ru
Feedback
Ethio - ዜና 🇪🇹

Ethio - ዜና 🇪🇹

Открыть в Telegram

የመረጃዎች ቁንጮ የሆነውን Ethio ዜና ለሚወዱት ጓደኞችዎ እና ቤተሰብዎ ያካፍሉ። አንድ ላይ፣ ዘምነን እንቆይ! ምርት እና አገልግሎታችሁን ገጻችን ላይ ለማስተዋወቅ ከፈለጉ ያናግሩን @Ethiozenaa_bot

Больше

📈 Аналитический обзор Telegram-канала Ethio - ዜና 🇪🇹

Канал Ethio - ዜና 🇪🇹 (@ethio_zena23) языкового сегмента Амхарский является активным участником. Сейчас сообщество объединяет 100 584 подписчиков, занимая 77 место в категории Картинки и 319 место в регионе Эфиопия.

📊 Показатели аудитории и динамика

С момента создания невідомо проект демонстрирует стремительный рост, собрав аудиторию из 100 584 подписчиков.

Согласно последним данным от 15 сентября, 2026, канал показывает стабильную активность. За последние 30 дней изменение числа участников составило -2 698, а за последние 24 часа — -110, при этом общий охват остаётся высоким.

  • Статус верификации: Не верифицирован
  • Уровень вовлечённости (ER): Средний показатель вовлечённости аудитории составляет 3.50%. В первые 24 часа после публикации контент обычно набирает 2.67% реакций от общего числа подписчиков.
  • Охват публикаций: В среднем каждый пост получает 3 522 просмотров. В течение первых суток публикация набирает 2 689 просмотров.
  • Реакции и взаимодействия: Аудитория активно поддерживает контент: среднее количество реакций на один пост — 27.

📝 Описание и контентная политика

Автор описывает ресурс как площадку для выражения субъективного мнения:
የመረጃዎች ቁንጮ የሆነውን Ethio ዜና ለሚወዱት ጓደኞችዎ እና ቤተሰብዎ ያካፍሉ። አንድ ላይ፣ ዘምነን እንቆይ! ምርት እና አገልግሎታችሁን ገጻችን ላይ ለማስተዋወቅ ከፈለጉ ያናግሩን @Ethiozenaa_bot

Благодаря высокой частоте обновлений (последние данные получены 16 сентября, 2026) канал поддерживает актуальность и высокий уровень охвата публикаций. Аналитика показывает, что аудитория активно взаимодействует с контентом, что делает его важной точкой влияния в категории Картинки.

100 584
Подписчики
-11024 часа
-6637 дней
-2 69830 дней
Архив постов
የትምህርት ሚኒስቴር የ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎችን የዩኒቨርሲቲ ምደባ ማጠናቀቁን አስታወቀ‼️ ምደባው የተማሪዎችን ውጤትና ምርጫ፣ የዩኒቨርሲቲዎችን የቅበላ አቅም፣ የክልል፣ የወረዳ፣ የዞን እና የትምህርት ቤት ስርጭት እንዲሁም የፆታ ሚዛን ታሳቢ በማድረግ መከናወኑን ሚኒስቴሩ ገልጿል። በተጨማሪም ከ600 ነጥብ 500 እና ከዚያ በላይ ያስመዘገቡ ተማሪዎች በመጀመሪያ ምርጫቸው መመደባቸውን አስታውቋል። ተማሪዎች የምደባ ውጤታቸውን በተዘጋጀው የኦንላይን ሥርዓት https://student.ethernet.edu.et/view-placement ማየት ይችላሉ ብሏል። ቅሬታ ያላቸው ምደባው ይፋ ከሆነበት ቀን ጀምሮ በ5 ቀናት ውስጥ በኦንላይን  ፦ https://student.ethernet.edu.et/complaints ብቻ ቅሬታ ማቅረብ እንደሚችሉ ተገልጿል።

