አለ ሕግ
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት Alternative legal enlightenment & Service Website: alehig.com https://linktr.ee/alehig WhatsApp👉 #+251920666595 Telegram👉 @MikiasMelak የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ #የሕግ_መረጃ
نمایش بیشتر📈 تحلیل کانال تلگرام አለ ሕግ
کانال አለ ሕግ (@alehig) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 16 096 مشترک است و جایگاه 489 را در دسته قانونی و رتبه 2 105 را در منطقه أثيوبيا دارد.
📊 شاخصهای مخاطب و پویایی
از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 16 096 مشترک جذب کرده است.
بر اساس آخرین دادهها در تاریخ 27 اوت, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 88 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر 9 بوده و همچنان دسترسی گستردهای حفظ شده است.
- وضعیت تأیید: تأیید نشده
- نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 26.81% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 10.50% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب میکند.
- دسترسی پستها: هر پست به طور میانگین 4 314 بازدید دریافت میکند. در اولین روز معمولاً 1 689 بازدید جمعآوری میشود.
- واکنشها و تعامل: مخاطبان بهطور فعال حمایت میکنند؛ میانگین واکنش به هر پست 15 است.
📝 توضیح و سیاست محتوایی
نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاههای شخصی توصیف میکند:
“ከጠበቃና የሕግ አማካሪ
አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት
Alternative legal enlightenment & Service
Website: alehig.com
https://linktr.ee/alehig
WhatsApp👉 #+251920666595
Telegram👉 @MikiasMelak
የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ #የሕግ_መረጃ”
به لطف بهروزرسانیهای پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 28 اوت, 2026)، کانال همواره بهروز و دارای دسترسی بالاست. تحلیلها نشان میدهد مخاطبان بهطور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته قانونی تبدیل کردهاند.
در حال بارگیری داده...
| تاریخ | رشد مشترکین | اشارات | کانالها | |
| 28 اوت | +7 | |||
| 27 اوت | +9 | |||
| 26 اوت | +6 | |||
| 25 اوت | 0 | |||
| 24 اوت | +6 | |||
| 23 اوت | +4 | |||
| 22 اوت | +4 | |||
| 21 اوت | +17 | |||
| 20 اوت | +11 | |||
| 19 اوت | +5 | |||
| 18 اوت | +5 | |||
| 17 اوت | +4 | |||
| 16 اوت | +7 | |||
| 15 اوت | +9 | |||
| 14 اوت | +18 | |||
| 13 اوت | +8 | |||
| 12 اوت | +3 | |||
| 11 اوت | +6 | |||
| 10 اوت | +4 | |||
| 09 اوت | +2 | |||
| 08 اوت | +2 | |||
| 07 اوت | +5 | |||
| 06 اوت | +1 | |||
| 05 اوت | 0 | |||
| 04 اوت | 0 | |||
| 03 اوت | 0 | |||
| 02 اوت | +1 | |||
| 01 اوت | +1 |
| 2 | እሁድ ነሐሴ 17 ቀን 2018 ዓ.ም በዲስ ዘመን ጋዜጣ የወጣ ክፍት የስራ ማስታወቂያ
የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በተዘረዘሩት ክፍት ስራ መደቦች ላይ በቋሚ ቅጥር ሰራተኞችን አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል፡፡
የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን ይከታተሉ
👉ዌብ ሳይት ↠ https://www.fsc.gov.et/
👉ፌስቡክ ↠ https://web.facebook.com/FSCEthiopia
👉ትዊተር (ኤክስ) ↠ https://x.com/federalsupreme1
👉ሊንክድኢን ↠ https://tinyurl.com/supereme-court-of-ethiopia
👉ቴሌግራም ↠ https://t.me/fscethiopiaPR
👉ዋትስአፕ ↠ https://tinyurl.com/fscethiopia
👉ዩቲዩብ ↠ https://www.youtube.com/@fscethiopia
