cookie

Мы используем файлы cookie для улучшения сервиса. Нажав кнопку «Принять все», вы соглашаетесь с использованием cookies.

avatar

በክርስቶስ ( in christ)

Who is ownership of kingdom በዚህ ቻናል መንፈሳዊ አገልግሎት እና ጉዳዬች ላይ ይተኮራል @ownkin

Больше
Рекламные посты
700
Подписчики
+224 часа
+47 дней
+2430 дней

Загрузка данных...

Прирост подписчиков

Загрузка данных...

የመገኘቱ ስሜት ውጤቱ ምንድን ነው? አንድ በጽኑ የምንፈልገው ነገር ሲገኝ በመጀመሪያ የሚሰማን ስሜት ከዚያ ካገኘነው ነገር ምንነት አንጻር የደንነት (ሴኪዩሪቲ) ስሜት ነው፣ ቤት ብንገዛ የሚሰማን የረፍት ስሜት መኪና ስንገዛ ከሚሰማን ይለያል፣ የናፈቅነውን ሰው ስናገኝ የሚሰማን የሸሸነውን ሰው ስናገኝ ከሚሰማን ይለያል፣ እግዚአብሔርን ማግኘት ወይም በህልውናው ውስጥ መገኘት ስሜቱ በምድር ላይ ካሉ ስሜቶች ሁሉ የተለየነ ነው፣ ዓይነቱም ብዙ ነው። ስለዚህ እግዜር ሲገለጥ ምን ይሆናል? አናውቅም- ብዙ ነገር ነው የሚሆነው ሲሆን ብቻ ነው የምናውቀው እግዚአብሔር እንደ እኛ አቪየስ አይደለም። ለአዳም ሲገለጥ ራቁትነቱን አሳየው - ለአብርሃም በድምጽ ተገልጦ አገር አስኮበለለው፣ ለሙሴ ተገልጦ ፈርቶ ወደ ሸሸበት ከአንዲት በትር ጋር መለሰው፣ ለያቆብ ተገልጦ የሚያስነክስ በረከት ባረከው፣ ለዮሴፍ ተገልጦ አገር ከችጋር የሚያድን ሕልም አሳየው፣ ለኢሳይያስ ተገልጦ በኅጢአት ወቀሳ መሞቴ ነው አሰኘው፣ ለዮሐንስ መጥምቁ ተገልጦ የምወደው በእርሱ ደስ የሚለኝ .. ብሎ ስለ ልጁ መሰከረ.. በደብረ ታቦር ተገልጡ ሶስቱንም እዚህ እንቅር አሰኛቸው፣ ለጳውሎስ ተገልጦ ዐይኑን አሳወረው፣ መልሶም አበራው ለጴጥሮስ ተገልጡ ከእስርቤት አወጣው፣ ለዮሐንስ ተገልጦ ሩኹን አሳተው …ስለዚህ ሪስክ የሌለው የእግዚአብሔር መገለጥ የለም! በዚህ ሁሉ ግን ተዝናንተው የተገለጠላቸው የሉም። የእግዚአብሔርን ህልውና አለ እና የለም በሚል የሚጠየቅ አይደለም - እኛ ዘንድ ስሜቱና ንቃቱ ነው የሚለዋወጠው፣ ለዚህ ነው በአንድ ጕባኤ እንኳን አንድ ላይም ሆነን አንዳንዶች የመገኘቱን ስሜት ተለማምደው ሌሎች ግን ያ የመንፈስ ስሜት የማይኖራቸው፣ ከእግዜር ጋር ልምምዳችን ቅርርባችን፣ መፈለጋችን፣ መጸለይ ማንበባችን በዳበረ ቍጥር የመገኘቱን ስሜት ይበልጥ እንረዳዋለን። ኤልሣዕ ለብላቴናው ኅልዎቱ የመለኮቱ የሰራዊቱ እንዲታየው ዐይኑን አብራ አለው ልዩነቱ የኅልዎቱ መኖር እና አለመኖር ሳይሆን የዐይን ማየትና አለማየት ነው - አቤቱ ዐይኖቻችንን አብራ! @ Solomon Telahun's page @cgfsd
Показать все...
🔥 10