ለክቡራን የባንካችን ደንበኞች፡ የባንክ ሂሳብን ከፋይዳ መታወቂያ ጋር ማስተሳሰርን በተመለከተ *** የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ባስተላለፈው መመሪያ መሠረት ከሐረሪ ክልል እና ከታች ከተዘረዘሩት ከተሞች
ለክቡራን የባንካችን ደንበኞች፡ የባንክ ሂሳብን ከፋይዳ መታወቂያ ጋር ማስተሳሰርን በተመለከተ *** የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ባስተላለፈው መመሪያ መሠረት ከሐረሪ ክልል እና ከታች ከተዘረዘሩት ከተሞች ውጪ በሚገኙ ቅርንጫፎች ሂሳብ የከፈታችሁ ደንበኞች እስከ ጥቅምት 30 ቀን 2019 ዓ.ም ሂሳባችሁን ከፋይዳ መታወቂያችሁ ጋር ማስተሳሰር እና ማጠናቀቅ ይኖርባችኋል። 👉 በአዲስ አበባ፣ ድሬዳዋ አስተዳደር፣ ባህር ዳር፣ ጎንደር፣ ደሴ፣ ደብረብርሃን፣ ኮምቦልቻ፣ ሀዋሳ፣ አርባ ምንጭ፣ ወላይታ ሶዶ፣ ሆሳዕና፣ ወራቤ፣ ቡታጂራ፣ ወልቂጤ፣ ሸገር፣ ጅማ፣ አዳማ፣ ሻሸመኔ፣ ቢሾፍቱ፣ ባቱ፣ አምቦ፣ መቐለ፣ አክሱም፣ ዓዲግራት፣ ጋምቤላ፣  አሶሳ እና በሐረሪ ክልል የምትገኙ እና እስካሁን ሂሳባችሁን ከፋይዳ መታወቂያ ጋር ያላስተሳሰራችሁ ደንበኞች ሂሳባችሁን ከፋይዳ መታወቂያችሁ ጋር በማስተሳሰር በሂሳባችሁ ላይ ወጪ ከማድረግ የተጣለውን እግድ ማስነሳት ትችላላችሁ፤ 👉 ደንበኞች የፋይዳ መታወቂያ ቁጥራቸውን (FAN) ይዘው በባንካችን ቅርንጫፎች በመገኘት ወይም ባሉበት ሆነው በበይነ መረብ ማስተሳሰሪያ አማራጭ (https://cbefayda.cbe.com.et) ሂሳባቸውን ከፋይዳ መታወቂያቸው ጋር ማስተሳሰር ይችላሉ፤ 👉 የፋይዳ መታወቂያ ያላወጣችሁ ደንበኞች ወደሚቀርባችሁ የባንካችን ቅርንጫፍ ማንነታችሁን የሚያረጋግጥ ማስረጃ ይዛችሁ በመቅረብ መመዝገብ እና የፋይዳ ቁጥራችሁን ማግኘት ትችላላችሁ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ለአዲሱ የ2019 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የመልካም ምኞት መልዕክት አስተላለፉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለአዲሱ የ2019 ዓ.ም የትምህርት ዘመን መበሰር
+1
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ለአዲሱ የ2019 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የመልካም ምኞት መልዕክት አስተላለፉ   ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለአዲሱ የ2019 ዓ.ም የትምህርት ዘመን መበሰርን ተከትሎ ለመላው የሀገሪቱ ተማሪዎች፣ መምህራን እና የትምህርት ባለድርሻ አካላት የመልካም ምኞት መልዕክት አስተላፈዋል።   ጠቅላይ ሚኒስትሩ በመልዕክታቸው እንደገለጹት፤ ወጣቱ ትውልድ የኢትዮጵያ ትልቁ ሀብት በመሆኑ እያንዳንዱ ተማሪ አዲሱን የትምህርት ዘመን በትጋትና በጽናት በመከታተል የሀገሪቱን የወደፊት ዕድል መቅረጽ በሚያስችሉ ክህሎቶች ሊገነባ እንደሚገባ አሳስበዋል።    በአሁኑ ወቅት እየተከናወኑ ያሉ የልማት ሥራዎች የነገውን ትውልድ ታሳቢ ያደረጉ በመሆናቸው፣ የታላቋን ኢትዮጵያ የስልጣኔ ታሪክ ወደፊት ለማስቀጠል የተማሪዎች ቁርጠኝነት ወሳኝ መሆኑንም አብራርተዋል።   በተጨማሪም ብቁ እና በራሱ የሚተማመን ትውልድ የመገንባት ጥረት ዋና ምሰሶ መምህራን መሆናቸውን በመጠቆም፤ ተማሪዎችን በማነቃቃትና የነገ ተፎካካሪ የሚያደርጋቸውን ዕውቀትና እሴት የማስታጠቅ አደራቸውን እንዲቀጥሉበት ጥሪ አቅርበዋል።  

