ማራናታ.....MARANATHA
ለአንዳንዶች የሚዘገይ እንደምመስላቸው ጌታ ሰለ ተስፋ ቃሉ አይዘገይም፥ ነገር ግን ሁሉ ወደ ንስሐ እንድደርሱ እንጅ ማንም እንዳይጠፋ ወዶ ሰለ እናንተ ይታገሳል።2ኛ ጴጥ 3፥9 ገና በጣም ጥቅት ጊዜ ነው፤ ሊመጣ ያለውም ይመጣል አይዘገይምም። ዕብራ 10፥37 የመወያያ ግሩፕ👇 @Marantawoch Inbox Comment @Thaddyapostolic
Больше📈 Аналитический обзор Telegram-канала ማራናታ.....MARANATHA
Канал ማራናታ.....MARANATHA (@maranathawoch) языкового сегмента Амхарский является активным участником. Сейчас сообщество объединяет 16 921 подписчиков, занимая 4 955 место в категории Религия и духовность и 1 996 место в регионе Эфиопия.
📊 Показатели аудитории и динамика
С момента создания невідомо проект демонстрирует стремительный рост, собрав аудиторию из 16 921 подписчиков.
Согласно последним данным от 24 июля, 2026, канал показывает стабильную активность. За последние 30 дней изменение числа участников составило 317, а за последние 24 часа — 21, при этом общий охват остаётся высоким.
- Статус верификации: Не верифицирован
- Уровень вовлечённости (ER): Средний показатель вовлечённости аудитории составляет 22.61%. В первые 24 часа после публикации контент обычно набирает 7.58% реакций от общего числа подписчиков.
- Охват публикаций: В среднем каждый пост получает 3 822 просмотров. В течение первых суток публикация набирает 1 282 просмотров.
- Реакции и взаимодействия: Аудитория активно поддерживает контент: среднее количество реакций на один пост — 36.
📝 Описание и контентная политика
Автор описывает ресурс как площадку для выражения субъективного мнения:
“ለአንዳንዶች የሚዘገይ እንደምመስላቸው ጌታ ሰለ ተስፋ ቃሉ አይዘገይም፥ ነገር ግን ሁሉ ወደ ንስሐ እንድደርሱ እንጅ ማንም እንዳይጠፋ ወዶ ሰለ እናንተ ይታገሳል።2ኛ ጴጥ 3፥9 ገና በጣም ጥቅት ጊዜ ነው፤ ሊመጣ ያለውም ይመጣል አይዘገይምም። ዕብራ 10፥37
የመወያያ ግሩፕ👇
@Marantawoch
Inbox Comment @Thaddyapostolic”
Благодаря высокой частоте обновлений (последние данные получены 25 июля, 2026) канал поддерживает актуальность и высокий уровень охвата публикаций. Аналитика показывает, что аудитория активно взаимодействует с контентом, что делает его важной точкой влияния в категории Религия и духовность.
Загрузка данных...
| Дата | Привлечение подписчиков | Упоминания | Каналы | |
| 25 июля | +15 | |||
| 24 июля | +21 | |||
| 23 июля | +11 | |||
| 22 июля | +15 | |||
| 21 июля | +12 | |||
| 20 июля | +17 | |||
| 19 июля | +9 | |||
| 18 июля | +10 | |||
| 17 июля | +20 | |||
| 16 июля | +5 | |||
| 15 июля | +16 | |||
| 14 июля | +8 | |||
| 13 июля | +6 | |||
| 12 июля | +16 | |||
| 11 июля | +20 | |||
| 10 июля | +5 | |||
| 09 июля | +7 | |||
| 08 июля | +6 | |||
| 07 июля | +3 | |||
| 06 июля | +11 | |||
| 05 июля | +19 | |||
| 04 июля | +1 | |||
| 03 июля | +17 | |||
| 02 июля | +12 | |||
| 01 июля | +20 |
| 2 | ✍SIDAMIC_SONG✅
#Soqqamannoha_guute_Dishitaawo_buute
Anga noosiha halaalu Degemmaawo baaru
"ተግቶ የሚያገለግለውን ግንጥ አይገድልም"
"እውነት በእጁ ያለውን ባህሩ አይሰምጥም"
#አለታ_ወንዶ_እናት_አጥቢያ_ዘማሪ_ወ/ም #ASRAT_DEMOZE | 570 |
| 3 | ተስፋህ ያኖረኛል!
