ru
Feedback
ገድለ ቅዱሳን

ገድለ ቅዱሳን

Открыть в Telegram

@Gedelat ለተለያዩ አስተያየት እና ጥቆማ ማድረስ ከፈለጉ በአድራሻችን ቢያደርሱን ይደርሰናል፡፡ በአድራሻችን ✍ @Mnfesawi_bot

Больше
6 509
Подписчики
-124 часа
-77 дней
-2530 дней
Архив постов
photo content
+1

[ ስንክሳር መስከረም - ፲ - ] .mp32.86 MB

🕊 † በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን † [   † መስከረም ፲ [ 10 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት †  ] †   🕊  በዓለ ስዕለ አድኅኖ   🕊   † ይህች ቀን በቤተ ክርስቲያን ስለ ቅዱሳት ስዕላት የሚነገርባት ክብርት ቀን ናት:: 'ስዕለ አድኅኖ' ማለት 'እግዚአብሔር በረድኤት የሚገለጥበት: አንድም በቅዱሳኑ አማካኝነት ጸጋ የሚገኝበት: የሚያድን ስዕል' ማለት ነው:: ስለዚህ ነገር አንዳንዶቹ ሊነቅፉን ይፈልጋሉ:: እኛ ግን ከማን እንደ ተማርነው እናውቃለን:: ከመነሻው እኛ ስዕልን አናመልክም:: ይልቁኑ አምልኮን እንፈጽምበታለን እንጂ:: ስዕልን ለሰው ልጆች የሰጠ ራሱ ባለቤቱ መሆኑን መጽሐፍ ቅዱስ ይመሠክራል:: እንዲያውም የመጀመሪያው ሰዐሊ ራሱ አምላካችን ነው:: አዳምን እንደ መልኩ: በምሳሌው ሲፈጥረው መላእክት የእግዚአብሔርን ምስል አዳም ላይ አይተዋልና:: [ዘፍ.፩፥፳፮] (1:26) ለሙሴም ስዕለ ኪሩብን እንዲስል ያዘዘ ራሱ ነው:: [ዘጸ.፳፭፥፳፪] (25:22) በዚያም ላይ ሆኖ ሙሴና አሮንን ሲነጋገራቸው ኑሯል:: በመቅደሰ ሰሎሞንም ተመሳሳይ ነገርን እናገኛለን:: [፪ዜና.፯፥፲፪] (7:12) , ፩ነገ.፱፥፩] (9:1) በሐዲስ ኪዳንም ጌታ ስዕለ ኪሩብ ያለበትን መቅደስ ቤቴ [ማቴ.፳፩፥፲፫] (21:13): የአባቴ ቤት [ዮሐ.፪፥፲፮] (2:16) ሲለው: በቅዱስ ሰውነቱ ሲመስለውም [ዮሐ.፪፥፳፩] (2:21) እንመለከታለን:: ቅዱስ ዻውሎስ ለገላትያ ሰዎች ስለ ስዕለ ስቅለት ሲያስታውሳቸው [ገላ.፫፥፩] (3:1): ቅዱስ ዮሐንስም በራዕዩ በደም የተረጨች ልብስ ብሎ ያላትን መተርጉማን ያትታሉ:: [ራዕይ.፲፱፥፲፫] (19:13) በትውፊት ትምሕርት ደግሞ የመጀመሪያው ስዕል በቅዱስ ሚካኤል ክንፍ ላይ የተሳለ ሲሆን ስዕሉም የእመቤታችን ነው:: "ሚካኤል በክነፊሁ ጾራ መንጦላዕተ ደመና ሠወራ" እንዳለ ቅዱስ ያሬድ:: በሐዲስ ኪዳን ደግሞ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለአቃርዮስና ለቬሮኒካ ፲፪ [12] ዓመት ደም ይፈሳት ለነበረችው ሴት) መልክአ ገጹን