የጣሊያን ባንኮች የኮይሻ ግድብን ለማጠናቀቅ የሚያስችል 400 ሚሊዮን ዩሮ #ለኢትዮጵያ ሊያበድሩ ነው አዲስ አበባ፣ መስከረም 5 ቀን 2019 ዓ.ም. ፦ #ኢትዮጵያ 1 ሺህ 800 ሜጋ ዋት ያመነጫል ተ
የጣሊያን ባንኮች የኮይሻ ግድብን ለማጠናቀቅ የሚያስችል 400 ሚሊዮን ዩሮ #ለኢትዮጵያ ሊያበድሩ ነው አዲስ አበባ፣ መስከረም 5 ቀን 2019 ዓ.ም. ፦ #ኢትዮጵያ 1 ሺህ 800 ሜጋ ዋት ያመነጫል ተብሎ የሚገመተውን የኮይሻ ግድብን ለማጠናቀቅ የሚያስችል የ400 ሚሊዮን ዩሮ ብድር ለማግኘት ከሦስት የጣሊያን ባንኮች ጋር ድርድር ላይ መሆኗን ብሉምበርግ ዘግቧል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ አሸብር ባልቻ እንደገለጹት፣ ተቋማቸው 3 ቢልዮን ዩሮ የሚያወጣውን ፕሮጀክት ለማጠናቀቅ ተጨማሪ 100 ሚልዮን ዩሮ የሚያክል ገንዘብ ከአገር ውስጥ ምንጮች ማሰባሰብ ይችላል" ያሉ ሲሆን "የብድር ስምምነቱ በቀጣይ ጥቅምት ወር ይፈረማል ብለን እንጠብቃለን" ሲሉ ተናግረዋል። በጊቤ ወንዝ ላይ እየተገነባ ያለው የዚህ ፕሮጀክት ማጠናቀቂያ በኢትዮጵያ የእዳ ሽግሽግ ምክንያት ከተያዘለት ጊዜ በሦስት ዓመታት ወደ ኋላ የቀረ ሲሆን አገሪቱ እ.ኤ.አ. በ2023 የዩሮቦንድ የዋጋ ወለድ ክፍያ መፈጸም ባለመቻሏ የ4.5 ቢልዮን ዶላር ብድር እንደገና የማደራጀት ሂደት ላይ ትገኛለች። ከአንድ ዓመት በፊት ኢትዮጵያ በገዛ ሀብቷ የገነባችውን 4.8 ቢልዮን ዶላር ወጪ የተደረገበትን ግድብ እንዳስመረቀች የሚታወስ ነው።  5 ሺህ 150 ሜጋ ዋት የሚያመነጨው ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የአገሪቱን የኃይል ማመንጨት አቅም በእጥፍ በማሳደግ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የመጀመሪያውን ዓመታዊ ትርፍ እንዲያስመዘግብ ረድቶታል።

አንድ ኪሎ ግራም ቡና በ2,376 ዶላር ተሸጠ! የቴስቲ ትሬዲንግ ባለቤት አቶ ፈይሰል አብዶሽ ያቀረቡት የጉጂ ስፔሻሊቲ ቡና በአንድ ኪሎ ግራም 2,376.50 ዶላር (ከ380 ሺህ ብር በላይ) በመሸጥ
አንድ ኪሎ ግራም ቡና በ2,376 ዶላር ተሸጠ! የቴስቲ ትሬዲንግ ባለቤት አቶ ፈይሰል አብዶሽ ያቀረቡት የጉጂ ስፔሻሊቲ ቡና በአንድ ኪሎ ግራም 2,376.50 ዶላር (ከ380 ሺህ ብር በላይ) በመሸጥ አዲስ ታሪካዊ ሪከርድ አስመዝገቧል።  ከዚህ ሽያጭ የሚገኘው ገቢም በጉጂ ዞን ለሚገነባው የጤና ጣቢያ ማጠናቀቂያ ይውላል። እንግሊዝና አሜሪካ በሚገኙት የM-Cultivo የኦንላይን ጨረታ መድረክ ላይ የተካሄደው ይህ ሽያጭ፣ የኢትዮጵያ ቡና ጥራትና ተሰሚነት በዓለም ገበያ ላይ እያደገ መምጣቱን የሚያሳይ ነው።  ከዚህ ግዙፍ ሽያጭ የሚገኘው ገቢም በጉጂ ዞን ሻኪሶ ወረዳ ለሚገነባው የጤና ጣቢያ ማጠናቀቂያ እንደሚውል ተገልጿል። ቴስቲ ኮፊ ከዚህ ቀደምም በይርጋ ጨፌ፣ ሲዳማ እና ሻኪሶ 5 ትምህርት ቤቶችን በመገንባት ከፍተኛ ማህበራዊ ኃላፊነት የተወጣ ኩባንያ ሲሆን፣ በ2017 በጀት ዓመት ብቻ 67 ሚሊዮን ዶላር የውጭ ምንዛሪ ለሀገር ውስጥ አስገኝቷል።

