en
Feedback
በክርስቶስ ( in christ)

በክርስቶስ ( in christ)

Open in Telegram

በክርስቶስ ቴሌግራም ቻናል ውስጥ ክርስቶስ ማዕከል ያደረጉ መልዕክቶች ይተላለፋሉ ። @cgfsd

Show more
1 556
Subscribers
No data24 hours
+87 days
+2930 days

Data loading in progress...

Tags Cloud
No data
Any problems? Please refresh the page or contact our support manager.
Incoming and Outgoing Mentions
---
---
---
---
---
---
Attracting Subscribers
July '26
July '26
+44
in 2 channels
June '26
+67
in 4 channels
Get PRO
May '26
+47
in 3 channels
Get PRO
April '26
+51
in 1 channels
Get PRO
March '26
+35
in 0 channels
Get PRO
February '26
+19
in 1 channels
Get PRO
January '26
+88
in 0 channels
Get PRO
December '25
+37
in 3 channels
Get PRO
November '25
+48
in 0 channels
Get PRO
October '25
+42
in 1 channels
Get PRO
September '25
+18
in 1 channels
Get PRO
August '25
+64
in 1 channels
Get PRO
July '25
+49
in 4 channels
Get PRO
June '25
+95
in 1 channels
Get PRO
May '25
+63
in 1 channels
Get PRO
April '25
+45
in 1 channels
Get PRO
March '25
+46
in 1 channels
Get PRO
February '25
+34
in 1 channels
Get PRO
January '25
+84
in 0 channels
Get PRO
December '24
+42
in 0 channels
Get PRO
November '24
+59
in 3 channels
Get PRO
October '24
+29
in 1 channels
Get PRO
September '24
+46
in 0 channels
Get PRO
August '24
+86
in 3 channels
Get PRO
July '24
+17
in 0 channels
Get PRO
June '24
+21
in 1 channels
Get PRO
May '24
+29
in 1 channels
Get PRO
April '24
+31
in 1 channels
Get PRO
March '24
+40
in 0 channels
Get PRO
February '24
+30
in 1 channels
Get PRO
January '24
+31
in 0 channels
Get PRO
December '23
+27
in 0 channels
Get PRO
November '23
+19
in 0 channels
Get PRO
October '23
+31
in 0 channels
Get PRO
September '23
+107
in 0 channels
Get PRO
