ru
Feedback
FastMereja.com

FastMereja.com

Открыть в Telegram

📈 Аналитический обзор Telegram-канала FastMereja.com

Канал FastMereja.com (@fastmereja) языкового сегмента Амхарский является активным участником. Сейчас сообщество объединяет 49 135 подписчиков, занимая 3 557 место в категории Образование и 653 место в регионе Эфиопия.

📊 Показатели аудитории и динамика

С момента создания невідомо проект демонстрирует стремительный рост, собрав аудиторию из 49 135 подписчиков.

Согласно последним данным от 02 июля, 2026, канал показывает стабильную активность. За последние 30 дней изменение числа участников составило -586, а за последние 24 часа — -9, при этом общий охват остаётся высоким.

  • Статус верификации: Не верифицирован
  • Уровень вовлечённости (ER): Средний показатель вовлечённости аудитории составляет 12.66%. В первые 24 часа после публикации контент обычно набирает 7.75% реакций от общего числа подписчиков.
  • Охват публикаций: В среднем каждый пост получает 6 221 просмотров. В течение первых суток публикация набирает 3 808 просмотров.
  • Реакции и взаимодействия: Аудитория активно поддерживает контент: среднее количество реакций на один пост — 31.

📝 Описание и контентная политика

Описание канала не предоставлено.

Благодаря высокой частоте обновлений (последние данные получены 03 июля, 2026) канал поддерживает актуальность и высокий уровень охвата публикаций. Аналитика показывает, что аудитория активно взаимодействует с контентом, что делает его важной точкой влияния в категории Образование.

49 135
Подписчики
-924 часа
-1147 дней
-58630 день
Архив постов
‘Trust’ እና ‘Google TV’ የተባሉ መተግበሪያዎች የባንክ አካውንትን ለአደጋ እያጋለጡ ነው ​#FastMereja I በኢንተርኔት ማስፈንጠሪያዎች (links) አማካይነት ወደ ስልኮች በመግባት የባንክ ሂሳብን የሚያጠፉ “Trust”፣ “Google TV” እና “Known” የተባሉ አደገኛ የአንድሮይድ መተግበሪያዎች በስፋት እየተሰራጩ መሆኑን የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አስታወቀ። እነዚህ መተግበሪያዎች በተለይ በGoogle Chrome፣ Telegram እና WhatsApp መድረኮች ላይ የሚጋሩ ሲሆን፥ ተጠቃሚዎች ሳያውቁ የገንዘብ ዝውውር በመፈጸም ከፍተኛ ጉዳት እያደረሱ ይገኛሉ። ​ይህ በቴክኖሎጂ የታገዘ የሳይበር ጥቃት በስፋት እየተስተዋለ የመጣው ተጠቃሚዎች ከተላኩላቸው አጠራጣሪ ሊንኮች ላይ መተግበሪያዎቹን ሲያወርዱ መሆኑ ታውቋል። መተግበሪያዎቹ አንዴ ስልክ ላይ ከተጫኑ በኋላ ከሞባይል ባንኪንግ ጋር የተያያዙ ሚስጥራዊ መረጃዎችን በመስረቅ ገንዘብ የመውሰድ አቅም እንዳላቸው ተገልጿል። ህብረተሰቡ ከዚህ መሰሉ የሳይበር ዘረፋ ራሱን ለመጠበቅ መተግበሪያዎችን ከታመኑ ምንጮች (እንደ Play Store ወይም App Store) ብቻ ማውረድ እንዳለበት ባንኩ አሳስቧል። ​ከተጠቀሱት የማህበራዊ ሚዲያ መድረኮች የሚላኩ አጠራጣሪ ሊንኮችን አለመክፈት እና በሞባይል ባንኪንግ መተግበሪያዎች ላይ የባዮሜትሪክ (የፊት ወይም የአሻራ) እና የፒን (PIN) የደኅንነት ማረጋገጫዎችን አጣምሮ መጠቀም ለአደጋው የመጋለጥ እድልን በእጅጉ እንደሚቀንስ ተነግሯል። #ሳይ_ቴክ

ማስተር ኤዶንያስ ጌቱ በዓለም አቀፉ የGTTF ጉባኤ ታሪክ ሰሩ #FastMereja I በፊሊፒንስ ማኒላ በተካሄደውና ከ170 በላይ ሀገራት በተሳተፉበት የዓለም አቀፍ ትሬዲሽናል ቴኳንዶ ፌዴሬሽን (GTTF) ዓለም አቀፍ ጉባኤና ሻምፒዮና ላይ የኢትዮጵያ ተወካይና የEGTTF ተጠሪ ማስተር ኤዶንያስ ጌቱ ከአፍሪካ በብቸኝነት በመገኘት የሀገሪቱን ባንዲራ በክብር አስጠብቀዋል። ማስተሩ በውድድሩ ላይ ላሳዩት ከፍተኛ ሙያዊ ብቃትና መሪነት የላቀው “Outstanding LEADER AWARD” የተሰኘ የክብር ሽልማት የተበረከተላቸው ሲሆን፣ ማርሻል አርትስን ከሀገራዊ የቱሪዝም ዘርፍ ጋር በማስተሳሰር “ስፖርታዊ ቱሪዝምን” ለማሳደግ ያለመ አዲስ ስትራቴጂካዊ ብሄራዊ ራዕይም ይፋ አድርገዋል። ለሰባት ቀናት በደመቀ ሁኔታ በተካሄደው በዚህ ታላቅ ዓለም አቀፍ መድረክ ላይ ማስተር ኤዶንያስ ጌቱ በዓለም አቀፍ ደረጃ በዳኝነት (Umpire) ከፍተኛ ሙያዊ ብቃታቸውን አሳይተዋል። ከዚህም በተጨማሪ እጅግ ማራኪና አስደናቂ የነበረውን የዲሞንስትሬሽን ቡድን (Demonstration Team) በበላይነት በመምራት መድረኩን ያስደመሙ ሲሆን፣ ይህንን ተከትሎም ስፖርቱን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለማስፋፋትና በመሪነት ላሳዩት ወደር የለሽ አስተዋጽኦ በታላላቅ ግራንድ ማስተሮች ፊት የላቀ መሪነት ሽልማት ተበርክቶላቸዋል። ይህ ታላቅ መድረክ የውድድር ስፍራ ብቻ ሳይሆን ለኢትዮጵያ አዲስ የኢኮኖሚና የባህል በር የከፈተ ሆኗል። በማስተር ኤዶንያስ መሪነት ይፋ የሆነው አዲሱ ራዕይ የስፖርቱን እሴቶች ከቱሪስት መዳረሻዎች ጋር በማጣመር የውጭ ሀገር ስፖርተኞችንና ጎብኚዎችን ወደ ኢትዮጵያ ለመሳብ ያለመ ነው። በፕሮግራሙ ላይ የታደሙት ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት፣ ከተለያዩ ዘርፎች የተውጣጡ ታዋቂ ግለሰቦች፣ አንጋፋ የቴኳንዶ ባለሙያዎች፣ ማስተሮች እና ግራንድ ማስተሮች ይህንን ራዕይ በከፍተኛ ደረጃ ያደነቁ ሲሆን፣ ማርሻል አርትስ የሀገርን ባህልና ገጽታ ለማስተዋወቅ ያለውን ታላቅ አቅም በተግባር ለማዋል ሙሉ ድጋፋቸውን እንደሚሰጡ አረጋግጠዋል።