በትምህርት ቤቶች ዙሪያ ተሽከርካሪን ደርቦ ማቆም 1 ሺህ ብር ያስቀጣል‼️ በአዲስ አበባ ከተማ የትምህርት ቤቶች መከፈትን ተከትሎ የሚፈጠረውን የትራፊክ መጨናነቅ ለመቀነስ፤ በመዲናዋ በሚገኙ ትምህርት
በትምህርት ቤቶች ዙሪያ ተሽከርካሪን ደርቦ ማቆም 1 ሺህ ብር ያስቀጣል‼️ በአዲስ አበባ ከተማ የትምህርት ቤቶች መከፈትን ተከትሎ የሚፈጠረውን የትራፊክ መጨናነቅ ለመቀነስ፤ በመዲናዋ በሚገኙ ትምህርት ቤቶች ዙሪያ ማንኛውንም ተሽከርካሪ ደርቦ ማቆም በጥብቅ እንደሚከለከልና እንደሚያስቀጣ የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ባለሥልጣን አስታወቀ። በትምህርት ቤቶች መግቢያና መውጫ ሰዓት በዋና መንገዶች ላይ ተሽከርካሪን ደርቦ ማቆም 1 ሺህ ብር እንደሚያስቀጣ የባለሥልጣኑ የሕዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር ወ/ሮ ገነት ዲባባ አስታውቀዋል።   ወላጆች ተሽከርካሪን መንገድ ላይ ለጥቂት ሰከንዶች ብቻ አቁመው ተማሪዎችን ማውረድ የሚችሉ ሲሆን፤ ነገር ግን ተሽከርካሪን ለደቂቃዎች በአካባቢው ማቆምም ሆነ አቁሞ መውረድ ፍጹም የተከለከለ መሆኑ ተገልጿል።    የትራፊክ መጨናነቅን ለማስቀረት ሲባል፤ በግል ተሽከርካሪ ወደ ትምህርት ቤት ይጓጓዙ የነበሩ ተማሪዎች በትምህርት ቤቶቻቸው የሰርቪስ ተሽከርካሪዎች እንዲጓዙ ከትምህርት ቤቶች ጋር ስምምነት ላይ ተደርሷል።   የትራፊክ ፍሰቱን በማሳለጥ ማኅበረሰቡን ለማስተናገድ ከ 500 እስከ 1,000 የሚደርሱ በጎ ፈቃደኛ ተማሪዎች ስምሪት የተሰጣቸው ሲሆን፤ ከትምህርት ቤት አመራሮች እና ከወላጅ ኮሚቴዎች ጋር በመቀናጀት አጥፊዎች ላይ ጥብቅ እርምጃ ይወሰዳል ተብሏል።