👉ቲክቶክ ↠ https://tiktok.com/@federal.supreme.court | 1 762 |
| 3 | ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለ1ሺህ501ኛው የነብዩ መሐመድ ልደት (መውሊድ) በዓል አደረሳችሁ።
በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የፍርድ አፈፃፀም ጽ/ቤት
መልካም የመውሊድ በዓል እንዲሆንላች ይመኛል። | 2 248 |
| 4 | በአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ለተለያዩ የአይ.ሲ.ቲ የስራ መደቦች አመልክታችሁ ለፈተና ለተጠራችሁ በሙሉ
ባሕር ዳር፣ ነሐሴ 16/2018 (የአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት)
የአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በተለያዩ የአይ.ሲ.ቲ የስራ መደቦች በ 27/04/2018 ዓ.ም ላወጣው የስራ ቅጥር አመልክታችሁ ወደ ቀጣይ የፈተና ሂደት ያለፋችሁ ተወዳዳሪዎቻችን በሚከተሉት የፈተና ማዕከላት በመገኘት ፈተናውን እንድትወስዱ እናሳውቃለን።
ፈተናው በ 18/12/2018 ዓ.ም ከላይ በተዘረዘሩት የፈተና ማእከላት ከጥዋቱ 2:30 ጀምሮ ይሰጣል።
ተፈታኞቻችን ወደፈተና ማዕከላት ከመምጣታቸው በፊት ከላይ በደብዳቤው የተጠቀሱትን የፈተና አሰጣጥ ሥርዓቶች እንዲተገብሩ እናሳስባለን። | 1 |
| 5 | በኢትዮጵያ ዲጂታል መታወቂያ (ፋይዳ) ላይ በስሕተት የተመዘገበ መረጃ ካለ ተቋሙ አጣርቶ በራሱ የማስተካከል ሥልጣን አለው::
ስለሆነም ፍርድ ቤቶች “በፋይዳ መታወቂያ ላይ የተፈጠረ ስሕተት ይታረምልኝ” የሚሉ አቤቱታዎችን በቀጥታ ተቀብለው የማየት ሥልጣን የላቸውም::
ፍ/ቤቶች የዚህ ዓይነት አቤቱታዎችን መቀበል የሚችሉት ተቋሙን አስተዳደራዊ መፍትሔ ጠይቀው ካልተሰጣቸው ወይም የተሰጣቸው መፍትሔ ላይ ቅሬታ ካላቸው ብቻ ነው:: "
-የኢትዮጵያ ብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም (ነሐሴ 1 ቀን 2018 ዓ.ም) ለፍ/ቤቶች የጻፈው ደብዳቤ
#hailu hasena | 4 384 |
| 6 | የውጭ ሀገር ዜጎች በኢትዮጵያ የመኖሪያ ቤት ባለቤት የሚሆኑበትን አሰራር የሚወስን አዲስ መመሪያ ወጣ
• በመመሪያው ድንጋጌ መሰረት የውጭ ሃገር ዜጎች በመንግስት ቀጥተኛ ድጎማ የተገነቡ የጋራ መኖሪያ ቤቶች (ኮንዶሚኒየም) ባለቤት መሆን አይችሉም።
የከተማና መሰረተ-ልማት ሚኒስቴር የውጭ ሀገር ዜጎች በኢትዮጵያ የመኖሪያ ቤት ባለቤት የሚሆኑበትን ዝርዝር ሁኔታ የሚወስን "መመሪያ ቁጥር 1147/2018" አውጥቷል።
መመሪያው የወጣው የውጭ ሀገር ዜጎች የመኖሪያ ቤት ባለቤት የሚሆኑበትን አግባብ ለመደንገግ የወጣውን አዋጅ ቁጥር 1388/2017 በጥቅሉ የተቀመጡ ጉዳዮችን በመለየት፣ የመኖሪያ ቤት ባለቤት ለመሆን የሚፈልጉ የውጭ ሀገር ዜጎች ማሟላት የሚገባቸውን ቅድመ ሁኔታዎች፣ ገደቦች እና ክልከላዎች በዝርዝር ለመደንገግ ነው።
የውጭ አገር ዜጋ ማለት ትውልደ ኢትዮጵያዊ የሆነ የውጭ ዜጋን ሳይጨምር ኢትዮጵያዊ ዜግነት የሌለው ወይም የሌላ አገር ዜግነት ያለው ማንኛውም ሰው ማለት መሆኑን የመመሪያው ትርጓሜ ያስረዳል።
በመመሪያው መሰረት፣ ማንኛውም የውጭ ሀገር ዜጋ የመኖሪያ ቤት ባለቤት ለመሆን የሚያስችል ፈቃድ ከሚኒስቴሩ ለማግኘት የሚከተሉትን መስፈርቶች ማሟላት አለበት፡-
• የጸና ፓስፖርት እና የጉዞ ሰነድ ማቅረብ፤
• የጸና የመግቢያ ቪዛ ወይም በኢትዮጵያ ውስጥ የሚኖር ከሆነ የጸና ቋሚ የመኖሪያ ፈቃድ፤
• ከሚኖርበት ሀገር የሚሰጥ ከወንጀል ነፃ መሆኑን የሚያረጋግጥ ማስረጃ፤
• ለቤት ግዥ የሚውል ዝቅተኛ የገንዘብ መጠን በባንክ ገቢ ማድረጉን የሚያሳይ ማስረጃ፤
• የውጭ ባለሀብት ከሆነ ደግሞ በኢንቨስትመንት ውስጥ ቢያንስ 150,000 የአሜሪካ ዶላር ድርሻ ያለው መሆኑን የሚገልጽ የኢንቨስትመንት ፈቃድ እና የጽሁፍ ማረጋገጫ ማቅረብ ይኖርበታል።
መመሪያው እንደ አካባቢው ለቤት ባለቤትነት የሚያስፈልገውና የውጭ ሃገር ዜጋው ማቅረብ የሚጠበቅበት ዝቅተኛ የገንዘብ መጠን በዝርዝር አስቀምጧል።
• በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተማ አስተዳደሮች የመኖሪያ ቤት ባለቤት ለመሆን ቢያንስ 150,000 የአሜሪካ ዶላር
• በኦሮሚያ(ሸገርን ሳይጨምር) ፣ አማራ፣ ትግራይ፣ ሲዳማ፣ ማዕከላዊ ኢትዮጵያ፣ ደቡብ ኢትዮጵያ፣ ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ፣ ሶማሌ፣ ሐረሪ ክልሎች እና ድሬዳዋ አስተዳደር 120,000 የአሜሪካ ዶላር፤
• በአፋር፣ ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ወይም ጋምቤላ ክልሎች ደግሞ ቢያንስ 100,000 የአሜሪካ ዶላር ማቅረብ ይኖርበታል።
በተጨማሪም ማንኛውም የውጭ ሀገር ዜጋ በኢትዮጵያ ውስጥ ሊኖረው የሚችለው ከፍተኛ የቤት ብዛት አንድ ብቻ እንደሆነ ተደንግጓል።
ማንኛውም የውጭ ሀገር ዜጋ ለመኖሪያ ቤት የሚሆን የውጭ ምንዛሬ በመረጠው ባንክ ገቢ ለማድረግ በመጀመሪያ ከሚኒስቴሩ የፈቃድ ደብዳቤ ማግኘት የሚኖርበት ሲሆን ባንኩም የቀረበለትን ምንዛሬ በዕለቱ ተመን ወደ ብር በመቀየር በዜጋው ስም በተከፈተ ዝግ የባንክ ሂሳብ ውስጥ ያስቀምጣል።
በዝግ ሂሳብ የተቀመጠው ገንዘብ የሚለቀቀው ግለሰቡ ቤት ሲገዛ ወይም በሊዝ ጨረታ መሬት ሲያገኝ ብቻ ይሆናል ይህም የሚከናወነው ሚኒስቴሩ ገንዘቡ እንዲለቀቅ የሚገልጽ የፈቃድ ደብዳቤ ለባንኩ ሲያቀርብ ባንኩ በአሰራሩ መሰረት ገንዘቡን እንዲለቀቅ ሲያደርግ ነው።
