ዳጉ-ጆርናል/Dagu-Journal
The best fiction is far more true than any journalism 📢 ተዓማኒ የመረጃ ምንጭ ፤ ለሙያው ስነምግባር ተገዢ በሆኑ ጋዜጠኞች ብቻ 👉 በፌስቡክ ገፆቻችን https://www.facebook.com/simon.dereje.56 👉 https://www.facebook.com/mik0Man
نمایش بیشتر📈 تحلیل کانال تلگرام ዳጉ-ጆርናል/Dagu-Journal
کانال ዳጉ-ጆርናል/Dagu-Journal (@zena24now) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 42 133 مشترک است و جایگاه 6 165 را در دسته اخبار و رسانهها و رتبه 772 را در منطقه أثيوبيا دارد.
📊 شاخصهای مخاطب و پویایی
از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 42 133 مشترک جذب کرده است.
بر اساس آخرین دادهها در تاریخ 03 ژوئیه, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر -322 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر -7 بوده و همچنان دسترسی گستردهای حفظ شده است.
- وضعیت تأیید: تأیید نشده
- نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 15.32% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 12.08% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب میکند.
- دسترسی پستها: هر پست به طور میانگین 6 457 بازدید دریافت میکند. در اولین روز معمولاً 5 091 بازدید جمعآوری میشود.
- واکنشها و تعامل: مخاطبان بهطور فعال حمایت میکنند؛ میانگین واکنش به هر پست 36 است.
📝 توضیح و سیاست محتوایی
نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاههای شخصی توصیف میکند:
“The best fiction is far more true than any journalism
📢 ተዓማኒ የመረጃ ምንጭ ፤ ለሙያው ስነምግባር ተገዢ በሆኑ ጋዜጠኞች ብቻ
👉 በፌስቡክ ገፆቻችን https://www.facebook.com/simon.dereje.56
👉 https://www.facebook.com/mik0Man”
به لطف بهروزرسانیهای پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 04 ژوئیه, 2026)، کانال همواره بهروز و دارای دسترسی بالاست. تحلیلها نشان میدهد مخاطبان بهطور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته اخبار و رسانهها تبدیل کردهاند.
در حال بارگیری داده...
| تاریخ | رشد مشترکین | اشارات | کانالها | |
| 05 ژوئیه | 0 | |||
| 04 ژوئیه | 0 | |||
| 03 ژوئیه | +2 | |||
| 02 ژوئیه | +4 | |||
| 01 ژوئیه | 0 |
| 2 | ቀጣይ ተፋላሚዎች
ፈረንሣይ ከ ሞሮኮ 🔥
#ዳጉ_ጆርናል | 3 213 |
| 3 | ፈረንሳይ ወደ ሩብ ፍፃሜው #WC2026
🇵🇾 Paraguay 0-1 France 🇫🇷
⚽️ Kylian Mbappe
FRANCE ARE THROUGH!
A classic it certainly was not, but France did enough to get the job done on a scorching evening in Philadelphia.
