ru
Feedback
በክርስቶስ ( in christ)

በክርስቶስ ( in christ)

Открыть в Telegram

በክርስቶስ ቴሌግራም ቻናል ውስጥ ክርስቶስ ማዕከል ያደረጉ መልዕክቶች ይተላለፋሉ ። @cgfsd

Больше
1 527
Подписчики
+124 часа
+107 дней
+4430 день
Архив постов
#Intimacy of kingdom    (የህብረት መንግስት) በወንጌላት መፀሃፍት መካከል የእግዚአብሔር መንግስት የሚለው ሀሳብ ተደጋግሞ እናገኘዋለን ። በተለይም ቀጥተኛ በሆነ መንገድ በተመሳሳይ ወንጌላት በማቴዎዮስ ፣ ማርቆስና በሉቃስ በግልፅ እንመለከተዋለን ። በዩሀንስ ወንጌል የእግዚአብሔር መንግስት ሀሳብ በስፋት ያለ ቢሆንም በቀጥታ ግን የእግዚአብሔር መንግስት የሚል ቃል ሲጠቀም አናገኝም ። kingdom ማለት kingship administration(ንጉሳዊ አገዛዝን)  ይጠቁማል ። የእግዚአብሔር መንግስት ስንል የእግዚአብሔር ንጉሳዊ አገዛዝ እያልን ነው ። በእግዚአብሔር መንግስት መኖር ማለት ደግሞ ለገዢው እየተገዙ መኖር የሚል ትርጓሜ አለው ። የእግዚአብሔርን ንጉሳዊ አገዛዝ(የእግዚአብሔር መንግስት) በተመሳሳይ ወንጌላት  በማቴዎስ ፣ ማርቆስና ሉቃስ ላይ አጋንት በማስወጣት ፣ በሽተኞችን   በመፈወስና ተአምራት በማድረግ እየተገለጠ እንደሆነ ያሳያል ። መንግስት ሃይል አለው አጋንት ሲወጣ በጨለማው ላይ ሃያል መሆኑን ፣ በፈውስ ሲመጣ ነፃነት የሚሰጥ መንግስት እንደሆነ፣ ተአምራት በማድረግ ንጉሱ ለመግዛት ከተፈጥሮ በላይ ከሁሉ በላይ እንደሆነ ያሳያል ። በዩሀንስ ወንጌል ውስጥ ተአምራት ቢኖር በትኩረቱ ግን የእግዚአብሔር መንግስት የዘላለም ህይወት በማለት ያቀርብልናል ፤ ይሔም የዘላለም ህይወት ወደፊት የምኖረው ብቻ ሳይሆን እግዚአብሔር የተወዳጀንበት እሱ የምናውቅበት እሱ የቀመስንበት ደግሞም ቀጥለን ለዘላለም ወደፊትም ይሔን ህብረት በሙላት ለእሱ በመገዛት የምንኖረው ህይወት ነው (ስለዚህ በዩሀንስ ወንጌል የዘላለም ህይወት ከእግዚአብሔር ጋር የሚኖር ወዳጅነት ፣ህብረት የሚል ይዘት አለው ) ። ንጉሳዊው የእግዚአብሔር መንግስት አገዛዝ ህይወትን በመስጠት ፣ ህይወትን በመለወጥ ፣ ህይወትን በማካፈል ይገለጣል የእግዚአብሔር መንግስትን የዘላለም ህይወት በማለት ከእግዚአብሔር ጋር የሚኖር ግንኙነት አድርጎ ያስገነዝበናል ። የእግዚአብሔር መንግስት ሰው በእግዚአብሔር አገዛዝ ውስጥ በመሆን ከእግዚአብሔር ጋር በሚኖረው ግንኙነትና ህብረት(intimacy ) ይገለጣል ። የህብረት መንግስት ነው ። ንጉሱ ከህዝቡ ጋር በጥልቅ መጣበቅ የሚኖርበት ፣ ንጉሱ ከህዝቡ የሚወዳጅበት ፣ ህዝቡ በመገዛት ንጉሱም በመግዛት ህይወትን በመካፈል ጥልቅ ግንኙነት የሚደረግበት ነው ። በዩሀንስ ወንጌል የእግዚአብሔር መንግስት የህብረት መንግስት ነው ። kingdom with intimacy !! በእግዚአብሔር መንግስት መደሰት ለሚገዛው ለንጉሱ በመገዛት የሚገኝ ነው ይህም ህብረት(intimacy) ይባላል ። @cgfsd

