ዳጉ-ጆርናል/Dagu-Journal
The best fiction is far more true than any journalism 📢 ተዓማኒ የመረጃ ምንጭ ፤ ለሙያው ስነምግባር ተገዢ በሆኑ ጋዜጠኞች ብቻ 👉 በፌስቡክ ገፆቻችን https://www.facebook.com/simon.dereje.56 👉 https://www.facebook.com/mik0Man
Больше📈 Аналитический обзор Telegram-канала ዳጉ-ጆርናል/Dagu-Journal
Канал ዳጉ-ጆርናል/Dagu-Journal (@zena24now) языкового сегмента Амхарский является активным участником. Сейчас сообщество объединяет 41 456 подписчиков, занимая 6 218 место в категории Новости и СМИ и 829 место в регионе Эфиопия.
📊 Показатели аудитории и динамика
С момента создания невідомо проект демонстрирует стремительный рост, собрав аудиторию из 41 456 подписчиков.
Согласно последним данным от 06 сентября, 2026, канал показывает стабильную активность. За последние 30 дней изменение числа участников составило -320, а за последние 24 часа — -35, при этом общий охват остаётся высоким.
- Статус верификации: Не верифицирован
- Уровень вовлечённости (ER): Средний показатель вовлечённости аудитории составляет 15.66%. В первые 24 часа после публикации контент обычно набирает 12.54% реакций от общего числа подписчиков.
- Охват публикаций: В среднем каждый пост получает 6 494 просмотров. В течение первых суток публикация набирает 5 200 просмотров.
- Реакции и взаимодействия: Аудитория активно поддерживает контент: среднее количество реакций на один пост — 31.
📝 Описание и контентная политика
Автор описывает ресурс как площадку для выражения субъективного мнения:
“The best fiction is far more true than any journalism
📢 ተዓማኒ የመረጃ ምንጭ ፤ ለሙያው ስነምግባር ተገዢ በሆኑ ጋዜጠኞች ብቻ