#ዳጉ_ጆርናል | 3 036 |
| 4 | መርጌታ ነን ገንዘብህን እናስመልሳለን በማለት ከ8 መቶ ሺህ ብር በላይ ያጭበረበሩ ወንድማማቾች በቁጥጥር ሥር ዋሉ
በምስራቅ ጎጃም ዞን አስተዳደር በሉማሜ ከተማ ነዋሪ የሆኑት ስመኝ አባትነህ እና ያዛቸው አባትነህ የተባሉት ወንድማማቾች በአርባ ምንጭ ከተማ በቡና ንግድ ስራ ከተሰማራ ግለሠብ ላይ ከፍተኛ ገንዘብ አጭበርብረው መውሠዳቸውን የሉማሜ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽ/ቤት አስታውቋል።
የከተማ አስተዳደሩ ፖሊስ ጽ/ቤት አዛዥ ኢንስፔክተር በድሉ መልሠው እንደገለጹት አካሉ መለሰ የተባለው ተበዳይ ቡና ያስረከበው ደንበኛ ብሩን ሊመልስለት ባለመቻሉ ተጠርጣሪወች የሐሰት ሰነድ በማዘጋጀት መርጌታ ነን ያልተመለሠልህን ገንዘብ እናስመልሳለን በማለት አታለው መውሠዳቸውን ተናግረዋል።
ፖሊስ በተጠርጣሪወች ላይ ክትትል በማድረግ በቁጥጥር ሥር አውሎ የተጭበረበረው ገንዘብ በከተማ አስተዳደሩ ገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ጽ/ቤት በግዜዊነት ኤግዚቢት ሆኖ እንዲቆይ በማድረግ አጭበርባሪ ግለሠቦች ተገቢውን ቅጣት እንዲያገኙ በትኩረት እየሠራ መሆኑን ፖሊስ አዛዡ ተናግረዋል።
#ዳጉ_ጆርናል | 4 173 |
| 5 | ሞሮኮ ካናዳን በማሸነፍ ሩብ ፋጻሜውን ተቀላቀለች
በ23ኛው የዓለም ዋንጫ የ16ቱ የጥሎ ማለፍ ጨዋታ ሞሮኮ አዘጋጇን ካናዳ 3 ለ 0 በማሸነፍ ሩብ ፋጻሜውን ተቀላቅላለች፡፡የሞሮኮን የማሸነፊያ ግቦች ኡናሂ (ሁለት) እና ራሂሚ ከመረብ አሳርፈዋል።
#ዳጉ_ጆርናል | 4 064 |
| 6 | የኬፕቨርዲ አሰልጣኝ ስጦታዎች
ጨዋታው ከመጀመሩ በፊት ወደ ተቃራኒ አሰልጣኞች ይሄዳሉ፤ የክብር ሰላምታና የክብር ስጦታ ያበረክታሉ።
ይህ የኬፕቨርዲው አሰልጣኝ ፔድሮ ሊያቶ ብሪቶ(በቢስታ) በአለም ዋንጫው አራት ጨዋታቸው ላይ ያሳዩት ተመሳሳይና አነጋጋሪ ተግባራቸው ነው።
ለአሰልጣኞቹ ለስፔኑ ሊዊስ ደላ ፉንቴ፥ ለሳኡዲ አረቢያው ጆርጀስ ዶኒስ፥ ለኡራጋዩ ማርሴሎ ቢየልሳ ትናንት ደግሞ ለአርጀንቲናው ሊዮኔል ስካሎኒ ስጦታ ሲያቀብሉ ታይተዋል።
ለሁሉም አሰልጣኞች የሚሰጡት ስጦታ ተመሳሳይ ነው፤ የትንሿ ሀገር የኬፕቨርዲ 10 ደሴቶችን የያዘና የሚገኙበትን ቦታ የሚጠቁም የካርታ ምስል ከማብራሪያ ጋር አበርክተዋል።
የቀድሞ የኬፕቨርዲ ተከላካይና አምበል፥ ለባለፉት ስድስት አመታት ደግሞ የብሄራዊ ቡድኑ አሰልጣኝ የሆኑት የ56 አመቱ በቢስታ በእጃቸው ለአሰልጣኞች ስጦታ እየሰጡ፥ በገነቡት ጠንካራ ቡድን ደግሞ ሃገራቸውን ለአለም አስተዋውቀው ትልቅ ገድል ፈፅመዋል።
500ሺህ ህዝብ ብቻ ያላት ትንሿ አፍሪካዊት ሀገር ኬፕቨርዲ አሁን በደንብ ታውቃለች፤ የአለም ዋንጫው ክስተትም ሆናለች፤ ነገ እሁድ ሰኔ 28 ከፖርቹጋል ነፃ የወጣችበትን 51ኛ አመት የምታከብረው ኬፕቨርዲ እድሜ ለአለም ዋንጫ ቡድኗ 'የት ነች? ከሚል ጥያቄም ነፃ ወጥታለች።
በታምሩ ዓለሙ
#ዳጉ_ጆርናል | 5 422 |
| 7 | "ጥቆላዬን ስሰራ የቴክኒክ ችግር ገጥሞኝ ነበር" ጋናዊዉ ጠንቋይ ናና ኩዋኩ ቦንሳም
ጋናዊዉ ጠንቋይ ናና ኩዋኩ ቦንሳም ከጥቂት ቀናት በፊት ካቦ ቨርዴ አርጀንቲናን ረትታ ታልፋለች ፤የአርጀንቲናም የአለምዋንጫ ጉዞ ይጠናቀቃል ታይቶኛል ሲል ተናግሮ ነበር።
ትናንት ምሽት ታድያ አርጀንቲና ድል ካደረገች በኋላ ትንቢቱ ፉርሽ የሆነበት ይህ ጠንቋይ "ጥቆላዬን ስሰራ የቴክኒክ ችግር ገጥሞኝ ነበር" ሲል ተናግሯል።
ካፈርኩ አይመልሰኝ ማለትም አይደል...