ሰላም የበክርስቶስ ቤተሰቦች ለሚመጡት ተከታታይ ጊዜያት #የክርስቶስ የመስቀል ስራ በሚል ሀሳብ ከተለያዩ አገልጋዩች ጋር በየ ሳምንቱ በተከታታይ በዚሁ ሀሳብ እንማራለን ። @cgfsd @ownkin
Показать все...
👍 21🥰 4
1. ስድብን የጠገበው፥ መስቀለኛው ንጉሥ (ማቴ. 27፡32-44) ልክ እንዲሁ፥ ኢየሱስ ሲሰቀል አራት ቡድኖች አንገታቸውን እየነቀነቁ ይሳለቁበት እንደነበር ማቴዎስ ከቍ.32-44 ባለው ያስመለክተናል። 1.    27፡27-31 በሮማውያን ወታደሮች ተሰደበ   የእሾህ አክሊል ደፍተው የአይሁድ ንጉሥ እያሉ   አሾፉበት (ቍ. 29) 2.    27፡27-31 በአላፊ አግዳሚው ሕዝብ ተሰደበ   [ሕዝቡ] በኀይል እየተሳደቡና ራሳቸውን እየነቀነቁ   አሾፉበት (ቍ. 40) 3.    27፡41-42 በአይሁድ መሪዎች ተሰደበ   የካህናት አለቆች፣ ጸሐፍትና የአይሁድ ሽማግሌዎች   አሾፉበት "ሌሎችን አዳነ፥ ራሱን ሊያድን አይችልም፤   የእስራኤል ንጉሥ ከሆነ፥ አሁን ከመስቀል ይውረድ...   በእግዚአብሔር ታምኖአል... ከወደደውስ አሁን ያድነው"   (ቍ. 42-43) 4.    27:43 አብረውት በተሰቀሉ ወንበዴዎች እንዲሁ   የስድብ ናዳ ያወርዱበት ነበር .................... ሳምሶን ጥላሁን @cgfsd
Показать все...
👍 7 4🥰 3👏 1
Фото недоступноПоказать в Telegram
ጌታ ኢየሱስ ትንሳኤህ ለእምነታችን ውበትን ሰጠ ። እናምንሃለን !! እናምንሃለን አዎን በደንብ እናምንሃለን የምናምንህ ደግሞ ታማኝ ስለሆንክ ነው ። ኢየሱስ ታማኝ እንደሆንክ ትንሳኤ ነገረን ፤ ትንሳኤህ እግዚአብሔር ታማኝ ነው ብሎ መሰከረን ። ትንሳኤ በሀይል ለእኛ የሚነግረን ታማኝነትህን ነው ።  እግዚአብሔር ለእኛ ባደረገው የደም ኪዳን ታማኝ መሆኑን ያረጋገጥነው በኢየሱስ ትንሳኤ ነው ። ጌታችን ያስተማርከውን የነገርከን ሁሉ እናምናለን መነሳትህ የተናገረከውን በሙሉ እኛ ዘንድ ግልፅ አድርጎልናል ። ትንሳኤህ በምድር ቆይታ የነገርከን ነገር ሁሉ እንድናምን እውነት አድርጎልና ። @cgfsd @ownkin
Показать все...
19
ይሔን መዝሙር ተጋበዙልኝ !! የእግዚአብሔር ሀሳብ በዚህ ልክ ይዘመራል ወይ ? እግዚአብሔር እንዴት ይመሰገናል ? በምን ይመሰገናል ? የሚለውን ጥያቄ ይመልሳል ። እግዚአብሔርማ በልጁ በሰራው ስራ ምክኒያት በኢየሱስ በኩል ይመሰገናል ። እግዚአብሔርን ማመስገን የፈለገ በኢየሱስ ስም በኩል ያመስግን ። እንዴት ያለን እድለኞች ነን ... እግዚአብሔርን በልጁ ኢየሱስ እናመሰግነዋለን ። ማመስገኛ አለን ፣ ምስጋና የምንልክበት አለን ። እግዚአብሔር የሚያስደስተው ምስጋና በኢየሱስ ስም በኩል የሚደርሰው ምስጋና ነው። እግዚአብሔር ሆይ ምህረትን ፣ፍቅርን ፣ ዘላለማዊ ህይወትን ፣ ፅድቅን በላክልን በኢየሱስ ስም በኩል አንተም ስለ ስራው ሁሉ በኢየሱስ ስም ተመስገን ። @cgfsd
Показать все...
8🥰 1
Показать все...