ሠጥቷቸዋል:: ['ቬሮኒካ' በላቲን 'ቬሮን-ኢኮን' 'እውነተኛ መልክ' እንደ ማለት ነው] ቀጥሎም ዮሐንስ ወንጌላዊ ለጢባርዮስ ቄሣር ስዕለ ስቅለቱን ሲስልለት ቅዱስ ሉቃስ ደግም የእመቤታችን 'ምስለ ፍቁር ወልዳን' ስሏል:: ከዚያም ሲያያዝ ይሔው ከእኛ ደርሷል:: ነገር ግን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በተለይ በከተሞች አካባቢ ቅርጾች በዝተዋልና ይሔ አላስፈላጊ መዋስ [ያውም ከመናፍቃን] ቢቀር መልካም ነው ባይ ነኝ:: ኋላ ቁጭ ብለው የሰቀሉትን ቁሞ ማውረድ ከባድ ነውና:: †   🕊   ጼዴንያ    🕊   † በዚህች ቀን ቅዱስ ሉቃስ የሳላትና ሥጋን የለበሰችው: ከፊቷም ወዝ የሚወጣትና ድውያንን የምታድነው የድንግል ማርያም ስዕለ አድኅኖ ወደ ጼዴንያ ከወዳጇ ከብጽዕት ማርታ ዘንድ ገብታለች:: ቅድስት ማርታ ሃብት ንብረቷን በአብርሃማዊ ተግባር [በምጽዋትና እንግዳን በመቀበል] ላይ ያዋለች ክብርት ሴት ናት:: ለእመ ብርሃን ካላት ፍቅር የተነሳ እንቅልፍ አልነበራትም:: ተግታ ታገለግላትም ነበር:: ስዕሏን እንዲያመጣላት የላከችው ኢትዮዽያዊው መነኩሴ አባ ቴዎድሮስ የስዕሏን ተአምራት ባየ ጊዜ ለራሱ ለመውሰድ ሞክሮ ነበር:: [እርሱ ምን ያድርግ! እኔም ብሆን ይህንኑ ነበር የማደርገው] ነገር ግን ከሁሉም በተሻለ የምትወዳት ቅድስት ማርታ ነበረችና በድንቅ ተአምር: በዚህች ቀን ወደ ጼዴንያ ገብታለች:: ቅድስት ማርታም ያለ ዕረፍት ስታገለግላት ኑራ ዐርፋለች:: ይህቺ ክብርት ስዕለ አድኅኖ የአሁን መገኛ 4 መረጃዎች አሉ:- ፩. ያለችው ኢትዮዽያ ውስጥ [ደብረ ዘመዳ በሚባል ገዳም] ነው:: የመጣችውም ከግማደ መስቀሉ ጋር ነው:: ፪. ያለችው በቀደመ ቦታዋ ነው:: ፫. የምሥራቅ አብያተ ክርስቲያናት ወስደዋታል:: ፬. በፈጣሪ ጥበብ ተሰውራለች:: †   🕊  ልደታ ለማርያም  🕊   † በግብጽ ውስጥ ከሚገኙ ገዳማት በአንዱ: ማለትም በአስቄጥስ ደብረ አባ መቃርስ የእመቤታችንን ዜና ሕይወት የሚናገር ፩ [1] መጽሐፍ አለ:: መጽሐፉ እንደሚለው እመ ብርሃን ድንግል ማርያም የተጸነሰችው ታሕሳስ ፲፯ [17] ቀን ነው:: በዚህ ሒሳብ መሠረት ደግሞ እመ አምላክ የተወለደችው መስከረም 10 ቀን ነው:: ዓለማቀፍ ትውፊቱ ግን ነሐሴ ፯ [7] ተጸንሳ: ግንቦት ፩ [1] ቀን መወለዷን ያሳያል:: †  🕊 ተቀጸል ጽጌ / አጼ መስቀል  🕊  † 'ተቀጸል ጽጌ' ማለት 'መስቀል ሆይ! በአበባ አጊጥ' እንደ ማለት ሲሆን 'አጼ መስቀል' ደግሞ አጼ ገብረ መስቀልን: አንድም አፄ ዳዊት ቀዳማዊን ይመለከታል:: ይህስ እንደ ምን ነው ቢሉ:- በሃገራችን ኢትዮዽያ የነገረ መስቀሉ ትምሕርት ከመጣ ጀምሮ መስቀል ይከበራል:: በአደበባባይ ግን