በሽብር ወንጀል፣ በሰው መነገድ፣ በአደገኛ ዕጽ ዝውውር፣ በገንዘብ ማጠብ፣ በከባድ ሙስና፣ በሳይበር ወንጀል እና በሌሎች ከባድ ወንጀሎች የተጠረጠረ ወይም ጥፋተኛ የተባለ ሰው የመኖሪያ ቤት ባለቤት መሆን አይችልም።
በተጨማሪም በመንግስት ቀጥተኛ ድጎማ የተገነቡ የጋራ መኖሪያ ቤቶች (ኮንዶሚኒየም)፤ ከትርፍ ውጭ ለሆነ ዓላማ በመንግስት ወይም ከህዝብ በተሰበሰበ ገንዘብ የተገነቡ ቤቶች፤ በመንግስት፣ በባለሀብት ወይም በመንግስታዊ ባልሆኑ ድርጅቶች ድጋፍ የተገነቡ ቤቶች፤ በህብረት ስራ ማህበራት የተገነቡ ቤቶች የውጭ ሀገር ዜጎች በባለቤትነት ሊይዟቸው አይችሉም።
ለባለቤትነት ፈቃድ ለማውጣት 50 የአሜሪካ ዶላር በዕለቱ ምንዛሬ መከፈል እንዳለበት መመሪያው ይደነግጋል።
የሚሰጠው ፈቃድ ለአንድ ዓመት ብቻ የሚያገለግል ሲሆን፣ ግለሰቡ በዚህ ጊዜ ውስጥ ቤት መግዛት ወይም መስራት ካልቻለና ከአቅም በላይ የሆነ ምክንያት ካጋጠመው ለተጨማሪ አንድ ዓመት ሊታደስለት ይችላል። ፈቃዱን ካልተጠቀመበት ግን ለሚኒስቴሩ መመለስ ይኖርበታል።
የመኖሪያ ቤቱን ላልተፈቀደ ወይም ለህገ-ወጥ ዓላማ የተጠቀመ የውጭ ሃገር ዜጋ ከ1,000 እስከ 3,000፣ ያለ ፈቃድ የመኖሪያ ቤት ባለቤት ሆኖ የተገኘ ከ2,000 እስከ 5,000 ዶላር እንዲሁም ህገ-ወጥ መሆኑን እያወቀ የረዳ ወይም የተባበረ ማንኛውም ሰው ከ30,000 እስከ 50,000 የኢትዮጵያ ብር መቀጮ እንደሚጣልበት መመሪያው ያመለክታል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
ነሐሴ 5 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia | 3 492 |
| 7 | بدون متن... | 3 938 |
| 8 | ከቴምብር ቀረጥ ነጻ የሆኑ
👉 በመንግሥት በጀት የሚተዳደሩ የመንግሥት መሥሪያ ቤቶች፤
👉 የአስመጪነት ፈቃድ ያላቸው ነጋዴዎች ለሽያጭ የሚያስመጡት ንብረት በአስመጪዎቹ ስም ሲመዘገብ፤
👉 መንግሥት ባጸደቃቸው ዓለም አቀፍ ስምምነቶች እና ኮንቬንሽኖች መሠረት ሰነዶች ነጻ ሊደረጉ ይችላሉ፤
👉 ተመሳሳይ መብት የተሰጠ መሆኑ ሲረጋገጥ ገንዘብ ሚኒስቴር ኢምባሲዎችን፣ ቆንስላዎችን እና ዲፕሎማቲክ ሚሲዮኖችን ከቴምብር ቀረጥ ነጻ ሊያደርጋቸው ይችላል፤
👉 የአክሲዮን ድርሻ የምስክር ወረቀት ሲመዘገብ፤
👉 ለኢንቨስትመንት በሚወሰድ ብድር የመያዣ ሰነድ፤
👉 አዲስ የካፒታል ዕቃ ፋይናንስ ንግድ ሥራ አክሲዮን ማህበር ለጥቃቅን፣ አነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞቹ በዱቤ ግዥ የሚያቀርባቸው የካፒታል ንብረቶች በስሙ ሲመዘገብ፤
👉 በኤክስፖርት ንግድ ሥራ ላይ የተሰማሩ ባለሀብቶች ለሥራ ማስከጃ ከሚወስዱት ብድር ጋር ተያይዞ የሚገኝ የመያዣ ሰነድ፤
👉 የኢትዮጵያ ሴቶች ፌዴሬሽን ሴቶች በገቢ ምንጭነት እንዲጠቀሙባቸው ከመንግሥት የተሰጡት ተሸከሪካሪዎች የባለቤትነት ስም ዝውውር ሰነድ፤
👉 የግብርና ምርት ማሳደጊያዎች አቅራቢ ድርጅት የማዳበሪያ አቅርቦት ለአርሶ አደር ለማደል ከሚወስደው ሜርቸንዳይዝድ ብደር ጋር በተገናኘ የመያዣ ሰነድ፤
👉 የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ለኢንተርፕራይዞች ለሊዝ ፋይናንስንግ ሥርዓት የሚያቀርባቸው ተሽከሪካሪዎች በባንኩ ንብረት ባለቤትነት ስም ማስመዝገቢያ፡፡
በታክስ ጉዳዮች ትምህርት ዳይሬክቶሬት የተዘጋጀ | 3 262 |
| 9 | Justices at the Federal Supreme Court have widened the protection they are holding over lawyers contesting a Ministry of Finance directive that requires them to register for value-added tax (VAT). Its Fourth Civil Appellate Bench upheld a temporary injunction for 190 lawyers. It extended similar protection to advocates in the Amhara, Sidama, South Ethiopia and Benishangul-Gumuz regional states, shielding them from enforcement while the directive's legality is decided. #Litigation #Supreme #Court #Lawyers #Ethiopia
Read more - https://shorturl.at/ARZcC | 4 127 |
| 10 | #እንድታውቁት
የሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ አገልግሎት የውክልና አገልግሎቱን በአምስት ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች ከወረቀት ነጻ በሆነ ሲስተም ተደራሽ ማድረግ መጀመሩን አሳውቋል።
ሜክሲኮ በሚገኘው ቅርንጫፍ አስር ልዩ እና መደበኛው ቅርንጫፍ ፣አያት አደባባይ ሎሚያድ ሱፐርማርኬት በሚገኘው ቅርንጫፍ አስራአንድ እንዲሁም ካዛንቺስ እናት ታወር ላይ በሚገኘው ቅርንጫፍ ስምንት እና ቦሌ በሚገኘው ቅርንጫፍ አስራሁለት ጽ/ቤቶች ነው አገልግሎቱን መስጠት የተጀመረው።
በቅርቡም በሁሉም ቅርጫፎች ተግባራዊ ለማድረግ እየሰራሁ እገኛለሁ ሲል የሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ አገልግሎት አስታውቋል።
ከተገልጋዮች ምን ይጠበቃል ?
