cookie

Sizning foydalanuvchi tajribangizni yaxshilash uchun cookie-lardan foydalanamiz. Barchasini qabul qiling», bosing, cookie-lardan foydalanilishiga rozilik bildirishingiz talab qilinadi.

avatar

ዳጉ-ጆርናል/Dagu-Journal

The best fiction is far more true than any journalism 📢 ተዓማኒ የመረጃ ምንጭ ፤ ለሙያው ስነምግባር ተገዢ በሆኑ ጋዜጠኞች ብቻ 👉 በፌስቡክ ገፆቻችን https://www.facebook.com/simon.dereje.56 👉 https://www.facebook.com/mik0Man

Ko'proq ko'rsatish
Reklama postlari
35 707
Obunachilar
Ma'lumot yo'q24 soatlar
+387 kunlar
+87330 kunlar

Ma'lumot yuklanmoqda...

Obunachilar o'sish tezligi

Ma'lumot yuklanmoqda...

📸⚪️🔥 ሰላም እደሩ 🙏 #ዳጉ_ጆርናል
Hammasini ko'rsatish...
🥰 9👍 3 3👎 2🤯 1
Photo unavailableShow in Telegram
ኢትዮጵያና የተባበሩት አረብ ኤሜሬቶች በራሳቸውን ገንዘብ ለመገበያየት ተስማምተዋል ተባለ! ኢትዮጵያና የተባበሩት አረብ ኤሜሬቶች ለግብይት የራሳቸውን ገንዘብ ለመጠቀም ስምምነት ተፈራርመዋል፡፡ስምምነቱን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዥ ማሞ ምህረቱ እና የተባበሩት አረብ ኤሜሬቶች ብሔራዊ ባንክ ገዢ ካሊድ ሞሃመድ ባላማ መፈረማቸውን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ባወጣው መግለጫ አስታውቋል፡፡ በዚህም በሁለቱ ሀገራት ለሚደረግ ግብይት የራሳቸውን ገንዘብ ማለትም ድርሃምና ብር ለመጠቀም ከስምምነት የደረሱ ሲሆን ሁለቱ አካላት ለተግባራዊነቱ ምቹ መደላድል ለመፍጠር ጥረት እንደሚያደርጉ ተገልጿል፡፡ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዥ ማሞ ምህረቱ የተባበሩት አረብ ኤሜሬቶች የኢትዮጵያ አንዷ የንግድ አጋርና የውጪ ኢንቨስትመንት ምንጭ መሆኗን ገልጸው ስምምነቱ የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት ይበልጥ እንዲጠናከር ያደርገዋል ብለዋል። በጋራ ጥቅም ላይ የተመሰረት ቀጣይነት ያለው ልማትና ብልጽግናን የሚያረጋግጥ ስለመሆኑም ተናግረዋል፡፡የተባበሩት አረብ ኤሜሬቶች ብሔራዊ ባንክ ገዥ ካሊድ ሞሃመድ ባላማ በበኩላቸው ስምምነቱ ሁለቱ ሀገራት የኢኮኖሚ ግንኙነታቸውን እያጠናከሩ መምጣታቸውን እንደሚያሳይ አመላክተዋል። #ዳጉ_ጆርናል
Hammasini ko'rsatish...
👍 35😁 3🔥 1