👉 በፌስቡክ ገፆቻችን https://www.facebook.com/simon.dereje.56
👉 https://www.facebook.com/mik0Man”
Благодаря высокой частоте обновлений (последние данные получены 07 сентября, 2026) канал поддерживает актуальность и высокий уровень охвата публикаций. Аналитика показывает, что аудитория активно взаимодействует с контентом, что делает его важной точкой влияния в категории Новости и СМИ.
Загрузка данных...
| Дата | Привлечение подписчиков | Упоминания | Каналы | |
| 07 сентября | 0 | |||
| 06 сентября | 0 | |||
| 05 сентября | +1 | |||
| 04 сентября | +1 | |||
| 03 сентября | +9 | |||
| 02 сентября | +2 | |||
| 01 сентября | +2 |
| 2 | በሸኖ ከተማ አቅራቢያ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የ6 ሰዎች ሕይወት ሲያልፍ 18 ሰዎች ቆሰለዋል።
በሸኖ ከተማ አስተዳደር ኦንቱ ቀበሌ፣ አዳ ሀሮ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በደረሰ ከባድ የትራፊክ አደጋ የስድስት ሰዎች ሕይወት ሲያልፍ፣ በ18 ሰዎች ላይ ደግሞ የአካል ጉዳት መድረሱን የአካባቢው የትራፊክ ደህንነት አስታውቋል።
የሸኖ ከተማ አስተዳደር የትራፊክ ደህንነት ማረጋገጫ ክፍል ኃላፊ ረዳት ኢንስፔክተር አዲሱ መርጋ እንደገለጹት አደጋው የደረሰው የሰሌዳ ቁጥሩ 3-A04933 አ.አ የሆነ ኤፍኤም የህዝብ ማጓጓዣ ተሽከርካሪ ባስ ከአዲስ አበባ ወደ ደሴ ሲጓዝ ከሚፈቀደው የፍጥነት ወሰን በላይ በማሽከርከሩ ምክንያት የተፈጠረ አደጋ ነው ብለዋል።
በአደጋው ሕይወታቸው ካለፉት 6 ሰዎች መካከል 2 ወንዶች እና 4 ሴቶች እንደሚገኙበት ታውቋል። በተጨማሪም ጉዳት ከደረሰባቸው 18 ተጓዦች 12 ወንዶች እና 6 ሴቶች ውስጥ 13ቱ ከባድ እና መካከለኛ አደጋ የገጠማቸው ሲሆን፣ አምስቱ ደግሞ ቀላል ጉዳት አጋጥሟቸዋል።
የሟቾች አስከሬን በህብረተሰቡና በትራፊክ ፖሊስ አባላት ትብብር ወደ ሸኖ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የተወሰደ ሲሆን፣ ተጎጂዎችም በዚሁ ሆስፒታል የህክምና እርዳታ እየተደረገላቸው ይገኛል።
ከባድ ጉዳት የደረሰባቸው ተሳፋሪዎች ለተሻለ ህክምና ወደ ሌሎች ከፍተኛ ሆስፒታሎች የተላኩ ሲሆን፣ አነስተኛ ጉዳት የደረሰባቸው ደግሞ ጉዟቸውን ወደ ደብረ ብርሃን እና አዲስ አበባ መቀጠላቸውን ተገልፅዋል።