ከራስ ጋር ንግግር፦ "እለት እለት እየበደልኩ የመመለሻ ቀኔን ትጠባበቃለህ፣ ደጋግሜ ብስትም የምታረምበትን እድል ሰጠሀኝ፣ ነውሬ ቢያሸማቅቀኝ፣ ውስጤ በሃጢአት ቢረክስ፣ ክፋቴ ጥግ ቢነካም አንተ ግን ነፍሴን ለማዳን ከበሬ ቆመሃል፣ ከዓለም ግዞት፣ ከዲያቢሎስ እስራት ልትታደገኝ ዛሬም የኔን መመለስ በጉጉት ትጠባበቃለህ። ፍቅርህ ሃያል ነው፣ መውደድህ ጥግ የለውም፣ ርህራሔህ አያበቃም። እኔ በጥፋቴ እያፈርኩም ዳግም ጥፋት ውስጥ ነኝ፣ ምንምእንኳን መንገድ መሳቴ ቢታወቀኝ፣ ካንተ ትዕዛዝ መውጣቴ ቢገባኝም ዛሬም እንዲሁ በጥፋቴ ቀጥዬአለሁ፣ አሁንም እዛው የፀፀት አዙሪት ውስጥ እገኛለሁ። ተፀፅቼ አልመለስ፣ ተረድቼም እራሴን ነፃ አላወጣም። አንተ ግን ከነሙሉ ጥፋቴ ልጅህ አደረከኝ፣ አንተ ግን ከነሙሉ ሃጢያቴ ወደቤትህ ጠራሀኝ።
በራሴ ያለኝ እምነት አይደለም አንተ የምታምንብኝ፣ ለራሴ የሰጠውት እድል አይደለም አንተ የሰጠሀኝ፣ በራሴ ተስፋ ያደረኩት አይደለም አንተ የጣልክብኝ ተስፋህ ያኖረኛል። መውደቄን ታውቃለህ ነገር ግን መነሳቴን ትጠብቃለህ፣ ነውሬን ታውቃለህ ነገር ግን ሁሌም የይቅርታ ጊዜ ትሰጠኛለህ፣ ስህተቴ አላልቅ ብሏል አንተ ግን አንድ ቀን እንደምታረም ታምናለህ። የምኖረው በስራዬ አይደለም፣ ውስጤ የሚረጋጋው፣ ነፍሴ ሰላም የሚኖራት፣ ህይወት ክብደቷን የምትቀንስልኝ በኔ ፅድቅ ወይም በኔ መልካምነት አይደለም፣ ይልቅ ሁሉን እያየህ በምትተውልኝ፣ ደጋግመህ እድል በምትሰጠኝ ባንተ በምትወደኝ አባቴ ምህረትና ርህራሔ ነው። እወድሃለሁ ነገር ግን ጥፋቴን አልተውኩም፣ አከብርሃለሁ ነገር ግን ዛሬም እዛው ሃጢአት ውስጥ ተዘፍቄያለሁ፣ እገዛልሃለሁ ነገር ግን አሁንም አንተን መበደሌን አላቆምኩም። ይቅርታ ለመጠየቅ እንኳን ያልበቃ፣ ምህረት እንደሚገባው የማያምን ማንነት ኖሮኛልና አንተ ብቻ በምህረት አይኖችህ ተመልከተኝ፣ በይቅርታ እጆችህ ዳሰኝ፣ እስራቴን ፍታልኝ፣ በነፃነት ወዳንተ እቀርብ ዘንድ ፍቀድልኝ።"
እግዚአብሔር ያውቃል ነገር ግን እንዳላወቂ ይሆናል፣ ፈጣሪ ይመለከታል ነገር ግን ምንም እንዳላየ ይሆናል። እንዳዋቂነቱ ቢፈርድ፣ እንደተመለከተውም የሚቀጣ አምላክ ቢሆን ምድር ባዶ በሆነች ወደ ምደረበዳነትም በተቀየረች ነበር። በምህረቱ ብዛት እስካሁን አለን፣ በሃዘኔታው ለዛሬ በቅተናል፣ በፍቅሩ ብዛት የማይገባን ስፍራ ተገኝተናል። የምንከፍለው ባይኖረንም ማመስገን ግን እንችላለን፣ የምንሰጠው ባይኖረንም በርሱ ምህረት የዳነችውን ነፍሳችንን ግን ወደርሱ ማስጠጋት እንችላለን፣ ውለታውን መመለስ ባይቻለንም ወደቤቱ መመላለስ ግን እንችላለን። ከሚገባን በላይ ላከበረን፣ ከፍቅራችን በላይ ፍቅሩን በተግባር ላሳየን፣ ከኛ ተስፋ በላይ ሁሌም ተስፋ ለማይቆርጥብን አምላካችን እራሳችንን እናሳይ፣ ወደርሱ እንጠጋ፣ በእርሱ የተወደደ ለእኛም አትራፊ የሆነ ህይወት እንኑር።
ያማረ ለሊት ይሁንልን | 1 536 |
| 4 | ዛሬም ልቤ ኢየሱስ ኢየሱስ ይለኛል
ፍለጋው መቼ ይቆማል
እሱ የነፍሴ ዋስትናዋ ነው
እፈልገዋለው
እፈልገዋለው *4
1)አልፋ እና ኦሜጋ ዘላለማዊ ነው የሱስ
ባለፀጋ አምላክ ህይወት ያለው ከነትርፉ
እሱን ከመፈለግ ወደኃላ አልልም
እፈልገዋለው ፍለጋዬ (አይቆምም)*2
እፈልገዋለው*4
2) ያየልኝን ክብር ያዘጋጀልኝን አክሊል
እጋደላለሁኝ ማንም እንዳይወስድብኝ
እጠብቀዋለው እስከሞት ታምኜ
ድልን በሚሰጠኝ በስሙ (አምኜ)*2
እፈልገዋለው*4
3) ከዚ ከቁርበቴ ከስጋዬ ተለይቼ
ጌታዬን እስካየው ፊትለፊት በአይኖቼ
እሱን ከመፈለግ ወደኃላ(ፍፁም ቸል) አልልም
እፈልገዋለው ነፍሴ (አታክትም)*2
4) የፍጥረት መፍትሄ የነፍስ ሁሉ መዳኒት ነህ
ጌታ እና ንጉስ ነው አምላክ ሁሌ ሚፈለግ
በፆም በፀሎት በሩን አንኳኳለሁ
ዘንበል ይልልኛል ደጁን (እጠናለሁ)*2 | 2 101 |
| 5 | ትበልጣለህ ለምኜ ካገኘውት
እግዛብሄር ከአንተ ከእጅህ በረከት
ስታጠግብ አኑረህኛል ስታሳየኝ ተአምራት
በምህረትህ ዛሬ እስትንፋሴ አለች እኔ ጋር
ነግር ግን ከሆነልኝ ሁሉ ትበልጥብኛለህ ጌታ
ትበልጣለህ ለምኜ ካገኘውት
ትበልጣለህ ፀልዬ ከተቀበልኩት
ትበልጣለህ እኩያ አቻ የለህም
ትበልጣለህ ከነገሮቼ በላይ ነህ
ዘመናትን ለምኜ አልቅሼበት ነበር
በእምነትም በተስፋ ስጠብቅም ነበር
የኔ አምላክ አንተ እንባን አትረሳም
ከጠየቁኝ ቆዩ ብለህ አትዘነጋም
ሰጠህኝ አትረፍርፈህው አስገረምከኝ
ቤቴን ሞልተህው
በሰጠህኝ ፀጋ በረከት ኢየሱስ አንተን አመልካለው
ከስጦታዬም ሰጪውን አምላኬን አከብረበታለው
ትበልጣለህ.....