አዋሽ ባንክ ከታክስ በፊት 40.7 ቢሊዮን ብር ያልተጣራ ትርፍ ማግኘቱን አስታወቀ። ​#FastMereja I አዋሽ ባንክ እ.ኤ.አ. ጁን 30 ቀን 2026 በተጠናቀቀው የሒሳብ ዓመት በታሪኩ ከፍተኛ የተባለውን እመርታ በማስመዝገብ፣ ጠቅላላ የተቀማጭ ገንዘብ መጠኑን ብር 467.8 ቢሊዮን ማድረሱን የባንኩ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ፀሐይ ሽፈራው በዛሬው ዕለት በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ አስታወቁ። ይህ አፈጻጸም ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የብር 135 ቢሊዮን (41 በመቶ) ጭማሪ ያሳየ ሲሆን፣ በባንኩም ሆነ በሀገሪቱ የግል ባንኮች ታሪክ በአንድ ዓመት ውስጥ የተመዘገበ እጅግ ከፍተኛው የተቀማጭ ገንዘብ ዕድገት መሆኑ ተነግሯል። ​የውጭ ምንዛሬ ግኝትን በተመለከተ፣ መንግሥት ካደረገው የውጭ ምንዛሬ ማሻሻያ ፖሊሲና ባንኩ ከተከተላቸው አሠራሮች በመነሳት ከፍተኛ ዕድገት የታየ ሲሆን፣ የ635 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ጭማሪ በማሳየት በሰኔ 2026 መጨረሻ ላይ ጠቅላላ የውጭ ምንዛሬ ግኝቱ 2.65 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር ደርሷል። በተመሳሳይ የባንኩ ጠቅላላ ሀብት ብር 622 ቢሊዮን የደረሰ ሲሆን፣ የተከፈለ ካፒታሉ ደግሞ በ38 በመቶ (የብር 10.6 ቢሊዮን) ዕድገት በማሳየት 38.5 ቢሊዮን ብር ደርሷል። ይህ የካፒታል መጠን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ለግል ባንኮች ካስቀመጠው ዝቅተኛው ባለ 5 ቢሊዮን ብር መመዘኛ ጋር ሲነጻጸር ከሰባት እጥፍ በላይ ከፍ ያለ በመሆኑ ባንኩ ሊያጋጥሙ የሚችሉ ስጋቶችን የመቋቋም አቅሙ በከፍተኛ ደረጃ ማደጉን ያሳያል ተብሏል። ​በበጀት ዓመቱ አዋሽ ባንክ ከብር 85.37 ቢሊዮን በላይ ጠቅላላ ገቢ የሰበሰበ ሲሆን፣ ጠቅላላ ወጪው ብር 44.62 ቢሊዮን ሆኖ ተመዝግቧል። በዚህም መሠረት ከቀረጥና ከቅናሽ በፊት ያለው ጠቅላላ ትርፍ (Gross Profit before Provision and Tax) ብር 40.7 ቢሊዮን የደረሰ ሲሆን፣ ይህም ካለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጸር የብር 11.8 ቢሊዮን ብልጫ አለው። ​ባንኩ በአሁኑ ወቅት ከ17 ሚሊዮን በላይ ደንበኞችን ማፍራት የቻለ ሲሆን፣ ይህንን ስኬት ያገኘው በሀገሪቱ ባሉት 1,010 መደበኛ ቅርንጫፎች፣ ከ10 በላይ የዲጂታል ቅርንጫፎች (e-branches)፣ ከ1,270 በላይ ኤቲኤሞች፣ ከ18,000 በላይ የባንክ ወኪሎች እንዲሁም እንደ Awash Birr Pro እና Online Banking ባሉ የኦንላይን ቴክኖሎጂዎቹ አማካኝነት ነው። ​አዋሽ ባንክ ባሳየው ተከታታይና እመርታ የተሞላበት የሥራ አፈጻጸም ምክንያት በGlobal Finance ለ5 ተከታታይ ዓመታት “የኢትዮጵያ ምርጥ ባንክ” ተብሎ የተመረጠ ሲሆን፣ የሽልማት ሥነ-ሥርዓቱም በሚቀጥለው ዓመት በሚካሄደው የዓለም ባንክና ዓለም አቀፍ የገንዘብ ድርጅት (IMF) ስብሰባ ወቅት እንደሚፈጸም ታውቋል። ባንኩ ከንግድ ሥራው ጎን ለጎን ማኅበራዊ ኃላፊነቱን ለመወጣት በተለያዩ ማኅበራዊና አካባቢያዊ ችግሮች ለተጠቁ የሕብረተሰብ ክፍሎች ድጋፍ የሚውል የብር 500 ሚሊዮን ወጪ ማድረጉም በመግለጫው ተጠቅሷል። #ቢዝነስ

