አለ ሕግ
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት Alternative legal enlightenment & Service Website: alehig.com https://linktr.ee/alehig WhatsApp👉 #+251920666595 Telegram👉 @MikiasMelak የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ #የሕግ_መረጃ
نمایش بیشتر📈 تحلیل کانال تلگرام አለ ሕግ
کانال አለ ሕግ (@alehig) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 16 208 مشترک است و جایگاه 487 را در دسته قانونی و رتبه 2 121 را در منطقه أثيوبيا دارد.
📊 شاخصهای مخاطب و پویایی
از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 16 208 مشترک جذب کرده است.
بر اساس آخرین دادهها در تاریخ 17 سپتامبر, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 172 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر 7 بوده و همچنان دسترسی گستردهای حفظ شده است.
- وضعیت تأیید: تأیید نشده
- نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 22.63% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 7.26% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب میکند.
- دسترسی پستها: هر پست به طور میانگین 3 667 بازدید دریافت میکند. در اولین روز معمولاً 1 177 بازدید جمعآوری میشود.
- واکنشها و تعامل: مخاطبان بهطور فعال حمایت میکنند؛ میانگین واکنش به هر پست 9 است.
📝 توضیح و سیاست محتوایی
نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاههای شخصی توصیف میکند:
“ከጠበቃና የሕግ አማካሪ
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website: alehig.com
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ #የሕግ_መረጃ”
به لطف بهروزرسانیهای پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 18 سپتامبر, 2026)، کانال همواره بهروز و دارای دسترسی بالاست. تحلیلها نشان میدهد مخاطبان بهطور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته قانونی تبدیل کردهاند.
در حال بارگیری داده...
| تاریخ | رشد مشترکین | اشارات | کانالها | |
| 18 سپتامبر | +5 | |||
| 17 سپتامبر | +7 | |||
| 16 سپتامبر | 0 | |||
| 15 سپتامبر | +2 | |||
| 14 سپتامبر | +2 | |||
| 13 سپتامبر | 0 | |||
| 12 سپتامبر | +5 | |||
| 11 سپتامبر | 0 | |||
| 10 سپتامبر | +2 | |||
| 09 سپتامبر | +11 | |||
| 08 سپتامبر | +2 | |||
| 07 سپتامبر | +2 | |||
| 06 سپتامبر | +8 | |||
| 05 سپتامبر | +3 | |||
| 04 سپتامبر | +15 | |||
| 03 سپتامبر | +17 | |||
| 02 سپتامبر | +11 | |||
| 01 سپتامبر | +15 |
| 2 | መልካም አዲስ ዓመት! 🙏