⚫በ https://dars.gov.et:5102 ሊንክ በመጫን መግባት፤
⚫ ብሄራዊ መታወቂያን በመጠቀም አስፈላጊ ዶክመንቶችን መጫን
⚫ ወደተጠቀሱት ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች ማቅናት
⚫ የተጫነውን መረጃ መያዝ የሚያስፈልግ ሲሆን ዶክመንቱ ተመሳክሮ ትክክለኛነቱ ሲረጋገጥ የኤሌክትሮኒክ ፊርማ (signature pad) በመፈረም የውክልና ሰነዱ በኦንላየን ይላካል።
⚫ በሰነዱ መገልገል ሲፈልጉ የሰነዱን ትክክለኛነት በQR Code ማረጋገጥ ይችላሉ።
የሰነዶች ማረጋገጫ እና ምዝገባ አገልግሎት ከወረቀትአልባ አገልግሎት በተጨማሪ በቴሌሳይን መተግበሪያ አማካይነት የቤተሰብ የጠበቃ እና የአስተዳደር ውክልና አገልግሎት ወደተቋም መምጣት ሳይጠበቅባቸው ካሉበት ሆነው ማግኘት የሚያስችላቸው አሰራር መተግበሩን አስታውሷል።
@TikvahethMagazine | 4 321 |
| 11 | ⚜አዲሱ የጉምሩክ አዋጅ ማሻሻያ ቁጥር 1425/2018
⚜New _ Customs Amendment Proclamation No. 1425/2026
⚠This New Proclamation is Effective from 23rd July; 2026 | 5 301 |
| 12 | بدون متن... | 5 176 |
| 13 | የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሕግ ተማሪዎች አፍሪካን ወክለው ለዓለም አቀፍ የምስለ-ችሎት ፍጻሜ አለፉ።
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የህግ ተማሪዎች በአህጉራዊው የዓለም አቀፍ የኢንቨስትመንት ህግ እና የግልግል ዳኝነት (arbitration) የምስለ-ችሎት ውድድር (FDI Moot) የዞኑ አሸናፊ በመሆን አፍሪካን ወክለው ለዓለም አቀፉ ፍጻሜ ማለፋቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገለጹ።
ለመጀመሪያ ጊዜ በተሳተፉበት በዚህ ፈታኝ ውድድር ከናይጄሪያ፣ ከኬንያ እና ከሌሎች የአፍሪካ ሀገራት የተወጣጡ 14 ቡድኖችን በመበለጥ ከሰብ-ሳሃራን አፍሪካ አንደኛ በመውጣት ውድድሩን አጠናቀዋል።
በዚህ ውድድር ላይ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲን ወክለው የተሳተፉት ፦
➡ ባምላክስራ ፋሲል (የ3ኛ ዓመት የህግ ተማሪ)
➡ ቃልኪዳን ሰብስቤ (የ4ኛ ዓመት የህግ ተማሪ)
➡ ዲቦራ ታደሰ (የ4ኛ ዓመት የህግ ተማሪ) እና
➡ ናሆት ግርማ (የ5ኛ ዓመት የህግ ተማሪ) ናቸው።
ለዚህ አህጉራዊ ውጤት ያበቃቸው ዋና ምክንያት ምንድን ነው ?
" ለዚህ ውጤት ያበቃን ቀደም ሲል በቪስ ሙት (Vis Moot) የነበረን ልምድ ነው። ከቡድናችን አራት አባላት መካከል ሦስቱ በዓለም አቀፍ የግልግል ዳኝነት ውድድር ላይ ለአንድ አመት ተወዳድረዋል። ይህ ልምድ በጣም ጠቅሞናል።
አሁን ላይ የተወዳደርንበት ጉዳይ ከአለም አቀፍ የኢንቨስትመንት ህግ እና የግልግል ዳኝነት ጋር የተያያዙ ውስብስብ ጥያቄዎችን ያካተተ ነበር።
ከዋና ዋናዎቹ የስነ-ስርዓት ክርክሮች መካከል ከሳሹ ቀደም ሲል አቤቱታውን ለሌላ አካል አቅርቦ ስለነበር አሁን እንዳይከለከል የሚለው እና የክስ ማገጃ ትእዛዝ መሰጠት አለበት ወይ ? የሚሉት ይገኙበታል።
የፍሬ-ነገር ክርክሩ በበኩሉ ፍትሃዊ እና እኩል እንክብካቤ እንዲሁም ንብረት መውረስን የሚመለከቱ ጥያቄዎችን አካቷል።
በውድድሩ ወቅት የገጠመን ትልቁ ፈተና ከዳኞቹ ለሚቀርቡ ዝርዝር እና ያልተጠበቁ ጥያቄዎች ምላሽ መስጠት ነው " ብለዋል።
የተወዳዳሪዎቹ መሪ የሆኑትና የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የቀድሞው የህግ ተማሪ፣ የህግ ባለሙያ ቦርጋ ደለሳ፥ ተማሪዎቹ እስካሁን ያለምንም ድጋፍ ለዚህ ድል የበቁ ቢሆንም፣ በመጪው ኦክቶበር (October) ወር በቻይና በሚካሄደው የመጨረሻ ፍጻሜ ላይ ለመሳተፍ ከፍተኛ የገንዘብ እና የተቋማት ድጋፍ ይፈልጋሉ ብለዋል።
በተለይም ፦
- ለዓለም አቀፍ ጉዞ፣
- ለእንግዳ ማረፊያ፣
- ለቪዛ፣
- ከምዝገባ ጋር የተያያዙ ወጪዎች እና ለዝግጅት ድጋፍ የሚያስፈልግ በመሆኑ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ፣ የሚመለከታቸው የመንግሥት ተቋማት (በተለይም የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን) የሕግ እና የንግዱ ማኅበረሰብ፣ እንዲሁም ሌሎች ድርጅቶች ትብብር እንዲያደርጉላቸውና እውቅና እንዲሰጧቸው ጠይቀዋል።