በቻይና 25 ኪሎ ግራም የምትመዝነው ወጣት አሁንም ክብደቷን ለመቀነስ እየሞከረች መሆኑን አስታወቀች 25 ኪሎ ግራም ብቻ የምትመዝነው ቻይናዊት ወጣት እንስት አስደንጋጭ ገላዋን ኦንላይን ካሳየች እና የበለጠ ከሲታ መሆን እንደምትፈልግ መግልጻን ተከትሎ ከፍተኛ ትኩረትን ስባለች። ቤቢ ቲንዚ በሚል መጠርያ የምትታወቀው ወጣቷ 160 ሴ.ሜ ቁመት ቢኖራትም ወደ 25 ኪሎ ግራም ብቻ ነው ክበደቷ ይመዝናል። አስገራሚው ነገር ግን እንስቷ አሁንም ቢሆን ክብደቷን መቀነስ መፈለጓ ነው። በቻይናው የቲክቶክ ተመሳሳይ ገፅ ዱዪን ላይ ከ42,000 በላይ አድናቂ ተከታዮች ያሏት እንስቷ ተከታዮቻ ስለጤንነቷ ያለማቋረጥ እንደሚጠይቋት ነው መረጃዎች ያሳያሉ። ቤቢ ቲንዚ ሁል ጊዜ እንደዚህ ያሉ ስጋቶችን እንደማያሳስቧት የምትናገር ሲሆን አፅም ብቻ የሚታይበት ምስሏ በህይወቷ ላይ ምንም አይነት አሉታዊ ተፅእኖ እንደሌለው ታክላለች። ከጊዜ ወደ ጊዜ እየመጣ ያለው የማህበራዊ ሚዲያ ተፅእኖ ፈጣሪኘት ከቻይና ጓንግዶንግ ግዛት የጓንግዙ ነዋሪዋ እንስት ቀጫጫን ሰውነትዋን ለማሳየት የሚረዱ ልብሶችን ለብሳ የራሷን ቪድዮዎች ያለማቋረጥ ትለጥፋለች። የሰውነት ቅርፅና ቀጫጫነቷን ተከትሎ ለሚሰጧት ትችቶች ግን ግድ የላትም። በአብዛኛዎቹ ቪዲዮዎቿ ላይ ቤቢ ቲንዚ በካሜራ ፊት ትጨፍራለች እንዲሁም ሰውነቷን አጋልጠው የሚያሳዩ ልብሶችን ታዘወትራለች። በዚህም ቀጭን እግሮቿን እና እጆቿን ታሳያለች።ቤቢ ቲንዚ በቻይና ማህበራዊ ሚዲያ እጅግ ብዙ ከታየች በኋላ ብዙዎች አኖሬክሲያ በተባለ ህመም እንደተጠቃችና አስቸኳይ የህክምና እርዳታ እንደሚያስፈልጋት ሲጠቁሟት አንዳንዶች ደግሞ የአፅም ዳንሰኛ በማለት ሲያሾፉባትና ቅፅል ስም ሲሰጧት ተስተውለዋል። ለእንስቷ ከተሰጡ አስተያየቶች መካከል ደግሞ 25 ኪሎ ግራም የሚመዘን ሰው ይኖራል ብሎ መገመት ይከብዳል ግን እውነታ ይህ ነው። እንዲሁም እኔ አንቺ ብሆን አጥንቶቼ እንዳይሰበሩ አይደለም መደነሰ ከመደበኛ እንቅስቃሴም እቆጠብ ነበር ሲሏት ተደምጠዋል። በሚሊዮን ሙሴ #ዳጉ_ጆርናል
Hammasini ko'rsatish...
😁 35👍 11👎 4🤬 3 1
😁 6👍 3🤬 2
በእኔ እና በእናትህ ጸብ ለምን ገባህ በማለት የገዛ ልጁን የገደለው አባት በእስራት ተቀጣ በምስራቅ ሀረርጌ ዞን ሜታ ወረዳ  ካሊድ ሃሰን የተባለው ግለሰብ ትዳር መስርቶ ልጆች  አፍርቶ የሚኖር ሲሆን  ከልጆቹ መሃል  የመጀመሪያ ልጁ የሆነውን መገርሳ  በመግደል ወንጀል በእስራት መቀጣቱ  ፖሊስ  ገልጿል  ። መገርሳ የተባለው ልጅ  ቤተሰቦቹ መካካል  በተደጋጋሚ ግጭት  ይፈጠር የነበረ ሲሆን  የተፈጠረው ግጭት  በሽማግሌዎች እንዲፈታ ያደረጋል  ። ነገር ግን የባል እና ሚስት ግጭት መቆም አልቻለም በመሆኑም እናቱ ግጭት በተፈጠረ ቁጥር ወደ ልጇ ቤት በተደጋጋሚ ትሄድ እንደነበር  እና በዛም ባለቤቷ ቅሬታ እንዳደረባቸው ብስራት ሬዲዮ እና ቴሌቪዥን ሰምቷል። አባት