እንኳን ለ2019 ዓ.ም የኢትዮጵያ ዘመን መለወጫ በዓል በሰላም አደረሰን አደረሳችሁ።
ይህ አዲስ ዓመት ያለፉትን ተግዳሮቶች አስወግደን አዳዲስ ስኬቶችን የምናሳካበት የሰላምና የዕድገት ዓመት ይሁንልን። በየትኛውም የዓለም ማዕዘን እንኑር ህብረታችንና ፍቅራችን የጸና ይሁን!
መልካም ምኞት ከጠበቃ እና ህግ አማካሪ Mikias Melak AleHig #ሚኪያስ #መላክ
#አለሕግ አለ ሕግ #AleHig #ከሜዲትራኒያን #ባህር 🌊🙏 | 2 073 |
| 3 | የታክስ አለመግባባትን በመስማማት ስለመፍታት
ነሐሴ 27/2018 ዓ.ም (የምስራቅ አ/አ/አነ/ግ/ከ/ቅ/ጽ/ቤት )
በተሻሻለው የፌዴራል ታክስ አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 1434/2018 አንቀጽ 61 የታክሱ ባለስልጣን የታክስ አለመግባባትን በመስማማት ለመፍታት ያለውን ስልጣን በተመለከተ የሚከተለውን ይላል፡-
👉 የታክሱ ባልስልጣን የታክስ አለመግባባቶችን በመስማማት የመፍታት ስልጣን ተሰጥቶታል።
👉 ማናቸውም በስምምነት የሚፈታ የታክስ ያለመግባባት በጽሁፍ የሚደረግ እና የተስማሚ ወገኖች ፊርማ ያረፈበት ሊሆን ይገባል።
👉 የታክስ አለመግባባቶችን በመስማማት የመፍታት ስልጣን የሰጠው ድንጋጌ ቢኖርም የሚከተሉት ሁኔታዎች ሲኖሩ ጉዳዩ በማስማማት ሊታይ አይችልም፦
1. የታክስ ማጭበርበር ወይም ሆን ተብሎ የተደረገ ታክስን የመሰወር ድርጊት መኖሩ ወይም ሌላ ከታክስ ጋር የተገናኘ ወንጀል መኖሩ ሲጠረጠር፤
2. በማስማማት የሚደረግ ስምምነት ከኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሕገ-መንግሥት እና ከሚመለከታቸው የታክስ ሕጎች ጋር የሚጋጭ ሲሆን፤
3. ከሁለቱ ወገኖች አንዱ በሽምግልና ሂደት ውስጥ ለመሳተፍ ፈቃደኛ ካልሆነ።
👉 ሚኒስቴሩ የአስማሚውን የትምህርት እና ሙያ ደረጃን ጨምሮ የመስማማት ሂደት የሚመራበትን ሥርዓት የሚወስን ዝርዝር የአፈፃፀም መመሪያ ያወጣል፡፡
ምንጭ ፣ገቢዎች ሚኒስቴር | 4 606 |
| 4 | በመኪና ሽያጭ ላይ የሚፈፀሙ የታክስ ስወራዎችንና ህገ-ወጥ የንግድ እንቅስቃሴዎችን ለመግታት ጠንካራ የህግ ማስከበር እርምጃ ሊወሰድ ነው።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የገቢዎች ቢሮ ባወጣው እንዳሳወቀው፤ በከተማዋ አንዳንድ የመኪና አስመጪዎችና የኮሚሽን ስራ ፈቃድ የሌላቸው ግለሰቦች በመቀናጀት ከፍተኛ የታክስ ስወራ ወንጀል እየፈፀሙ ይገኛሉ።
ህገ-ወጥ አሰራሩ በተለይም የመኪና አስመጪዎች የሚያስገቧቸውን ተሽከርካሪዎች መደበኛ የንግድ ፈቃድና አድራሻ ለሌላቸው ደላሎች አሳልፈው በመስጠት፣ ህጋዊ ደረሰኝ ሳይቆርጡ ዋጋን ቀንሰው በመሸጥ ግብር እንዳይከፈል የሚያደርጉበት እንደሆነ ተጠቅሷል።
ይህ ድርጊት በፌደራል የገቢ ግብር አዋጅ እና በተጨማሪ እሴት ታክስ አዋጅ መሰረት በወንጀል የሚያስጠይቅ በመሆኑ፣ ቢሮው ከሚመለከታቸው የህግ አካላት ጋር በመቀናጀት ቁጥጥሩን እንደሚያጠናክር ገልጿል።
ቢሮው የኮሚሽን ንግድ ፈቃድ ያላቸውም ሆኑ የመኪና አስመጪዎች ከእንደዚህ አይነት ህገ-ወጥ አሰራር እንዲወጡ ያስጠነቀቀ ሲሆን፤ ማንኛውም የመኪና ሽያጭ በህጋዊ የንግድ ቦታ፣ በደረሰኝ እና መደበኛ ታክስ ተከፍሎበት ብቻ መከናወን እንዳለበት አሳስቧል።
ሀና ሰይፉ
ነሐሴ 28/2018 ዓ.ም | 3 139 |
| 5 | ኢትዮጵያ በአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ያሳየችው የንግድ እንቅስቃሴ አበረታች ውጤት ማስመዝገቡ ተገለጸ
ኢትዮጵያ በአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ያሳየችው የንግድ እንቅስቃሴ አበረታች ውጤት ማስመዝገቡ ተገለጸ ኢትዮጵያ ስምምነቱን በቀዳሚነት ከፈረሙና ካጸደቁ ሀገራት መካከል አንዷ ስትሆን፤ እ.ኤ.አ ጥቅምት 9 ቀን 2025 በይፋ ንግድ መጀመሯ ይታወሳል።
የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር በማህበራዊ ትስስር ገጹ እንዳጋራው መረጃ ንግዱ በይፋ ከተጀመረበት ጊዜ አንስቶ እስከ ማዝያ ወር 2018 ዓ.ም ድረስ ባለው አጭር ጊዜ ውስጥ ብቻ ኢትዮጵያ ከሌሎች አባል ሀገራት ጋር ባደረገችው የንግድ ልውውጥ፦ከ14 ሚሊዮን ዶላር በላይ የሚያወጡ ምርቶችን ወደ ውጭ የላከች ሲሆን፤ ከ8 ሚሊዮን ዶላር በላይ የሚገመቱ ምርቶችን ደግሞ ወደ አገር ውስጥ አስገብታለች።
Read More
Source: Ethio FM 107.8
@Ethiopianbusinessdaily | 4 185 |
| 6 | የጠቅላላ ጉባኤ ስብሰባ ጥሪን ይመለከታል
ለኢትዮጵያ የሕግ ባለሙያዎች ማኅበር አባላት፡
ቀደም ሲል በተላለፈው ጥሪ መሰረት የኢትዮጵያ የሕግ ባለሙያዎች ማኅበር የ2018 በጀት ዓመት መደበኛ የጠቅላላ ጉባኤ ስብሰባ ቅዳሜ ነሀሴ 30 ቀን 2018 ዓ.ም አዲስ አበባ ሜክሲኮ ሰንጋተራ አካባቢ በሚገኘው የኅብረት ባንክ ዋና ህንጻ (ህብረት ታወር) አዳራሽ ከጠዋቱ 2:30 ጀምሮ እንደሚካሄድ እየገለጽን ለዝግጅት እንዲመቸን በጉባኤው የምትገኙ መሆኑን በኢሜል አድራሻችን 2014barassociation@gmail.com ስልካችሁን በመጻፍ እንድትመዘገቡ በማክበር እንጠይቃለን፡፡
የአባልነት ክፍያ ያላጠናቀቃችሁአባላት በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሂሳብ ቁጥር 1000540887091 ገቢ በማድረግ የከፈላችሁበትን ደረሰኝ በኢሜል መላክ ትችላላችሁ።
የጉባኤው ረቂቅ አጀንዳዎች፡
1. የ2018 በጀት ዓመት የማኅበሩን የስራ ክንውንና የውጭ ኦዲተር ሪፖርት መርምሮ ማጽደቅ፤
2. የማኅበሩን የ2019 በጀት ዓመት እቅድ ተወያይቶ መወሰን፤
3. ለማኅበሩ በጎ ፈቃደኛ ባለውለታዎች የእውቅና አሰጣጥ ስነ-ስርዓት ማካሄድና ሌሎችም ናቸው።
ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር 011-553-01-22 በመደወል መጠየቅ ይቻላል።
ኅብረት ባንክ ለማኅበራችን ለሚያደርገው የተለመደ ትብብር ከፍተኛ ምስጋናችንን እናቀርባለን።
ከሰላምታ ጋር
የኢትዮጵያ የሕግ ባለሙያዎች ማኅበር (ELA) | 3 690 |
| 7 | የተሻሻለው አዋጅ ስለታክስ ማጭበርበር ምን ይላል?
ነሐሴ 20/2018 ዓ.ም (የገቢዎች ሚኒስቴር)
በተሻሻለው የፌዴራል ታክስ አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 1434/2018 መሰረት “የታክስ ማጭበርበር” ማለት ታክስን ለመሰወር ወይም ህጋዊ ያልሆነ የታክስ ጥቅም ለማግኘት ሲባል የሚከተሉትን ድርጊቶች መፈጸም ነው፤
👉 ሐሰተኛ የሂሳብ መዝገቦችን፣ ሰነዶችን፣ ደረሰኞችን ወይም ሌሎች ሰነዶችን ማቅረብ፣
👉 ገቢን፣ ግብይትን ወይም ታክስ የሚከፈልበትን እንቅስቃሴ መደበቅ፣
👉 ሐሰተኛ ደረሰኞችን ማዘጋጀት ወይም መጠቀም፣
👉 ሐሰተኛ የታክስ ማስታወቂያ ማቅረብ
👉 ሰነዶችን ማጥፋት፣ መቀየር፣ መደበቅ፣
👉 ከአንድ በላይ ወይም ትይዩ የሂሳብ መዛግብትን ወይም ሰነዶችን ማዘጋጀትና መያዝ፣ እንዲሁም ለታክስ ባለስልጣኑና ለሌሎች አካላት ማቅረብ፤
👉ሐሰተኛ የተቀናሽ ወጪዎችን፣ የግብር ወይም የታክስ ነፃ መብት፣ የተመላሽን ወይም የማካካሻ ጥያቄን ማቅረብ፤
👉 ሕጋዊ ባልሆነ መንገድ የታክስ ግዴታን ለመቀነስ ማናቸውንም ሌሎች ድርጊቶች መፈጸም ወይም ሕግ እንዲፈፅሙ የሚያስገድዳቸውን አለመፈጸም፡፡
በአዋጁ የተሻሻሉ የታክስ ስሌቶች እና የይርጋ ጊዜ ገደብን በተመለከተ ሲገልጽ የታክስ ባለስልጣኑ የማጭበርበር ድርጊት የተፈጸመ መሆኑን የሚያረጋግጥ ማስረጃ ያገኘ እንደሆነ የራስ ታክስ ስሌት ማስታወቂያውን ካቀረበበት ቀን ጀምሮ በሚቆጠር 10 (አስር) ዓመት ውስጥ ሊያሻሽል ይችላል ይላል፡፡
ይሁን እንጂ በአዋጁ ንዑስ አንቀጽ 5 ላይ የታክስ ማጭበርበር ድርጊት መፈጸሙ በማስረጃ የተረጋገጠ በሚሆንበት ጊዜ የታክሱ ባለስልጣን የ10 (አስር) ዓመቱን የይርጋ ጊዜ ገደብ ሳያልፍ በማናቸውም ጊዜ የታክስ ውሳኔ ማሻሻያን ሊያደርግ እንደሚችል ይገልጻል፡፡ | 4 607 |