ይህ እድል የነዚህ አራት ተማሪዎች ብቻ ሳይሆን አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲን፣ ኢትዮጵያን እና የአፍሪካን የሕግ ትምህርት በዓለም አቀፍ መድረክ ለማስተዋወቅና ለመወከል የሚሰጥ ትልቅ ዕድል መሆኑን ገልጸዋል።
ተወዳዳሪዎቹን ማግኘት የምትፈልጉ፣ የቡድኑ መሪ የሆኑትን የህግ ባለሙያ ቦርጋ ደለሳን በስልክ ቁጥር +251925494142 ማግኘት ትችላላችሁ።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
ነሐሴ 6 ቀን 2018 ዓ/ም | 5 269 |
| 14 | በኢትዮጵያ በውርስና ስጦታ ላይ አዲስ ታክስ ሊጣል ነው
በኢትዮጵያ በውርስና ስጦታ ላይ አዲስ ታክስ ሊጣል ነው በኢትዮጵያ በውርስ ወይም በስጦታ በሚገኙ ገቢዎች ላይ አዲስ የታክስ ዓይነት ሊጣል መሆኑ ተገለጸ።
ከአንድ ሚሊዮን ብር በላይ የሆኑ የውርስና የስጦታ ገቢዎች ለዚህ ታክስ እንደሚዳረጉ ተመልክቷል።
ዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም (IMF) የአምስተኛውን ዙር የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ሪፎርም ግምገማ ተከተሎ ይፋ ባደረገው ባለ 132 ገጽ ሙሉ ሪፖርት እንደጠቆመው፣ የአገሪቱ የታክስ መሠረት በጣም ጠባብ በመሆኑ መንግሥት በየዓመቱ የአገር ውስጥ ገቢውን ለማሳደግ አዳዲስ የታክስ ዓይነቶችን ለመተግበር አቅዷል።
በዚሁ ሪፖርት መሠረት በውርስና ስጦታ ከአንድ ሚሊዮን ብር በላይ በሚገኝ ገቢ ላይ ታክስ ይጣላል።
በሲጋራ፣ በአልኮልና በነዳጅ ምርቶች ላይ የሚጣለው ታክስ እንደሚጨምር የተገለጸ ሲሆን፣ ይህም አገራዊ ገቢን ከመጨመር ባለፈ ለጤና ፖሊሲዎች አተገባበር ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳለው ተመልክቷል።
Source: Ethio FM 107.8
@Ethiopianbusinessdaily | 4 968 |
| 15 | بدون متن... | 4 570 |
| 16 | "በችኮላና በጥድፊያ" የሚዘጋጁ ህጎች፣ በህግ አወጣጥ ስርዓቱ ላይ አለመረጋጋት እየፈጠሩ መሆኑን በጥናት ተመላክቷል።
👉 አንዳንድ መመሪያና ደንቦች ከመውጣታቸው በፊት ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ቀርበው የማይገመገሙ መሆኑ ደግሞ ችግሩን አባብሶታል ተብሏል።
👉 ህጎች በወጡ በሳምንት እና በአመታቸው ማሻሻያ የተደረገባቸውም እንዳሉም ተገልጿል።
(ቲክቫህ ኢትዮጵያ)
በኢትዮጵያ የህግ አወጣጥ ሂደት ውስጥ ተደጋጋሚ ማሻሻያዎች፣ የአዋጅ መሻሮችና መጣረሶች እየታዩ መሆኑን፣ ይህንንም መረጋጋት ለማምጣት የሚያስችል ሁሉን አቀፍ ፖሊሲም ሆነ ወጥ የህግ ማዕቀፍ በሀገሪቱ አለመኖሩን ፌደራል የህግ እና ፍትህ ኢንስቲትዩት ያካሄደው ጥናት አመለከተ።
ጥናቱ "የህግ አወጣጥ ስርዓት መረጋጋት በኢትዮጵያ" በሚል ርዕስ የተካሄደ ሲሆን፣ ዓላማውም በሀገሪቱ ያለውን የፖሊሲና የህግ ማዕቀፍ እንዲሁም የአተገባበር ስርዓት ከረጅምና ከአጭር ጊዜ እቅዶች እንዲሁም ከቦትስዋና፣ ከጋናና ከደቡብ አፍሪካ ተሞክሮዎች አንጻር በመመርመር የመፍትሄ ሀሳብ ማቅረብ ነው።
ህግ የማህበረሰብንና የመንግስትን መስተጋብር የሚመራ መሳሪያ እንደመሆኑ ተለዋዋጭነት ባህሪው ቢሆንም፣ የሚወጡ ህጎች ጥራት፣ ግልጽነት፣ ወጥነት፣ ተገማችነትና ቀጣይነት ሊኖራቸው እንደሚገባ ጥናቱ ያስቀምጣል።
ከ2010 ዓ.ም ወዲህ የተካሄደው የመንግስት ለውጥ ተከትሎ በርካታ ህጎች የመውጣታቸውን ያህል፣ በችኮላና በጥድፊያ የሚወጡ ህጎች የህግ አወጣጥ ስርዓቱ የተረጋጋ እንዳይሆን፣ በህዝብና በባለሙያዎች ያልተመከረበት እንዲሆን እንዳደረጉት ጥናቱ ጠቁሟል።
ይህም ባለሀብቶች የረጅም ጊዜ የኢንቨስትመንት ውሳኔ እንዳይወስኑ፣ ዜጎችም ስለ መብትና ግዴታቸው ያላቸው ግንዛቤ አናሳ እንዲሆን አስተዋጽኦ እንዳደረገ ተመላክቷል።
ጥናቱ ከ2010 እስከ 2018 ዓ.ም በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የወጡ አዋጆችን ሙሉ በሙሉ መመርመሩን ገልጿል።
ከሌሎች ሀገራት ተሞክሮ በመነሳት፣ የህግ አወጣጥ ስርዓት መረጋጋት በስድስት ተያያዥ ተቋማዊ ምሶሶዎች ላይ የተመሰረተ መሆኑን የለየው ጥናቱ እነሱም የህገ መንግስት የበላይነት በተግባር መረጋገጥ፣ ውጤታማ የስልጣን ክፍፍልና ሚዛን፣ ጠንካራ የፓርላማ ኮሚቴ ስርዓት፣ በሙያ የታገዘ የረቂቅ ዝግጅት ተቋም፣ ትርጉም ያለው የህዝብ ተሳትፎ፣ እና ገለልተኛ የዳኝነት ቁጥጥር ናቸው።