በአብዛኛ አገር አቅዋራጭ ከፍተኛ አውቶብሶች የሰውን ሕይወት ጭነው በግዴለሽነት የሚያደርሱት አደጋ በመበራከቱ አሽከርካሪዎች ከፍተኛ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ ረዳት ኢንስፔክተር አዲሱ መርጋ ጨምረው ገልፀዋል።
#ዳጉ_ጆርናል | 4 726 |
| 3 | የ 3ተኛ ሳምንት የ እንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ተጠባቂ ጨዋታ:
⏰ ተጠናቀቀ
አርሰናል 2-1 ቼልሲ
#ዳጉ_ጆርናል | 5 174 |
| 4 | Нет текста... | 5 194 |
| 5 | https://youtu.be/buvgGDIueJU?is=mLmHlieEpNhLY6f- | 5 756 |
| 6 | ካቮድ ኮመርሻል ለደንበኞቹ ዘመናዊ የኤሌክትሪክ መኪኖችንና የፈርኒቸር ምርቶችን የሽልማት ዕጣ አወጣ
ካቮድ ኮመርሻል ሪል እስቴት ባለፉት ዘጠኝ ወራት ሲተገብር የቆየውን የደንበኞች ማበረታቻ የሽልማት መርሃ ግብር የማጠቃለያ ዕጣ አወጣጥ ስነ-ስርዓት አከናውኗል።
በዚህ ወቅት የካቮድ ኮመርሻል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ የምወድህ ታደሰ እንደገለፁት ፣ የእጣ ማዉጣት መርሀ-ግብሩ ፍትሃዊ፣ ታማኝ እና ግልጽ በሆነ መልኩ ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ሎተሪ አስተዳደር ጋር በመተባበር ተከናውኗል።
በገዟቸው የሱቅ መለያ ኮድ (Shop Code) እና በሳይቱ ኮድ አማካኝነት ደንበኞች በዕጣው እንዲካተቱ ተደርጓል ያሉት ዋና ስራ አስፈፃሚው ካቮድ ኮሜርሻል የንግድ ቦታዎችን ከመገንባት ባለፈ በሀገር ኢኮኖሚ ላይ በጎ ተፅዕኖ የመፍጠር አላማ እንዳለው አመልክተዋል።
ካቮድ ኮመርሺያል የወደፊት የንግድ እይታውን የሚያንጸባርቅ “አራዳው ነጋዴ” የተሰኘ አዲስ የማርኬቲንግ እንቅስቃሴ ይፋ ያደረገ ሲሆን ይህም የዛሬን ውሳኔ ከነገው ስኬት ጋር በማገናዘብ ረጅም ርቀት ማየት የሚችል፣ የንግድ ቦታዎችን በጥበብ የሚመርጥ እና የወደፊት ተስፋውን የሚገነባ ብልህ ነጋዴን የሚወክል መሆኑ ተገልጿል።
በመርሃ ግብሩ ይፋ የተደረጉት የ1ኛ እና 2ኛ ዕጣ ሽልማቶች ዘመናዊ የኤሌክትሪክ መኪኖች ናቸው።
1ሚሊዮን ብር የሚያወጡ የኦቪድ ፈርኒቸር ምርቶች ደግሞ በሶስተኛ እጣ የተካተቱ የሽልማት አይነቶች መሆናቸው በመርሀግብሩ ላይ ተገልጿል።
ከ4ኛ እስከ 10ኛ ዕጣ ያሉ የሽልማት አይነቶች ደግሞ የተለያየ ዋጋ ያላቸው የፈርኒቸር ምርቶችን ያካትታሉ።
ቅድስት ደጀኔ
#ዳጉ_ጆርናል | 5 534 |
| 7 | ከወራት በፊት ህይወቱ ያለፈዉ ብሪታንያ ናይጄሪያዊ ኢጎ ቲኒ የሞቱ ምክኒያት ከብልት ማስተለቅ ሰርጀሪ በኋላ የገጠመዉ ተጓዳኝ የጤና ችግር ነዉ ተባለ
