ ይገደል።
ኢየሱስ ሲመጣ ደግሞ ሕጉ ጠብቆ እና አጥብቆ የሞት ፍርድ የሚገባው የገደለ ብቻ ሳይሆን በወንድሙ ላይ የሚቆጣ ሁሉ የሞት ፍርድ እንደሚገባው አበክሮ እና አዘክሮ ተናግሯል፦
ማቴዎስ 5፥21-22 ለቀደሙት፦ አትግደል እንደ ተባለ ሰምታችኋል፤ የገደለም ሁሉ ፍርድ ይገባዋል። እኔ ግን እላችኋለሁ፥ በወንድሙ ላይ የሚቆጣ ሁሉ ፍርድ ይገባዋል።
"የገደለም ሁሉ ፍርድ ይገባዋል" ማለት በዘሌዋውያን 27፥17 "ፈጽሞ ይገደል" የሚለው ከሆነ "በወንድሙ ላይ የሚቆጣ ሁሉ ፍርድ ይገባዋል" ማለት "ፈጽሞ ይገደላል" ማለት ነው። እንደውም ኢየሱስ እንቅጩን ፍርጥ አርጎ፦ "በሰይፍ የሚገድል ማንም ቢኖር ራሱ በሰይፍ እንዲገደል ይገባዋል" ብሏል፦
ራእይ 13፥10 "በሰይፍ የሚገድል ማንም ቢኖር ራሱ በሰይፍ እንዲገደል ይገባዋል"።
በተጨማሪ ሬካብ እና ወንድሙ በዓና ወደ ኢያቡስቴ ቤት ገብተው ኢያቡስቴን ገድለዉት እራሱን ቆረጡት፥ ዳዊትም ሬካብን እና ወንድሙ በዓናን አስገድሎ እጃቸውን እና እግራቸውን እንዲቆረጥ አድርጓል፦
2 ሳሙኤል 4፥7 ወደ ቤትም በገቡ ጊዜ እርሱ በእልፍኙ በምንጣፉ ላይ ተኝቶ ሳለ መቱት፥ ገደሉትም፤ ራሱንም ቈርጠው ወሰዱት።
ሳሙኤል 4፥12 ዳዊትም ጕልማሶቹን አዘዘ፥ ገደሉአቸውም፤ እጃቸውን እና እግራቸውን ቈርጠው በኬብሮን በውኃ መቆሚያ አጠገብ አንጠለጠሉአቸው።
ኢዮአብ እና ሠራዊቱ በአሞን ከከተማ ይኖሩ የነበሩትን የአሞን ልጆች አውጥተው በመጋዝ ተረተሩአቸው፤ በመጥረቢያም ቈራረጡአቸው። ዳዊትም በአሞን ልጆች ከተሞች ሁሉ እንዲሁ አደረገ፦
1ኛ ዜና መዋዕል 20፥3 በውስጥዋም የነበሩትን ሕዝብ አውጥተው በመጋዝ ተረተሩአቸው፤ በመጥረቢያም ቈራረጡአቸው። ዳዊትም በአሞን ልጆች ከተሞች ሁሉ እንዲሁ አደረገ። ዳዊትም ሕዝቡም ሁሉ ወደ ኢየሩሳሌም ተመለሱ። καὶ τὸν λαὸν τὸν ἐν αὐτῇ ἐξήγαγε καὶ διέπρισε πρίοσι καὶ ἐν σκεπάρνοις σιδηροῖς καὶ ἐν διασχίζουσι· καὶ οὕτως ἐποίησε Δαυὶδ τοῖς πᾶσιν υἱοῖς ᾿Αμμών. καὶ ἀνέστρεψε Δαυὶδ καὶ πᾶς ὁ λαὸς αὐτοῦ εἰς ῾Ιερουσαλήμ. | 1 |
| 19 | ገድል
በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።
2፥193 ሁከት እስከማይገኝ እና ሃይማኖት ለአላህ ብቻ እስከሚኾን ድረስ "ተጋደሉዋቸው"። وَقَاتِلُوهُمْ حَتَّىٰ لَا تَكُونَ فِتْنَةٌ وَيَكُونَ الدِّينُ لِلَّهِ