3
(የጌተሰማኒው አልቃሽ )   #በታላቅ ጩኸት እና እንባ የተፀለየ ፀሎት😭 ኢየሱስ በዚህ ምድር በኖረበት ዘመን ከሞት ሊያድነው ወደሚችለው ጸሎትንና ልመናን ከታላቅ ጩኸትና ከእንባ ጋር አቀረበ፤ ፍጹም ትሑት ሆኖ በመታዘዙም ጸሎቱ ተሰማለት። ዕብራውያን 5:7 #ከመጨነቅ የተነሳ በብርቱ የተፀለየ ፀሎት😭 እጅግ ተጨንቆም በብርቱ ይጸልይ ነበር፤ ላቡም እንደ ደም ነጠብጣብ ወደ ምድር ይፈስ ነበር። ሉቃስ 22:44 #በግንባሩ በመደፋት የተፀለየ ፀሎት 😭 ጥቂት ዕልፍ ብሎ በግንባሩ በመደፋት፣ “አባቴ ሆይ፤ ቢቻል ይህ ጽዋ ከእኔ ይለፍ፤ ነገር ግን እኔ እንደምፈልገው ሳይሆን አንተ እንደምትፈልገው ይሁን” ብሎ ጸለየ። ማቴዎስ 26:37-39 #ምድር ላይ በመውደቅ የተፀለየ ፀሎት 😭 ጥቂት ዕልፍ ብሎም በምድር ላይ በመውደቅ ቢቻል ሰዓቱ ከእርሱ እንዲያልፍ ጸለየና፣ ማርቆስ 14:35 ኢየሱስ😭 እንዴት ቢፀልይ ይሁን ግን ? @cgfsd @ownkin
Показать все...
13👍 1
Фото недоступноПоказать в Telegram
ቅዱስ ማቴዎስ እንደሚነግረኝ ጌታዬ ኢየሱስ ከመወለዱ ጀምሮ በኃያላን ሊቀላ የሚፈለግ ስደተኛ ተፈናቃይ ሕጻን ነበር። ከተፈናቀለበት ሲመለስም ወደቤቱ ሊመለስ ስላልቻለ በናዝሬት አደገ። በውሃ ተጠምቆ ሲወጣ ከሰማይ የተወደደ ልጅ መሆኑ ቢነገርለትም በገዛ ቀየው የተገፋ ማስጠንቀቂያው ትምህርቱ ልምምዱ ሁሉ ብዙ ንትርክ የሚያስነሳበት ዓይነት ነበር። ስልጣን አልነበረውም የሚያደርገውን ሁሉ በምን ስልጣን እንደሚያደርግ ማብራራት ይጠበቅበት ነበር። የሚበላውን ሌሎች የሚሰጡት ድኻ ነበር። እርሱ ግን ለማስረዳት በሚከብድ ኃይል የተሞላ ነበር። በመንፈስ ቅዱስ ተሞልቶ ወደምድረበዳ ሄዶ ለአርባ ቀናት ተርቦና ተጠምቶ፣ በሰይጣን ተፈትኖ ይመጣል። ሕሙማንን ሲነካ ይፈወሳሉ አጋንንት በፊቱ ይርዳሉ። እውነትም ኃያል በማለት የመጥምቁ ዮሐንስን ምስክርነት ለማጽናት እገደዳለሁ። ከማቴዎስ ገጾች ላይ ብቅ የሚለው በስደት የሚኖረው ተፈናቃዩና ጎዳና አዳሪው ኢየሱስ በአንዳች ኃይል የተሞላ የተስፋ ገንቦ ሆኖነው። ብጹዕ ሆኖ በመንፈሱ ድኻ የመንግሥተ ሰማያት የእርሱ የሆነ የሚገባ ሌሎችን የሚያስገባ ድኻ የሚያዝን የሚጽናናና ሌሎችን አልቃሾች የሚያጽናና። የዋሕ በመስቀሉ ሞት ምድርን የሚወርስ ቀሊል ቀንበሩን ሌሎች ላይ አድርጎ ራሳቸውን ወደመካድ የሚመራ ልዝብ ልስልስ መሪ ዓለምን የሚያንበረክክ ጽኑ ፍቅር። ጽድቅን የሚራብ የሚጠማ የሞቱን ጽዋ ጨልጦ የራሱን ብቻ ሳይሆን የሌሎችን የጽድቅ ረሃብ የሚያረካ። ምህረትን የሚያደርግ ለጠላቶቹ የሚሞት በእግዚአብሔር አብ የትንሳዔን ምህረት የሚያገኝ፣ የትንሳዔን ምህረት የሚያስገኝ።