August '23
+17
in 0 channels
Get PRO
July '23
+16
in 0 channels
Get PRO
June '23
+9
in 0 channels
Get PRO
May '23
+14
in 0 channels
Get PRO
April '23
+22
in 0 channels
Get PRO
March '23
+22
in 0 channels
Get PRO
February '23
+5
in 0 channels
Get PRO
January '23
+23
in 0 channels
Get PRO
December '22
+17
in 0 channels
Get PRO
November '22
+11
in 0 channels
Get PRO
October '22
+27
in 0 channels
Get PRO
September '22
+26
in 0 channels
Get PRO
August '22
+52
in 0 channels
Get PRO
July '22
+21
in 0 channels
Get PRO
June '22
+17
in 0 channels
Get PRO
May '22
+13
in 0 channels
Get PRO
April '22
+42
in 0 channels
Get PRO
March '22
+20
in 0 channels
Get PRO
February '22
+27
in 0 channels
Get PRO
January '22
+9
in 0 channels
Get PRO
December '21
+6
in 0 channels
Get PRO
November '21
+16
in 0 channels
Get PRO
October '21
+11
in 0 channels
Get PRO
September '21
+2
in 0 channels
Get PRO
August '21
+10
in 0 channels
Get PRO
July '21
+5
in 0 channels
Get PRO
June '21
+12
in 0 channels
Get PRO
May '21
+234
in 0 channels
Date
Subscriber Growth
Mentions
Channels
12 July+3
11 July+3
10 July+2
09 July+2
08 July+3
07 July+4
06 July+4
05 July+8
04 July+10
03 July+3
02 July+2
01 July0
Channel Posts
የዕብራውያን መፀሃፍ ውስጥ በተለይ (ዕብ 9:15-22) ላይ "ኪዳን" (covenant) የሚለውን ቃል " ኑዛዜ" ወይም " የአደራ ሰነድ " (will/ Testament) ከሚለው ሕጋዊ ትርጉም ጋር ያዛምደዋል ። የኑዛዜው ሰነድ የሚሰራው ተናዛዡ ሲሞት ብቻ ነው ፤ የአዲሱ ኪዳን በረከቶችም ተፈፃሚ ሊሆኑ የቻሉት በክርስቶስ ሞት ነው ። ለዚህ ነው አዲሱ ኪዳን በደም የተመረቀ ነው የሚባለው ። የክርስቶስ ደም የክርስቶስን ሞት ራሱን አሳልፎ መስጠት የሚወክል ስለሆነ ። @cgfsd

2
መንፈስ ቅዱስ በተመለከተ bible thinkers ላይ ጥናት ተጀመሯል ጠቃሚ ስለሆነ join አርጋችሁ እንድትማሩ recommended አረጋለሁ ። በዚህ አጋጣሚ https://t.me/bibilicalthinker channal ብትገቡ ብዙ ታተርፋላችሁ እምነታችን በአግባቡ የሚሞግት channal ስለሆነ ።
271
3