አቶ ኢሳያስ ጅራ የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት ሆነው ዳግም ተመረጡ ​ የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን (EFF) ባካሄደው ጠቅላላ ጉባኤ አቶ ኢሳያስ ጅራን ለቀጣይ አራት ዓመታት በፕሬዝዳንት
አቶ ኢሳያስ ጅራ የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት ሆነው ዳግም ተመረጡ ​ የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን (EFF) ባካሄደው ጠቅላላ ጉባኤ አቶ ኢሳያስ ጅራን ለቀጣይ አራት ዓመታት በፕሬዝዳንትነት ዳግም መርጧል። ለቦታው ብቸኛ እጩ የነበሩት አቶ ኢሳያስ ከተሰጡት 88 ድምፆች መካከል 81ድምፅ በማግኘት ማሸነፋቸውን ፌዴሬየፌዴሬሽኑሽኑ አስታውቋል። ​በአህጉራዊው የእግርኳስ ኮንፌዴሬሽን (CAF) የሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ እና በFIFA ውስጥ ተሳትፎ ያላቸውን አቶ ኢሳያስን በመወከል፣ የፊፋ ፕሬዝዳንት ጂያኒ ኢንፋንቲኖ በስልክ የእንኳን ደስ አለዎት መልዕክት አስተላልፈዋል። ​በተመሳሳይ ምርጫ የድሬዳዋ እግርኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት እና የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር አለሙ መግራ መስቀሌ የፌዴሬሽኑ ምክትል ፕሬዝዳንት ሆነው ተመርጠዋል።

አስተማማኝ መረጃ በማጣት እና በተዛቡ ዜናዎች ተስፋ ቆርጠዋል‼️ እውነትን መሰረት ያደረጉ ተጨባጭ መረጃዎችን፣ ወቅታዊ ሀገር አቀፍና ዓለም አቀፍ ዜናዎችን እዚህ ያገኛሉ! 👇👇 https://t.me/seledadotio https://t.me/seledadotio

ማስጠንቀቂያ የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ለኢ-ፓስፖርት ማመልከት የሚፈልጉ ዜጎች ከሐሰተኛ ድረ-ገጾች እንዲጠነቀቁ አሳስቧል። አገልግሎቱ እንዳስታወቀው አንዳንድ አጭበርባሪዎች የኤምባሲዎችን ገጽ
ማስጠንቀቂያ የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ለኢ-ፓስፖርት ማመልከት የሚፈልጉ ዜጎች ከሐሰተኛ ድረ-ገጾች እንዲጠነቀቁ አሳስቧል። አገልግሎቱ እንዳስታወቀው አንዳንድ አጭበርባሪዎች የኤምባሲዎችን ገጽ በመምሰል ሐሰተኛ የኢ-ፓስፖርት ማመልከቻ ፖርታሎችን እያሰራጩ ነው። ይህም አመልካቾችን ለተጨማሪ ወጪና እንግልት ሊዳርግ እንደሚችል አገልግሎቱ ገልጿል። በመሆኑም ለኢ-ፓስፖርት ማመልከት የሚፈልጉ ዜጎች https://immigration.gov.et/?fbclid የሚለውን ይፋዊ ድረ-ገጽ ብቻ እንዲጠቀሙ አሳስቧል።

#MoE በትግራይ ክልል በሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች ሲማሩ የነበሩ ተማሪዎች፤ ከዚህ በፊት ሲማሩበት የነበረውን፦ - ዩኒቨርሲቲ፣ - የትምህርት ዘመን፣ - የትምህርት ፕሮግራም እና ሌሎችንም አስፈላጊ መረጃዎ
#MoE በትግራይ ክልል በሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች ሲማሩ የነበሩ ተማሪዎች፤ ከዚህ በፊት ሲማሩበት የነበረውን፦ - ዩኒቨርሲቲ፣ - የትምህርት ዘመን፣ - የትምህርት ፕሮግራም እና ሌሎችንም አስፈላጊ መረጃዎች በመሙላት በሌሎች የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች በጊዜያዊነት ለመመደብ በ https://student.ethernet.edu.et/university-transfer/ ድረ-ገጽ በመግባት የራሳቸውን ፋይዳ (የመለያ ቁጥር) በመጠቀም ከዛሬ ጀምሮ  እስከ መስከረም 8/2019 ዓ.ም ድረስ ማመልከት እንደሚችሉ ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል። ቀደም ሲል በወረቀት ማመልከቻ ያስገቡ ተማሪዎች በዚሁ ድህረ ገጽ አማካኝነት በድጋሚ ማመልከት እንደሚጠበቅባቸው ተገልጿል።