| 8 | እሁድ ነሐሴ 17 ቀን 2018 ዓ.ም በዲስ ዘመን ጋዜጣ የወጣ ክፍት የስራ ማስታወቂያ
የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በተዘረዘሩት ክፍት ስራ መደቦች ላይ በቋሚ ቅጥር ሰራተኞችን አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል፡፡
የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን ይከታተሉ
👉ዌብ ሳይት ↠ https://www.fsc.gov.et/
👉ፌስቡክ ↠ https://web.facebook.com/FSCEthiopia
👉ትዊተር (ኤክስ) ↠ https://x.com/federalsupreme1
👉ሊንክድኢን ↠ https://tinyurl.com/supereme-court-of-ethiopia
👉ቴሌግራም ↠ https://t.me/fscethiopiaPR
👉ዋትስአፕ ↠ https://tinyurl.com/fscethiopia
👉ዩቲዩብ ↠ https://www.youtube.com/@fscethiopia
👉ቲክቶክ ↠ https://tiktok.com/@federal.supreme.court | 4 379 |
| 9 | ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለ1ሺህ501ኛው የነብዩ መሐመድ ልደት (መውሊድ) በዓል አደረሳችሁ።
በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የፍርድ አፈፃፀም ጽ/ቤት
መልካም የመውሊድ በዓል እንዲሆንላች ይመኛል። | 3 891 |
| 10 | በአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ለተለያዩ የአይ.ሲ.ቲ የስራ መደቦች አመልክታችሁ ለፈተና ለተጠራችሁ በሙሉ
ባሕር ዳር፣ ነሐሴ 16/2018 (የአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት)
የአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በተለያዩ የአይ.ሲ.ቲ የስራ መደቦች በ 27/04/2018 ዓ.ም ላወጣው የስራ ቅጥር አመልክታችሁ ወደ ቀጣይ የፈተና ሂደት ያለፋችሁ ተወዳዳሪዎቻችን በሚከተሉት የፈተና ማዕከላት በመገኘት ፈተናውን እንድትወስዱ እናሳውቃለን።
ፈተናው በ 18/12/2018 ዓ.ም ከላይ በተዘረዘሩት የፈተና ማእከላት ከጥዋቱ 2:30 ጀምሮ ይሰጣል።
ተፈታኞቻችን ወደፈተና ማዕከላት ከመምጣታቸው በፊት ከላይ በደብዳቤው የተጠቀሱትን የፈተና አሰጣጥ ሥርዓቶች እንዲተገብሩ እናሳስባለን። | 1 |
| 11 | በኢትዮጵያ ዲጂታል መታወቂያ (ፋይዳ) ላይ በስሕተት የተመዘገበ መረጃ ካለ ተቋሙ አጣርቶ በራሱ የማስተካከል ሥልጣን አለው::
ስለሆነም ፍርድ ቤቶች “በፋይዳ መታወቂያ ላይ የተፈጠረ ስሕተት ይታረምልኝ” የሚሉ አቤቱታዎችን በቀጥታ ተቀብለው የማየት ሥልጣን የላቸውም::
ፍ/ቤቶች የዚህ ዓይነት አቤቱታዎችን መቀበል የሚችሉት ተቋሙን አስተዳደራዊ መፍትሔ ጠይቀው ካልተሰጣቸው ወይም የተሰጣቸው መፍትሔ ላይ ቅሬታ ካላቸው ብቻ ነው:: "
-የኢትዮጵያ ብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም (ነሐሴ 1 ቀን 2018 ዓ.ም) ለፍ/ቤቶች የጻፈው ደብዳቤ
#hailu hasena | 7 737 |
| 12 | የውጭ ሀገር ዜጎች በኢትዮጵያ የመኖሪያ ቤት ባለቤት የሚሆኑበትን አሰራር የሚወስን አዲስ መመሪያ ወጣ
• በመመሪያው ድንጋጌ መሰረት የውጭ ሃገር ዜጎች በመንግስት ቀጥተኛ ድጎማ የተገነቡ የጋራ መኖሪያ ቤቶች (ኮንዶሚኒየም) ባለቤት መሆን አይችሉም።
የከተማና መሰረተ-ልማት ሚኒስቴር የውጭ ሀገር ዜጎች በኢትዮጵያ የመኖሪያ ቤት ባለቤት የሚሆኑበትን ዝርዝር ሁኔታ የሚወስን "መመሪያ ቁጥር 1147/2018" አውጥቷል።
መመሪያው የወጣው የውጭ ሀገር ዜጎች የመኖሪያ ቤት ባለቤት የሚሆኑበትን አግባብ ለመደንገግ የወጣውን አዋጅ ቁጥር 1388/2017 በጥቅሉ የተቀመጡ ጉዳዮችን በመለየት፣ የመኖሪያ ቤት ባለቤት ለመሆን የሚፈልጉ የውጭ ሀገር ዜጎች ማሟላት የሚገባቸውን ቅድመ ሁኔታዎች፣ ገደቦች እና ክልከላዎች በዝርዝር ለመደንገግ ነው።