photo content

(ድሆችን ማስጎምዠት ) ድሃው ቄስ ታመው በአልጋ ውለዋል ። አንድ ጠያቂም መጥቶ:- " ለእርስዎ ሕመም መድኋኒቱ ቀላል ነበር " አላቸው ። እርሳቸውም :- " ምንድነው ልጄ ?" አሉት ። " የጎድን ስጋ ቀቅሎ ቂቤ ሁለት ማንኪያ ጣል አድርጎ፣ ቅመም ጨምሮ ትኩሱን ቢበሉበት ይነቀላል " አላቸው። ቄሱም ቀስ ብለው ከመኝታቸው ቀና አሉና :- " ያልከውን በሙሉ አንድ ሳታጓድል ካላመጣህ ገዝቼሃለሁ "።               ገፅ 24   ረጅሙ ፈትል (ዲያቆን አሸናፊ መኮነን)     @cgfsd

ትርጉምን ፍለጋ እምብዛም የሚያስመካ የሺህ አመታት ታሪክና ትውፊት (tradition) በሌለበት፣ የሚያማልል ስርዓተ-አምልኮ (liturgy) በሌለበት፣ በውል የተሰናሰለና የተደራጀ ወጥ አስተምህሮ (doctrine) እምብዛም በሌለበት ሁኔታ እስከ አሁን ድረስ በሺዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን ወደ ፕሮቴስታንት ሰፈር (ጴንጤ) ለምን ይጎርፋሉ? እኔ ያገኘሁት መልስ ለተራው ሕዝብ የሚመች ተጨባጭ፣ ተግባራዊ፣ ዐዉዳዊ፣ ክርስትና መኖሩ ነው። ክርስትና በመጀመሪያው መቶ ክፍለ ዘመን መላውን የሮማ ኢምፓየርን ያናወጠው ከታች ካለው ማህበረሰብ ሁኔታ ጋር የተሰናሰለ ተግባራዊ የሕይወት ልምምድን ያገናዘበ በመሆኑ እንደሆነ ብዙ ምሁራን ይስማማሉ (Roodney Stark, 1997)። በኢትዮጵያም ሰዎች ሁሉ ከእግዚአብሔር ጋር በቀጥታና በቀላሉ በክርስቶስና በቃሉ መካከልኝነት በየዕለቱ ግንኙነት እንዲያደርጉ እና ተጨባጭ መንፈሳዊ ርባና ያለው፣ ለሕይወታቸው ትርጉም የሚሰጥ ሕብረት እንዲፈጥሩ የሚያበረታታ እንቅስቃሴ የተደረገዉ በፕሮቴስታንቱ በኩል ነው። ይህ ነገር አሁንም ተጠናክሮ እስከቀጠለ ድረስ ፕሮቴስታንቱ ምንም ያህል ቢተችም ሰው ትርጉም ፈልጎ ወደ እሱ መፍለሱ አይቀሬ ነው እላለሁ። እናንተስ ምን ትላላችሁ? ✍️ አበባየው ቢተው @cgfsd

-- Reading books with ReadEra https://readera.org

Jesus Christ is already exalted in his humiliation and humiliated in His exaltation. Jeremy R.Treat @cgfsd

(የተስፋ ተማጥኖ ) ሪቫይቫልና የጌታን ምፅአት ሁለቱንም ተስፋ እናደርጋለን። በእርግጥ በዚህ ምድር የትኛውም ኑሮ ያለ ተስፋ እንደማይቻል ግልፅ ነው። እንደ ቤተክርስቲያን ብዙ ጊዜ ሪቫይቫንም የጌታን ምፅአትም ተስፋ እንደርጋለን። ሪቫይቫል ላይ የተለያዩ ምልከታና ትርጉም ውዝግብ ቢኖርም እንደ ቤተክርስቲያን አስፈላጊ ሊሆን ይችላል። የደኩሙ ጎኖችን ፣ ልክ ያልሆኑ ልምምዶችን ለማስተካከል ያስፈልጋል። የጌታ ምፅአት ዳግም መምጣት ግን ዋነኛ በጊዜ የማይገደብ ቤተክርስቲያን በዚህ ምድር እስካለች ድረስ የሁልጊዜ ተስፋዋ ነው። ከክርስቶስ ዳግም መምጣት በላይ የትኩረት አቅጣጫ የሆነ ተስፋ ለክርስትና የለም። ሪቫይቫል አስፈላጊ ቢሆንም ከምፅአት በላይ ተስፋ የምናደርግበትና የምንታመንበት መሆን የለበትም። ሪቫይቫል ተኮር ፀሎት ፣ ስብከት ፣ ዝማሬ ላይ አተኩረን ምፅአቱን የሚገባው ትኩረት ካልሰጠነው የተሰፋ መዛነፍ ያጋጥመናል። ሪቫይቫል ያስፈልገናል ነገር ግን የምንሰጠው ቦታና ትኩረት በአግባቡ መፀሃፍ ቅዱሳዊና ከዋናው ተስፋ ምፅአቱ ስር በታች በሆነ መልኩ ሊሆን ይገባዋል። @cgfsd