ዛሬ ምሽት(2:30) የጀመርነውን Pneumatology Class የመጨረሻ ክፍል እንማማራለን። ባለፈው የአብንና የወልድን Eternal relations of origins አይተናል። ዛሬ የመንፈስ ቅዱስን relation of origin to the Father and the Son እናያለን። * መንፈስ ቅዱስ የሚሠርጸው(የሚወጣው) በምዕራቧ ቤተክርስቲያን(በካቶሊኮች እና በብዙ ፕሮቴስታንቶች) እንደሚታመነው Hypostetically ከአብ እና ከወልድ ነው ወይስ በምስራቋ ቤተክርስቲያን እና በሌሎች ኦርቶዶክሳዊያን እንደሚታመነው ከአብ ብቻ? (እና ከወልድ Hypostetically ሳይሆን Economically) * መጽሐፍ ቅዱስ ምን ይላል? Should we affirm the Filioque("..And the Son")? *ሁለቱም የላቲን እና የግሪክ አባቶች(Augustine, Cyril, Basil the great, Gregory Of Nyssa, Athanasius ) ምን አስተማሩ? Hypostetical(Personal)processionን ወይስ Just Economic procession? ይኼ ከነበሩት ቤተክርስቲያንን በ 1054 ዓ.ም ለሁለት ከከፈሉት ጉዳዮች አንዱ ነበር። ሁለቱም አብያተክርስቲያናት ተወጋግዘዋል(ካቶሊኮች በ Lyon ጉባኤ Filioqueን ዶግማ አድርገዋል። የምስራቅ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ደግሞ በበኩሏ ይሄንን ትምህርት Soul damning የሆነ አደገኛ ምንፍቅና ነው ብለው ያምናሉ። ውግዘቱ እኛንም የሚመለከት ነው ምክንያቱም ሁሉም የፕሮቴስታንት ሪፎርመሮች የ Filioqueን Clause affirm ስላደረጉ።) በዚህ ጉዳይ ዙሪያ የራሳችሁን Research ሰርታችሁ ኑ። እንወያይበታለን። ኦርቶዶክሳዊያን ቢኖሩ ደግሞ የእነርሱንም Perspective ከራሳቸው ለመስማት More በጣም አሪፍ ይሆናል።
198
4
@cgfsd
594
5
ክርስቶስን ጌታ አድርጋችሁ በልባችሁ ቀድሱት። እናንተ ስላላችሁ ተስፋ ምክንያትን ለሚጠይቋችሁ ሁሉ መልስ ለመስጠት ሁል ጊዜ የተዘጋጃችሁ ሁኑ፤ ነገር ግን ይህን ሁሉ በትሕትናና በአክብሮት አድርጉት፤ 1 ጴጥሮስ 3:15
410
6
አስር ልጆቿንና ባሏን በጦርነት ያጣች የትግራይ እናት በአንድ ቪዲዮ ተመለከትኩ ፤ ሀዘኗን መቋቋም አቅቷት መናገር ስትቸገር። ምን ያህል ጦርነት አስከፊ እንደሆነ ፀያፍ ተግባር እንደሆነ ግልፅ ነው ። አሁንም የጦርነት ቅስቀሳ አለ እያሉ እናቶች ሲያለቅሱ ልጆቻቸውን ስደት ሲልኩ ማየት እጅግ ያማል። ትግራይ የመሄድ እድል ባይገጥመኝም እዛም ዘመድ ባይኖረኝም እንኳን ከጓደኞቻችን ፣ ከማህበራዊ ሚዲያ፣ በእየ ከተማው ተሰደው የሚመጡን ወጣቶችና አዛውንቶች ስይ ምን ያህል ጉዳዩ አስከፊ እንደሆነ መረዳት እችላለሁ። ግን ለምን ? ከትናንት ስሕተቶች የማንማረው ይህን ህዝብ ልናፅናናው ከጎን ልንቆም ይገባል ። መፅናናት ያስፈልጋቸዋል! ስለ ሰው ለማዘን ለመጨነቅ የግድ ከእኛ ዘር ሀረግ መሆን የለበትም ለክርስቲያን ባልንጀራው ያገኘው የሰው ልጅ በጠቅላላ እንጂ የዘር ሀረጉ ብቻ አይደለም ።ጦርነት እንዲቆም ፣ እናቶችና አባቶች እንዲፅናኑ ፣ ልጆች በሰላም እንዲኖሩ የመፀለይ ግዴታ አለብን ። እግዚአብሔር ሆይ በቃ በለን 😭 ህዝብን አስብ ። እንፀልይ !😭😭