#ዳጉ_ጆርናል | 5 543 |
| 8 | ሊዮኔል ሜሲ ከምሽቱ የካቦ ቨርዴ አስቸጋሪ ጨዋታ በኋላ ለጋዜጠኞች - "ጨዋታዉ ከተጠናቀቀ በኋላ ከእኔ ጋር ፎቶግራፍ ለመነሳት እና መለያዬን ሲጠይቁኝ ነበር። ሜዳ ላይ ግን አስቃይተዉናል" ሲል የካቦ ቨርዴን ቡድን አድንቋል።
#ዳጉ_ጆርናል | 5 399 |
| 9 | 📢የጥገና ሥራ ለማከናወን የሚቋረጥ የኃይል አቅርቦት🎯
ነገ እሁድ ሰኔ 28 ቀን 2018 ዓ.ም በጥቁር አንበሳ 132 ኪ.ቮ ሃይል አስተላላፊ መስመር ሰበታ ወጪ መስመር ላይ የጥገና ሥራ ለማከናወን የኃይል አቅርቦት የሚቋረጥባቸው አካባቢዎች፦
✅ከንጋቱ 12፡00 እስከ ጠዋቱ 2፡00 ድረስ:-
👉በልደታ ክፍለ ከተማ ዙሪያ እና በጭድተራ ፊት ለፊት፣መላው የመርካቶ ዙሪያ፣ ፔፕሲ ፋብሪካ፣ የድሮው አትክልት ተራ፣ ኤሊያና ሆቴል፣ ሰባራ ባቡር፣ አዲስ ከተማ ቴሌ፣ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ (CBE) ኮል ሴንተር እና አካባቢው ፣
👉በአምስተኛ ፖሊስ ጣቢያ ዙሪያ፣ ሰንጋተራ፣ ጥቁር አንበሳ፣ ሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI)፣ የደም ባንክ፣ ፋና ሚዲያ፣ ንብ ባንክ ዋና መሥሪያ ቤት እና ጎላ ሚካኤል ሙሉ፣ በህንፃ ኮሌጅ ዙሪያ፣ ኮካ፣ አብነት፣ መድር-ኃይል፣
👉ጦር ኃይሎች ሆስፒታል እና ቶሎሳ ሰፈር፣ በልደታ ደሴ ሆቴል ዙሪያ፣ መላው ብስራተ ገብርኤል ዙሪያ፣ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ዋና መሥሪያ ቤት (Commercial Bank of Ethiopia HQ)፣ ፍልውሃ፣ ዘውዲቱ ሆስፒታል፣
👉ጋንዲ ሆስፒታል፣ የሳይንስ ሙዚየም፣ አራት ኪሎ (ባሻ ወልዴ፣1080)፣ ቅድስት ማርያም፣ አንድነት ፓርክ፣ መላው የጨርቆስ ዙሪያ፣ ፌደራል ፖሊስ፣ በልደታ ፀበል ዙሪያ፣ በልደታ ኮንዶሚኒየም ዙሪያ እና አካባቢው ፣
👉ኮሜርስ ኮሌጅ (Commerce)፣ ጥቁር አንበሳ፣ ቴሌ ዳታ ሴንተር፣ አድዋ ዜሮ ዜሮ (Adwa 00)፣ ወዳጅነት ፓርክ እና አካባቢያቸው የኃይል አቅርቦት ተቋርጦ ይቆያል፡፡
ስለሆነም በተጠቀሱት አካባቢዎች የምትገኙ ክቡራን ደንበኞቻችን የጥገና ሥራው ተጠናቆ የኃይል አቅርቦቱ እስኪ መለስ ድረስ በትዕግስት እንድትጠብቁን በትህትና እንጠይቃለን።
#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት | 5 149 |
| 10 | بدون متن... | 4 433 |