የድምጻዊ ዴቪዶ የቅርብ ጓደኛ ነበር የተባለዉና በናይጄሪያ ማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ እዉቅና ያለዉ ኢጎ ቲኒ በመጋቢት ወር ነበር በ 43 አመቱ ህይወቱ ማለፉ የተሰማዉ።
የጎልማሳዉ ታዋቂ ሰዉ ህልፈት እስካሁን ይፋ ሳይደረግ ቆይቶ የነበረ ቢሆንም ምክኒያቱ ከታወቀ በኋላ የአለም መገናኛ ብዙሃንን ትኩረት ስቧል።
ግለሰቡ ህይወቱ ከማለፉ በፊት በታይላንድ ባንክሆክ የብልቅ ማስተለቅ ቀዶ ህክምና አድርጎ ነበር ተብሏል።
ግለሰቡ ከህክምናዉ በኋላ የልብ ህመም አጋጥሞት ነበር ተብሏል። በተጨማሪም በህክምዉ ሀኪሞች የጠቅመዉት የነበረዉ 40 ሚሊ ሊትር ሀይሉሮኒክ የተሰኘ አሲድ በሳንባዉ ላይ ተገኝቷል መባሉ ተሰምቷል።
ግለሰቡ ህይወቱ ከማለፉ በፊት ማሳጅ በሚደረግበት ወቅት ሁለት ጊዜ ራሱን ስቶ ነበርም ተብሏል። ግለሰቡ ወዲያዉ ወደ ሆስፒታል ቢወሰድም ወደ ሳንባዉ የደም ዝዉዉር በመቋረጡ ህይወቱ አልፏል።
በበረከት ሞገስ
#ዳጉ_ጆርናል | 5 018 |
| 8 | አትሌት ገመቹ ጎዳና በ3ሺህ ሜትር መሰናክል የዳይመንድ ሊግ አጠቃላይ አሸናፊ ሆነ
የ2026 ዳይመንድ ሊግ የዙር ውድድር ሲጠናቀቅ ኢትዮጵያዊው አትሌት ገመቹ ጎዳና በወንዶች 3000 ሜትር መሰናክል አጠቃላይ አሸናፊ ሆኗል።
በመጀመሪያው ቀን የዙሪክ ዳይመንድ ሊግ የፍፃሜ ውድድር በ5ሺህ ሜትር አሸናፊ የነበረችውን ኢትዮጵያዊቷን አትሌት ፍሬወይኒ ኃይሉን ጨምሮ፣ አምስት አፍሪካውያን አትሌቶች አትሌቶች አጠቃላይ አሸናፊዎች ነበሩ።
በሁለተኛው ዕለት ደግሞ ገመቹ ጎዳና ከኢትዮጵያ ሁለተኛ ከአፍሪካ ስድስተኛው የዳይመንድ ሊጉ አሸናፊ ሆኗል።
ገመቹ ሞሮኳዊውን የዓለምና የኦሊምፒክ ሻምፒዮን ሱፊያን ኤል ባካሊ አስከትሎ ሲገባ ርቀቱን ለማጠናቀቅ 8:08.67 ወስዶበታል። ሱፊያን ኤል ባካሊ 2ኛ፣ ኬንያዊው ሲሞን ኮዌች ደግሞ 3ኛ ሆነዋል። ሳሙኤል ፍሬው ሰባተኛ ደረጃን በመያዝ ውድድሩን አጠናቅቋል።
በወንዶች 5ሺህ ሜትር ቢኒያም መሀሪ 4ኛ፣ በሴቶች 800 ሜትር ሳይዳ ፀሀዬ 3ኛ እንዲሁም በ1500 ሜትር ብርቄ ኃየሎም 9ኛ ደረጃን በመያዝ ያጠናቀቁበት የምሽቱ ዳይመንድ ሊግ ውድድር ተጠቃሽ ውጤቶች ናቸው።
#ዳጉ_ጆርናል | 5 158 |
| 9 | በአዲስ አበባየአከራይና ተከራይ ውል ምዝገባና እድሳት ጊዜ ተራዘመ
የአዲስ አበባ ቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ የአከራይና ተከራይ ውል ምዝገባና እድሳት የመጨረሻ ጊዜ እስከ ጳጉሜ 5 ቀን 2018 ዓ.ም. መራዘሙን አስታወቀ።
ቢሮው የጊዜ ገደቡን ለማራዘም የተገደደው በተለያዩ ምክንያቶች ውላቸውን ማደስ ያልቻሉ ወገኖች በመኖራቸው እና ከህብረተሰቡ በቀረቡ ተደጋጋሚ ጥያቄዎች ምክንያት እንደሆነ ገልጿል።