"ገድል" የሚለው የግዕዝ ቃል "ተጋደለ" ከሚል ሥርወ ቃል የመጣ ሲሆን "ውጊያ" "ትግል" "ፍልሚያ" "መዋጋት" "መጋደል" ማለት ነው፦
1ኛ ጢሞቴዎስ 1፥18 በእርሱ መልካም "ጦርነት" ትዋጋ ዘንድ ይህችን ትእዛዝ አደራ እሰጥሃለሁ።
እዚህ አንቀጽ ላይ "ጦርነት"War" ለሚለው በግዕዙ የገባው ቃል "ገድል" ሲሆን የግዕዙ መጽሐፍ "በከመ ተነብዮ ዘላዕሌከ ከመ ትጽናዕ በኵሉ "ገድል" ሠናይ" ይለዋል። ለቅዱሳን ነቢያት እና ሐዋርያት ከጥንት ጀምሮ የተሰጠ ሃይማኖት አንድ ሃይማኖት ሲሆን ለቅዱሳን ነቢያት እና ሐዋርያት ስለ ተሰጠ ሃይማኖት መጋደል ይገባል፦
ይሁዳ 1፥3 ለቅዱሳን አንድ ጊዜ ፈጽሞ ስለ ተሰጠ ሃይማኖት "እንድትጋደሉ" እየመከርኋችሁ እጽፍላችሁ ዘንድ ግድ ሆነብኝ።
ከጥንት የነበሩት ነቢያት በጦርነት ኃይለኞች ሆኑ፥ የባዕድ ጭፍሮችን አባረሩ፦
ዕብራውያን 11፥34 በጦርነት ኃይለኞች ሆኑ፥ የባዕድ ጭፍሮችን አባረሩ።
"ኢትዮጽያዊ ቄርሎስ" በሚል ማዕረግ የሚጠራው የሥነ መለኮት ምሁር አቦ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ ሃይማኖትን በካዱት ሰዎች ላይ ያለው ብይን በብሉይ ኪዳን እና በአዲስ ኪዳን የሞት ፍርድ እንደሆነ ተናግሯል፦
መጽሐፈ ምሥጢር 2፥28 "እነሆ ሃይማኖትን በካዱት ላይ በብሉይ ኪዳን እና በአዲስ ኪዳን የሞት ትእዛዝ ወጣ"።
መጽሐፈ ምሥጢር 2፥29 "የሐዋርያት አለቃ ቅዱስ ጴጥሮስ ቀሌሜንጦስን፦ "ፍጽምት ስለምትሆን ሃይማኖት "ሰይፈህን መዘህ በኢየሱስ ክርስቶስ የማያምኑትን ከሀዲዎች እና ጨካኞች በብረት ሰይፍ ተዋጋ" አለው"።
መጽሐፈ ምሥጢር 2፥35 "በኢየሱስ ክርስቶስ ሃይማኖት ቤተ ክርስቲያንን እንድናነሳት እና እንድናጸናት ሥልጣንን አገኘን፥ ይህንንም የተላለፈ ሰይፍ ይለፍበት ብለው አሜን ወአሜን"።
ፍጽምት ስለምትሆን ሃይማኖት የብረት ሰይፍን መዞ መጋደል በብሉይ ኪዳን እና በአዲስ ኪዳን የታዘዘ መሆኑን አበክሮ ይገልጻል። ይህንን ከተረዳን ዘንዳ ዓለም እስኪሰማና እስኪስማማ ድረስ ጂሃድ በሐቅ እና በባጢል መካከል ያለ ትግል ነው፥ እስከ ፍርዱ ቀን ድረስ እውነት ለማንገሥ ሐሠትን ለማርከሥ መጋደል ግዴታ ነው፦
2፥193 ሁከት እስከማይገኝ እና ሃይማኖት ለአላህ ብቻ እስከሚኾን ድረስ "ተጋደሉዋቸው"። وَقَاتِلُوهُمْ حَتَّىٰ لَا تَكُونَ فِتْنَةٌ وَيَكُونَ الدِّينُ لِلَّهِ
አንቀጹን ልብ ብለነው ከሆነ "ተጋደሉ" እንጂ "ግደሉ" አይልም። ልዩነቱን እስቲ እንመልከት፦
2፥244 በአሏህ መንገድ "ተጋደሉ"፡፡ وَقَاتِلُوا فِي سَبِيلِ اللَّهِ