የሳዑዲ ዓረቢያ ድንበር ጠባቂዎች ባንድ ሳምንት ውስጥ ብቻ ከ600 በላይ ኢትዮጵያዊያን በቁጥጥር ሥር አዋሉ። ኢትዮጵያዊያኑ ከነሃሴ 28 እስከ ጳጉሜ 4 በነበሩት ቀናት ውስጥ በቁጥጥር ሥር የዋሉት፣ ያለ ሕጋዊ ሠነድ የአገሪቱን ድንበር አቋርጠው ሊገቡ ሞክረዋል ተብለው መሆኑን የአገሪቱ ጋዜጦች ዘግበዋል። በተጠቀሰው የሳዑዲ ድንበር ጠባቂዎች በቁጥጥር ሥር ካዋሏቸው 1 ሺሕ 273 የውጭ ዜጎች መካከል፣ 55 በመቶዎቹ ኢትዮጵያዊያን መኾናቸውን ዘገባው ጠቅሷል። ኢትዮጵያዊያን ሳዑዲ ድንበር ላይ የሚያዙት፣ ባብዛኛው ከየመን ተነስተው ሊገቡ ሲሞክሩ እንደሆነ መረጃዎች ያመለክታሉ።

በትግራይ በሚገኙ ዩኒቨርስቲዎች ይማሩ የነበሩ ተማሪዎች በሌሎች ዩኒቨርስቲዎች በጊዚያዊነት እንዲመደቡ ተወሰነ። ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እንደገለጹት፣ በትግራይ ክልል በሚገኙ ዩኒቨርስቲዎች ይማሩ የነበሩ ተማሪዎች ደህንነታቸው ወደሚጠበቅባቸው ሌሎች የመንግሥት ዩኒቨርስቲዎች በጊዚያዊነት ተመድበው ትምህርታቸውን እንዲቀጥሉ ትምህርት ሚኒስቴር መወሰኑን ገልጸዋል። በዚህም ተማሪዎች ለምዝገባ በአካል ወደ ትምህርት ሚኒስቴር መምጣት ሳይጠበቅባቸው ከዛሬ ማታ ጀምሮ ይፋ በሚደረገው የበየነ መረብ (Online) መተግበሪያ በመጠቀም መመዝገብ እንደሚችሉ አስታውቀዋል። በምዝገባው ወቅትም ተማሪዎች ከዚህ በፊት ይማሩበት የነበረውን ዩኒቨርስቲ፣ የትምህርት ዘመናቸውን እና የሚማሩበትን የትምህርት መርሐ ግብር (field of study) በመግለጽ ባሉበት ቦታ ሆነው የዝውውር ፎርሙን በአጭር ግዜ እንዲሞሉ አሳስበዋል። ዛሬ በአካል በትምህርት ሚኒስቴር ግቢ የተገኙት በርካታ ተማሪዎች የተለያዩ ጥያቄዎች ያቀረቡ ሲሆን ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋና ሚኒስትር ዴኤታ ፕሮፌሰር ክንደያ ገብረህይወትን ጨምሮ ሌሎች የትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራሮች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል።

ውሃ ውሃ ለሕይወት አስፈላጊ ነው። በርካታ ዓለም አቀፍ መመሪያዎች አንድ ሴት በቀን ሁለት ሊትር፣ ወንድ ደግሞ 2.5 ሊትር ውሃ ቢጠጣ ለጤና መልካም መሆኑን ይመክራሉ። ብዙዎቻችን ፕሮቲን፣ ቫይታሚን፣
ውሃ ውሃ ለሕይወት አስፈላጊ ነው። በርካታ ዓለም አቀፍ መመሪያዎች አንድ ሴት በቀን ሁለት ሊትር፣ ወንድ ደግሞ 2.5 ሊትር ውሃ ቢጠጣ ለጤና መልካም መሆኑን ይመክራሉ። ብዙዎቻችን ፕሮቲን፣ ቫይታሚን፣ ካርቦሃይድሬት እና ፋይበር ላይ እናተኩራለን። ውሃን በሕይወታችን ውስጥ እንደ ጠቃሚ ንጥረ ነገር አድርገን አናስብም። ውሃ በሁሉም የሰውነታችን ተግባራት ውስጥ ወሳኝ ሚና ይጫወታል። የሃርቫርድ የሕክምና ትምህርት ቤት የውሃን አንዳንድ ቁልፍ ሚናዎች እንደሚከተለው ዘርዝሯል። በሰውነታችን ውስጥ የውሃ ወሳኝ ሚና፤ • ንጥረ-ነገሮችን እና ኦክስጂንን ወደ ሴሎች ማጓጓዝ • ከሽንት ከረጢት ውስጥ ባክቴሪያዎችን ማስወገድ • የምግብ መፈጨትን መርዳት • የሆድ ድርቀትን መከላከል • የደም ግፊትን መደበኛ ማድረግ • መገጣጠሚያዎችን ማለስለስ • የአካል ብልቶችን እና ጡንቻዎችን መከላከል • የሰውነት ሙቀትን መቆጣጠር • የኤሌክትሮላይት (ሶዲየም) ሚዛንን መጠበቅ