| 11 | በትምህርት ቤቶች ዙሪያ የትንባሆ መሸጫ ክልከላ ርቀት ወደ 500 ሜትር ከፍ ተደረገ
የአዲስ አበባ ምግብ መድሃኒት ባለስልጣን በትምህርት ቤቶች ዙሪያ የትንባሆ ምርቶች መሸጫ ክልከላ ርቀት ወደ 500 ሜትር ከፍ መደረጉን አስታውቋል፡፡ እርምጃው ህፃናትና ወጣቶችን ከትንባሆ ጭስና ሱስ አደጋ ለመከላከል እንዲሁም በትምህርት ቤቶች አካባቢ ጤናማ እና ንፁህ አካባቢ ለመፍጠር የተወሰደ የጤና ጥበቃ ፖሊሲ መሆኑ ተጠቅሷል።
አዲሱ ደንብ የትንባሆ ምርቶች በትምህርት ቤቶች በቅርብ ርቀት ላይ እንዳይገኙ በማድረግ የህፃናት መጋለጥን ለመቀነስ ያለመ ሲሆን እርምጃው በተለይም በተማሪዎች ዘንድ የትንባሆ ምርት መዳረሻን ለመገደብ እና የሱስ መጀመሪያ ዕድሜን ለመቀነስ የሚያግዝ መሆኑ ተነግሯል።
በተጨማሪም በተካሄደ ሰፊ የቁጥጥር ዘመቻ 1.3 ሚሊዮን ሕገወጥ ሲጋራዎች በቁጥጥር ሥር መዋላቸው ተገልጿል። ይህ እርምጃ በገበያ ውስጥ የሚሰራጩ ሕገወጥ የትንባሆ ምርቶችን ለመቆጣጠር የተደረገ የሕግ ማስከበር እንቅስቃሴ አካል ነው ተብሏል፡፡
በደንቡ መሠረት ትንባሆን የተከለከሉ ቦታዎች ላይ ሲሸጥ የተገኘ ማንኛውም ግለሰብ እስከ 6 ወር ቀላል እስራት ወይም እስከ 5,000 ብር የሚደርስ የገንዘብ ቅጣት ሊጣልበት እንደሚችል ተጠቁሟል።
የባለሥልጣኑ ዋና ሥራ አስኪያጅ ዶ/ር ሙሉ እመቤት ታደሰ ለብስራት ሬዲዮ እንደገለፁት
ይህ የቁጥጥር እርምጃ በከተማ አስተዳደሩ የጤና ፖሊሲ አቅጣጫ መሠረት በተደረገ ውሳኔ መተግበሩን አስረድተዋል።
ህብረተሰቡ የትንባሆ ቁጥጥር ሕጎችን በማክበር ከጭስ ነፃ፣ ንፁህና ጤናማ የከተማ አካባቢ ለመፍጠር ከመንግስት አካላት ጋር እንዲተባበር ጥሪ ቀርቧል።
በሳምራዊት ስዩም
#ዳጉ_ጆርናል | 5 748 |
| 12 | ግብፅ አውስትራሊያን በመለያ ምት በመርታት ወደ 16ቱ ዙር ተሸጋግራለች።
በግብፅ እና በአውስትራሊያ መካከል የተደረገው እጅግ ማራኪ ጨዋታ በፈርኦኖቹ አሸናፊነት ተጠናቋል።
#ዳጉ_ጆርናል | 6 160 |
| 13 | ከስምንት ቀናት በኋላ የቬንዙዌላ የመሬት መንቀጥቀጥ ሰለባ የነበረ ሰው በሕይወት ተገኘ
ቬንዙዌላ ውስጥ በተከሰቱ ሁለት ተከታታይ የመሬት መንቀጥቀጦች ምክንያት በፈራረሰ ሕንፃ ፍርስራሽ ውስጥ ለስምንት ቀናት ተይዞ የነበረ አንድ ሰው በሕይወት ተረፈ።የአደጋ ጊዜ ሰራተኞች ሄርናን ጊልን ለመጀመሪያ ጊዜ ካገኙት ከ100 ሰዓታት በላይ ከ140 ቶን ፍርስራሽ ነፃ ማውጣት ችለዋል።