እንዲከበር ያደረጉት የቅዱስ ካሌብ ልጅ አፄ ገብረ መስቀል ናቸው:: በወቅቱ ንጉሡ: ሠራዊቱ: ዻዻሱና ሕዝቡ በተገኙበት ቅዱስ ያሬድ "መስቀል መልዕልተ ኩሉ ነገር: ያድኅነነ እምጸር-መስቀል ከሁሉ ነገር በላይ ነው: ከጠላትም ያድነናል" እያለ ይዘምር ነበር:: የአበባ ጉንጉንም ለመስቀሉና ለንጉሡ ይቀርብ ነበር:: ከ፰፻ [800] ዓመታት በሁዋላም አፄ ዳዊት ግማደ መስቀሉን ባስመጡ ጊዜ መስከረም ቀን ተተክሎ ታላቅ በዓልም ሆኖ ተከብሯል:: †   🕊   ንግሥተ ሳባ    🕊   † ይሕቺ ደግ ኢትዮዽያዊት ከ፫ [3] ሺ ዘመናት በፊት የነበረች ደግ እናት ናት:: በሥጋዊ ደረጃ ከታንዛንያ እስከ የመን ያስተዳደረች ስመ ጥር ንግሥት ስትሆን በመንፈሳዊው ደረጃ ደግሞ እግዚአብሔር የቀባውን ሰው ፍለጋ ወደ ኢየሩሳሌም ተጉዛለች:: ከዚያውም አምልኮተ እግዚአብሔርን ከሥርዓተ ኦሪት ጋር አምጥታለች:: ድንግልናዋን ለታላቁ ንጉሥ ሰሎሞን ሰጥታ ምኒልክን ወልዳለች:: ይህቺ ንግሥት በጌታችን (በፈጣሪ) አንደበትም ተመስግናለች:: [ማቴ.፲፪፥፵፪] (12:42) በስምም "ሳባ: አዜብና ማክዳ ተብላ ትታወቃለች:: ዛሬ ዕለተ ዕረፍቷ ነው:: እመ ብርሃን ድንግል ማርያም ጣዕሟን ፍቅሯን: ጸጋ በረከቷን: ከስዕሏም ረድኤት ትክፈለን:: የቅዱሳኑም ክብር አይለየን:: 🕊 [  † መስከረም ፲ [ 10 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት   ] ፩. ቅድስት ድንግል እግዝእትነ ማርያም ፪. በዓለ ስዕለ አድኅኖ ፫. ቅዱስ እፀ መስቀል [ተቀጸል ጽጌ] ፬. ቅዱስ ሉቃስ ወንጌላዊ ፭. ቅድስት ማርታ ዘጼዴንያ ፮. ቅድስት ዮዲት ጥበበኛዋ ፯. ንግስተ ሳባ / ማክዳ / አዜብ ፰. ቅድስት መጥሮንያ ሰማዕት ፱. አፄ ዳዊት ንጉሥ ፲. ቅድስት አትናስያና ፫ [3] ልጆቿ [   †  ወርሐዊ በዓላት    ] ፩. ቅዱስ ናትናኤል ሐዋርያ ፪. ቅዱስ ኒቆላዎስ ዘሜራ ፫. ቅዱስ  ያዕቆብ ሐዋርያ [ወልደ እልፍዮስ] ፬. ቅድስት እሌኒ ንግስት ፭. ታላቁ ቅዱስ ቆስጠንጢኖስ " የማታስተውሉ የገላትያ ሰዎች ሆይ! በዓይናችሁ ፊት ኢየሱስ ክርስቶስ እንደ ተሰቀለ ሆኖ ተስሎ ነበር:: ለእውነት እንዳትታዘዙ አዚም ያደረገባችሁ ማን ነው ? " [ገላ.፫፥፩] (3:1) † ወስብሐት ለእግዚአብሔር † † ወለወላዲቱ ድንግል † † ወለመስቀሉ ክቡር † [ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ  ]          †              †               † ▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬ 💖                   🕊                    💖

