cookie

Мы используем файлы cookie для улучшения сервиса. Нажав кнопку «Принять все», вы соглашаетесь с использованием cookies.

avatar

ዳጉ-ጆርናል/Dagu-Journal

The best fiction is far more true than any journalism 📢 ተዓማኒ የመረጃ ምንጭ ፤ ለሙያው ስነምግባር ተገዢ በሆኑ ጋዜጠኞች ብቻ 👉 በፌስቡክ ገፆቻችን https://www.facebook.com/simon.dereje.56 👉 https://www.facebook.com/mik0Man

Больше
Рекламные сообщения
34 383Подписчики
-824 часа
+1407 дней
+1 86730 дней
Архив постов
የኤርትራ ጦር ከዛላንበሳና አጎራባች ወረዳዎች ሰዎችን አግቶ እየወሰደ ነው ተባለ የዛላአንበሳ ከተማ ከንቲባ ብርሃነ በርሄ ለጣቢያችን እንደተናገሩት ከምስራቃዊ ዞን  ከአንድ መቶ በላይ ሰዎች ታግተዉ ተወስደዋል ብለዋል፡፡ ከዛላ አንበሳ 26 ሰዎች ፣ ከጉለም ወረዳ  50  እንዲሁም ከኢሮብ 28 ሰው በኤርትራ ሰራዊት እንደተወሰደ  ገልፀው በዚህ ሳምንት ደግሞ ቁጥሩ መጨመሩን መናገራቸውን ዳጉ ጆርናል ከኢትዮ ኤፍኤም ዘገባ ተመልክቷል። አሁን ላይ ዛላንበሳ ከተማን ጨምሮ  ምስራቃዊው ዞን ሙሉ በሙሉ በኤርትራ ጦር ቁጥጥር ስር እንደሆነ የሚናገሩት የከተማዋ ከንቲባ ማህብረሰቡም ብዙ በደል እና ጥቃት እየደረሰበት ነዉ ብለዋል፡፡ የኤርትራ ጦር የአካባቢዉን ነዋሪዎቹ በአልጀርስ ስምምነት መሰረት  ኤርትራዊ እንደሆኑ በመግለጽ  በኃይል  እንደተቆጣጠረም ተነግሯል፡፡ የፌድራል መንግስት ምንም አይነት ትኩረት አልሰጠንም የሚሉት አቶ ብርሀነ ዳግም ጦርነት አንፈልግም ግን ደግሞ ማንነታችንን እና ህልውናችንን ሊያስከብርልን ይገባል ብወዋል። በከተማዋ የሚገኙ መሰረተ ልማቶች በጦሩ  ሙሉ በሙሉ እንደወደሙ ተነስቶ  በከተማው እንዲሁም በአካባቢው ያለው ነዋሪ ለከፋ ችግር እንደተጋለጠም ተናግረዋል፡፡ ከዚህም ጋር ተያይዞ ከ 30ሺ በላይ ነዋሪ ተፈናቅሎ በመቀሌ፤ በአዲግራት እንዲሁም በተለያዩ አከባቢዎች በመጠለያ ጣቢያ እንደሚገኝ  አቶ ብርሀነ ገልፀዋል፡፡ #ዳጉ_ጆርናል
Показать все...
👍 8🤬 1
የሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነትን ተከትሎ በአማራ ክልል ስር ሲተዳደሩ የቆዩት የራያ አካባቢዎች ያለ አስተዳዳሪ ወደ ሁለተኛ ሳምንታቸው እየተሻገሩ ነው ከየካቲት ጀምሮ አልፎ አልፎ ሲከሰት የነበረው “በህወሓት ታጣቂዎች” እና “በአካባቢው ሚሊሺያዎች” መካከል ሲደረግ የነበረው የተኩስ ልውውጥ ከሚያዝያ 5/2016 ዓ.ም. ጀምሮ ከፍ ባለ ሁኔታ ተካሂዶ ከሰሜን ኢትዮጵያው ጦርነት ወዲህ የነበረውን መዋቅር ቀይሮታል። ላለፉት ሦስት ዓመት ገደማ አካባቢዎቹን ሲመሩ የነበሩት ከአማራ ክልል በኩል የተሾሙ አስተዳዳሪዎች፤ ከሚመሯቸው የራያ ወረዳ እና ከተሞች ሸሽተው ቆቦ ከተማ እና ሌሎች አጎራባች አካባቢዎች ውስጥ ተጠልለዋል። በቆቦ ከተማ የሚገኙት ከራያ አካባቢዎች የሸሹት የመንግሥት ሹመኞች ብቻ አይደሉም። የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሰብዓዊ እርዳታ ማስተባበሪያ ጽህፈት ቤት (ኦቻ) በዚህ ሳምንት መጀመሪያ በወጣው ሪፖርት 50 ሺህ ሰዎች ከራያ ወረዳ እና ከተማ አስተዳደሮች እንደተፈናቀሉ አስታውቋል። ከተፈናቃዎቹ ውስጥ 42 ሺህ ያህሉ የሚገኙት በሰሜን ወሎ ዞን ስር በምትገኘው ቆቦ ከተማ እንደሆነ ጽህፈት ቤቱ ገልጿል። ሌሎች የራያ አካባቢዎች ነዋሪዎች ግን አሁንም ባሉበት ኑሯቸውን ቀጥለዋል። የአማራ እና ትግራይ ክልሎች የየራሳቸው አስተዳዳሪዎች የተሾሙላቸው የአላማጣ እና የኮረም ከተሞች ያለምንም አስተዳዳሪ ከቀሩ ሁለት ሳምንታት ተቃርበዋል። ከሁለቱም ክልሎች የተሾሙ አመራሮች የሚገኙት በየክልላቸው ውስጥ በሚገኙ አጎራቦች አካባቢዎች ውስጥ ነው። በአላማጣ እና ኮረም ከተማዎች ውስጥ የፌደራል እና የመከላከያ ሠራዊት አባላት እንደሚገኙ ቢቢሲ ያነጋገራቸው የሁለቱ ከተማዎች አምስት ነዋሪዎች ተናግረዋል። በከተሞቹ ውስጥ የሚገኙት የፌደራል መንግሥት እንዲሁም የአካባቢ አስተዳደሮችን ተቋማት እና ቢሮዎች እየጠበቁ ያሉት በሁለቱ የፀጥታ አካላት መሆኑን ነዋሪዎች ገልጸዋል። ቢቢሲ ያነጋገራቸው የአላማጣ ከተማ ነዋሪዎች በአሁኑ ሰዓት ከተማዋ ውስጥ አንጻራዊ ሰላም እንዳለ ጠቅሰዋል። ባንኮች፣ የኢትዮ ቴሌኮም ቢሮዎች እንዲሁም የተወሰኑ መደብሮች መከፈታቸውን ሦስት ነዋሪዎች ተናግረዋል። በከተማዋ ውስጥ የሚገኙ አንዳንድ መደብሮች ያልተከፈቱት አካባቢዎቹን ላይ አስተዳዳሪ አለመኖሩ በፈጠረባቸው ስጋት ምክንያት መሆኑን የሚናገሩ አንድ የአላማጣ ነዋሪ፤ በከተማዋ ውስጥ የሚገኙት የፌደራል ፖሊስ እና የመከላከያ ሠራዊት አባላት እየተንቀሳቀሱ ያሉት በዋና የአስፓልት መንገዶች ላይ እንደሆነ አስረድተዋል። ከትግራይ ክልል በኩል የተሾሙት የአላማጣ ከተማ ከንቲባ አቶ ዝናቡ ደስታም በተመሳሳይ በከተማዋ ሁለቱ የፌደራል መንግሥት ኃይሎች ቢኖሩም የፀጥታ ሁኔታው በበቂ ሁኔታ እየተሸፈነ አለመሆኑን ለቢቢሲ ተናግረዋል። በአማራ ክልል በኩል የተሾሙት የአላማጣ ከንቲባ አቶ ኃይሉ አበራ በበኩላቸው የመከላከያ ሠራዊት እና ፌደራል ፖሊስ አባላት ከተማዋ ውስጥ መኖራቸውን አንስተው በአሁኑ ሰዓት ስላለው ሁኔታ ግን “ዝርዝር መረጃ” እንደሌላቸው ጠቅሰዋል። ባለፈው ሳምንት መጀመሪያ የመንግሥት ኃላፊዎች ከአላማጣ መውጣታቸውን ተከትሎ በመንግሥት ተቋማት ደረጃ የሚሰጡ አገልግሎቶች እስካሁን ድረስ እንደቆሙ መሆኑን ሦስት ነዋሪዎች ገልጸዋል። የከተማዋ አስተዳደር መሥሪያ ቤቶች፣ ትምህርት ቤቶች እና የጤና ተቋማት አገልግሎት እየሰጡ እንዳልሆነም ጠቅሰዋል። አንድ የከተማዋ ነዋሪ*፤ “[የጤና አገልግሎት] የለም ማለት ይቻላል። አሁን በቅርብ አንዲት ወላድ ነበረች፤ ደም [ያስፈልጋል] ተብላ ወደ ወልዲያ ሄዳለች። ምንም ዓይነት አገልግሎት የለም። በጣም ተቸግራ እዚህ ያሉ ዶክተሮች በግል ተባበሯት፤ …ወደ ቆቦ በትራንስፖርት ሄዳ፣ ከቆቦ ወደ ወልዲያ ወሰዷት” ሲል በከተማዋ ላለው ሁኔታ ማሳያ ጠቅሷል። በኮረም