የውጭ አገር ዜጋ ማለት ትውልደ ኢትዮጵያዊ የሆነ የውጭ ዜጋን ሳይጨምር ኢትዮጵያዊ ዜግነት የሌለው ወይም የሌላ አገር ዜግነት ያለው ማንኛውም ሰው ማለት መሆኑን የመመሪያው ትርጓሜ ያስረዳል።
በመመሪያው መሰረት፣ ማንኛውም የውጭ ሀገር ዜጋ የመኖሪያ ቤት ባለቤት ለመሆን የሚያስችል ፈቃድ ከሚኒስቴሩ ለማግኘት የሚከተሉትን መስፈርቶች ማሟላት አለበት፡-
• የጸና ፓስፖርት እና የጉዞ ሰነድ ማቅረብ፤
• የጸና የመግቢያ ቪዛ ወይም በኢትዮጵያ ውስጥ የሚኖር ከሆነ የጸና ቋሚ የመኖሪያ ፈቃድ፤
• ከሚኖርበት ሀገር የሚሰጥ ከወንጀል ነፃ መሆኑን የሚያረጋግጥ ማስረጃ፤
• ለቤት ግዥ የሚውል ዝቅተኛ የገንዘብ መጠን በባንክ ገቢ ማድረጉን የሚያሳይ ማስረጃ፤
• የውጭ ባለሀብት ከሆነ ደግሞ በኢንቨስትመንት ውስጥ ቢያንስ 150,000 የአሜሪካ ዶላር ድርሻ ያለው መሆኑን የሚገልጽ የኢንቨስትመንት ፈቃድ እና የጽሁፍ ማረጋገጫ ማቅረብ ይኖርበታል።
መመሪያው እንደ አካባቢው ለቤት ባለቤትነት የሚያስፈልገውና የውጭ ሃገር ዜጋው ማቅረብ የሚጠበቅበት ዝቅተኛ የገንዘብ መጠን በዝርዝር አስቀምጧል።
• በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተማ አስተዳደሮች የመኖሪያ ቤት ባለቤት ለመሆን ቢያንስ 150,000 የአሜሪካ ዶላር
• በኦሮሚያ(ሸገርን ሳይጨምር) ፣ አማራ፣ ትግራይ፣ ሲዳማ፣ ማዕከላዊ ኢትዮጵያ፣ ደቡብ ኢትዮጵያ፣ ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ፣ ሶማሌ፣ ሐረሪ ክልሎች እና ድሬዳዋ አስተዳደር 120,000 የአሜሪካ ዶላር፤
• በአፋር፣ ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ወይም ጋምቤላ ክልሎች ደግሞ ቢያንስ 100,000 የአሜሪካ ዶላር ማቅረብ ይኖርበታል።
በተጨማሪም ማንኛውም የውጭ ሀገር ዜጋ በኢትዮጵያ ውስጥ ሊኖረው የሚችለው ከፍተኛ የቤት ብዛት አንድ ብቻ እንደሆነ ተደንግጓል።
ማንኛውም የውጭ ሀገር ዜጋ ለመኖሪያ ቤት የሚሆን የውጭ ምንዛሬ በመረጠው ባንክ ገቢ ለማድረግ በመጀመሪያ ከሚኒስቴሩ የፈቃድ ደብዳቤ ማግኘት የሚኖርበት ሲሆን ባንኩም የቀረበለትን ምንዛሬ በዕለቱ ተመን ወደ ብር በመቀየር በዜጋው ስም በተከፈተ ዝግ የባንክ ሂሳብ ውስጥ ያስቀምጣል።
በዝግ ሂሳብ የተቀመጠው ገንዘብ የሚለቀቀው ግለሰቡ ቤት ሲገዛ ወይም በሊዝ ጨረታ መሬት ሲያገኝ ብቻ ይሆናል ይህም የሚከናወነው ሚኒስቴሩ ገንዘቡ እንዲለቀቅ የሚገልጽ የፈቃድ ደብዳቤ ለባንኩ ሲያቀርብ ባንኩ በአሰራሩ መሰረት ገንዘቡን እንዲለቀቅ ሲያደርግ ነው።
በሽብር ወንጀል፣ በሰው መነገድ፣ በአደገኛ ዕጽ ዝውውር፣ በገንዘብ ማጠብ፣ በከባድ ሙስና፣ በሳይበር ወንጀል እና በሌሎች ከባድ ወንጀሎች የተጠረጠረ ወይም ጥፋተኛ የተባለ ሰው የመኖሪያ ቤት ባለቤት መሆን አይችልም።
በተጨማሪም በመንግስት ቀጥተኛ ድጎማ የተገነቡ የጋራ መኖሪያ ቤቶች (ኮንዶሚኒየም)፤ ከትርፍ ውጭ ለሆነ ዓላማ በመንግስት ወይም ከህዝብ በተሰበሰበ ገንዘብ የተገነቡ ቤቶች፤ በመንግስት፣ በባለሀብት ወይም በመንግስታዊ ባልሆኑ ድርጅቶች ድጋፍ የተገነቡ ቤቶች፤ በህብረት ስራ ማህበራት የተገነቡ ቤቶች የውጭ ሀገር ዜጎች በባለቤትነት ሊይዟቸው አይችሉም።
ለባለቤትነት ፈቃድ ለማውጣት 50 የአሜሪካ ዶላር በዕለቱ ምንዛሬ መከፈል እንዳለበት መመሪያው ይደነግጋል።
የሚሰጠው ፈቃድ ለአንድ ዓመት ብቻ የሚያገለግል ሲሆን፣ ግለሰቡ በዚህ ጊዜ ውስጥ ቤት መግዛት ወይም መስራት ካልቻለና ከአቅም በላይ የሆነ ምክንያት ካጋጠመው ለተጨማሪ አንድ ዓመት ሊታደስለት ይችላል። ፈቃዱን ካልተጠቀመበት ግን ለሚኒስቴሩ መመለስ ይኖርበታል።
የመኖሪያ ቤቱን ላልተፈቀደ ወይም ለህገ-ወጥ ዓላማ የተጠቀመ የውጭ ሃገር ዜጋ ከ1,000 እስከ 3,000፣ ያለ ፈቃድ የመኖሪያ ቤት ባለቤት ሆኖ የተገኘ ከ2,000 እስከ 5,000 ዶላር እንዲሁም ህገ-ወጥ መሆኑን እያወቀ የረዳ ወይም የተባበረ ማንኛውም ሰው ከ30,000 እስከ 50,000 የኢትዮጵያ ብር መቀጮ እንደሚጣልበት መመሪያው ያመለክታል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