1 189
7
ልጅነቴ ያላለቀ ነኝና ብላቴና   ሙሉ ሰው አድርገኝ ጌታ    ቃልህን : አብላኝና.... 🎶 ተስፋዬ ጋቢሶ(ጋሼ)
485
8
(አጭሩና ረጅሙ መዝጊያ) በአዲስ ኪዳን መጽሐፍት መካከል ከፍተኛ ውዝግብ ከሚያስነሱ ክፍሎች መካከል የማርቆር ወንጌል መዝጊያ አንዱ ነው ። ክርክሩ የማርቆስ ወንጌል የሚያበቃው ምዕራፍ 16 ቁጥር 8 ላይ ነው ወይስ ምዕራፍ 16 ቁጥር 20 ላይ ነው ማለቂያው የሚል የቆየ የሙግት ሀሳብ አለ ። 16:8 የሚሉት አጭሩ መዝጊያ በመባል ሲጠሩ 16:20 ደግሞ ረጅሙ መዝጊያ በመባል ይታወቃሉ ። አጭሩ መዝጊያ የሚያምኑ መነሻ የሆናቸው የተወሰኑ የድሮ የመፀሃፍ ቅዱስ ማንስክሪፕት ቅጂዎች ላይ እስከ ቁጥር ስምንት ድረስ ብቻ መገኘቱ ነው ። በተለይ ከ3ተኛና 4ተኛ ክፍለ ዘመን በኋላ በርካታ ቅጂዎች ይገኛሉ ፤ከእነዚህም ውስጥ ከአንድ ሺ ከሚበልጡ ቅጂ ውስጥ ሶስት ቅጂ ላይ የማርቆስ 16:8 ድረስ ብቻ ሲሆን ከቁጥር 9-20 አይገኝም ። እነዚህም ቅጂዎች :- ቫቲካነስ ኮዴክስና ሲናይቲከስ ኮዴክስ ይገኙበታል ። በእነዚህ ቅጂዎች ላይ የማርቆስ 16:8 በኋላ ያሉ ቁጥሮች የለም ። በአንድኛው ባዶ ቦታ በሌላኛው ተራርቆ በተፃፉ ፊደላት ምክኒያት ባዶ ቦታውን  ወደ ሉቃስ ወንጌል የሚያስገባ መሸጋገሪያ በመሆን ተቀምጧል። በእነዚህ ክስተት ምክኒያት የማርቆስ ወንጌል 16:9-20 ያለው ሀሳብ የተጨመረ በቀድሞ ኦሪጂናል ጥቅቅል መፀሃፍ ውስጥ የለም የሚል መላምት መበራከት ቀጥሏል ። ከዛም ከቁጥር 9-20 ያለው ስነፅሁፋዊ ይዘቱም ከሌሎቹ ማርቆስ ወንጌል መፀሃፍ ጋር የተለየ ነው የሚል ውስጣዊ ሙግትም ይሰነዝራሉ ። ብለው አንዳንድ አስተምሮዎች ከ9-20 ያለው ከሙሉ የመፀሃፍ ቅዱስ ትምህርት እንደሚጋጭ ያምናሉ በተለይም መርዝ ብትጠጡ አይገላችሁም ፣ እባብ ብትጨብጡ የሚለው ጥቅስ በመምዘዝ ከክርስትና ትምህርት ይጋጫል የሚል እይታ አላቸው ፤ ነገር ግን ይህ እይታ ውሃ የማያነሳ ነው የሁልጊዜ አስገዳጅ ሁኖ አልቀረብም ፣ ከዛም ከተልዕኮ አንፃር የተጠቀሰም በመሆኑ ተአምራዊ መልክ ሊኖር እንደሚችል ማሰብ ያስፈልጋል ። ከዛም በመቀጠል በታሪካዊ ማስረጃ በመጥቀስ የቤተክርስቲያን ታሪክ አባት ተደርጎ በሚቆጠረው አውሳብዮስ የለም እንዳሉ በመጥቀስ ይነሳል አውሳብዮስ የማርቆስ 16:9-20 ያነሱት የተጨመረ ነው  ከማለት አንፃር ሳይሆን ከሌሎች የወንጌላት መፀሃፍ ጋር ትንሳኤውን እንደማይጋጭ ግልፅ ከማድረግ አንፃር ነው ። አጭሩ መዝጊያ 16:8 ልክ ያልሆነበት ሌላኛው አግባብ ማርቆስ ቁጥር 8 የጨረሰው ሆን ብሎ(intentionally ) የሚል ሀሳብ ያነሳሉ ( book from perspective on ending mark  )።  