አዋርደዋለው ለክብርህ ሲሉኝ
በቤትህ እያለው ሌላ ምን ያደርጋል
አምላኬ የአንተነት ከሁሉ ይበልጣል | 1 946 |
| 6 | ታላቅ መንፈሳዊ ጉባኤ
እግዚአብሔርም በምድር ሁሉ ላይ ይነግሣል፤ በዚያ ቀን እግዚአብሔር አንድ፥ ስሙም አንድ ይሆናል።
ዘካርያስ 14፥9
በኢትዮጵያ ሐዋሪያዊት ቤተክርስቲያን የደቡብ ምስራቅ ኢትዮጵያ ሰበካ የሻኪሶ ቅርንጫፍ ሰበካ አመታዊ ጉባኤ በሻኪሶ እናት አጥብያ ቅጥር ጊቢ ውስጥ ይካሄዳል
ለ25ተኛው ዙር እንኳን በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን ጉባኤውም ከሐምሌ 24-26/2018ዓ.ም ማለትም ዓርብ, ቅዳሜ እና እሁድ ሙሉ ቀን ይካሄዳል የበረከቱ ተካፋይ ይሆኑ ዘንድ ሁላችሁም ተጋብዛችኋል 🙏
ኑ የእግዚአብሔርን ማዳን እዩ... | 2 069 |
| 7 | New apostolic song
Singer:ዲያቆን ምህረቱ ዼጥሮስ
እደነቃለው በህይወት
አብረሃም ባያውቀኝ
አለኝ በስሜ የጠራኝ
ቸል አልልም የመዳኔን ነገር
ስጋ እና አለም ተውኝ
ከእናንተ ጋራ አልመክርም
እደነቃለው በህይወት መፃፍ ላይ
እደነቃለው ስሜ ተፅፏል
እደነቃለው መዳኔ
ሳያንሰኝ ልጅ አደረገኝ
የማያረጀውን አዲሱን ልብሴን
በጥምቀት አለበሰኝ አይደሁም እራቁቴን
ውበቴ ሆነ እሱ ሲገለጥ(ሲመጣ) በክብር
እኔም እታያለው ደምቄ ከእርሱ ጋር
አብረሃም....
ከጨለማ ፍርሃት አወጣኝ
እንድሆን የእግዛብሄር ወገን
ከፅድቅእና ሰላም መሃል
መረጠኝ አለም ሳይፈጠር
እደነቃለው...
እንደፍቃዱ ሁሉን የሚሰራ
ልጁ አደረገኝ በክርስቶስ ስራ
ተቀብሎኝ ከክብር ጋራ
አስቀመጠኝ ሰማያዊ ስፍራ
እደነቃለው...
በማይወሰን ደስታ ሀገር
በሚሰነብት ሰላም ሀገር
የሚሞተው በህይወት ሲቀየር
በኢየሱስ ያለን መዳን በክብር ስናገኝ
እንነግሳለን ዘላለም ከእርሱ ጋር*4 | 2 739 |
| 8 | ፍቃድህን የሚያደርግ
አለምም ምኞቱም በከንቱ ያልፋሉ
እንደጠዋት ጤዛ ሆነው ይደርቃሉ
ዘላለም ይኖራል ፍቃድህን የሚያደርግ
አስተውሎ ሚኖር የሚሄድ በአንተ ህግ
ፍቃድህ ተገልጦ
አንተን የሚያስደስት በመውጣት መግባቴ
የአንተ ፍቃድ ይሁን ሁል ጊዜ በህይውቴ
በመንገድህ ምራኝ እየሱስ አባቴ
መልካም መልካሙን የምታስብል
ህይወት አቅጣጫዬን አንተ አሳምርልኝ
መልካም ነህ *2 መልካም እየሱስ
አላማህ በኔ ላይ ፍቅር ነው እና
ያቅዱስ መንፈስህ በእኔ ይፈሰስ እና
ይምራኝ ያሳየኝ ክቡር ፍቃድህን
በሀሳብህ ኖሬ ከጥፋት እንድድን
ተገልጦ ይታይ እያበራ
ፍቃድህ በልቤ ተራራ
አላማህ በህይወቴ እንዲታየኝ
ፍቃድህን ጌታ አስታውቀኝ
እኔ ያንተ ብቻ ያንተ ብቻ ነኝ
ማንም ምንም አይሰልጥንብኝ
እኔ ያንተ ብቻ ያንተ ብቻ ሆኛለው
ፍቅርህ ይግዛኝ ያበርታኝ | 2 591 |
| 9 | ፈቃድህ ፈቃዴ ይሁን!