በቬንዙዌላው አስከፊ የመሬት መንቀጥቀጥ ፍርስራሽ ውስጥ ለ32 ሰዓታት የተቀበሩት እናትና የ18 ቀናት ጨቅላ ሕፃን በሕይወት ተረ በቬንዙዌላው አስከፊ የመሬት መንቀጥቀጥ ፍርስራሽ ውስጥ ለ32 ሰዓታት የተቀበሩት እናትና የ18 ቀናት ጨቅላ ሕፃን በሕይወት ተረፉ ​#FastMereja I በሰሜናዊ ቬንዙዌላ በደረሰው ተከታታይ እና አስከፊ የመሬት መንቀጥቀጥ ሳቢያ በፈረሰ የመኖሪያ ሕንፃ ውስጥ ለ32 ሰዓታት ያህል በፍርስራሽ ስር ተቀብረው የነበሩት አንዲት እናት እና የ18 ቀናት ዕድሜ ያላቸው ጨቅላ ልጃቸው በተአምራዊ ሁኔታ በሕይወት ተርፈው መውጣታቸውን ዓለም አቀፍ የነፍስ አድን ቡድኖች አስታውቀዋል። ​ዳያና ፓቲኞ የተባለችው እናት ላ ጉዋይራ በተባለችው የባሕር ዳርቻ ከተማ በሚገኘው ባለ 8 ፎቅ የመኖሪያ ሕንፃ ላይ ሳለች ነበር 7.2 እና 7.5 በሬክተር ስኬል የተመዘገቡት ድርብ የመሬት መንቀጥቀጦች ያጠቁት። ሕንፃው ሲደረመስ ሕፃን ልጇን ኋን ዳቪድን አቅፋ አብራ በፍርስራሹ ውስጥ ብትቀበርም፣ ህጻኑን ከደረቷ ሳትለይ ለሰዓታት መቆየቷንና በሕይወት ለመቆየቷም ዋነኛው ምክንያት እሱ እንደነበር ለቢቢሲ በሰጠችው ቃል ገልጻለች። የነፍስ አድን ሠራተኞች ፍርስራሹን በመቆፈር መጀመሪያ የ18 ቀናት ጨቅላ ሕፃኑን አውጥተው ለተጨነቀው አባቱ ያስረከቡ ሲሆን፣ ከአንድ ሰዓት ተኩል ተጨማሪ ከፍተኛ ጥረት በኋላ እናቲቱንም በሕይወት ማውጣት ችለዋል። እናቲቱ በጉልበቷ ላይ ስብራት የደረሰባት ቢሆንም፣ ሕፃኑ ግን ምንም ዓይነት ከባድ ጉዳት ሳይደርስበት መተርፉ አነጋጋሪ ሆኗል።

ፖሊስ መስላ በፊቼ ከተማ ስትዘርፍ የነበረችው ሴት በቁጥጥር ስር ዋለች ​#FastMereja I ​በሰሜን ሸዋ ዞን የፊቼ ከተማ አስተዳደር፣ የፖሊስ የደንብ ልብስ በመልበስ እና የጦር መሳሪያ በመያዝ የዘረፋ ወንጀል ስትፈጽም የነበረች ሴት በቁጥጥር ስር ዋለች። ተጠርጣሪዋ አበባ ቁንቢ ትባላለች። ​የፊቼ ከተማ ፖሊስ መምሪያ ምክትል ኢንስፔክተር ቶልቻ ኃይሉ ለቢቢሲ እንደገለጹት፣ ተጠርጣሪዋ የፖሊስ የደንብ ልብስ በመልበስ እና ሽጉጥ በመታጠቅ የተለያዩ የዘረፋ ወንጀሎችን ስትፈጽም ቆይታለች። ​በተለያዩ የንግድ ተቋማት በመሄድ የዞን ፖሊስ መምሪያ አባል ነኝ ገንዘብ ረስቼ ወጥቼ ነው በማለት የምትፈልገውን ከሱቅ ትወስዳለች። ​እምነት ለማትረፍ ስትል የራሷን ፎቶ እና ሽጉጥ ታጥቃ የተነሳችውን ምስል በማሳየት እቃዎችንና አልባሳትን በግድ ትወስድ እንደነበር ፖሊስ አስታውቋል። ​በሌላ በኩል፣ ሌሊትን በመጠቀም ከሌሎች ተባባሪዎቿ ጋር በመሆን ሰዎችን በጦር መሳሪያ በማስፈራራት ስትዘርፍ እንደነበር ምርመራው አረጋግጧል። ​ከህብረተሰቡ በደረሰ ጥቆማ መሰረት ፖሊስ ክትትል በማድረግ ተጠርጣሪዋን ተከራይታ በምትኖርበት ቤት ውስጥ ከ​አንድ የቱርክ ሽጉጥ፣ ​አንድ የወገብ ካርታ፣​ሁለት የክላሽንኮቭ ጥይት ካርታ፣ ​አንድ ጎራዴ፣ ​ከተለያዩ የፖሊስ የደንብ ልብሶች እና ሶስት የፖሊስ ዱላዎች ጋር በቁጥጥር ስር ውላ ምርመራ እየተጣራባት እንደሚገኝና ለህግ እንደምትቀርብ የፊቼ ከተማ ፖሊስ አስታውቋል። #ችሎት

አያንቱ ጎበና ከመቱ ዩኒቨርስቲ በሜዲካል ላብራቶሪ በ3.87 በከፍተኛ ነጥብ 4 ሜዳልያ ተሸላሚ ሆናለች 1. ከህክምና ኮሌጅ በከፍተኛ ውጤት የወርቅ ሜዳልያ 2. በሴቶች ከዩኒቨርስቲው በከፍተኛ ውጤት
አያንቱ ጎበና ከመቱ ዩኒቨርስቲ በሜዲካል ላብራቶሪ በ3.87 በከፍተኛ ነጥብ 4 ሜዳልያ ተሸላሚ ሆናለች 1. ከህክምና ኮሌጅ በከፍተኛ ውጤት የወርቅ ሜዳልያ 2. በሴቶች ከዩኒቨርስቲው በከፍተኛ ውጤት የወርቅ ሜዳልያ 3. ከሜዲካል ላብራቶሪ ዲፓርትመንት በከፍተኛ ውጤት የወርቅ ሜዳልያ 4. ከመቱ ዩኒቨርሲቲ በከፍተኛ ማዕረግ በከፍተኛ ውጤት የብር ሜዳልያ