ይህ ሀሳብ አሳማኝ ሊሆን የሚችለው ከአንድ ነገር ጎን ብቻ ሊሆን ይችላል የማርቆስ ወንጌል አፃፃፍ ጥድፊያ የተሞላ እንደመሆኑ መጠን በቶሎ የማርቆስ ወንጌል ፀሃፍ ዘግተት ሊሆን ይችላል ። ምን አልባት እንደ አንድ ሙግት ነው ግን በቂ አይደለም ። ምክኒያቱም የማርቆስ ወንጌል ከጴጥሮስ ስብከት ተመሳሳይነት አለው በተለይም የሐዋሪያት ስራ ላይ  ጴጥሮስ ለቆርነሌዎስ የሰበው ስብከት ውስጥ ማርቆስ ወንጌል ጋር የይዘት መመሳሰል ሊኖረው ይችላል ። እንደተባለው ማርቆስ ወንጌሉን ከጴጥሮስ ሰምቶ ወይም በጴጥሮስ ንድፍ ከፃፈ ፤ ጴጥሮስ ደግሞ በስብከቱ ውስጥ የክርስቶስ ትንሳኤ በተደጋጋሚ ያነሳል አልፎ ተርፎ አይን እማኝ እንደሆነ ግልፅ ነው ። ስለዚህ ከትንሳኤ በኋላ ያለው ክስተት ትዕዛዝ  ሊነሳ ያስፈልጋል ። ከማርቆስ ወንጌል አመጣጥ አንፃር በጥድፊያ የተሞላና ስለማገልገል ሲነሳ ስለተመለከት በቀደሙት ምዕራፍ በመጨረሻው ላይ ተልዕኮን የሚያክል አደራ ያለበት የአገልግሎት ትዕዛዝ የማያሳይ ከሆነ አሁንም ከፅሁፍ ውስጣዊ ባህሪ አንፃር ይጋጫል ። በቁጥር ስምንት የሚያልቅ ከሆነ ትንሳኤውን እንደ መልካም ዜና ማየት ይከብዳል ምክኒያቱ በብዥታ ስለሚያልቅ ። አሳማኝ የሆነው የማርቆስ መዝጊያ ረጅሙ ነው ። በቁጥር 20 የሚያልቀው ነው ። ከውስጣዊውም ፣ ከውጫዊም ፣ ከታሪካዊ ማስረጃ ብንመለከት አሳማኙ ረጅሙ መዝጊያ ነው ። በእርግጥ በሶስቱ ቅፆች ከቁጥር 8 በኋላ አለመገኘቱ ጥርጣሬ ቢያስነሳም በሌሎች በሺ የሚቆጠሩ መጣጥፎች ላይ መገኘቱ በርካታ መረጃ እንዳለ ያሳያል( እውነት ለሁሉ ገፅ የማርቆስ ወንጌል 16:9-20 ትክክለኝነት) ። በቤተክርስቲያን አባቶች ከሶስቱ ቅጂዎች በፊት ከቁጥር 9 እስከ 20 ያለው ጠቅሰው በማስተማራቸውና በመፃፋቸው ምን ያህል ማርቆስ 16:9-20 የመፀሃፍ ቅዱሳችን አካል እንደሆነ ማረጋገጫ ይሆናል ። @cgfsd
534
9
ሐዋሪያው ጳውሎስ የክርስቶስን የፍቅር ጥልቀት ፣ ስፋት፣ ርዝመት ተናግሮ ከመታወቅ ያልፋል እያለ ይሔን ታላቅ ፍቅር ለማወቅ መንገዱ ብሎ የሚጠቁመው መንገድ አብረን፣ በጋራ በአንድነት፣ በህብረት፣ የቅዱሳን አንድነት ይላል። ፍቅሩን ታላቅ ነው ብሎ በግላዊ መንገድ ብቻ እንድንለማመደው አይጠቁመንም በጋራ በህብረት ይለናል ። ፍቅር በራሱ ግላዊነት አይታይበትም ። ሰው ብቻውን መሸከም የማይችለው ከእሱ የከበደ ሽክም ቢገጥመው ብቻውን አይሸከምም ይልቅ ሸክሙን የሚያግዘው ሌላ ሰው ይፈልጋል አብሮት እንዲሸከም ያደርጋል ፤ የእግዚአብሔር ፍቅር ከእኛ አቅም በላይ በመሆኑ መፍትሔው በጋራ ለማወቅ መጣጣር ነው ፣ በጋራም ቢታወቅ አይደለም ነገር ግን በመያያዝ ውስጥ ፍቅሩን ማጣጣም ስለሚኖር ነው ። የእግዚአብሔርን ፍቅር በትክክል ለመለማመድ ትክክለኛ ቦታ ለጳውሎስ በጋራ አብረን እንጂ ለብቻ አያወጣም። ይሔ ፍቅር በስላሴ መካከል የነበር ነው ። በአብ በወልድ ፣ በመንፈስ ቅዱስ መካከል የነበረ የህብረት ግንኙነት ነው ። በስላሴ መካከል ያየነው ፍቅር በራሱ ህብረታዊነት አለበት ። ስለዚህ የእግዚአብሔርን ፍቅር ለመለማመድ ትክክለኛው ስፍራ ህብረት ነው ። አስቴር አበበ በአንድ የመዝሙር Track ላይ እግዚአብሔር ፍቅር ነው የሚል ሀሳብ ትዘምራለች ነገር ግን የእግዚአብሔርን ፍቅር የምታብራራው በአማኞች የህብረት ህይወት ውስጥ ያለ የምንለማመመደው ጉዳይ የእርስ በእርስ ግንኙነታችን አድርጋ ነው ።  