ኢትዮጵያን በተመለከተ ግን ሀገሪቱ የህግ አወጣጥ ስርዓት መረጋጋትን የተመለከተ ፖሊሲ እንደሌላት፤ ጠቅላላ የህግ አወጣጥ ስርዓትን የሚመራ ፖሊሲም እንደሌለ፤ የሚወጡ ህጎችም በአብዛኛው በጸደቁ ፖሊሲዎች ላይ ከመመስረት ይልቅ የአስፈጻሚውን ጊዜያዊ ፍላጎት የሚያንጸባርቁ ሆነው መገኘታቸውን ለይቷል።
በህግ ማዕቀፍ ረገድም ኢፌዲሪ ህገ መንግስት፣ ደንብ ቁጥር 6/2008፣ አዋጅ ቁጥር 1263/2014 እና ሌሎች ሰነዶች ቢኖሩም፣ ከማርቀቅ እስከ አፈጻጸምና ክትትል ድረስ ያለውን ሂደት በአንድ ወጥነት የሚገዛ ማዕቀፍ አለመኖሩ ተጠቁሟል፤ ያለው አሰራርም በተበታተኑና በተበጣጠሱ መመሪያዎች ላይ የተመሰረተ ነው።
በአተገባበር ደረጃም ከተለዩ ክፍተቶችም ውስጥ :-
- ተደጋጋሚ የአዋጅ ማሻሻያዎች (ለምሳሌ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎትና የኤክሳይዝ ታክስ አዋጆች በወጡ በአመታቸው ማሻሻያ የተደረገባቸው መሆኑ) ፣
- ሰፊ የአዋጅ መሻሮች (ለምሳሌ አዋጅ ቁጥር 1263/2014 ብቻውን 18 አዋጆችንና 35 ደንቦችን መሻሩ)፣
- ተደራሽ ያልሆኑ መመሪያዎች ፣
- ተቃራኒ ይዘት ያላቸው አዋጆች መውጣት፣
- ከበላይ ህጎችና ከህገ መንግስቱ ጋር የሚጋጩ ድንጋጌዎች መኖር (በህገ ወጥ መንገድ የተገኘ ገንዘብ ህጋዊ ማስመሰልን በተመለከተ የሰብዓዊ መብት ጥሰት የያዘ ድንጋጌ በመሆኑ ማክሰኞ ወጥቶ በሳምንቱ ማክሰኞ ማሻሻያ የተደረገበት ሂደት መኖሩ)
- የበታች ህጎች ያለ ተገቢ ግምገማ መውጣት ( በተለይ ታክስ አካባቢ ይሄ ችግር በአደገኛ ሁኔታ መስተዋሉ)
- አዋጆች በተግባር ያለመፈጸም ይገኙበታል።
ከጥንካሬ አኳያም የተለያዩ ግኝቶችን ያስቀመጠው ጥናቱ ባለ ሶስት ደረጃ የምርመራና የንባብ ሂደት፣ የፍትህ ሚኒስቴር ማጣራት ሚና፣ የህግ ማዕከልና አማካሪዎች መኖር፣ እንዲሁም በቅርቡ የተቋቋመው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የህግ ማሻሻያና ቁጥጥር መሪ ስራ አስፈጻሚ እንደ አዎንታዊ እርምጃዎች ተጠቅሰዋል።
በሌላ በኩል የባለሙያ እጥረት፣ የተቋማት አለመናበብ፣ የአመራር ትኩረት ማነስ እና ወጥ የህግ ይረቀቅልኝ ስርዓት አለመኖር እንደ ዋና ዋና ድክመቶች ተለይተዋል።
ጥናቱ ከጋና፣ ከደቡብ አፍሪካና ከቦትስዋና ተሞክሮ በመነሳት ፦
° ፍርድ ቤቶች ግልጽ የህገ መንግስት ተጣጣሚነት የመተርጎም ስልጣን እንዲኖራቸው ማድረግ፣
° የፓርላማ ኮሚቴ ስርዓትን ማጠናከር፣
° ሙያዊ የረቂቅ ዝግጅት አቅምን ማጎልበት፣
° የህዝብና የባህል እንዲሁም የሃይማኖት ተወካዮች ተሳትፎን ተቋማዊ ማድረግ፣
° ህግ ማውጣትን ከፖለቲካ ፍጥጫ ነጻ ማድረግ፣
° የተጠቃለለ ፖሊሲና ሁሉን አቀፍ ህግ ማዘጋጀት፣
° ገለልተኛ የህግ ኮሚሽን ማቋቋም፣
° በዩኒቨርሲቲዎች የሌጂስሌቲቭ ድራፍቲንግ ስልጠናና ካሪኩለም ማዘጋጀት፣
° የህግ አወጣጥ ሉዓላዊነትን ከውጭ ተጽእኖ መጠበቅ፣ እንዲሁም የበታች ህጎችን ከአዋጅ ጋር ተጣጥመው መውጣታቸውን የሚከታተል ስርዓት መዘርጋት የሚሉ ምክረሃሳቦችን አቅርቧል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
ነሐሴ 3 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia | 5 466 |
| 17 | ስለ ነጻ የጥብቅና አገልግሎት ክፍለ ከተማ ምርጫ ማሳወቂያ
ውድ የማህበራችን አባላት፣
ከፍትህ ሚኒስቴር ለማህበሩ በተላከ ደብዳቤ (ቁጥር 409-28/0521/19፣ ሐምሌ 29 ቀን 2018 ዓ.ም.) የተላለፈውን መረጃ ለአባላት እናደርሳለን።
የፍትህ ሚኒስቴር ነጻ የህግ ድጋፍ ለሚሹ የህብረተሰብ ክፍሎች ጠበቃ የመመደብ ስልጣን በህግ የተሰጠው ሲሆን፣ እስካሁን ጉዳዮች ለጠበቆች ሲመደቡ የሚደረገው በተመዘገበው አድራሻ መሰረት ነው። ይህ አሰራር በጠበቆች ዘንድ ቅሬታ ሲያስነሳ የቆየ ከመሆኑም በላይ፣ ነጻ የህግ ድጋፍ ተጠቃሚዎች ላይም አላስፈላጊ መጓተት እያስከተለ ይገኛል።
በመሆኑም ጠበቆች ነጻ የጥብቅና አገልግሎት መስጠት የሚፈልጉበትን ክፍለ ከተማ (Subcity) አስቀድመው መርጠው እንዲያስመዘግቡ ሚኒስቴሩ ጠይቋል።
የክፍለ ከተማ ምርጫ ምዝገባ ሊንክ፦
https://docs.google.com/forms/d/e/1FAIpQLSfKR2tHgvj8AaD5o0nwUjYw9XbkFZcrQDd96OavsujXUx0rRA/viewform
የጊዜ ገደብ