በመሆኑም እስከተጠቀሰው ጊዜ ድረስ ውላቸውን ያላደሱ አከራዮች እና ተከራዮች በየክፍለ ከተሞቻቸው፣ በመሶብ አንድ ማዕከላት እንዲሁም ለአገልግሎቱ በተዘጋጁ ቦታዎች በመቅረብ አስፈላጊውን እድሳት እንዲፈጽሙ ጥሪ አስተላልፏ።
#ዳጉ_ጆርናል | 5 994 |
| 10 | ተማሪዎችን ለሥራ ዓለም የሚያዘጋጀው "The Vocational Shift" መጽሐፍ ለንባብ በቃ
በኢትዮጵያ የትምህርት ሥርዓት ውስጥ የሚታየውን የንድፈ-ሐሳብ (Theory) እና የተግባር ትምህርት ክፍተት ለመድፈን ያለመ አዲስ መጽሐፍ በዛሬው ዕለት በደመቀ ሁኔታ ተመርቆ ለንባብ በቃ። መጽሐፉ ተማሪዎችን ለሥራ ዓለምና ለሥራ ፈጠራ ብቁ አድርጎ ለማዘጋጀት ትልቅ አስተዋፅኦ ይኖረዋል ተብሏል።
በዶ/ር ታደሰ መኮንን የተጻፈው "The Vocational Shift: A Practical Guide to Integrating TVET and CTE into General Education" የተሰኘው ይህ መጽሐፍ፣ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትን (TVET) እንዲሁም የሙያ መመሪያን (CTE) ከጠቅላላ ትምህርት ካሪኩለም ጋር በማቀናጀት ተማሪዎችን ከዕውቀት ወደ ተግባራዊ ብቃት የሚያሸጋግር መመሪያ ነው።
ደራሲው ዶ/ር ታደሰ መኮንን ከመምህርነት እስከ ኮሌጅ አመራርነት በቆዩባቸው ረጅም የሥራ ዓመታትና በዶክትሬት (PhD) ምርምራቸው ወቅት የታዘቧቸውን የትምህርት ክፍተቶች መሠረት በማድረግ ያዘጋጁት እንደሆነ ገልጸዋል።የትምህርት ሥርዓቱ ተማሪዎችን ለፈተና ማለፍ ብቻ ሳይሆን ለሕይወትና ለሥራ ዓለም ማዘጋጀት እንዳለበት ማሳየት እንደሆነ ተጠቅሷል።
መጽሐፉ በ4 ዋና ዋና ክፍሎችና በ11 ምዕራፎች የተዋቀረ ሲሆን፤ የትምህርት አመራሮች፣ መምህራን፣ ተማሪዎችና ማህበረሰቡ ለሙያ ትምህርት ያላቸውን አመለካከት እንዲቀይሩ ያለመ ነው።
መጽሐፉ በእንግሊዝኛ የተዘጋጀው የትምህርት ሚኒስቴር ከ7ኛ እስከ 12ኛ ክፍል የሚጠቀመውን የማስተማሪያ ቋንቋ መሠረት በማድረግ ሲሆን፣ በቀጣይም በልዩ ልዩ የሀገሪቱ ቋንቋዎች ተተርጉሞ ይዘጋጃልተብሉዋል።
ደራሲው በመጨረሻም መጽሐፉ በመደርደሪያ ላይ የሚቀመጥ ሳይሆን በትምህርት ቤቶች ውስጥ ወርዶ በተግባር ላይ እንዲውል ጥሪ ያቀረቡ ሲሆን፣ የሚመለከታቸው የፖሊሲ አውጪዎችና አመራሮችም ለትግበራው በትብብር እንዲሰሩ አሳስበዋል።
በሰብል እበበ
#ዳጉ_ጆርናል | 5 875 |
| 11 | Нет текста... | 5 447 |
| 12 | የጌጅ ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ ከ3 ሺህ በላይ ተማሪዎችን አስመረቀ
👉ምሩቃኑ የጋዎን መያዣ ገንዘባቸውን ለበጎ አድራጎት አውለዋል
ጌጅ ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያሰለጠናቸውን 3 ሺህ 176 ተማሪዎችን በዛሬው ዕለት አስመርቋል።