የሪሚዲያል መርሃ ግብር የዩኒቨርሲቲ ቅበላ መቁረጫ ነጥብ ይፋ ሆነ። ለ2019 ዓ/ም የሪሚዲያል መርሃ ግብር ተማሪዎች ወደ ዩኒቨርሲቲ ለመግባት የሚያስችላቸው የመቁረጫ ነጥብ በተማሪዎች ውጤት፣ በዩኒቨ
የሪሚዲያል መርሃ ግብር የዩኒቨርሲቲ ቅበላ መቁረጫ ነጥብ ይፋ ሆነ። ለ2019 ዓ/ም የሪሚዲያል መርሃ ግብር ተማሪዎች ወደ ዩኒቨርሲቲ ለመግባት የሚያስችላቸው የመቁረጫ ነጥብ በተማሪዎች ውጤት፣ በዩኒቨርሲቲዎች የቅበላ አቅም፣ እና በሀገራዊ የትምህርት ፍትሃዊነት መርህ ላይ ተመስርቶ መወሰኑን ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል። በዚህም መሰረት ከታችን የተገለጸውን ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎች ለሪሚዲያል መርሃ ግብር የዩኒቨርሲቲ ቅበላ ብቁ መሆናቸውን ሚኒስቴሩ አሳውቋል። 1. የተፈጥሮ እና የማህበራዊ ሳይንስ ወንድ ተማሪዎች 👉 ከ600 ውስጥ 240 እና ከዚያ በላይ (40%) 2. የተፈጥሮ እና የማህበራዊ ሳይንስ ሴት ተማሪዎች 👉 ከ600 ውስጥ 228 እና ከዚያ በላይ (38%) በልዩ ድጋፍ የሚታይ የተማሪ ምድብ 1. ከአፋር፣ ሶማሌ፣ ቤንሻንጉል ጉሙዝ እና ጋምቤላ ክልሎች የተፈጥሮ ወይም ማህበራዊ ሳይንስ ለተፈተኑ ወንድና ሴት ተማሪዎች 👉 ከ600 ውስጥ 222 እና ከዚያ በላይ (37%) 2. ከአርብቶ አደርና ከፊል አርብቶ አደር አካባቢዎች የተፈጥሮ ወይም ማህበራዊ ሳይንስ ለተፈተኑ ተማሪዎች 👉 ከ600 ውስጥ 222 እና ከዚያ በላይ (37%) 3. በማህበራዊ ሳይንስ የተፈተኑ ዓይነ ስውር ወንድና ሴት ተማሪዎች 👉 ከ500 ውስጥ 185 እና ከዚያ በላይ (37%) 4. በተፈጥሮ ወይም በማህበራዊ ሳይንስ የተፈተኑ መስማት የተሳናቸው ወንድና ሴት ተማሪዎች 👉 ከ600 ውስጥ 222 እና ከዚያ በላይ (37%)