ፊት እየሰጠሃት ነው በትንሽ ትልቁ እያኮረፈች ወደ አንተ ቤት የምትመጣው  በሚል ከልጃቸው ጋር ይጋጫሉ ። ሚስት አባት እና ልጅ መጣላታቸውን ሲያውቁ ወደ ህግ በመሄድ ክስ  ይመሰርታሉ ። አቶ ካሊድ ባለቤታቸው እና ልጃቸው እንደከሰሷቸው ሲያውቁ  በንዴት ከሌሊቱ 6 ሰዓት ላይ  ስለታም መጥረቢያ በመያዝ  ወደ ልጃቸው ቤት ሄደው  ልጃቸው በር እንደከፈተላቸው  በመጥረቢያ ጉዳት እንዳደረሱበት የምስራቅ ሀረርጌ ዞን  ከፍተኛ  ፍርድ ቤት የኮሙኒኬሽን ጉዳዮች  ሃላፊ አቶ ሱሌማን ቱጅሃን በተለይ ለብስራት ሬዲዮ እና ቴሌቪዥን ተናግረዋል ። ድርጊቱን ከፈጸሙ በኋላ ወደ ቤታቸው ያመራሉ:: የአካባቢው ነዋሪዎች እና የተጎጂውን ባለቤት ጩኸት በመስማት ወደ ቦታው በማምራት ተጎጂውን የህክምና አገልግሎት እንዲያገኝ  ያደርጋሉ፡፡ ነገር ግን ጭንቅላቱ ላይ ከፍተኛ ጉዳት  ደርሶበት ህይወቱ ሊያልፍ መቻሉ ተረጋግጧል።ፖሊስ ጉዳዩን በማጣራት ተከሳሽ ካሊድ በቁጥጥር  ስር በማዋል ድርጊቱን መፈጸሙን የሚያሳዩ መረጃዎቹን በማሰባሰብ መዝገቡን ለዓቃቢ ህግ ይልካል ።  ዓቃቢ ህግ ጥር 16 ቀን 2016 ዓ.ም ተከሳሽ ካሊድ የገዛ ልጁን በመግደል ከባድ የሰው መግደል ወንጀል ክስ ይመስርታል።የምሰራቅ ሀረርጌ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት  ጉዳዩን በመመልከት  ሃምሌ 2 ቀን 2016 ዓ.ም በዋለው ችሎት  ተከሳሽ ካሊድ ሀሰን በ14  ዓመት እስራት እንዲቀጣ የተወሰነበት መሆኑን የምስራቅ ሀረርጌ ዞን  ከፍተኛ  ፍርድ ቤት የኮሙኒኬሽን  ጉዳዮች  ኃላፊ አቶ ሱሌማን ቱጅሃን ጨምረው ለብስራት ሬዲዮ እና ቴሌቪዥን ተናግረዋል። በኤደን ሽመልስ #ዳጉ_ጆርናል
Hammasini ko'rsatish...
👍 25👎 12😢 7 1😁 1
ትራፊክ አደጋ የ6 ሰዎች ሕይወት ሲያልፍ 14 ሰዎች ላይ የአካል ጉዳት ደረሰ በሶማሌ ክልል ቀብሪበያህ ወረዳ ጉዮው በተባለ ቦታ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የሥድስት ሰዎች ሕይወት አለፈ፡፡ በተጨማሪም በ14 ሰዎች ላይ የአካል ጉዳት መድረሱ ተገልጿል፡፡ አደጋው የተከሰተው በሁለት ተሸከርካሪዎች ግጭት መሆኑ ተመላክቷል፡፡ #ዳጉ_ጆርናል
Hammasini ko'rsatish...
👍 5🤔 3😱 1💔 1
Photo unavailableShow in Telegram
እስራኤል በጋዛ የሚገኘዉን ብቸኛ የካንሰር ታማሚዎች ሆስፒታልን የጦር ካምፕ አድርጋዋለች ተባለ እስራኤል በጋዛ ብቸኛዉ የካንሰር ታማሚዎች ሆስፒታል ነዉ የተባለለትን ተቋም የጦር ካምፕ አድርጋዋለች መባሉ ተሰምቷል። ይህ የእስራኤል ድርጊትን ተከትሎም ቱርኪዬ ሆስፒታሉን እስራኤል ለወራት እንደ ወታደራዊ ጣቢያ ተጠቅማበታለች ያለች ሲሆን ፤ ይህም  የጋዛ ብቸኛ ልዩ የካንሰር ሆስፒታል ላይ ጉዳት በማድረሱ የእስራኤልን ጦር በማውገዝ ጥፋተኛ እና ተጠያቂዎቹ "በአለም