እግዚአብሔር ፍቅር ነው በማለት እንዲህ ትላለች    "የሌላውን እርቃን ተባብረን ስንሸፍን    ሞገስ አለ ከላይ የሚለቀቅልን በመያያዛችን      ፍቅር ነው ፍቅር እግዚአብሔር ፍቅር       እኛም ተጠርተናል እሱን እንድንመስል የክርስቶስ ፍቅር ስፋቱ፣ ርዝመቱ፣ ከፍታውና ጥልቀቱ ምን ያህል እንደሆነ ከቅዱሳን ሁሉ ጋር የመገንዘብ ኀይልን እንድታገኙ ነው። ኤፌሶን 3:18 @cgfsd
372
10
እፍራው ወይስ እንውደደው? በተደጋጋሚ ሲነገር የምንሰማው ትምህርተ ስላሴ ከባድ እንደሆነ ነው ። እርግጥ ነው በሰው መረዳት ልክ የሆነ አይደለም ። ስለ ስላሴ የሚነገር አባባል አለ " ስላሴን በሙላት ማወቅ አይምሮን ያሳጣል ስላሴን አለማወቅ ደግሞ ህይወት ያሳጣል " ።  ስላሴን ተረድተነው የማንጨርሰው ቢሆንም ለመረዳት ፣ ለማወቅ ፣ ለመገንዘብ ከመፈለግ  ወደኋላ ማለት የለብንም ። የስላሴን ትምህርት ውስብስ ብቻ እያደረግነው ከሄድን ትምህርቱን እየፈራነው ከአክብሮት ፍርሃት ይልቅ የዕውቀት መራቀቅ ብቻ እያደረግነው እንሄዳለን ። ይልቅ ከአክብሮት አንፃር እየፈራነው የስላሴን አስተምሮውን  መውደድ ያስፈልጋል። ብዙ ሰው ጋር ስላሴ ትምህርት ከባድ የሚለው አስተሳሰሰብ ስላሴን ለማወቅ ፍላጎት እንዳይኖር እያደረገ ይገኛል። የስላሴን ትምህርት መፍራት ያለብን ከአክብሮት አንፃር እንጂ ከማወቅ ወይም ለማወቅ ከመፈለግ መሆን የለበትም። የስላሴን አስተምሮ መወደድ ያሻናል ። @cgfsd
459
11
The eternal generation is our assurance of Gods love yididiya
460
12
#የናዝሬቱ ኢየሱስ ምን ያህል የሰው ልጅ ወገን እንደሆነ ከሚያስረዱን መጠሪያዎቹ መካከል የናዝሬቱ ኢየሱስ እየተባለ የተጠራበት መጠሪያ ነው ። የናዝሬቱ ኢየሱስ ማለት የተለየ በማዕረግ የሚገኝ ስም አይነት አይደለም ። የአንድ የአካባቢ መንደር መጠሪያ ነው። የናዝሬቱ ኢየሱስ ሲባል በአካባቢ ስም መለያ ተደርጎ እየተጠራ ነው ። ምሳሌ ጳውሎስ የጠርሴስ ሰው ነው ፤ የጠርሴሱ ሳውል ቢባል በአካባቢው ስም ለመለያነት ከሌሎች ስም እየተለየበት ነው ። ናዝሬት ኢየሱስ ያደገበት መንደር በመሆኑ በዛው ስም መለያ ተደረጎ ተሰጠው ። በአካባቢው ስም እንደ መለያ ሲጠራ ይሔም የሚያሳየው ምን ያህል ወደ ሰው አለም እንደቀረበ ፤  የሰው ወገን በምን ያህል እንደሆነ ነው ። በሰው ቋንቋ ፣ በሰው አኗኗር ፣ በሰው መንደር ፣ በፍፁም ሰውነት ሲገለጥ ሲጠራ የሰው ልጅ ወገንና እንደ ኾነ ምስክርነቱ ነው ። የናዝሬቱ ኢየሱስ
526
13
No text...
629
14
በማህበራዊ ሚዲያ ያየነው ክስተት ነበር ። አንድ በሌላ ቤተ-እምነት ያለ ሰው  ወደ አንድ ከተማ በመሄድ የወንጌል ስርጭት የወጡትን    ጥያቄ ይጠይቃል ከዛም መሃል አንዷ እንደዚህ በማለት መለሰች ። " ክርስቶስ ስንት ባህሪ አለው ?  እሷም መልሳ " በእርግጥ ብዙ ባህሪ አለው" ..ብላ መዘርዘር .......አንድ ገጠር በመሄድ ወንጌል የሚሰብክ ወዳጃችን እንደነገረን ቤተክርስቲያን ውስጥ ስላሴን አብራሩ ሲባሉ ' ሶስት ክርስቶስ' እያሉ ማብራሪያ ይሰጣሉ። ታዲያ እንደ ወንጌላዊያን አማኞች ዶክትሪን መማር ያለብን አይመስላችሁም ?  ፍትህ ለንፁህ ዶክትሪን✊