[ ድምፀ ተዋሕዶ ] ጾመ ፍልሠታ ከመግባቱ አስቀድሞ ከቆመበት እነሆ ቀጥሏል።

photo content

[ የእግዚአብሔር ሕግ - ፴፪ - ] .mp311.39 MB

🕊 💖 🕊 [ 🕊 ድምፀ ተዋሕዶ 🕊 ] 🍒 🍒 [ ሕይወት የሚገኝባቸው የቅድስት ቤተክርስቲያን መንፈሳዊ ትምህርቶች በሊቃውንተ ቤተክርስቲያን በድምፅ ይቀርባሉ። ] [ ሳምንታዊ መርሐ-ግብር ]
🕊                        💖                       🕊           [  🕊  ድምፀ ተዋሕዶ   🕊  ]   🍒                                                    🍒 [  ሕይወት የሚገኝባቸው የቅድስት ቤተክርስቲያን መንፈሳዊ ትምህርቶች በሊቃውንተ ቤተክርስቲያን በድምፅ ይቀርባሉ።  ]         [   ሳምንታዊ መርሐ-ግብር   ] 🩵                        †                         🩵 [  ❝ የእግዚአብሔር ሕግ ፍጹም ነው ! ❞  ]             [    ክፍል ሠላሳ ሁለት   ]           💛   ድንቅ ትምህርት  💛 [ በመምህራችን ቀሲስ ኅብረት የሺጥላ ] 🍒                                                    🍒 ❝ የሚሰማኝ ግን በእርጋታ ይቀመጣል ፥ ከመከራም ሥጋት ያርፋል። ❞ [ ምሳ.፩፥፴፫ ] ════════════════                            †††                ✟𝐎𝐑𝐓𝐇𝐎𝐃𝐎𝐗Y✟ 🕊                        💖                       🕊                              👇

photo content

+1
4 ያቺን የጥሪ ቀን.mp38.01 MB

🕊 💖 🕊 🩵 [ መዝሙረ ተዋሕዶ ] 🩵 🕊 💖 🕊 ኦርቶዶክሳዊ መዝሙር ንጹሕና የተቀደሰ ነው ፥ ለእግዚአብሔር ምስጋናና ልመና የሚቀርብበት ፣ ይቅርታና ምሕረት የሚጠየቅበት ፣ ሰውን ሳይሆን
🕊                        💖                        🕊   🩵       [   መዝሙረ ተዋሕዶ   ]        🩵 🕊                        💖                     🕊 ኦርቶዶክሳዊ መዝሙር ንጹሕና የተቀደሰ ነው ፥ ለእግዚአብሔር ምስጋናና ልመና የሚቀርብበት ፣ ይቅርታና ምሕረት የሚጠየቅበት ፣ ሰውን ሳይሆን እግዚአብሔርን ደስ ለማሰኘት የሚዘጋጅ ንጹሕ መስዋዕት ነው ፥ በአበው ጸሎት ይዘጋጃል ፥ ከስጋዊና ከደማዊ ሀሳብ የራቀ ነው ፥ ልቦናን ወደ ንስሐ ይጠራል ፥ ከኃጢአትና ከክፉ ሥራ የመለየት ኃይል አለው ፥ ክፉ መንፈስን ከሰው ልብ ያርቃል ፥ መረጋጋትን ልቦናን ዘልቆ የሚሰማ ውስጣዊ ሰላምን ይሰጣል ፥ በአሚነ ሥላሴ ያጸናል ፥ የክርስቶስን የባህርይ አምላክነትና መሐሪነት ይመሰክራል ፥ የእመቤታችንን ፍቅር በልቦና ያሳድራል ፥ በእናትነቷና በምልጃዋ እንድንታመን ያደርጋል ፥ በቅዱሳን ጸሎትና በቃል ኪዳናቸው ያጸናናል ፥ ሥርዓተ ቤተክርስቲያንን ያስተምረናል ፥ ፈሪሐ  እግዚአብሔርንና ያጎናጽፈናል፡፡ 🕊                        💖                      🕊 ተወዳጆችሆይ ፦ በተቀደሰ ሰማያዊ ያሬዳዊ ዜማ ነብሳችንን እናስጊጣት፡፡ ከደጋጎቹ አባቶቻችን ጋር ከዓለም ርኩሰት በተለየ የተቀደሰ ዝማሬ አምላካችን እግዚአብሔርን እናመሥግን፡፡ ለስጋዊ ጆሮዎች ከሚመች ከረከሰ የተሃድሶ የኑፋቄ እርሾ ልቦናችንን እንጠብቅ፡፡ ገንዘብን ስለመውደድ ከሆነ ከሥጋዊ ሥራ ፈጽሞ እንለይ፡፡ 🌸                                                  🌸                            †††                ✟ 𝐎𝐑𝐓𝐇𝐎𝐃𝐎𝐗Y ✟ 🕊                        💖                        🕊