የቬንዙዌላ ተጠባባቂ ፕሬዝዳንት ዴልሲ ሮድሪጌዝ ሐሙስ ዕለት ጊልን በሆስፒታል ውስጥ ጎብኝተው በማህበራዊ ሚዲያ ላይ ባስተላለፉት ቪዲዮ "ሕያው ተአምር" ሲሉ ጠርተውታል። እስከ ሐሙስ ምሽት ድረስ፣ ሰኔ 24 ቀን ቬንዙዌላ በደረሰው የመሬት መንቀጥቀጥ 2,595 ሰዎች መሞታቸው ተረጋግጧል፣ እናም በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች አሁንም የደረሱበት አልታወቀም።
ተጠባባቂ ፕሬዝዳንቷ ሮድሪጌዝ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ሲናገሩ የመሬት መንቀጥቀጡ “በፍፁም ባላሰብነው መጠን የተፈጥሮ አደጋ” ሲሉ ጠርተውታል። የመሬት መንቀጥቀጡ ከተከሰተ በኋላ በሺዎች የሚቆጠሩ ባለስልጣናት መሰማራታቸውን በመግለጽ መንግሥታቸው በጣም በዝግታ ምላሽ ሰጥቷል የሚለውን ትችት እንደማይቀበሉት ተናግረዋል።
በስምዖን ደረጄ
#ዳጉ_ጆርናል | 6 289 |
| 14 | የኢትዮጵያን የቱሪዝም መዳረሻዎች ያስተዋውቃል የተባለው የፎቶ አውደ ርዕይ ተከፈተ
በአዲስ አበባ ቴክኖ ኢትዮጵያ ከአዲስ አበባ ቱሪዝም ኮምሽን እና ከቦርድ ሴል ፎን አዲስ አበባ እንዲሁም ከህፃናት እና ወጣቶች የትያትር ኮምፕሌክስ ጋር በመተባበር ያዘጋጀው የፎቶ አውደ ርዕይ ተከፍቷል።
ለ10 ቀናት የሚቆየው አውደርዕዩ የቴክኖ አዲሱን ካሞን 50 ፕሮ ስልክ ለማስተዋወቅ የተዘጋጀ ሲሆን በስልኩ የተነሱ 100 ፎቶዎች ለዕይታ ቀርበዋል።
ፎቶዎቹ የኢትዮጵያን የቱሪዝም መዳረሻዎች፣ የተፈጥሮ ውበቶች፣ ባህላዊ እሴቶችና የማኅበረሰቡን የዕለት ተዕለት ኑሮ የሚያሳዩ ምስሎችን ያካትታሉ።
በእለቱም ቴክኖ ኢትዮጵያና አዲስ አበባ ቱሪዝም ኮሚሽን በቱሪዝምና ቴክኖሎጂ ዘርፎች በጋራ ለመስራት የሚያስችል ስምምነት ተፈራርመዋል።
ስምምነቱ የሀገሪቱን የቱሪዝም መዳረሻዎች በሀገር ውስጥና በውጭ ለማስተዋወቅ እንዲሁም ማኅበረሰቡ ሀገሩን የመጎብኘት ባህሉን እንዲያጠናክር አስተዋፅኦ እንደሚያበረክት ተገልጿል።
አውደርዕዩ በአዲስ አበባ ወጣቶች እና ህፃናት ትያትር ቤት የሚከናወን ሲሆን በ10 ቀናት ውስጥ ከ10 ሺህ በላይ ጎብኚዎች ይሳተፋሉ ይጠበቃል ተብሏል።
በሳምራዊት ስዩም
#ዳጉ_ጆርናል | 5 913 |
| 15 | ስድስት ቀናት በሚፈጀው የአያቶላ አሊ ካሜኒ የቀብር ስነ ስርዓት ላይ 20 ሚሊዮን ሰዎች እንደሚገኙ ይጠበቃል
ኢራን የቀድሞው የጠቅላይ መሪ አያቶላህ አሊ ካሜኒ በአሜሪካ እና እስራኤል በተካሄዱት ጥቃቶች ከተገደሉ ከአራት ወራት በላይ በኋላ ለቀድሞ የጠቅላይ መሪዋ በርካታ ቀናትን የሚጠይቅ የህዝብ ሀዘን እና የቀብር ሥነ ሥርዓቶችን ጀምራለች። የቀድሞው አያቶላህ አስከሬን ከዛሬ አርብ ጀምሮ በቴህራን ግራንድ ሞሳላ ውስጥ ሽኝት የተጀመረ ሲሆን በትውልድ ከተማቸው ማሽሃድ የቀብር ስነ ስርዓቱ ይፈፀማል።