672
15
“እየተንቀጠቀጠና እየተደነቀ፦ ጌታ ሆይ፥ ምን አደርግ ዘንድ ትወዳለህ? አለው።”— ሐዋርያት 9፥6
637
16
በህይወት ከሰራው በሞቱ ባሰ ለዛ ኪዳን ሰው ምህረት ደረሰ አንድ እድል ብቻ ባይለምንህ ይኖር ነበረ  በቸርነትህ      አቤት ምህረት 🎶 @cgfsd
694
17
በመሪነት አገልግሎት ያለ አንድ ወንድም ነበር ፤ እሱም ሰፋ ያለን ሰአት ወስዶ በተደጋጋሚ ሲፀልይና የእግዚአብሔር ቃል ያጠናል። እኛም ከተለማመድነው የፀሎት የበለጠ ረዘም ያለ ሰአት የሚወስድ የፀሎት ልምምድ እንዳለው አስተውለን። ምንድን ነው ዋነኛ   የፀሎት ትጋትህ ምክኒያት ? ብለን ስጠይቀው እንዲህ መለሰልን " የምመራው ይህ ህዝብ እግዚአብሔር ማን ነው ? ብሎ ቢጠይቀ ምን ብዬ መልሳለሁ ? መልስ እንዳይታጣብኝ ነው ። @cgfsd
716
18
ስሰማው ያደኩት የእናቴ ፀሎት አለ ። ስትፀልይ ደጋግማ እንዲህ ትላለች "እግዚአብሔር አገዛዝህ ተመችቶናልና ግዛን " @cgfsd
696
19
እኔ ግን ወደ እልፍኜ ልግባ በስውር ወደሚያየኝ አምላክ በዚህ አለም አደባባይ እንዳበራ የፅድቅ ፀሃይ 🎶
688
20
Problem of evil እከይ ወይም በምድር ላይ ሆነ በህይወታችን ላይ የሚመጥብን ክፉ ነገሮች እንደ ሰውም እንደ ምድር ላይ ነዋሪም ለምን የሚል ጥያቄ እናነሳለን ( የህመም ጉዳዩች ፣ የተፈጥሮ አደጋ ፣ ሞት ፣ ስቃይ ፣ ጭካኔ ...ብዙ ብዙ )። የማቴዎስ ወንጌል በተራራው ስብከት ላይ problem of evil ለምን እንደዚህ ሆነ ብሎ ከማብራራት ይልቅ መፍትሔው ላይ ትኩረት ያደርጋል ። መፍትሔውም የእግዚአብሔር መንግስት መገለጥ ነው ይለናል ። የእግዚአብሔር መንግስት መገለጥ ደግሞ እንደ ማቴዎስ ወንጌል ሁለት አይነት መልክ አለው ። የመጣና የሚመጣ መንግስት ነው ። የእግዚአብሔር መንግስት መጥቷል ንጉሱ መሲህ በመምጣቱ አገዛዙ መንግስቱ በዚህ ምድር  ይፋዊ በሆነ መንገድ መጥቷል፤ ደግሞ ንጉሱ ክርስቶስ ኢየሱስ በዳግም መምጣቱ ሁሉን ሊገዛ ይመጣል መንግስቱም በፍፅምና ይመጣል ።  የእግዚአብሔር መንግስት የመጣና የሚመጣ ነው ። በአሁን በመምጣቱ ለሰው መንፈሳዊ ነፃነት በመስጠት ፣ የህይወት ለወጥ በማድረግ ፣ የጨለማው መንግስትን በመግለጥ፣ እውነተኛ ሰላም በማቀናጀት ፣ ፅድቅ በቤተክርስቲያን በኩል ለአለም በማስተዋወቅ፣ በማፅናናት ፣ ፍቅር በመስጠት problem of evil እየገለጠና አቅም እያሳጣ አለ ። በሙላት ሲመጣ ደግሞ ክፋት ፈፅሞ ይጠፋል ይደመሰሳል ። ያኔ መልስ ያጣንለት ለምን እንደዚህ ሆነ እየተባለ የሚነሱ የለምን ጥያቄ በመንግስቱ በሙላት መገለጥ ውስጥ ግሩም መልስ ያገኛል ። የእግዚአብሔር መንግስት አሁን በመካከላችን መኖሩ በመገኘቱ በማፅናናትና ህይወትን በማካፈል መልስ እየሰጠን ሲሆን በሙላት ወደፊት መምጣቱ ደግሞ ፈፅሞ መልስ ይሰጠናል ።  መፍትሔው የእግዚአብሔር መንግስት ነው ። @cgfsd
722