ነሐሴ 5 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia | 4 909 |
| 13 | بدون متن... | 5 699 |
| 14 | ከቴምብር ቀረጥ ነጻ የሆኑ
👉 በመንግሥት በጀት የሚተዳደሩ የመንግሥት መሥሪያ ቤቶች፤
👉 የአስመጪነት ፈቃድ ያላቸው ነጋዴዎች ለሽያጭ የሚያስመጡት ንብረት በአስመጪዎቹ ስም ሲመዘገብ፤
👉 መንግሥት ባጸደቃቸው ዓለም አቀፍ ስምምነቶች እና ኮንቬንሽኖች መሠረት ሰነዶች ነጻ ሊደረጉ ይችላሉ፤
👉 ተመሳሳይ መብት የተሰጠ መሆኑ ሲረጋገጥ ገንዘብ ሚኒስቴር ኢምባሲዎችን፣ ቆንስላዎችን እና ዲፕሎማቲክ ሚሲዮኖችን ከቴምብር ቀረጥ ነጻ ሊያደርጋቸው ይችላል፤
👉 የአክሲዮን ድርሻ የምስክር ወረቀት ሲመዘገብ፤
👉 ለኢንቨስትመንት በሚወሰድ ብድር የመያዣ ሰነድ፤
👉 አዲስ የካፒታል ዕቃ ፋይናንስ ንግድ ሥራ አክሲዮን ማህበር ለጥቃቅን፣ አነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞቹ በዱቤ ግዥ የሚያቀርባቸው የካፒታል ንብረቶች በስሙ ሲመዘገብ፤
👉 በኤክስፖርት ንግድ ሥራ ላይ የተሰማሩ ባለሀብቶች ለሥራ ማስከጃ ከሚወስዱት ብድር ጋር ተያይዞ የሚገኝ የመያዣ ሰነድ፤
👉 የኢትዮጵያ ሴቶች ፌዴሬሽን ሴቶች በገቢ ምንጭነት እንዲጠቀሙባቸው ከመንግሥት የተሰጡት ተሸከሪካሪዎች የባለቤትነት ስም ዝውውር ሰነድ፤
👉 የግብርና ምርት ማሳደጊያዎች አቅራቢ ድርጅት የማዳበሪያ አቅርቦት ለአርሶ አደር ለማደል ከሚወስደው ሜርቸንዳይዝድ ብደር ጋር በተገናኘ የመያዣ ሰነድ፤
👉 የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ለኢንተርፕራይዞች ለሊዝ ፋይናንስንግ ሥርዓት የሚያቀርባቸው ተሽከሪካሪዎች በባንኩ ንብረት ባለቤትነት ስም ማስመዝገቢያ፡፡
በታክስ ጉዳዮች ትምህርት ዳይሬክቶሬት የተዘጋጀ | 4 627 |
| 15 | Justices at the Federal Supreme Court have widened the protection they are holding over lawyers contesting a Ministry of Finance directive that requires them to register for value-added tax (VAT). Its Fourth Civil Appellate Bench upheld a temporary injunction for 190 lawyers. It extended similar protection to advocates in the Amhara, Sidama, South Ethiopia and Benishangul-Gumuz regional states, shielding them from enforcement while the directive's legality is decided. #Litigation #Supreme #Court #Lawyers #Ethiopia
Read more - https://shorturl.at/ARZcC | 4 859 |
| 16 | #እንድታውቁት
የሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ አገልግሎት የውክልና አገልግሎቱን በአምስት ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች ከወረቀት ነጻ በሆነ ሲስተም ተደራሽ ማድረግ መጀመሩን አሳውቋል።
ሜክሲኮ በሚገኘው ቅርንጫፍ አስር ልዩ እና መደበኛው ቅርንጫፍ ፣አያት አደባባይ ሎሚያድ ሱፐርማርኬት በሚገኘው ቅርንጫፍ አስራአንድ እንዲሁም ካዛንቺስ እናት ታወር ላይ በሚገኘው ቅርንጫፍ ስምንት እና ቦሌ በሚገኘው ቅርንጫፍ አስራሁለት ጽ/ቤቶች ነው አገልግሎቱን መስጠት የተጀመረው።
በቅርቡም በሁሉም ቅርጫፎች ተግባራዊ ለማድረግ እየሰራሁ እገኛለሁ ሲል የሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ አገልግሎት አስታውቋል።
ከተገልጋዮች ምን ይጠበቃል ?