ከራስ ጋር ንግግር፦ "ለራሴ የማውቅ ይመስለኝ ነበር ነገር ግን በፍፁም አላውቅም፤ የሚሆነኝን መምረጥ የምችል፣ የሚገባኝን የማደርግ ይመስለኝ ነበር። ነገር ግን ምርጫዬ ስህተት ነበር፣ ድርጊቴ መጥፎ ነበር። እንግዲ ትናንት ተሳሳትኩ፣ ትናንት ወደቅኩ፣ በማይሆንኝ መንገድ ተጓዝኩ፣ የማይሆነኝን ተግባር ፈፀምኩ ዛሬ ግን ያንተን ፍቃድ ላስቀድም ወደድኩ፣ አሁን ግን ባንተ ቀዳሚነት ልከተልህ ወሰንኩ። ለራሴ የማስበው ትልቅ እንደሆነ አስብ ነበር አንተ ያሰብክልኝን ስመለከት ግን ምንያህል ለራሴ በትንሹ እንዳሰብኩ ተረዳው። በእውቀቷ የምትመካ ነፍስ ከእውቀቷ በላይ ጠላት የላትም፣ ለራሴ ከእኔ በላይ የሚውቅ የለም ያለ ሰው የፈጣሪውን በረከት የሚርቅ ሰው ነው። ብዙ ጊዜ "እኔ ያልኩት ብቻ ካልሆነ፣ የእኔ ምርጫ ብቻ ነው ትክክል፣ በእኔ ህይወት ማንም አይመለከተውም" ብዬ ፎክሬ ነበር። የሆንኩትን ስሆን የደረሰብኝ ሲደርስብኝ ግን መታረምን መርጬያለሁ፣ ዳግም ላለመውደቅ ራሴን ጠብቄያለሁ። ብቻዬን እንደሆንኩ ሳስብ የመንፈስ ድካሜ ሊጥለኝ ይሞክራል፣ ያንተ ፍቃድ አለማስተዋሌ ሲታወቀኝ ተነሳሽነቴ ሁሉ ይጠፋል።
ፈቃድህ ፈቃዴ ይሁን፤ ምርጫህ ምርጫዬ ይሁን፣ ፍላጎትህ ፍላጎቴ ይሁን። አንተ እጄን ይዘህ ምራኝ፣ በጨለማው በዱር በገደሉ፣ አቀበት ቁልቁለቱ በአውላላው ሜዳ ላይ፣ በችግር በመከራ በምቾቱ በእጦቱ ሁሉ አንተ ከፊቴ ቅደምልኝ። ያ ፍፁም ሃሳብህ በእኔ ላይ ይደረግ፣ ያ ምስራችን የሚያመጣልኝ፣ ብርታትን የሚድለኝ፣ ውስጤን በሃሴት የሚሞላው፣ ልቤን የሚያሞቀው ምርጫህ በእኔ ላይ ይሁን። ከእቅፍህ ወጥቼ ዳግም መሰቃየትን አልፈልግም፣ ህግህን ጥሼ እንደገና ዋጋ መክፈል አልፈልግም። ምራኝ ብዬ እጄን ሰጥቼሃለሁ፣ መንገድህ መንገዴ ይሁን ብዬ ወዳንተ ቀርቤያለሁ። ውሳኔዬ ትልቅ ነውና እንዲሁ መፈፀም ቢከብደኝ እንኳን አንተ በእኔ ላይ አድረህ ፈፅምልኝ። ለዓመታት የታሰርኩበት መጥፎም ጥሩም ልማድ አለኝ። ከእሱም በአንዴ ነቅዬ መውጣት ይሳነኝ ይሆናል፣ አንተ ግን እርሱን ማድረግ ትችላለህና ነቅለህ አስወጣኝ፣ እኔንም ገፍትረህ ወደ መረጥክልኝ ጎራ ቀላቅለኝ። አቅሜ አንተ ነህ፣ ብርታቴ አንተ ነህ።"
ረጅም ርቀት ሩቅ መንገድ በራስህ ምርጫ በራስህ ውሳኔ ተጉዘሃል፣ ያለማንም ጣልቃገብነት፣ ያለማንም አስገጅነት በራስህ ፍቃድ ብዙ ስህተቶችን ፈፅመሃል፣ ዛሬ ላይ ልታነሳቸው ይቅርና ልታስባቸው እንኳን የማትደፍራቸውን ተግባራት ፍፅመሃል። ምርጫና ውሳኔዎችህ ላይ የአምላክ ፍቃድ፣ የእርሱም ጣልቃገብነት ቢኖርበት ዛሬ በትናንት ምርጫዎችህ ባላፈርክ፣ ስራዎችህንም ለመናገር ባላፈርክ ነበር። ማንም ሰው መንፈሱ ሲደሀይ ስጋው መራመድ ያቅተዋል፣ ውስጡ በባዶነት ሲሞላ ሰላምና መረጋጋት ይርቀዋል። መንፈሳዊ ህይወትህን ችላ ብለህ፣ ከፈጣሪህ ጋር ያለህን ግንኙነት ረስተህ፣ ዓለምና ዓለምን ብቻ መርጠህ በፍፁም ረፍትና ሰላምን ልታገኝ አትችልም። መንፈሳዊ እድገት የሌለበት ህይወት ባዶ ነው፣ እግዚአብሔር አምላክ ያልባረከው ቤት ተስፋቢስ ነው። ያለምንም ክፍያ ያገኘሀውን ጊዜ ለሰጪው ለመስጠት አትሰስት፣ ከአምላክህ ጋር በፍቅር ውደቅ፣ የእጆችህ ስራዎችም ይባረኩልህ ዘንድ ፍላጎትህን በርሱ ፍቃድ ላይ አፅና።
ግሩም ድንቅ ቀን ይሁንልን! | 2 644 |
| 10 | "በዚህ ዘመን ከእግዚአብሔር ከሚያርቁን ነገሮች አንዱ ሀጢያትን Normalize ማድረግ ነው"
ከእግዚአብሔር የሚያርቁን ብዙ ነገሮች አሉ። በመጽሐፍ ቅዱሳችን ውስጥ ቅዱስ ሐዋርያው ጳውሎስ ለገላትያ ሰዎች በጻፈው መልዕክት ውስጥ የተጻፉት ከጌታ ኢየሱስ የሚያርቁንና ወደ መንግሰት ሰማይ የማያስገቡ ጉዳዮች እንደሆኑ በአጽንኦት ይገልጻል።
ገላትያ 5
19 የሥጋ ሥራም የተገለጠ ነው እርሱም ዝሙት፥ ርኵሰት፥