አቀፍ ፍርድ ቤቶች ለፍርድ እንደሚቀርቡ" ዝታለች ። በተጨማሪነትም እስራኤል በማዕከላዊ ጋዛ ኑሴራት የስደተኞች ካምፕ ላይ ባደረሰችው ጥቃት ቢያንስ 11 ፍልስጤማውያን አምስት ህፃናትን ጨምሮ መሞታቸው ተዘግቧል። ከጥቅምት 7 ጀምሮ በእስራኤል በጋዛ ጦርነት በፍልስጤም በኩል ቢያንስ 38 ሺህ 664 ሰዎች ተገድለዋል የተባለ ሲሆን 89 ሺህ 97 ያህሉ ደግሞ ቆስለዋል ይባላል ። በጥቅምት 7 በሀማስ መሪነት በእስራኤል የሞቱት ሰዎች ቁጥር 1 ሺህ 139 ሆኖ የሚገመት ሲሆን በደርዘን የሚቆጠሩ ሰዎች አሁንም በጋዛ ታግተዉ ይገኛሉ። ሀይ ባይ ያጣዉ የእስራኤል ጦር በዉጊያዉ በጋዛ ላይ ባደረገው ጦርነት ምክንያት የታንክ እና ጥይቶች እጥረት መኖሩን ለእስራኤል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ባቀረበው ሪፖርት አመልክቷል። በበረከት ሞገስ #ዳጉ_ጆርናል
Hammasini ko'rsatish...
😢 37👍 9 1🔥 1👏 1💔 1
አዲስ አበባ ከተማ በ2016 በጀት ዓመት ከህዝብ መፀዳጃ ቤቶች አገልግሎት ከሁለት ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ አገኘች አዲስ አበባ ከተማ ባለፉት አስራ ሁለት ወራት ከህዝብ መፀዳጃ ቤቶች አገልግሎት ከሁለት ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ ማግኘቷን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የከተማ ውበትና አረንጓዴ ልማት ቢሮ አስታውቋል።በቢሮው የተቀናጀ ዘላቂ ማረፊያ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ አጃይብ ኩምሳ ለብስራት ሬድዬና ቴሌቪዥን እንደተናገሩት የአዲስ አበባን ፅዳትና ውበት ለማስጠበቅ ባለፉት ጊዜያት የመፀዳጃ ቤቶችን ቁጥር ለመጨመር  በርካታ ስራዎች ሲሰሩ ቆይተዋል። ከጊዜ ወደ ጊዜ በአዲስ አበባ ከተማ ያለው የመፀዳጃ ቤት አገልግሎት እየተሻሻለ በመምጣቱ ባለፉትአስራ ሁለት ወራት ውስጥ የተገልጋዮች ቁጥር ጨምሯል።በዚህም በዘንድሮ በጀት አመት ይህን ያህል ገቢ ማግኘት ተችሏል ሲሉ አቶ አጃይብ ጨምረው ለጣቢያችን ገልፀዋል ።በ2016 በጀት አመት የተገኘው ገቢ ጥሩ አፈጻጸም የታየበት ነው ሲሉ የተናገሩት አቶ አጃይብ የመፀዳጃ ቤት አገልግሎት በተለያዩ የአዲስ አበባ አካባቢዎች ላይ ተደራሽ እንዲሆን በመደረጉ የተገልጋዮች ቁጥር እንዲጨምር አስተዋጾኦ አድርጓል ብለዋል። ይህን ተከትሎ ባለፉት አስራ ሁለት ወራት የተገኘው ገቢ የተሻለ ውጤት የታየበት ነው ሲሉ ዳይሬክተሩ  ተናግረዋል።በአሁኑ ወቅት በአዲስ አበባ  ከተማ 3መቶ 58 የሚሆኑ የህዝብ መፀዳጃ ቤቶች መኖራቸው የተገለፀ ሲሆን የመፀዳጃ ቤት አገልግሎትን የተሻለ ለማድረግ  በ2017 በጀት አመት ተጨማሪ አዳዲስና ዘመናዊ የሆኑ መፀዳጃ ቤቶች እንደሚገነቡ ተጠቅሷል። በቅድስት ደጀኔ #ዳጉ_ጆርናል