⚫በ https://dars.gov.et:5102 ሊንክ በመጫን መግባት፤
⚫ ብሄራዊ መታወቂያን በመጠቀም አስፈላጊ ዶክመንቶችን መጫን
⚫ ወደተጠቀሱት ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች ማቅናት
⚫ የተጫነውን መረጃ መያዝ የሚያስፈልግ ሲሆን ዶክመንቱ ተመሳክሮ ትክክለኛነቱ ሲረጋገጥ የኤሌክትሮኒክ ፊርማ (signature pad) በመፈረም የውክልና ሰነዱ በኦንላየን ይላካል።
⚫ በሰነዱ መገልገል ሲፈልጉ የሰነዱን ትክክለኛነት በQR Code ማረጋገጥ ይችላሉ።
የሰነዶች ማረጋገጫ እና ምዝገባ አገልግሎት ከወረቀትአልባ አገልግሎት በተጨማሪ በቴሌሳይን መተግበሪያ አማካይነት የቤተሰብ የጠበቃ እና የአስተዳደር ውክልና አገልግሎት ወደተቋም መምጣት ሳይጠበቅባቸው ካሉበት ሆነው ማግኘት የሚያስችላቸው አሰራር መተግበሩን አስታውሷል።
@TikvahethMagazine | 5 115 |
| 17 | ⚜አዲሱ የጉምሩክ አዋጅ ማሻሻያ ቁጥር 1425/2018
⚜New _ Customs Amendment Proclamation No. 1425/2026
⚠This New Proclamation is Effective from 23rd July; 2026 | 6 020 |
| 18 | بدون متن... | 5 784 |
| 19 | የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሕግ ተማሪዎች አፍሪካን ወክለው ለዓለም አቀፍ የምስለ-ችሎት ፍጻሜ አለፉ።
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የህግ ተማሪዎች በአህጉራዊው የዓለም አቀፍ የኢንቨስትመንት ህግ እና የግልግል ዳኝነት (arbitration) የምስለ-ችሎት ውድድር (FDI Moot) የዞኑ አሸናፊ በመሆን አፍሪካን ወክለው ለዓለም አቀፉ ፍጻሜ ማለፋቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገለጹ።
ለመጀመሪያ ጊዜ በተሳተፉበት በዚህ ፈታኝ ውድድር ከናይጄሪያ፣ ከኬንያ እና ከሌሎች የአፍሪካ ሀገራት የተወጣጡ 14 ቡድኖችን በመበለጥ ከሰብ-ሳሃራን አፍሪካ አንደኛ በመውጣት ውድድሩን አጠናቀዋል።
በዚህ ውድድር ላይ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲን ወክለው የተሳተፉት ፦
➡ ባምላክስራ ፋሲል (የ3ኛ ዓመት የህግ ተማሪ)
➡ ቃልኪዳን ሰብስቤ (የ4ኛ ዓመት የህግ ተማሪ)
➡ ዲቦራ ታደሰ (የ4ኛ ዓመት የህግ ተማሪ) እና
➡ ናሆት ግርማ (የ5ኛ ዓመት የህግ ተማሪ) ናቸው።
ለዚህ አህጉራዊ ውጤት ያበቃቸው ዋና ምክንያት ምንድን ነው ?