photo content

[ ስንክሳር መስከረም - ፱ - ] .mp37.42 MB

🕊 † በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፤፤ † [  † መስከረም ፱ [ 9 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት †  ] † 🕊  ቅዱስ ሚካኤል ሊቀ መላእክት 🕊  † † ቅዱሳት መጻሕፍት እንደሚነግሩን የመላእክት ሁሉ አለቃቸው በፈጣሪው ኃይል ብዙ ድንቆችን ሠርቷል:: ከመጀመሪያው ሰው አዳም ጀምሮ እስከ ዛሬ ድረስ: አምነው ለሚጠሩት ረዳት ነው:: ዘወትርም ያድናቸው ዘንድ በሚፈሩት ሰዎች ዙሪያ ይሠፍራል:: [መዝ.፴፫፥፯] (33:7) ¤ እግራችን እንዳይሰናከል ዘወትር ይጠብቀናል:: [መዝ.፺፥፲፩] (90:11) ¤ የቅዱስ ሚካኤል ስሙ ድንቅ ነው:: [መሳ.፲፫፥፲፰] (13:18) ¤ ከእርሱ በቀርስ የሚያጸና ማን አለና! [ዳን.፲፥፳፩] (10:21) ¤ ለሕዝቡም የሚቆም ታዳጊ መልአክ ነው:: [ዳን.፲፪፥፩] (12:1) ¤ በፊቱ ሲቆምም ስለ ክብሩ ጫማ አውልቆ: ባጭር ታጥቆ ነው:: [ኢያ.፭፥፲፫] (5:13) + ይህ ድንቅ መልአክ ከሺህ ዓመታት በፊት በሮም ከተማ ይህንን ድንቅ ተአምር በዚህች ዕለት መሥራቱን ቤተ ክርስቲያን ትመሰክራለች:: በድሮው የሮም ግዛት 'ሩፍምያ' የምትባል ከተማ ነበረች:: ይህች ከተማ ክርስቲያኖችም: ኢአማንያንም ተቀላቅለው የሚኖሩባት ናት:: በከተማዋ የክርስቲያኖች ቁጥር ትንሽ ቢሆንም በእምነት ግን ጠንካሮች ነበሩ:: በተለይ ደግሞ የቤተ ክርስቲያኗ መጋቢ ባለ ፍጹም እምነት ሰው ነበር:: በቦታው የቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን በመኖሩም ብዙ ተአምራት ይደረጉ ነበር:: ተበለጥን የሚል ስሜት የተሰማቸው አሕዛብ [ዮናናውያን] ግን ይሕንን ቤተ ክርስቲያን ለማጥፋት ተማማሉ:: በቀጥታ ሔደው ቢያፈርሱት ወይም ቢያቃጥሉት በሕግ እንደሚጠየቁ ያውቃሉና በሥጋዊ ጭንቅላታቸው ዘዴ ያሉትን መከሩና ወሰኑ:: በከተማዋ ዳር የሚያልፍ አንድ ትልቅ ወንዝ አለ:: በሞላ ጊዜ ያገኘውን ሁሉ ጠርጐ የሚወስድም ነበር:: ታዲያ ክፋተኞቹ ሌሊት ሌሊት እየተነሱ የሚሔድበትን መንገድ ዘግተው: ወደ ቤተ ክርስቲያኑ አቅጣጫ መንገድ ከፈቱለት:: ከቀናት በኋላ ከባድ ዝናብ በዚህች ቀን ጣለ:: ወንዙ ትልቅ ነውና ያገኘውን ሁሉ እያገላበጠ ደረሰ:: በወቅቱ በቅዱሱ መልአክ መቅደስ ውስጥ ከመጋቢው በቀር ሰው አልነበረምና አስፈሪ ድምጽ ሰምቶ ቢወጣ ወንዙ እየደነፋ ወደ ቤተ ክርስቲያኑ እየመጣ ነው:: አሰበው: ከደቂቃዎች በሁዋላ ቤተ ክርስቲያኑ እንዳልነበረ ሊሆን ነው:: እርሱ አንድ ተስፋ ነበረውና ወደ ውስጥ ገብቶ ቅዱስ ሚካኤልን ተማጸነ:: ከዚያ ላለመውጣትም ወሰነ:: ትንሽ ቆይቶ በታላቅ ኃይል ወንዙ ደረሰ:: በዚህ ጊዜ ግን ቅዱስ ሚካኤል በግርማ ከሰማይ ወርዶ በወንዙ ፊት ቆመ:: መጋቢውንም "ጽና: አትፍራ" ብሎት በያዘው የብርሃን በትረ-መስቀል መሬትን አንድ ጊዜ መታት:: በዚያች ቅጽበትም ትልቅ ሸለቆ ተፈጠረ:: ወንዙም በሸለቆው ውስጥ አልፎ ሔደ:: +የሚገርመው ሸለቆው የተፈጠረው በቤተ ክርስቲያኑ በታች ነው:: ቅዱስ ሚካኤል ግን መጋቢውን ባርኮት በክብር