እነዚህ አንቀጽ ላይ ተጋደሉ" ለሚለው የገባው ቃል "ቃቲሉ" قَاتِلُوا ሲሆን "ግደሉ" ለማለት ቢፈልግ "ኡቅቱሉ" اقْتُلُوا ይሆን ነበር፦
2፥191 ባገኛችኋቸውም ስፍራ ሁሉ "ግደሉ"-ዋቸው፡፡ وَاقْتُلُوهُمْ حَيْثُ ثَقِفْتُمُوهُمْ
እነዚህ አንቀጽ ላይ ግደሉ" ለሚለው "ኡቅቱሉ" اقْتُلُوا ሲሆን መከላከል"Defensive" ሳይሆን "ማጥቃት"Offensive" ነው። ተጨማሪ አንድ አንቀጽ እንመልከት፦
9፥111 በአሏህ መንገድ ላይ ይጋደላሉ፣ ይገድላሉ፣ ይገደላሉ"፡፡ يُقَاتِلُونَ فِي سَبِيلِ اللَّهِ فَيَقْتُلُونَ وَيُقْتَلُونَ
አያችሁ? "ይጋደላሉ" ለሚለው የገባው ቃል "ዩቃቲሉነ" يُقَاتِلُونَ ሲሆን፣ "ይገድላሉ" ለሚለው ግን "የቅቱሉነ" يَقْتُلُونَ ነው። "ቀትል" قَتْل ማለት እና "ቂታል" قِتَال ማለት ሁለት ለየቅል ቃላት እና ትርጉም አላቸው፥ "ቂታል" قِتَال ማለት በግዕዝ "ገድል" ማለት ነው። "ተጋደሉ" የግሥ መደብ ሲሆን "ገድል" የስመ መደብ ነው፥ ስለዚህ "ገድል" ማለት ጂሃዱል ቀልቢያህ፣ ጂሃዱል ቀውሊያህ እና ጂሃዱል ዐመሊያህ ተጠቅሞ የአሏህን ንግግር የበላይ ማድረግ ነው። ሁከት እስከማይገኝ እና ሃይማኖት ለአሏህ ብቻ እስከሚኾን ድረስ ከኩፋሮች ጋር እንጋደላለን፥ ዓለም በአሏህ ሸሪዓህ እስክትደዳደር ድረስ መጋደሉ ይቀጥላል። ተወዳጁ ነቢያች"ﷺ" የታዘዙበት መርሕ ይህ ነው፦
ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 3 ሐዲስ 18
ኢብኑ ዑመር እንደተረከው፦ የአሏህ መልእክተኛም”ﷺ” እንዲህ አሉ፦ “ሰዎችን "ከአሏህ በቀር በእውነት የሚመለክ አምላክ አለመኖሩን እና ሙሐመድም የአሏህ መልእክተኛ ነው" ብለው እስኪመሰክሩ፣ ሶላትን እስኪቆሙ እና ዘካህን እስኪያወጡ ድረስ "እንድጋደላቸው" ታዝዣለሁ"። عَنِ ابْنِ عُمَرَ، أَنَّ رَسُولَ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم قَالَ " أُمِرْتُ أَنْ أُقَاتِلَ النَّاسَ حَتَّى يَشْهَدُوا أَنْ لاَ إِلَهَ إِلاَّ اللَّهُ وَأَنَّ مُحَمَّدًا رَسُولُ اللَّهِ، وَيُقِيمُوا الصَّلاَةَ، وَيُؤْتُوا الزَّكَاةَ
እዚህም ሐዲስ ላይ "አን ኡቃቲለ" أَنْ أُقَاتِلَ ማለት "እንድጋደል" ማለት ሲሆን "እንድገድል" ለማለት ቢሆን ኖሮ "አን አቅቱለ" أَنْ أَقْتُلَ ይሆን ነበር፥ "እንድገድል" ቢል ኖሮ "በሃይማኖት መስገደድ የለም" ከሚል መርሕ ጋር ይጋጭ ነበር። ገድል አጠቃላይ ሦስቱንም የጂሃድ ክፍል የሚይዝ ቃል ነው፦