“ኸርት አታክ ኢትዮጵያ’ ከ200 በላይ ለሚሆኑ የልብ ሕሙማን ነጻ ሕክምና ሊሰጥ ነው! #Fastmereja I «ኸርት አታክ ኢትዮጵያ» (Heart Attack Ethiopia) የተሰኘው የበጎ አድራጎት ድርጅት፣ 5ኛው ዙር ዘመቻው ከ200 በላይ ለሚሆኑ ዜጎች ውስብስብና ነጻ የልብ ሕክምና አገልግሎት ለመስጠት ዝግጅቱን ማጠናቀቁን በዛሬዉ እለት በሰጡት መግለጫ አስታዉቋል። ለዚህ በጎ ተግባር ከ55 በላይ ዓለም አቀፍ የልብ ህክምና ስፔሻሊስቶችን የያዘውና በዶክተር ተስፋዬ ተሊላ የሚመራው የህክምና ቡድን የፊታችን ቅዳሜ አዲስ አበባ እንደሚገቡ ተገልጿል። የዘንድሮው 5ኛ ዙር ዘመቻ ከተመሠረተ ጀምሮ ትልቁ ሲሆን፣ ሕክምናው በጥቁር አንበሳ፣በቅዱስ ጳውሎስ ፣ በካርዲያክ ሴንተር እና ዘንድሮ አዲስ በተጨመረው በኮሪያ ሆስፒታል በአጠቃላይ በ4 ማዕከላት ውስጥ እንደሚደረግ ተገልጿል። ይህን ህክምና የሚሰጡ ባለሙያዎች ከካናዳ፣ ሕንድ፣ አሜሪካ፣ ሩዋንዳ እና ቦትስዋናን ጨምሮ ከ6 አገራት የተውጣጡ ከ55 በላይ የበጎ ፈቃደኛ የልብ ሐኪሞች፣ ሰርጅኖችና ነርሶች ወደ ኢትዮጵያ መጥተው ህክምናዉን እንደሚሰጡ ነዉ የተገለፀዉ። ድርጅቱ ህክምናውን በነጻ የሚሰጥ ሲሆን፣ ህሙማንን የመለየቱ ስራ እና የወረፋ ሂደት ግን በአገር ውስጥ ሆስፒታሎች አሰራር አማካኝነት በውስጥ የሚለይ መሆኑን አስረድተዋል። የዘመቻው ዓላማ ጊዜያዊ ሕክምና መስጠት ብቻ ሳይሆን በሀገር ውስጥ ዘላቂ አቅም መገንባት ሲሆን ለዚህም ስድስት የሀገር ውስጥ ባለሙያዎች ለከፍተኛ ስልጠና ወደ ሕንድ የሚላኩ ሲሆን፣ በሐምሌ 11 በሚካሄደው የጋላ ዲነር መርሐ-ግብር ላይ የሕክምና ማዕከል ግንባታ ዕቅድ (Hub-and-Spoke Plan) ይፋ እንደሚደረግ ነዉ የተገለፀዉ። ድርጅቱ ለጤና ሚኒስቴር፣ የሕክምና ቁሳቁሶችን በነጻ ላጓጓዘው የኢትዮጵያ አየር መንገድና ለባለሙያዎች ምስጋና ያቀረበ ሲሆን፣ ይህንን ሰብአዊ ሥራ ለማገዝ እያንዳንዱ አካል ድጋፍ እንዲያደርግ ጥሪ አቅርቧል። በዶክተር ኦብስኔት መርዕድ እና በዶክተር ተስፋዬ ተሊላ የተመሠረተው ተቋም ላለፉት ሁለት ዓመታት ከስድስት ወራት በላይ በነጻ ሕክምና ሲሰጥ የቆየ ሲሆን፣ ባለፉት አራት ዙሮች ብቻ ከ6 ሚሊዮን ዶላር በላይ የሚያወጣ ወጪ በመሸፈን የ461 ሰዎችን ሕይወት መታደግ ችሏል። #ጤና

"የላካችሁላትን መልዕክት አድርሻለሁ፣ በደስታ እንባና በሳቅ ደጋግማ “ወይኔ ታድዬ፣ ሰዉ ይሄን ያህል ነዉ የሚወደኝ” እያለች እጅግ በጣም ሁላችሁንም አመስግናለች! ጎንበስ ብላ የኔ ማሮች የኔ ዉዶች
"የላካችሁላትን መልዕክት አድርሻለሁ፣ በደስታ እንባና በሳቅ ደጋግማ “ወይኔ ታድዬ፣ ሰዉ ይሄን ያህል ነዉ የሚወደኝ” እያለች እጅግ በጣም ሁላችሁንም አመስግናለች! ጎንበስ ብላ የኔ ማሮች የኔ ዉዶች እግዚአብሔር ይባርክልኝ በይልኝ ብላኛለች።" ድምጻዊት እጅጋየሁ ሽባባው (ጂጂ) መልዕክት በእህቷ ሶፊያ በኩል የተላለፈ

🏢 የሰመር ሪል እስቴት ልዩ የቤት ባለቤት የመሆን እድል! በከተማችን እምብርት ቡልጋሪያ አደባባይ አካባቢ የሚገኙትን እጅግ ዘመናዊ፣ ሰፊ እና ምቹ የመኖሪያ አፓርታማዎችን በፈለጉት የካሬ አማራጭ ለ
🏢 የሰመር ሪል እስቴት ልዩ የቤት ባለቤት የመሆን እድል! በከተማችን እምብርት ቡልጋሪያ አደባባይ አካባቢ የሚገኙትን እጅግ ዘመናዊ፣ ሰፊ እና ምቹ የመኖሪያ አፓርታማዎችን በፈለጉት የካሬ አማራጭ ለሽያጭ አቅርበናል። 📐 የምርጫዎትን የካሬ እና የመኝታ አማራጮች ይምረጡ፦ 🛏️ ባለ 1 መኝታ – 81 ካሬ 🛏️ ባለ 2 መኝታ – 111 እና 134 ካሬ 🛏️ ባለ 3 መኝታ – ከ168 ካሬ ጀምሮ 💰 እጅግ አስገራሚ ዋጋ እና ልዩ የክፍያ አማራጭ፦ 💵 ዋጋ፦ በካሬ 89,000 ብር ብቻ! 📉 ቅድመ ክፍያ፦ 10% ብቻ በመክፈል ውል ያሰሩ! 🏦 የባንክ ብድር፦ 50% የባንክ ብድር የተመቻቸለት። ⏳ ጊዜ አይውሰዱ! ይህ ታላቅ የዋጋ ቅናሽ የሚቆየው ለውስን ጊዜ ብቻ ስለሆነ፣ ቀድመው በመምጣት የዕድሉ ተጠቃሚ ይሁኑ። 📍 ቦታ፦ ቡልጋሪያ አደባባይ አካባቢ 📞 ለበለጠ መረጃ አሁኑኑ ይደውሉልን፦0912355631 የህልምዎን ቤት ዛሬውኑ በእጅዎ ያስገቡ! #Summer #AddisAbabaBusiness #apartmentforrentplantation #shopforsale #apartmentforrent #amibaraproperties #realestate #የንግድቦታ #Temerrealestate #teklehaymanotmall