ዐረገ:: በማግስቱ ክርስቲያኖቹ ይህንን አይተው ደስ አላቸው:: መልአኩንም አከበሩት:: አሕዛብ ግን አፈሩ:: † 🕊 ቅዱስ ቢሶራ ሰማዕት  🕊  † † በዘመነ ሰማዕታት ክርስቲያን መሆን ብቻ የሚያስከፍለው ዋጋ ብዙ ነበር:: ከምንም በላይ መከራው የጸናባቸው ግን የቤተ ክርስቲያን መሪዎች ነበሩ:: ክደው ያስክዳሉ በማለት አብዝተው ያሰቃዩአቸው ነበር:: ቶሎም አይገድሏቸውም:: መከራውን ከማራዘም በቀር:: ከእነዚህም አንዱ አባ ቢሶራ ነው:: እርሱ በምድረ ግብፅ 'መጺል' ለምትባል ሃገር ኤዺስ ቆዾስ ነበረ:: በእድሜው አረጋዊ: በትምሕርቱ ምሑር: በምግባሩ ቅዱስና በእረኝነቱም የተመሠከረለት በመሆኑ በምዕመናን ዘንድ ተወዳጅ ነበር:: መከራው እየገፋ ሲመጣ ግን ቅዱሱ በመፍራት ፈንታ የሰማዕትነት ፍቅር አደረበት:: ስለ ሃይማኖት መሞትን እና ቶሎ ወደ ክርስቶስ መሔድን ናፈቀ:: ነገር ግን መልካም እረኛ ነውና በጐቹን [ምዕመናንን] እንዲሁ ሊተዋቸው አልወደደም:: ሰብስቦ ምን እንዳሰበ አማከራቸው:: የሰሙት ነገር ክርስቲያኖችን አስለቀሳቸው:: "አቡነ ለመኑ ተኀድገነ-አባታችን ለማን ትተኸን ትሔዳለህ?" ሲሉም ከእግሩ ወደቁ:: እርሱ ግን አስረድቷቸው: አጽናንቷቸውም በእንባ ተሰናበታቸው:: አንዳንዶቹ ደግሞ "አብረንህ እንሞታለን" ብለው ተከተሉት:: ቅዱስ አባ ቢሶራን ከብዙ ስቃይ በኋላ አረማውያን ከነተከታዮቹ በዚህ ቀን ገድለውታል:: †   🕊  ቅዱስ ያሳይ ንጉሥ  🕊  † † በቀደመው ዘመን መንግስታቸውን ትተው ከመነኑ ነገሥታት አንዱ ቅዱስ ያሳይ ነው:: ምናኔ በቁሙ ከባድ ነው:: መንግስትን: ዙፋንን: ክብርን ትቶ መመነንን ደግሞ ከማድነቅ በቀር እንዲህ ብለው ሊገልጹት ይከብዳል:: ቅዱስ ያሳይም መንግስቱን ትቶ ልምላሜ ወደሌለበት ደረቅ በርሃ ሔደ:: በዚያም ከአንዲት ዛፍ በቀር ምንም ነገር አላገኘም:: በዚያች ደረቅ ዛፍ ላይ ወጥቶ ለዓመታት በጾምና በጸሎት ተጋደለ:: በዘመነ ተጋድሎው ከዛፏ አልወረደም: ሰውም አይቶ አያውቅም:: በመጨረሻም ስለ ቅድስናው ዛፏ ለምልማለች:: እርሱም በዚህች ቀን ዐርፏል:: † አምላከ ቅዱሳን ተራዳኢ መልአክን ይዘዝልን:: ከወዳጆቹ በረከትም አይለየን:: 🕊 [  † መስከረም ፱ [ 9 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት  ] ፩. ቅዱስ ሚካኤል ሊቀ መላእክት ፪. ቅዱስ ቢሶራ ሰማዕት ፫. ቅዱስ ያሳይ ንጉሥ ፬. ቅዱስ ፋሲለደስ ሰማዕት [ ልደቱ ] ፭. "14,730" ሰማዕታት [ የቅዱስ ፋሲለደስ ማሕበር ] † " የፋርስ መንግስት አለቃ ግን ሀያ አንድ ቀን ተቁዋቁዋመኝ:: እነሆም ከዋነኞቹ አለቆች አንዱ ሚካኤል ሊረዳኝ መጣ:: እኔም ከፋርስ ነገሥታት ጋር በዚያ ተውሁት:: " † [ዳን.፲፥፲፫] (10:13) † ወስብሐት ለእግዚአብሔር † † ወለወላዲቱ ድንግል † † ወለመስቀሉ ክቡር † [ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ  ]          †              †               † ▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬ 💖                   🕊                    💖