ከተማም በተመሳሳይ የመንግሥት አገልግሎት ሰጪ መሥሪያ ቤቶች ዝግ መሆናቸውን ሦስት የከተማዋ ነዋሪዎች ለቢቢሲ ተናግረዋል። የቀድሞ አስተዳዳሪዎች ለቀው በወጡባት ኮረም ከተማም የመንግሥት መሥሪያ ቤቶች እና ተቋማት እየተጠበቁ ያሉት በፌደራል ፖሊስ እና በመከላከያ ሠራዊት አባላት መሆኑን ተናግረዋል። ይሁንና ከአላማጣ ከተማ በተለየ መልኩ የትግራይ ክልል ታጣቂዎች በከተማዋ ውስጥ እንደሚንቀሳቀሱ ሦስት ነዋሪዎች ገልጸዋል። ቢቢሲ ያነጋገራቸው ነዋሪዎች ታጣቂዎቹ በከተማዋ ነዋሪዎች ላይ “ዝርፊያ ፈጽመዋል” ሲሉ ከሰዋል። ታጣቂዎቹ የሰፈሩት በከማው ውስጥ በሚገኙት ስድስት ትምህርት ቤቶች ውስጥ መሆናቸውን የሚናገሩ አንድ ነዋሪ፤ “የትምህር ቤት መጽሐፍት ‘የአማራ ክልል ናቸው’ በሚል ተቀድደዋል” ሲሉ በትግራይ ታጣቂዎች ተፈጽሟል ያሉትን ድርጊት ጠቅሰዋል። ሌላ ነዋሪ በበኩላቸው፤ በከተማዋ ውስጥ በታጣቃዎቹ በሚፈጸሙት ድርጊቶች ሳቢያ ነዋሪዎች አሁንም ወደ ቆቦ ከተማ እየሸሹ መሆኑን ተናግረዋል። በቆቦ ከተማ የሚገኙት በአማራ ክልል የተሾሙት የአላማጣ ከተማ ከንቲባ አቶ ኃይሉም የኮረም ከተማ ነዋሪዎች አሁንም ወደ ቆቦ ከተማ እየገቡ መሆኑን ለቢቢሲ አረጋግጠዋል። በትግራይ ክልል በኩል የራያ አካባቢ ወረዳ እና ከተማዎችን በስሩ የያዘው የደቡባዊ ትግራይ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሀፍቱ ኪሮስ፤ በኮረም ከተማ የትግራይ ክልል ታጣቂዎች ገብተዋል ስለመባሉ እና ታጣቂዎቹ ፈጽመዋቸዋል ስለተባሉ ድርጊቶች ከቢቢሲ ጥያቄ ቀርቦላቸዋል። በአሁኑ ሰዓት በኮረም “በጣም የተረጋጋ ሰላም እና ደኅንነት” መፈጠሩን የሚናገሩት ዋና አስተዳዳሪው፤ “ኮረም እና አላማጣም ላይ በአሁኑ ሰዓት የፌደራል ኃይሎች የፀጥታ እና ሰላሙን የመጠበቅ ሥራ በከፍተኛ ሁኔታ እየፈጸሙ ነው” ብለዋል። አቶ ሀፍቱ፤ የትግራይ ክልል ታጣቂዎች በከተማዋ ስለመግባታቸው እና በትምህርት ቤቶች ውስጥ ስለ መስረፈራቸው ማረጋገጫ ከመስጠትም ሆነ ከማስተባበል ተቆጥበዋል። እንደ ራያ ባሉ አካባቢዎች ላይ ከዚህ ቀደም በፌደራል መንግሥት እና በትግራይ ክልል ጊዜያዊ መስተዳደር መካከል የነበረው “ከመከላከያ ሠራዊት ውጪ ሌላ ታጣቂ ኃይል አይኑር” የሚለው “ንግግር” በአሁኑ ሰዓት “መቀየሩን” ዋና አስተዳዳሪ ገልጸዋል። የፕሪቶሪያ ስምምነትን የተፈራረሙት የፌደራል መንግሥቱ እና ህወሓት ከስምምነቱ በታች ያሉ ጉዳዮችን በፖለቲካዊ ንግግር እየፈቱ እና “እያሻሻሉ” እየሄዱ መሆኑን የሚናገሩት አቶ ሀፍቱ፤ “ለምሳሌ አሁን ማሻሻያዎች አሉ። በዚያ አካባቢ ከመከላከያ ሠራዊት እና ከፌደራል ፖሊስ ውጪ ማንኛውም ታጣቂ መኖር የለበትም የሚል የውይይት ሀሳብ እንደነበር ይታወቃል። አሁን እሱ ተቀይሯል። ሌላ እድገት አለው” ብለዋል። ዋና አስተዳዳሪው “ተቀይሯል” ያሉት የታጣቂዎች ጉዳይ የሚወያዩት አካላት ይፋ እንደሚያደርጉት በመጥቀስ ዝርዝሩን ከመናገር ተቆጥባዋል። ሁለቱ ክልሎች በሚወዛገቡባቸው አካባቢዎች ባለፉት ሳምንታት የተፈጠረውን ሁኔታ የአፍሪካ ኅብረት እና በኢትዮጵያ የሚገኙ የተለያዩ አገራት ተወካዮች እንዳሰሰባቸው እና ሁሉም ወገኖች ከግጭት እንዲቆጠቡ አሳስበዋል። የአማራ እና የትግራይ ክልሎች በይገባኛል በሚወዛገቡባቸው አካባቢዎች ላይ የህወሓት ታጣቂዎች ወረራ ፈጽመዋል ብሎ ባለፈው ሳምንት የአማራ ክልል መንግሥት መክሰሱ ይታወሳል። ለወሰን እና ለማንነት ጉዳዮች መፍትሄ ለመስጠት እየሠራ መሆኑን የገለጸው የፌደራል መንግሥቱ የህወሓት ኃይሎች ትጥቅ መፍታት አለባቸው ሲል ከቀናት በፊት ባወጣው መግለጫ አመልክቷል። Via ቢቢሲ #ዳጉ_ጆርናል
Показать все...
👍 9🕊 3😢 1
የደብረብርሃን ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት የት እንዳሉ እንደማይታወቅ ተነገረ ከሶስት ዓመት በፊት የደብረ ብርሀን ዩንቨርስቲ ፕሬዝዳንት ሆነው የተሾሙት ንጉስ ታደሰ (ዶ/ር) በቢሯቸው ከታዩ አንድ ወር አልፏቸዋል ተብሏል። ስማቸው እንዳይጠቀስ የፈለጉ የዩንቨርሲቲው አስተዳድር አመራር አባል ለአል ዐይን አማርኛ እንዳሉት "ፕሬዝዳንቱ ከመጋቢት 17 ቀን 2016 ዓ. ም ጀምሮ በስራ ላይ አይተናቸው አናውቅም" ብለዋል። "ፕሬዝዳንቱ ንጉስ ታደሰ ከተጠቀሰው ቀን አንስቶ የት እንደሄዱ እና መቼ እንደሚመለሱ አናውቅም" ሲሉም እኝህ አመራር ነግረውኛል ሲል አል አይን መዘገቡን ዳጉ ጆርናል ተመልክቷል። ይሁንና ፕሬዝዳንቱ በቢሮ መታየት ካቆሙ ከተወሰኑ ቀናት በኋላ ባልታወቁ ሀይሎች መታገታቸውን ሰምተናል ሲሉም አክለዋል። የሰማን ሸዋ ዞን ፖሊስ፣ ኮማንድ ፖስት፣ ትምህርት ሚንስቴር እና የደብረብረሀን ከተማ ፖሊስ ስለ ደብረ ብርሀን ዩንቨርስቲ ፕሬዝንት ንጉስ ታደሰ (ዶ/ር) ጉዳይ ምላሽ እንዲሰጡን ያደረግነው ጥረት አልተሳካም። እንዲሁም የፕሬዝዳንቱ ቤተሰብ ተጨማሪ መረጃ እንዲሰጡን ያደረግነው ተደጋጋሚ ጥረት አልተሳካም። #ዳጉ_ጆርናል
Показать все...
😁 11🤔 9👍 3 2😢 2🙏 1
በካፋ ዞን አንድት ሴት ህፃን ጫካ ውሰጥ ተጥላ ተገኘች በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በካፋ ዞን የሺሾ እንዴ  ሚያዚያ 18 ቀን 2016 ዓ.ም ከቀኑ 5:00 ሰዓት በ01 ቀበሌ ልዩ ስፍራው እግዚአብሔር አብ ተብሎ በሚጠራበት ጫካ ዉስጥ ተጥላ መገኘቷን ፖሊስ አስታውቋል። ፖሊስም ህፃኗን በማንሳት ወደህክምና ተቋም በመውሰድ አስፈላጊውን የህክምና እርዳታ እንድታገኝ የተደረገ ሲሆን ህፃኗ በጥሩ ጤንነት ላይ እንደምትገኝ የደብቡ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ፖሊስ ኮሚሽን የህዝብ ግንኙነት እና ኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር ምክትል ኢንስፔክተር ደጀኔ አሰፋ ለብስራት ሬዲዮ እና ቴሌቪዥን ተናግረዋል። ከአከባቢው ህብረተሰብ ጋር በመሆን የህፃኗን ቤተሰብ በአከባቢው ባህል መሰረት ኦቶ ወይም በአፈርሳታ እያፈላለገ ሲሆን ህፃኗን ከሺሾ እንዴ ከተማ አስተዳደር ሴቶችና ህፃናት ጽ/ቤት ጋር በመሆን በጊዜያዊነት ለአንድ ግለሰብ እንድታሳድጋት መሰጠቷን ተገልጿል። #ዳጉ_ጆርናል
Показать все...