ከተመራቂዎቹ መካከል ዩኒቨርሲቲ ኮሌጁ በመጀመሪያ ዲግሪ መርሃ ግብር ያሰለጠናቸው 2 ሺህ 500 ተማሪዎች ሲሆኑ፣ በቴክኒክና ሙያ (TVET) መርሃ ግብር ደግሞ 644 ተማሪዎችን አስመርቋል። በተጨማሪም ተቋሙ በድህረ-ምረቃ መርሃ ግብር በቢዝነስ አድሚኒስትሬሽን የትምህርት መስክ ያሰለጠናቸውን 32 ተማሪዎች ያስመረቀ ሲሆን፣ ከአጠቃላይ ተመራቂዎች ውስጥ 2 ሺህ 261 ያህሉ ሴቶች መሆናቸው ተገልጿል።
ተማሪዎቹ በአካውንቲንግ እና ፋይናንስ፣ ማኔጅመንት፣ ማርኬቲንግ እና ሴልስ፣ ኮምፒውተር ሳይንስ፣ ሂዩማን ሪሶርስ ማኔጅመንት፣ እንዲሁም ሃርድዌር እና ኔትወርኪንግ የትምህርት ዘርፎች ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የቆዩ ናቸው።
በምረቃ ስነ-ስርዓቱ ላይ "አፍሪካ ኢንተርናሽናል ሂውማኒቴሪያን ዴቨሎፕመንት"የተባለ አገር በቀል የግብረሰናይ ድርጅት ተወካይ ተገኝተው መልዕክት አስተላልፈዋል።
ድርጅቱ ከ2012 ዓ.ም ጀምሮ ረዳት ለሌላቸው አረጋውያን እና አካል ጉዳተኞች ቋሚ ወርሃዊ የገንዘብ ድጋፍ በማድረግ፣ አቅም በማጣት ከትምህርት ገበታ ለተፈናቀሉ ህፃናት የትምህርት ቁሳቁስና ክፍያ በመሸፈን፣ እንዲሁም የመታከም አቅም ለሌላቸው ህሙማን የህክምና ወጪ በመሸፈን እያከናወነ ያለውን የበጎ አድራጎት ስራ ለታዳሚያን አብራርተዋል።
ተወካዩ አክለውም፣ ተመራቂዎች ወደ ስራ ዓለም ሲቀላቀሉና ገቢ ማግኘት ሲጀምሩ የድርጅቱ ቋሚ አባል በመሆን ይህንን የበጎ አድራጎት ስራ እንዲደግፉ ጥሪ አቅርበዋል።
ለጅማሬ ያህል ምሩቃኑ ለጋዎን መያዣነት ያስያዙትን ገንዘብ ለድርጅቱ እንዲያበረክቱ በዕለቱ ጥሪ የተላለፈ ሲሆን ፣ ተማሪዎቹም ጥሪውን ተቀብለው ለጋዎን መያዣ የሰጡትን ገንዘብ ለግብረሰናይ ድርጅቱ ለመስጠት በህብረት ድምፅ ማሰማታቸውን ብስራት ሬድዮ ተመልክቷል ።
በሚኪያስ ፀሐዬ
#ዳጉ_ጆርናል | 5 705 |
| 13 | Нет текста... | 5 283 |
| 14 | https://youtu.be/_xMpWDIwLqw?is=4IyQIHhVqxPRjyK7 | 5 460 |
| 15 | ከ1 ሚሊዮን በላይ ቱሪስቶች የጉራጌ ዞንን ጎብኝተዋል ተባለ።
በዞኑ በተለይም የመስቀል በዓልን ምክኒያት በማድረግ የቱሪስቶች ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ መምጣቱን የጉራጌ ዞን ባህልና ቱሪዝም መምሪያ አስታውቋል ።
የመምሪያዉ ኃላፊ ወይዘሮ መሰረት አመርጋ ከብስራት ሬዲዮ ጋር ባደረጉት ቆይታ እንደተናገሩት በ2018 በጀት ዓመት በዞኑ ከ1 ነጥብ 2 ሚሊዮን የሚበልጡ ቱሪስቶች የቱሪስት መስህብ ስፍራዎችን ጎብኝተዋል።
በዚህም ከ6 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ መገኘቱ ተገልጿል ። ከመስቀል በዓል በተጨማሪ ለአረፋ በዓል ወደ ዞኑ የሚገቡ ቱሪስቶች ቁጥር ከፍተኛ መሆኑ ለቱሪዝም ዘርፉ ከፍተኛ መነቃቃትን መፍጠር ተችሏል ነው የተባለው።