photo content

[ + የሐሜት መርዝ + ] .mp312.65 MB

🕊 💖 🕊 🩵 [ ምክረ ቅዱሳን ] 🩵 ▷ " የ ሐ ሜ ት አ ስ ከ ፊ ነ ት ! " [ 💛 ከቅዱስ ይስሐቅ ሶርያዊ 💛 ] ▬▬▬▬▬▬ ♱ ▬▬▬▬▬▬ ❝ እንግዲህ ክፋትን ሁሉ ተንኰልንም ሁሉ ግብ
🕊                        💖                        🕊      🩵       [   ምክረ ቅዱሳን   ]        🩵  ▷   "  የ ሐ ሜ ት አ ስ ከ ፊ ነ ት   !  " [ 💛   ከቅዱስ ይስሐቅ ሶርያዊ  💛   ] ▬▬▬▬▬▬   ♱    ▬▬▬▬▬▬ ❝ እንግዲህ ክፋትን ሁሉ ተንኰልንም ሁሉ ግብዝነትንም ቅንዓትንም ሐሜትንም ሁሉ አስወግዳችሁ ፥ ጌታ ቸር መሆኑን ቀምሳችሁ እንደ ሆነ ፥ ለመዳን በእርሱ እንድታድጉ አሁን እንደ ተወለዱ ሕፃናት ተንኰል የሌለበትን የቃልን ወተት ተመኙ። ❞ [ ፩ጴጥ.፪፥፩ ] 🌸                                                  🌸                            †††                ✟ 𝐎𝐑𝐓𝐇𝐎𝐃𝐎𝐗Y 🕊                        💖                        🕊