የካሊፎርኒያ ኮሌጅ በጋዛ ያለውን ጦርነት በመቃወም የተነሳውን ውጥረት ተከትሎ ተጠባቂውን የተማሪዎች የምረቃ ስነስርአት ሰረዘ በሎስ አንጀለስ የሚገኘው የደቡባዊ ካሊፎርኒያ ዩኒቨርሲቲ ያለውን የደህንነት ስጋት በመጥቀስ ዋናውን እና በግንቦት 10 እንዲካሄድ ቀጠሮ የተያዘለትን የምረቃ ሥነ-ሥርዓት ሰርዟል። ይህ እርምጃ የተወሰደው በእስራኤል እና በጋዛ ጦርነት ምክንያት በመላው ዩናይትድ ስቴትስ ውስጥ በደርዘን የሚቆጠሩ ካምፓሶች ተቃውሞ በተቀሰቀሰበት ወቅት ነው። በአትላንታ ኤሞሪ ዩኒቨርሲቲ 28 ተቃዋሚዎች ግቢውን ለቀው ለመውጣት ፈቃደኛ ባለመሆናቸው ሐሙስ ዕለት ተይዘዋል ። በኒውዮርክ ከተማ፣ ኮሎምቢያ ዩኒቨርሲቲ በግቢው ውስጥ ያለውን ተቃውሞ ለማስቆም ቀነ ገደብ ተጥሏል።ተማሪዎች ግን ድንኳን ሰርተው ተቃውሞ ማሰማታቸውን ቀጥለዋል። በመግለጫው የደቡባዊ ካሊፎርኒያ ዩኒቨርሲቲ እንዳስታወቀው 65,000 ተማሪዎች፣ ቤተሰብ እና ጓደኞቻቸው የሚታደሙበት የምረቃ ሥነ ሥርዓት ግቢው ማስተናገድ እንደማይችል ይፋ አድርጓል። እሮብ እለት፣ ፖሊስ ግቢውን ጥሶ በመግባት ከ93 ያላነሱ ሰዎችን በቁጥጥር ስር አውሎ እንደነበር ከስፍራው የወጡ መረጃዎች አመላክተዋል። በዋሽንግተን ዲሲ በሚገኘው ጆርጅ ዋሽንግተን ዩኒቨርሲቲ በተማሪዎች ተቃውሞ የፍልስጤም ኬፊህ ወይም ሻርፕ እና በፍልስጤም ባንዲራ የመጀመሪያው የአሜሪካ ፕሬዝዳንት የጆርጅ ዋሽንግተን ሀውልት ለብሶ ታይቷል። በሌላ በኩል በጋዛ በቀጠለው ውጊያ ዙሪያ አንድ የእስራኤል ከፍተኛ ባለስልጣን ወታደሮቹ በታቀደው የምድር ጦር ዘመችም መሰረት “ወደ ፊት እየገሰገሱ ነው” ነው ብለዋል። የራፋህ ምስራቃዊ ክፍል በየጊዜው በመድፍ እየተደበደበ ይገኛል። ከደቡብ ሊባኖስ በተነሳው የሂዝቦላ የሚሳኤል ጥቃት አንድ እስራኤላዊ የጭነት መኪና ሹፌር መገደሉን የእስራኤል ጦር አስታውቋል። የእስራኤል ሚዲያዎች አካባቢው በተመታበት ጊዜ ሰውዬው ወደ እስራኤል ሰሜናዊ ድንበር አቅራቢያ ለወታደሮች የመሠረተ ልማት ስታዎችን ሲያከናውን ነበር ብለዋል ። በሊባኖስ እና በእስራኤል ድንበር ላይ በሄዝቦላህ እና በእስራኤል ጦር መካከል የተኩስ ልውውጥ መደረጉን የእስራኤል ጦር አስታውቋል። በኢራን የሚደገፈው ቡድን ከጋዛውያን ጎን መቆሙን በተደጋጋሚ አሳይቷል። በስምኦን ደረጄ #ዳጉ_ጆርናል
Показать все...
👍 40 11👏 4👎 1
"እግዚአብሔር በቅዱሳኑ ላይ ድንቅ ነው።" መዝሙር 68፤35 ገዳመ ወንያት መንታዎቹ ደብር አቡነ ሐራ ድንግል ገዳም ወር በገባ በ11ኛው ቀን ጻድቁ አቡነ ሐራ መታሰቢያ በዓላቸው ነው።ገዳሙ የተአምራት የበረከት የፈውስ ቦታ ነው።ከጻድቁ መቃብር ተዝቆ በማያልቅ ሞልቶ በማይፈስ አፈር እጹብ ድንቅ ተአምራት ይደረጋል። በጻድቁ መካነ መቃብር ላይ የሚገኘውን ቤተክርስቲያን ያሰሩት አፄ ዮሐንስ፬ኛ በጽኑ ነቀርሳ በሳይንሳዊ አጠራር ካንሰር በሽታ ተይዘው የእግዚአብሔር ቸርነት የጻድቁን አማላጅነት ተስፋ አድርገው ከመቀሌ ድረስ ገስግሰው መጥተው በጻድቁ ጸበል ድንቅ ስለተደረገላቸው ፈውስን ስላገኙ የክብር አልጋና ዘውዳቸውን ሰጥተዋል ቤተክርስቲያኑንም አሰርተዋል። ጻድቁ ዛሬም ውሉደ ጥምቀትን ሁሉ ከክፉ ደዌ በጸበላቸው ይፈውሳሉ።ከባሕር ዳር ወደ ጎንደር መንገድ ስንወጣ ዘንዘልማ የምትባል አነስተኛ ከተማ አለች ከዘንዘልማ በስተቀኝ ታጥፎ በ12ኪሎሜትር ላይ ይገኛል።ብዙዎች በጻድቁ አማላጅነት ከደዌ ስጋ ድነዋል መካኖች ወልደዋል እውሮች በርተዋል ለምጻሞችም ነጽተዋል። የጻድቁ በረከት ይደርብን በቃልኪዳናቸው ይጠብቁን ከእለት እኪት ከቀሳፊ ነገር ይሰውሩን ከፍቅር ረሐብ ከዘረኝነት ደዌ ከዝሙት እሳት ከምንፍቅና አሽክላ ይታደጉን።የገዳመ ወንያት አቡነ ሐራ ድንግል አንድነት ገዳም በዓላውያን መንግስታት ዘመን በደረሰበት መከራና ፈተና የተነሣ ተዳክሞ በመቆየቱ የገዳሙ የይዞታ ቦታ በመሉ በአካባቢው አርሶ አደር እና በሌሎች ጥቃቅን ነጋዴዎች እጅ ከገባ አያሌ ዘመናትን ያስቆጠረ ሲሆን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ አንድነት ገዳሙ ወደ ቀደመ ክብሩ መመለሱን ተከትሎ በርካታ አባቶች መነኮሳትና እናቶች መነኮሳይያት ወደ ገዳሙ በመግባት በመልሶ ማቋቋም ሥራ ላይ ተሰማርተው የሚገኙ ቢሆንም የገዳሙ ይዞታ ለረጅም ዘመናት በሌሎች ግለሰቦች እጅ ተይዞ በመቆየቱ ምክንያት እንኳንስ ለገዳሙ ልማት ይቅርና ለመነኮሳቱ መጠለያ ቤት መሥሪያ ቦታ በመጥፋቱ ገዳሙ በከፍተኛ ችግር ላይ ይገኛል፡፡ ይህን መሬት ለማስመለስ ከ100 ሚሊዮን ብር በላይ የካሳ ክፍያ ተጠይቋል።ለዚህም ሚያዚያ 19/2016 ዓ/ም ታላቅ የገቢ ማሰባሰብያ መርሀ ግብር በካፒታል ሆቴል ለማካሄድ ቀን ተቆርጧል በሐገር ቤትም በውጭም ያላችሁ የፃድቁ ወዳጆችና ህዝበ ክርስቲያን እንድትረባረቡ ገዳሙ በመንፈስ ቅዱስ ስም ጠይቋችኃል #ዳጉ _ጆርናል
Показать все...