" ለዚህ ውጤት ያበቃን ቀደም ሲል በቪስ ሙት (Vis Moot) የነበረን ልምድ ነው። ከቡድናችን አራት አባላት መካከል ሦስቱ በዓለም አቀፍ የግልግል ዳኝነት ውድድር ላይ ለአንድ አመት ተወዳድረዋል። ይህ ልምድ በጣም ጠቅሞናል።
አሁን ላይ የተወዳደርንበት ጉዳይ ከአለም አቀፍ የኢንቨስትመንት ህግ እና የግልግል ዳኝነት ጋር የተያያዙ ውስብስብ ጥያቄዎችን ያካተተ ነበር።
ከዋና ዋናዎቹ የስነ-ስርዓት ክርክሮች መካከል ከሳሹ ቀደም ሲል አቤቱታውን ለሌላ አካል አቅርቦ ስለነበር አሁን እንዳይከለከል የሚለው እና የክስ ማገጃ ትእዛዝ መሰጠት አለበት ወይ ? የሚሉት ይገኙበታል።
የፍሬ-ነገር ክርክሩ በበኩሉ ፍትሃዊ እና እኩል እንክብካቤ እንዲሁም ንብረት መውረስን የሚመለከቱ ጥያቄዎችን አካቷል።
በውድድሩ ወቅት የገጠመን ትልቁ ፈተና ከዳኞቹ ለሚቀርቡ ዝርዝር እና ያልተጠበቁ ጥያቄዎች ምላሽ መስጠት ነው " ብለዋል።
የተወዳዳሪዎቹ መሪ የሆኑትና የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የቀድሞው የህግ ተማሪ፣ የህግ ባለሙያ ቦርጋ ደለሳ፥ ተማሪዎቹ እስካሁን ያለምንም ድጋፍ ለዚህ ድል የበቁ ቢሆንም፣ በመጪው ኦክቶበር (October) ወር በቻይና በሚካሄደው የመጨረሻ ፍጻሜ ላይ ለመሳተፍ ከፍተኛ የገንዘብ እና የተቋማት ድጋፍ ይፈልጋሉ ብለዋል።
በተለይም ፦
- ለዓለም አቀፍ ጉዞ፣
- ለእንግዳ ማረፊያ፣
- ለቪዛ፣
- ከምዝገባ ጋር የተያያዙ ወጪዎች እና ለዝግጅት ድጋፍ የሚያስፈልግ በመሆኑ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ፣ የሚመለከታቸው የመንግሥት ተቋማት (በተለይም የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን) የሕግ እና የንግዱ ማኅበረሰብ፣ እንዲሁም ሌሎች ድርጅቶች ትብብር እንዲያደርጉላቸውና እውቅና እንዲሰጧቸው ጠይቀዋል።
ይህ እድል የነዚህ አራት ተማሪዎች ብቻ ሳይሆን አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲን፣ ኢትዮጵያን እና የአፍሪካን የሕግ ትምህርት በዓለም አቀፍ መድረክ ለማስተዋወቅና ለመወከል የሚሰጥ ትልቅ ዕድል መሆኑን ገልጸዋል።
ተወዳዳሪዎቹን ማግኘት የምትፈልጉ፣ የቡድኑ መሪ የሆኑትን የህግ ባለሙያ ቦርጋ ደለሳን በስልክ ቁጥር +251925494142 ማግኘት ትችላላችሁ።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
ነሐሴ 6 ቀን 2018 ዓ/ም | 5 484 |
| 20 | በኢትዮጵያ በውርስና ስጦታ ላይ አዲስ ታክስ ሊጣል ነው
በኢትዮጵያ በውርስና ስጦታ ላይ አዲስ ታክስ ሊጣል ነው በኢትዮጵያ በውርስ ወይም በስጦታ በሚገኙ ገቢዎች ላይ አዲስ የታክስ ዓይነት ሊጣል መሆኑ ተገለጸ።
ከአንድ ሚሊዮን ብር በላይ የሆኑ የውርስና የስጦታ ገቢዎች ለዚህ ታክስ እንደሚዳረጉ ተመልክቷል።
ዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም (IMF) የአምስተኛውን ዙር የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ሪፎርም ግምገማ ተከተሎ ይፋ ባደረገው ባለ 132 ገጽ ሙሉ ሪፖርት እንደጠቆመው፣ የአገሪቱ የታክስ መሠረት በጣም ጠባብ በመሆኑ መንግሥት በየዓመቱ የአገር ውስጥ ገቢውን ለማሳደግ አዳዲስ የታክስ ዓይነቶችን ለመተግበር አቅዷል።
በዚሁ ሪፖርት መሠረት በውርስና ስጦታ ከአንድ ሚሊዮን ብር በላይ በሚገኝ ገቢ ላይ ታክስ ይጣላል።
በሲጋራ፣ በአልኮልና በነዳጅ ምርቶች ላይ የሚጣለው ታክስ እንደሚጨምር የተገለጸ ሲሆን፣ ይህም አገራዊ ገቢን ከመጨመር ባለፈ ለጤና ፖሊሲዎች አተገባበር ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳለው ተመልክቷል።
Source: Ethio FM 107.8
@Ethiopianbusinessdaily | 5 033 |