photo content

A lemedanu hiywot.mp34.22 MB

💛                        †                         💛 🌼  [  አዲስ ዓመት ማክበር ማለት ! ]   🌼 🌸                                                    🌸 [ እነዚህን ሰዎች መራቅ ጠላትም ማድረግ ይፈቀዳል፡፡ ......... ] 🕊 ❝ የበደሉንን ሰዎችስ ወዳጅ ማድረግ ይገባል ? አዎ ! ለእግዚአብሔር ክብር ሲባል የበደሉንን ሰዎች ወዳጅ ማድረግ ይገባናል፡፡ ሰውን ወዳጅ  ማድረግ ሲባል ያንን ሰው ከገንዘባችን ፣ ከማዕዳችን እንዲካፈል በእኛም እንዲደገፍ ማድረግ ማለት አይደለም፡፡ አንድን ሰው እውነተኛ ወዳጅ ኾነነው አንድም አደረግነው የሚባለው ነፍሱን እንዳይጎዳ ብንገሥፀውና ብንመክረው ፣ ቢበድል [በበደሉ የሚጎዳው እርሱ ራሱ ነውና] እንደ ጠላት ሳይኾን እንደ ወዳጅ ቀረብ ብለን የሚረባውን ብንነግረው ፣ ከወደቀበት የኃጢአት አረንቋ  እንዲነሳ ብናደርገው ለዚህም ዘወትር በጸሎት ፣ በስግደት ፣ በስሙ በመመጽወት ብንረዳውና ወደ እግዚአብሔር እንዲቀርብ ብናደርገው ነው፡፡ ለእግዚአብሔር ክብር ሲባል ሰውን ጠላት ማድረግስ ? አዎ ! ይቻላል፡፡ ለመኾኑ ስለ እግዚአብሔር ክብር ብሎ ሰውን ጠላት ማድረግ ሲባል ምን ማለት ነው ? ስለ እግዚአብሔር ብሎ ሰውን ጠላት ማድረግም ይፈቀዳል፡፡ ይህን ከዚህ በፊት ያላከናወነው ከኾነም ከአሁኑ አዲስ ዓመት መጀመር እንችላለን ፤ ለእግዚአብሔር ብለን ሰውን ጠላት ማድረግ፡፡ ለምሳሌ ፦ አንድ መልካም ያልሆነ ፣ ክፋትን የተመላ ፣ ንግግሩ [ ትምህርቱ ] ኹሉ በምንፍቅና መርዝ የተለወሰ ፣ ዘወትር ነፍሳችንን የሚያውካትና የሚጎዳት ሰው ካለ ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ " ቀኝ ዐይንህም ብታሰናክልህ አውጥተህ ከአንተ ጣላት" እንዳለ [ ማቴ.፭:፳፱ ] እነዚህን ሰዎች መራቅ ጠላትም ማድረግ ይፈቀዳል፡፡ ምንም እንኳን እንደ ቀኝ አይናችን የምናያቸው ወዳጆቻችን ቢሆኑም ነፍሳችንን የሚጎዷት ከኾነ ከእኛ ዘንድ ልናርቃቸው ይገባል፡፡ ❞ [ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ] ▬▬▬▬▬▬   ♱    ▬▬▬▬▬▬                           †††                ✟ 𝐎𝐑𝐓𝐇𝐎𝐃𝐎𝐗Y ✟ 🕊                        💖                        🕊

photo content