ባለስልጣናት የቀብር ሥነ ሥርዓቱ ከመላው ኢራን እስከ 20 ሚሊዮን የሚደርሱ ሐዘንተኞችን ሊያስተናግድ እንደሚችል አጃንስ ፍራንስ ፕሬዝ ዘግቧል። ይህ የሆነው ኢራን እና ዩናይትድ ስቴትስ በሰኔ ወር ግጭታቸውን ለማስቆም የመጀመሪያ ስምምነት ከተፈራረሙ በኋላ ደካማ የሆነ የተኩስ አቁም ስምምነት መጀመሩን ተከትሎ ነው።
የካሜኒ አስከሬን በየካቲት ወር በአሜሪካ እና በእስራኤል ጥቃት ከተገደሉት የቤተሰብ አባላት አስከሬን ጎን ለጎን ለሦስት ቀናት በግራንድ ሞሳላ ውስጥ ይቀመጣል። ባለስልጣናት በቴህራን የሚገኙ የመንግስት እና የግል ቢሮዎች ከቅዳሜ እስከ ሰኞ እንዲዘጉ ትዕዛዝ ሰጥተዋል፣ የትራፊክ ገደቦች ደግሞ የከተማውን መሃል ለግል ተሽከርካሪዎች እንደሚዘጉ ተወስኗል። በቴህራን ላይ ያለው የአየር ክልል ከዛሬ ጀምሮ በከፊል ተዘግቶ ሰኞ እለት ሙሉ በሙሉ ይዘጋል።
በቴህራን ከሚካሄዱት ሥነ-ሥርዓቶች በኋላ፣ የቀድሞው ከፍተኛ መሪ አስከሬን በማሻድ ከመቀበሩ በፊት ወደ ኢራቅ ቅዱስ ከተሞች ናጃፍ እና ካርባላ ይወሰዳል። የፓኪስታኑ ጠቅላይ ሚኒስትር ሼህባዝ ሻሪፍን ጨምሮ ከተለያዩ ሀገራት የተውጣጡ ተወካዮች በሥነ ሥርዓቶቹ ላይ ይገኛሉ ተብሎ ይጠበቃል። የካሜኔይ ቦታን የተረከቡት ልጃቸው ሞጅታባ ሲሆኑ፣ ከፍተኛ መሪ ከሆኑበት ጊዜ አንስቶ በሕዝብ ፊት አልታዩም።
በስምዖን ደረጄ
#ዳጉ_ጆርናል | 5 550 |
| 16 | بدون متن... | 5 037 |
| 17 | በኢትዮጵያ 50 ሚሊዮን የሚገመቱ ዜጎች የንፁህ መጠጥ ውሃ እንደማያገኙ ተነገረ
በኢትዮጵያ የንጹህ መጠጥ ውሃ ተደራሽነትን በበቂ ሁኔታ ለማሳካት የሚያስችል አዲስ የውሃና ሳኒቴሽን አስተዳደር ሞዴል ለውይይት ቀርቧል።በውይይቱ የፌዴራልና የክልል ውሃና ኢነርጂ ተቋማት ኃላፊዎች፣ ባለሙያዎች፣ የውሃ አገልግሎት ተቋማት፣ የልማት አጋሮችና ሌሎች የሚመለከታቸው አካላት ተሳትፈዋል።
መንግሥት በቀጣዮቹ አራት ዓመታት 100 በመቶ የኢትዮጵያን ህዝብ በንጹህ መጠጥ ውሃ ተደራሽ ለማድረግ አቅዶ እየሰራ መሆኑን የመጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ዶ/ር አስፋው ዲንጋሞ መግለፃቸውን ብስራት ሬድዮ ሰምቷል። መንግሥት ከልማት አጋሮችና መንግሥታዊ ካልሆኑ ድርጅቶች ጋር በመተባበር በገጠርና በከተማ ከ230 ሺህ በላይ የውሃ ተቋማትን በመገንባት ከ82 ሚሊዮን በላይ ዜጎችን የንጹህ መጠጥ ውሃ ተጠቃሚ ማድረግ እንደቻለ ገልጸዋል።