20 መዳራት፥ ጣዖትን ማምለክ፥ ምዋርት፥ ጥል፥ ክርክር፥ ቅንዓት፥ ቁጣ፥ አድመኛነት፥
21 መለያየት፥ መናፍቅነት፥ ምቀኝነት፥ መግደል፥ ስካር፥ ዘፋኝነት፥ ይህንም የሚመስል ነው። አስቀድሜም እንዳልሁ፥ እንደዚህ ያሉትን የሚያደርጉ የእግዚአብሔርን መንግሥት አይወርሱም።
እነዚህ ከላይ የተዘረዘሩ ጉዳዮች ከእግዚአብሔር የሚያርቁን ናቸው። ሆን ብለን ካልሆነ በስተቀር ብዙ ጊዜ ካስተዋልን መጥፎ ነገሮችን ስናደርግ ህሊናችን "ተው" የሚል ደወል ያቃጭልብናል። ሆኖም ግን እኛ ሰዎች ሀጢያትን Normalize ከማድረጋችን የተነሳ ህሊናችን ለመጥፎ ድርጊታችን ምላሽ መስጠት ያቆመ ይመስላል። በተደጋጋሚ መጥፎ ማድረግ ለለመደው ሰው ህሊናው ይደነዝዝና መጥፎው ነገር ሲያደርግ ምንም አይመስለውም። ከእግዚአብሔር ጋር እንደሚያጣለው፡ እግዚአብሔርም እንደሚጸየፍ እያወቀ ከማድረግ ወደኋላ አይልም። ምክንያቱ ደግሞ እግዚአብሔር የሰጠው በጎ ህሊናው የሚለውን እየሰማ እንዳልሰማ ስላለፈው ነው።
"እግዚአብሔር አምላክም ምን ያህል ኃጢአትን እንደሚጸየፍ ለሰው ለማሳየትና ሰውም ኃጢአተኛነቱን አምኖ 'የአዳኝ ያለህ!' ብሎ እንዲጮኽ ብዙ ነገሮችን አድርጎአል። አንደኛው በጎ ህሊና... " ( ቢሾፕ ደጉ ከበደ - የመዳን እውቀት ገጽ 13 )
ስለዚህ ይኼ ህሊና በተደጋጋሚ ለሚሰጠን ማስጠንቀቂያ የሚገባውን ምላሽ ካልሰጠን የሆነ ጊዜ ላይ ያ የምናደርገውን መጥፎ ነገር እንደ ትክክል ይወስደዋል። ብዙ ጊዜ በመጥፎ ሁነቶች የተረገጠ ህሊና ከእግዚአብሔር ጋር አያኖርም ለሰውም ሰላም አይሰጥም። በዚህ ዘመን ከእግዚአብሔር ከሚያርቁን ነገሮች አንዱ ሀጢያትን Normalize ማድረግ ወይም አቅልሎ ማየት ነው። ኃጢአትን እግዚአብሔር በሚያይበት መልክ ብናይ መልካም ነው። ኃጢአት በእግዚአብሔር ዘንድ እጅግ የተጠላ የማይወደድ መሆኑን ለውስጣችን አጥብቀን መናገር ያስፈልጋል። የኃጢአት ትንሽ የለም። የሰው ጻድቅ የለም ሁላችንም የእግዚአብሔር ክብር ጎድሎብናል።
ሮሜ 3:23 "ሁሉ ኃጢአትን ሠርተዋልና የእግዚአብሔርም ክብር ጎድሎአቸዋል፤ "
ሆኖም ዕለት ዕለት በፊቱ ምህረት እየለመንን ራሳችንን እያነጻን ወደፊት መሮጥ የብልህነት መንገድ ነው። ኃጢአት መስራት አይቅለልብን።
ቅዱስ ቃሉ እንደሚለን ቀኑን ሙሉ እግዚአብሔርን በመፍራት መኖር ያስፈልጋል። እግዚአብሔርን የሚፈራ ሰው ኃጢአት መስራት እጅግ ይከብደዋል። ኃጢአት መስራት አይቀልበትም፡ ለህሊናው ቶሎ የሚገባውን ምላሽ በመስጠት ራሱን ማሸሽ ካለበት ነገር ያሸሻል። አንዳንድ ነገሮችን በመጋፈጥ አናሸንፋቸውም በመሸሽ እንጂ። ዝሙትን በመሸሸ ( 1ኛ ቆሮ 6:18) እናሸንፋለን፡ ብንጋፈጠው እንወድቃለን።
እንግዲህ ጌታ ኢየሱስ ከክፉ ስራቸው አልመለስ ብለው እምቢ ያሉትን ለማይረባ አዕምሮ አሳልፎ እንደሚሰጥ በቃሉ ላይ በግልጽ ተጽፏል። (ሮሜ 1:28)
በዚህ ዘመን ኃጢአትን It is okay (ምንም ማለት አይደለም ) ማለት የተለመደ እየሆነ መጥቷል። ሰው እርግጠኛ ባልሆነበት ነገር ነገ በንስሃ እመለሳለሁ ፤ ዛሬ ኃጢአት ብሰራበት ምን አለበት? ይላል። ። ድሮ ድሮ ነውር የምንላቸው ነገሮች በአደባባይ ቀልለው ሲሰጡ ይስተዋላሉ። ዘመኑ እግዚአብሔር የማይፈራበት፡ ሰው የማይታፈርበት ከሆነ ሰነባብቷል። ግን አሁንም እግዚአብሔር የምህረት እጁን ዘርግቶ እየጠበቀን ስለሆነ እንመለስ። በቃ የቀድሞውን ነገር እንተወው። እግዚአብሔር የእንደገና አምላክ ነው። በየትኛውም ኃጢአት ውስጥ ብንሆንም አንድ እርግጠኛ የምሆነው ነገር ከተመለስን እግዚአብሔር ይመለሳል፤ የምህረት አምላክ ነውና። በየቀኑ ህሊናህ እየወቀሰህ እማይሆን ህይወት ውስጥ ያለህ፡ ኢየሱስ ና ይልሃል። የወደቀ ይነሳል፡ የሳተ ይመለሳል ይልሃል። ተመለስ!