Hammasini ko'rsatish...
😁 20👍 13🤔 2
በርናቤዪ የአለማችን የወቅቱ ምርጡ ተጫዋች ኪሊያን ምባፔ በደመቀ መልኩ በሻምፒዮንስ ሊግ ዋንጫዎቿ ታጅባ አቀባበል አድርጋለች 🔥 #ዳጉ_ጆርናል
Hammasini ko'rsatish...
👍 21 4🔥 1
በ2016 ዓመት በመልካም ወጣት መርሀ ግብር ከ30 ሺ በላይ ወጣቶች ይሳተፋሉ ተባለ ለሰባተኛ ጊዜ የሚሰጠው የመልካም ወጣት ስልጠና በ2016 ዓ.ም ከ30 ሺ በላይ ወጣቶች ተመዝግበው ስልጠናው በሀዋሳ ከተማ ሊሰጥ መሆኑን የአዲስ ኪዳን ቤተክርስቲያን የመልካም ወጣት መስራች አገልጋይ ዮናታን አክሊሉ ለብስራት ሬዲዮና ቴሌቪዥን ተናግረዋል። እንደ አገልጋይ ዮናታን ገለፃ የምንፈልጋትን ኢትዮጵያ ለማግኘት ያላትን ሀይል በመጠቀም ከሀሳብ ወደ ትግበራ መግባት የሚቻለው በወጣቶች በመሆኑ ከተለያዩ ወጣቶች ላይ የሚታዩ ችግሮችን ለመቅረፍ መሆኑን ተናግረዋል።የ2016 ዓ.ም  የመልካም ወጣት ስልጠና መርሃ ግብር የሚካሄደው ከሀምሌ 21እስከ ጳጉሜ 2 ድረስ ነው። እስካሁን በመልካም ወጣት መርሀ ግብር ከ180 ሺህ በላይ ወጣቶች የተሳተፉበት ሲሆን በዘንድሮው የመልካም ወጣት መርሃ ግብር ላይ  ከ30 ሺህ በላይ የሚሆኑ ወጣቶች ከሀገር ውስጥም ሆነ ከውጪ የሚመጡ ሰልጣኞች ስልጠናውን እንደሚወስዱም ተነግሯል። የመልካም ወጣት ዋንኛ ራዕይ በሁለንተናዊ አቅጣጫ ወጣቶችን የበለጸጉ እንዲሆን ማስቻል፣ማንቃት፣መንገድን በማሳየት ብቁ ማድረግ እንደሆነም ተጠቁሟል፡፡ በኢትዮጲያ ካለዉ ህዝብ ዉስጥ 70 በመቶ የሚሆነዉ ወጣት እንደመሆኑ በመርሃ ግብሩ በስራ ፈጠራ፣ ከሱስና ሱሰኝነትን መላቀቅ እንዲሁም ወንጀልን ለመከላከል በሚሉ ሀሳቦች ላይ ስልጠና ይሰጣል። ስነልቦናዊ ጫናዎች ማከም ትልቅ ትኩረት የሚያስፈልገው ጉዳይ በመሆኑ በቤተክርስትያን በመንግስት  ይህ አይነቱ መርሃ ግብር መደገፍ እና መበረታት   እንደሚገባው ተጠቁሟል ። በመልካም ወጣት ፕሮጀክቶች በሀዋሳ እና በወላይታ የሚገነቡ የህክምና ተቋማት አሉ ።ወላይታ ላይ ከ500 ሚሊየን ብር በላይ የሚያወጣ 500 አልጋዎች የሚኖሩት የስነአዕምሮ ማዕከል እየተገነባ ነው። እንዲሁም በሀዋሳ ከተማ በ1ቢሊየን 200ሚሊየን ብር እየተገነባ ያለ የህክምና ተቋም መኖሩን እና በአንድ አመት ውስጥ እነዚህ ፕሮጀክቶች እንደሚጠናቀቁ ተናግረዋል። መልካም ወጣት ስልጠና ላይ ለመካፈል ማንኛውም ፍላጎት ያለው ወጣት መሳተፍ እንደሚችል አገልጋይ ዮናታን ጨምረው ለ ብስራት ሬዲዮና ቴሌቪዥን ተናግረዋል በምህረት ታደሰ #ዳጉ_ጆርናል
Hammasini ko'rsatish...
👎 83👍 46😁 24 9🔥 3
Boshqa reja tanlang

Joriy rejangiz faqat 5 ta kanal uchun analitika imkoniyatini beradi. Ko'proq olish uchun, iltimos, boshqa reja tanlang.