ታሪክ ሰሪው የኛንጋቶም ተወላጅ የመጀመሪያው የህክምና ዶክተር ​#FastMereja I ከኛንጋቶም ወረዳ የመጡት ዶክተር ሶያ ኩሩፓ፣ ከጅማ ዩኒቨርሲቲ በህክምና ሙያ በመመረቅ የህዝባቸው የመጀመሪያው የህክምና ዶክተር በመሆን ታሪክ ሰርተዋል። ዶክተር ሶያ፣ ለሰባት ዓመታት የዘለቀው አስቸጋሪ የትምህርት ጉዞ፣ ለወደፊት ለሚመጡት የገጠር ወጣቶች ተስፋ የሚሰጥ መሆኑን ገልጸዋል። ​ዶክተር ሶያ ኩሩፓ፣ የተወለዱትና ያደጉት በኛንጋቶም ወረዳ በሚገኝ ራቅ ያለ አርብቶ አደር ማህበረሰብ ውስጥ ነው። በዚያ አካባቢ የትምህርትና የጤና አገልግሎት አቅርቦት እጅግ ውስን በሆነበት ሁኔታ ውስጥ ማደግ፣ የህክምና ዶክተር የመሆንን ህልም የሩቅ ተስፋ አድርጎት እንደነበር ያስታውሳሉ። ​ይሁን እንጂ በቤተሰብ፣ በማህበረሰብ እና በአማካሪዎች ድጋፍ፣ እንዲሁም በራሳቸው የጽናት ብርታት ሰባት ዓመታትን በጅማ ዩኒቨርሲቲ በማሳለፍ የህክምና ትምህርታቸውን አጠናቀዋል። ይህ ስኬት የግል ድል ብቻ ሳይሆን፣ የቤተሰባቸው፣ የኛንጋቶም ህዝብ እና ለመላው የገጠር ማህበረሰብ የሚተርፍ የትምህርት ተምሳሌት መሆኑን ተናግረዋል። ​ዶክተሩ አክለውም፣ ይህ ስኬት ሌሎች ወጣቶች ከኋላ የመጡበት ሁኔታ የአቅማቸውን ጣሪያ መወሰን እንደሌለበት ማሳያ ነው ብለዋል። በሙያ ዘመናቸውም በተለይ ለጤና አገልግሎት ተደራሽነት ለሚቸገሩ አካባቢዎች ቅድሚያ በመስጠት እንደሚያገለግሉ ያላቸውን ቁርጠኝነት አረጋግጠዋል።

የዱባይ ፖሊስ በኢትዮጵያውያን ላይ የመጨረሻ ጥብቅ ማስጠንቀቂያ ሰጠ ​#FastMereja I በተባበሩት አረብ ኤምሬቶች የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በዲጂታል መድረኮች በሚያደርጓቸው እንቅስቃሴዎች ላይ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ የዱባይ ፖሊስ እና የኢትዮጵያ ቆንስላ ጽህፈት ቤት ጥብቅ ማስጠንቀቂያ አስተላልፈዋል። ይህ ማስጠንቀቂያ የተሰጠው በትውልድ ኢትዮጵያውያን መካከል በማህበራዊ ሚዲያ ላይ እየተደረጉ ያሉ አንዳንድ ህገ-ወጥ ድርጊቶችን ለመከላከል ነው። ​የዱባይ ፖሊስ እና የኢትዮጵያ ቆንስላ ጽህፈት ቤት በጋራ ባዘጋጁት መድረክ እንደተገለጸው፣ በአረብ ኤምሬቶች የሳይበር ወንጀል ህግ መሰረት የሚከተሉት ድርጊቶች ከፍተኛ ቅጣት እንደሚያስከትሉ ተገልጿል፦ 📌 ​የጥላቻ ንግግር: በማህበረሰቡ መካከል መከፋፈልን፣ ጥላቻን እና ንቀትን የሚያንጸባርቁ የብሄር ፖለቲካ ቅስቀሳዎችን ሶሻል ሚዲያ ላይ መለጠፍ። 📌 ​ስድብ እና ስም ማጥፋት: ግለሰቦችን ወይም ተቋማትን በቪዲዮ፣ በጽሁፍ ወይም በኮሜንት መዝለፍ እና ስም ማጥፋት ህግ የተከለከለ ነው። 📌 ​ያለ ፈቃድ መረጃ ማውጣት: የግለሰቦችን ግላዊነት የሚነኩ ምስሎችን፣ ቪዲዮዎችን ወይም መረጃዎችን ያለ ፈቃድ ማሰራጨት በህግ የሚያስቀጣ ነው። 📌 ​የገንዘብ ማሰባሰብ: ያለ መንግስት ፈቃድ በማህበራዊ ሚዲያ በኩል በስምምነት ገንዘብ ማሰባሰብ በኢምሬትስ ህግ የተከለከለ ነው።

ባይናንስ የኢትዮጵያ ብር በፕላትፎርሙ ላይ እንደማይገኝ አረጋገጠ ​#FastMereja | ዓለም አቀፉ የክሪፕቶ ከረንሲ መገበያያ ድረ-ገጽ ባይናንስ (Binance) በኢትዮጵያ አገልግሎት ስለመጀመሩ በተሰራጨው መረጃ ላይ ማስተካከያ ሰጥቷል። ኩባንያው የኢትዮጵያ ብር በድረ-ገጹ ላይ እንደማይገኝ በግልጽ አስታውቋል። ​ከዚህ ቀደም የባይናንስ ፕላትፎርም በኢትዮቴሌኮም በኩል በኢትዮጵያ ተደራሽ እንደሆነ ተገልጾ የነበረ ቢሆንም፣ ባይናንስ ለብርሜትሪክስ በላከው መግለጫ የኢትዮጵያ ብር (ETB) በፕላትፎርሙ ላይ እንደማይገኝ አረጋግጧል። ኩባንያው ይህ ውሳኔ የሀገሪቱን የቁጥጥር መመሪያዎች መሰረት ያደረገ መሆኑን ገልጿል። ​ባይናንስ አክሎም በኢትዮጵያ የሚሰጡ መመሪያዎችን እና ህጎችን ለማክበር ቁርጠኛ እንደሆነና ለተጠቃሚዎች ድጋፍ ማድረጉን እንደሚቀጥል ገልጿል። ይሁን እንጂ የፕላትፎርሙ አጠቃላይ ተደራሽነት በኢትዮቴሌኮም በኩል ስለመመለሱ ወይም አለመመለሱ የሰጠው ግልጽ ማብራሪያ የለም። ​በኢትዮጵያ የብሔራዊ ባንክ መመሪያ መሰረት የኢትዮጵያ ብር ብቸኛው ህጋዊ የመገበያያ ገንዘብ ነው። ባንኩ ከዚህ ቀደም በተደጋጋሚ እንዳስጠነቀቀው፣ ያለፈቃድ የሚፈጸሙ የቨርቹዋል ንብረት ግብይቶች ህጋዊ እውቅና የላቸውም።