@MARANATHAWOCH
@MARANATHAWOCH | 3 395 |
| 11 | እግዚአብሔር እረኛዬ ነው፥ የሚያሳጣኝም የለም። በጥልቅ ማብራሪያ አብራራልኝ! እግዚአብሔር ያስተማረኝን ላካፍላችሁ ቤተሰብ
ይህ ቃል በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ እጅግ በጣም ከሚታወቁትና የሰውን ልብ በሰላም ከሚሞሉት ክፍሎች አንዱ የሆነው የመዝሙረ ዳዊት 23፥1 ቃል ነው። ንጉሥ ዳዊት በልጅነቱ ራሱ እረኛ ስለነበረ፣ የእረኛንና የበግን ጥልቅ ግንኙነት በሚገባ ያውቅ ነበር።
ይህንን ቃል ይበልጥ ለመረዳት በሁለት ዋና ዋና ክፍሎች ከፍለን በጥልቀት ማየት እንችላለን፡
1. "እግዚአብሔር እረኛዬ ነው"
ይህ ሐረግ ስለ ፈጣሪ ማንነት እና ከሰው ልጆች ጋር ስላለው ግንኙነት ጥልቅ መልእክት ያስተላልፋል፡
የግል ግንኙነት (Personal Relationship)፦ ዳዊት "እግዚአብሔር እረኛችን ነው" አላለም፤ ይልቁንም "እረኛዬ" በማለት የግል አድርጎታል። ይህ የሚያሳየው ፈጣሪ የዓለም ሁሉ ጌታ ቢሆንም፣ ከእያንዳንዱ ሰው ጋር ቅርብ የሆነ የግል ዝምድና (Relationship) እንዳለው ነው።
ጥበቃና እንክብካቤ (Protection and Care)፦ በጎች በተፈጥሯቸው ራሳቸውን መከላከል የማይችሉ፣ ደካማ፣ አቅጣጫ የሚጠፋቸውና ሙሉ በሙሉ በእረኛቸው ላይ ጥገኛ የሆኑ ፍጥረታት ናቸው። እረኛ ከሌላቸው በቀላሉ ለአደጋ ይጋለጣሉ። እኛም የሰው ልጆች በሕይወት ጎዳና ስንጓዝ የፈጣሪ ጥበቃ፣ ምሪት እና እንክብካቤ እንደሚያስፈልገን ያሳያል። እግዚአብሔርም እንደ መልካም እረኛ አይተወንም፣ ከአደጋ ይጠብቀናል።
አመራር (Guidance)፦ እውነተኛ እረኛ በጎቹን ከኋላ ሆኖ በዱላ አይነዳም፤ ከፊት ሆኖ እየመራ ይሄዳል እንጂ። እግዚአብሔርም በሕይወታችን ውስጥ ከፊታችን እየቀደመ፣ የተሻለውንና ሰላም ያለበትን መንገድ ይመራናል።
2. "የሚያሳጣኝም የለም"
ይህ የቃሉ ክፍል ደግሞ እግዚአብሔርን እረኛ በማድረግ የሚገኘውን ውጤት ያሳያል፡
እውነተኛ እርካታ (Contentment)፦ "የሚያሳጣኝ የለም" ማለት "የምመኘውን የቅንጦት ነገር ሁሉ አገኛለሁ" ማለት አይደለም። ይልቁንም፣ "ለሕይወቴ እና ለመንፈሴ የሚያስፈልገኝን ሁሉ እግዚአብሔር በጊዜው ስለሚሰጠኝ፣ በውስጤ ሙሉ ነኝ፤ ምንም የጎደለኝ ነገር የለም" የሚል የጥልቅ እርካታ መግለጫ ነው።
ከጭንቀት ነጻ መሆን (Freedom from Anxiety)፦ በግ እረኛው አጠገቡ እስካለ ድረስ ስለ ቀጣዩ ቀለቡም ሆነ ስለሚጠጣው ውሃ አይጨነቅም፤ ኃላፊነቱን ሁሉ ለእረኛው ትቶ ያርፋል። እግዚአብሔርን እረኛው ያደረገ ሰውም ስለ ነገ ከመጨነቅ፣ ከፍርሃት እና ከመከራ ስጋት ነጻ ይሆናል፤ ምክንያቱም ፈጣሪው ሁሉንም እንደሚያዘጋጅለት ሙሉ እምነት አለውና።
ሁለንተናዊ አቅርቦት (Holistic Provision)፦ እረኛ ለበጎቹ መብልና መጠጥ ብቻ ሳይሆን፣ ሰላማዊ ማረፊያ፣ የቆሰለውን መፈወስ፣ የጠፋውን መፈለግን ሁሉ ያደርጋል። እግዚአብሔርም መንፈሳዊ ሰላምን፣ ጤናን፣ ጥበብንና በሕይወት የሚያስፈልገንን ሁሉ በሙላት ይሰጠናል።
ማጠቃለያ
በአጠቃላይ "እግዚአብሔር እረኛዬ ነው፥ የሚያሳጣኝም የለም" የሚለው ቃል የፍጹም መታመን (Trust) እና የሰላም (Peace) መግለጫ ነው። እኛ አቅም ባይኖረንም፣ ሁሉን ቻይ የሆነው አምላክ ሕይወታችንን እንደሚመራና የሚያስፈልገንን ሁሉ ሞልቶ እንደሚያሳርፈን የሚያረጋግጥ ጥልቅ የሕይወት መርህ ነው።
@MARANATHAWOCH
@MARANATHAWOCH | 3 668 |
| 12 | #Call_conference
🕎እግዚአብሔር በምድር ሁሉ ላይ ይነግሣል በዚያን ቀን እግዚአብሔር አንድ ስሙም አንድ ይሆናል ትንቢተ ዘካርያስ 14፡9
✍#በኢትዮጵያ ሐዋርያዊት ቤቴክርስትያን በአለታ ቅርንጫፍ ሰበካ አለታ ጩኮ ከተማ ንዑስ መሐል ከተማ አጥብያ 3ተኛ ዙር ዓመታዊ ኮንፈሪንስ ሐምለ17-19/2018ዓ/ም በታላቅ ድምቀት ይካሄዳል እርስዎስ የበርከት ተከፍይ እንድሆኑ በአክብሮት ተጋብዘዋል ፡፡
አድራሻ:- አለታ ጩኮ ከግብርና ፅህፈት ቤት ትንሽ ወረድ ብሎ ነው
👉 እንወርሳለን
👉እናጠምቃለን
👉እንበዛለን፡፡
ኑ ሁላችሁም ተጋብዛችኃል🙏 | 3 495 |
| 13 | ላንተ ያልዘመርኩ ለማን ልዘምር ነው
ዝም አያሰኝም ውለታህ ብዙ ነው
እንካ ምስጋና ተቀበል ጌታዬ
ታመልክሃለች(አመልክሃለሁ) ወዳሃለች ነፍሴ
ዘምራለው እልል እላለው
ክበር እንጂ ምን እላለው