👍 35 12👎 7🔥 1
👍 1
አሜሪካ ወታደሮቿን ከቻድ በጊዜያዊነት ልታስወጣ መሆኑ ተነገረ ዩናይትድ ስቴትስ ሁሉንም ወታደሮቿን ከጎረቤት ኒጀር ለማስወጣት ከተስማማች ከቀናት በኋላ የተወሰኑ ወታደሮቿን ከቻድ በጊዜያዊነት እንደምታስወጣ ተሰምቷል። የዩናይትድ ስቴትስ የፔንታጎን ፕሬስ ሴክሬታሪ ሜጀር ጄኔራል ፓት ራይደር እንደተናገሩት ዩናይትድ ስቴትስ አንዳንድ ወታደራዊ ኃይሎቿን ከቻድ “ለመቀየር” አቅዳለች፣ ነገር ግን ምን ያህሉ እንደሚወጡ እና ወደየት እንደሚዘዋወሩ ግን አልገለጹም። "ይህ ከቻድ የግንቦት 6 ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ በኋላ የሚቀጥል የፀጥታ ትብብር ግምገማ አካል የሆነ ጊዜያዊ እርምጃ ነው" ብለዋል ። ይህ መረጃ የተሰማው የቻድ አየር ሃይል አዛዥ ዩናይትድ ስቴትስን በዚህ ወር መጀመሪያ ላይ በዋና ከተማዋ ኒጃሜና አቅራቢያ የሚገኘውን የአየር ጦር ሰፈር እንቅስቃሴ እንድታቆም ማዘዛቸውን ተከትሎ ስለምሆኑ ሮይተርስ የዜና ወኪል ዘግቧል። ጄኔራል ራይደር በተጨማሪም ከኒጀር ገዥው ወታደራዊ መንግስት፣ የሀገር ውስጥ ጥበቃ ብሔራዊ ምክር ቤት ጋር ውይይት የጀመረው እሮብ እለት ሲሆን ዓላማውም “ሥርዓት እና ኃላፊነት በተሞላበት ሁኔታ የአሜሪካ ኃይሎች ከአገሪቱ መውጣታቸውን” ለማረጋገጥ ነው። ዩናይትድ ስቴትስ በቀጠናው የሚገኙ ታጣቂዎችን እንቅስቃሴን ለመከታተል እንደ ቀዳሚ ቦታዋ ኒጀርን ትመለከታት ነበር። ነገር ግን ካለፈው ሀምሌ ወር ጀምሮ በስልጣን ላይ ያለው ገዥው ወታደራዊ መንግስት የዩናይትድ ስቴትስ ወታደሮች በሀገሪቱ ላይ እንዲሰማሩ እና የፈረንሳይ ወታደሮችን እንዲቆዩ የፈቀደውን ወታደራዊ ስምምነት ወረቀት ቀዷል። ይህ ውሳኔ የኒጀር ወታደራዊ መንግስት ከምዕራባውያን ጋር ያለውን ግንኙነት ለመቁረጥ የጀመረው ጥረት አካል ነው። በአበረ ስሜነህ #ዳጉ_ጆርናል
Показать все...
👍 14🔥 1
በምዕራብ አርሲ ሻላ ወረዳ ውስጥ ከ230 ኩንታል በላይ ካናቢስ የተባለ አደንዛዥ እፅ እንዲወገድ ተደረገ በምዕራብ አርሲ ዞን ሻላ ወረዳ በቁጥጥር ስር የዋለ ከ230 ኩንታል በላይ የሚገመት ካናቢስ የተባለ አደንዛዥ እፅ እንዲወገድ መደረጉን የምዕራብ አርሲ ዞን ፖሊስ መምሪያ አስታዉቋል።የምዕራብ አርሲ ዞን ዋና መምሪያ አዛዥ ረዳት ኮሚሽነር ዶ/ር ደረጄ ኢተና በሻላ ወረዳ በተለያዩ ከህብረተሰቡ በተሰጠ ጥቆማ 230 ካናቢስ ከፍተኛ አደንዛዥ እፅ በቁጥጥር ስር የዋለ መሆኑን ተናግረዋል:: በአርሲ ዞን እንደ ሻላ ያሉ ጥቂት ወረዳ ውስጥ አርሷአደሩ ከበቆሎ እና ከማሽላ ምርቶች ጋር አደንዛዥ እፅን እንደሚያመርት የጠቀሱት ኃላፊው ህብረተሰቡ በተለያዩ ጊዜያት መድረክ በመፍጠር አስፈላጊውን የግንዛቤ ማስጨበጫ  ትምህርት በመስጠት የምርቱን ስፋት በሂደት መቀነሱን ተናግረዋል። የአደንዛዥ እፅ ንግድ እና ዝውውር የተደራጀ የቡድን ሰንሰለት ያለው በመሆኑ በከፍተኛ ገንዘብ በመደለል በድብቅ የሚመረት የሚደረግ ቢሆንም የተለያዩ የፀጥታ አካላት እና ተቋማት ጋራ በመስራት የአደንዛዥ እጹን በቁጥጥር ስር ማዋሉን ገልፀዋል።በቅርቡ በተደረገ የተቀናጀ አሰሳ በሻላ ወረዳ ላይ አደንዛዥ እፅ በቁጥጥር ስር ውሎ እንዲወገድ መደረጉን ገልፀዋል። አደንዛዥ እፅ የወጣቶችን አዕምሮ ለወንጀል ድርጊት የሚያነሳሳና ሀገር ተረካቢ የሆነውን ወጣት ለሞራል መላሸቅ እንዲገጥመው እና ለከፍተኛ የአዕምሮ ችግር የሚያገልጥ በመሆኑ የአደንዛዥ እፅ ዝውውር እና ንግድ ላይ ከመስራት ባሻገር በዚህ ተግባራት የተሰማሩ በርካታ ግለሰቦችን ለፍትህ ማቅረብ እንደሚያስፈልግ ረ/ኮሚሽነር ደረጄ ኢተና ጨምረው ለብስራት ሬድዮና ቴሌቭዥን ተናግረዋል። በምህረት ታደሰ #ዳጉ_ጆርናል
Показать все...
👍 16👏 4 1😁 1
የኬንያ አየር መንገድ በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ በሰራተኞቼ ላይ ተፈፅሟል ያለውን እስር ተቃወመ የኬንያ አየር መንገድ የዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ጦር ሰራተኞቼ እንዲፈቱ ፍርድ ቤት ቢወስንም ካለፈው ሳምንት ጀምሮ ሁለት ሰራተኞቹን በቁጥጥር ስር አውሏል ሲል ከሷል። ሁለቱ የአየር መንገዱ ሰራተኞች በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ወታደራዊ መረጃ ክፍል ባለፈው አርብ በቁጥጥር ስር የዋሉ ሲሆን “በጣም ጠቃሚ” ጭነት ላይ ያለ የጉምሩክ ሰነድ ጠፍተዋል በሚል ነው ሲል የኬንያ አየር መንገድ በመግለጫው ገልጿል። አየር መንገዱ ጭነቱን ወደ ኪንሻሳ ያላነሳው ባልተሟላ ሰነድ የተነሳ ነው ብሏል። "የኬንያ አየር መንገድ የጭነት ንብረቱ ያልተሟላ ሰነድ ስለ መኖሩ ለወታደራዊ መኮንኖች ለማስረዳት የተደረገው ጥረት ሁሉ ከንቱ ሆኖ ተገኝቷል" ሲል አክሏል። ወታደራዊ መኮንኖቹ የኬንያ ኤምባሲ ባለስልጣናት እና የአየር መንገዱ ቡድን ለአጭር ጊዜ ሁለቱን ሰዎች እንዲጎበኟቸው የተፈቀደላቸው እስከ ማክሰኞ ድረስ ብቻ ነው። ሐሙስ እለት የኬንያ አየር መንገድ እንደገለፀው ፍርድ ቤት ሰራተኞቹ ላክ ምርመራ እንዲጥል በመወስን ከእስር እንዲፈቱ የቀረበውን ጥያቄ ተቀብሏል። "ፍርድ ቤቱ ትእዛዝ ቢሰጥም የወታደራዊ መረጃ ክፍል አሁንም በድብቅ እንደያዛቸው ይገኛል፣ ሆኖም እነዚህ በወታደራዊ መረጃ ተቋም ውስጥ የታሰሩ ሰላማዊ ሰዎች ናቸው" ሲል አየር መንገዱ አክሎ ተናግሯል። በቁጥጥር ስር በዋሉበት ወቅት የሰራተኞቹ ስልኮች መያዛቸውን የኬንያ አየር መንገድ ገልጿል። የተጠቀሰው ጭነት ምን እንደያዘ ግልፅ ያልተደረገ ሲሆን ከዲሞክራቲክ ኮንጎ ባለስልጣናት ዘንድ በጉዳዩ ላይ እስካሁን የተሰጠ አስተያየት የለም ። በስምኦን ደረጄ #ዳጉ_ጆርናል
Показать все...
👍 5🔥 1
የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት 244 የስነምግባር ጥሰት የፈጸሙ ሰራተኞቹን መቅጣቱን እና በህግ ተጠያቂ ማደረጉን ገለፀ 👉 አገልግሎቱ አመራሮቹ እና ለሙስና ተጋላጭ የሆኑ ሰራተኞቹ ሀብታቸዉን እንዲያስመዘግቡ አድርጓል። የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎትከዚህ በፊት ይነሳበት የነበረዉን የሙስና ተግባር ለመከላከል የተለያዩ ለዉጦችን እየከወንኩኝ እገኛለሁ ማለቱን ብስራት ሬዲዮና ቴሌቪዥን ሰምቷል። ለዚህም በማሳያነት በባለፉት ዘጠኝ ወራት ያከወናቸዉን ተግባራት በዛሬዉ እለት ይፋ አድርጓል። በተመሳሳይ የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት የስነምግባር ጥሰት የፈጸሙ 244 ሰራተኞቹን ከስራ እንዲታገዱ ፣ ከሀላፊነት እንዲነሱ እና በህግ እንዲጠየቁ ማድረጉንም አሳዉቋል። አገልግሎቱ ይህንን ያለዉ በዛሬዉ እለት የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት የሕግ እና ፍትሕ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የ የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት የ2016 በጀት አመት የዘጠኝ ወራት የስራ አፈጻጸምን በገመገመበት ወቅት ነዉ። የአገልግሎት አሰጣጡን ለማዘመን የኢ - ፓስፖርት (E-passport) ለመቀየር የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን እየከወነ መሆኑንም ብስራት ከሪፖርቱ ሰምቷል። በተመሳሳይ በዉጪ የሚታተመዉን ፓስፖርት በሀገር ዉስጥ ለማድረግ የዲዛይን ስራዎች ተጠናቅቀዋል የተባለም ሲሆን ህትመቱን ከሚሰራዉ ተቋም ጋር ዉል መታሰሩን እና ህትመቱን በአጭር ጊዜ ዉስጥ ለመጀመር ማቀዱንም ይፋ አድርጓል። ተቋሙ የጸጥታ ችግር ባለባቸዉ ኦሮሚያ እና አማራ ክልሎች ስራዎቹን ለመከወን እንዳልቻለ የገለጸ ሲሆን በአንጻሩ በትግራይ ክልክ ተቋርጦ የነበረዉን አገልግሎት ለማስጀመር የዳሰሳ ጥናት መስራቱን አስታዉቋል። በበረከት ሞገስ #ዳጉ_ጆርናል
Показать все...