መንፈስ ቅዱስ በንስሃና በእምነት የመጣውን ሕዝብ ከመሲሁ ጋር አንድ አድራጊ ነው ። ገፅ72 @cgfsd
መንፈስ ቅዱስ በንስሃና በእምነት የመጣውን ሕዝብ ከመሲሁ ጋር አንድ አድራጊ ነው ።   ገፅ72 @cgfsd

ክርስቶስ የወጣበትና የገባበትን መልካአ ምድር ለመጎብኘት ጉጉት እንዳለን ሁሉ ክርስቶስ ያነበበውንና ይሰብክ የነበረውን ብሉይ ኪዳን ማጥናትና ማንበብ ላይ ስፍራ አንሰጥም ይለናል መጋቢ ኢሳይያስ @cgfsd

ልዩ የሆነው የእግዚአብሔር መገኘት በድነት ውስጥ አለ ! በመዳን መደሰት በረከቱ ብዙ ነው ። @cgfsd

ስንሰበር ስሜታችን ስለተጎዳ ይመስለናል ነገር ግን አንዳንድ ጊዜ ስሜታችን ሳይሆን እኔነታችን ስለሚጎዳ ነው የምንሰበረው ። ቲሞቲ ኬለር @cgfsd

የሞተላቸውን እወድለታለሁ !🎶 ዘሪቱ ከበደ

(የአሸዋ ሰጎን እና የሳሎን ውሻ) የአሸዋ ሰጎን ለየት ያለ ትዕይት አለው ። ራሱን  በአሸዋ ውስጥ ይደብቃል ። ሙሉ ሰውነቱ ውጭ እንዳለ ራሱን ብቻ አሸዋ ውስጥ ይቀብራል ። ነፋስ ቢነሳ ፣ ቀውጢ ቢመጣ የሚሰሚው ጉዳይ አይኖር ራሱን አሸዋ ውስጥ ቀብሮ ይኖራል ። የበረታ ነፋስ ከመጣ ጠራርጎ  ይወስደዋል ጆሮ ዳባ ልበስ ብሎ ባልሰማ ተደብቆ የቆየበት አሸዋ አያድነውም ።  የሳሎን ውሻ መላመድ ነው ባህሪው ፣ ከአሳዳጊው ስር ስር መሆን ፣ የመጣውን መልመድ ፣ አሳዳጊው ሳሎን ውስጥ መንጎራደድ መገለጫው ነው ። ክርስትናንና ፖለቲካን ስንመለከት የአሸዋ ሰጎንና የሳሎን ውሻ መሆን አያዋጣም ። ቤተክርስቲያን እንደ አሸዋው ሰጎን ምንም አላቅም እያገባኝም ብላ ባልሰማ ባላየ ራሷን አሸዋ ውስጥ ብትደብቅ የሚመጣው ነፋስ የሞራል ውድቀት ፣ ጦርነት ፣ አምላክ የለሽ ስርአት ይሸረሽራታል ። እንደ ሳሎኑ ውሻው ፖለቲካን ለምዳ ለፖለቲካው ቤተኛ መሆን  የፖለቲካው ውድቀት ውድቀቷ፣ የፖለቲካው ግፍ ግፏ ፣ በደሉ በደሏ ይሆናል ፣ ምክኒያቱ ቤተኛ ሆናለች ። ቤተክርስቲያን አያገባኝም በማለት እንደ ባለ አሸዋው ሰገን ባይተዋር ፤ እንደ ሳሎኑ ውሻ ሁሉ ያገባኛል በማለት ቤተኛ መሆን የተጠራችበት ተልዕኮ ያስረሳታል ።  ቤተክርስቲያን ለፖለቲካው ህሊና መሆን አለባት ። ህሊና ክፉንና ደጉን መመዘኛ ሚዛን ነው ። የፅድቅ መለኪያ እንደመሆኗ የተበላሸው ፖለቲካ ክፍቱቱን በፅድቋ  ትመዝናለች። ፖለቲካው ሲያጠፋ እረፉ የምትል ይሔ ግፍ ነው ብላ በደልን ክፋት የምታነቅፍ ፣ ደግሞ ስልጣን ከእግዚአብሔር ስለሆነ ፖለቲካው ውስጥ ገብታ የምትቆጣጠር ሳይሆን ማንም ይሁን አይሁን ፤ አማኝ ይሁን አይሁን የምትፀልይ ናት ። ቤተክርስቲያን በፖለቲካው ዙሪያ የሚኖሯት መፀሃፍ ቅዱሳዊ አቋም የስልጣን(power) ይገባኛል ላስተዳድረው ሳይሆን የፅድቅ አቋም ነው ። @cgfsd