ምን እላለው
ክበር እንጂ *2
ምኔን ልስጥህ መዝሙር እንጂ | 4 436 |
| 14 | The Lord reigns
Let the earth rejoice
Let the earth rejoice
Let the earth rejoice
Let the people be glad
That our God reigns
A fire goes before Him
And burns up all His enemies
The hills melt like wax
At the presence of the Lord
At the presence of the Lord
The heavens declare
His righteousness
The people see His glory
For You O Lord are exalted
Over all the earth
Over all the earth
Our God reigns
Our God reigns
Hear O Israel
The Lord thy God is one God
And thou shalt love the Lord thy God
with all of thy heart
And thou shalt love the Lord thy God
with all thy soul
And thou shalt love the Lord thy God
with all of thy mind
And thou shalt love the Lord thy God
with all of thy strength
Hear O Israel
The Lord thy God is one God | 5 308 |
| 15 | The Lord reigns
Let the earth rejoice
Let the earth rejoice
Let the earth rejoice
Let the people be glad
That our God reigns
A fire goes before Him
And burns up all His enemies
The hills melt like wax
At the presence of the Lord
At the presence of the Lord
The heavens declare
His righteousness
The people see His glory
For You O Lord are exalted
Over all the earth
Over all the earth
Our God reigns
Our God reigns
Hear O Israel
The Lord thy God is one God
And thou shalt love the Lord thy God
with all of thy heart
And thou shalt love the Lord thy God
with all thy soul
And thou shalt love the Lord thy God
with all of thy mind
And thou shalt love the Lord thy God
with all of thy strength
Hear O Israel
The Lord thy God is one God | 1 |
| 16 | በ7 ዓመቱ ንጉሥ ሆኖ የነገሠውና እግዚአብሔርን ደስ የሚያሰኝ ነገር ያደረገው ታናሹ የይሁዳ ንጉሥ ማን ነው? | 50 |
| 17 |
✍ማዕበሉ በውስጥህ ሲነሳ…✅
አንዳንድ ጊዜ የምትዋጋው ማዕበል በባሕሩ ላይ አይደለም፤ በልብህ ውስጥ ነው። አእምሮህ ያለ እረፍት ይሮጣል፤ ልብህ በሸክም ይከብዳል፤ ሐሳቦችህም እንደ ማዕበል እየተፋጠጡ ሰላምህን ይሰርቃሉ። የሕይወት ጫጫታ ሲበዛ፣ ሁሉም ነገር ለአፍታ ቆሞ ብታርፍ ትመኛለህ፤ ነገር ግን ያንን እረፍት ከየት እንደምታገኘው አታውቅም።
ከውጭ የሚታየው ማዕበል አንዳንድ ጊዜ ያስፈራል፤ ነገር ግን በውስጥ የሚነሳው ማዕበል ይበልጥ ያደክማል። ሰዎች ፈገግታህን ያያሉ፤ እግዚአብሔር ግን ዝም ብሎ የሚጮኸውን ልብህን ያያል።
ነገር ግን የውስጥህ ጩኸት ከፍ ብሎ በሚሰማበት ሰዓት እንኳን፣ ከዚያ ሁሉ በላይ የሚናገር አንድ ድምፅ አለ፤ እርሱም በማዕበል ላይ ሥልጣን ያለው የክርስቶስ ድምፅ ነው።
መጽሐፍ ቅዱስ በማርቆስ 4፥39 እንዲህ ይላል፦
ነቅቶም ነፋሱን ገሠጸው ባሕሩንም፦ ዝም በል፥ ፀጥ በል አለው። ነፋሱም ተወ ታላቅ ፀጥታም ሆነ።
በዚያች ቀን ኢየሱስ ያረጋጋው ባሕር ብቻ አልነበረም፤ በደቀ መዛሙርቱ ልብ ውስጥ የነበረውን ፍርሃትም አረጋጋ። ዛሬም ያው ጌታ በሕይወታችን ውስጥ እየሠራ ነው። ወደ ቃሉ በእምነት በቀረብን ቁጥር፣ ያ ቃል የምናነበው ጽሑፍ ብቻ ሳይሆን በነፍሳችን ውስጥ የሚናገር የሕይወት ድምፅ ይሆናል።