የብሔር ብሔረሰቦችን ቀንን አስመልክቶ በርካታ እንግዶች በዞኑ መታደማቸዉም ታውቋል። በየጊዜዉ የሚደረጉ ሃይማኖታዊ ጉዞዎች ለአብነት ያህልም ጥንታዊው ኢየሱስ ገዳም በርካታ የቱሪስት ፍሰትን ከሚያስተናግዱ የመስህብ ስፍራዎች መካከል ተጠቃሽ መሆኑ ተጠቁሟል ።
በመባ ወርቅነህ
#ዳጉ_ጆርናል | 5 298 |
| 16 | በሁለት ወራት ዉስጥ ከ40 ሚሊዮን በላይ ዜጎች ነፃ የህክምና አገልግሎት አግኝተዋል ተባለ
በክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ባለፉት ሁለት ወራት ከ40 ሚሊዮን በላይ ዜጎች ነፃ የሕክምና አገልግሎት ማግኘታቸውን የጤና ሚኒስቴር አስታወቀ ።
የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ደረጄ ዱጉማ እንደተናገሩት በክረምት በጎ ፈቃድ መርሃ ግብር ለ20 ሚሊዮን ዜጎች ነፃ የሕክምና አገልግሎት ለመስጠት ታቅዶ የነበረ ቢሆንም ከ40 ሚሊዮን በላይ ዜጎች አገልግሎቱን አግኝተዋል ።
በመርሃ ግብሩ ከተለያዩ የጤና ተቋማትና የጤና ባለሙያዎች ጋር በመተባበር ዜጎች የሕክምና ምርመራና ሌሎች ነፃ የጤና አገልግሎቶችን ማግኘታቸው ተገልጿል ።
በተመሳሳይ መልኩ የደም እጥረትን ለመቀነስ በተደረገው ጥረት 160 ሺህ ዩኒት ደም መሰብሰቡን ዶክተር ደረጄ መናገራቸዉን ብስራት ሬዲዮ ሠምቷል ።
በክረምት በጎ ፈቃድ መርሃ ግብሩ 70 ሺህ ነፃ የቀዶ ሕክምና አገልግሎቶችም መሰጠታቸውን የጤና ሚኒስቴር ደኤታው አክለዋል ። ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ እንደገለጸው የበጎ ፈቃድ የጤና አገልግሎቱ በተለይም የህክምና ወጪን በመሸፈን የመታከም አቅም ለሌላቸው ዜጎች እፎይታን የሰጠ ነዉ ብለዋል ።
በመባ ወርቅነህ
#ዳጉ_ጆርናል | 5 380 |
| 17 | የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅሶችን በመጠቅለያዎቹ ላይ የሚያሰፍረው የአሜሪካው በርገር ቤት ኢን-ኤንድ-አውት ተቃውሞ ቢገጥመውም መቼም ታሪካዊ ልምዱን እንደማይተው አስታወቀ
በአሜሪካ አገር 424 ቅርንጫፎች ያሉት እና ከ28,000 በላይ ሰራተኞችን የሚያስተዳድረው ዝነኛው የፈጣን ምግብ ሰንሰለት ኢን-ኤንድ-አውት በሚሸጣቸው የበርገር ማሸጊያዎች ላይ የሚያትማቸው የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅሶች በደንበኞች እና በሲቪል መብት ተሟጋቾች መካከል ሰፊ የሃሳብ መከፋፈል ፈጥረዋል።
ተቋሙ በለስላሳ መጠጥ መያዣ እቃዎች የታችኛው ክፍል እና በበርገር መጠቅለያ ወረቀቶች ላይ እንደ “ዮሐንስ 3:16”፣ “ምሳሌ 3:5”፣ “ምሳሌ 24:16”፣ “ናሆም 1:7”፣ “ሉቃስ 6:35” እና “ራዕይ 3:20” የመሳሰሉ ጥቅሶችን የሚያትምባቸው ሲሆን፣ ይህም አሰራር የተጀመረው ከ46 ዓመት በፊት በድርጅቱ መስራች በነበሩት ሐሪ ስናይደር አማካኝነት የቤተሰቡን የክርስትና እምነት ለማንጸባረቅ ታስቦ ነበር።