ቶጎ አፍሪካ የኢትዮጵያን የቀን መቆጠሪያ መጠቀም እንዳለባት አሳስባለች። ቶጎ የአፍሪካ ሀገራት የአውሮፓውያንን የቀኝ ግዛት ዘመን የቀን መቆጠሪያ በማስወገድ የራሳቸውን አህጉራዊ ማንነት የሚያንፀባርቁ
ቶጎ አፍሪካ የኢትዮጵያን የቀን መቆጠሪያ መጠቀም እንዳለባት አሳስባለች። ቶጎ የአፍሪካ ሀገራት የአውሮፓውያንን የቀኝ ግዛት ዘመን የቀን መቆጠሪያ በማስወገድ የራሳቸውን አህጉራዊ ማንነት የሚያንፀባርቁበት አዲስ ዓመት እና በዓላት ሊኖሯቸው እንደሚገባ ጥሪ አቀረበች። የምዕራባውያንን የቀኝ ግዛት ዘመን የቀን መቆጠሪያዎችን በማስወገድ አፍሪካውያን የራሳቸውን አህጉራዊ ማንነትና ታሪክ የሚያንፀባርቅ የጊዜ አቆጣጠር ሊኖራቸው እንደሚገባ ቶጎ ጥሪ አቅርባለች። ቶጎ ከአፍሪካ ህብረት ጋር በመተባበር አህጉራዊ አንድነትን የሚያጎለብት አዲስ ዓመት እንዲታወጅ የጠየቀች ሲሆን፣ ለዚህም መፍትሔው መላው አፍሪካውያን የራሳቸውን ማንነት ለመመለስ የኢትዮጵያን የቀን መቆጠሪያ (ካላንደር) መጠቀም እንደሆነ አሳስባለች። በዓለም አቀፍ ደረጃ የኢትዮጵያ ካላንደር የነፃነት፣ የራሷን የቻለች ሀገር እና የጥንታዊ ሥልጣኔ ምልክት ተደርጎ ትልቅ አድናቆትና ክብር እየተቸረው ይገኛል። ሆኖም ግን ይህ የአፍሪካ ሀገራት የኢትዮጵያን የጊዜ አቆጣጠር እንደ አህጉራዊ ኩራትና መፍትሔ አድርገው በሚመለከቱበት በአሁኑ ወቅት፣ በሀገር ውስጥ የካላንደር ለውጥ እንዲደረግ የሚደረጉ እንቅስቃሴዎችና ፍላጎቶች በብዙዎች ዘንድ አላስፈላጊና የሀገርን ታሪካዊ ቅርስ የሚሸረሽር ተደርጎ በመወሰዱ ከፍተኛ ቅሬታን ፈጥሯል። https://t.me/Ethio_Zena23 https://t.me/Ethio_Zena23

ተደጋጋሚ የድሮን ጥቃት‼️ በራያ ኮረም ትናንት መስከረም 2/2019 ዓ.ም ከተፈፀመው የድሮን ጥቃት በተጨማሪ ዛሬም ሁለት ጊዜ ተፈፅሟል። ጥቃቱ ዛሬ ረፋድ ላይ በራያ ኮረም በበሬ ገበያ አከባቢ #መስ
+1
ተደጋጋሚ የድሮን ጥቃት‼️ በራያ ኮረም ትናንት መስከረም 2/2019 ዓ.ም ከተፈፀመው የድሮን ጥቃት በተጨማሪ ዛሬም ሁለት ጊዜ ተፈፅሟል። ጥቃቱ ዛሬ ረፋድ ላይ በራያ ኮረም በበሬ ገበያ አከባቢ #መስኮተ_ብርሀን ትምህርት ቤት ላይ የተፈፀመ ሲሆን የህወሓት አንድ ዙ-23 የጫነች #ፓትሮል እና የተለያዩ ተተኳሽ የጫነች አንድ FSR መኪና በጥቃቱ ጉዳት ደርሶባቸዋል።

ነፃ ኢንተርኔት ይፈልጋሉ👇🏃

Repost from N/a
❗️❗️❗️❗️❗️❗️❗️❗️ እንዴዴዴዴዴዴዴ ኧረ ፍጠኑ ጥያቄና መልስ ጀምረናል🔥🔥 ✔️ ቀድሞ ለመለሱ 5 ሰዎች የካርድ ሽልማት አለ Request to Join ያድርጉ   🟣 የአለማችን ብዙ ህዝብ ያላት ሀገር ማን ነች ❓

የፍቅረኛችሁን   ሰው   ስም   የመጀመርያ ፊደል   በመጫን  ስለ ፍቅረኛዎ ይወቁ ❣︎❣ 😍😍😍 ዳይ ለሁላችሁም ነው እንዳያመልጥዎ!!

ተማሪ ነህ ?