ይሁን እንጂ ከ40 እስከ 50 ሚሊዮን የሚገመቱ ዜጎች በንጹህ መጠጥ ውሃ ተደራሽ አለመሆናቸውን ጠቅሰው ይህንን ክፍተት ለመሙላት የተቀናጀ ስትራቴጂና የተጠናከረ የትግበራ ሥራ እየተካሄደ መሆኑን ተናግረዋል።በውሀና ኢነርጂ ሚኒስቴር የህዝብ ግንኙነት ስራ አስፈፃሚ አቶ ጌትነት ስሜ ለብስራት ሬድዮ እንደተናገሩት በውሃ ፕሮጀክቶች ዕቅድ፣ ግንባታና አስተዳደር ሂደት ፣ ፈጣን የህዝብ ቁጥር እድገት፣ የኃይልና የነዳጅ ዋጋ ጭማሪ እንዲሁም ሌሎች ተያያዥ ችግሮች እያጋጠሙ ይገኛሉ።
በተጨማሪም የውሃ ተቋማት ላይ የሚያጋጥሙ ችግሮችን ለመቅረፍ አማራጭ የኃይል ምንጮችን በተለይም በገጠሩ ክፍል ላይ የፀሐይ ኃይልን መጠቀም እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል።ለዚህም የተዘጋጀው የአስተዳደር ሞዴል የውሃ ተቋማትን በወቅቱ የመጠገን አቅምን ለማሳደግ፣ የውሃ ጥራትን በተከታታይ ለመከታተል ያስችላል ነው ያሉት።
የአገልግሎት ተጠያቂነትን በማጠናከር የማህበረሰብና የግሉን ዘርፍ ተሳትፎን ለማሳደግ እንደሚረዳ የገለፁት አቶ ጌትነት የውሃ አገልግሎት ተቋማትን በፋይናንስና በተቋማዊ አቅም ጭምር ለማጠናከር የሚያግዝ መሆኑን አብራርተዋል።
በቅድስት ደጀኔ
#ዳጉ_ጆርናል | 5 553 |
| 18 | بدون متن... | 5 152 |
| 19 | እስራኤል የኢራን ተደራዳሪዎችን ለመግደል አቅዳለች ሲሉ የአሜሪካ መገናኛ ብዙሃን ዘገቡ
ኒውዮርክ ታይምስ እና ዘ ዋሽንግተን ፖስት የአሜሪካ ባለስልጣናት እስራኤል በዚህ አመት መጀመሪያ ላይ በዋሽንግተን እና ቴህራን መካከል የተፈጠረውን ግጭት ለማስቆም በታለመ ውይይት ወቅት የኢራን ተደራዳሪዎችን ለመግደል አቅዳ እንደነበር ዘግበዋል።
ስማቸው እንዳይገለጽ የፈለጉ ባለስልጣናት ለሁለቱም የዜና ማሰራጫዎች እንደተናገሩት እስራኤል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አባስ አራግቺን እና የኢራን ፓርላማ አፈ-ጉባኤ የሆኑትን የአገሪቱን ዋና ተደራዳሪ መሐመድ ባገር ጋሊባፍን ለመግደል አቅዳለች ብለዋል። ለኒውዮርክ ታይምስ የተናገሩ ባለስልጣናት አሜሪካ በመካከለኛው ምስራቅ ያሉ ሀገራት ኢራንን ስለ አደጋው እንዲያስጠነቅቁ ጠይቀዋል።