👍 14👏 6🔥 2
የሜክሲኮ የምግብ አቅራቢ የአይጥ መረቅን ከ50 ዓመታት በላይ ለደንበኞቹ ሲያቀርብ መቆየቱን አስታወቀ በሜክሲኮ ሜርካዶ ሪፐብሊካ ደ ሳን ሉዊስ ፖቶሲ በሚሰኘው ገበያ ውስጥ በርካታ ነገሮችን ፈልጎ ማግኘት ይቻላል፣ ነገር ግን ከሁሉም በላይ ልዩ የሆነው የአይጥ ስጋን በመሸጥ የሚታወቅ የቆየ የምግብ አቅራቢ ድርጅት ታዋቂ ነው። ለበርካታ የዓለም ህዝብ የአይጥ ስጋ በፍፁም የማይለመድ እና ነውር ቢሆንም በሜክሲኮ ሳን ሉዊስ ፖቶሲ ክልል ውስጥ ግን ለየት ያለ ጣዕሙ እና ለመድኃኒትነት ይውላል በሚል ለረጅም ዓመታት ጥቅም ላይ ውሏል። ይሁን እንጂ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ የአይጥ ሥጋ የሚሸጡባቸው ሱቆች እና አከፋፋዮች ከአካባቢው ገበያ እየጠፉ ይገኛል። በሜርካዶ ሪፑብሊካ ደ ሳን ሉዊስ ፖቶሲ ውስጥ ግን አንዱ አከፋፋይ አሁንም ሁለቱንም ማለትን ጥሬ የአይጦች ስጋ እና የአይጥ መረቅ ከተለያዩ አትክልቶች እና ቅመማ ቅመም ጋር አዋህዶ መሸጡን ቀጥሏል። እያንዳንዱ የአይጥ መረቅ አንድ ሙሉ ሳህን የሚይዘው  በ100 የሜክሲከ ፔሶ ወይም በ5.80 የአሜሪካን ዶላር ዋጋ ተቆርጦለታል።በሜርካዶ ሪፑብሊካ የመጨረሻው የአይጥ ስጋ ሻጭ ሆሴ ሬሜዲዮስ ሄርናንዴዝ "ካሚሎ" በመባልም የሚታወቅ ሲሆን በቅርቡ ከዚህ ዓለም በሞት ከተለየችው ወላጅ እናቱ ይህንኑ ንግድ ወርሷል። በአንድ ወቅት በገበያው ውስጥ በደርዘን የሚቆጠሩ የአይጥ ስጋ ሻጮች እንደነበሩ ያስታውሳል፣ ነገር ግን ሁሉም ጡረታ ወጥተዋል አልያም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል። አሁን ላይ በገበያው ውስጥ ብቸማ አቅራቢ ሆኖ ቀጥሏል። ስራው እየተቀዛቀዘ በርካቶች ከዘርፉ ቢወጡን በቅርብ ጊዜ ውስጥ የቤተሰብን ንግድ ለመተው እቅድ የለኝም ሲል ይናገራል። ይህው የቤተሰቡ ንግድ ለ52 ዓመታት ዘልቋል። በተቻለም መጠን ለረጅም ጊዜ እንዲቆይ ለማድረግ የአቅሜን ያህል መስራቴን እቀጥላለሁ ሲል ይደመጣል። ካሚሎ የሚያቀርበውን የአይጥ ሾርባ ለማዘጋጀት  በሳን ሉዊስ ፖቶሲ ዙሪያ ካሉ የከተማ አካባቢ እና በዙሪያው ክሚገኙ ገጠራማ ስፍራዎች ተይዘው ይመጣሉ። የአይጥ ሥጋ በተለይ የደም ማነስ፣ የስኳር በሽታ ወይም ካንሰር ላለባቸው ሰዎች ጠቃሚ ሲሆን የሰውነትን በሽታ የመከላከል አቅምን ለማጠናከር እና የምግብ ፍላጎትን ለመጨመር ይረዳል ተብሎ በአካባቢው ማህበረሰብ ዘንድ ይታመናል። በሜርካዶ ሪፑብሊካ ደ ሳን ሉዊስ ፖቶሲ ውስጥ በሚገኘው ካሚሎ ሁለቱንም የአይጥ መረቅ በ100 ፔሶ የሚሸጥ ሲሆን ጥሬ አይጥ ገዝተው ቤት ይዘው ለሚሄዱ በ90 ዋጋ ይቀርባል።የስጋውን ጣዕም በትክክል ለማሟላት በአትክልቶችና ቅመማ ቅመሞች ለማብሰል ይመክራል ሲሉ የሬስቶራንቱ ባለሙያዎች ይናገራሉ። በስምኦን ደረጄ #ዳጉ_ጆርናል
Показать все...
😁 24👍 13🤬 12😱 4👎 3🤯 3🤔 2 1
🤯 5
ሀሰተኛ የጋብቻ ሰርተፍኬት እና መታወቂያ በመያዝ አገልግሎት ለማግኘት የሞከረው ግለሰብ በቁጥጥር ስር  ዋለ ረቡዕ ሚያዚያ 16/2016ዓ.ም  በየካ ክፍለ ከተማ  በሀሰተኛ  ማስረጃ  አገልግሎት  ለማግኘት የሞከሩ አራት ደንበኞች እና ባለሙያዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን  የአዲስ አበባምዝገባ እና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ አስታውቋል፡፡ በየካ ክ/ከተማ ወረዳ 6 የሲቪል ምዝገባ እና የነዋሪነት አገልግሎት ጽ/ቤት ሁለት ሃሰተኛ ሰነድ ይዘው አገልግሎት ለማግኘት የቀረቡ ተገልጋዮችን ጨምሮ  ሌሎች ሁለት በወንጀል ተግባሩ የተጠረጡ ግለሰቦች በፖሊስ ቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ እየተደረገባቸው እንደሚገኝ የአዲስ አበባ ሲቪል ምዝገባ እና የነዋሪነት አግልግሎት ኤጀንሲ  ዋና ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ዮናስ ዓለማየሁ በተለይም ለብስራት ሬዲዮ እና ቴሌቪዥን ተናግረዋል  ። አንደኛው ግለሰብ ሃሰተኛ የመታወቂያ እና ያላገባ ህገ ወጥ ማስረጃ በመያዝ ለጽ/ቤቱ ሰራተኛ ጉቦ በመስጠት አገልግሎት ለማግኘት የሞከረ ሲሆን   ከዓመታት በፊት ማስረጃውን በሌላ አገናኝ ደላላ ያገኘው መሆኑን ተረጋግጧል፡፡ በመሆኑም  ደላላው እና  ሁለተኛው ተጠርጣሪ የቂርቆስ ክ/ከተማ ነዋሪነት መልቀቅያን አስመስሎ በማሰራት አገልግሎት ለማግኘት ሙከራ ሲያደርግ ሃሰተኛ ሰነዱን ካዘጋጀው አስመዝጋቢ የቤት ባለቤት ነዋሪ ግለሰብ ጋር በፖሊስ ቁጥጥር ስር ውለዋል። በአንደኛው ወንጀል የተጠረጠረው የጽ/ቤቱ ሰራተኛ ከዚህ ቀደም በወንጀል ተጠርጥሮ በኤጀንሲው ታግዶ የፖሊስ ምርመራ እየተደረገበት ያለ መሆኑ ተረጋግጧል፡፡  ሁለተኛው  ድርጊት ሃሰተኛ መልቀቅያ በቂርቆስ ክ/ከተማ ወረዳ 8 ነዋሪነት ስም አስመስሎ ለመገልገል ሲቀርብ በማስረጃው ላይ በጽ/ቤቱ ጥርጣሬ በማደሩ  የቂርቆስ ክ/ክተማ የሲቪል ምዝገባ እና የነዋሪነት አገልግሎት ጽ/ቤት ጋር መረጃ በመለዋወጥ ድርጊቱ ለፖሊስ እንዲተላለፍ በየካ ክ/ከተማ ሲቪል ምዝገባ እና የነዋሪነት አገልግሎት  ጽ/ቤት መደረጉን አቶ ዮናስ ዓለማየሁ ጨምረውም ለብስራት ሬዲዮ እና ቴሌቪዥን ተናግረዋል። በኤደን ሽመልስ #ዳጉ_ጆርናል
Показать все...