ሰላምን የሚያወርድ ጨቋኞቹ እየሰቀሉት የሚመሰክሩለት እውነትም ይኽ ሰው የእግዚአብሔር ልጅ ነበር ማቴ27፥54 ። ስለጽድቅ ብሎ የተሰደደ ባለመንግሥት። እኔ ደካማዋ ላይ በረከትህ ይውረድብኝ ጌታዬ! ✍ ሳራ ከድር
Показать все...
12
(አኗሪ ) ክርስቶስ በልባችን ማኖር የእኛ ስራ አይደለም በልባችን የሚያኖር አካል አለ እርሱ መንፈስ ቅዱስ ይባላል ። መንፈስ ቅዱስ ክርስቶስን በልባችን ላይ ለማኖር ብዙ ኢንቨስትመንቶችን ያረጋል ። እኛን በህልውናው ያውደናል ፣ የእግዚአብሔር ፍቅር እንድንለማመድ የቀመስነውን ፍቅር መልሶ መላልሶ ያስታውሰናል ፣ በልባችን ሊኖር የተገባውን ክርስቶስ ማን እንደሆነ ይነግረናል ፣ እኛ የተረጨንበትን ክቡር ደም ያሳስበናል ። ክርስቶስን በልባችን ማኖር የመንፈስ ቅዱስ ድርሻ መሆን ካወቅንበት አንዱ ምክኒያት መካከል ክርስቶስን በልብ ማኖር የሚቻለው በውስጥ ሰውነት በመንፈሱ በኩል በመጠንከር ስለሆነ ነው ።   በውስጥ ሰውነት መጠንከር በውስጠኛው ማንነታችን ከመንፈስ ቅዱስ ጋር በሚኖር ጣፋጭ ህብረት በሀሳብ ፣ በዕውቀት ፣ በስሜት ፣ በፈቃዳችን መንፈስ ቅዱስ ላይ ጥገኛ መሆን ነው ። በመንፈስ ቅዱስ ውስጠኛው ሰውነታችን ሲበረታ ልባችን ክርስቶስ ለማኖር ዝግጁ ይሆናል ። ሀሳባችን ፣ ስሜታችን ፣ ፈቃዳችን ክርስቶስ ለማኖር ይጓጓሉ ።በመንፈሱ በውስጥ ሰውነት መጠንከር ክርስቶስ በልባችን እንዲኖር ልባችንን ብቁ ያደርገዋል ። @cgfsd @ownkin
Показать все...
15👍 3
(ቤተኝነት ለቤተኛው ) ክርስቶስ በልባችሁ እንዲኖር ብሎ ሲፀልይ ሐዋሪያው ጳውሎስ በመንፈስ ቅዱስ አማካኝነት ወደ እናንተ ማንነት የገባው ክርስቶስ እናንተ ለቤትነት ይፈልጋችኋል እያለ ነው ። የክርስቶስ ቤተመቅደስ ናችሁ ማለት የክርስቶስ መኖሪያ ቤት ናችሁ ማለት ሲሆን ክርስቶስ በልባችሁ ይኑር ማለት ግን እናንተ ቤት ያደረጋችሁ ክርስቶስ ቤተኝነት ይሰማው ፣ በራሱ ቤት ነፃነት ያግኝ፣ የደም ዋጋ ያወጣበት የቤቱን ባለቤትነት ማንም አይጋራው። ክርስቶስን በልባችን ማኖር በነፍሳን ላይ ቤተኛ እና ባለቤት ማድረግ ነው ። @cgfsd @ownkin
Показать все...
15👍 1