💡የእግዚአብሔርን ቃል ስናነብ፣ ቃላትን ብቻ አናነብም ፤ ፍርሃትን የሚያስታግስ፣ ተስፋን የሚያነሣ፣ ድካምን የሚያበረታ፣ ሰላምን ወደ ልብ የሚተነፍስ የጌታን ድምፅ እንሰማለን። መጽሐፍ ቅዱስ መረጃን ብቻ አይሰጥም፤ ሕይወትን ይሰጣል። እውቀትን ብቻ አይጨምርም፤ ልብን ይለውጣል።
ምናልባት ዛሬ የምንፈልገው ተጨማሪ መልሶችን አይደለም። የምንፈልገው እረፍት ነው። ተጨማሪ መፍትሔዎችን ሳይሆን፣ ጌታ "እኔ እዚህ አለሁ፤ አትፍራ፤ ከአንተ ጋር ነኝ" የሚል መገኘቱን ነው።
ስለዚህ ማዕበሉን ችላ አንበለው፤ ነገር ግን ለእርሱ አንገዛ። ወደ እግዚአብሔር ቃል እንሽሽ። ያ ሕያውና ኃይለኛ ቃል ለነፍሳችን መልሕቅ፣ ለእምነታችን ጽናት፣ ለነገያችም ተስፋ ይሆናል።
ምክንያቱም አንዳንድ ጊዜ ትልቁ ተአምር ማዕበሉ መቆሙ አይደለም፤ ማዕበሉ ገና በዙሪያችን እያለ እንኳን ልባችን በክርስቶስ ሰላም ተሞልቶ መቆሙ ነው።
✍አእምሮንም ሁሉ የሚያልፍ የእግዚአብሔር ሰላም ልባችሁንና አሳባችሁን በክርስቶስ ኢየሱስ ይጠብቃል።
ወደ ፊልጵስዩስ ሰዎች 4:7
🌻🌻ብሩህ ቀን ይሁንላችሁ🌻🌻
@MARANATHAWOCH
@MARANATHAWOCH | 4 716 |
| 18 | ግጥም
አሳዳጇን እኔ
ከልቡ ራራልኝ አዘነልኝ ለኔ
አይኖቼንም ከፍቶ ሆነኝ ብርሃኔ
ፍቅሩም አሸነፈኝ የሀያሉ ጌታ
በምህረት አወጣኝ ከዛ ከሞት ቦታ
ማንነቴን አይቶ ያለብኝን ሀጥያት
ሊያድነኝ ወደደ መጣ በምህረት
አሳዳጇን እኔን በፍቅሩ ለውጦ
ከቀጣውም ይልቅ ምህረቱን አብልጦ
ልጁ አደረገኝ ሀጥያቴንም ምሮ
አዲስ ሰው አረገኝ አሮጌውንም ሽሮ
በፍቅርህ ተገዝቼ ስላንተ አወራለው
አንተኝ እንዳገለግል ሁለንተናዬን ባርከው
ነፃ አውጥተህኛል ከሀጥያት ባርነት
እጄን ይዘህ መራህኝ ወደ እውነት መንገድ
ፍፁም አልረሳውም ያለፈ ህይወቴን
ምህረት ተደርጎልኝ ዛሬ ላይ መቆሜን
እይኖቼ ተከፍተው ብርሃን ማየቴን
ሳኦልነቴ ተቀይሮ ጳውሎስም መባሌን
ፍፁም አልረሳውም ያደረክልኝን
ለአሳዳጇ ለኔ ምህረት የሆንክልኝን
ከነሀጥያቴ ምህረት የሆንክልኝ
ሞቴም ተቀይሮ ህይወት የሰጠህኝ
አገለግላለው ቆሜ በመሰውያ
እመሰክራለው ስለአንዱ ጌታ
✍️ እህት እያኤል | 5 430 |
| 19 | ቀንህን ያለ ኢየሱስ አትጀምር
ዓለምን ከመጋፈጥህ በፊት ዓለምን ወደ ፈጠረው ኢየሱስ ፊት ቅረብ። የቀኑ ጫናና የሕይወት ጉዳዮች ትኩረትህን ከመውሰዳቸው በፊት ልብህን ለእርሱ ስጥ።
ጸሎትን ሁሉም ነገር ከተበላሸ በኋላ የምትመለስበት የመጨረሻ አማራጭ አታድርገው።
ከማንኛውም ነገር በፊት የመጀመሪያ ምላሽህ ይሁን።
ምክንያቱም በቀንህ ውስጥ የምትገጥማቸው ብዙ ጦርነቶች ቀኑ ሳይጀምር በስውር ከኢየሱስ ፊት በምታሳልፈው ጊዜ አስቀድመው ይሸነፋሉ።
በኢየሱስ ፊት የምታሳልፈው አንድ አፍታ ሁሉንም በራስህ ለመቆጣጠር ከምታደርገው የአንድ ቀን ጥረት የበለጠ ሰላም ይሰጥሃል።
👉ቃሉ ለውሳኔዎችህ ጥበብን ይሰጥሃል።
👉መንፈሱ በድካምህ ውስጥ ኃይልን ያበረታሃል።
👉መገኘቱ ሁኔታዎች ሊነጥቁህ የማይችሉትን ሰላም ይሞላሃል።
ስለዚህ
👉ስልክህን ከማንሳትህ በፊት መጽሐፍፍ ቅዱስህን አንሳ።
👉በሰዎች አስተያየት ውስጥ ከመዘፈቅህ በፊት የእግዚአብሔርን ድምፅ አዳምጥ።
👉የዛሬን ሸክሞች ከመሸከምህ በፊት በኢየሱስ እግር ስር አኑራቸው።
ያልተረጋጋ ቀንን ለመጋፈጥ ከሚያዘጋጅህ ነገር ሁሉ የተሻለው ፈጽሞ ከማይለወጠው ኢየሱስ ጋር ጊዜ ማሳለፍ ነው።
ምክንያቱም ቀንህን ከእርሱ ጋር ስትጀምር ቀኑን ብቻህን አትገጥመውም
👉በመንፈሱ ትመራለህ፣
👉በጸጋው ትሸፈናለህ፣
👉በመገኘቱ ትበረታለህ፣
እናም የሚመጣው ምንም ቢሆን ከፊትህ የሄደው እግዚአብሔር አስቀድሞ በዚያ እንዳለ በእምነት ትጓዛለህ።
መልካም ቀን ተመኘሁላችሁ🙏🙏🙏
@MARANATHAWOCH | 5 082 |
| 20 | እያባበለኝ
ባጠፋ ብበድል እንኳን ከቶ አልተወኝም
በምክሩ ልቤን ለወጠው እያባበለኝ
ባለማወቅ ሚሮጥ እግሬ ለሞት ስጠራ
ሁልግዜ ይመልሰኛል ጌታዬ እየመራ
እያባበለኝ *2 እግሮቼ ፀኑ ይህው አቆመኝ
እያባበለኝ*2 በቤቱ አለው ስለመከረኝ
አውቃለው ምን እንደሚያደርግ ምን እንደሚያስብልኝ
ጌታ ያለው ይሁንልኝ ከቶ አልጠራጠረውም
መልካም ነው በኔ አላማው
ፍቅር ነው የእርሱ ነገር
ካሰቀመጠኝ ቦታ አልኖርም
ትላንትን ዛሬ ስደግም
ሁልጊዜ እያባበለኝ
እንዴት ያለ ቸር ወዳጅ ነው
ልቤን በምክሩ የመለሰው
ጌታዬን እወደዋለው
በብዙ የቅኖች መንጋ የጠፋ አንዱን ፍለጋ
ክብሩን ጥሎ ወርዶ የጠራኝ
እኔ ስሆን ሀጥያተኛ ፊቱን ተግቼ ምፈልግ
እርሱ ነው ደጄን የጠናው | 4 524 |