👍 16 1
የበዓል ቅርጫ ቤትዎ ድረስ ብናመጣልዎትስ? አጋፔ online ቅርጫዎች ነን። ለገና በዓል እምነት የጣሉብን ደንበኞቻችን ሁሉ አስደስተናል!ለመጪው ፋሲካ ደግሞ ከቀድሞው በላይ ተዘጋጅተናል።የበዓል ቅርጫ በአቅራቢያዎ ካላገኙ የስራ ሁኔታዎ ለሊት ተነስቶ በቅርጫ ስራ ለመሳተፍ ካልፈቀደልዎ ሳይደክሙና እንቅልፎን ሳያጡ ድካምና ጊዜዎን ቆጥበን ማለዳ ከወፏ ዜማ ቀድመን ትኩስ ስጋ ከቤትዎ እናደርሳለን። ውጪ ሀገር ሆነው አገር ቤት ያሉ ቤተሰቦቾን በአውድ ዓመት ቅርጫ ሰርፕራይዝ ማድረግ ከፈለጉም ይዘዙን! ለመመዝገብ ☎️ 09-20-80-98-21 09-20-72-91-52 ወይም 0913552085 ይደውሉ፡፡ ለተጨማሪ መረጃ ደግሞ የቴሌግራም ገጻችንን ይቀላቀሉ፡፡ https://t.me/+HRT-JSbRFPQ3MzVk #ዳጉ_ጆርናል
Показать все...
👍 13 3
በጋዛ የጅምላ መቃብር መገኘቱን ተከትሎ ዩናይትድ ስቴትስ 'ግልጽ' ምርመራ እንዲደረግ እስራኤልን ጠየቀች ዋይት ሀውስ በእስራኤል ከበባ ከወደሙ የጋዛ ሆስፒታሎች የጅምላ መቃብሮች መገኘታቸውን ተለትሎ ከእስራኤል ባለስልጣናት በጉዳዩ ላይ ምላሽ እንደሚፈልግ አስታውቋል።ከ300 በላይ ሰዎች በእስራኤል ወታደሮች መገደላቸው የተረጋገጥው በካን ዮኒስ ናስር ሆስፒታል ተቀበሩ የተባሉ ከ300 በላይ ሰዎች እስካሁን ድረስ በመገኘታቸው ነው።በሰሜናዊው አል-ሺፋ ሆስፒታል ውስጥ ሌሎች የጅምላ መቃብሮችም ይገኛሉ። በዚህ ጉዳይ ላይ መልስ እንፈልጋለን ሲሉ የዩናይትድ ስቴትስ የብሔራዊ ደህንነት አማካሪ ጄክ ሱሊቫን ለጋዜጠኞች ተናግረዋል።በተጨማሪም ይህንን በጥልቀት እና በግልፅ መመርመር እንፈልጋለን ሲሉ አክለዋል።በሌላ በኩል የእስራኤል ጦር በኑሴይራት ውስጥ የሃማስ ‘ስናይፐር ሴል’ አጠፍቻለሁ ሲል አስታውቋል።የእስራኤል ጦር ሰሜናዊ እና ደቡባዊ ጋዛን የሚከፍለው በኔትዛሪም ኮሪደር አቅራቢያ በርካታ ተዋጊዎችን በመግደል እና ወታደራዊ መሠረተ ልማቶችን በማውደም በአካባቢው ጥቃት ማድረሱን ቀጥሏል። ወታደሮቹ በሰሜን በሻቲ የሚገኘውን የሃማስ ማስጀመሪያ ቦታዎችን በመምታታቸው በማዕከላዊ ጋዛ ኑሴይራት የስደተኞች ካምፕ ውስጥ የሚገኘውን የቡድኑን “ስናይፐር ሴሎች” አንዱን “በትክክለኛ የአየር ድብደባ” በማውደም ላይ መሆናቸውን ጦሩ አስታውቋል።በአጠቃላይ ባለፉት 24 ሰዓታት የእስራኤል ጦር በወሰደው ዘመቻ 30 የሃማስ ኢላማዎችን መምታቱንም አክሏል። በተመሳሳይ ጊዜ፣ የእስራኤል የመጨረሻ የጦር ማዕበል በሆነችው በራፋህ በሚገኝ መኖሪያ ቤት ውስጥ ተጠልለው የነበሩ ቢያንስ አምስት ሰዎችን መግደልን ጨምሮ በሲቪል ዜጎች ላይ ከባድ ጉዳት አድርሷል ሲል የፍልስጥኤሙ ዋፋ የዜና ወኪል ዘግቧል። በሰምሃል አለባቸው #ዳጉ_ጆርናል
Показать все...
👍 30💔 12😢 7🙏 3😁 2😱 2👎 1
ከኢትዮ ቴሌኮም እውቅና ውጪ በህገወጥ መንገድ ወደ ውጪ ሀገር ስልክ ሲያስደውል የነበረ ግለሰብ ተያዘ በሀረሪ ክልል ጀኒላ ወረዳ ጆራ ጀርባ ተብሎ በሚጠራው ስፍራ ከኢትዮ ቴሌኮም እዉቅና ውጪ በህገወጥ መንገድ  ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም ወደ ውጪ ሀገር በማስደወል ህገ ወጥ ተግባር ሲፈፅም የነበረው ግለሰብ ከግብራበሮቹ ጋር ከነ ቁሳቁሶቹ በቁጥጥር ስር መዋሉን የሀረሪ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን አስታውቋል። የሀረሪ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን የጅኒላ ወረዳ ፖሊስ አዛዥ ኮማንደር ሙፍቱ ከድር ለብስራት ሬዲዮና ቴሌቪዥን እንደተናገሩት  በተጠርጣሪነት የተያዘው ግለሰብ ከኢትዮ ቴሌኮም እውቅና ውጪ የስልክ መስመሮችን በመዘርጋት የኢትዮ ቴሌኮምን በከፍተኛ ደረጃ የሚጎዳ እና ኪሳራ ላይ የሚጥል ተግባር ፈፅሟል። ግለሰቡ በድብቅ ሰዎችን ወደ ውጪ ሀገር በማስደወል የግል ጥቅሙን በህገ ወጥ መንገድ ሲያካብት እንደነበር እና በዚህ ተግባር ላይ እያለም እጅ ከፍንጅ መያዙን ተናግረዋል።ለዚህ ተግባር አገልግሎት እንዲሁም በህገወጥ ተግባር ወደ ሀገር ውስጥ ያስገባቸው ብዛት ያላቸው የዋይፋይ ሳጥኖች፣ የተለያዩ ኬብሎች ፣ፍላሾች ፣ አንቴናዎች፣ሲም ካርዶች እና ሞባይሎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ገልፀዋል። በዚህ ተግባር በተባባሪነት ከአንደኛው ተጠርጣሪ ጋር ግንኙነት ያላቸው ሌሎች አራት ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ እየተጣራባቸው እንደሆነ እና በቀጣይ ጊዜያት የምርመራ መዝገባቸው ተጠናቆ ለሚመለከተው የፍትህ አካል እንደሚላክ ኮማንደር ሙፍቱ ከድር ጨምረው ለብስራት ሬድዮና ቴሌቭዥን ተናግረዋል። በምህረት ታደሰ #ዳጉ_ጆርናል
Показать все...
👍 17 7😁 6👏 3😢 2
የቲክ ቶክ ቻይና ዋና ድርጅት መተግበሪያውን የመሸጥ እቅድ እንደሌለው አስታወቀ የቲክ ቶክ የቻይና እናት ኩባንያ ባይትዳንስ ዩናይትድ ስቴትስ በጣም ተወዳጅ የሆነውን የቪዲዮ መተግበሪያ እንዲሸጥ ወይም በአሜሪካ ውስጥ እንዲታገድ የሚያስገድድ ሕግ ካወጣች በኋላ ንግዱን የመሸጥ ፍላጎት የለኝም ሲል ኩባንያው አስታውቋል። "ባይት ዳንስ ቲክ ቶክን ለመሸጥ ምንም እቅድ የለውም" ሲል ኩባንያው በያዘው የማህበራዊ ሚዲያ መድረክ ቱቲያኦ ላይ በይፋ መለያው አጋርቷል። ቴክቶክ ከመገናኛ ብዙሃን አስተያየት እንዲሰጥ ለቀረበለት ጥያቄ ወዲያውኑ ምላሽ ከመስጠት ተቆጥቧል። በዚህ ሳምንት መጀመሪያ ላይ ቲክ ቶክ “ህገ-መንግስታዊ ያልሆነውን” ህግ በፍርድ ቤት እንደሚቃወም ተናግሯል። የባይትዳንስ መግለጫ የመጣው ቲክ ቶክን ከሚሰጠው ስልተ ቀመር ውጭ ለመሸጥ አማራጮችን እያፈላለገ መሆኑን መገናኛ ብዙሃን ከዘገቡ በኋላ ነው። ባይትዳንስ ቲክ ቶክን እንደሚሸጥ የውጭ መገናኛ ብዙሃን እያጋሩት ያሉት ዘገባዎች እውነት አይደሉም ብሏል ኩባንያው። ባይት ዳንስ ቲክ ቶክን ለመሸጥ ምንም እቅድ የለዉም ”ሲል ኩባንያው በማህበራዊ ሚዲያ ፕላትፎርም ቱቲያኦ ላይ በይፋ መለያው ላይ ለጥፏል። ቲክቶን በአሜሪካ የማገድ እርምጃ በዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን ረቡዕ እለት ተፈርሟል። ቲክ ቶክ የተጠቃሚውን መረጃ ለቻይና መንግስት ጋር ሊያጋራ ይችላል በሚል ስጋት በአሜሪካ የተወነጀለ ሲሆን ኩባንያው ግን ውንጀላውን የሀሰት ሲል አድርጓል። በስምኦን ደረጄ #ዳጉ_ጆርናል
Показать все...