የሻርክ እና የወይዘሮ ሸዋዬ ታሪክ እና ከሞት በላይ የሆነ ታማኝነት በአንድ አረንጓዴማ በሆነች የገጠር ከተማ በስሟ ኩየራ በምትባል መንደር ውስጥ ሻርክ የሚባል እና ወይዘሮ ሸዋዬ የሚባሉ እናት አብረው ይኖሩ ነበር። ሻርክ ተራ ውሻ አልነበረም፤ እርጋታው፣ አስተዋይነቱ እና ለአሳዳጊው የነበረው ፍቅር በመንደሩ ሰው ሁሉ ዘንድ የሚደነቅ እና የሚወደድ ነበር። የእሱ አለም... የእሱ መጠለያ እና መላ ህይወቱ ወይዘሮ ሸዋዬ ነበሩ። ወይዘሮ ሸዋዬ ሻርክን ከትንሽነቱ ጀምረው ነበር ያሳደጉት። በርግጥ ትንሽ ከፍ ብሏል። ጎረቤታችው በፓስፖርት ከውጭ አምጥተውት በሳምንቱ ከዛ ጠፍቶ ሸዋዬ ጋር ገባ። ቢሞክሩት ወስደው ቢያስሩት እሱ ምግብ አልበላም እያለ ገመድ እየበጠሰ መኖርያውን ከሸዋዬ ጋር አደረገ። እሷ ልጆቿ በስራ ምክንያት ውጭ ስለሚውሉ ሻርክ ደግሞ ብቸኝነቷን የሻረላት የልብ ጓደኛዋ ሆነ። . ዓመታት እያለፉ ሲሄዱ በሁለቱ መካከል ያለው ትስስር እየጠነከረ መጣ። ወይዘሮ ሸዋዬ ማለዳ ተነስተው ወደ ማሳቸው ሲሄዱ ሻርክ ከፊት ቀደም እያለ መንገዱን ይመራ ነበር። እርሻ ውስጥ ስራቸውን ሲሰሩ እሱ ከዛፍ ጥላ ስር ሆኖ አካባቢውን በትኩረት ይጠብቃል። ማታ ወደ ቤት ሲመለሱም የእርሷን ድካም የሚያውቅ ይመስል እግሯ ስር ተኝቶ እጆቿን በምላሱ ይልስ ነበር። ውጣ ሲባል እንኳ ከሳሎን አይወጣም እያያቸው ነበር የሚውለው። መንደርተኞቹ ሁልጊዜ፣ "የሸዋዬ ውሻ እኮ ከሰው በላይ ያስባል" ይሉ ነበር። ሻርክ ወይዘሮ ሸዋዬ ደስ ሲላቸው አብሮ ይቦርቃል፣ ሲከፋቸው ወይም ሲደክማቸው ደግሞ ዝም ብሎ አጠገባቸው በመቀመጥ አጋርነቱን ያሳይ ነበር። ወይዘሮ ሸዋዬ ህይወታቸው ከማለፉ በፊት ባሉት የመጨረሻ ወራት በጠና ታመው አልጋ ላይ ውለው ነበር። በእነዚያ አስቸጋሪ ቀናት ሻርክ ከቤት አልወጣም። ለህክምና ሆስፒታል ሲሄዱም ተከትሎ ይሄዳል። የምግብ ፍላጎቱ ሙሉ በሙሉ ጠፍቶም ነበር። ስትመለስም ከአልጋዋ ስር አይነሳም ነበር ፣ እሷ በምትሰቃይበት ጊዜ ሁሉ እሱም በሀዘን ያለቅስ ነበር። ወይዘሮ ሸዋዬ የመጨረሻዋን ትንፋሽ ከመውሰዷ በፊት፣ እየተንቀጠቀጠች ያለችውን እጇን ዘርግታ የሻርክን ጭንቅላት ዳሰሰችው። አይኖቿ የእንባ ጠብታ አውርደው ለዘላለም ሲከደኑ፣ ሻርክ ረዥም እና የሚያሳዝን የጩኸት ድምፅ አሰማ ወዳጁ መሄዷን ነፍሱ አውቃው ነበር። የቀብር ሥነ ሥርዓቱ ተፈጽሞ መንደርተኛው ሁሉ ወደየቤቱ ሲበተን ሻርክ ግን አብሮ አልተመለሰም። ሻርክ የመቃብር ስፍራ ላይ ልክ በህይወት እያለች እግሯ ስር እንደሚቀመጠው ሁሉ ዛሬም አንገቱን ደፍቶ ተቀምጧል። የመንደሩ ሰዎች ሊወስዱት፣ ምግብ ሊሰጡትና ሊያጽናኑት ሞክረውም ነበር። እሱ ግን ትንሽ ይበላና ትንሽ ቆይቶ ወደ መቃብሩ ይመለሳል ከዛም ቆይቶ ወደቤት። ዝናብ ሲዘንብ፣ ፀሐይ ሲያቃጥል ሻርክ ከቦታው አይንቀሳቀስም። እሱ አሁንም እየጠበቃት ነው። ሻርክ በዚህ ድርጊቱ ለሰው ልጆች ትልቅ ትምህርት አስተላልፏል... ፍቅር፣ ታማኝነት እና ትስስር በሞት እንኳ የማይበጠሱ መሆናቸውን። እሱ የአሳዳጊውን አካል አጥቶ ሊሆን ይችላል፣ ነገር ግን በእሱ ልብ ውስጥ የእሷ ትውስታ እና ፍቅር እስከ መጨረሻው እስትንፋሱ ድረስ ህያው ሆኖ ይኖራል። በኤፍሬም ታምሩ

photo content

4.5 ሚሊዮን ብር ወጪ የሆነበት “ሳላያት” ፊልም ተመረቀ ​#FastMereja | የሮማንቲክ ኮሜዲ ዘውግ ያለው “ሳላያት” የተሰኘ አዲስ ፊልም ሰኔ 22 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ አዲሱ ህፃናትና ወጣቶች ቲያትር ቤት ተመረቀ፣ ከሰኔ 25፣ 2018 ዓ.ም ጀምሮ በመላው ሀገሪቱ በሚገኙ ሲኒማ ቤቶች እንደሚታይ የፊልሙ ፕሮዲዩሰር ገልጸዋል። ​የፊልሙ ፕሮዲዩሰር እንደገለጹት፣ ፊልሙን ለመስራት እስከ ስምንት ወር የሚጠጋ ጊዜ የፈጀ ሲሆን፣ ለፊልም ስራው ከ4.5 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ መደረጉ ተገልጿል፣ ፊልሙ የሮማንቲክ ኮሜዲ ዘውግ ያለው እና የህብረተሰቡን የእለተ እለት ህይወት የሚዳስስ ነው ብለዋል። በእውነት መልቲሚዲያ ተዘጋጅቶ በሞሪያድ ኢንተርቴመንት የቀረበው ሳላያት ፊልም አለምሰገድ ተስፋዬ፣ ናታይ ጌታቸው፣ መኮንን ለአከ፣ አስቴር አለማየሁ፣ ክላራ ሙሉጌታ፣ ሊና ካሳ እና ሌሎች ተዋናዮች የተጣመሩበት ነው።

የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለሥልጣን ያከናወናቸውን አዳዲስ የጥራት መቆጣጠሪያና የላብራቶሪ ሥራዎች አስተዋወቀ! #Fastmereja:-የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለሥልጣን (EFDA) ወደ ሀገር ውስጥ የሚገቡና በሀገር ውስጥ የሚመረቱ የሕክምና ግብዓቶችን ጥራት በላቀ ደረጃ ለመቆጣጠር የሚያስችሉ የላብራቶሪ ምርመራ ሥራዎቹን አስተዋወቀ። ጥራቱን ያልጠበቀ እና ሀሰተኛ መድኃኒት ወደ ሕብረተሰቡ እንዳይደርስ የሚያደርገውን የቁጥጥር ሥርዓት ይበልጥ ግልጽ ለማድረግ አጠቃላይ ዕድሳት የተደረገለትና ዓለም አቀፍ ዕውቅና ያገኘው የመድኃኒት ጥራት መቆጣጠሪያ ላብራቶሪ በይፋ ሥራ መጀመሩ ተገልጿል። የባለሥልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ሄራን ገርባ እንደገለጹት፣ ተቋሙ ባከናወናቸው ሰፊ ሥራዎች ዉጤታማ መሆናቸዉን ገልፀዉ የቁጥጥር ሥርዓቷን የዓለም ጤና ድርጅት (WHO) ML Maturity Level 3 (ML3) ደረጃ ላይ ማድረስ ተችሏል ሲሉ ተናግረዋል። ይህ የ-ML3 ደረጃ ተቋሙ የተረጋጋና በሚገባ የሚሠራ የቁጥጥር ሥርዓት እንዳለው ማረጋገጫ ሲሆን፣ በመላው ዓለም 70 የሚጠጉ፣ በአፍሪካ ደግሞ ኢትዮጵያን ጨምሮ 9 አገራት ብቻ ናቸው ይህንን ማሟላት የቻሉት። ይህም አገሪቱ በዘርፉ የአፍሪካ የልህቀት ማዕከል ለመሆን ለጀመረችው ጉዞ ትልቅ እምርታ መሆኑ ተገልጿል። ይህ የ-WHO Maturity Level 3 (ML3) የብቃት ደረጃ ተቋሙ አስተማማኝ፣ በሚገባ የተደራጀና ውጤታማ የቁጥጥር ስርአት (Stable and well-functioning regulatory system) እንዳለው የሚያረጋግጥ መሆኑ ነዉ የተገለፀዉ። ይህ ጠንካራ አሠራር የሕዝብን ጤና ከመጠበቅ ባለፈ የአገር ውስጥ ምርትን በማበረታታት ለውጭ ንግድና ለኢንቨስትመንት በር የሚከፍት ከፍተኛ ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ እንዳለዉ ተነግሯል። እንዲሁም የተቀነባበሩ ምግቦች፣ መድኃኒቶች፣ የሕክምና መሣሪያዎች፣ የውበት መጠበቂያዎች እና የትንባሆ ምርቶች ላይ ጥብቅ ቁጥጥር ማድረግ የባለሥልጣኑ ቀዳሚ ኃላፊነት መሆኑ ተገልፆ በአሁኑ ወቅት ምርቶች ወደ ገበያ ከመግባታቸው በፊት ጥብቅ ፍተሻ እንዲሁም ክትትል እየተከናወነ እንደሚገኝ ተገልጿል። እንዲሁም ህብረተሰቡ”የእኔ ጤና፣ በእኔ እጅ” የሚለውን መርህ በመከተል ራሱን ጥራታቸውን ካልጠበቁና አስመስለው ከተሠሩ (Falsified) የሕክምና ምርቶች እንዲጠብቅ አሳስቧል። #ጤና

በደቡብ አፍሪካ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ከፍተኛ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ ብፁዕ አባ ሄኖክ አባታዊ ጥሪ አቀረቡ #FastMereja I በደቡብ አፍሪካ በተለያዩ ከተሞች በስደት ላይ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን በተቀሰቀሱ ወቅታዊ ውጥረቶችና በሀገሪቱ ዜጎች በሚደረጉ የተቃውሞ ሰልፎች ምክንያት ከፍተኛ ሥጋት ውስጥ መውደቃቸውን ተከትሎ፣ የደቡብ አፍሪካና ምዕራብ አፍሪካ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አባ ሄኖክ አስቸኳይ የአባታዊ ጥንቃቄና የጽናት መልዕክት አስተላለፉ። በደቡብ አፍሪካ በተፈጠሩ ወቅታዊ ውጥረቶች እና ከሀገር እንድትወጡ በሚሉ ሰልፎች ምክንያት ወገኖቻችን በከፍተኛ ሥነ-ልቦናዊ ጫና ውስጥ እንዳሉ እንረዳለን ያሉት ሊቀ ጳጳሱ፣ ተፈታኝ በሆነው ማዕበል ውስጥ የማይናወጥ መጠጊያ በሆነው በእግዚአብሔር ቃል እንዲጸኑና ልባቸው በፍርሃት እንዳይናወጥ ጥሪ አቅርበዋል። ወቅቱ ወንድም ወንድሙን ለሞት አሳልፎ የሚሰጥበት የፈተና ጊዜ መሆኑን በማስታወስ፣ ምዕመናን በመንፈሳዊ ጥንካሬና በጸሎት ወደ ፈጣሪ እንዲጠጉ አሳስበዋል። ብፁዕ አባ ሄኖክ በስደት ላይ የሚገኙ ወገኖች አሁን ላይ ቀዳሚ ተግባራቸው ሊሆን የሚገቡ አራት ዋና ዋና የጥንቃቄ እርምጃዎችን እንደሚከተለው አደራ ብለዋል፦ ውጥረቶችና ሰልፎች በሚበራከቱባቸው አካባቢዎችና የንግድ ማዕከላት ያለ በቂ ምክንያት ከመንቀሳቀስ መቆጠብና በተለይም በምሽት ሰዓት እንቅስቃሴን ሙሉ በሙሉ ማስቀረት። የአካባቢውን ወቅታዊ የጸጥታ ሁኔታ፣ ከኤምባሲም ሆነ ከማኅበረሰብ መሪዎች የሚወጡ ይፋዊ መግለጫዎችንና የደኅንነት ማስጠንቀቂያዎችን በንቃት መከታተል። ከሌሎች ወገኖችና ከቅርብ ጓደኞች ጋር ያለውን የመረጃ ልውውጥ ማጠናከርና ድንገተኛ አደጋ ቢከሰት እንኳ በፍጥነት የሚደርስ የሰንሰለት መረጃዎችን መዘርጋት። በማኅበራዊ ሚዲያዎችም ሆነ በአካል ከሚደረጉ አላስፈላጊ ክርክሮችና ግጭትን ሊቀሰቅሱ ከሚችሉ አነቃቂ ሁኔታዎች ራስን ማራቅና በትዕግሥት መጠበቅ። ሊቀ ጳጳሱ በደቡብ አፍሪካና በምዕራብ አፍሪካ ለሚገኙ ኢትዮጵያውያን በሙሉ ያስተላለፉትን መልዕክት ሲያጠቃልሉ፣ እግዚአብሔር መከራውን አሻግሮ የፀጥታና የማረፍ ጊዜ እንዲሰጥ በመጸለይ ኢትዮጵያን፣ ደቡብ አፍሪካንና ምዕራብ አፍሪካን ባርከዋል።