እግዚአብሔር በሁሉ ቦታ ይገኛል፤ በልዩ ቦታም ይገኛል ። በልዩነት የሚገኘው ግን ለህብረት ነው ። @cgfsd

በክርስቶስ ቻናል 1500 እያለፍን ነው 😁 ። የበክርስቶስ ቤተሰቦች ስለ ቤተሰብነታችሁ እናመሰግናለን ።  ቻናሉ 8 አመት ሞልቶታል ። 8 አመት የመቆየቱን ያክል ብዙ አልሰራንበትም ። በቀጣዩ ጊዜ አሻሽለን በተከታታይነት መፀሃፍ ቅዱሳዊ መሰረት ያላቸውን ሀሳቦች ፣ ተልዕኮ ተኮር የሆኑ ፣ ወደ ተግባራዊ ህይወት (Devotional ) የሚጋብዙን ይዘት ያላቸውን ስራዎች ጨምረን ለመስራት እንሞክራለን ። ቢሻሻል ፣ ቢጨምር ፣ ቢታረም ፣ ቢቀጥል የምትሉትን አስተያየታችሁን በዚህ በኩል 👉@filicross ሀሳባችሁን መስጠት ትችላላችሁ ። @cgfsd

ምናልባት አንዳንዱን ነገር አጥርተን የምናየው በእምባ በረጠቡ አይኖቻችንስ ቢሆን?! ✍️ አበበ አብዲሳ @cgfsd
ምናልባት አንዳንዱን ነገር አጥርተን የምናየው በእምባ በረጠቡ አይኖቻችንስ ቢሆን?! ✍️ አበበ አብዲሳ @cgfsd

ጌታዬ ድምፅህ ውስጥ ልብ አለ   ለአፍታ የሰማህ እግርህ ስር ዋለ

(የመስቀል እሳቤ) በቆሮንቶስ መፀሃፍ ሐዋሪያው ጳውሎስ መስቀልን የመስቀሉ ቃል በማለት መስቀሉን ይጠራል(1ቆሮ 1:18) ። ግሩም አገላለፅ ነው ። የመስቀሉ ቃል የመስቀሉ ስራ እንደማለት ነው  ። የመስቀሉ ቃል የመስቀሉ ስራ ተብሎ ሊገለፅ ይችላል ። ሐዋሪያው ጳውሎስ መስቀሉን ሲገልፅ ስለ አሰቃቀል ሂደቱ ወይም ስለ ቢስማሩ አልፎ ጅራፉን ሲጠቅስ ወይም ሲያነሳ አናይም ፤ ይልቁን የመስቀሉን ምክኒያት የመስቀሉን ስራ ውጤት ያብራራል ። መስቀል አንድ በቀራንዮ ላይ የተከናወነ የአንድ ቀን ክስተት ሳይሆን እንደ ቅዱስ ጳውሎስ ውጤቱ የቀጠለና ምክኒያቱም ስለሰው ልጅ ድነት የሆነ አድርጎ ያስቀምጥልናል ። ለዚህም ነው የመስቀሉ ስራ ውጤትና ምክኒያት ላይ ትኩረት ስላደረገ ጳውሎስ የመስቀሉ ቃል የሚለውን ቃል ስለ መስቀል ስራው ወካይ አድርጎ ያስገባውል ። የመስቀሉ ቃል መስቀሉን የሚገልፅ ድንቅ ቃል ። @cgfsd