የክፍለ ከተማ ምርጫውን ከደብዳቤው ቀን (ሐምሌ 29/2018 ዓ.ም.) ጀምሮ በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ ማጠናቀቅ ያስፈልጋል።
እባክዎ ልብ ይበሉ
በተጠቀሰው ጊዜ ውስጥ ምርጫቸውን ያላስመዘገቡ ጠበቆች፣ ወደፊት ለነጻ የጥብቅና አገልግሎት በሚመደቡበት ክፍለ ከተማ ላይ የሚያነሱትን ቅሬታ ሚኒስቴሩ እንደማይቀበል በግልጽ አስታውቋል።
ማህበሩ ይህንን አስፈላጊ የጊዜ ገደብ ግምት ውስጥ በማስገባት፣ አባላት በተቻለ ፍጥነት ምዝገባቸውን እንዲያከናውኑ በአጽንኦት ያሳስባል።
የኢትዮጵያ ፌዴራል ጠበቆች ማህበር
ሐምሌ 30 ቀን 2018 ዓ.ም. | 4 408 |
| 18 | ስለ ነጻ የጥብቅና አገልግሎት ክፍለ ከተማ ምርጫ ማሳወቂያ
ውድ የማህበራችን አባላት፣
ከፍትህ ሚኒስቴር ለማህበሩ በተላከ ደብዳቤ (ቁጥር 409-28/0521/19፣ ሐምሌ 29 ቀን 2018 ዓ.ም.) የተላለፈውን መረጃ ለአባላት እናደርሳለን።
የፍትህ ሚኒስቴር ነጻ የህግ ድጋፍ ለሚሹ የህብረተሰብ ክፍሎች ጠበቃ የመመደብ ስልጣን በህግ የተሰጠው ሲሆን፣ እስካሁን ጉዳዮች ለጠበቆች ሲመደቡ የሚደረገው በተመዘገበው አድራሻ መሰረት ነው። ይህ አሰራር በጠበቆች ዘንድ ቅሬታ ሲያስነሳ የቆየ ከመሆኑም በላይ፣ ነጻ የህግ ድጋፍ ተጠቃሚዎች ላይም አላስፈላጊ መጓተት እያስከተለ ይገኛል።
በመሆኑም ጠበቆች ነጻ የጥብቅና አገልግሎት መስጠት የሚፈልጉበትን ክፍለ ከተማ (Subcity) አስቀድመው መርጠው እንዲያስመዘግቡ ሚኒስቴሩ ጠይቋል።
የክፍለ ከተማ ምርጫ ምዝገባ ሊንክ፦
https://docs.google.com/forms/d/e/1FAIpQLSfKR2tHgvj8AaD5o0nwUjYw9XbkFZcrQDd96OavsujXUx0rRA/viewform
የጊዜ ገደብ
የክፍለ ከተማ ምርጫውን ከደብዳቤው ቀን (ሐምሌ 29/2018 ዓ.ም.) ጀምሮ በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ ማጠናቀቅ ያስፈልጋል።
እባክዎ ልብ ይበሉ
በተጠቀሰው ጊዜ ውስጥ ምርጫቸውን ያላስመዘገቡ ጠበቆች፣ ወደፊት ለነጻ የጥብቅና አገልግሎት በሚመደቡበት ክፍለ ከተማ ላይ የሚያነሱትን ቅሬታ ሚኒስቴሩ እንደማይቀበል በግልጽ አስታውቋል።
ማህበሩ ይህንን አስፈላጊ የጊዜ ገደብ ግምት ውስጥ በማስገባት፣ አባላት በተቻለ ፍጥነት ምዝገባቸውን እንዲያከናውኑ በአጽንኦት ያሳስባል።
የኢትዮጵያ ፌዴራል ጠበቆች ማህበር
ሐምሌ 30 ቀን 2018 ዓ.ም. | 3 |
| 19 | በኢትዮጵያ የወንጀል ፍትህ ሥርዓት ውስጥ ወንጀል ፈጽመው የታረሙ ግለሰቦች በድጋሚ ወደ ወንጀል ድርጊት የመመለሳቸው ሁኔታ አሳሳቢ ደረጃ ላይ እንደሚገኝ ጥናት አመልክቷል።
👉 በጥናቱ ከተካተቱና ወንጀል ፈጽመው ታርመው ከወጡት ታራሚዎች ውስጥ 94 በመቶዎቹ ከ5 አመት ባነሰ ጊዜ ውስጥ በሌላ ወንጀል በድጋሚ ወደማረሚያ ቤት የተመለሱ ናቸው።
በኢትዮጵያ የወንጀል ፍትህ ሥርዓት ውስጥ ወንጀል ፈጽመው የታረሙ ግለሰቦች በድጋሚ ወደ ወንጀል ድርጊት የመመለሳቸው ሁኔታ አሳሳቢ ደረጃ ላይ እንደሚገኝና ይህንን ለመግታት የተቀናጀ የመረጃ አያያዝና የህግ ማዕቀፍ እንደሚያስፈልግ የኢትዮጵያ የህግ እና ፍትህ ኢንስቲትዩት ያከናወነው ጥናት አመልክቷል።
ኢንስቲትዩቱ አመታዊ የጥናትና ምርምር ማጽደቂያ መርሃ ግብሩን ያከናወነ ሲሆን በመድረኩ "የወንጀል ደጋጋሚነት እና የማረሚያ ቤት ሚና በኢትዮጵያ፣ የሕግ ማዕቀፍ እና አተገባበር ስርዓት" የተሰኘ ጥናቱን ይፋ አድርጓል።
በፌደራል ማረሚያ ቤቶች ላይ ትኩረቱን አድርጎ የቀረበው ይህ ጥናት፣ ወንጀለኞች ታርመውና ታንጸው ሰላማዊ ዜጋ እንዲሆኑ ከማድረግ አንጻር አሁንም ሰፊ ክፍተቶች መኖራቸውን አመልክቷል።
ቀደም ሲል በተፈጸመ ወንጀል፣ ቅጣት በተሰጠ ወይም በይቅርታ ቀሪ እንዲሆን በተደረገ በአምስት አመት ጊዜ ውስጥ ስድስት ወር የሚያስቀጣ አዲስ ወንጀል ሰርቶ መገኘት የወንጀል ደጋጋሚነት የሚባል ሲሆን በወንጀል ፍትህ ስርዓት ውስጥ ማረሚያ ቤቶች ታራሚዎችን እያረሙ ስለመሆን ወይም አለመሆናቸው የሚለይበት ዋናኛ መለኪያ ነው።
ይሁን እንጂ በጥናቱ ከተካተቱት 127 የወንጀል ድጋሚ ፈጻሚዎች መካከል ከአምስት ዓመት ቆይታ በኋላ በወንጀል ድርጊት የተገኙት 5.6 በመቶዎቹ ብቻ ሲሆኑ ቀሪዎቹ ማለትም 94.4 በመቶ የሚሆኑት ከአምስት ዓመት በታች በሆነ ጊዜ ወደ ማረሚያ ቤት ተመልሰዋል ይህም የፌደራል ማረሚያ ቤቶች ታራሚዎችን የማረም ሂደት ላይ ውጤታማነት እንደማይታይበት አመላካች ሆኗል።