👍 31 4🤔 2
ኬቨን ደ ብረይነ በፕሪሚየር ሊጉ የመጀመሪያውን የግምባር ኳስ በመግጨት አስቆጥሯል 😲 ሁሉንም ማሳካት ተችሎታል... ብራይተን 0-3 ማን ሲቲ ጎሎቹን ለመመልከት 👉 @mikoethio #ዳጉ_ጆርናል
Показать все...
👍 19🔥 7👏 2😁 2👎 1
👍 2🥰 1😱 1
የቡርኪናፋሶ ጦር በ223 ሰዎች ላይ የበቀል እርምጃ መውሰዱን የሰብዓዊ መብት ድርጅት አስታወቀ በተያዘው አመት ከ220 በላይ ንፁሀን ዜጎች፣ ቢያንስ 56 ህፃናት በቡርኪናፋሶ ጦር በአንድ ቀን ተጨፍጭፈዋል ሲል የሰብዓዊ መብት ተሟጋቹ ሂውማን ራይትስ ዎች አስታውቋል። በሰራዊቱ ላይ የተፈፀመው ጥቃት ለመበቀል ጦረ በሶሮ መንደር 179 ሰዎች ሲገድል 44 ሌሎች  ሰዎች ደግሞ በአቅራቢያው በሚገኘው ኖንዲን መንደር ውስጥ መገደላቸውን የመብት ተሟጋች ቡድሙ ያደረገው ምርመራ አረጋግጧል።የጅምላ ግድያው "በሀገሪቱ ከአስር አመታት ወዲህ ከተከሰቱት እጅግ የከፋ የጦር ሰራዊት ጥቃት" ሲል ገልጿል። የቡርኪናፋሶ ባለስልጣናት በሪፖርቱ ላይ አስተያየት እስካሁን አልሰጡም። ባለፈው ወር የህዝብ አቃቤ ህግ አሊ ቤንጃሚን ኩሊባሊ ከጅምላ ግድያው ጀርባ ያለውን ቡድን ለመለየት ምስክሮች እንዲቀርቡ ጠይቀዋል። በወቅቱ የሟቾችን ቁጥር 170 አድርሶታል። ከጥቃቱ የተረፉ መንደርተኞች ለሂውማን ራይትስ ዎች እንደተናገሩት በአካባቢው የሚንቀሳቀሱ ታጣቂዎች እንዳለፉ  ከ30 ደቂቃ በኋላ ወታደራዊ ኃይሉ ወደ ኖንዲን መንደር መውረዱን ተናግረዋል። ወታደሮቹ ከቤት ወደ ቤት እየሄዱ ነዋሪዎችን ከቤታቸው እያባረሩ ወንጀሉን ፈፅመዋል ሲሉ ተደምጠዋል። በመቀጠል 5 ኪሜ ርቀት ላይ ወደምትገኘው ሶሮ መንደር ደርሰው ከአንድ ሰአት በኋላ በመንደሩ ሰዎች ላይ ተኩስ መክፈታቸውን ከጥቃቱ  የተረፉት እማኞች ገልጸዋል። በሁለቱም መንደሮች ወታደሮቹ ለመደበቅ ወይም ለማምለጥ በሞከሩ ሰዎች ላይ መተኮሳቸውን እማኞቹ አክለዋል። የጅምላ ግድያው በወታደሮች የተወሰደው በታጣቂ ቡድን ለተፈፀመባቸው ጥቃት የበቀል እርምጃ ነው ተብሎ ታምኖበታል። የመንደሩ ነዋሪዎች የታጠቁ ተዋጊዎችን ይረዱ ነበር በሚል ተከሰዋል። በሰሜናዊ ያትንጋ ግዛት አቅራቢያ በሚገኝ የጦር ካምፕ ላይ ታጣቂ ቡድኖች ጥቃት ሰንዝረዋል።የሂዩማን ራይትስ ዎች ዋና ዳይሬክተር ቲራና ሃሰን እንዳሉት በኖንዲን እና በሶሮ መንደር የተፈፀመው እልቂት የቡርኪናፋሶ ወታደሮች በፀረ-ሽምቅ ዘመቻቸው በሰላማዊ ሰዎች ላይ የፈፀሙት የቅርብ ጊዜ የጅምላ ግድያ ነው ሲሉ ተደምጠዋል። በአበረ ስሜነህ #ዳጉ_ጆርናል
Показать все...
👍 15👎 14😢 4 3🤩 1
አቶ ታዬ ደንደአ የፀረሰላም ኃይሎችን በመደገፍ እና የጦር መሳሪያ ይዞ በመገኘት ወንጀል ክስ ተመሰረተባቸው የሰላም ሚኒስትር ዴዔታ የነበሩት አቶ ታዬ ደንደአ የፀረሰላም ኃይሎችን በመደገፍና ጦር መሳሪያ ይዞ በመገኘት ወንጀል ክስ ተመሰረተባቸው። ክሱ የተመሰረተው በፌዴራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ 1ኛ ሕገ-መንግስትና ሕገ-መንግስት ሥርዓት ላይ የሚፈጸሙ ወንጀል ጉዳዮችን በሚመለከተው ችሎት ነው። የፍትሕ ሚኒስቴር የተደራጁና ድንበር ተሻጋሪ ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ዐቃቤ ሕግ በተከሳሽ ታዬ ደንደአ ላይ ሶስት ክሶችን አቅርቧል። በ1996 ዓ.ም የወጣውን የወንጀል ሕግ አንቀጽ 251/ሐ እና አንቀጽ 257/ሰ ስር የተመላከተውን ድንጋጌ እና የጦር መሳሪያ አዋጅን መተላለፍ የሚል ክስ አቅርቦባቸዋል። በክሱ ላይ እንደተመላከተው÷ተከሳሹ የሰላም ሚኒስትር ዴዔታ ሆነው ሲሰሩ የሀገርን፣ የመንግስትንና የህዝብን ደህንነት ማረጋገጥ ሲገባቸው ይህን ወደጎን በመተው  ፀረሰላም ኃይሎችን የሚደግፉ የፕሮፖጋንዳ መልዕክቶችን በማስተላለፍ በስማቸው በተከፈተ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ላይ ድጋፍ የሚገልጹ መልዕክቶችን  ሲያስተላልፉ ነበር የሚል ነው፡፡ እንዲሁም ፍቃድ ሳይኖራቸው የጦር መሳሪያ አዋጁን በመተላለፍ በታህሳስ 1 ቀን 2016 ዓ.ም  ከረፋዱ 5 ሰዓት  ላይ በልደታ ክ/ከ ወረዳ 6  በሚገኝ መኖሪያ ቤታቸው ውስጥ በተደረገ ብርበራ አንድ ታጣፊ ክላሽን ኮቭ  መሳሪያ ከ2 ክላሽ ካዝና  እና ከ60 ጥይት ጋር ይዘው መገኘታቸው ተጠቅሶ ክስ ቀርቦባቸዋል። ተከሳሽ አቶ ታዬ ደንደአ በአራት ጠበቆቻቸው ተወክለው ችሎት ቀርበው የክስ ዝርዝሩ ተነቦላቸዋል። ክሱ ከተነበበ በኋላ በጠበቆቻቸው በኩል የዋስትና መብታቸው እንዲከበርላቸው ጥያቄ ቀርቧል። ዐቃቤ ሕግ በበኩሉ የዋስትና ጥያቄያቸውን ሊያስከለክሉ የሚችሉ ነጥቦችን ጠቅሶ ተከራክሯል። ሰበር ሰሚ ችሎት ዋስትናን በልዩ ሁኔታ ሊከለክል የሚችልባቸው ነጥቦች ማለትም በተደራራቢ ክስ መከሰሳቸውን እና የተከሰሱት ድንጋጌ ከፍ ያለ ቅጣት የሚያስጥል ከሆነ ዋስትና ሊያስከለክል ይችላል በማለት ተከራክሯል። የተከሳሽ ጠበቆችም ሰበር ሰሚ ችሎት ያስቀመጣቸው ዋስትናን ሊያስከለክሉ የሚችሉ ድንጋጌዎች ተከሳሹ ላይ በቀረበው ክስ የሚመለከቱ አለመሆናቸው ጠቅሰው መልስ ሰጥተዋል። በተጨማሪም  ህጻን ልጃቸውን ጥለው የታሰሩ መሆናቸውን ጠቅሰው÷ በሕገ-መንግስቱ የተቀመጠው የሕጻናት መብት ታሳቢ ተደርጎ በውጭ ሆነው እንዲከታተሉ ጠይቀዋል። አቶ ታዬ ደንደአ በበኩላቸው÷በቁጥጥር ስር ሲውሉ በራሳቸው እና በቤተሰባቸው ላይ የሰብዓዊ መብት ጥሰት እንደደረሰባቸው ገልጸው አቤቱታ በቃል አቅርበዋል። ምርመራው ታሕሳስ 24 ማለቁንና ዘግይቶ ክስ መቅረቡንም ተቃውመዋል። ዐቃቤ ሕግ ሌሎች ምርመራዎች ሲከናወኑ መቆየታቸውን ገልጾ መልስ ሰጥቷል። ፍርድ ቤቱም  በአያያዝ ላይ ያቀረቡትን የመብት ጥያቄ በሚመለከት በጽሑፍ በዝርዝር ማቅረብ እንደሚችሉ ገልጿል። ዋስትናውን በሚመለከት መርምሮ ብይን ለመስጠትም ለሚያዝያ 24 ቀን 2016 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል። Via FBC #ዳጉ_ጆርናል
Показать все...