የድርጅቱ ደጋፊዎች ማናቸውም የግል ኩባንያ በራሱ ምርት ላይ የፈለገውን ነገር የማድረግ ሙሉ መብት እንዳለውና ጥቅሶቹም ማንንም ደንበኛ እምነት እንዲቀይር እንደማያስገድዱ ይከራከራሉ።
በአንጻሩ ነቃፊዎች ደግሞ ተቋሙ የተለያየ እምነት ያላቸውንና ምንም እምነት የሌላቸውን በሚሊዮን የሚቆጠሩ ደንበኞችን የሚያስተናግድ አገር አቀፍ የንግድ ሰንሰለት በመሆኑ፣ የበርገር መጠቅለያ ወይም የፈሳሽ መያዣ የወረቀት ብርጭቆዎች ላይ የሃይማኖት መልዕክቶች ፈጽሞ መኖር የለባቸውም ሲሉ ይተቻሉ።
የአሁኗ የድርጅቱ ዋና ስራ አስፈጻሚ እና የመስራቹ የልጅ ልጅ የሆኑት ሊንሲ ስናይደር ይህንን ተግባር እንደ ቤተሰብ መዘከሪያ ቅርስ በመቁጠር ከአቋማቸው ፍንክች እንደማይሉ በተደጋጋሚ የገለጹ ሲሆን፣ በጥቅሶቹ ምክንያት ነቀፌታ እና የተሟጋቾች ግፊት ቢኖርም የኩባንያው ቅርንጫፎች መስፋፋታቸውን እና የድርጅቱ ተወዳጅነት ከመጨመር ወደ ኋላ አላለም።
Via መዝናኛ ሚዲያ
#ዳጉ_ጆርናል | 4 854 |
| 18 | Нет текста... | 4 764 |
| 19 | የኦሮሚያ ኅብረት ሥራ ባንክ ከውጭ ሀገር ወደ ሀገር ውስጥ ገንዘብ ለማስተላለፍ የሚያስችል ‘CoopRemit’ የተሰኘ አዲስ የሬሚታንስ መተግበሪያ ሥራ ላይ ማዋሉን አስታወቀ።
ባንኩ ነሀሴ 24 ቀን 2018 ዓ.ም ይፋ ያደረገው ይህ መተግበሪያ፤ ደንበኞች ከ‘App Store’ እና ‘Play Store’ በቀላሉ በማውረድ ሊጠቀሙበት የሚችሉ ሲሆን፣ በገበያ ዋጋ ላይ የተመሰረተ ከፍተኛ የምንዛሪ ዋጋ (Best Rate) የሚሰጥ መሆኑ ተገልጿል።
መተግበሪያው የሌሎች ተቋማትን ዕለታዊ የምንዛሪ ተመን በማነጻጸር የተሻለውን መምረጥ የሚያስችል በመሆኑ ደንበኞች መረጃ ላይ የተመሰረተ ውሳኔ እንዲሰጡ ያግዛቸዋል።
በተጨማሪም ከውጭ የሚላከው ገንዘብ ወደ ኦሮሚያ ኅብረት ሥራ ባንክም ሆነ ወደ ሌሎች የሀገር ውስጥ ባንኮች ሂሳብ በቀጥታ፣ በፈጣንና በአስተማማኝ ሁኔታ የሚደርስ ነው ተብሏል።
የባንኩ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ደርቤ አስፋው እንደተናገሩት፤ ደንበኞች ገንዘባቸውን በቪዛ፣ በማስተር ካርድ፣ በአፕል ፔይ ወይም በጉግል ፔይ በመጠቀም በቀጥታ በ‘CoopRemit’ መተግበሪያ በኩል መላክ ይችላሉ።
#ዳጉ_ጆርናል | 5 530 |
| 20 | 6’—Isak ⚽, Gakpo 🎁
9’—Isak ⚽, Gakpo 🎁
Alexander Isak and Cody Gakpo combining twice in the first nine minutes to put Liverpool up 2-0 ⚡ | 6 281 |