በሸዋሮቢት ከተማ በደረሰ ከባድ የእሳት አደጋ በመኖሪያ ቤቶችና ንብረት ላይ ጉዳት ደረሰ! #FastMereja I ከሌሊቱ 9፡00 ገደማ፣ በሸዋሮቢት ከተማ አስተዳደር 02 ቀበሌ መግቢያ መንገድ አካባቢ ባጋጠመ ድንገተኛ የእሳት አደጋ በመኖሪያ ቤቶች እና በንብረት ላይ ከፍተኛ ውድመት ደርሷል። ምንም እንኳን የእሳት አደጋው በንብረት ላይ የከፋ ጉዳት ቢያስከትልም፤ በሰው ህይወትና አካል ላይ ያደረሰው ምንም አይነት ጉዳት አለመኖሩ ተረጋግጧል። ለጊዜው የዚህ አሳዛኝ የእሳት አደጋ መነሻ መንስኤ ያልታወቀ ሲሆን፤ የከተማው ፖሊስ በአደጋው ዙሪያ ጥብቅ ማጣራት እያካሄደ ይገኛል። ፖሊስ የምርመራውን ውጤት እንዳጠናቀቀ ትክክለኛውን መረጃ ለህዝብ ይፋ እንደሚያደርግ አስታውቋል።

የንግድዎን ህልም ዛሬ ያሳኩ! በመሀል ከተማ ቡልጋሪያ አካባቢ የሚገኙ ዘመናዊ ሱቆች ለሽያጭ። ✅ ከ25 ካሬ ሜትር ጀምሮ ✅ በከፍተኛ የንግድ እንቅስቃሴ ቦታ ✅ ከ750,000 ብር ቅድመ ክፍያ ጀምሮ
የንግድዎን ህልም ዛሬ ያሳኩ! በመሀል ከተማ ቡልጋሪያ አካባቢ የሚገኙ ዘመናዊ ሱቆች ለሽያጭ። ✅ ከ25 ካሬ ሜትር ጀምሮ ✅ በከፍተኛ የንግድ እንቅስቃሴ ቦታ ✅ ከ750,000 ብር ቅድመ ክፍያ ጀምሮ ✅ ለንግድ ስራዎ ተስማሚ እና ተፈላጊ አካባቢ የነገውን ትርፍ ዛሬ በመወሰን ይጀምሩ! 📞 ለበለጠ መረጃ  :-0912355631

ቤተሳይዳ ሜዲካል ፕላዛ በኢትዮጵያ የመጀመሪያውን ዓለም አቀፍ የጄሲአይ (JCI) የጥራት ዕውቅና አገኘ #FastMereja I ቤተሳይዳ አሜሪካን ሜዲካል ፕላዛ በጤና አገልግሎት ጥራትና በታካሚዎች ደህንነት ዙሪያ ባሳየው የላቀ ብቃት፣ የጆይንት ኮሚሽን ኢንተርናሽናል (JCI) የወርቅ ደረጃ ዕውቅናን በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ ማግኘቱን አስታወቀ። በየዓመቱ ከ10 ሺህ በላይ ዜጎች ወደ ውጭ አገር ለሕክምና በመጓዛቸው ሳቢያ የምታጣውን ከ700 ሚሊዮን ዶላር በላይ የውጭ ምንዛሬ ለማስቀረት ታስቦ የተቋቋመው ይህ ሜዲካል ፕላዛ፣ አንደኛ ዓመት ክብረ በዓሉን እና የዕውቅና ማብሰሪያ መርሐግብሩን የጤና ሚኒስትሯ ዶ/ር መቅደስ ዳባ በተገኙበት አክብሯል። የጤና ሚኒስትሯ ዶ/ር መቅደስ ዳባ በሥነ ሥርዓቱ ላይ እንደገለጹት፣ በአሁኑ ወቅት በጤናው ዘርፍ የአገልግሎት ጥራት፣ ፍትሐዊነትና ተደራሽነትን ለማረጋገጥ በርካታ የሪፎርም ሥራዎች እየተሠሩ ይገኛሉ። መንግሥት እንደ ቤተሳይዳ ያሉ አገልግሎትን የሚያዘምኑ፣ አቅም ያላቸውንና ደረጃቸውን የጠበቁ የግል የጤና ተቋማት የሚያደርጉትን የማስፋፊያ ሥራዎች በቅርበት የመደገፍና የማገዝ ቃል ኪዳን እንዳለውም ሚኒስትሯ አረጋግጠዋል። ተቋሙ ይህንን ታዋቂ የዓለም አቀፍ ምስክር ወረቀት ለማግኘት የታካሚዎች መብትና ደህንነትን፣ ጥራቱን የጠበቀ የመድኃኒት አስተዳደርን እንዲሁም አስተማማኝ የኢንፌክሽን ቁጥጥርን ጨምሮ ከ1 ሺህ 300 በላይ ጠንከር ያሉ መስፈርቶችን ማለፉ በዕለቱ ተገልጿል። ይህ የጥራት ዕውቅና ደረጃውን ጠብቆ ለማስቀጠል ሲባል በየሦስት ዓመቱ በሚደረግ ጥብቅ ድጋሚ ምርመራ የሚታደስ ይሆናል። የቤተሳይዳ አሜሪካን ፕላዛ ሥራ አስፈጻሚ ዶ/ር አየለ ተሾመ በበኩላቸው፣ ዕውቅናው ኢትዮጵያን በዓለም አቀፍ የጤና አጠባበቅ ልቀት ካርታ ላይ የሚያስቀምጣት መሆኑን ገልጸው፣ አገራችን በዓለም ላይ እጅግ የተከበሩ መመዘኛዎችን የሚያሟሉ ተቋማትን መገንባትና ማንቀሳቀስ እንደምትችል ማረጋገጫ ነው ብለዋል። ከአንድ ዓመት በፊት ተመርቆ ወደ ሥራ የገባው ይህ ሜዲካል ፕላዛ፣ በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ (AI) የታገዙና በድምፅ መታዘዝ የሚችሉ ዘመናዊ የሕክምና መሣሪያዎችን በሥራ ላይ ያዋለ ሲሆን፣ ይህም ያለ ኦፕሬሽን የልብ፣ የአንጎልና የደም ሥር ችግሮችን ለመፍታት እንደሚያስችል ተጠቁሟል። ተቋሙ በአሁኑ ወቅት አገልግሎቱን ይበልጥ ለማስፋፋት ዘመናዊ የካንሰር ሕክምና እና የሰው ሠራሽ ማፅነስ (IVF) ማዕከላትን በማቋቋም ላይ እንደሚገኝ ተነግሯል።