(መንፈሱና መስቀሉ ) በቆሮንቶስ መፀሃፍ ላይ መስቀል ጥበበ እግዚአብሔር ነው ። መስቀል በቆሮንቶስ መፀሃፍ ላይ እንዴት ተገለጠ ብንል ጥበብ እግዚአብሔር የሚለው መልስ ገላጭ ሁኖ እናገኘዋለን ። መስቀል የእግዚአብሔር አስደናቂ ጥበብ እንደሆነ ስዕል ይስልናል ። ጥበቡም የእግዚአብሔር ሃይል ፣ እቅድ ፣ ርህራሄ ፣ ማዳን ፣ ፍቅር ፣ቸርነት ፣ የፀጋውን ባለጠግነት ፣ ልብ የሚገልጥ ጥበብ ነው ። እግዚአብሔር ለአለሙ ምስቅልቅል የሰጠው መልስ በጥበብ ነው እርሱም መስቀል ነው ። ጥበብ እንደመሆኑ መጠን መስቀል በእግዚአብሔር ልብ ውስጥ ያለው ምክር ለመረዳት መንፈስ ቅዱስ ያስፈልጋል ። መንፈስ ቅዱስ የእግዚአብሔር ጥልቅ ነገር የሚገለጥበት የእውነት መንፈስ ነው ። ስለዚህ የጥበቡን ጥልቀት ለመረዳት የመንፈሱ እርዳታ ያስፈልጋል ። መግለጥ የመንፈሱ ስራ ነውና ።  በቆሮንቶስ መፀሃፍ የመስቀሉን ጥበብነት ሲገልጥ በአይን ያልታየ፣ በሰው ልብ ያልታሰበ(1ቆሮ 2:5) በማለት እቅዱ የእግዚአብሔር ብቻና አስደናቂ  እንደሆነ ይነግረናል።  መንፈሱን ደግሞ በመስቀሉ ዙሪያ የሚኖረው ሚና ገላጭ ነው ይለናል ።     ይሁን እንጂ፣ እንደ ተጻፈው፣ “ዐይን ያላየውን፣ ጆሮ ያልሰማውን፣ የሰውም ልብ ያላሰበውን፣ እግዚአብሔር ለሚወዱት አዘጋጅቶአል፤” እግዚአብሔር ግን ይህን በመንፈሱ አማካይነት ለእኛ ገልጦልናል። መንፈስም የእግዚአብሔርን ጥልቅ ነገር እንኳ ሳይቀር ሁሉን ይመረምራል።  በውስጡ ካለው ከራሱ መንፈስ በስተቀር ከሰው መካከል የአንድን ሰው ሐሳብ የሚያውቅ ማን አለ? እንደዚሁም ከእግዚአብሔር መንፈስ በስተቀር፣ የእግዚአብሔርን ሐሳብ የሚያውቅ ማንም የለም። 1 ቆሮንቶስ 2:9-11    በነገራችን ላይ ይሔ ጥቅስ ስለ መስቀሉ እንደሚያወራ ልብ ማለት ያስፈልጋል ። የእግዚአብሔር ጥበብ የሆነውን የመስቀል ስራ በመንፈሱ አብሪነትና አስረጂነት ይብራራል ። ጥልቅ የመስቀሉን እውነት ለመረዳት የመንፈሱ አስረጂነት ያስፈልጋል ። @cgfsd

የነርሲያው ቤኔዲክት ፀሎት ቸርና ቅዱስ አባት ሆይ፤ ማንነትህ የማስተውልበት ጥበብ፣ አንተን የምረዳበት ብሩህ ልቡና አንተን የምሻበት ትጋት አንተን የምጠብቅበት ትዕግስት አንተን የማይባቸው ዐይኖች አንተን የማሰላስልበት ልብ አንተን የማውጅበት ሕይወት በመንፈስ ኋይልና በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስጠኝ ። @cgfsd

በክርስቶስ ( in christ) - Статистика и аналитика Telegram-канала @cgfsd