👎 45👍 19 1😁 1
👍 1
ተዋናይ አማኑኤል ሃብታሙ ዛሬ ጠዋት ከቤተሰብ እና ጠበቃው ጋር መገናኘቱ ተዘገበ ተዋናይ አማኑኤል ሃብታሙ "እብደት በሕብረት" የተሰኘ የአንድ ሰው ቴአትሩን ለማሳየት ወደ እስራኤል አገር ሊጓዝ ሲል ከአዲስ አበባ ኤርፖርት በፖሊሶች መያዙ ይታወሳል።በአዲስ አበባ ፖሊስ መምሪያ ውስጥ ታስሮ የሚገኘው ተዋናዩ የቅርብ ወዳጅ የሆነው ያሬድ ሹመቴ እንደገለጸው አማኑኤል ሃብታሙ "እጁ ከተያዘበት ሰዓት አንስቶ የተከሳሽነት ቃል ሳይሰጥ እንዲሁ በእስር ላይ" እንደሚገኝ ቤተሰቦቹን ዋቢ አድርጎ ጽፏል። ይኹን እንጂ የቤተሰብ ጠበቃ የማግኘት መብቱ ተጠብቆለት ከቤተሰብ እና ከጠበቃ ጋር ዛሬ ጠዋት ሊገናኝ መቻሉን እና "በመልካም" ሁኔታ ላይ መኾኑ ተመልካቷል። በሕጉ መሰረት ወደ ቀጣይ ሕጋዊ ሂደቶች ለማምራት እስከ ነገ የሚሆነውን ለማየትም ቤተሰቦቹ እየተጠባበቁ ነው ተብሏል።  እያዩ ፈንገስ የአንድ ሰው ቴያትር 'ቧለቲካ' የተሰኘው ምዕራፉ ለዕይታ ከቀረበ ከእጭር ጊዜ በኋላ ማለትም ከጥር 2 ቀን 2016 ጀምሮ የመንግስት የፀጥታ አካላት ለዓለም ሲኒማ የስራ ሀላፊዎች ባስተላለፉት ትእዛዝ  ለህዝብ እንዳይታይ መከልከሉ አይዘነጋም። Via Addis Maleda #ዳጉ_ጆርናል
Показать все...
👍 35👎 11🤔 7🤬 7😁 3😢 2
ጀርመን በፍቅር ስም ሲያጭበረብር የነበረ የናይጄሪያ የማፍያ ቡድን አባላትን በቁጥጥር ስር ማዋሏን አስታወቀች የጀርመን ፖሊስ በማፍያ ቡድን ውስጥ ከፍተኛ  በፍቅር ስም የማጭበርበር ድርጊቶችን ያቀነባበሩ 11 ናይጄሪያውያንን በቁጥጥር ስር አውሏል። ይህው የብላክ አክስ የተሰኘው ቡድን በአለም አቀፍ ደረጃ "በርካታ የወንጀል ድርጊቶች" ውስጥ ይሳተፋል ሲል የባቫርያ ፖሊስ ባወጠው መግለጫ ገልጿል። በጀርመን ውስጥ ድርጅቱ የሚያተኩረው በፍቅር ቀጠሮ ማጭበርበር እና በገንዘብ ማጭበርበር ላይ ነው ሲል ሃይሉ አክሏል። መግለጫው “የውሸት መታወቂያዎችን በመጠቀም አጭበርባሪዎቹ ለምሳሌረ ለማግባት ፍላጎት እንዳላቸው በማሳየት ለተጨማሪ ግንኙነት በተደጋጋሚ በተለያዩ ሰበቦች ገንዘብ ይጠይቃሉ” ብሏል።በአለም አቀፍ ደረጃ የወሮበሎች ቡድን ዋና ዋና የስራ ቦታዎች "የሰዎች ህገወጥ ዝውውር፣ ማጭበርበር፣ ህገወጥ የገንዘብ ዝውውር፣ የወሲብ ንግድ እና የአደንዛዥ ዕፅ ዝውውር" ናቸው። በቁጥጥር ስር የዋሉት ተጠርጣሪዎች ሁሉም የናይጄሪያ ዜግነት ያላቸው እና ከ29 እስከ 53 ዓመት እድሜ ያላቸው እንደሆኑ ተመላክቷል። ከሁለት አመት በላይ የፈጀውን የፖሊስ ምርመራ ተከትሎ በተያዘው ሳምንት ማክሰኞ በባቫሪያ ክልል በተደረገው የፖሊስ ዘመቻ ግለሰቦቹ በቁጥጥር ስር ውለዋል ። እ.ኤ.አ. በ 2021 በብላክ አክስ ላይ በተደረገው ምርመራ ቡድኑ ናይጄሪያ ውስጥ ፖለቲካ ውስጥ ዘልቆ በመግባት የግድያ ዘመሻ እንደፈጸመ የሚያሳይ ማስረጃ መገኘቱን መገናኛ ብዙሃን ዘግበው የነበረ ቢሆን የተወሰደበት እርምጃ ግን የለም። በቅድስት ደጀኔ #ዳጉ_ጆርናል
Показать все...
👍 22 2😁 2👏 1
ከወላይታ ሶዶ - አዲስ አበባ የኤሌትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ ተሸካሚ ታወር ብረትን የሰረቀዉ ግለሰብ በእስራት ተቀጣ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በስልጤ ዞን  በሁልባራግ ወረዳ በዋጮ ሆቢሶ ቀበሌ ልዩ ስሙ ሰላም መሊቅ ተብሎ በሚጠራ አካባቢ ከወላይታ ሶዶ - አዲስአበባ የኤሌትሪክ ሀይል ማስተላለፊያ ተሸካሚ ታወር ብረትን የሰረቀዉ ግለሰብ በእስራት መቀጣቱን የስልጤ ዞን ፖሊስ መምሪያ አስታዉቋል። ነሰሩ ወርቀ - ነጋ የተባለው ግለሰብ  ዋሚያዚያ 05 ቀን 2016 ዓ.ም በግምት ከምሽቱ 3:00 ሰዓት በሚሆንበት ጊዜ ሆን ብሎ በህገወጥ መንገድ በአቋራጭ  ለመበልፀግ በማሰብ ንብረትነቱ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሆነ  ከወላይታ ሶዶ -ገለን ወደ አዲሰ አበባ የተዘረጋውን ዋና የኤሌክትሪክ ኃይል 400 ኪሎ ዋት ከፍተኛ የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ ታወር ሰርቆ እጅ ከፍንጅ መያዙን የስልጤ ዞን ፖሊስ መምሪያ ሕዝብ ግንኙነትና ሚድያ ጉዳዮች ድቪዥን ኃላፊ ኮማንደር ከድር  ኤርጎሻ ለብስራት ራዲዮና ቴሌቪዥን ተናግረዋል።                  ግለሰቡ ግምቱ እስከ 100 ሺህ ብር ሊያወጣ የሚችል የኤሌክትሪክ ሽቦ መሸከሚያ  ታወር ብረት ሰርቆ ለመውሰድ እያዘጋጀ እያለ  በአካባቢው ህብረተሰብ እጅ ከፍንጅ ተይዞ  ለሁልባራግ ወረዳ ፖሊስ ተላልፎ የተሰጠ ሲሆን ፖሊስም ተከሳሹንና የተሰረቀውን ንብረት በኢግዝቢትነት በመያዝ ቃል ከመቀበል ጀምሮ  አስፈላጊ ናቸው ብሎ ያመነባቸውን  ማስረጃዎች በማሰባሰብና ምርመራ  በማጣራት  መዝገብ  አደራጅቶ ለሁልባራግ ወረዳ  ዐቃቤ ህግ  አቅርቧል። ዐ/ህግም ተከሳሹ  በ1996  ዓ/ም  የወጣውን የኢፌዲሪ  የወንጀል  ህግ አንቀጽ  669(1)(ለ) ላይ የተደነገገውን በመተላለፉ በፈጸመው  የስርቆት ወንጀል ክስ መስርቶ ለሁልባራግ ወረዳ ፍ/ቤት አቅርቧል። ፍ/ቤቱም ከዐ/ህግ የቀረበለትን  ይህንን የስርቆት ወንጀል  ክስ ከተገቢ ማስረጃዎች ጋር አገናዝቦ ከመዘነ በኋላ  በተከሳሹ ላይ  የጥፋተኝነት ብይን ሰጥቷል። በዚህም መሠረት የሁልባራግ  ወረዳ  ፍ/ቤት  ሚያዚያ 16 ቀን 2016  ዓ/ም  ባስቻለው የወንጀል ችሎት ተከሳሹን ነስሩ ወርቀነጋ ላይ የ5 አምስት ዓመት ከ6 ወር ጽኑ  ወስኖበታል ሲሉ የስልጤ ዞን ፖሊስ መምሪያ ሕዝብ ግንኙነትና ሚድያ ጉዳዮች ድቪዥን ኃላፊ ኮማንደር ከድር  ኤርጎሻ ለብስራት ራዲዮና ቴሌቪዥን ተናግረዋል። በበረከት ሞገስ #ዳጉ_ጆርናል
Показать все...
👍 23😁 7👎 1👏 1🤬 1