ሪያዱ አስ-ሷሊሒን መጽሐፍ 1, ሐዲስ 184
አቢ ሠዒድ አል-ኹድሪይ”ረ.ዐ.” እንደተረከው፦ “የአሏህ መልእክተኛ”ﷺ” እንዲህ ሲሉ ሰምቻቸዋለሁ፦ “ከእናንተ ውስጥ እኩይ ነገር ያየ በእጁ ይቀይረው፣ ካልቻለ በምላሱ ያውግዝ፣ ይህንንም ካልቻለ በልቡ ይጥላው። በልብ መጥላት ደካማው ኢማን ነው”። عن أبي سعيد الخدري رضي الله عنه قال: سمعت رسول الله صلى الله عليه وسلم يقول: “من رأى الخد منكرًا فليغيره بيده ، فإن لم يستطع فبلسانه، فإن لم يستطع فبقلبه وذلك أضعف الإيمان
በእጅ፣ በምላስ እና በልቡ ያልታገለ የጎመንዘር ያህል ኢማን የለውም። ምእምናን ማለት በገንዘቦቻቸው እና በነፍሶቻቸውም በአሏህ መንገድ የታገሉት ብቻ ናቸው፥ እነዚያ እነርሱ እውነተኞቹ ናቸው፦
49፥15 ምእምናን እነዚያ በአሏህ እና በመልእከተኛው ያመኑት ከዚያም ያልተጠራጠሩት “በገንዘቦቻቸው እና በነፍሶቻቸውም በአሏህ መንገድ የታገሉት ብቻ ናቸው”፡፡ እነዚያ እነርሱ እውነተኞቹ ናቸው፡፡ إِنَّمَا الْمُؤْمِنُونَ الَّذِينَ آمَنُوا بِاللَّهِ وَرَسُولِهِ ثُمَّ لَمْ يَرْتَابُوا وَجَاهَدُوا بِأَمْوَالِهِمْ وَأَنفُسِهِمْ فِي سَبِيلِ اللَّهِ ۚ أُولَـٰئِكَ هُمُ الصَّادِقُونَ
አምላካችን አሏህ በእርሱ መንገድ ከሚጋደሉ ባሮቹ ያርገን! ለነፍሲያ ተብሎ ከሚደረግ የዘር፣ የብሔር፣ የዘውግ ገድል ይጠብቀን! አሚን።
✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://t.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም | 13 382 |
| 20 | ምሥጢረ ትዳር
ይህ ወንድ ልጅ አንድ ሚስት አለው፥ ያቺ ሚስቱ በአካል አራት ናቸው። አራቱ ሴቶች በአካል፣ በስም እና በግብር አራት ሲሆኑ በሚስትነት ግን አንድ ናቸው፥ አራቱም ሴቶች ሚስት የሚለውን ቃል ይጋራሉ።
ኸዲጃ ሚስት ናት፣
ዘይነብ ሚስት ናት፣
ሰሚራህ ሚስት ናት፣
አሚራህ ሚስት ናት።
ነገር ግን አራቱ አካላት አንድን ሚስትነት ስለሚጋሩ ለወንድ አንድ ሚስት ናቸው።
ስለዚህ አንድ ወንድ አራት ሴቶች ሲያገባ ሚስቱ ግን አንዲት ናት።
ይህ "ምሥጢረ ትዳር" ካልተገለጸልህ አይገባህም። | 14 604 |