የጥናቱ ውጤት በዝርዝር ሲታይ 57.9 በመቶ የሚሆኑት ለሁለተኛ ጊዜ ወደ ማረሚያ ቤት የተመለሱ ሲሆኑ፣ 31 በመቶዎቹ ደግሞ ለሦስተኛ ጊዜ የተፈረደባቸው ናቸው።
ከእስር ከተፈቱ በኋላ ወደ ወንጀል ለመመለስ የሚወስድባቸውን ጊዜ በተመለከተ፣ 36.5 በመቶ የሚሆኑት ከ2 እስከ 5 ዓመት ባለው ጊዜ ውስጥ ሲመለሱ፣ 23 በመቶ የሚሆኑት ደግሞ ከ6 ወር እስከ 1 ዓመት ባለው አጭር ጊዜ ውስጥ በድጋሚ ወንጀል ፈጽመው ይገኛሉ።
17.5 በመቶ የሚሆኑት ደግሞ ከ6 ወር በታች በሆነ ጊዜ ወደ ወንጀል መመለሳቸውን ውጤቱ ያሳያል።
በተጨማሪም፣ ታራሚዎቹ ቀደም ሲል ተከሰው ከተቀጡበት ወንጀል (52 በመቶ ዝርፊያ/ስርቆት) ጀምሮ፣ በአሁኑ ጊዜ ተይዘው ወደ ማረሚያ ቤት እንዲገቡ ካደረጋቸው አዲስ ወንጀል (53.6 በመቶ ዝርፊያ/ስርቆት) ድረስ ተመሳሳይ የወንጀል ዓይነት ደጋግመው መፈጸማቸው በጥናቱ ተመዝግቧል።
የተቀሩት አደንዛዥ ዕፅ መጠቀም እና ማዘዋወር ፣ውንብድና ፣ የግብር ስወራና ማጭበርበር ፣ ህገወጥ የሰዎች ዝውውር ፣የሙስና ወንጀሎች እና ሌሌችም ወንጀሎች ይገኙበታል።
በጥናቱ በድጋሚ ወንጀል እንዲፈጽሙ ካደረጓቸው ምክንያቶች መካከል 13.4 በመቶ የሚሆኑት ስራ ባለማግኘታቸው ምክንያት ተመልሰው ወንጀል ውስጥ መገኘታቸውን ተናግረዋል።
ገንዘብ ለማግኘት አለመቻል እንዲሁም ከማረሚያ ቤት ከወጡ በኋላ ክትትልና ድጋፍ አለመኖርም ተመልሰው በወንጀል ውስጥ እንዲገኙ ማድረጉን የጥናቱ ውጤት ያመለክታል።
በተጨማሪም ከእስር የወጡ ግለሰቦች በማህበረሰቡና በቤተሰቦቻቸው ዘንድ ተቀባይነት ማጣታቸው፣ በማረሚያ ቤቶች ውስጥ በቂ የሙያና የስነ-ልቦና ስልጠና አለመስጠት እንዲሁም በእስር ላይ እያሉ አዳዲስ የወንጀል ስልቶችን መማር በድጋሚ ወንጀል እንዲሰሩ እንዳደረጋቸው ገልጸዋል።
ሌላው በጥናቱ የተጠቀሰው የፌደራል ማረሚያ ቤቶች ወንጀለኞችን በዘመናዊ መንገድ ለመለየት የሚያስችል ወጥና የተደራጀ የዲጂታል መረጃ አያያዝ (Database) ስርዓት አለመኖሩ ሲሆን በተለይም በአዲስ አበባ የፖሊስ ደረጃ የጣት አሻራ ምርመራ በሁሉም ተጠርጣሪዎች ላይ የማይደረግ በመሆኑ፣ ድጋሚ ወንጀል ፈጻሚዎችን ማንነት እና እንደሃገር ያለውን የወንጀል ደጋጋሚነት ምጣኔ በትክክል ለመለየት አስቸጋሪ አድርጎታል ተብሏል።
ጥናቱ ይህንን የፍትህ ስርዓቱን ክፍተት ለማረም የወንጀል ደጋጋሚዎች ከሌሎች ታራሚዎች ተነጥለው ለብቻ የሚያዙበት ራሱን የቻለ የተለየ የተሃድሶ ፕሮግራሞች እንዲኖሩ እንዲሁም የእርምት ጊዜያቸውን ጨርሰው ከማረሚያ ቤት የሚወጡ ታራሚዎች ወደ ማህበረሰቡ መልሶ መቀላቀልን በተመለከተ የተዘጋጀው ረቂቅ ህግ በአጭር ጊዜ ውስጥ እንዲጸድቅና ተግባራዊ እንዲሆን ምክረሃሳብ አቅርቧል።
በመድረኩ የተገኙት የፍትህ ሚኒስቴር ተወካይ ጥናቱ የወሰዳቸው የናሙናዎች መጠን (Sample size) አነስተኛ መሆኑን የተናገሩ ሲሆን በምክረ ሃሳብ ደረጃ ለተነሱት ሃሳቦች ግን ረቂቁ ተጠናቅቆ ለሚኒስትሮች ምክር ቤት መላኩን እና በቅርቡ ይጸድቃል ተብሎ እንደሚጠበቅ አመልክተዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
ነሐሴ 2 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia | 4 142 |
| 20 | መንግሥት 7 የክሪፕቶ ካረንሲ መተግበሪያዎች በሀገር ውስጥ እንዳይሠሩ ሙሉ በሙሉ መታገዳቸውን ዛሬ በይፋ አሳውቋል።
መተግበሪያዎቹ ለሕገወጥ የገንዘብ ዝውውር ሽፋን ይሰጡ እንደነበር አመልክቷል።
ከዚህ ቀደም የተለያዩ የክሪፕቶ ከረንሲ መተገበሪያዎች የኢትዮጵያን ብር ከP2P መድረክ ላይ ማስወጣታቸው የሚዘነጋ አይደለም።
ይህ በእንዲህ እንዳለ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል (EEP) ተገቢው መመሪያ በሌለበት ሁኔታ ከ36 የዳታ ማይኒንግ ድርጅቶች ጋር ሕገ-ወጥ የኃይል ሽያጭ ውል የፈጸሙ 4 ከፍተኛ አመራሮች ላይ እርምጃ መወሰዱን አመልክቷል።
በሌላ በኩል፤ በሕገ-ወጥ የገንዘብ ዝውውር፣ በሐዋላ እና በጥቁር ገበያ ተሳታፊ የሆኑ 169 ኢትዮጵያውያንና የውጭ ሀገር ዜጎች በሕግ ተጠያቂ እንዲሆኑ መደረጉን አሳውቋል።
በተጨማሪ በተደራጀ መንገድ ከንግድ ባንክ ደንበኞች አካውንት ላይ በማጭበርበር ገንዘብ የወሰዱ 36 ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ውለው የባንክ ሒሳባቸው እንዲታገድ ተደርጓልም ብሏል።
Source: Tikvah Ethiopia
@Ethiopianbusinessdaily | 4 927 |