እስራኤል የክልል ግጭቶችን ለማስቆም ውይይቶችን ለማደናቀፍ በሚደረገው ጥረት ተደራዳሪዎች ላይ በማነጣጠር ረገድ ጥሩ ታሪክ አላት። በጥቅምት ወር የእስራኤል ጦር በዶሃ ውስጥ ጥቃት ፈጽሟል፣ የቡድኑ ባለስልጣናት ከእስራኤል ጋር የተኩስ አቁም ሀሳብ እያጠኑ እያለ ጥቃቱ መፈፀሙ ይታወሳል።
በስምዖን ደረጄ
#ዳጉ_ጆርናል | 5 658 |
| 20 | የኢትዮ-ኬንያ የጠረፍ ንግድ መመሪያ ጸድቆ በይፋ ሥራ ላይ እንዲውል ተወሰነ
በኢትዮጵያና በኬንያ የጋራ ድንበር አካባቢ የሚኖሩ ማኅበረሰቦችን በሕጋዊ የንግድ ሥርዓት ተጠቃሚ ለማድረግና የአካባቢውን ሰላምና ዕድገት ለማጠናከር የተዘጋጀው “የኢትዮጵያ እና የኬንያ የጠረፍ ንግድ መመሪያ” በንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ጽድቆ ስራ ላይ እንዲውል መወሰኑን ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ አስታውቋል።
ይህ መመሪያ የወጣው ሁለቱ ሀገራት ታህሳስ 10 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማ የተፈራረሙትን “የተቀላጠፈ የጠረፍ ንግድ ማዕቀፍ” በተግባር ለማስፈጸም ሲሆን በፍትሕ ሚኒስቴር መመሪያ ቁጥር 1144/2018 ሆኖ ተመዝግቧል። የዚህ መመሪያ ዋነኛ ግብ በድንበር አካባቢ የሚኖሩ ዜጎች ከመሃል ሀገር በቀላሉ ሊያገኟቸው የማይችሏቸውን መሠረታዊ የፍጆታ ምርቶች በሕጋዊና ቀላል በሆነ መንገድ የጠረፍ ንግድ አሠራር እንዲያገኙ ማስቻል ነው ።
ከዚህ ባለፈ መመሪያው በድንበር አካባቢ የሚስተዋለውን ሕገ-ወጥ የንግድ እንቅስቃሴና ኮንትሮባንድ ለመቀነስ፣አነስተኛ የመነገድ አቅም ላላቸው የድንበር አካባቢ ነዋሪዎችና ዜጎች አዳዲስ የሥራ ዕድሎችን ለማመቻቸት ያስችላል ተብሏል።በመመሪያው በኢትዮጵያና በኬንያ ጎረቤት ሕዝቦች መካከል ያለውን ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ትስስር በማጠናከር በአካባቢው አስተማማኝ ሰላምና ጸጥታ እንዲሰፍን ለማድረግ ያስችላል።
እንዲሁም በቅንጅታዊ አሠራር የጠረፍ ንግድ መረጃ አያያዝንና የቁጥጥር ሥርዓትን ለማጠናከር ያግዛል፡፡ በጠረፍ ንግድ ሥርአት ውስጥ ሊገበያዩ የሚችሉት 50 የምርት አይነቶች ሲሆኑ ግብይቱ ሊፈጸም የሚችለው ከኢትዮጵያ እና ከኬንያ የድንበር በር ጀምሮ በኢትዮጵያ በኩል 50 ኪሎ ሜትር፤ በኬንያ በኩል ደግሞ 100 ኪሎ ሜትር ርቀት ውስጥ ባሉ የጠረፍ አካባቢዎች ነው፡፡
በትግስት ላቀው
#ዳጉ_ጆርናል | 5 631 |
اکنون در دسترس! پژوهش تلگرام ۲۰۲۵ — مهمترین بینشهای سال 
